Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convert to Pdf
  • Reading List
  • Summary
  • Audiobook
  • Search
  • Upload
  • myzon
  • Log in
  • Register
English  አማርኛ  Français  العربية
Book of the day

የአማርኛ_እና_የጋሞኛ_የቋንቋ_ቅየራ_ትንተናደብረ_ብርሀን_ዩኒቨርሲቲ.pdf


  • word cloud

የአማርኛ_እና_የጋሞኛ_የቋንቋ_ቅየራ_ትንተናደብረ_ብርሀን_ዩኒቨርሲቲ.pdf
  • Extraction Summary

ምዕራፍ አንድ መግቢያ ይህ ጥናት በመማርያ ክፍል ውስጥ ተሳትፎ እንደሚያሳድግ ገልጸዋል ስድስተኛው ጥያቄ ደግሞ የቋንቋ ቅየራ ተማሪዎች እንዲመልሱ ለማበረታታት ያስችላል በሚል ከመምህራን የተሰጠው ምላሽ በምልከታም መረጋገጡን የመረጃው ትንተና ያሳያል ሌላው የአፍመፍቻ ቋንቋን እየቀየሩ ማስተማር በሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት ውስጥ የሚኖረው ጠቀሜታ በክፍል አስተዳደርና በተማሪዎች መነሳሳት ላይ የሚኖረው ሚና ነው ቀጣዩ ምሳሌ ለዚህ ማሳያ ሊሆን ይችላል ተብሎ በምልከታ ከተገኘው መረጃ የተወሰደ ነው ቀሩ መምህር የቤት ስራ የማይሰራ ተማሪ ተማሪ ነውገ ተማሪ ለመምህርቷም ሆነ ለጓደኛው ምንም ምላሽ አልሰጠም ተማሪ ።

  • Cosine Similarity

በመሆኑም የቋንቋ ቅየራ ጥናት በማህበራዊ ስነልሳን ሰፊ ቦታ ይዞ ይገኛል በዚህ ርዕሰጉዳይ ላይ የሚሰሩት ጥናቶች እንደየአጥሂዎቹ ፍላጎትና ቋንቋዎቹ እንደሚጠኑበት አውድ ይለያያሉሌ በሀገራችን ከሰማንያ በላይ ቋንቋዎች ዘህሀዐከ ፀ ይነገራሉጉ ቋንቋዎቹ በትምህርት ስርዓቱና በአስተዳደር ውስጥ የተለያየ ሚና አላቸው በተለይ የአማርኛ ቋንቋ ኢአፈፈት ክልሎች ውስጥ ያሉ ተማሪዎች አማርኛን በሁለተኛ ቋንቋነት ሲማሩ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ቅየራ ሚና ምን እንደሆነ ማጥናት እንዲሁም ስለቋንቋ ቅየራ መምህራን ያላቸውን አመለካከት ማጥናት ስልቱን በቋንቋ ማስተማር ውስጥ እንዴት መጠቀም እንደሚቻል አቅጣጫ ለመጠቆም ይረዳል ይህ ጥናት የሚካሄደው በመማርያ ክፍል ውስጥ በሚደረግ የቋንቋ ቅየራ ላይ ነው በደቡብ ብሔር ብሔረሰብ ክልል ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው የተለያየ ሲሆን አማርኛን ከ ኛ ክፍል ጀምረው በሁለተኛ ቋንቋነት ይማሩታል ስለሆነም በአማርኛ መማርያ ክፍላቸው ውስጥ የቋንቋ ቅየራ የሚጠበቅ የሂደቱ አካል ነው የዚህ ጥናት አጥሂም በክልሉ ከሚገኙ ማህበረሰቦች ውስጥ የጋሞኛ አፈፈት የኛ ክፍል ተማሪዎች በአማርኛ ትምህርት ወቅት የሚፈጽሙትን የቋንቋ ቅየራ ሁኔታና ምክንያቶቹን የተማሪዎቹ የቋንቋ ቅየራ በመማርያ ክፍል ውስጥ ያለውን አገልግሎት እንዲሁም መምህራን ስለቋንቋ ቅየራ ያላቸውን አመለካከት ይተነትናል የጥናቱ ችግር ምንነት ከላይ እንደተገለፀው እኤአ ከ በኋላ የቋንቋ ቅየራ በዓለም ዓቀፍ የማኅበራዊ ስነልሳን ጥናት ዘርፍ ትኩረት እያገኘ በመምጣቱ በርካታ የቋንቋ ምሁራን ርዕሰ ጉዳዩን ለማብራራት መፃህፍት ጽፈዋል በጉዳዩ ላይም በርካታ ጥናቶችን አድርገዋል በተለይ ከእንግሊዝኛ ቋንቋ መማር ጋር ተያያዥነት ያላቸው የቋንቋ ቅየራ ጥናቶች በብዛት ይገኛሉ በበርካታ የዓለማችን ልሳነ ክልኤ ሀገራት አንደበተ ርቱዓንን ጨምሮ በአንድ ምልልስ ውስጥ የቋንቋ ቅየራ ይጠቀማሉ ቅየራውም ከሁለት ቋንቋዎች የተወሰዱ ቃላትን መጠቀም ሊሆን ይችላል ክፎ ዐቪበ ፀ ሀገራችን ኢትዮጵያም በርከት ያሉ ቋንቋዎች የሚናገሩ የተለያዩ ህዝቦች ካሉባቸው የዓለማችን ሀገራት አንዷ ስትሆን ከ የሚደርሱ ቋንቋዎች እንደሚነገሩባት ይገለጻል ሀበ ፀ እነዚህ የተለያየ ቋንቋ ተናጋሪ ማህበረሰቦች በአካባቢያዊ መቀራረብም ሆነ በሌሎች ማህበራዊ ግንኙነቶች በሚፈጥሯቸው መስተጋብሮች ቋንቋቸው ንክኪ ይፈጥራል ከዚህም በተጨማሪ በሀገሪቱ ያሉ ቋንቋዎች በመደበኛው የስራና የትምህርት መስክ የተለያየ ሚና አገልገሎት ስላላቸው ግንኙነቱ አይቀሬ ነው ይህ ጥናት በዚህ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ግንኙነት አንድ ገጽታ ላይ የሚሰራ ሲሆን ትኩረቱም የብዙ ቋንቋዎች መገኛ በሆነው በደቡብ ክልል ነው በክልሉ ከ በላይ የአፍ መፍቻ ቋንቋዎች ሲገኙ ህህዐበ ፀ የክልሉ የስራ ቋንቋ አማርኛ ነው በትምህርት ቤትም ተማሪዎቹ በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው አስከ አራተኛ ክፍል ከተማሩ በኋላ እንግሊዝኛ የማስተማሪያነት ሚናውን ሲረከብ የአፍ መፍቻቸው ግን በአንድ የትምህርት ዓይነትነት መሰጠቱን እስከ አስረኛ ክፍል ድረስ ይቀጥላል አማርኛ ደግሞ ከኛ ክፍል ጀምሮ እስከ ኛ ክፍል ድረስ እንደሁለተኛ ቋንቋ ይሰጣል በመሆኑም በተማሪዎቹ አፍ መፍቻና በሁለተኛ ቋንቋቸው አማርኛ መካከል ግንኙነት ይፈጠራል ወላይታ ከክልሉ ዞኖች አንዱ ሲሆን እስከ ዓም ድረስ በዞኑ ውስጥ በአራት ተቀራራቢ የቋንቋ መልኮች ለሚግባቡ ጎሳዎች ወላይታ ጋሞ ጎፋና ዳውሮ ወጋጎዳ በሚል የተሰየመ በጋራ አፍ መፍቻ ቋንቋ መልክ ተዘጋጅቶ ትምህርት በመሰጠት ላይ ቆይቷል ነገር ግን ከ ወዲህ አራቱም ጎሳዎች በወረዳ ተዋቅረው እያንዳንዱ ወረዳ የየራሱን ቋንቋ በአፍመፍቻነት በመጠቀም ትምህርቱ እየተሰጠ ይገኛል የምርምሩ ዋነኛ ጉዳይም ከእነዚህ አራት የዞኑ ወረዳዎች ውስጥ አንዱ በሆነው የጨንቻ ወረዳ በሚነገረው ጋሞኛ ቋንቋ አፈፈት ተማሪዎች በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ወቅት የሚፈጠሩትን የቋንቋ ቅየራ ሁኔታ ጠቀሜታና ስለቅየራው መምህራን ያላቸውን አመለካከት በመዳሰስ ትንታኔ መስጠት ነው የጥናቱ አነሳሽ ምክንያት የዚህ ጥናት አነሳሸ ምክንያት የአጥሂው የስራ ላይ ገጠመኝ ነው ይኸውም አጥሂው በአዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ ሽሮ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚያስተምርበት ወቅት አፋቸውን በጋሞኛ የፈቱና በክልላቸው ትምህርታቸውን ጀምረው በማቋረጥ በተለይ አምስተኛና ሰባተኛ ክፍል ላይ ወደ አዲስ አበባ መጥተው የሚማሩ በርካታ ተማሪዎች አጋጥመውታል ተማሪዎቹም አዲስ አበባ መጥተው መማር ሲጀምሩ በአማርኛ ቋንቋ መግባባት ያለመቻል ችግሮች ይገጥሟቸዋል እነዚህ ተማሪዎች በክፍል ውስጥም ሆነ ከክፍል ውጪ በሚኖራቸው መስተጋብር ሳቢያ መሻሻልን የሚያመጡ ቢሆንም ይህ መሻሻል እስኪመጣ ግን በክፍል ውስጥ አልፎ አልፎ ከሚታይ በስተቀር የጋሞኛ ቋንቋን ጣልቃ በማስገባት ለመሳተፍ ከመሞከር ይልቅ ዝምታን እንደሚመርጡ አጥፒው መገንዘብ ችሏል ይህ ዝምታን የመምረጥ ሁኔታ ከገቡበት አውድ መነሻነት ከአማርኛ አፈፈቶች ጋር ስለሚቀላቀሉ ሊሆን ይችል ይሆን። የጥናቱ ዓላማዎች የዚህ ጥናት አጠቃላይ ዓላማ በደቡብ ክልል የሚገኙ የጋሞኛ አፈፈት ተማሪዎች አማርኛን በሚማሩበት ክፍል ውስጥ የአማርኛና የጋሞኛ ቋንቋ ቅየራ ሁኔታ የክፍል ውስጥ አገልግሎቱንና ስለስልቱ መምህራን ያላቸውን አመለካከት መተንተን ነው ከዚህ በታች ደግሞ የጥናቱ ዝርዝር ዓላማዎች ተዘርዝረዋል ሩ መምህራን ስለቋንቋ ቅየራ ያላቸውን አመለካከት መተንተን ሩ የጋሞኛ አፈፈት ተማሪዎች አማርኛን በሚማሩበት ወቅት የሚፈጠረውን የቋንቋ ቅየራ ሁኔታን መለየት እና ሩ የተማሪዎቹ የቋንቋ ቅየራ ለቋንቋ መማር ያለውን ጠቀሜታ መግለፅ የሚሉት ናቸው የጥናቱ ጠቀሜታ ይህ ጥናት በማኅበራዊ ስነልሳን ውስጥ ከሚካተቱ ርዕሰጉዳዮች አንዱ በሆነው የቋንቋ ቅየራ ላይ የተሰራ ነው በመሆኑም ጥናቱ ለቋንቋ ትምህርት ፖሊሲ አውጪዎችና ስርአተ ትምህርት አዘጋጆች ለቋንቋ መምህራን ጠቀሜታ ይሰጣል ዘርዘር ባለ መልኩ የጥናቱ ዋና ዋና የሚባሉ ጥቅሞች የሚከተሉት ናቸው ሀ አማርኛን እንደ ሁለተኛ ቋንቋ ለሚያስተምሩ ክልሎች የማስተማሪያ መጽሀፍትን ለሚያዘጋጁ አካላት የአፍ መፍቻ ቋንቋ በቋንቋ ትምህርቱ ውስጥ ሊኖረው የሚገባውን ስነዘዴያዊ ጠቀሜታ ይጠቁማል ለ ለክልሉና ለዞኑ የቋንቋ ትምህርት ባለሙያዎች በጋሞኛ አፈፈት የሆኑ ተማሪዎችን ለሚያስተምሩ መምህራን የጋሞኛ አፈፈት ተማሪዎች ታላሚውን ቋንቋ በሚማሩበት ወቅት የሚፈጥሩትን የቋንቋ ቅየራ ምክንያትና የቋንቋ ቅየራው ያለውን ስነትምህርታዊ ጠቀሜታ ይጠቁማል በመሆኑም ባለሙያዎቹ የቋንቋ መማርያ መጻህፍትን ሲያዘጋጁም ሆነ መምህራኑ አማርኛ ቋንቋን ሲያስተምሩ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ምን ሚና ሊኖረው እንደሚችልና እንደሚገባ ያስገነዝባል ተብሎ ይታሰባል ሐ በጋሞኛ አፈፈት የሆኑ ተማሪዎችን ለሚያስተምሩ መምህራን ተማሪዎቹ ታላሚሜውን ቋንቋ በሚማሩበት ወቅት የሚፈጠረውን የቋንቋ ቅየራ ተንትኖ በማሳየት የቋንቋ ማስተማሪያ ስልታቸውን እንዲያሻሽሉ ያደርጋል መ በቋንቋ ቅየራ ላይ ጥናት የሚያደርጉ አጥፒዎችን ያነሳሳል ለጥናታቸውም መነሻ ወይም መንደርደሪያም ይሆናቸዋል ተብሎ ይታመናል የጥናቱ ወሰን ጥናቱ የተከናወነው በደቡብ ብሄር ብሄረሰብ ክልል ወላይታ ዞን በጨንቻ ወረዳ አስተዳደር ጨንቻ የመጀመሪያ ደረጃ ኛና ኛ ሳይክል ትምህርት ቤት እና ቱቱሻ የመጀመሪያ ደረጃ ኛና ኛ ሳይክል ትምህርት ቤት በሚገኙ የአምስተኛ ክፍል የጋሞኛ አፈፈት ተማሪዎች ላይ ነው አማርኛ ቋንቋን ሶስተኛ ክፍል ላይ እንደ ሁለተኛ ቋንቋ መማር የጀመሩት እነዚህ ተማሪዎች በአማርኛ ቋንቋ መማርያ ክፍል ውስጥ የሚፈፅሙትን የቋንቋ ቅየራ መጠን ጠቀሜታ እና መምህራን ስለ ቋንቋ ቅየራ ያላቸውን አመለካከት በመተንተን ላይ የተወሰነ ነው በመምህራኑ ንግግር የሚከሰተው የቋንቋ ቅየራ የዚህ ጥናት ትኩረት አይደለም። ቓቃላትንና ትኩረት ሊሰጥባቸው የሚገቡ የቋንቋውን ይዘቶች መተርጎም ነው በተለይ ሂሳብ ሳይንስ የቴክኖሎጂ ቃላትና ይዘቶችን በማስተማር ወቅት ትምህርቱ ቀላልና ሳቢ እንዲሆን ያስችላል አጥፒው የቋንቋ ቅየራ አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳይኖረው ጥንቃቄ ሊደረግባቸው የሚገቡ ጉዳዮችን ገልጸዋል ለምሳሌ የቋንቋ ቅየራ እኩል በእኩል ባይደረግ አንድ ቃል ተናግሮ ወዲያው መተረጎም ጥሩ እንደሆነ ይመክራሉ ምክንያቱም ተማሪዎች ታላሚውን ቋንቋ ለመማር ጥረት ከማድረግ ይልቅ መምህሩ ይተረጉምልናል የሚሉ ጠባቂዎች እንዳይሆኑ ሌላው የቋንቋ ቅየራ በታችኛው የክፍል ደረጃ በብዛት ሊከሰት ቢችልም ተማሪዎቹ ከፍ እያሉ ሲሄዱ እየቀነሰ መሄድ ይገባዋል እንዲሁም መምህሩ የቋንቋ ቅየራ የሚጠቀመው የራሱን የቋንቋ ክፍተት ለመሙላት ከሆነ ሌላ የመማር ችግር ሊፈጠር ስለሚችል ይህ እንዳይሆን መምህሩ የሁለቱንም ቋንቋዎች ይዘት ማወቅና ክፍል ከመግባቱ አስቀድሞ የቋንቋ አጠቃቀሙን አስመልክቶ መዘጋጀት አለበት የእሀዐ ጥናት ምንም እንኳን በሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት ላይ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ሚና ምን እንደሆነ መተንተኑ ከዚህ ጥናት ጋር ቢያመሳስለውም የጥናቱ አካባቢ ቋንቋዎቹ እንዲሁም ይህ ጥናት የቋንቋ ቅየራ አሉታዊ ተጽዕኖ ላይ አለማተኮሩ የሚለያዩባቸው ነገሮች ናቸው ከዚህም በተጨማሪ የእሀዐ ጥናት በቋንቋም ሆነ በሌሎች የትምህርት ዓይነቶች ላይ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ምን ሚና እንዳለው ሲያጠና ይህ ጥናት ግን የቋንቋ ቅየራና በሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት ላይ ብቻ በሚኖረው ሚና ላይ የተወሰነ ነው መ ሽእ«ሀህዘ በ በሲሪሳንካ ኮሎምቦ ዩኒቨርሲቲ የተሰራው ይህ ጥናት ዓላማው እንግሊዝኛ በሁለተኛ ቋንቋነት በሚሰጥባቸው ትምህርት ቤቶች ውስጥ የተማሪዎቹ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ያለውን ሚና ተማሪዎች በሁለተኛ ቋንቋ ያላቸው ብቃት በቋንቋ ቅየራ ደረጃ ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ እንዲሁም መምህራን የቋንቋ ቅየራ ስለሚኖረው ስነትምህርታዊ ጠቀሜታ ያላቸውን አመለካከት ማሳየት ነው በውጤቱም የቋንቋ ቅየራ በሁለተኛ ቋንቋ መማርያ ክፍል ውስጥ አፍመፍቻን መቀላቀል ያሉት ጠቀሜታዎች በዋናነት በሶስት እንደሚከፈሉ ተለይቷል እነሱም « ማኅበራዊ መስተጋብራዊ ጠቀሜታፁ ይህም የቋንቋ ቅየራ ተማሪዎቹ መምህራኑን እንደ እንግሊዝኛ መምህር ብቻ ሳይሆን ተማሪዎቹን ሊያግዝ የመጣ ልሳነክልኤ አስተማሪና አማካሪ አድርገው እንዲቆጥሩት ያስችላል ስነትምህርታዊ ጠቀሜታ የቋንቋ ቅየራ ከባድ ጽንሰሀሳቦችን ለማብራራት ሁለተኛና አፍመፍቻ ቋንቋቸውን እያነጻጸሩ ለማስተማር ሰዋሰዋዊ ህጎችን ለማብራራት ከበድ ያሉ ቃላትን ፍቺ ለመስጠት አዳዲስ መረጃዎችንና ለተማሪዎቹ ባዕድ የሆኑ ባህሎችን ለማስተዋወቅ ይጠቅማል ለክፍል ቁጥጥር አስተዳደራዊእ ጠቀሜታ። ተማሪዎች መልስ እንዲሰጡና ግራ ያጋቧቸው የትምህርት ይዘቶች ካሉ እንዲጠይቁ ለማድረግ ሲሆን ይህ የቋንቋ ቅየራ ጠቀሜታ ተማሪዎች በታላሚው ቋንቋ እውቀታቸው እየጨመረ ሲሄድ ጠቀሜታው እንደሚቀንስ በውጤቱ ተረጋግጧል ምንም እንኳን የተወሰኑ መምህራን በሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት ውስጥ ለአፍ መፍቻ ቋንቋ ቅየራ አሉታዊ አመለካከት ቢኖራቸውም አብዛኛዎቹ መምህራን ግን በአዎንታዊ መልኩ እንደሚመለከቱት የዚህ ጥናት ውጤት ያሳያል ተማሪዎች በታላሚ ቋንቋ ያላቸው እውቀት እየጨመረ ሲመጣ የቋንቋ ቅየራ ስነትምህርታዊ ሜናው እየቀነሰ እንደሚመጣም በጥናቱ ተጠቁሟል ሌላው በዚህ ጥናት የተገኘው ውጤት መምህራን በተለይም ልሳነ ክልኤ የሆኑት ያለምንም ስነትምህርታዊና ተግባቦታዊ ጠቀሜታ የቋንቋ ቅየራ እንደሚያካሂዱ ነው በተጨማሪም በታላሚው ቋንቋ የተገለጸላቸውን ባለመረዳታቸው ተማሪዎች መምህሩ እንዲተረጉምላቸው የሚጠይቁበት አጋጣሚ በመኖሩ ለቋንቋ ቅየራ ተማሪዎቹም አነሳሽ እንደሆኑ አጥፒው ገልጸዋል ይህ የእ«ሀሀህሀጺ ጥናት ከሌሎቹ ጥናቶች በተለየ መልኩ ከዚህ ጥናት ጋር ይመሳሰላል ለምሳሌ ሁለቱም የአፍ መፍቻ ቋንቋ በሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት ላይ የሚኖረውን ሚና መምህራን ስለ ቋንቋ ቅየራ ያላቸውን አመለካከት እንዲሁም የቋንቋ ቅየራ ደረጃን መተንተናቸው የሚያመሳስላቸው ሲሆን የቋንቋዎቹና የአውዱ መለየት ይህ ጥናት ተማሪዎች ስለቋንቋ ቅየራ ያላቸውን አመለካከት ማካተቱ እንዲሁም የመምህራንን የቋንቋ ቅየራ አለመተንተኑ ከእህዕህህዉ ጥናት እንዲለይ ያደርገዋል ሠ ከ ልከአዉ ። ጋሪ ፈ ያቆ ቀዖራ ይ መሥሃራ ፆሆጎሃው መሰዳያታ ለመወሰን እስማማለሁ አልስማማም እቸገራለሁ የቋንቋ ቅየራ ላይ መምህራን ያላቸው ተቁ አመለካከት ኛ ኝ ሯ ኝ ሯ ጁ የቋንቋ ቅየራ የቋንቋ እድገትን ይገታል የሚል እምነት የለኝም የቋንቋ ቅየራ የደካማ ቋንቋ ችሎታ ማሳያ ነው ብዬ አላምንም የቋንቋ ቅየራ እየተጠቀሙ ማስተማርን አልቃወምም የቋንቋ ቅየራ በሚጠቀም ሰው ላይ የተለየ አሉታዊ ስሜት አይሰማኝም የቋንቋ ቅየራ የተማሪዎችን ተሳትፎ ይጨምራል ብዩ አምናለሁ የቋንቋ ቅየራ ተማሪዎች በራስ የመተማመን ስሜት እንዲኖራቸው ያደርጋል የሚል ዕምነት አለኝ የቋንቋ ቅየራ ተማሪዎች የትምህርቱን ይዘት እንዳይረዱ እንቅፋት ይሆናል ብዩ አላምንም የቋንቋ ቅየራ በኛ ቋንቋ ትምህርት ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ይኖረዋል ብዩ አምናለሁ በኛ ቋንቋ ክፍለጊዜ የቋንቋ ቅየራን ተጠቅሞ ማስተማር የትምህርቱን ሂደት ማገዝ ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖ አለው የሚል ዕምነት አለኝ ቋንቋ ቅየራ የቋንቋ እድገትን ይገታል የሚል እምነት የለኝም ለሚለው የመጀመሪያ ጥያቄ የኙ በመቶ መምህራን ምላሽ የቋንቋ ቅየራ የቋንቋ እድገትን ይገታል የሜል እምነት እንዳላቸው የሚየሳይ ነው ለዚህም እምነታቸው በምክንያትነት የሰጧቸው መልሶች ተከታዮቹ ናቸው። የቋንቋ ቅየራ ተማሪዎችን ያደነጋግራል በታላሚ ቋንቋ እየተማሩ አፍመፍቻቸውን መጠቀም ታላሚ ቋንቋውን በአግባቡ እንዳያሳድጉት ያደርጋል የቋንቋ ቅየራ ተማሪዎች ቋንቋውን ለመማር የሚያደርጉት ጥረት አናሳ ከማድረጉም ባሻገር በመምህሩ ትርጉም ላይ ጥገኛ ትርጉም ጠባቂ ያደርጋቸዋል ታላሚውን ቋንቋ እንዳይረዱት ያደርጋል ቅየራው ሙሉ መልዕክት እንዳይተላለፍ ሊያግድ ስለሚችል ታላሚ ትምህርታቸው ላይ ችግር ይፈጥራል ቋንቋ በመቀየር የሚያስተምር መምህር ከታላሚው ይልቅ ለአፍመፍቻቸው ትኩረት ስለሚያደርግ የታላሚው ቋንቋ ትምህርት ተጎጂ ይሆናል ከሙሉው የቋንቋ ዕውቀት ይልቅ የተወሰነ የቃላት ዕውቀት ብቻ እንዲኖራቸው ያደርጋል የሰዋሰው ችግር እንዲኖርባቸው ያደርጋል ተማሪዎቹ ለሁለቱም ቋንቋ ትኩረት የማይሰጡ ሊሆኑ ይችላሉ ከአንዱም ላይሆኑ ይችላሌ በአፍመፍቻቸውና በታላሚው ቋንቋ መሀከል ያለው ልዩነት ግራ ሊያጋባቸው ይችላል መደበላለቅ የቋንቋውን ጣዕም ያጠፋል ከመረጃው ማየት እንደሚቻለው መምህራኑ የቋንቋ ቅየራ የቋንቋ እድገትን ይገታል ብለው ያስባሉ ቅየራው በቋንቋ መማር ውስጥ ያስከትላቸዋል ብለው የሚያስቧቸውን እንቅፋቶችም የቋንቋ ቅየራ የቋንቋ እድገትን ይገታል ያሉባቸውን ምክንያቶች ዘርዝረዋል ምንም እንኳን አብዛኛው መምህራን የቋንቋ ቅየራ የቋንቋ እድገትን ይገታል የሚል ምላሽ ቢሰጡም ሌሎች ተዛማጅ ጥናቶች ግን ይህንን አይደግፉም እህከከ እጩ የቋንቋ መምህራን ስለቋንቋ ቅየራ ያላቸውን አመለካከት በተመለከተ ባጠኑት ጥናት ግኝት መሰረት አብዛኛዎቹ መላሾች የቋንቋ ቅየራ በታላሚ ቋንቋ የተሻለ ብቃት እንዲገኝ የሚያስችል እንደሆነ ገልጸዋል ር በተራ ቁጥር እና መምህራኑ በምክንያትነት የሰጧቸው ሀሳቦች በቋንቋ ቅየራ መሆናቸውን ጠቅሶ እነዚህ ችግሮች ለምን ወቅት ሊፈጠሩ የሚችሉ ችግሮች እንደሚፈጠሩና እንዴት መቆጣጠር እንደሚቻል ደግሞ ከሀ በጥናቱ እንደሚከተለው ገልዷል ተማሪዎቹ በትምህርቱ መነሻ ላይ የቋንቋ ቅየራ መጠቀማቸው እንዲፈሩ ያደርጋቸዋል በሁለተኛ ቋንቋ የመግባባት ችሎታቸውን ከመቀነሱም ባሻገር በቋንቋ ቅየራ ላይ አሉታዊ አመለካከት እንዲኖራቸው ሊያደርግ ይችላል ስለሆነም መምህሩ ቀድሞ ምሳሌ በመስጠት ተማሪዎቹ የቋንቋ ቅየራን መልኩ እንዲገነዘቡት ማስቻል አለበት ሀ « በአዎንታዊ የቋንቋ ቅየራ የቋንቋ እድገትን ይገታል ማለት እነዚህ ችግሮች መኖራቸው አለመሆኑንም ያስረዳል የቋንቋ ቅየራ የደካማ ቋንቋ ችሎታ ማሳያ ነው ብዬ አላምንም ለሚለው ሁለተኛ መምህራን የቋንቋ ቅየራ የደካማ ይህም ለምሳሌ ጥያቄ ምላሻቸውን ከሰጡት ውስጥ በመቶ ቋንቋ ችሎታ ማሳያ ነው ብለው አለማመናቸውን መረጃው ይገልጻል በተመሳሳይ ርዕስ ካጠኑ ሃ ሃ ርከቨፀበ ን ጠቅሰው ምሁራን ጋር ተመሳሳይ ውጤት አሳይቷል የቋንቋ ቅየራ ልምድ በራሱ የቋንቋ ድክመትን አያሳይም ከዚያ ይልቅ በንግግር ውስጥ ተግባቦት ከፍ እንዲል የራሱን ሚና ይጫወታል የሚል ሀሳብ ሰጥተዋል ከመምህራኑ መካከል አስራ አንዱ የቋንቋ ቅየራ የደካማ ቋንቋ መምህራን ሃሳባቸውን ችሎታ ማሳያ ነው ብለው የሚያምኑ ናቸው እነዚህ ለመደገፍ ያቀረቧቸው ምክንያቶችም የሚከተሉት ናቸው ተማሪው የሚቀይረው ታላሚሜውን ቋንቋ ባለመቻሉ ነው ይህም ደካማነት ነውን ተማሪው ብቻ ሳይሆን መምህሩም የሚያስተምረውን ቋንቋ በደንብ አለመቻሉ ነው ወደ ራሱ ቋንቋ ተስቦ እንዲቀይር የሚያደርገውገ በብዛት ሊቀይሩ የሚችሉት በቋንቋው ድክመት ሲኖርባቸው ነውጎ እነዚህ መምህራን ያቀረቧቸው ነጥቦች በቋንቋ ቅየራ ወቅት እውነተኛ ስጋቶች መምህራን የቋንቋ ብቃት ክፍተት። ለሚለው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ የሚከተሉትን ስጋቶች ገልጸዋል መምህሩ ማስተማር ያለበት ታላሚውን ቋንቋ ብቻ ነው ሌላ ቋንቋ ሲጠቀም ለታላሟው ቋንቋ እድገት ጠንቅ ነው ተማሪው የሚማርበትን ቋንቋ አማርኛ በትክክል እንዳይሞክር ያደርጋል እንዲሁም ወደአንዱ ጋሞኛ እንዲያደላ ያደርጋልሀገ ተማሪዎች ታላሟውን ቋንቋ ለማወቅ እንዳይጥሩ ያደርጋል ጋሞኛንም ሆነ ታላሚውን ቋንቋ ሁለቱንም ቋንቋዎች አፍ መፍቻቸውን አማርኛን በየተመደበላቸው ጊዜ መማር ይገባቸዋል መቀየር የለባቸውምርገ መምህሩ እነሱን ለማስረዳት ብሎ የሚያደርውን የቋንቋ መቀየር ተማሪዎቹም እንደጥሩ ነገር ቆጥረው ያንኑ ይለምዱታል በሚማሩት በታላሚው ቋንቋ ችሎታ እንዳይኖራቸው ያደርጋል በሚማሩት በታላሚው ቋንቋ ላይ ተፅዕኖ ይፈጥራል በመማር ማስተማር ወቅትም ክፍለጊዜ ይገድላል የቋንቋ ቅየራ እየተጠቀሙ ማስተማርን እንቃወማለን የሚሉ መምህራን ቁጥር አነስተኛ መሆኑን ከመረጃው ማየት ተችሷል እነዚህ መምህራን በቁጥር በመቶኛ ናቸው እነዚህ አነስተኛ ቁጥር ያላቸው መላሾች ግን ለሀሳባቸው ድጋፍ የሚሆኗቸውን ስጋቶች አስቀምጠዋል መምህራኑ እንደ ስጋት ካስቀመጧቸው ሀሳቦች ውስጥ ጥቂት ከሌሎች ተዛማጅ ጥናቶች ጋር የሚስማሙ ሀሳቦች አሉሌ በተራቁጥር ላይ የቀረበውን ሀሳብ በተመለከተ የቋንቋ ቅየራ በታችኛው የክፍል ደረጃ በብዛት ሊከሰት ቢችልም ተማሪዎቹ የታላሚው ቋንቋ ብቃታቸው ከፍ እያለ ሲሄድ እየቀነሰ መሄድ እንደሚገባው እል«ሀህዉ እና ከእዐሀዐጪ ገልጸዋል በተራቁጥር ላይ የቀረበውም ሀሳብ በ እሀሀ እንደስጋት ቢቆጠርም መምህሩ ስጋቱን ለማስወገድ ምን ማድግ እንደሚገባው ተማሪዎች ታላሚውን ቋንቋ ለመማር ጥረት ከማድረግ ይልቅ መምህሩ ይተረጉምልናል የሚሉ ጠባቂዎች እንዳይሆኑ የቋንቋ ቅየራ እኩል በእኩል አንድ ቃል ተናግሮ ወዲያው መተርጎም አይገባም በማለት ይመክራሉ ሀዐ ፀ ከነዚህ ሁለት ስጋቶች ውጪ በመምህራን የቀረቡት ስጋቶች ግን በሌሎች አጥሂዎች ተቀባይነት የሌላቸው ናቸው ለምሳሌ በተራቁጥር የቀረበው ሀሳብ በ አሀሀ የቋንቋ ቅየራ ለመምህሩ የመማር ማስተማር ሂደቱን ያቀላል ግራ የማያጋባና ቀላል አገላለጽ ከታላሚው ቋንቋ ለመምረጥ የሚፈጀውን ጊዜ ያስቀርለታል ሀ ከሚለው ሀሳብ ጋር የሚቃረን ነው የቋንቋ ቅየራ በሚጠቀም ሰው ላይ የተለየ አሉታዊ ስሜት አይሰማኝም ለሚለው አራተኛ ጥያቄ ብልጫ ያላቸው የጥናቱ ተሳታፊ መምህራን አይስማሙም ቀድሞ ከነበሩት ሶስት ጥያቄዎች በተለየ ሁኔታ በርከት ያሉ መላሾች በዚህ ጥያቄ ላይ አቋም ለመያዝ ተቸግረዋል የቋንቋ ቅየራ በሚጠቀም ሰው ላይ አሉታዊ አመለካከት አለን ያሉት መምህራን የቃላት የትርጉም ለውጥና የአነጋገር ስርዓት ለውጥ እንዲፈጠር ያደርጋልጎ ለመምህሩ ተጨማሪ ስራ ይሆንበታል ጊዜውንም ይሻማበታል በተማሪዎች ላይ ግራ መጋባትን ይፈጥራል ዐዓ አንድ ሰው በንግግሩ ወቅት በጀመረበት ቋንቋ ብቻ ተጠቅሞ ሀሳቡን መግለጽ አለበት ኀ ለተማሪው በሚሰጠው እውቀት ላይ ክፍተት ይፈጥራል የሚሉትን ምክንያቶች በመግለጽ እምነታቸውን አስረድተዋል መምህራን በቋንቋ ቅየራ ላይ ያላቸውን አመለካከት ለተጠየቁበት ለዚህ ጥያቄ ከሰጡት ምላሽ ሁለት ጉዳዮችን መረዳት ይቻላል አንደኛው ከቀዳሚዎቹ ጥያቄዎች በተለየ ሁኔታ በጥያቄው ላይ የሚስማሙ እና የማይስማሙ መላሾች ተቀራራቢ ቁጥር እንዳላቸው መረጃው ያሳያል ሁለተኛው በመቶ መላሾች በጥያቄው ላይ ውሳኔ መስጠት አለመቻላቸውን መረጃው አሳይቷል በዚህም መምህራን የቋንቋ ቅየራን በተመለከተ ያላቸው ግንዛቤ የተሟላ ባለመሆኑ በስልቱ ላይ ያላቸው እምነት ክፍተት እንዳለበት ከውጤቱ መረዳት ይቻላል በዓለማችን ላይ የቋንቋ ቅየራን በተመለከተ ሁለት አይነት አተያይ እንዳለ በምዕራፍ ሁለት ተገልዷል የመጀመሪያው አሉታዊ አመለካከት ነው በብዛት ይህ አመለካካት ያላቸው ቀደም ባለው ጊዜ በቋንቋ ቅየራ ላይ ጥናቶችን ያደረጉ ምሁራን እንደሆኑ ሃ ዐ የተለያዩ ምሁራንን በመጥቀስ ይገልጻሉ ሌላው አመለካከት ደግሞ በብዙሀኑ የስነልሳን ባለሙያዎች እየተደገፈና ተቀባይነትን እያገኘ የመጣው አመለካከት ነው ይህ አመለካከት የቋንቋ ቅየራ ማህበራዊ ጠቀሜታው የጎላ ስለሆነ የተለያዩ ስልቶች ተቀይሰውለት በአግባቡ ጥቅም ላይ ሊውል ይገባዋል የሚልና ስለ ቋንቋ ቅየራ አዎንታዊ ስሜት ያለው ነው በ ህ እና ሃሃጸሀከሀከ ስለዚህ በመጠይቁ ለቋንቋ ቅየራ አሉታዊ አመለካከት አለን ያሉትም ሆነ ውሳኔ ለመስጠት ያልቻሉት መምህራን ስለስልቱ በቂ ግንዛቤ አግኝተው በቋንቋ ማስተማር ሂደት ውስጥ በአግባቡ ሊጠቀሙበት ይገባል የቋንቋ ቅየራ የተማሪዎችን ተሳትፎ ይጨምራል ብዬ አምናለሁ ለሚለው አምስተኛው ጥያቄ ከሠንጠረዥ ማየት እንደሚቻለው አብዛኛዎቹ መምህራን በክፍል ውስጥ የቋንቋ ቅየራ መኖር መጠቀም የተማሪዎችን ተሳትፎ ይጨምራል ብለው እንደሚያምኑ የጥናቱ ትንተና ይጠቁማል ይህ የመምህራኑ አቋም በበርካታ ምሁራን የተደገፈ ነው እንደ እዌ አገላለጽ የቋንቋ ቅየራ ይዘቱን ለመረዳት ያስችላል የትምህርት ተሳትፎንና አዳዲስ ጽንሰሀሳቦችን የመረዳት አቅምን ይጨምራ ሀ ሃ በተመሳሳይ መልኩ የቋንቋ ቅየራ የተማሪዎችን የክፍል ውስጥ ተሳትፎ እንደሚያሳድግ ገልጸዋል ስድስተኛው ጥያቄ ደግሞ የቋንቋ ቅየራ ተማሪዎች በራስ የመተማመን ስሜት እንዲኖራቸው ያደርጋል የሜል ዕምነት አለኝ የሚል ነው ከመላሽ መምህራን ውስጥ ቱ በመቶ የቋንቋ ቅየራ በራስ የመተማመን ስሜት ይፈጥራል ብለው ያምናሌ የቋንቋ ቅየራ በራስ የመተማመን ስሜት ስለመፍጠሩ የማይስማሙት መምህራን ጥቂት ቢሆኑም ለአቋማቸው በርካታ ምክንያቶች በማቅረብ ሀሳቡን ይቃወማሉ ተማሪው ታላሚ ቋንቋው አማርኛው ገብቶት ሳይሆን በተተረጎመለት በቋንቋ ቅየራ አማካኝነት በማወቁ በራስ የመተማመን ስሜት አይኖረውም ማወቅ የሚገባቸውን የሚማሩትን ቋንቋ አቀላጥፈው መናገር አለመቻላቸው እንዲፈሩ ያደርጋቸዋል እንጂ በራስ መተማመንን አይፈጥርላቸውም በራስ መተማመን የሚመጣው በሚማሩት ቋንቋ ሙሉ ክህሎት ሲኖራቸው ነው በራስ የመተማመን ስሜት በድፍረት ቋንቋውን ከመናገር ይልቅ ወደአፍ መፍቻቸው እንዲያዘነብሉ ያደርጋል የቋንቋ ቅየራ ተማሪዎች ትምህርቱን እንዲረዱት ሊያግዝ ይችላል እንጂ በራስ የመተማመን ስሜት እንዲኖራቸው የሚያደርግ አይመስለኝም በሚማሩት ቋንቋ እጥረት ምክንያት አፍመፍቻቸውን መቀላቀላቸው የፍርሀት የሀፍረት ስሜትና የሞራል ውድቀትን ያመጣል እንጂ በራስ መተማመንን አይፈጥርም ከመላሽ መምህራኑ ውስጥ ከአጋማሸ በላይ የሆኑት ተሳታፊዎች የቋንቋ ቅየራ በራስ የመተማመን ስሜትን ይፈጥራል ማለታቸውን መረጃው ያሳያል ይሁን እንጂ በመቶ መምህራን የቋንቋ ቅየራ ተማሪዎቹ በራስ መተማመናቸውን ከማዳበር ይልቅ የፍርሀትና የሀፍረት ስሜት እንዲላበሱ ያደርጋል ማለታቸው በትንተናው ታይቷል እነዚህ መምህራንም የቋንቋ ቅየራ የተማሪዎቹን በራስ የመተማመን ስሜት እንዴት እንደሚያጠፋ ማብራሪያዎችን አስቀምጠዋል ተዛማጅ ጥናቶች እንደሚሉት ከሆነ የቋንቋ ቅየራ የተማሪዎች ንግግር ክፍተትን ይሞላል እጩ የተማሪዎችን የመግባባት እድል ያሰፋል ተማሪዎቹ አላስፈላጊ ጭንቀትን አስወግደው በሂደት በታላሚው ቋንቋ ቀልጣፋ ተናጋሪ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል እዐሀዐ ይህም የቋናቋ ቅየራ ተማሪው የንግግር ክፍተቱን እንዲሞላ ካስቻለው በራስመተማመን ስሜት መግባባት ይችላል ማለት ነው ስለዚህ የዚህ ጥናት ግኝት ከዚህ በላይ ከተጠቀሱት ከጥናቶች ውጤት ጋር የተስማማ ነው ማለት ነው። ኛው ጥያቄ የቋንቋ ቅየራ ተማሪዎች የትምህርቱን ይዘት እንዳይረዱ እንቅፋት ይሆናል ብዬ አላምንም የሚል ሲሆን የተሰጠው ምላሽ እንደሚያመለክተው አብዛኛዎቹ መምህራን የቋንቋ ቅየራ ተማሪዎች የትምህርቱን ይዘት እንዳይረዱ እንቅፋት ነው ብለው አለማሰባቸውን መረጃው ያሳያል የቋንቋ ቅየራ ትምህርቱን ለመረዳት እንቅፋት ነው የሚሉ መምህራን ጥቂት ሲሆኑ ሁሉም መላሾች ግን በምን ምክንያት የቋንቋ ቅየራ ሁለተኛ ቋንቋ ትምህርትን ለመረዳት እንቅፋት እንደሚሆን አልገለጹም በሌሎች ጥናቶች የተረጋገጠውም የቋንቋ ቅየራ በሁለተኛና በውጪ ቋንቋ ትምህርት ውስጥ የተማሪዎችን የመማር ሂደት በመደገፍ ታላሚውን ቋንቋ አቀላጥፈው እንዲናገሩ ድጋፍ ሊሆን እንደሚችል ነው እሀፀሀ እ ሃ የቃለመጠይቁ የመጀመሪያ ክፍል ስምንተኛ ጥያቄ የቋንቋ ቅየራ በኛ ቋንቋ ትምህርት ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ይኖረዋል ብዬ አምናለሁ የሜል ነው ከግማሽ በላይ የሚሆኑት መላሾች ቋንቋ ቅየራ በኛ ቋንቋ ትምህርት ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አለው ብለው የሚስማሙ ናቸው የቋንቋ ቅየራ አሉታዊ ተጽዕኖ አለው የሚሉ መምህራን እንደሚከተለው ምክንያታቸውን ዘርዝረዋል ተማሪዎቹ ትርጉም ጠባቂ እንዲሆኑ ያደርጋል ለታላሚው ቋንቋ አማርኛ የሚሰጠው ትኩረት አናሳ ይሆናል በታላሟው ቋንቋ አማርኛ የሚያደርጉት ክሂሎችን በተለይ ንግግር ሊያዳብሩ የሚችሉ ልምምዶችን አቅም ይቀንሳል በአማርኛ የተማሩትን ይዘት ወደጋሞኛ መቀየሩ መተርጎሙ የትምህርቱን ሰዓት ይገላል ከዚህ በላይ ከተዘረዘሩት የመምህራኑ ምክንያቶች እንደሚስተዋለው በመምህራኑ እንደተጽዕኖ የተቀመጡት ሀሳቦች በጥያቄ ቁጥር ላይ በቋንቋ ቅየራ ወቅት ስጋት ናቸው ብለው መምህራን ካቀረቧቸው ጋር ተመሳሳይነት አላቸው በመሆኑም እነዚህ ሀሳቦች በተጽዕኖነት ቢቀርቡም ቀድሞ እንደተገለጸው መምህራን የቋንቋ ቅየራውን ሚና በመወሰንና በክፍል ውስጥ በምን ያህል ልክ ጥቅም ላይ ሊውል ይገባዋል በሚሉ ጉዳዮች ላይ ቀድሞ በመዘጋጀት ስጋቶቹን በማስወገድ ተጽዕኖውን መከላከል ይቻላል የክፍል አንድ የመጨረሻ ጥያቄ በኛ ቋንቋ ትምህርት ክፍለጊዜ የቋንቋ ቅየራን ተጠቅሞ ማስተማር የትምህርቱን ሂደት ማገዝ ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖ አለው የሚል ዕምነት አለኝ የሚል ነው ከመላሽ መምህራን አብዛኛዎቹ የቋንቋ ቅየራን ተጠቅሞ ማስተማር በኛ ቋንቋ ትምህርት ክፍለጊዜ የትምህርቱን ሂደት ማገዝ ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖ እንዳለው የሚስማሙ ናቸው አስራ ሰባት በመቶ መምህራን በሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት ወቅት የቋንቋ ቅየራ እየተጠቀሙ ማስተማር ትምህርቱን በማገዝ ሂደት ላይ አዎንታ ሚና እንዳለው ይስማማሉ ይህ ማለትም አፋቸውን በጋሞኛ የፈቱ ተማሪዎች አማርኛን እንደሁለተኛ ቋንቋ በሚማሩበት ወቅት የቋንቋ ቢቀይሩ ከመምህራን አሉታዊ ግብረ መልስ አያጋጥማቸውም ስለዚህ ተማሪዎቹ የቋንቋ ቅየራን እንደ አንድ ስልት በመጠቀም የሁለተኛ ቋንቋ ትምህርታቸው አጋዥ ሊያደርጉት መቻላቸውን የመረጃው ትንታኔ ያሳያል የጥናቱ ተሳታፊ መምህራን ለዚህ ጥያቄ የሰጡት ምሳሽ በእህከከ ከተደረገው ጥናት ውጤት ጋር ተመሳሳይ ነው እንደ እህከከ ጥናት ውጤት እንግሊዝኛ የመማሪያ ቋንቋ በሆነበት ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ የህጠህ አፈፈት ተማሪዎችን የሚያስተምሩ መምህራን አብዛኛዎቹ የትምህርት ሂደቱን ለማገዝ የተማሪዎቹን አፍመፍቻ ቋንቋ እንደሚጠቀሙ ሲገልጹ ተማሪዎችም የቋንቋ ቅየራ የትምህርቱን ሂደት ማገዝ ላይ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል ዩፀ መምህራኑ በጽሁፍ መጠይቁ ክፍል አንድ የቋንቋ ቅየራ አተያያቸውን በተመለከተ ለተጠየቁት ጥያቄዎች የሰጧቸውን ምላሾች በሚከተለው መልኩ ማጠቃለል ይቻላል አብዛኛዎቹ መምህራን አተያይ ስልቱ የደካማ ችሎታ ማሳያ ነው ብለው አያስቡም ተቀራራቢ ቁጥር ያላቸው መላሾች የቋንቋ ቅየራን በአዎንታዊነቱና በአሉታዊነቱ እንደሚመለከቱት የገለጹ ሲሆን በዚህ ጥያቄ ላይ ለመወሰን አልቻልኩም ያሉ መምህራንም በርካቶች ሲሆኑ ይህ ቁጥርም በዚህ የመጠይቁ የመጀመሪያ ክፍል ውስጥ ከተካተቱ ጥያቄዎች ውስጥ ብዙ መምህራን ለመስማማትና ላለመስማማት ያልወሰኑበት ጥያቄ ነው በርከት ያሉ መላሾች አሉታዊ አመለካከት የያዙባቸው በተራቁጥር የቋንቋ ቅየራ የቋንቋ እድገትን ይገታል እና የቋንቋ ቅየራ በኛ ቋንቋ ትምህርት ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ይኖረዋል ብዬ አምናለሁ በሚሉት ጥያቄዎች ላይ ነው እነዚህን ሁለት ጥያቄዎች አስመልክቶ መምህራኑ የሰጡት ምላሽ በቋንቋ ቅየራ ላይ ስላላቸው አመለካከት ከሰጧቸው ሌሎች ጥያቄዎች ምላሽ ጋር የሚቃረን ነው በጥያቄዎቹ ላይ ለምን አሉታዊ አመለካከት እንዳላቸው ምክንያቶችን አስቀምጠዋል ምሁራን ግን እነዚህ ምክንያቶች የቋንቋ ቅየራ በክፍል ውስጥ ሲተገበር ሊፈጠሩ የሚችሉ ስጋቶች መሆናቸውና አንድ መምህር እንዴት ባለ መልኩ እነዚህን ችግሮች አስወግዶ ስልቱን በሚገባ መጠቀም እንዳለበትም ሀሳባቸውን ሰንዝረዋል በመሆኑም በመምህራኑ የተገለጹት ሀሳቦች ከአሉታዊ አመለካከት የመነጩ ሳይሆን ስልቱን በሚጠቀሙበት ወቅት ከሚገጥሟቸው ችግሮች ስጋት መነሻነት እንደሆነ የመረጃ ትንተናው ያሳያል የተማሪዎች የክፍል ውስጥ የቋንቋ ቅየራ ሁኔታ በዚህ ክፍል የሚተነተኑት አብዛኛዎቹ መረጃዎች ከተማሪዎች በምልከታ የተገኙት ሲሆኑ ከጽሁፍ መጠይቅ የተሰበሰቡት መረጃዎችም እንደየአስፈላጊነቱ በትንተናው ውስጥ ተካተዋል መረጃዎቹ በምልከታ የተሰበሰቡት ከሁለት ትምህርት ቤት ነው እነሱም ቱቱሻና ጨንቻ የመጀመሪያ ደረጃ ኛ እና ኛ ሳይክል ትምህርት ቤቶች ናቸው ሁለቱም ትምህርት ቤቶች በተለያየ የቋንቋ አውድ ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎችን የሚያስተምሩ ሲሆን በቱቱሻ የሚገኙት አብዛኛዎቹ ተማሪዎች ልሳነ ዋህድ በጨንቻ የሚማሩት አብዛኛዎቹ ተማሪዎች ደግሞ ልሳነ ክልዔ ናቸው በቱቱሻ አንድ እና በጨንቻ ሁለት የአምስተኛ ክፍል ሴክሽኖች ያሉ ሲሆን በየትምህርት ቤቶቹ አራት አራት ጊዜ ምልከታ ተደርጓል ምልከታ በተደረገባቸው ወቅቶች የቀረቡት ትምህርቶች የንግግርና የማንበብ ክሂሎች የቃላትና የሰዋሰው ይዘቶች ናቸው ትንተናው ሲከናወንም በቅድሚያ በመቅረጸ ድምጽወምስል የተቀረጹት የተማሪ ምልልሶች በአጥሂው አማካኝነት ወደጽሁፍ ተቀይረዋል የጋሞኛ ንግግሮች ወደ ጽሁፍ የተቀየሩት የአማርኛ ስርዓተ ጽህፈት ፊደላትን በመጠቀም ነው በመቀጠልም ወደጽሁፍ የተቀየረውን የተማሪዎች የጋሞኛ ንግግር ከአንደኛ ደረጃ እስከ ኮሌጅ መሰናዶ ያለውን ትምህርታቸውን በጨንቻ ወረዳ በተማሩ የጋሞኛ አፈፈት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ወደአማርኛ ከተተረጎመ በኋላ የጋሞኛ አፈፈት በሆኑ አማርኛ መምህራን እንዲረጋገጥ ተደርጓል ከዚህ በታች በሁለቱም ትምህርት ቤቶች የተደረጉትን የቋንቋ ቅየራዎች መጠንና ዓይነት የሚሜያሳይ ሰንጠረዥ አለ ሰንጠረኾን ተከትሎ በምልከታው ወቅት በታዩት ዝርዝር የቋንቋ ቅየራ መረጃዎች ላይ ትንተና ይደረጋል ጦሪዥ ፈጋ ያያፉሥምሮሦ ይ። የዓረፍተ ነገር ቅየራ ደረጃ ድምር በምልከታው ወቅት በሁለቱም ትምህርት ቤቶች በአጠቃላይ የቋንቋ ቅየራዎች ተካሂደዋል ከነዚህ ውስጥ አብዛኛው ቅየራ የተካሄደው በቱቱሻ ገጠራማው ትምህርት ቤት ነው ተማሪዎቹ ከሜገኙበት አውድ በመነሳት መገመት እንደሚቻለው በከተማ ያሉት ተማሪዎች የተመዘገበው ቅየራ አንሶ በገጠራማው ክፍል በሚገኙት ተማሪዎች የተከናወነው ቅየራ የበዛበት ምክንያት በገጠር የሚገኙት ተማሪዎቹ በታላሚሜው ቋንቋ ካላቸው የዕውቀት ውሱንነት የመነጨ ሊሆን መቻሉን ነው እሀህሀዘዉ በጥናታቸው እንደገለጹት በታላሜው ቋንቋ ከፍተኛ ብቃት ካላቸው ይልቅ ችሎታቸው አነስተኛ የሆኑ ተማሪዎች ቅየራን እንደ ስነትምህርታዊ ስልት ይጠቀሙበታል ተማሪዎች በታላሚ ቋንቋ ያላቸው እውቀት እየጨመረ ሲመጣ የቋንቋ ቅየራ ስነትምህርታዊ ሚናው እየቀነሰ ይመጣል ይህ በምልከታ የተገኘው ውጤት ተማሪዎቹ በቃለመጠይቅ የሰጡትን መረጃ ትክክለኛነት የሚያረጋግጥ ነው ሰንጠረዝ ላይ ከሰፈረው አጠቃላይ መረጃ ትኩረት የሚሰጠው ሌላው ጉዳይ የቋንቋ ቅየራው በየደረጃው ያለው ልዩነት ነው በሁለቱም ትምህርት ቤት ተማሪዎች በዲስኩር ቃላት ደረጃ ተቀራራቢ የቅየራ ቁጥር አለ ዮሴፍ በሀረሬ ቋንቋ ላይ ባደረጉት ጥናት አብዛኛው የቅየራ የታየው በቃል ደረጃ እንደሆነ ገልጸዋል ዮሴፍ በጨንቻ ከተማ የሚገኘው የጨንቻ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ከዮሴፍ ጥናት ጋር በሚመሳሰል ሁኔታ ከፍተኛ የቃላዊና ሀረጋዊ ደረጃ ቅየራ ሲያስመዘግቡ በቱቱሻ የሚገኙት ተማሪዎች ግን በቃልና ሀረግ ደረጃ ያካሄዱት ቅየራ ዝቅተኛ ነው በቱቱሻ ተማሪዎች ከፍተኛ ቅየራ የተከናወነው በዓረፍተ ነገር ደረጃ ነው የጨንቻ ተማሪዎች ዓረፍተ ነገር ደረጃ ያካሄዱት ቅየራ ግን በጣም ዝቅተኛ መጠን ብቻ ነው ከዚህም መረዳት እንደሚቻለው በቋንቋ ቅየራ ደረጃዎችና የታላሚሜ ቋንቋ ዕውቀት መካከል ቁርኝት እንዳለ ነው ይኸውም ተማሪዎች በታላሚው ቋንቋ ያላቸው ብቃት ከፍ ሲል በብዛት የሚኖረው የቅየራ ደረጃ ቃላዊ ሲሆን ዝቅተኛ የታላሚ ቋንቋ ብቃት ያላቸው ተማሪዎች ግን በብዛት የሚያከናውኑት የቋንቋ ቅየራ በሀረጋትና በዓረፍተ ነገር ደረጃ የሚከናወን ነው በመቀጠልም በየትምህርት ቤቶቹ የተመዘገበው የቋንቋ ቅየራ ትንተና እንደሚከተለው ቀርቧል ከጨንቻ ተማሪዎች በምልከታ የተገኘ የቋንቋ ቅየራ ትንተና ይህ ክፍል በጨንቻ የከተማ ወረዳ በሚገኘው ጨንቻ የመጀመሪያ ደረጃ ኛና ኛ ሳይክል ትምህርት ቤት ተማሪዎቹ አማርኛ ቋንቋ ሲማሩ በተደረገ ምልከታ የተሰበሰቡ መረጃዎች የተተነተኑበት ነው በትምህርት ቤቱ አራት ምልከታዎች ሲደረጉ በመተንተን ሂደት የቅየራዎቹ ደረጃና ሚናቸው በዝርዝር ተገለዷል አውዳቸውን መግለጽ የግዴታ አስፈላጊ በመሆኑም እያንዳንዱ ቅየራ አውዱን መሰረት በማድረግ ተተንትኗል የትንተናውን ስፋት ለማጥበብ በተመሳሳይ አውድ የተከናወኑ ቅየራዎችን አንድ ላይ እንዲተነተኑ ተደርጓል በማዕዘናዊ ቅንፍ ውስጥ የተቀመጠው የተማሪዎቹ አንዳንዴ የመምህራን ንግግር ሲሆን ከእሩይ በኋላ በኢታሊክ አጻጻፍ የተጻፈው የንግግሩ የአማርኛ ፍቺ ነው ሩ መምህር ዶብተር አውጡ ዳውተሬኒ መጽሀፌኒ ኬሲቴ ተማሪ ኤሮ ተማሪ ኤሮሾበ ቀረጻ መምህር ሀ ኤሮ አብዛኛውን ጊዜ መምህራቸው በጋሞኛ ትእዛዝ ስታስተላልፍላቸው ተማሪዎቹ ትዕዛዝ መቀበላችውን የሚያረጋግጡበት ቃል ነው በተደጋጋሚ የታየ የቅየራ ዓይነት ሲሆን ሾ የሚል ምዕላድ ተቀጥሎ የተነገረበትም አጋጣሚ አለ የምእላዱ መጨመር ትእዛዙን በፍቅርና በትህትና መቀበልን ያመለክታል ቀ ፖማሪ ብሳና አይደልገ ፖማሪ አይደለም ተማሪ ዋኖ ምሃ ልጂሥ። ናፖው ተማሪ አዮን አዋዛ ዳናፖና ያ ቀረጻ እና መምህር ለ ከምልልሱ ማየት እንደሚቻለው ረዣዥም አረፍተ ነገር የምትናገረው መምህርቷ ስትሆን ተማሪዎቹ ለሚጠየቁት ጥያቄዎች አጫጭር መልሶችን በመስጠት የተገደቡ ናቸው ምንም እንኳን ክፍለጊዜው አማርኛ ያነበቡት ምንባብም በአማርኛ ቢሆንም ተማሪዎቹም ሆነ አስተማሪያቸው የሚግባቡት በጋሞኛ ነው አንዳንድ ጊዜ መምህርቷ በአማርኛ ለምትጠይቃቸው ጥያቄዎች በቅሎ እንስሳ መመደብ የሚሉትን ቃላት እየቀየሩ ከመመለስ ውጪ ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል መልኩ ምልልስ የሚያከናውኑት ንግግራቸውን ወደ ጋሞኛ በመቀየር ነው በዚህ የመምህርና የተማሪዎች የንግግር ልውውጥ የሚታየው የቋንቋ አጠቃቀም የአፍመፍቻ ቋንቋ ቅየራ በሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት ሊኖረው ከሚገባ አዎንታዊ ሜናው ይልቅ አሌታዊ ሚናው የጎላ መሆኑ ነው በጥናቱ የተሳተፉ መምህራን የቋንቋ ቅየራ ላይ ያላቸውን አተያይ በተመለከተ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጧቸው ምላሾች ውስጥ በሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት የቋንቋ ቅየራ መጠቀም ይህን ጊ መሰል ችግር ሊያመጣ እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸዋል ለምሳሌ በሰንጠረዥ የቋንቋ ቅየራ የቋንቋ እድገትን ይገታል የሚል እምነት የለኝም ለሚለው ጥያቄ በመቶ መምህራን ምላሽ የቋንቋ ቅየራ የቋንቋ እድገትን ይገታል የሚል እምነት እንዳላቸው የሚየሳይ ነው ለዚህም እምነታቸው በምክንያትነት ከሰጧቸው መልሶች ውስጥ በታላሚ ቋንቋ እየተማሩ አፍመፍቻቸውን መጠቀም ታላሚ ቋንቋውን በአግባቡ እንዳያሳድጉት ያደርጋል የቋንቋ ቅየራ ተማሪዎች ቋንቋውን ለመማር የሚያደርጉት ጥረት አናሳ ከማድረጉም ባሻገር በመምህሩ ትርጉም ላይ ጥገኛ ትርጉም ጠባቂ ያደርጋቸዋል ታላሚውን ቋንቋ እንዳይረዱት ያደርጋል ቅየራው ሙሉ መልዕክት እንዳይተላለፍ ሊያግድ ስለሚችል ታላሚ ትምህርታቸው ላይ ችግር ይፈጥራል ቋንቋ በመቀየር የሚያስተምር መምህር ከታላሚው ይልቅ ለአፍመፍቻቸው ትኩረት ስለሚያደርግ የታላሚው ቋንቋ ትምህርት ተጎጂ ይሆናል ከሙሉው የቋንቋ ዕውቀት ይልቅ የተወሰነ የቃላት ዕውቀት ብቻ እንዲኖራቸው ያደርጋል የሰዋሰው ችግር እንዲኖርባቸው ያደርጋል የሚሉት ስጋቶች ከላይ ባለው የክፍል ውስጥ ምልልስ የተስተዋሉ ችግሮች ናቸው በርግጥ እሀሀዉ መምህሩ ቋንቋዎችን እያቀያየረ መጠቀሙ የተማሪዎችን የመግባባት ዕድላቸውን ስፋት ያረጋግጣል ትኩረታቸው ወደ ይዘቱ እንዲሆን ከማድረጉም ባሻገር ከሚያውቁት ወደማያውቁት እንዲሸጋገሩ ያስችላቸዋል በተጨማሪም የቋንቋ ቅየራ ተማሪዎቹ አላስፈላጊ ጭንቀትን አስወግደው በሂደት በታላሚው ቋንቋ ቀልጣፋ ተናጋሪ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል ቢሉም ቅየራው በምን ያህል ልክ ሊሆን እንደሚገባው ቀድሞ መወሰንና ስልት መንደፍ ያስፈልጋል መምህሩ ሊጠነቀቅባቸው ከሚገባቸው ጉዳዮች ውስጥም የቋንቋ ቅየራ በምን ያህል ደረጃ መከናወን አለበት። ፈደድያመረ ዳውፇቃሦ ፅሄር ረ ዳዴፉ ፅራ ቀረጻ መምህር ሐ በጋሞኛ ጸታ አመልካች ቅጥያ ምዕላድ ባይኖርም ምልልሶቹ ወደ አማርኛ ሲተረጎሙ በተናጋሪዎቹ ጾታ አመልካች እንዲተረጎሙ ተደርጓል በመጀመሪያው የክርክር ክፍለጊዜ ከታየው ምልልስ ይልቅ በዚህ በሁለተኛው ክፍለ ጊዜ ሰፋ ያለ ምልልስ ተከናውኗል ክርክሩ አንድ ሰው በህይወቱ እውቀት ይሻለዋል ወይስ ገንዘብ በሚል ርእስ የተከናወነ ነው ምንም እንኳን ክርክሩ በዋነኛነት በጋሞኛ የተከናወነ ቢሆንም በቱቱሻ ከተከናወኑት መስተጋብሮች በርከት ያሉ የአማርኛ ቃላትን በመጠቀም ንግግር የተደረገባቸው ምልልሶች የሚገኙት በዚህ ክፍለ ጊዜ ነው ተማሪዎቹ በተናገሯቸው የጋሞኛ ዓረፍተነገሮች ውስጥ የቀየሯቸው ቃላት እውቀትኤሮ ብርሚሻ ሻይ ገንዘብሚሻ ልብስመይኦ ክፍልክፍሌ መጀመሪያሲንሳ አንደኛኢሲኖ ደብተርደውተር ሰባትላኾ አይምሮወዘና ሰዓትሰዓቴ አትሸወድምበሌቲኪ ሲጀመርሲንሳ እሺኤሮ ግንራሺ የሚሉት ናቸው ከነዚህ ቃላት ውስጥ ሻይ ክፍል ደብተር ሰዓት የሚሉት ቃላት ከአማርኛ በውሰት ቋንቋውን የተቀላቀሉ ናቸው የቅየራውን ሁኔታ በተመለከተ በመጀመሪያው የክርክር ክፍለጊዜ ትንተና ላይ እንደተገለጸው መምህሩ በየመሀሉ እየገባ ተማሪዎቹ በአማርኛ እንዲከራከሩ ማሳሰቢያ በመስጠት እንዲሁም ራሱም በአማርኛ እየተናገረ ተማሪዎች ፈለጉን እንዲከተሉ አቅጣጫ ቢያሳይም ተማሪዎቹ ግን በአማርኛ ንግግራቸው ጋሞኛን ከመቀላቀል ይልቅ በጋሞኛ ንግግራቸው ውስጥ የተወሰኑ የአማርኛ ቃላትን በመቀየር መግባባትን መርጠዋል በዚህም ክፍለ ጊዜ መምህራን የቋንቋ ቅየራ በሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት ውስጥ አዎንታዊ ሜና እንዲኖረው ተገቢውን ዝግጅትና ጥንቃቄ አለማድረጋቸውን ከምልከታው መገንዘብ ተችሏል በመሆኑም ስልቱ ከአዎንታዊ ሚናው ይልቅ ቀደም ባሉት የቱቱሻ ትምህርት ቤት የክፍል ውስጥ ምልከታ ትንተናዎች ላይ በዝርዝር እንደተገለጸው በጥናቱ ተሳታፊ መምህራን የተጠቆሙ አሉታዊ ገጽታዎቹ ጎልተዋል እነዚህ ከታች የተዘረዘሩት ቅየራዎች በተማሪዎቹ ምልልስ ውስጥ ቀጥታ ከመማር ማስተማሩ ጋር ተያያዥነት የሌላቸው የቋንቋ ቅየራዎች ናቸው አብዛኛዎቹ ተማሪዎቹ እርስበእርሳቸውም ሆነ ከመምህራቸው ጋር በሚኖራቸው መስተጋብር ተደጋግመው የተከሰቱ የዲስኩር ቃላት ሲሆኑ የተወሰኑ ከጋሞኛና ከአማርኛ በተወሰዱ ቃላት የተዋቀሩ ጥምር ቃሎችም ተካተዋል ሩ ተማሪ ኤር ተማሪ ያ ያፈፖሆን ተማሪ ዎ ተማሪ ሀይ ቋሪጳሠጩጭ ተማሪ ዴኤስ ተማሪ ሀዖኔስ ይሬታጳረጋጣያያፉጳ ተማሪ ሃ ሺቂቴ ኢንቴ ፇዎታኛ ፖሦሮፇም መደደ ሦጠ ፈያሆ ሃሪያሥ ለውድ ሦያሯሳ መደያሆሪኃው ያኛ ታሃ ቀሪያፇጎፇራ ዖጳ ው ተማሪ ግድ ጌስ ግድ ይላል ተማሪ ጊዶይራ ሀሳኦ ዎፇሃ ዖፇው ልድ ፖሦናገሮ ተማሪ ሀዴ ናኤ ኦቻ ጂ ያሐፇው ጂሷሯ ጨፅፀቃታፖ ተማሪ ሃሄሲ አዋ ሀሳኤ ሪይሯሃ ምፇ ሪጎላ ምፇ ያወራ ተማሪ ዋና ዋና ቆፎታ ዎና ዎና ሠፀዐቻ ቀረጻ እና መምህር ሐ በአጠቃላይ በሁለቱም ትምህርት ቤቶች በተደረጉ የ ክፍለጊዜ ምልከታዎች በተገኘው መረጃ መሰረት በስምንቱ የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ክፍለጊዜዎች ከቃላት እስከ አረፍተነገር የሚደርሱ የጋሞኛ ቋንቋ አላባዎች ቅየራ ሲመዘገብ አብዛኛውን የቋንቋ ቅየራ ያከናወኑት በገጠር አካባቢ የሚገኙት የቱቱሻ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ናቸው ከነዚህ ቅየራዎች ውስጥ አስራ ሶስቱ በዲስኩር ቃላት ሀምሳ ዘጠኙ በቃላትና ሀረጋት እንዲሁም ስልሳ ሰባቱ በዓረፍተ ነገር ደረጃ የተከናወኑ ናቸው በከተማና በገጠር ባሉ ትምህርት ቤቶች መካከል ቅየራ የሚካሄድባቸው ደረጃዎች ላይ ልዩነት አለ ለምሳሌ በከተማ በመቶ ቃላትና ሀረጋት ሲመዘገቡ በገጠሩ ትምህርት ቤት ግን በመቶ በዓረፍተ ነገር ደረጃ ያሉ ቅየራዎች ናቸው በኛ ቋንቋ ትምህርት የአፍመፍቻ ቋንቋ ቅየራ ያለው ሚና የቋንቋ ቅየራ በመማርያ ክፍል ጠቀሜታ እንዳለው የተለያዩ ምሁራን ገልጸዋል እጪ«ሀህህዉ እሀህዐ እ ሯ«ቧ በይበልጥም እህከ አፍመፍቻ ቋንቋ በኛ እና በውጪ ቋንቋ መማርያ ክፍል ውስጥ ሊኖረው ስለሚችለው ሚና አብራርተዋል ይህ የጥናቱ ክፍል የቋንቋ ቅየራ በኛ ቋንቋ መማርያ ክፍል ውስጥ የሚኖረውን ሚና በተመለከተ የተሰበሰቡ መረጃዎች የተተነተኑበት ነው ትንተናው በሁለት ንዑሳን ክፍሎች የተከፈለ ሲሆን በቀዳሚው ክፍል መምህራን ሁለተኛ ቋንቋ በሚያስተምሩበት ወቅት የተማሪዎችን የአፍ መፍቻ ቋንቋ ቅየራ ተጠቅመው ማስተማራቸው ያለውን ሚና አስመልክቶ ከመምህራኑ የተሰጡ ምላሾች ትንተና በምልከታ ከተገኘው መረጃ ጋር ተሰናስሎ ቀርቧል በሁለተኛው ክፍል ደግሞ በሁለተኛ ቋንቋ መማርያ ክፍል ውስጥ የቋንቋ ቅየራ ለተማሪዎች ያለውን ጠቀሜታ በተመለከተ በምልከታና በጽሁፍ መጠይቅ ከመምህራን የተገኙ መረጃዎች ሌሎች አጥፒዎች ስለርዕሰጉዳዩ ካቀረቧቸው ሀሳቦች ጋር ተዋህደው የቀረቡበት ነው ቋንቋ ቅየራ በኛ ቋንቋ ትምህርት ለመምህራን ያለው ሚና የሁለተኛም ሆነ የውጪ ቋንቋ ትምህርት በሚሰጥበት መማርያ ክፍል የትምህርቱ ዋነኛ ዓላማ ተማሪውን በታላሚው ቋንቋ ብቃት እንዲኖረው ማስቻል ነው ይህንን ዓላማ ለማሳካት አንዱ የማስተማርያ ስልት የሆነው ቋንቋ ቅየራ ነው ለጥናቱ ምልከታ በተደረገባቸው ትምህርት ቤቶች የሚገኙ አማርኛን እንደሁለተኛ ቋንቋ የሚያስተምሩ መምህራን ይህንን ስልት ለተለያየ አገልግሎት ሲጠቀሙበት ተስተውሷል ከምልከታው በተጨማሪም መምህራን ስለቋንቋ ቅየራ ሚና መረጃ ሰጥተዋል ለመምህራን በተዘጋጀው የጽሁፍ መጠይቅ ውስጥ የመጨረሻውን ክፍል ያዘው መምህራን ሁለተኛ ቋንቋን ሲያስተምሩ የተማሪዎችን አፍመፍቻ ቋንቋ እየቀየሩ መጠቀም ሊኖረው የሚችለው ሚና ምንድን ሊሆን ይችላል የሚለው ነው በዚህ ርዕሰጉዳይ ላይ ባተኮረው ቀጣዩ ትንተና በመጀመሪያ የመምህራንን የጽሁፍ መጠይቅ ምላሽ በሰንጠረዥ በማቅረብ ከሰንጠረዥ በማስከተልም በምልከታ የተገኘውን መረጃ በርዕሰጉዳዩ ላይ ጥናት ካደረጉ ሌሎች አጥሂዎች ውጤት ጋር በማሰናሰል ቀርቧል የሰንጠረ አተናተን በአብዛኛው መምህራን የአፍመፍቻ ቋንቋ በሁለተኛ ቋንቋ ማስተማር ወቅት በክፍል ውስጥ የተማሪዎችን የአፍ መፍቻ ቋንቋ መቀየር በተለይ ለመምህራን ሊኖረው የሚችለው ሜና ተብሎ ከተመረጠው የቋንቋ ቅየራ ሚና ዝቅተኛ ቁጥር ባላቸው መምህራን እስከተመረጠው ጠቀሜታ ድረስ በቅደም ተከተል የተዘረዘረበት ነው ሥጋጠሪ ፈ ቆያ ቀዖሪ ። ዕማማቀቻታሥ ዲሪደል ተማሪዎች በህብረት እንስማማለን ተማሪዎች በህብረት አንስማማም ተማሪዎች በህብረት ሰማማኤቶኮ ዳፇያጋማም ቀረጻ መምህር ሀ በመምህርቷና በተማሪዎቹ መካከል የተደረገው የንግግር ልውውጥ የቤት ስራ ያልሰራ ተማሪ እንዲወሰድበት በተፈለገው እርምጃ ላይ ተማሪዎቹ መስማማት አለመስማማታቸውን የገለጹበት ነው ምልልሱ በታላሜ ቋንቋ ውስጥ የተማሪዎቹ አፍ መፍቻ ቅየራ የተከናወነበት ነው የቅየራው ሚናም መምህርቷ በክፍል ውስጥ ከተማሪዎች ጋር ለሚኖራት መስተጋብርና የክፍል አስተዳደር ድጋፍ ሆኖ ማገልገል ነው የቋንቋ ቅየራ መምህሩ ለሚኖረው ክፍል አስተዳደር ከፍተና ሚና እንደሚጫወት በርዕሰ ጉዳዩ ላይ ጥናት ያደረጉ ምሁራንም ከእፉህህህ ገልጸዋል ከላይ ባለው ምልልስ ውስጥ የተከናወነው የቋንቋ ቅየራ ሚናም ለዚህ አስረጅ ነው መምህርቷ በሰነዘረችው ሀሳብ ላይ ተማሪዎቹ መስማማት አለመስማማታቸውን ከጠየቀች በኋላ የአማርኛ ቋንቋ ብቃታቸው አነስተኛ ለሆኑ ተማሪዎች በጋሞኛ ደግማላቸዋለች ተማሪዎቹም የተወሰኑት በአማርኛ ሲመልሱ የተወሰኑት ግን በጋሞኛ ምላሻቸውን ሰጥተዋል ስለዚህ በዚህ መስተጋብር የክፍሉን ተማሪዎች ሁሉንም እንደ ቋንቋ ምርጫቸውና ብቃታቸው ለማስተናገድለመቆጣጠር የቋንቋ ቅየራ እንደ ስልት መጠቀሟን ማየት ተችሷል በሁለተኛ ቋንቋ ማስተማርያ ክፍል ውስጥ መምህራን የተማሪዎችን የአፍ መፍቻ ቋንቋ መቀየራቸው ሌሎች ጠቀሜታዎች እንዳሉት መምህራን የጽሁፍ መጠይቁ ላይ ከሰጡት መረጃ ማወቅ ተችሏል እነዚህ ጠቀሜታዎችም የምክር ለመስጠት ይረዳል ትምህርቱን በጥልቀት ለማስረዳት ይረዳል ትምህርቱን መረዳታቸውን ለማረጋገጥ ያስችላል እንዲሁም በመምህሩና በተማሪው መሀከል አዎንታዊ ግንኙነት ለመፍጠር ያስችላል የሜሉ ናቸው በምልከታ ወቅት መምህራን የቋንቋ ቅየራን ለነዚህ አገልግሎት ሲያውሉት ስላልታየ በምልከታ ማረጋገጥ አልተቻለም ቢሆንም የጽሁፍ መጠይቅ ትንተና እንደሚያሳየው መምህራን የተማሪዎችን አፍ መፍቻ ቋንቋ ተጠቅመው ምክር ለመስጠት ይችላሉ ትምህርቱን በጥልቀት ያስረዳሉ ተማሪዎች ትምህርቱን መረዳታቸውን ያረጋግጣሉ በሁለተኛ ቋንቋ ማስተማር ወቅት መምህራን የተማሪዎችን አፍመፍቻ ቋንቋ በመቀየር የሚኖረውን ሚና በተመለከተ ሀሳባቸውን የሰጡ እንደ ከአህርህሣዘኋ ያሉ አጥሂዎች በዚህ ጥናት ከተገኘው ውጤት ጋር የሚቀራረብ ሀሳብ ሰጥተዋል በተጨማሪ ጄሐዘዝበከ እንደሚሉት መምህራን ሁለተኛ ቋንቋን ወይም ታላሚ ቋንቋን ሲያስተምሩ የተማሪዎችን አፍ መፍቻ ቋንቋ እየቀየሩ መጠቀማቸው በመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ በሶስት ዋናዋና ምድቦች የሚከፋፈሉ ወደስምንት የሚጠጉ ሚናዎች አሉት ሶስቱ ዋና ዋና ክፍሎችም ለክፍል አመራር ርዐዐበ በበበበበ የትምህርትን ይዘት ለመደገፍ ቨሀቨበ እና ለማህበራዊ ትስስሮሽ ርል ሀ ናቸው በሁለቱ ጥናት አቅራቢዎችም ሆነ በዚህ ጥናት ውጤት መካከል ያለው ልዩነት አንድ ነው ይኸውም መምህራን በሁለተኛ ቋንቋ መማሪያ ክፍል በሚያስተምሩበት ወቅት የተማሪዎቹን የአፍመፍቻ ቋንቋ መጠቀማቸው በቀዳሚነት በሚኖረው ሚና ላይ ሲሆን እ«ሀህዉጪ የቋንቋ ቅየራው ዋነኛ ሚናው ተግባቦታዊ ጠቀሜታ ነው ሲሉ እንደ ጅዐህበከ ጥናች ውጤት ደግሞ የስልቱ ዋነኛ ሚሜና ለክፍል አያያዝ ነው በዚህ ጥናት ከመምህራን የተገኘው መረጃ ውጤት ከሁለቱ ምሁራን ሀሳብ የተለየ ነው በመምህራኑ ምላሽ የቋንቋ ቅየራው ዋነኛ ሚና የትምህርቱን ይዘት ማስረዳት ስነትምህርታዊ ነው ከዚህ ልዩነት ውጪ ግን በዚህ ጥናት ላይ መምህራኑ የሰጡት ምላሽ ቀደም ሲል ከተጠቀሱትም ሆነ ከሌሎች በተመሳሳይ ርዕስ ከሰሩ ምሁራን ስራዎች ጋር ተመሳሳይ ነው የቋንቋ ቅየራ በኛ ቋንቋ ትምህርት ለተማሪዎች ያለው ሚና ከዚህ በመቀጠል ተማሪዎች የአፍመፍቻ ቋንቋቸውን በሁለተኛ ቋንቋ መማርያ ክፍል ውስጥ መቀየራቸው ስለሚኖረው ሚና መምህራን በጽሁፍ መጠይቅ የሰጡት መረጃ በምልከታ ከተገኘው ውጤት ጋር ተጋምዶ እንደሚከተለው ቀርቧል መምህራኑ የአፍመፍቻ ቋንቋ ቅየራ በኛ ቋንቋ ትምህርት ለተማሪዎች ሊኖረው ስለሚችለው ሜና የሰጧቸው ምላሾች ትንተና እስማማለሁን አልስማማም እና ለመወሰን እቸገራለሁን በሚሉ ሶስት አማራጮች የተከፋፈሉ ሰባት ጥያቄዎችን በያዘ ሰንጠረዥ የተደገፈ ሲሆን በሠንጠረ መምህራኑ ለተሰጧቸው ሰባት ጥያቄዎች ከቀረቡላቸው ሶስት አማራጮች ውስጥ የመረጧቸውን ምላሾች በቁጥርና በመቶኛ ተተንትኗል የምላሾቹ አቀማመጥም ጥያቄዎቹ ለመምህራኑ በቀረቡባቸው የተራ ቅደም ተከተል ሳይሆን ብዙሀኑ በ ቋንቋ መማርያ ክፍል ውስጥ የአፍመፍቻ ቋንቋ መቀየር ያለው ሚና ነው በማለት ከመረጡት የቋንቋ ቅየራ ሚና ጥቂቶች እስከመረጡት ድረስ ያለ ቅደም ተከተላዊ አካሄድን የተከተለ ነው መሠጠሪኛ ፈሩ ድያ ዖራ ። ጳ ተማሪ ጊኬ ዳጳም ተማሪ ዮታንዲስ ናራቋሥ ተማሪ ሀይ ዳሪ ዳፅሪደ ፓሇናረሃ ቀረጻ መምህር ሀ በተማሪዎቹ የንግግር ልውውጥ ተማሪዎቹ ባደረጓቸው የክፍል ተግባቦቶች ለሀሳባቸው አጽንኦት ለመስጠት ወይም በሌላም ምክንያት የቋንቋ ቅየራን መጠቀማቸውን ማስተዋል ተችሏል የመምህራኑ ምላሽም ሆነ የቋንቋ ቅየራ ለተማሪዎች የሚኖረውን ሚና አስመልክቶ ከምልከታ የተገኙት መረጃዎች ሌሎች ምሁራን ከሰጡት ሀሳብ ጋር ተዛማጅነት አላቸው ለምሳሌ እዐሀሀል እንደገለጹት የቋንቋ ቅየራ የተማሪዎችን የመግባባት እድል ያሰፋል መረዳታቸውንም ከፍ ያደርጋል በማለት የጥናታቸውን ውጤት ገልጸዋል ዐ እንደ እዌ ግኝት የቋንቋ ቅየራ የተማሪዎችን የንግግር ክፍተት ይሞላል የትምህርት ተሳትፎን ይጨምራል ይዘቱን ለመረዳት ያስችላል አዳዲስ ጽንሰሀሳቦችን የመረዳት አቅምን ይጨምራል ሀ ከዚህም በተጨማሪ በሁለተኛ ቋንቋ መማርያ ክፍል ውስጥ የአፍመፍቻ ቋንቋ ቅየራ ያሉት ጠቀሜታዎች በዋናነት በሶስት እንደሚከፈሉና እነሱም የማኅበራዊ ጠቀሜታ የስነትምህርታዊ ጠቀሜታ የክፍል ቁጥጥር ጠቀሜታ እንደሆኑ እልሀህህጴኋ ህ አስፍረዋል በመሆኑም መምህራኑ የቋንቋ ቅየራን ለተማሪዎቹ የሚኖረውን ጠቀሜታ አስመልክቶ የሰጡት ምላሽ ከላይ ከተጠቀሰው ስራና ከሌሎችም በሁለተኛና በውጪ ቋንቋ ትምህርት የቋንቋ ቅየራ በሚኖረው ጠቀሜታ ዙርያ ከተሰሩ ጥናቶች ጋር የሚስማማ ነው ምዕራፍ አምስት ማጠቃለያና አስተያየት ማጠቃለያ ይህ ጥናት የጋሞኛ አፈፈት ተማሪዎች አማርኛን እንደሁለተኛ ቋንቋ በሚማሩበት ወቅት የሚታየው የቋንቋ ቅየራ ሁኔታ ሜና እንዲሁም መምህራንና ተማሪዎች ስለ ስልቱ ያላቸውን አተያይ በተመለከተ የተሰራ ነው ጥናቱ በደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መስተዳድር በወላይታ ዞን ጨንቻ ወረዳ ላይ የተሰራ ሲሆን በወረዳው በገጠርና በከተማ የሚኖሩ የአምስተኛ ክፍል የጋሞኛ አፈፈት ተማሪዎች አማርኛ በሚማሩበት ወቅት ያላቸውን የቋንቋ ቅየራ ላይ ትንታኔ አቅርቧል ጥናቱ በቅልቅል የምርምር ዓይነት የተሰራ ነው በዚህ ጥናት ትንተና የተካሄደው ከአራቱ የቅይጥ የምርምር ስልቶች አንዱ በሆነው በገላጭ ዘዴ ነው መረጃዎቹም በመቅረጸድምፅ ወምስል በተደረገ ምልከታ በቃልና በጽሁፍ ጥያቄ ከመምህራንና ከተማሪዎች ተሰብስበዋል መምህራንና ተማሪዎች ስለቋንቋ ቅየራ ያላቸውን አመለካከት መተንተን የዚህ ጥናት አንዱ ዓላማ ነው በጥናቱ በተገኘው ውጤትም አብዛዎቹ መምህራንና ተማሪዎች በቋንቋ ቅየራ ላይ አዎንታዊ አመለካከት አላቸው በተጨማሪም በሁለተኛ ቋንቋ መማር ማስተማር ውስጥ እንደ አንድ ስልት ጥቅም ላይ ሊውል ይገባል የሚል ሀሳብ እንዳላቸው የትንታኔው ውጤት ያመለክታል የተወሰኑ መምህራን ግን ቅየራ ለታላሚው ቋንቋ የሚሰጠውን ትኩረት ይቀንሳል ተማሪዎችን በመምህሩ ትርጉም ላይ ጥገኛ እንዲሆኑና ታላሜሚውን ቋንቋ ለማወቅ ጥረት እንዳያደርጉ ያደርጋል ተማሪዎች እስከመጨረሻው ይዘውት የሚዘልቁ ከሆነም አጉል ልማድ ይሆናል በማለት በክፍል ውስጥ እንደስልት ጥቅም ላይ ሊውል አይገባውም ብለው መቃወማቸውን የጥናቱ ውጤት ጠቁሟል የጋሞኛ አፈፈት ተማሪዎች አማርኛን በሚማሩበት ወቅት የሜፈጠረውን የቋንቋ ቅየራ ሁኔታን መለየት የጥናቱ ሁለተኛ ንዑስ ዓላማ ነው በምልከታ ከተሰበሰበው መረጃ ከሁለቱም ትምሀርት ቤቶች በስምንት ክፍለጊዜ ምልከታ ቅየራ ተከናውኗል አብዛኛዎቹ የቋንቋ ቅየራ በቱቱሻ ትምህርት ቤት የተመዘገቡ ናቸው እነዚህ ቅየራዎች የዲስኩር ቃላት የቃላዊና ሀረጋዊ የዓረፍተ ነገር ቅየራ ደረጃ ናቸው በከተማና በገጠር ባሉ ትምህርት ቤቶች መካከል ቅየራ የሚካሄድባቸው ደረጃዎች ላይ ልዩነት ሲኖር በከተማ በመቶ ቃላዊና ሀረጋዊ ቅየራዎች ሲመዘገቡ በገጠር የተመዘገቡት በዓረፍተ ነገር ደረጃ ያሉ ቅየራዎች ናቸው ይህ በቱቱሻ ትምህርት ቤት የታየው በዓረፍተ ነገር ደረጃ ያለው የቅየራ ሁኔታ በጣም በመብዛቱ ተማሪዎቹ በክፍል ውስጥ መስተጋብራቸው በታላሜው ቋንቋ አማርኛ በመግባባት አፍ መፍቻቸውን ከመቀላቀል ይልቅ በአፍ መፍቻቸው በመግባባት ከታላሚው ቋንቋ የተወሰኑ ቃላትን በመቀየር ነው የክፍል ውስጥ ተግባቦታቸውን የሚያከናውኑት በመሆኑም በትምህርቱ ዓላማ ተማሪዎቹ በሁለተኛ ቋንቋ በብቃት እንዲግባቡ ማስቻል ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳድራል ሶስተኛው የጥናቱ ዓላማ የተማሪዎቹ የቋንቋ ቅየራ ለቋንቋ መማር ያለውን ጠቀሜታ መግለጽ ነው ስልቱ ለተማሪዎችም የተለያዩ ጠቀሜታዎች እንዳሉት የጥናቱ መረጃዎች ይጠቁማሉ ለምሳሌ ያህል ያልገባቸውን የቋንቋ ትምህርት ይዘት እንዲጠይቁ ይረዳል በትምህርታቸው ላይ መነሳሳት እንዲኖራቸው ያደርጋል በቡድን ውይይት ላይ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ያግዛል በተመሳሳይ መልኩ ለመምህራንም አዳዲስ ጽንሰሀሳቦችን ይዘቶችንና የቃላትን ፍቺ ለማስተዋወቅ ትዕዛዝ ለማስተላለፍ የክፍሉን ሥነስርዓት ለማስጠበቅ ተማሪዎች እንዲመልሱ ለማበረታታት ትምህርቱን በጥልቀት ለማስረዳት እንደሚያስችል የትንታኔው ውጤት ያመለክታል በአጠቃላይ የቅየራቹ ሚና ስነትምህርታዊ የተማሪዎች የዲስኩር ክፍተቶች መሙላት ማኅበራዊ መስተጋብራቸውን መደገፍና የተሳካ የሀሳብ ልውውጥ እንዲኖር ማድረግ ነው አስተያየት የቋንቋ ቅየራ ግለሰቦች በመስማማት እንዲኖር ወይም ግለሰቦች በመስማማት እንዲቀር የሚያደርጉት ነገር አይደለም በዓለማችን እየተፈጠረ ባለው የልሳነ ክልዔነትና የልሳነብዙነት አውድ አማካኝነት እየተስፋፋ ያለ የማህበራዊ ግንኙነቶች ውጤት ነው በመሆኑም የስነልሳን ምሁራን በተለይም የማህበራዊ ስነልሳን ምሁራኖችና ቋንቋ ትምህርት መሳርያ አሰናጅ ባለሙያዎች አማርኛን እንደሁለተኛ ቋንቋ ለሚማሩ ተማሪዎች በሚቀረጸው ስርዓተትምህርት የአፍ መፍቻ ቋንቋ ሚና ትኩረት ሊደረግበት ይገባል መምህራን በቋንቋ ቅየራ ላይ አዎንታዊ አመለካከት ቢኖራቸውም ስልቱን እንዴትና በምን ያህል መጠን ሊገለገሉበት እንደሚገባ ያሳቸው ግንዛቤ አናሳ መሆኑን የዚህ ጥናት መረጃዎች ያሳያሉ በመሆኑም አማርኛ ቋንቋ እንደኛ ቋንቋ በሚሰጥባቸው ክልሎች ዞኖችና ወረዳዎች ያሉ የትምህርት ባለሙያዎች በየአካባቢያቸው ካሉ የከፍተኛ ተቋማት የስነልሳን መምህራን ጋር በመነጋገርና ስልቱ በቋንቋ መማር ውስጥ ስላለው ሚና ለመምህራን የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በማመቻቸት ግንዛቤ ሊፈጠርና መምህራኑም በሁለተኛ ቋንቋ ማስተማሪያ ክፍል ውስጥ እንዲጠቀሙበት ሊደረግ ይገባል ተማሪዎች በስልቱ መጀመሪያ ላይ ሲጠቀሙ ሊፈሩና በስልቱም ላይ አሉታዊ እሳቤ ሊኖራቸው ይችላል ስለዚህ መምህራን ተማሪዎች ስልቱን እንዲጠቀሙ በተለያዩ መንገዶች ሊያለማምዷቸው ይገባል መምህራን በሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት ወቅት የአፍ መፍቻ ቋንቋ ቅየራ ያለውን ዓይነተ ብዙ ጠቀሜታ ተገንዝበው እንደ አንድ የመማሪና ማስተማሪያ ስልት ሊጠቀሙበት ይገባል በመጨረሻም ይህ ጥናት ሲሰራ ተዛማጅ ጥናታዊ ጽሁፎችን ለማግኘት በተደረገው አሰሳ በርካታ ዓለማቀፋዊ ጥናቶችን ከመረጃ መረብ ላይ ማግኘት ሲቻል በሀገር ውስጥ ግን በዮሴፍ ደመቀ ከተሰራው ስራና ዮሴፍ የጠቀሳቸው አጥፔፒው ግን ካላገኛቸው ሁለት ተዛማጅ ጥናቶች ውጪ ሌላ ማግኘት አልተቻለም በመሆኑም በአሁኑ ሰዓት ዓለምአቀፋዊ ትኩረት ባገኘው የማኅበራዊ ስነልሳን ዘርፍ ሀገራችንም እንደልሳነ ብዙህ ሀገርነቷ በሰፊው ሊጠና በሚገባው ዘርፍ ላይ የተሰሩት ጥናቶች ውሱን በመሆናቸው ጥናት ማድረግ የሚሹ ሰዎች ትኩረት እንዲያደርጉበት ለመግለጽና በርካታ ሊፈተሹ የሚገቡ ጉዳዮች ያሉበት የጥናት መስክ እንደሆነ ለመጠቆም እፈልጋለሁ ዋቢዎች ዮሴፍ ደመቀ ሀሠረሪ ለፉምሙ ያፈቋ ይዕዐታሆ ፍሰ ሦማሪዎሥቻ ሳማሂኛ ፇጋር ፍኃ ሄ በዳማረሃኛኝ ሠረሪ መጎሳዕሰ ዖሚዖነሂዳምው ልሰ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Comments:


memezon

Download options | Convert to Pdf | Book of the day

© dirzon | Terms of Service | Privacy | About | Services | Contact