Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
የአማራ ህዝብን አንግልት ሊረዱ ያልቻሉያልፈለጉ የአማራ ልሂቃንን ጭምር በመሆኑ በብዙ ፈተና የተሞላ ነው አነዚህን ፈተናዎች አልፎ ከትርከትነት ተሻግሮ ስልጣን የያዘውን አማራ ጠልነት ለመሸፋፈን ከሚጠቀምባቸው ስልቶች አንዱ የሚታገለው የአማራ ገዥ መደብ ማን ነው።
ከኢትዮጵያ የሃገረመንግስትነት ታሪክ ጋር ጥብቅ የስነልቦና ቁርኝት ያለው ህዝብ ነውበመሆኑም ለምዕተ ዓመታት ከአማራ ማንነቱ ይልቅ በኢትዮጵያዊ ማንነቱ ላይ ትኩረት ያደረገ የፖለቲካ ተሳትፎ ሲያራምድ የኖረ ህዝብ ነውይህ ማለት ግን ኢትዮጵያ ባለፈችበት የታሪከ ምዕራፎች ሁሉ ልዩ ተጠቃሚነት ያለው ህዝብ ነበር ማለት አይደለምይልቅስ በሃገሪቱ የተነሱ አገዛዞች በሌሎች የሃገሪቱ ህዝቦች ላይ ያደርሱት የነበሩት በደልና ጫና ሁሉ በአማራ ህዝብ ላይም ደርሷልበመሆኑም ሌሎቹ የሃገሪቱ ህዝቦችና የአካባቢ መሪዎች የተበደሉ ሲመስላቸው በነገስታቱ ላይ ያካሂዱ የነበረው አመፅ አሁን የአማራ ከልል በተባለው ህዝብና በአካባቢው ባላባቶችም ሲደረግ የኖረ ነው የአማራ ህዝብ ነገስታቱ ያደርሱብኛል ያለውን የአስተዳደር ግድፈትብዝበዛ እና በደል በህዝባዊ ግጥሞቹና የተለያዩ ስነቃላዊ ተግባቦቶቹ ሲገልፅ ኖሯልበደሉ ከፍ ያለ ሲመስለውም ነገስታቱን የሚቃወም ግልፅ ዓመፅ ሲያካሂድ ነበር ለዚህ ቀዳሚው ተጠቃሽ አማኝ የጎጃም ገበሬዎች አማፅ ነውይህ አመፅ በሃገራችን የተለያዩ ቦታዎች ከተደረጉ አመፆች አንዱ ነው በባሌ በጌዲኦ በትግራይ ከተደረጉ አመፆች እኩል በጎጃምም የገበሬዎች አመፅ ተካሂዷልይህ ሁሉ የሚያሳየው ዛሬ በበርካታ አማራ ጠል የዘውግ ብሄርተኞች እንደሚታሰበው የነገስታቱ ስርዓት ለአማራው ህዝብ የተለየ ምቹ ፖሊሲ እንዳልነበረው ነው ከገበሬው አመፅ በተጨማሪም በሌሎች የሃገራችን ከፍሎች እንደ ካዎ ጦና ያሉ የአካባቢ ባላባቶች በንጉሰ ነገስቶች አስተዳደር ላይ ያምፁ እንደነበረው ሁሉ በአሁኑ ወቅት የአማራ ክልል ተብሎ በተከለለው አካባቢ የነበሩ ባላባቶችም ያመፁ ነበር ለምሳሌ በማይጨው ጦርነት በርካቶቹ የጎጃምየወሎ እና የየጁ መኳንንት ንጉሰ ነገስቱን በመቃወም በጦርነት አንዲሳተፉ የቀረበላቸውን ጥሪ እስከ መግፋት ደርሰው ነበርበተመሳሳይ በዛሬው የአማራ ከልል የተለያዩ አካባቢዎችን ይመሩ የነበሩ ራስደጃዝማቾች በአንድ የአማራ ማንነታቸው ህብረት ፈጥረው ሌሎችን የሚወጉ ሳይሆኑ እርስ በእርሳቸው የማያባራ ደም መፋሰስ ያስከተለ ውጊያ የሚያደርጉ ነበሩለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነው በሸዋው ንጉስ ምኒልከና በጎጃሙ ራስ ተከለሃይማኖት መካከል የተደረገው በደም አፋሳሽነቱ ወደር የሌለው የኢምባቦ ጦርነት ነው እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ኢትዮጵያ ባሳለፈችው ረዥም የታሪከ ምዕራፍ ውስጥ አማራው እንደ ህዝብ ብቸኛ አድራጊ ፈጣሪና ሁለንተናዊ ተጠቃሚ እንደሆነ አድርጎ የመውሰዱ ነገር ከሰላሳ አመት ወዲህ ያለው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ዋነኛ ማጠንጠኛ ሆኗልቆ በዚህ ስሁት አሳቤ ላይ ተቁሞ ህገመንግስት ተፅፏልበመሆኑም የትናንት ጨቋኝ ተደርጎ የተወሰደውን የአማራ ህዝብ አንደ ህዝብ ማሳደድ መግደል ማፈናቀል ንብረቱን የመንጠቁ ወንጀል ህጋዊ ማዕቀፍ አግኝቷልበመሆኑም የአማራ ህዝብ ሁለንተናዊ መከራ በህገመንግስት የተፈቀደ ተገቢ ተግባር እስከ መምሰል ደርሷልስለሆነም ሰላሳ አመት የዘለቀው በአማራ ህዝብ ላይ የሚደረገው ዘር ማጥፋትንማፅዳትን የጨመረ ወንጀል ጠያቂም ተጠያቂም የሌለው ቀጣይቱን የጠበቀ ሰንሰለታማ የወንጀል ትርዒት ሆኗል በሃገሪቱ ለውጥ መሰል ነገር በመጣ ቁጥርየዓምን ለውጥ ተከትሎ በበደኖአርባጉጉ ወዘተ የታየው አሰቃቂ የአማራ ህዝብ ፍጅት ሌላው ቀርቶ የግለሰቦችን ሞት አይነት ድንገተኛ ከስተትየአርቲስት ሃጫሉን ሞት ያስታውሷል በተከሰተ ቁጥር ሳይቀር የአማራ ህዝብ በህይወት የመኖር መብት እንደ ዋዛ አደጋ ውስጥ ይወድቃልአማራው በተወሰነለት ከልሉም ሆነ ከከልሱ ውጭ በህይወት የመኖር መብቱ ያለምንም ጠያቂና ከልካይ ይጣሳልበተለይ በኦሮሚያ ከልል አማራውን የሚጨፈጭፉ ታጣቂዎች በግልፅ ሰልጥነውበገፍ ታጥቀውያለምንም ከልካይ በተሽከርካሪ እየተንቀሳቀሱ ህፃን አዋቂ ሳይለዩ በቀንም ሆነ በሌሊት አማራ ያሉትን ሁሉ ይረሽናሉንብረቱን ይዘርፋሉ ያፈናቅላሉአማራው አማራ መሆኑ ብቻ ወንጀል ሆኖ ይህ ሁሉ በደልና መከራ ሲወርድበት ጠበቅ አድርጎ የሚጠይቅ አካል ስለሌለ በወንጀሉ የሚጠየቅም አይኖርምና የአማራው በደል እንደ ተገቢ ነገር ቀጥሏል የአማራ ህዝብ ከሰላሳ አመት ወዲህ እያስተናገደው ያለው አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰትን የጨመረ በደል ስምረት ያገኘው አማራውን ጨቋኝ አድርጎ የሚያቀርበው አስተሳሰብ ስልጣን በመያዙ ምክንያት ነውየአማራውን ህዝብ ጨቋኝ አድርገው የሚፈርጁት እነዚህ ቡድኖች ኢትዮጵያን የሰራውም አማራ ነው ብለው ያስባሉበዚህም ምክንያት ኢትዮጵያም መፍረስና ወደ ተለያዩ ዘውጎች ቅርጫነት መቀየር አልያም ፈርሳ እንደገና መሰራት ያለባት ሃገር ነች ብለው ያምናሉኢትዮጵያን በአማራ በኩል ሲጡሉየኖሩትእነዚህ አማራ ጠል የፖለቲካ ሃይሎች በህወሃት የትጥቅ ትግል ድል አማካይነት ወደ ቤተመንግስት ሲገቡ አማራን የሃገሪቱ መርገም ሁሉ መነሻ አድርጎ የሚያስበውን እሳቤያቸውን የህገመንግስትም ሆነ የሌሎች ማህበረፖለቲካዊ ደምባደምብ ማዕቀፎች ሁሉ ማጠንጠኛ አድርገዋል እነዚህ ቡድኖች ይህን ሲያደርጉ የአማራው ልሂቅ እየተፈፀመ ያለው ወንጀል ሁሉ ወደ እርሱ የተወረወረ ለዘመናት ለመንቀል የሚያስቸግር ፍላፃ መሆኑን ሊረዳና አደጋውን በሚመጥን ሁኔታ ሲታገለው አልቻለም በምትኩ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የከሳሾቹንና የአሳዳጆቹን አማራጠል መንገድ ሲያቀና የኖረእያቀና ያለ ነው ይህ የአማራ አብዛኛው ልሂቅ ወቅታዊ ተጨባጭ ሁኔታን ያለመገንዘብ አደገኛ አካሄድ የአማራን ህዝብ ከሩብ ምዕተዓመት ለበለጠ ዘመን በህይወት የመኖር መብትን ማጣትን የጨመረ ውድ ዋጋ አስከፍሏል ይበልጥ የሚያሳስበው አማራ ጠሉ አስተሳሰብ ስልጣን ከያዘበት ዘመንዓም አንስቶ እስከ ዛሬ ድረስ የአማራ ህዝብ ያለበት አደገኛ ሁኔታ የአማራ ህዝብ እንደ ህዝብ ለሰራው ታሪካዊ በደሉ የሚከፈል ተገቢ የታሪከ ማካካሻ ተደርጎ አየተወሰደ ያለ መሆኑ ነውይህን አደገኛ ሁኔታ ለመቀልበስ ከአማራ ልሂቃን የሚቀድም አካል አይኖርምስለሆነም ነገሩ ከሆነው በላይ እንዳይከፋና ጭራሽ አማራ የሚባለውን ህዝብ የሚያጠፋ እንዳይሆን መታገል የአማራ ልሂቃን እና ህዝብ ድርሻ ነው አመርቂ ትግል ለመታገል ደግሞ የችግሩን አስከፊነት በሆነው ልከ መረዳትና ችግሩን በትክከል ሊያስወግድ የሚችለውን የትግል መስመር መያዝ ያስፈልጋል የአማራ ህዝብ ማንነቱን መነሻ አድርጎ የተሰነዘረበትን አጅግ አሰቃቂ የጥፋት በትር ለመመከት በማንነቱ መደራጀት ውዴታ ሳይሆን ግዴታ መሆኑ ብዙ ማከራከሩ እያበቃ ነውበመሆኑም በርካታ በማንነታቸው የተደራጁ የአማራ ሃይሎች ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋልሆኖም የአማራውን ህዝብ ጊዜ የማይሰጥ አንገብጋቢ በደል ነቅሶ አውጥቶና የአማራ ህዝብ ዋነኛ ጥያቄዎችን በግልፅ አስቀምጦ ህዝቡን ማታገል ላይ ብዙ የሚቀር መሆኑ የሚያከራከር አይደለምይህን ከፍተት ለመድፈን የአማራ ህዝብ ያለበት ጊዜ የማይሰጥ ችግር የሚያሳስበው አካል ሁሉ ሊረባረብ ይገባልይህ ሰነድ የተዘጋጀውም ከፍተቱን በመሙላት በኩል የሚጠበቀውን ስራ ለማስጀመር ያህል ነው ሰነዱ በአሁኑ ወቅት እንዲዘጋጅ ያደረገው የወዲያው ምከንያት ደግሞ በሃገራችን በቅርቡ እንደሚካሄድ የሚነገርለት የምከክር መድረከ ላይ የአማራ ሃይሎች የሚወከሉት ተደራዳሪዎች የአማራ ህዝብ ያለበትን ችግር ግዝፈት ለማጤንና ችግሮቹን ለመፍታት ከሌሎች የፖለቲካ ሃይሎች ጋር ለመደራደር የሚረዱ መነሻ ሃሳቦችን ለመጠቆም ነው የሰነዱ አስፈላጊነት በሃገራችን ዘውግ ህገመንግስታዊ መሰረት ተሰጥቶት የፖለቲካችን ዋነኛ ማጠንጠኛ ከተደረገ ከሰላሳ አመታት በላይ አስቆጥሯልየዘውግ ፖለቲካው ዋነኛ መሰረት ደግሞ የአማራ ዘውግ ሌሎችን ዘውጎች ጨቁኗል የሚል እሳቤ ነውበመሆኑም የአማራ ህዝብ እና የአማራ ማንነት አላቸው የሚባሉ ምልከቶች ሁሉ ለአደገኛ የህልውና አደጋ ተጋልጠዋል የአማራ ህዝብ በአሰቃቂ ሁኔታ እንዲገደልና ደከሞ ያፈራውን ንብረቱን አንዲያጣ ሆኗልየማንነቱ መገለጫ የተባሉ ባህሎቹ እንዲጣጣሉአንዲወድሙና ቀጣይነታቸው አደጋ ውስጥ እንዲወድቅ ሆኗልይህ ሁሉ ሲሆን የአማራ ህዝብ በማንነቱ የመጣበትን አደገኛ ፈተና በማንነቱ ተደራጅቶ ሳይመክት ረዥም ዘመናትን አሳልፏልበዚህም ምክንያት በአማራው ህዝብ ላይ ያነጣጠሩ አደገኛ ትርከቶችን ተከትለው የሚከሰቱ አሰቃቂ ጥቃቶች የሚመከቱበት የተደራጀ ስትራቴጂ ሳይነደፍ ቆይቷል አማራው ተጠቂ የሆነባቸው መንገዶች ፈርጀ ብዙ ቢሆኑም የአማራ ህዝብ ከእነዚህ ጥቃቶች የሚድንበትን መንገድ መተለም ቀርቶ በዘውግ በተደራጀው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ አማራውን እንደ አንድ ዘውግ ወስዶ ከዘውጉ ጋር በተገናኘ የሚደርሱበት አሰቃቂ በደሎችን ለማስቆም የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች በተገቢው መንገድ ሰንዶ ማቀረቡ በአማራ ሊሂቃን ዘንድ በቅጡ ያልተሰራበት ጉዳይ ነውበመሆኑም በጣም ዘግይተውም ቢሆን በአማራው ስም የተደራጁ የተለያዩ ድርጅቶች ከልዩነታቸው ባሻገር ለአማራ ህዝብ በመቆማቸው ሳቢያ የህዝባቸውን ፋታ የማይሰጥ አንገብጋቢ መከራ ለማቃለል ሲባል የሚጋሯቸውን የአማራ ህዝብ ዋነኛ ጥያቄዎች አጠናቅረው ለማቅረብ የሚችሉበትን መድረከ መፍጠር አልቻሉም በተቃራኒው አማራው በድሎናል የሚሉት ወገኖች ከአንድ ዘውግ ሳይሆኑ አንኳን አማራውን በተመለከተ በጋራ የሚያቆማቸው በርካታ አጀንዳዎችን በፍጥነት ማቅረብ የሚቸሉበት መግባባት ላይ ከደረሱ ዘመናት ተቆጥረዋልይህ በአማራው እና አማራው በድሎናል በሚለው ልሂቅ መካከል ያለው ሰፊ የዝግጁነት ልዩነት የአማራን ህዝብ ፈተና የሚያከብድ ብቻ ሳይሆን መከራውን እያባባሰ የሚያራዝም አደገኛ ሁኔታ ነው ይህን ለማስቀረት በተለያየ ስም የሚጠሩ የአማራ ሃይሎች ከልዩነታቸው ባሻገር ቢያንስ የአማራ ህዝብን ህልውና ለማስቀጠልና አንደ ሰው ሊከበሩለት የሚገቡትን ሰብዓዊ መብቶቹን ለማስከበር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ የሚይዙት የጋራ አቋም ሊኖራቸው ያስፈልጋል ይህ ሰነድ ያስፈለገውም የአማራ ህዝብን ህልውና ለማስከበር በአማራ ሃይሎች መሃከል ሊኖር የሚገባውን የጋራ አቋም ሊያመጡ የሚችሉ የጋራ የመታገያ አጀንዳዎች እና ከተለያዩ ሃይሎች ጋር ለመደራደር የሚስቸሉ ነጥቦችን ለመጠቆም ነው በሃገራችን በቅርቡ ሁሉንም የፖለቲካ ሃይሎች የሚሳትፍ ሃገራዊ ምከከር እንደሚደረግ መንግስት ይፋ ማድረጉ ደግሞ የዚህን ሰነድ አስፈላጊነት አስቸኳይ ያደርገዋል የአማራ ህዝብ በኢትዮጵያ አብዮተኞች ዕይታ ከትናንት እስከ ዛሬ ኢትዮጵያ ረዥሙን የታሪኳን ዘመን ያሳለፈችው በዘውዳዊ አስተዳደር ስርዓት ስር ነውዘውዳዊውን አስተዳደር ለመገርሰስም ሆነ ከዛ በኋላ የመጡ ስርዓቶችን ለመቀየር ግብታዊ አብዮቶችተራዛሚ የትጥቅና ሰላማዊ ትግሎች ተደርገዋልእነዚህን ትግሎች የመሩ አብዮተኞችና ተከታዮቻቸው የሜታገሉትን ስርዓት በደሎች ሁሉ በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ ከአማራ ህዝብዘውግና ከአማራ ማንነት ጋር ያቆራኛሉአነዚህ አብዮተኞች የኋላ ኋላ ራሳቸውን ሻዕብያህወሃትኦነግኦብነግ ወዘተ አይነት ግልፅ የዘውግ ብሄረተኝነት ቀይረዋልየተቀሩት እንደ መኢሶኢሰፓኢህአፓኢጭአህአትወዝሊግ ወዘተ ያሉት ደግሞ ኢትዮጵያዊ ምልከታ ያለው ፓርቲ ይዘው ተጉዘዋልሆኖም በሁለቱም ጎራ ያሉ ታጋዮች ይነስም ይብዛ ኢትዮጵያ በፊውዳሉ ዘመን ያለፈችበት ፖለቲካዊ ችግሮች ሁሉ በአንድም በሌላ መንገድ ከአማራ ህዝብ ጋር ያገናኛሉ ኢትዮጵያ በታሪኳ ላለፈችበት ሁለንተናዊ ችግር አማራውን ሃላፊ አድርጎ የማቅረቡ አካሄድ በማታገያ ርፅዮትነት ድምፀት ሲገለፅ በሃገራችን የብሄር ጭቆናየተዛባ የብሄረሰቦች ግንኙነት ነበር የሚል ተደርጎ ይቀርባል እዚህ ላይ ጨቋኝ ሆኖ የቀረበው የአማራ ዘውግ ሲሆን ተጨቋኙ ደግሞ የተቀሩት የኢትዮጵያ ዘውጎች ናቸውአሁን ላይ የአማራ ዘውግ ተወላጆችን ከኢትዮጵያ ዳርቻ ሁሉ የሚያሳድደው አማራጠል ትርከት ውልደቱ ይህ እሳቤ ነው የዚህ አማራጠል ትርከት መሃንዲስ ደግሞ አማራው ዋለልኝ መኮንን ነውበእርግጥ የአማራጠል የዘውግ ብሄርተኝትን በኢትዮጵያ ያስጀመረችው በአፄ ምኒልከ መሪነት አሳፋሪ የሸንፈት ማቅን የተከናነበችው ጣሊያን ነች። ፆይህ በርካታ የዓለማችን ምሁራን የተስማሙበት ሃቅ ቢሆንም በሃገራችን የዘውግ ፖለቲከኞች ዘንድ ግን ኢትዮጵያ ከተፈጠረችበት ዘመን ጀምሮ አማራ በዘውግ ማንነቱ ተደራጅቶ ሌሎችን ዘውጎች እየጨቆነ ሲገዛባት የኖረች ተደርጎ ብያኔ ይሰጣልይህ ስሁት ብያኔ ኢትዮጳያን የተቀሩት የዓለም ሃገራት ካለፉበት የታሪክ ምዕራፍ የተለየ የፖለቲካ ቀመር ያላት ሃገር አድርጎ ያስባልከዚህ አልፎ ይህ አስተሳሰብ የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት የአማራ የበላይነትትምከህተኝነት ሌሎችን ለመጨቆን ሲል ራሱን የሚደብቅበት ጎሬ አድርጎ አስከ ማሰብ ይዘልቃል በመሆኑም ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነትን መዋጋት አማራን መዋጋትበግልባጩ አማራን ማሳደድማሸማቀቅ እና ከሃገራዊ ፖለቲካ ስዕሉ ገሸሽ እንዲል ማድረግ ደግሞ ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነትን ማፈራረስ አድርገው ያስባሉለዚሁም ይሰራሉበአጭር አገላለፅ አማራውን በማሳደድ ኢትዮጵያዊ ብሄርኝነትን ይዋጋሉኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነት በማፈራረስ አማራውን ከኢትዮጵያ ፖለቲካ ገሸሸ ለማድረግ ይሞክራሉ የሃገራችን የዘውግ ፖለቲከኞች ከከርስቶስ ልደት በርካታ ዘመናት በፊት በኢዛና ሃተታ ከ በርፀዩቨርክ የተገለፀውና ጥንታዊ ህልውና ያለውን የብሄረኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ዛሬ እንኳን በቅጡ መቀጣጠል ያልቻለው የአማራ ትምከህተኝነትየበላይነት ጎሬ ነው ብለው ማሰባቸው የሃገራችን ፖለቲካ በአጠቃላይ እና የአማራ ንቅናቄ በተለይ ትልቁ ፈተና ነውእነዚህ ወገኖች ሃገራዊ ስልጣን የመያዝ ዕድል ማግኘታቸው ደግሞ ፈተናውን ይበልጥ ከባድና ውስብስብ አድርጎታልአማራ ጨቁኖናል የሚሉት የሃገራችን የዘውግ ብሄርተኞች የፌደራል ስልጣን መንበር ላይ መቀመጣቸው ስሁት ሃሳባቸው የረባ ተግዳሮት እንዳይገጥመው ጉልበት ጭምር የሚጠቀሙ በመሆኑ የተሳሳተው ትርከት እንከን የለሽ እውነት መስሎ አማራውን በተለይ ማንገላታቱን ቀጥሏል የአማራ ጠል የዘውግ ብሄርተኞች የሚያምኑት አስተሳሰብ ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነትን ርዕዮትን የአማራ ትምከህተኝነት ጭንብል አድርጎ የማሰቡ ስልጣን ላይ የመውጣት በለስ ቀንቶታል ሆኖም ስልጣን ላይ መውጣቱ ስሁትነቱን አይለውጠውምየዚህ አሳቤ ስሁትነት የሚረጋገጥበት አንዱ መንገድ የአማራ ህዝብ ከልሂቃን እስከ አርሶ አደሩ ድረስ ከትህነግ ጋር የነበራቸው የአጋርነት መስተጋብር ነው እንደሚታወቀው ትህነግ በ በግልፅ አማራ ጠላቴ ነው ብሎ ማኒፌስቶ ፅፎ ትግል የጀመረ ድርጅት ነውድርጅቱ የኋላ ኋላ ይህን የ ማኒፌስቶ የሚተካ ሌላ የማታገያ ሰነድ ፃፍኩ ባለበት ሰነዱም አማራውን ሊታገሉት የሚገባ ጨቋኝ ዘውግ እንደሆነ ከመግለፅ አልተቆጠበምይህም ሆኖ የአማራ ልሂቃን እና አርሶ አደሮች ከትህነግ ጋር በትጥቅ ትግል ከመሰለፍ ጀምሮ የጦር ሜዳ ደጀን አስከመሆን በደረሰ ሁለንተናዊ ድጋፍ ቤተመንግስት እንዲገባ ረድተዋል ስልጣን ከያዘ በኋላም በግልዕ በአማራው ህዝብ ላይ የጥፋት አዋጅ አያወጀና እያስፈፀመ ባለበት ሁኔታ ጭምር የአማራ ልሂቃን ወይ እንደ ኢህዴንብአዴን ባሉ ፓርቲዎች ስር ገብቶ አብሮ በማስፈፀም ወይ በዝምታ አብረውት ተሰልፈዋል ከዚህ መረዳት የሚቻለው ለረዥም ዘመናት የአማራ ዘውግ ተኮር አሳቤ በኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ውስጥም ሆነ ለብቻው ህልውና ያላገኘ አሳቤ አንደነበረ ነውይህ ደግሞ የዘውግ ብሄርተኞች የአማራ ዘውገኝነት በረቀቀ መንገድ በኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ወስጥ አድፍጦ ኖሯል የሚሉት እሳቤ ከአውነታው የተፋታ መሆኑን ያስረግጣልምከንያቱም የአማራ የዘውገኝነት እሳቤ በኢትዮጵያ ብሄርተኝነትም ሆነ በሌላ መንገድ አድፍጦ ቢኖር ኖሮ ወያኔ ወደ ስልጣን ከመጣበት ዘመን ጀምሮ አጅግ አሰቃቂ በሆነ መንገድ አማራው በየተገኘበት ሲታደን ለማስቆም ሲንቀሳቀስ በታየ ነበር አውነታው የአማራ ህዝብ ከግለሰባዊ ማንነቱ ባለፈ ኢትዮጵያዊነትን ዋነኛ ማንነቱ አድርጎ የኖረሌላው ኢትዮጵያዊም አንደዚሁ የሚያስብ አድርጎ ሲገነዘብ ዘመናትን ያሳለፈ መሆኑ ነውአማራ ጠላቴ ነው የሚል የትግል ሰነድ ቀርፆ የመጣውን ትህነግን ለድል እንዲበቃ እስከማገዝ ያደረሰው አካሄዱም ከዚሁ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ወገን አድርጎ ከማየቱ የመነጨው የአማራ ህዝብልሂቅ ግንዛቤ ነውከሁሉም በላይ አብዛኛው የአማራ ልሂቅከተሜውም ሆነ አርሶ አደሩ ስለ ኢትዮጵያ እና ታሪኳ የነበረው ግንዛቤ ትህነግንም ሆነ የትግራይን ህዝብ የጨመረ ነበረበየአማራ ህዝብ ዘንድ ስለትህነግ የነበረው ግንዛቤ ትህነግ የወጣው ብዙውን ታሪከና ባህል ከአማራ ህዝብ ጋር ከሚጋራው ከትግራይ ህዝብ ውስጥ በመሆኑ ለኢትዮጵያዊነት ታማኝ ከመሆን ያለፈ ሌላ ጥቅምና ፍላጎት ይኖረዋል ብሎ የማያስብ ነው የዚህ ጥልቅ ዕምነት መዘዝ ነው የአማራ ህዝብ በትህነግ የደረሰበትን የከህደት መራር ፅዋ ሲጎነጭ እንዲኖር ያደረገው የአማራ ህዝብ የትህነግን አመጣጥና ወደ ስልጣን ግስጋሴ እንደ ጥንቱ የነአፄ ዮሃንስ ዘመኑ ዘይቤ አድርጎ ያስባልበቀድሞው የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች ውስጥ የአካባቢያዊ መሳፍንትሽፍቶችና የጦር አበጋዞች አመፅ የተለመደ ነበርእነዚህ አማፅያን በመጀመሪያ አመፃቸውን የሚጀምሩት በአካባቢያቸው ያሉ ሃይሎችን ዘውግ ሳይለዩ አስተባብረው ነውቀስ በቀስ ጉልበት አግኝተው የንጉሰ ነገስትነት ስለጣን መጨበጥ ከቻሉ የሚመሰርቱት አስተዳደር ግን ዲሞከራሲያዊ ባይሆንም ሁሉንም የሚያካትትበዘውግ ልዩነት ያላደረገ ነበርየአማራ ህዝብም የትህነግን ግስጋሴ ከዚህ የተለየ ሊሆን አንደሚችል ሊያስብ የሚችልበት የታሪከም ሆነ የባህል መሰረት አልነበረም በዚህም ምክንያት ትህነግ ስልጣን ከያዘ በኋላ ሲፈፅም የነበረው የመድሎኝነትና የዘረኝነት ተግባር ሁሉ በአማራው ህዝብና ሊሂቅ ዘንድ እንደ አላፊና ጊዜያዊ ሁኔታ ተደርጎ ነበር የተቆጠረው በጊዜው ለአማራው ልሂቅ ጎልቶ ይታየው የነበረው ትህነግ የመንግስቱ ሃይለማርያምን ወታደራዊ አምባገነን አስተዳደር ደምስሶ መጣሉ ብቻ ነበርና ለረዥም ዘመን ይህንኑ በማዳነቅ ላይ ተጠምዶ ቆይቷልበመሆኑም ትህነግ የተፀነሰበትን አማራን በሌሎች የሃገሪቱ ዘውጎች ሁሉ እንደጠላት እንዲታይ የማድረጉን ሁለንተናዊደባ በአደገኝነቱ መጠን ለአማራው ልሂቅ ሲታየው አልቻለም በሃገራችን ከ ዓም ጀምሮ የረበበው አማራ ጠል የዘውግ ፖለቲካ ማጠንጠኛ አማራውን ጠልቶ የማስጠላት እና የማሳጣት አካሄድ በትህነግ ፊታውራሪነት በሌሎች ደቀመዝሙርነት የተዳወረ ነው በሌላ አባባል ከ ዓም ወዲህ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ተንሰራፍቶ የተተከለው የዘውግ ፖለቲካ ዋነኛ ዓላማውና መለዮው አማራውን የተቀሩት ብሄረሰቦች አጥብቀው ሊታገሉት የሚገባበኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ሁለተኛ ተመልሶ ስልጣን መያዝ የሌለበትአያንዳንዱ እንቅስቃሴው በከፍተኛ አንከሮ መታየት ያለበት አይነተኛ ባለጋራ አድርጎ ማቅረቡ ነውእንዲህ አይነት ዓላማን ባነገበ የፖለቲካ ስርዓት ውስጥ አማራው አንደ አንድ በሃገሩ የሚኖር ህዝብ መብቱ ተከብሮለት ሁለንተናዊ ደህንነቱ ተጠብቆ ሊኖር የማይቸል መሆኑ አጠያያቂ አይደለም በህግ የፀናው የዘውግ ፖለቲካ ያመፀበት የአማራ ህዝብ አጅግ በማይመች ፖለቲካዊ ከባቢ ውስጥ የሚኖር ግዞተኛና ባይተዋር መሆኑ የአደባባይ ሚስጥር ነውበሃራችን በተተከለው አማራ ጠል የዘውግ ፖለቲካ ውስጥ አማራ መሆን ትልቅ ፈተና አዝሎ የሚመጣ ማንነት ነው የአማራው ህዝብ ይህ ሁሉ ፈተና የተደቀነበት ቢሆንም የአማራው ልሂቅ ይህን የዘውግ ፖለቲካው የደቀነበትን አደገኛ ሁኔታ ወዲያው ተገንዝቦ በአንቁላሉ መቅጨት አለመቻሉና ረዥም የቸልታ ዘመን ውስጥ መከረሙ የአማራን ህዝብ ከባድ ዋጋ አስከፍሏል እያስከፈለም ይገኛል የዘውግ ፖለቲካው ከ ዓም በአማራ ህዝብ ላይ ያደረሰው ጉዳትና የተጋረጠው ፈተና በኢትዮጵያ ከ ዓም ጀምሮ ስሩን የተከለው የዘውግ ፖለቲካ ዋነኛ ተልዕኮው ባለፉት የሃገሪቱ ረዥም የታሪከ ምዕራፎች አማራው ይዞት ነበረ ብሎ የሚያስበውን የአዛዥ ናዛዥነትየሃገር ባለቤትነት እና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ምዕራፍ መዝጋት ነውበአስተሳሰቡ ቀንቃኞችእምነት ባለፉት ዘመናት ነበረ የሚሉትን የአማራውን ሁለንተናዊየበላይነት ታሪከ ምዕራፍ መዝጋቱ ብቻ በቂ አይደለምይልቅስ አማራውን መበቀልም ትግላቸውን ይበልጥ ትርጉም ሰጭ የሚያደርግ እርምጃ እንደሆነ ያስባሉበመሆኑም አማራውን ነበረበት ከሚሉት የበላይነት አውርዶ በበቀል ለበቅ ለመግረፍ የሚያስችላቸውን በህጋዊ ማዕቀፍ የታገዘ ተበቃይ ስርዓት መዘርጋትን ዋነኛው የሃገሪቱ ዘውግ ፖለቲካ ዘይቤ አደረጉ የዘውግ ፖለቲካው አማራውን የሚበቀልበት አካሄድ ህጋዊፖለቲካዊባህልዊ ስነልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ ገፅታዎች ያሉት ነውየአማራው ህዝብ የዘውግ ፖለቲካውን የበቀል በትሮች የሚያስተናግድበት መንገድም የተለያየ ነውየአማራ ከልል ተብሎ ከተከለለው ግዛት ውጭ ያለው የአማራ ህዝብ እነዚህን የበቀል እርምጃዎች የሚያስተናግድበት መንገድ በከልሉ ከሚኖረው አማራ የባሰና የተለየ ነውበተጨማሪም በከልላቸውም ሆነ ከከልላቸው ውጭ የሚኖሩ አማሮች የሚጋሯቸው የጋራ ፈተናዎችም አሉ። የትምህርትየጤና አገልግሎት ዕድገት ወደኋላ እንዲቀር በመደረጉ ሳቢያ ለከፍተኛ ድህነትና ሁለንተናዊ ጉስቁልና እንዲጋለጥ መደረጉ ነውሌላው ቀርቶ በሃገራችን ባለው የዘውግ ስርዓት ለከልሎች የሚበጀተው በጀት መጠን የሚወሰነው በክልሉ በሚኖሩ ዘውጎች ቁጥር በመሆኑ የተወሰነው የአማራ ህዝብ የገባበት ጠፋ በሚል ሰሚን በሚያስገርም ምከንያት ቁጥሩን ሆን ብሎ ተብሎ ተቀንሷልስለሆነም የአማራ ህዝብ ከአጠቃላዩ የሃገሪቱ በጀት የሚገባውን ያህል ድርሻ እንዳያገኝ ተደርጓል ይህ ደግሞ ድሮም በቋፍ ያለውን የከልሉን የድህነት መጠን አንሮታል አራተኛው የአማራ ህዝብ ፈተና ባህሉን ለማሳደግና የታሪከ ትዝታዎቹ ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ የሚያደርገው እንቅስቃሴ ሁሉ የትምከህተኝነቱ አካል ተደርጎ ከመታየቱም ባሻገር የአማርኛ ቋንቋን ጨምሮ የአማራ ህዝብ ባህል እና ማንነት መገለጫ የተባሉ ነገሮችን ሁሉ ለማውደም የሚደረገው ጥረት ነውእንደሚታወቀው አሁን ሃገራችን የምትመራበት አማራ ጠል የዘውግ ፖለቲካ የሃገሪቱ ብሄረሰቦች ሁሉ ባህላቸውን እንዲያሳድጉ ማንነታቸውን እንዲጠብቁ መብት እንደሰጠ ይሰበካል ሆኖም ነገሩ ወደ አማራ ዘውግ ሲመጣ ልዩ መልከ ይይዛል አማራው ባህሉን ለመሳደግየታሪከ ትዝታዎቹን ለመዘከር የሚያደርገው እንቅስቃሴ በአማራ ጠል የዘውግ ፖለቲካው ቀሳውስት ዘንድ የትምከህተኝነቱአበልጣለሁ ባይነቱ መገለጫ ተደርጎ ይፈረጃል በታሪከ ትዝታው ትልቅ ቦታ የሚሰጣቸው ነገስታትን በሚዘከርበት ጊዜ የተለያዩ ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ትንኮሳዎችን ያስተናግዳል አንደ ዘውጋዊም ሆነ ሃገራዊ ምልከቶች የሚወስዳቸው እንደ ባንዲራ ያሉ መገለጫዎቹን በነፃነት ይዞ እንዳይንቀሳቀስ በአዋጀ ሳይቀር የሚከለከልበት ወቅት አለ ይህ ለሌሎች ብሄረሰቦች በገፍ የተፈቀደ ለአማራ ህዝብ ሲሆን ግን የሚከለከል የዘውግ ፖለቲካው በአማራ ማንነት ላይ የጋረጠው ስነልቦናዊ መልክ ያለው ፈተና ነው ሌላው በአሳሳቢነቱ ዋነኛ ሆኖ ሊጠቀስ የሚችለው የአማራ ህዝብ ፈተና የአማራ ከልል በውስጡ የሚኖሩ ብሄረሰቦችን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት ለመስጠት ሲል ባዋቀራቸው ልዩ ዞኖችና ወረዳዎች በኩል የሚመጣው ፈተና ነውየዘውግ ፖለቲካው አማራ የተባለውን ዘውግ የሌሎችን ባህል ባለማከበር ጨፍላቂነትበአሃዳዊነት በፀረህብረብሄራዊነት የሚከስ ነው በአማራ ጠሉ የዘውግ ፖለቲካ ምስለኔዎች የሚመራው የአማራ ከልል መንግስት ከዚህ ክስ የዳነ መስሎት የአማራ ክልል ከሌሎች የሃገሪቱ ክልሎች እጅግ በተለየ መንገድ በውስጡ ለሚኖሩ ሌሎች ዘውጎች ከፍ ያለ ራስን በራስ የማስተዳደር መብት ሰጥቷል በመሆኑም በአማራ ከልል የተለያዩ የብሄረሰብ አስተዳደር ዞኖች እና የልዩ ወረዳዎች መዋቅሮች ዘርግቷል ይህም ሆኖ አማራን በደህና ለማንሳት ተፈጥሮው የማይፈቅድለት በሃገራችን ያረበበው አማራ ጠሉ የዘውግ ፖለቲካ አማራውን በጨፍላሳቂነት በአሃዳዊነትና በፀረህብረ ብሄራዊነት ከመከሰስ ወደ ኋላ ብሎ አያውቅምየአማራ ከልል በውስጡ ለሚኖሩ ሌሎች ዘውጎች ራሳቸውን የሚያስተዳድሩባቸው የአዊየቅማንትየኦሮሞየአርጎባየዋግህምራ የብሄረሰብ አስተዳደር መዋቅሮች መዘርጋቱ የዘውግ ፖለቲካው አማራውን የሚከስበትን የጨፍላዊነት ክሱን የሚያስቀርለት ሳይሆን የዘውግ ፖለቲካው አማራውን ከልሉ ድረስ ተጉዞ የሚዋጋበት መቆናጠጫ ቦታ የሆነበት ሁኔታ አለ በአማራ ከልል የሚኖሩ እነዚህ ብሄረሰቦች በአማራው ከልል የሚተዳደሩበት ሁኔታ በሃገሪቱ ሌሎች ከልሎች ህዳጣንአብበበክ ሆነው ከሚኖሩ ዘውጎች አኗኗር እጅግ የተሻለ የመብት ይዞታ እንዳላቸው የታወቀ ነው ቢሆንም አማራውን መከሰስ የፖለቲካ ተሳትፏቸው ዋነኛ ዓላማ አድርገው የሚያስቡ የዘውግ ፖለቲካው ቀሳውስት ግን እነዚህን ብሄረሰቦች በአማራ ክልል ህዝብ እና መንግስት የተበደሉ አድርጎ በማቅረብ ከልሉን ላለመረጋጋት በሚዳርግ እንቅስቃሴ ውስጥ ጭምር እንዲገቡ ከፍተኛ ግፊተና እገዛ ያደርጋሉ በዚህ ረገድ የአዊ እና የዋግ ህምራ ብሄረሰብ አስተዳደሮች የዘውግ ፖለቲካውን ግፊት አምብዛም ጆሮ ያልሰጡ ናቸው በአንፃሩ በአማራ ከልል የኦሮሞ ዞን አስተዳደር ኦነግ የተባለው ታጣቂ እና በቅማንት አስተዳደር ዞን የቅማንት ታጣቂዎች የሚባሉ አካላት ግን የከልሉን ሰላም አደጋ ውስጥ የሚከቱ ደም አፋሳሽ የነውጥ ድርጊቶችን ይፈፅማሉ ይህን ድርጊት የሚፈፅሙት የቅማንት ሃይሎች በህወሃት ሞግዚትነት የሚንቀሳቀሱ ሲሆኑ የአጣየ ከተማን እስከማጥፋት የደረሰው የኦነግ ታጣቂ ቡድን ደግሞ ኦነግ ዘመም በሆኑ የኦሮሞ ብሄርተኞች ሁሉ ድጋፍ የማያጣ ነውለዚህ ምስከሩ በከሚሴ አካባቢ የሚንቀሳቀሰው ሃይል በፓርላማ ኦህዴድ ብልፅግናን ወከለው በተቀመጡ የብሄረሰቡ የፓርላማ ወኪሎች ሳይቀር ጥብቅና ሲቆምለት በሃገሪቱ ቴሌቪዥን የታየ መሆኑ ነውየቅማንት ታጣቂቶችም ሆኑ በከሚሴ አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የኦነግ ታጣቂዎች የዘውግ ፖለቲካው በአማራ ህዝብ ላይ ያለውን እረፍት የመንሳት ተልዕኮ የሚያስፈፅሙ ወኪሎቹ ናቸው የአማራውን ህልውና የማይፈልገው የዘውግ ፖለቲካ የአማራ ከልል የሚባለው ሰፊ ከልልና አማራ የሚባለው ማንነት ራሱ መኖሩን የሚፈልግ አይደለምከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ ስልጣን ላይ ባሉት የዘውግ ብሄርተኞች ዘንድ አማራ ከሚባለው ሰፊ ከልልና አማራ ከሚባለው ማንነት ይልቅ ጎጃምጎንደርወሎሸዋ የሚባል ማንነት እንዲኖር የመስራት ዝንባሌ አለይህ ዝንባሌ የመጣው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያበበ የመጣው የአማራ ንቅናቄ የዘውግ ብሄርተኞችን አማራውን የማሳደድ አጀንዳ የሚገዳደር በመሆኑ ስጋት ስለፈጠረባቸው ነው ይህን በአሰጊ ሁኔታ እያደገ የመጣውን የአማራ ንቅናቄ ለመገዳደር ደግሞ አማራውን በአካባቢ በታትኖ ማጥቃቱ ውጤታማ ስልት ነው ስለሆነም የቅማንት እና የኦነግ ታጣቂ ቡድኖችን ማስታጠቅና ሁለንተናዊ ድጋፍ ማድረግ አማራ ጠል የዘውግ ፖለቲካው የአማራ ከልል እንዳይረጋጋ ብቻ ሳይሆን አማራ ከልል የሚባለው ከልል ህልውናው እንዳይኖር ለመበታተን የሚጠቀምባቸው ፖለቲካዊ ጠጠሮቹ ናቸውየዘውግ ብሄርተኞቹ በአዊ እና ዋግህምራ በኩልም ተመሳሳይ የነውጥ ሃይሎችን ለማስነሳት ጥረት ያደረጉ ቢሆንም እምብዛም አልተሳካላቸውም የዘውግ ብሄርተኞች በአማራ ከልል የሚገኙ ብሄረሰቦችን ሁሉ ባለታጣቂ ለማድረግ የሚመኙበት ዋነኛው ምክንያት ትልቁን የአማራ ከልል ሲበታትኑ በአነዚህ ብሄረሰቦች ውስጥ ቅርጫ አድርገው ማስቀመጥ ስለሚፈልጉ ነውይህም ማለት የቅማንት ታጣቂዎች የሚያስፈልጉት ጎንደርን የቅማንት ከልል በማድረግጎጃምን የአገው ብሄረሰብ ግዛት በማድረግወሎንና ሸዋን የኦሮሞ በማድረግ የብሄረሰቦች ባለጋራ አድርገው የበየኑትን የአማራ ከልልና የአማራ ማንነት በማጥፋት አዲሲቱ የሚሏትን ከአማራ የበላይነት ነፃ የሆነች ሃገር ለመመስረት በምኞት ፈረስ ይቃትታሉለዚህ ትልቅ ተግዳሮት የሆነባቸው ሰፊ ግዛታዊ ከልል ባለው በአዊ አና ዋግ ህምራ ዞን አጀንዳቸውን ተቀብሎ ሊንቀሳቀስ የፈቀደ ጉልህ ታጣቂ አካል አለመኖሩ ነው የሆነው ሆኖ የአማራ ንቅናቄ ጎልብቶየጠራ መስመር ይዞ የተከፈተበትን ጥቃት መከላከል ካልቻለ የከልሉም ሆነ የአማራ ማንነት ህልውና ቀጣይነት አደጋ ውስጥ ያለ ነገር ነው ከአማራ ክልል ውጭ የሚኖሩ አማሮች የሚገጥማቸው ፈተና የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሃገራችን የዘውግ ፖለቲከኞች የአማራው ዘውግ ጨቁኖናል ከሚሉበት ምክንያት አንዱ የአማራ ዘውግ አባላት በመላ ሃገሪቱ ተበትነው መኖራቸው ነውየጉልበት ስራ ሊሰራ ወደ ከልላቸው የሄደውን አማራ ሁሉ ለመጨቆን የሄደ አድርገው ይቆጥሩታል የአማራ ህዝብ በመላ ሃገሪቱ ሊበተን የቻለበት ምከንያት በጥናት ሊረጋገጥ የሚገባው ነገር ሆኖ ከጥናት በመለስ ግን አሁን አማራ ከልል በሚባለው ቦታ ላይ ያለው ጥልቅ ድህነት ሰዎች ስራ ፍለጋ ከአካባቢያቸው ርቀው እንዲሄዱ ማድረጉየአካባቢው ድህነት የአንድ አመትን የዝናብ ማጠር መቋቋም ስለማያስችል ተደጋጋሚ ድርቅ በሚከሰትባቸው ቦታዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች ወደ ሌላ ቦታ ወስዶ የማስፈሩ መንግስታዊ መፍትሄበተለይ በደርግ ስርዓት በርካታ አማሮች በመላ ሃገሪቱ ተበትነው እንዲኖሩ ማድረጉ ነው የአማራን ነገር ሁሉ ከጨቋኝነት ትርክት ጋር የሚያገናኘው የዘውግ ፖለቲካችን ታዲያ አማራው ተቸግሮ ያደረገውን ነገርም በሆነው ልክ የመመርመር ስክነት የለውምና የአማራ ከልል ከሚባለው ግዛት ውጭ የተገኘ አማራን ሁሉ በጨቋኝነት ፈርጆ ያሳድዳል የዘውግ ፖለቲካውን ዘይቤ የቀረፁ ልሂቃን የዘውጋቸው ጥንታዊ ግዛት በአማራ ገዥዎች አስገዳጅነት ወደ ኢትዮጵያ ኢምፓየር እንዲካለል ተደርጓልየአማራ ባህልም በግድ ተጭኖበታል ብለው ያምናሉበመሆኑም በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ የኖሩበት ዘመን ሁሉ በአማራ ቅኝ ግዛት ስር የኖሩበት ዘመን አድርገው ያስባሉበመሆኑም ከክልሉ ውጭ የሚኖረው አማራ ሁሉ የአማራ ነገስታትን ቅኝ አገዛዝ ለማሳለጥ የመጣ ነፍጠኛ ነው የሚል ሰፊ ተቀባይነት ያለው ትርከት ፈጥረዋል ትርከቱ ብቸኛ እውነት ለመሆን በመድረሱ ሳቢያ ከከልላቸው ውጭ የሚኖሩ አማሮች ላይ የሚደርሰው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ምንም ተጠያቂነት የማያመጣ ተገቢ ድርጊት እስከመምሰል ደርሷልስለሆነም የአማራ ከሚባለው ከልል ውጭ ያሉ አማሮች አማራ መሆናቸውና በሌላ ከልል መገኘታቸው ብቻ ወንጀል ሆኖ በአሰቃቂ ሁኔታ ዘውግ ተኮር ጭፍጨፈ ይፈፀምባቸዋልንብረታቸው ይዘረፋልይፈናቀላሉ በታጣቂዎች ታግተው ከመገደላቸው በፊት ቁም ስቅልበዐርከበ እንዲያዩ ይደረጋልበመንግስት ስራ ተቀጥረው ያሉ የአማራ ዘውግ ተወላጆች አማራ መሆናቸው ብቻ ወንጀል ተደርጎ ከስራቸው እንዲባረሩ ይደረጋልትህነግ ስልጣን እንደያዘ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያባረራቸው የሃገሪቱ ምርጥ ምሁራን ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ሁኔታ አማሮች ናቸውትህነግ ስልጣን ላይ ውሎ ሲያድርም በመንግስት ሲቪል ቢሮከራሲ ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ የአማራ ዘውግ ተወላጆች በተጠና መልኩ ስራቸውን አንዲለቁና ለትህነግ ካድሬዎች እንዲያስረከቡ ተደርጓል ከአማራ ከልል ውጭ ሄደው ኑሯቸውን በቋሚነት የመሰረቱ የህብረተሰብ ከፍሎች ቀርቶ ለተወሰነ ጊዜ ከፍተኛ ትምህርት ለመከታተል ከከልላቸው ውጭ የሄዱ አማራ ተማሪዎች ዘውጋቸውን መሰረት ያደረገ እገታአሰቃቂ ግድያየስነልቦና ጫናን የሚያስከትሉ ማስፈራሪያዎችን ያስተናግዳሉከከልላቸው ውጭ ያሉ የአማራ ተማሪዎች ይህ ሁሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሲደረግባቸው የፌደራሉ መንግስትም ሆነ ወንጀሉ የሚፈፀምበት ከልል መንግስታት ወንጀሉን ለማስቆም ይህ ነው የሚባል እርምጃ ሲወስዱ ታይቶ አይታወቅምበአንዳንድ ክልልሎች ለምሳሌ ኦሮሚያ እና ቤኒሸንጉል ጉሙዝ ከልሎች መንግስት ራሱ ባመነው ሁኔታ የመንግስት መዋቅር ላይ ያሉ ባለስልጣናት ሳይቀሩ በወንጀሉ የሚሳተፉበት ሁኔታ አለ የእገታዝ ፖለቲካ ሰለባነት ከላይ እንደተጠቀሰው ከአማራ ከልል ውጭ የሚኖረው የአማራ ህዝብ የፊውዳሉ ስርዓት የአማራ የበላይነት ቅሪት ምልከት ተደርጎ ይቆጠራልበዚህም ምከንያት በርካታ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ያስተናግዳልበእዚህ የአማራ ተወላጆች ላይ የሚደርሰው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሁለት ምከንያቶችን ያዘለና መንታ ቱርፋት ያለው ነገር ነው አንደኛው ሰዎቹ የፊውዳሉ ስርዓት በአማራ በኩል ሃገሪቱን ሲበዘብዝ የነበረበት ጨቋኝ ስርዓት ቅሪት ተደርገው ይቆጠራሉበመሆኑም በእነሱ ላይ የሚደረገው የመብት ጥሰት ሁሉ ጨቋኙን አማራ ሰራሸ የቀድሞ ስርዓት የመዋጋት ትግል ተደርጎ ይቆጠራልና ሰፋሪወራሪቅኝ ገዥነፍጠኛ የሚል ስም ተለጥፎባቸው ይሳደዳሉይህን በማድረግ አካባቢውን ከአማራ አፅድቶ ባለቤት ለተባለው የአካባቢው ዘውግ ተወላጅ ማስረከብ ያስትላል ይህ በዘውግ ፖለቲካው ዘንድ የሃገር ባለቤትነትን ማረጋገጥ ተብሎ የሚጠራ እንደ ወሳኝ ድል የሚቆጠር ነገር ነውይህ ድል ለአማራጠሉ የዘውግ ፖለቲካ ተደራቢ ፖለቲካዊ ጥቅም አዝሎ የሚመጣ ነገር ነው ሁለተኛው አማራ ጠል የዘውግ ፖለቲካው ከአማራ ከልል ውጭ ባሉ አማሮች ላይ የሚያሳድረውን ሁለንተናዊ ጉዳት በአማራ ከልል ያለው ሰፊ ህዝብ በሚቃወምበት ጊዜም ሆነ በአጠቃላይ በዘውግ ፖለቲካው ስርዓት ላይ ተቃውሞ እንዳያነሳ የፖለቲካ ሙቀቱን የሚቆጣጠርበት ልጓም ሆኖ የሚያገለግል መሆኑ ነው በክልሉ ያለው ህዝብ ከክልሉ ውጭ ያሱ አማሮች የሆነ ቦታ ላይ የደረሰባቸውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት የመቃወም እንቅስቃሴ ሲጀምር የባሰ አንዳታስጨርሷቸው አርፋችሁ ተቀመጡ የሚለው የዘውግ ፖለቲካው ቀሳውስት ማስፈራሪያ ይሁን ማስጠንቀቂያ ወይ ምከር የማይታወቅ ነገር ይከተለላልይህ ነገር ከአማራ ከልል ውጭ ያሉ አማሮች ራሳቸውም አንድ ቦታ ስለተደረገው ግድያ ስታወሩ የእኛ ህይወት አደጋ ላይ ስለሚወድቅ ስለግድያው አታንሱ የሚል ልመና ያስከትላሉበዚህ መንገድ የዘውግ ፖለቲካው ከአማራ ከልል ውጭ ያሉ አማሮችን እንደ እገታ በመያዝ በአማራ ከልል ያለው አማራ የዘውግ ፖለቲካው በማንነቱ ምከንያት ለሚያደርስበት በደል የሚሰጠውን ፖለቲካዊ ምላሽ አንዳይኖር ይቆጣጠራሉ ማንነትን የማጣት ስጋት አማራ ከሚባለው ክልል ውጭ የሚኖረው የአማራ ህዝብ በዘውጋዊ ማንነቱ ምክንያት አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ጨምሮ ፈርጀ ብዙ ተፅዕኖዎችን ማስተናገዱ የጋረጠበትን ፈተና ለማለፍ አማራነቱን መካድንና የማያስገድለውን ዘውጋዊ ማንነት ተላብሶ መኖርን እንደ የቢቸግር አማራጭ ይወስዳልበመሆኑም በሃገራችን ህገመንግስት ለሌሎች ብሄረሰቦች በሰፊው የተፈቀደውና በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ህግጋት የተረጋገጠው የሰው ልጆች ማንነታቸውን ጠብቀው የመኖርባህላቸውን የማሳደግ መብት ከክልሉ ውጭ ላለው የአማራ ህዝብ በህይወት ከመኖር እና ካለመኖር ጋር የሚያያዝ ፈተና ይዞ የሚመጣ ነገር ይሆናል ማለት ነው ይህ ማንነትን የማጣት የግዴታ ውሳኔሌላ መዘዝ ይዞ የሚመጣ ነው በማንነት ምከንያት ላለመሞት ማንነትን የመቀየር ውሳኔው ከአማራ ከልል ውጭ የሚኖሩ አማሮች ወይ የሴሉ ወይ ቁጥራቸው በጣም አናሳ እንደሆነ አድርጎ የሚያሳይ በመሆኑ አማሮች ለወደፊቱ እንኳን በአካባቢው አስተዳደራዊ መዋቅር ህልውናቸውን በሚመጥን መንገድ መወከል አለባቸው የሚል የፍትሃዊነት ትግል ለማንሳት አስቸጋሪ የሚያደርግ መሆኑ ነውየዚህ ሁሉ ድምር ውጤት ከአማራ ከልል ውጭ የሚኖሩ አማሮች ሰብዓዊና ፖለቲካዊ መብቶች ጥሰትየስነልቦና ጉዳት ሁለንተናዊ ዋስትና የማጣት የመብት ጥሰቶች በማያቋርጥ አዙሪትበቢርህ ርሸርዩ ውስጥ እንዲቀጥሉ ያደርጋል ህብረብሄራዊ ፌደራሊዝም ያስፈለገበት ዋናው ምክንያት በአንድ አካባቢ ያሉ ህዳጣን ማህበረሰቦች የቋንቋየባህል እና ስነልቦና ማንነታቸው ብዙሃን በተባሉት በሌሎች እንዳይዳጥና አንዳይጠፋ ዋስትና ለመሰጠት ነውየፌደራል መዋቅሩ ስኬት በዋናነት የሚለካውም ከዚሁ አኳያ ነውአማራ ጠል የዘውግ ብሄርተኞች የብሄረሰቦችን መብት በማከበር የሚያንቆለጳጵሱት የሃገራችን ፌደራሊዝም ከከልላቸው ውጭ ህዳጣን ሆነው የሚኖሩ የአማራ ዘውግ ተወላጆችን ማንነት የሚድጥ መሆኑ የፌደራላዊ አስተዳደር ስርዓትን ዋነኛ ዓላማ የሳተ ያደርገዋል ፖለቲካዊ ውክልና የማጣት ችግር በሃገራችን የዘውግ ፖለቲካ አቀንቃኞች ዘንድ አሁን ያለው ዘውግ ተኮር ፖለቲካ የህዝቦችን ብዝሃነት ለማከበር ታስቦ የተዘረጋ እንደሆነይነገራልሆኖም በሃገሪቱ በሚገኙ ከልሎችያለው እውነታ የተገላቢጦሽ ነውበኢትዮጵያ ያሉ የከልል ህገመንግስቶች በአመዛኙ ከልሎችን የአንድ ዘውግ ወይም የተወሰኑ የከልሉ ባለቤት የተባሉ ዘውጎች ብቻ አምባ የማድረግ ከነባራዊ እውነታ ያፈነገጠ ተልዕኮ ያዘሉ ናቸውነባራዊው አውነታ በሁሉም ከልሎች ብዙሃን እና ህዳጣን የሚባሉ ዘውጎች የሚኖሩ መሆናቸው እንጅ በአንድ ዘውግ ብቻ የተሞላ ከልል አለመኖሩ ነው ሆኖም የኢትዮጵያ ከልላዊ ህገመንግስቶች ይህን እውነታ ባገናዘበ መንገድ የህዳጣንን መብት ጭምር ታሳቢ በሚያደርግ መንፈስ ያልተፃፉ ናቸው በመሆም በከልሎች ተጨባጭ ሁኔታ የከልል ባለቤት የተባሉ ብዙሃን ዘውጎች እና ህዳጣን ዘውጎች የተዛባ መብት አሰጣጥ የሚያመጣው ቀውስ የሃገሪቱ ፌደራሊዝም ትልቅ እንከን ሆኖ ይታያልየፌደራሊዝም ስርዓትን በዋነነት አስፈላጊ የሚያደርገው ደግሞ በአንድ አስተዳደራዊ ክልል ውስጥ የሚገኙ ህዳጣን ህዝቦች ሁለንተናዊ መብትህልውና እና ጥቅም ለማስከበር ሲባል ነው ይህ በብዙሃን እና ህዳጣን መካከል የሚታየው የተዛባ ግንኙነት ከከልላቸው ውጭ የሚኖሩ ዘውጎች ሁሉ ፈተና ቢሆንም ከከልላቸው ውጭ በሚኖሩ የአማራ ዘውግ አባላት ላይ ደግሞ ችግሩ በጣም የገዘፈ ነውየዚህ ምከንያቱ የአማሮቹ ጉዳይ ህዳጣን ከመሆናቸው በተጨማሪ የሃገሪቱን ፖለቲካ የሚዘውረው አማራጠል ትርከር ሰለባም ስለሆኑ ነው አማራ ያልሆኑ ሌሎች ዘውጎች ከክልላቸው ሲወጡ የሚገጥማቸው ፈተና በንዑስነታቸው ብቻ የሚመጣ አንጅ ትርክት የተደገፈ የጨቋኝነት ከስም የታከለበት አይደለምና ፈተናቸውም ከአማራው ፈተና ያነሰ ነውየአማራ ዘውግ ከሌሎች ዘውጎች በበለጠ ቁጥር ከከልሉ ውጭ በሆኑ ከተሞች የሚኖር መሆኑ ደግሞ ችግሩ በጉልህ ሁኔታ እንዲስተዋል አድርጎታል በኢትዮጵያ ከተሞች በርከት ያለ ቁጥር ያለው የአማራ ዘውግ ይኖራል ሆኖም በእነዚህ ከተሞች የአማራው ቁጥር የብዙሃንነትን ድርሻ ያለፈ ቁጥር ቢኖረው እንኳን በከተሞቹ የአስተዳደር መዋቅር ውስጥ ውክልና እንዲኖረው አይደረግምውከልና ሊሰጠው ቀርቶ በእነዚህ ከተሞች መገኘቱ ራሱ የጨቋኝነቱ ማስረጃ ተደርጎ የሚቀርብ ነገር ነው በአንፃሩ ያለ ከልላቸው ያሱ ሌሎች ዘውጎች በርከት ብለው በሚገኙባቸው ከተሞችም ሆነ ክልሎች ቁጥራቸውን በሚመጥን ምጥንታቨ በተሰላ ሁኔታ አስተዳደራዊ ውከልና ይኖራቸዋልለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሚሆኑት የድሬዳዋ አስተዳደር እና የሃረሬ ከልል አስተዳደራዊ ቀመሮች ናቸው እንደሚታወቀው የድሬዳዋ አስተዳደር በማንኛውም ከልል ውስጥ ያልተዋቀረ የራሱ አስተዳደር ያለው የሃገራችን ግዛት ከፍል መሆኑ በፌደራል ህገመንግስቱ እውቅና የተሰጠው ነው ይህ ማለት ድሬዳዋ የኦሮሚያም የሶማሌ ከልልም አካል አይደለም ማለት ነው ሆኖም በዚህ አስተዳደራዊ ግዛት ውስጥ የሚኖሩት የኦሮሞ እና የሱማሌ ዘውግ አባላት ቁጥር ከአማራ ዘውግ ተወላጆች ይብለጥ ይነስ በማይታወቅበት ሁኔታ አማራ ጠል የዘውግ ፖለቲካው በከተሞች ያለውን የአማራውን ድምፅ ለማፈን ሲል አስተዳደራዊ መዋቅሩ ለኦሮሞሱማሌሌሎች እንደ ቀደም ተከተላቸው የሚል የውከልና ምጥጥን ያለው አስተዳደር ዘርግቷል በተመሳሳይ በሃረሬ ከልል ከሃራሬ ዘውግ ተወላጆች በመቀጠል የኦሮሞ ዘውግ ተወላጆች የአስተዳደራዊ ምጥንታውን ተጋርተው በህገመንግስት የሃራሪዎች የተባለውን ከልል በጋራ ያስተዳድራሉ ይህ አይነቱ ምጥንታ ከከልላቸው ውጭ ለሚኖሩ በቁጠር በርካታ አማሮች የተሰራበት የኢትዮጵያ ከልል ፈልጎ ማግኘት አይቻልምአማሮች በተለያዩ ከልሎች በብዙ ቁጥር በመኖራቸው መጠን አስተዳደራዊ ውክልና ሊያገኙ ቀርቶ ጉልህ እና ነባር ብዙሃን በሆኑበት እንደ መተከል ባለ አካባቢ እንኳን ምንም አይነት የአስተዳደራዊ ውከልና ድርሻ የላቸውምበመሆኑም በአማራ ጠል የዘውግ ፖለቲካው የሚያደርስባቸውን አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚከላከሉበትወንጀሉን የፈፀመባቸውን አካል ተጠየቂ የሚያደርጉበት ፖለቲካዊ አስተዳደራዊና ህጋዊ ከለላ የለም በተለያዩ ክልሎች በብዙ ቁጥር ተበትኖ የሚኖረው የአማራ ህዝብ በሃገሪቱ ከተሞች በርከት ብሎ ይኖራልበመሆኑም የዘውግ ፖለቲካው የኢትዮጵያ ከተሞችን የዘውግ ፖለቲካው ዋነኛ ተግዳሮቶች አድርጎ ይወስዳልበሃገሪቱ ያሉ ከተሞች በዘውግ በተከለሉ ከልሎች ውስጥ የሚገኙ ቢሆኑም በአንዳንድ ከተሞች ከከልሉ ባለቤት ዘውጎች የበለጠ ቁጥር ያለው የሌላ ዘውግ ህዝቦች ይኖራሉከነዚህ ዘውጎች ውስጥ የአማራ ዘውግ አባላት በርካታውን ቁጥር ይይዛሉየኢትዮጵያን ከተሞች በአንድ ዘውግ ስር በዘውጋዊ አስተዳደር ለማስተዳደር የህዝቦቻቸው የዘውግ ስብጥር ስለማይፈቅድ የኋላ ኋላ ከተሞቹ በከንቲባ በሜመራ የከተማ አስተዳደር መዋቅር እንዲተዳደሩ ተደርጓልሆኖም ይህ መዋቅር ራሱ በዘውግ ፖለቲካው ትልቅ ተፅዕኖ ስር ከመውደቅ አልዳነም የከተሞችን የዘውግ ስብጥር ባገናዘበ መልኩ ለማስተዳደር የተዘረጋው የከተማ አስተዳደር መዋቅር በሁለት መንገድ የሚወራለትን የከተሞችን ህብረብሄራዊነት ባገናዘበ መልኩ ለማስተዳደር አልቻለምአንደኛው የከተሞቹ ከንቲባዎች በቀጥታ በዘውግ ከልሉ ፕሬዚደንቶች የሚሾሙ መሆኑ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በከተማ አስተዳደሮቹ ፓርላማዎች ውስጥ የዘውግ ኮታ በከልሉ ትዕዛዝ የሚቀመጥ መሆኑ ነውይህ ኮታ የማስቀመጥ አሰራር በመጀመሪያ የተጀመረው በኦሮሚያ ከልል ሲሆን የደቡብ ከልልም ይህን ልምድ ቀስሞ ተግባራዊ አድርጎታል በኮታ ስርዓቱ መሰረት የኦሮሞ ዘውግ ነዋሪዎች ብዙሃን ባልሆኑባቸው የኦሮሚያ ከልል ከተሞች የሚገኙ የከተማ አስተዳደር ምከር ቤቶች ፓርላማ ውስጥ ፐርሰንት ኮታ ለኦሮሞ ይሰጣሉሆኖም የኦሮሚያ ከልል ትንሽ ቆይቶ የፐርሰንት ኮታውን ወደ ፐርሰንት አሳድጓልበዚህ መንገድ የከተማ አስተዳደር መዋቅሩ ለይስሙላ በከንቲባና የዘውግ ስብጥር ባለው ካውንስል የሚመራ ነውይባልእንጅ ዞሮ ዞሮ የከተሞችን ስብጥር የማይመስል ነው ይልቅስ የዘውግ ፖለቲካው የቀመረውን በአንድ ከልል ውስጥ የከልሉ ባለቤት የተባለውን ዘውግ አድራጊ ፈጣሪነት ማስጠበቀን ያስቀጠለ ነውይህ አካሄድ በኦሮሚያ ከተሞች አማራው በአመዛኙ የብዙሃንነት ቁጥር ይዞ የሚገኝ ቢሆንም በዘውግ አስተዳደራዊ መዋቅሮች ውስጥ ወከልና ያሳጣዋልበመሆኑም በዘውግ ፖለቲካው ሳቢያ የሚመጣበትን የሰብዓዊ መብት ጥሰት መሞገትመከላከልና ማስቀረት የሚችልበት መንገድ በማጣቱ በኦሮሚያ ከተሞቸ የአማራው ዘውግ ተኮር ጥቃት እንዲቀጥል ሆኗል በአማራ ከልል ውስጥም ከከልሉ ውጭም የሚኖሩ አማሮች የጋራ ተግዳሮቶች ህገመንግስታዊ መገለል ህገመንግስታዊ ስርአት መገንባት ዲሞከራሲያዊ ሽግግር ለማድረግ ብሎም ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለመገንባት በጣም አስፈላጊና ወሳኝ ነገር ነዉህገመንግስት ከግጭት እና ከአለመረጋጋት በኋላ የሚገኝ ማህበረሰብ ግጭትን አዎንታዊ ወደሆነ ገንቢ ሃይል በመቀየር ሰላምን በማምጣት በመጠበቅና በመገንባት የሰላም ሰነድ ሆኖ ሊያገለግል ይችላልበመሆኑም ህገመንግስት የሚዘጋጅበት ሂደት ከህገመንግስቱ ዉስጣዊ ይዘት እና አፈፃፀም እኩል የሆነ ትኩረት ሊሰጠዉ የሚገባ ጉዳይ ነዉሀገ መንግስትየፖለቲካ ፓርቲዎች የድርድር ውጤት ብቻሳይሆን የህዝቡ አና ሌሎችያገባናል የሚሉ ሃይሎች ማህበራት ተቋማትና አደረጃጀቶች ትርጉም ያለዉና የነቃ ተሳትፎ ዉጤት መሆን ይኖርበታል ፖለቲካዊ ተቃርኖ ባየለበት እንደ ኢትዮጵያ ባለ ማህበረሰብ ህገመንግስት የሚዘጋጅበት ሂደት ከህገመንግስቱ ዉስጣዊ ይዘት እና አፈፃፀም እኩል የሆነ ትኩረት ሊሰጠዉ የሚገባ ጉዳይ ነዉአንድ ህገመንግስት የተረቀቀበት የተዘጋጀበት እና የፀደቀበት ሂደት የህገመንግስቱን ይዘት ስኬትና ህዝባዊ ተቀባይነት ይወስናል በተለይም ሂደቱን ጥቂት ልሂቃን የመሩት መሆኑ ወይም ሂደቱ ሰፊ ህዝባዊ ተሳትፎ የነበረበት መሆኑ ለህገመንግስቱ ህዝባዊ ተቀባይነትም ሆነ ለይዘቱ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከታል የህገመንግስት ዝግጅት አራት ደረጃዎች ያሉት ሲሆን ማርቀቅ በ መምከርህዝባዊ ዉይይትክፀቋቨዐበ መቀበል ልዐዕሀፀቨዐከ እና ማፅደቅ ህቨርበ ሲሆኑ በእነዚህ ሂደቶች ሁሉ ሁሉን አቃፊነት አሳታፊነት እና ነፃ ፈቃድ በጣም አስፈላጊ ነዉ ስለዚህ በእነዚህ በአራቱ ሂደቶች ዉስጥ ማን ተሳተፈ ማንስ በእነዚህ ሂደቶች በሁሉም ወይም በአንዱ አልተሳተፈም የሚለዉ ጥያቄ ህገመንግስቱ የማን ህገመንግስት ነዉ የሚለዉን የሚመልስ ሲሆን የህገመንግስቱ ቅቡልነትም የሚወስነዉ በዚህ ነዉከዚህ አንፃር አሁን በስራ ላይ ያለዉን ህገ መንግስት የተዘጋጀበት ሂዳት ያሳተፋቸው ተሳታፊዎች በኢትዮጵያ ያሉ የፖለቲካ ሃይሎችን ወካይነት ጉዳይ በርካታ ጥያቄዎች የሚነሳበት ነው ከደርግ ዉድቀት ማግስት ደርግን አሸንፈናል በሚል ስልጣን የተቆጣጠሩት ብሄርተኮር የፖለቲካ ቡድኖች በትህነግ ፊት አዉራሪነት የሰላም ኮንፈረንስ ያካሄዱ ሲሆን በኮንፈረንሱም ደርግን ለመጣል በትጥቅ ተሳትፎ ያደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ለኮንፈረንሱ ሲባል የተፈጠሩ ድርጅቶች በድምሩ ወደ የሚጠጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳታፊሆነዋልኮንፈረንሱን የጠራዉ አጀንዳዉን የቀረጸዉ የሽግግሩን ቻርተር ያዘጋጀዉ የኮንፈረንሱን ተሳታፊዎች ማንነት የወሰነዉና ፓርቲዎች የሚኖራቸዉን መቀመጫ የደለደለው ደግሞ ትህነግ መራሹ ኢህአዴግ ብቻ ነበር ኢህአዴግ የፖለቲካ ፓርቲዎች በኮንፈረንሱ የሚሳተፉበት ሁሉንም ያስማማ ግልጽ መመዘኛ ማውጣት እና ይህንም በገለልተኛነት የሚያስፈጽም ዲሞክራሲያዊ ተቋም ማቋቋም ሲገባዉ የኮንፈረንሱን ተሳታፊዎች ለብቻዉ ወስኗልበመሆኑም ከትህነግ ፖለቲካዊ አቋም እና የህገመንግስት ምርጫ ጋር የማይስማሙ የፖለቲካ ድርጅቶች ቡድኖች እና ማህበረሰቦች በሂደቱ እንዳይሳተፉ ተደርጓል ከተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች በተጨማሪ አብዛኛዉ የህብረተሰብ ከፍልና ባለድርሻ አካላት ማለትም የገበሬዎች ማህበርየከተማ ነዋሪዎች ማህበር የቀበሌ ማህበር የሰራተኞች ማህበር የመምህራን ማህበር የሴቶች ማህሀበር ወጣቶች ማህበር የተማሪዎች ሃኪሞች የህግ ባለሙያዎች እና ሌሎች የንግድ እና የሙያ ማህበራት የሀገሪቱን አጣ ፈንታ በወሰነዉ ኮንፈረንስ ላይ ተሳታፊ አልነበሩም ከሁሉም በላይ በጣም የሚገርመው በሃገሪቱ ህዝብ ብዛት ከመጀመሪያዎቹ ተርታ የሚጠራው የአማራ ህዝብ የሽግግሩን መንግስት ለማቋቋም በተደረገዉ በዚህ የሰላም ኮንፈረንስ ላይ እንደ ዘውግ በአንድም የፖለቲካ ፓርቲ ወይም ቡድን ያልተወከለ መሆኑ ነው በኮንፈረንሱ ለኢህአዴግ መቀመሜ ለኦነግ መቀመጫ እና ቀሪዉ መቀመጫ ድግሞ ለሌሎች ብሄር ተኮር ድርጅቶች የተመደበ ሲሆን በወቅቱ አማራን ወከሎ መቀመጫ ያገኘ አንድም ፓርቲ አልነበረም ሆኖም ይህ አማራ እንደ ዘውግ በጭራሽ ያልተወከለበት ኮንፈረንስ ከአማራ ህዝብ ፍላጎት አንፃር ምንም አይነት ጥልቅ ሰፊ እና ሁሉን አቀፍ ውይይት ሳይደረግበት የሽግግር መንግስቱን ቻርተር በማጽደቅና የሽግግሩን መንግስት በማቋቋም ተጠናቋል አዚህ ላይ ትልቅ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ቁምነገር አለየአማራው ህዝብ አንደ ዘውግ ያልተወከለበት ኮንፈረንስ የሽግግር መንግስት ቻርተር አፅድቆ የሽግግር መንግስት መስርቷልየሽግግር ቻርተሩ ደግሞ አሁን በስራ ላይ ያለውን ህገመንግስት ዋነኛ ይዘት የቀረፀ ዶከመንት ነውአማራው ባልተወከለበት መድረከ የተረቀቀውናየተረቀቀው በዲማ ኮንፍረንስ በአቶ ኢሳያስ አፈወርቂበአቶ ሌንጮ ለታ እና በአቶ መለስ ዜናዊ እንደሆነ የአደባባይ ሚስጥር ነው የፀደቀው የሸግግር መንግስት ቻርተር አሁንህገመንግስት ለሆነው ዶክመንት ዋነኛ ምንጭ በመሆኑ ነው በተመሳሳይ አማራው እንደ ዘውግ ያልተወከለበት ኮንፈረንስ የሃገራችንን ፖለቲካ አስከ ዛሬ ድረስ በአጅጉ የሚዘውሩ ጉልህ ውሳኔ ያሳለፈውን የሽግግር መንግስት ያቋቋመ ነው ይህ አማራው እንደ ዘውግ በምንም መልከ ያልተወከለበት የሸግግር ምከር ቤት ያቋቋመው የሸግግር መንግስት ከ ዓም ወዲህ ስልጣን የያዘውን አማራ ጠል የዘውግ ፖለቲካ ስር የሚያስይዙ ትልልቅ ፖለቲካዊ ተግባራትን ከውኖ መሰረታዊ ውሳኔዎችን ወስኗልየሸግግሩ መንግስት ከከወናቸው ዋነኛ የፖለቲካ ተግባራት መካከል የህገመንግስት አርቃቂ ኮሚሽን ማቋቋም ከልላዊ የአካባቢ ምርጫ አንዲካሄድ ማድረግና የህገመንግስት አጽዳቂ ጉባኤ አንዲቋቋም በማድረግ ህገመንግስቱ እንዲዘጋጅ ማድረግ ነዉበሌላ አባባል የህገመንግስት አርቃቂ ኮሚሽን የማቋቋም እና ረቂቁን ህገመንግስት አጽድቆ ህዝብ እንዲወያይበት የማድረግ የሚያከሉ ትልልቅ ፖለቲካዊ ውሳኔዎች አንዲወስን ስልጣን የተሰጠው የሽግግሩ መንግስት የህዝብ ተወካዮች ምከር ቤት አማራው አንደዘውግ በጭራሽ ያልተወከለበት ነበር በተጨማሪም የሸግግሩ መንግስቱ ቻርተር ህገመንግስቱ በሚዘጋጅበት ጊዜ ተግባራዊ መሆን ስላለባቸዉ እና ከግምት ዉስጥ መግባት ስለሚኖርባቸዉ አንኳር መርሆዎቸም ሆነ የህገመንግስት አርቃቂ ኮሚሽን አባላት እንዴት እንደሚመረጡ ምንም ያስቀመጠዉ ነገር አልነበረም ከዚህ ዉጭ በሌሎች ሀገራት አንደሚደረገዉ ህገመንግስቱ በሚረቀቅበት ሆነ በሚፀድቅበት ጊዜ ጠቅላላ ከትትል የሚያደርግ ገለልተኛ አካል አልተቋቋመም ነበር ምንም እንኳን በኮንፈረንሱ የህገመንግስት የህግ ምሁራን አና ባለሙያዎች እንዲከታተሉት የተጠቆመ ቢሆንም ኢህአዴግ ህገ መንግስቱ የህግ ሰነድ ሳይሆን የፖለቲካ ሰነድ በመሆኑ የሚያስፈልገዉ ፖለቲካዊ ከትትትል እና ቁጥጥር እንጅ የህግ ክትትል እና ቁጥጥር አይደለም በማለት ሃሳቡን ዉድቅ አድርጓል ትህነግ መራሹ ኢህአዴግ በወቅቱ ራሱም እንዳመነው ህገመንግስቱ የፖለቲካ ሰነድ ነውየትህነግ መራሹ ኢህአዴግ የፖለቲካ ዘይቤ ደግሞ አማራውን ቅጣት የሚገባው ጨቋኝና ትምከህተኛ አድርጎ ማቅረብ ነውበዚህ መንፈስ በተፃፈ ህገመንግስት በምትመራ ሃገር ውስጥ የአማራው ስቃይ ይቆማል ብሎ ማሰብ የህወሃት በአማራው ላይ ያላትን የጠላትነት አቋም መጋራት ነው ወደ ሽግግር መንግስቱ አማራን አግላይ አካሄድ ስንመለስ አማራው ያልተወከለበት የሽግግሩ መንግስት የህዝብ ተወካዮች ምከር ቤት አጠቃላይ መቀመጫ የነበረው ሲሆን ከዚህ ውስጥ ትህነግ እንደፈለገ ይዘውረው የነበረው ኢህአዴግ መቀመጫኦነግ መቀመጫ ሲኖረው ቀሪው መቀመጫ በኮንፍረንሱ ለተሳተፉ ሌሎች የዘውግ ፓርቲዎች ተሰጥቷልይህ ምከር ቤት አባላት ያሉት ተጠሪነቱ ለሽግግር መንግስቱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱ የሆነ የህገመንግስት አርቃቂ ኮሚሽን አቋቁሟል የኮሚሽኑ አባላት ስብስብ ሲታይ ሁሉም ባላቸዉ ሙያዊ ብቃት የተመረጡ ሳይሆን ለኢህአዴግ ባላቸዉ ታማኝነት የተመረጡ አንደሆኑ ግልጽ ነበር ከዚህም በተጨማሪ የረቂቅ ህገመንግስቱ አዘጋጆች ህገመንግስቱን በሚያረቁበት ጊዜ የትህነግን ዕቅድ አላማ እአና ፍላጎት እንዲያካቱ ግልጽ የሆነ ትእዛዝ እና መመሪያ እንደተሰጣቸው ዶር ነጋሶን ጨምሮ አዘጋጆቹ ራሳቸው የተናገሩት ነውሆኖም በኮሚሽኑ የተዘጋጀዉ ሰነድ በወቅቱ ሲቀርብበት የነበረዉ ትችት ስለ ህገመንግስታዊነት እና ስለዲሞክራሲ መርሆዎችና አሳቤዎች ማብራሪያ ከመስጠት ይልቅ ሰነዱ የኢህአዴግን ብሄር ተኮር ፖለሲና ፕሮግራም የሚያንፀብርቅ ብቻ ነበር የሚል ነዉ በብዙ ሀገራት እንደሚደረገዉ ህገመንግስት ከመረቀቁና ለህዝባዊ ዉይይት ከፍት ከመደረጉ በፊት ለህዝቡ ሰፊ የሆነ የስነዜጋ እና የንቃተ ህግ ትምህርት መሰጠት ይኖርበታል ምከንያቱም አብዛኛዉ ህዝብ በዚህ ዙሪያ የሚኖረዉ ግንዛቤ በጣም አነስተኛ ስለሚሆን ህዝቡ ስለህገመንግስቱ አስፈላጊነትና ወሳኝነት አዉቆ በንቃት ትርጉም ያለዉ ተሳትፎ ለማድረግ እንዲቻል ነዉበመሆኑም ህዝቡ ህገመንግስቱ ስለሚወጣበት ሂደትበህገ መንግስቱ ስለሚካተቱ አንኳር ጉዳዮች በቂ ግንዛቤ እንዲኖረዉ ለሂደቱ ተገዥ አንዲሆንና በሂደቱም ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግ የሚያስችል ግንዛቤ እንዲኖረዉ መደረግ ነበረበት ሆኖም ግን በኢትዮጵያ ዉስጥ የሽግግሩ መንግስቱም ሆነ የህገመንግስት አርቃቂ ኮሚሽንኑ የኤሌከትሮኒከስ አና ህትምት ሚዲያዎችን በመጠቀም ህዝቡ በተለይም በገጠሩ አካባቢ የሚኖረዉ ህዝብ ስለጉዳዩ በቂ ግንዛቤ እንዲኖረዉ ምንም አይነት ሙከራ አላደረገም በመሆኑም ህዝቡ የእራስን ዕድል በራስ መወሰን እስከ መገንጠል ፖስት ዘ ፈርስት ፓስት በሚባለዉ የምርጫ ስርዓት ብሄር ተኮር ወይስ መልከአምድራዊ ፌደራሊዝም ፓርላሚንታዊ ወይስ ፕሬዜዳንታዊ ስርዓት እና በሌሎች አንኳር ጉዳቾ ላይ ምንምአይነት ግንዛቤ ሳይኖረዉ ነዉ ዉይይት ለማድረግ የተሞከረዉበተጨማሪም በወቅቱ የነበሩ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከሂደቱ ራሳቸዉን በማግለላቸዉ እና የሂደቱን ተአማኒነትቅቡልነት ጥያቄ ዉስጥ በመከተታቸዉ ምክንያት ህገመንግሰቱን የማርቀቅም ሆነ የማጽደቅ ተግባር ህዝባዊ ተሳትፎ ሳይኖረዉ ኢህአዴግ በብቸኝነት የከወነዉ ተግባር እንደሆነ ነዉ በመጨረሻም አርቃቂው ኮሚሽን ትርጉም ያለዉ ህዝባዊ ዉይይት ሳያደርግ እና የኢትዮጵያ ህዝብ ፍላጎቱን በሚገባ ሳይገልጽ ህገመንግስቱን አርቅቆ ለሽግግሩ መንግስት ምከር ቤት አስረከቧል ሆኖም ግን ህገ መንግስቱ ከተረቀቀ በኋላ ሙሉ ረቂቁ ለኢትዮጵያ ህዝብ እንዲደርስ ተደርጎ ህዝቡ በረቂቅ ህገመንግስቱ ዉይይት አላደረገም የአርቃቂ ኮሚሽኑ ሰብሳቢ የነበሩት ዶር ነጋሶ ጊዳዳ በትልቁ ከሚፀፅተኝ እና ከሚቆጨኝ ነገር ዉስጥ ብለዉ ከጠቀሱት ነገር መካከል አንዱ ረቂቅ ህገመንግስቱ ከተዘጋጀ በኃላ ለህዝቡ ቀርቦ በቂ ዉይይት አለመደረጉ እንደሆነ ደጋግመዉ ገልፀዋል ይህን ሁሉ በሃገራችን ፖለቲካ ላይ ዘላቂነት ያለው ፖለቲካዊ ውሳኔ ያሳለፈው ኮንፍረንስሽግግር መንግስት ውስጥ ያልተወከለው የአማራ ህዝብ በሽግግሩ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ሆነ በሽግግር ቻርተሩ ዝግጅት ምንም አይነት ተሳትፎ አልነበረውምና የአማራ ህዝብ በሽግግር መንግስቱ ውስጥ አንዳች ድርሻ ያልነበረውሆን ተብሉ የተገለለ ህዝብ ነውበመሆኑም ህገመንግስቱን ጨምሮ በሸግግር መንግስቱ ወቅት ወጥተው እስከ ዛሬ የሃገሪቱ ፖለቲካ ዋነኛ ማጠንጠኛ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የአማራ ህዝብ የመገዛት ግዴታ የለበትም እነዚህ የአማራ ጠል የዘውግ ፖለቲካው ዋነኛ አማዳት እንዲቀየሩ መታገልም የአማራው ህዝብ ቀዳሚ ስራ ነው ለአንድ ከልል ብለን ህገመንግስት አንቀይርም ለሚለው ወቅታዊው የአማራ ጠል የዘውግ ፖለቲካው ዝንባሌ ሁነኛ መልስ የሚሆነው ባልተሳተፈበት ህግ የመገዛት ግዴታ ያለበት ከልልም ሆነ ህዝብም እንደሌለ መታወቅ አለበት የሚል ነው አማራ ጠሉ የዘውግ ፖለቲካ ለአንድ ከልል ብለን ህገመንግስት አንቀይርም ከሚለው ዘይቤው በተጨማሪ የአማራ ህዝብ በህገመንግስቱ አለመወከሉን ጠቅሶ ተገቢውን ህገመንግስታዊ ውከልና ለመጠየቅ እንዳይታገል በኮንፈረንሱ በኢህዴን በኩል ተወከለሃል የሚል ደካማ ከርከር ይዞ ይመጣል ይህ ያልሆነ ምከንያት በማምጣት አማራውን ለማግለል በጥንቃቄ የተሰራውን የድህረ ዓም ስርዓት ለማስቀጠል የሚደረግ መሟሟት ነው እንጅ ከስሙ ጀምሮ ኢህዴን በሚል ሃገራዊ ማዕቀፍ ውስጥ የተመሰረተ ፓርቲ የሃገሪቱን ህዝብ የማውቀው እንደ ዘውግ ብቻ ነው በሚል መሰረታዊ እሳቤ ላይ ቆሞ በተዘጋጀ ህገመንግስት ውስጥ ኢህዴን የሚባል ህብረብራዊ ፓርቲ የአማራን ህዝብን መወከል እንደማይችል ማወቅ ከብዶ አይደለም የኢህዴን አፈጣጠርና ማንነት ከአማራ ህዝብ ጋር ያለው ቁርኝት ይመርመር ከተባለ ደግሞ በህገመንግስቱ አማራ በኢህዴን ተወከሎ ነበር የሚለው ከርከር አማራውን ማግለል ትከከል ነው የሚለውን የአማራ ጠሉ የዘውግ ፖለቲካን ዋኛነኛ አስኳል ያረገዘ አደገኛ አሳቤ እንደሆነ ግልፅ ይሆናልኢህዴን አማርኛ ቋንቋ በሚናገሩ ሰዎች የተሞላ የህወሃትን አማራ ጠል አላማ ለማስፈጸም የተፈጠረና ፈጽሞ የአማራን ህዝብ የማይወከል አንደ ነበር የሚያጠያይቅ አይደለም በመሆኑም አማራ የሆኑ አንዳንድ ግለሰቦች በግለሰብ ደረጃ በኮንፈረንሱ ከመሳተፋቸው በቀር በሽግግሩ መንግስትም ሆነ በሽግግሩ መንግስት አማካኝነት ህገመንግሰቱን ለማርቀቅ እና ለማጽደቅ በተፈጠሩት አደረጃጀቶች ውስጥ የአማራ ህዝብ እአንደዘውግ ያልተወከለበት እና የዚህ ህዝብ ይሁንታ የሌለበት እንደሆነ ሊታወቅ ይገባል በወቅቱ የአማራ ህዝብ እየደረሰበት የሚገኘዉን ጥቃት ለመመከት በማለም የተቋቋመዉ የአማራ ህዝብ ተወካይ መአህድ እንኳን የተቋቋመዉ ኮንፈረንሱ ከተካሄደ በኋላ ነበር በመሆኑም የአማራ ህዝብ የሀገሪቱን የወደፊት እጣ ፈንታ በወሰነዉ በዚህ ኮንፈረንስ ላይ እንዲሳተፍ ባለመደረጉ ምከንያት ፍላጎቱንና ጥቅሙን ለማስከበር አልቻለም በተጨማሪም ኢህአዴግ በአማራ በኩል በሚጠላት በጥንታዊቷ ኢትዮጵያ ላይ ይዞት ለመጣዉ አፍራሽ ራዕይና አደገኛ ሴራ በተደራጀ መልኩ ተቃዉሞዉን የሚያሰማበት እድል አልነበረዉም በዚያን ጊዜ የአማራ ህዝብ ሀገሪቱን እንደገና በብሄር የማደራጀትን የህወሃትን አካሄድ አምርሮ የሚቃዎም እንደነበር ለማንም ግልጽ ሲሆን የህወሃትን ሀገር የማፍረስ ራዕይ አምርሮ በመቃወሙ እና በመታገሉ ምከንያት ከፍተኛ ዋጋ እንዲከፍል ተደርጓል በሃገራዊ ፖለቲካው ከስልጣን ድርሻ መገፋት በአማራ ከልል የሚኖሩም ሆኑ በተለያየ ምከንያት ከከልሉ ውጭ የሚኖሩ የአማራ ዘውግ አባላት በጋራ የሚያስተናግዱት ተግዳሮት ስልጣን ላይ ያለው የዘውግ ፖሰቲካ በየትም ቦታ ያለን የአማራ ዘውግ አባል ባለጋራ አድርጎ የመመልከቱ ዝንባሌ ነውይህ አስተሳሰብ በየትም ቦታ ያለ አማራ የዘውዳዊ ስርዓትን መልሶ ለማምጣት ይሰራል ብሎ ያስባል ከዚህ በተጨማሪ ከአማራ ዘውግ የተገኘ ሰው ወደ ሃገራዊ ስልጣኑ ዋነኛ መንበር ከመጣ የድሮው ስርዓት ተመልሶ መጣ ማለት ነው የሚል ሰፊ እምነት አለበመሆኑም በሃገሪቱ የአማራ ዘውግ አባላት የፌደራሉ መንግስት ዋነኛ ስልጣን ላይ መምጣት እንደሌባቸው ባልተፃፈ ህግ ስምምነት ላይ የተደረሰ እስከሚመስል ድረስ መግባባት አለ የዚህን አስተሳሰብ ሰፊ ህልውና አማሮቹ ራሳቸው ስለሚረዱት በብሄራዊው ፖሰቲካ መንበረ ስልጣን ላይ ሁለተኛ መሆንንን እንደ ዕጣ ከፍላው አድርገው ወስደዋልበሌላ አባባል የአማራ ዘውግ አባላት በዘውጋቸው ምከንያት በሃገራቸው የፖለቲካ ስልጣን ላይ የመሳተፋቸው ዕድል ተገድቧል ማለት ነው ይህ አካሄድ ለሃገሪቱ ዘውጎች ሁሉ የተሰጠውን የፖለቲካ ተሳትፎ የማድረግ መብት የሚፃረር ነውየሚብሰው ችግር ደግሞ አማራው በሌሎች ብሄረሰቦች ዘንድ የጨቋኝነት መልክ የተሰጠው ዘውግ ስለሆነ ከስልጣን ተገልሎ በቀጠለ ቁጥር ስልጣን ጠቅልለው በያዙ ዘውጎች የበቀል በትር ሊያርፍበት የሚችል መሆኑ ነው ከትግራይ ዘውግ የተነሱት የትህነግ መራሹ መንግስት ሹማምንት እና አሁን በስልጣን ላይ ያሱት የኦሮሞ ብሄር ሹማምንት በአማራው ህዝብ ላይ ያደረጉትንየሚያደርጉትን ማየት በቂ ነው በድህረህወሃት የአማራ ህዝብ የገጠሙት ፈተናዎች ትህነግ ከተፀነሰበት ከ ዓም ጀምሮ በግልፅ የአማራ ዘውግን በጨቋኝነት ፈርጆትግሉም ከአማራ ህዝብ ጋር አንደሆነ አስቀምጦ የተንቀሳቀሰ አካል ነውየኋላ ኋላ ትግል የማደርገው ከአማራ ገዥ መደብ ጋር ነው ቢልም በስልጣን ዘመኑ የበቀል በትሩን አንስቶ ሲገርፈውሲያሳድደው ሲያፈናቅለው ሲገድልና ሲያስገድለው የነበረው የአማራውን አርሶ አደር ነው ከትህነግ ከስልጣን መነሳት በኋላ የመጣው በዋናነት የኦሮሞ ልሂቃን የሚመሩት ስርዓት ደግሞ ወደ ስልጣን እንደመጣ ሰሞን በአፉ ትህነግ አማራውን ማሳደዱንበሌሎች ዘውጎች እንዲጠላ ማድረጉን የሚነቅፍ ሲሆን በሆዱ ያለውን ለማወቅ ግን ረዥም ጊዜን የወሰደ ነበርሆኖም ይህ ስርዓት እንደ ትህነግ ማኒፌስቶ ፅፎ የአማራው ዘውግ ባለጋራየ ነው አይበል እንጅ በተግባር የሚሰራው ሲመረመር ግን በአማራ ጠል ፖለቲካዊ ስነልቦና ከትህነግ ጋር አንድና ያው ፈለጉንም ተከታይ አንደሆነ አጠያያቂ አይደለምአሁን ሃገሪቱን የሚመራው ቡድን ከትህነግ አንድ ስለመሆኑ በህወሃት ዘመን አማራው ዘውግ ተኮር ጥቃቶችን ባስተናገደባቸው ከልሎች ማለትም በኦሮሚያበቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በደቡብ ከልል አሁንም ጥቃቶቹ እንደ አዲስ መቀጠላቸው ነው በአሁኑ ወቅት የአማራ ህዝብ እየደረሰበት ያለውን ዘውግ ተኮር አሰቃቂ የዘር ማፅዳትና ዘር ማጥፋት ወንጀሎችን በማህበራዊ ድረገፆች ከማዘዋወር ባለፈ በመደበኛ ሁኔታ በፓርላማና በመደበኛ የመገናኛ ብዙሃን መዘገብማውገዝመነጋገሪያ ማድረግና ተጠያቂ አካል እንዲኖር የማድረጉ ስራ አልተሞከረምጭራሽ ስለዚህ ሽፍንፍን ዘውግ ተኮር ጭፍጨፋ ማውራት ለውጥ ማደናቀፍህሀዝብን ከህዝብ ማጋጨትዘረኝነት የሚሱ የተገላቢጦሽ የሆኑ ፍረጃዎችን የሚያመጣ ሆኗል በመንግስት ስር ያለው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ነገሩን ለማጣራት አንዳንድ ሙከራዎችን ቢያደርግም ችግሩን በሆነው ልክ ያላቀረበና ቀጣይነቱን ማስቁም ያልቻለ ነው በድህረትህነግ ዘመን ለአማራው ጭፍጨፋ ትኩረት አንዳይሰጠው ያደረገው ዋናው ምክንያት የለውጥ አመራር ነኝ የሚለው ኦህዴድብልፅግና መራሹ መንግስት የሚያወራው ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝትህብረብሄራዊ አንድነትና መደመር የሚለው ፍልስፍናው በተግባር ከሚሰራው እጅግ የተለየ መሆኑ ነው የመንግስት ባለ ሁለት መልከ ተፈጥሮ በአማራ ህዝብ ላይ የሚፈፅመውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ለማስቆም በህዝቡ ዘንድ ሊኖር የሚገባውን የጠያቂነት መንገስ ገድሎታልትህነግ ስልጣን ላይ በነበረበት ዘመን በሰፊው ህዝብ ዘንድ ቢያንስ ሰብአዊ መብት እንዳይጣስ የመጠየቅየማስገደድ የአንድነት መንፈስ ነበረ አሁን ግን የመንግስት እስስታዊ ባህሪ በሚያስተዳድረው ሃገር ግዛት ስር የሚደረግን አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ማስቆም የመንግስት ትንሹ ግዴታ መሆኑንና ይህን ማስጠበቅ ያልቻለ መንግስት ተጠያቂ መሆን እንዳለበት በህዝብ ዘንድ መግባባት እንዳይኖር ከልከሏልበመሆኑም በተለይ በቤኒሻንጉል እና በወለጋ የአማራ ህዝብ በየዕለቱ የሚጎነጨውን መራራ የግፍ ፅዋ በስሜት እንኳን የሚረዳው ጠፍቷል በመሆኑም በቤኒሻንጉል እና በወለጋ የሚፈሰው የንፁሃን ደም ከሚከረፋው ይልቅ የእንጦጦ ፓርከ መገንባት የሚያስፈነድቀው በርከቷልየመንግስት ቀዳሚው ግዴታ ህዝብን መጠበቅ እንጅ ማዝናናት እንዳልሆነ ማወቅ ከባድ ባይሆንም እንደ ከባድ ነገር ብዙ አከራከሯልበሟቾቹ አማሮች ጫማ መቁም ከባድ ነገር ሆኗል አሁን በስልጣን ላይ ባለው መንግስት እስስታዊ ባህሪ ምከንያት በርካታ ለሰብዓዊ መብት መከበር ሲሞግቱ የነበሩ ግለሰቦችም ሆኑ ድርጅቶች ጭፍጨፋውን ማስቆም ላልፈለገውላልቻለው መንግስት ወግነው በተጨፍጫፊው የአማራ ህዝብ ላይ ፊት እንዲያዞሩ ሆኗልስለ ጭፍጨፋው ከተነሳም የሚወቀሰው ቸልተኛው መንግስት ሳይሆን ጭፍጨፋውን የሚቃወሙ ሰላላ ድምፆች ናቸው ከሰብዓዊ መብት ጥሰት በተጨማሪ ከትህነግ መወገድ በኋላ በተለይ በከልሉ የሚኖረው የአማራ ህዝብ የገጠመው ፈተና በከልሉ የሚደረግ ማንኛውም ነገር በፌደራል መንግስቱ በአንከሮና በጥርጣሬ የሚታይ መሆኑ ነውለአህዴድ መራሹ የፌደራል መንግስት ሱዳን ኢትዮጵያን ለመውረርትህነግ ሃገር ለማጥፋት ከሚያደርገው ግዙፍ ዝግጅት ይልቅ የአማራ ህዝብ ራሱን ለመከላከል የሚያደርገው የቢቸግር ጥረት ያሳስበዋል ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነው ለሌሎች ከልሎች የተፈቀደው የከልሎችን ወታደራዊሃይል በተደራጀ ልዩ ሃይል የማጠናከር ተግባር ለአማራ ከልል ሲሆን የበጀትን ጉዳይ እንደ ምክንያት በማንሳት የከለከለ መሆኑ ነው ይህ ተግዳሮት ሌሎች ከልሎች በበቂ ሁኔታ ልዩ ሃይል ሲያሰጥኑበኦሮሚያ ከልል አንደውም ልዩ ሃይል ቀርቶ እንደ ኦነግ ሸኔ አይነት አማ ቡድኖች እንኳን በነፃነት ሰፊ የወታደር ስልጠና ሲያደርጉበትግራይ ከልል መከላከያን የሚበልጥ የውትድርና ስልጠና ሲደረግ የአማራ ከልል ተመሳሳዩን ለማድረግ ሲሞከር በግልፅም ሆነ በስውር እንዲከለከል አድርጓልየዚህ ሁሉ ድምር ውጤት አማራ ከልልን አጥር የሌለው ቤት አድርጎታየአማራን ህዝብም ሲዘጋጅ የኖረን አደገኛ ጠላት ቁጭ ብሎ ጠብቆ መሞትን የመሰለ አማራው አይቶት የማያውቀው ውርደት ውስጥ እንዲገባ ግድ ብሎታል የፌደራል መንግስት በአማራ ከልል የሚደረገውን አንቅስቃሴ በአንከሮበጥርጣሬ የማየቱ አዝማሚያ የመነጨው ከልሉ ጠንከሮ ከወጣ አማራውን በማጥቃቱ ድል አድራጊነቱን ለሚያረጋግጠው የዘውግ ፖለቲካ ተግዳሮት ስለሚሆን ነው በመሆኑም በሌሎች ክልሎች የአማራውን ሞት ማስቆም ያልቻለው ጭራሽም አላወቅኩም የሚለው የፌደራል መንግስት የአማራ ክልል የፀጥታ ሃይሎች አማራው ወደ ሚጨፈጨፍዓፍበት ክልል ገብተው የህዝባቸውን ህይወት ለመታደግ የሚያቀርቡትን ጥያቄ መቀበል አይፈልግም የሰው ልጆችን በህይወት የመኖር መብት ማስጠበቅ የማንኛውም ህጋዊ አካል ሃላፊነት ስለሆነ የአማራ ከልል መንግስት አንዳንድ ባለስልጣናት ይህንኑ የአማራ ህዝብ በህይወት የመኖር መብት ለማስጠበቅ የሚያደርጉት አነስተኛ አንቅስቃሴ የፌደራል መንግስት በአንክሮ አይቶ ወዲያውኑ የማስቆም አርምጃ ወስዷልየአማራ ህዝብ በተለያዩ ከልሎች ለተከታታይ ሶስት አመት አሰቃቂ ጭፍጨፋ ሲደረግበት ወንጀሉን ለማስቆም ግን ተመሳሳዩን ፈጣን እርምጃ ሲወስድ አልታየም በአማራ ህዝብ ላይ ዘውግ ተኮር ጭፍጨፋ የሚያደርጉ ከልሎች ባለስልጣናትን ተጠያቂ አላደረገምየአማራ ህዝብ የሚደርስበት ዘውግ ተኮር ጭፍጨፋ መቆም አለበት በሚል የሚንቀሳቀሱ በጣም ጥቂት የአማራ ከልል ባለስልጣናትን በአንክሮ ተከታትሎ የማሳደዱን የፌደራል መንግስቱን አቋም ሁሉም የዘውግ ብሄርተኞች በፕሮፖጋንዳ የሚደግፉት ነው የአማራ ህዝብ በጉልበት በህወሃት እንደ ተወሰዱበት አምኖ እንዲመለስላቸው የሚታገልባቸውን ራያወልቃይትሁመራንመተከልንደራን የመሳሰሉ መሬቶችን አስመልከቶ የድህረትህነግ መንግስት አቋም አይታወቅምይህን አስመልከቶ ጠሚኒስትር አብይ ወደ ስልጣን እንደመጡ የወልቃይት ጥያቄ የመልካም አስተዳደር እንጅ የማንነት አይደለም ሲሉ አሁን ያለው መንግስት እነዚህን ቦታዎች በተመለከተ ከአማራ ህዝብ ይልቅ ወደ ትህነግ የተጠጋ አቋም እንዳለው ፍንጭ ከመስጠቱ ባለፈ የሚታወቅ ነገር የለም ሆኖም ትህነግ እና ጠሚው የወጡበት የኦህዴድ ብልፅግና አማራው ተስፋፊና ጨቋኝ ነው የሚሉ የአንድ ጎራ ሰልፈኞች በመሆናቸው የአማራ ህዝብ በእነዚህ ታሪካዊ ግዛቶቹ ላየ የሚያነሳውን ጥያቄ አስመልከቶ ተመሳሳይ አቋም አንደሚያራምዱ ማወቅ አይከብድም በአማራ ጠሉ የዘውግ ፖለቲካ አስተሳሰብ አማራው የሚያነሳቸው በሃይል የተነጠቁበት ግዛቶች የማስመለስና የማንነት ጥያቄዎች የተስፋፊነት እብሪት ተደርገው የሚወሰዱ ሲሆን ሌሎች ዘውጎች የሚያነሷቸው ጥያቄዎች ግን የብሄረሰቦች የነፃነት ትግል ተደርገው ይወሰዳሉበድህረትህነግ ዘመን የአማራ ህዝብ የግዛት ወሰንን በተመለከተ የፌደራል መንግስቱ ቸልተኝት የሚያሳየው ትህነግ በሃይል በወሰዳቸው መሬቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ከሱዳን ጋር በሚያዋስነው ግዛት ያለውን የአልፋሽቃ አካባቢ ላይ ጭምር ነውእነዚህን ግዛቶች አስመልክቶ መንግስት በግልፅ ለመሬቶቹ ስንል አንዋጋም አስከማለት ደርሷልጠቅለል ተደርጎ ሲታይ በድህረ ትህነግ ዘመን ወደ ስልጣን የመጣው አስተዳደር ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝትን በአፉ የዘውግ ብሄርተኝነትን በተግባሩ እያስኬደ ለመቀጠል የሚያስችለው የማደናገር እና የማሳመን ርዐክየህ ከ ርዐክህበር የተባለ የፖለቲካ ቀመርን ይዞ መምጣቱ ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነትን አጥብቆ የሚወደው የአማራ ህዝብ በኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ሽፋን ተጠቅልሎ የመጣበትን የህልውና አደጋ አንዳይገነዘብ አድርጎታልበተጨማሪም በድህረ ትህነግ ስልጣን ላይ የወጣው አህዴድ መራሹ ሃይል አገነባዋለሁ የሚለው ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝት ካለም ዋነኛ መልኩ አማራጠልነት እንደሆነ መረዳቱ ኢትዮጵያ ሲሉት ብቻ ለሚበቃው ለአማራው ልሂቅ እጅግ ከብዶ ይገኛልየዚህ ዋናው ምከንያቱ የአማራ ህዝብ የኢትዮጵያ ብሄርተኝነትን አንግቤያለሁ የሚል አካልን በቀላሉ የማመን ዝንባሴ ስላለው ነው ትህነግን የተካው ስርዓትም ይህን ጠንቅቆ ስለሚረዳ የአማራን ህዝብ የሚወደውን የኢትዮጵያ ስም በመጥራት በህልውናው ላይ ያንዣበበውን አደጋ ጭምር እስከማይረዳ ድረስ አደናግሮ በአማራው ላይ የከረመውን ግልፅ ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ለመታገል ሲል እንኳን አማራው በአንድ ላይ እንዳይቆም አድርጎታልበመሆኑም የዘውግ አቻዎቻቸው ሶስት አመት ሙሉ በግፍ ሲጨፈጨፉ የሚያዩ የሚሰሙ አማሮች ጭፍጨፋውን በማድረግም ሆነ ባለመከላከል የሚያሳልጠውን ኦህዴድ መር መንግስት ከኦሮሞ ሊሂቃን በበለጠ ሲደግፉ ይስተዋላል ይህ የአማራ ልሂቃን በአስገራሚ ሁኔታ ስልጣን ላይ ላለው መንግስት የሚያሳዩት ጠንካራ ድጋፍ አማራው ሲጨፈጨፍ ማስቆም የማይፈልገውንየአማራውን እንግልት እንደ ትግል መልስ የሚቆጥረውንአማራጠል ኢትዮጵያን ለመገንባት ጎንበስ ቀና የሚለውን ኦህዴድብልፅግና መር ስርዓት የአማራ ስርዓት እስከማስባል ደርሷልይህ በሌላ ከልል በተለይ በኦሮሚያ ከልል ቄሮ ታግሎ ባመጣው ድል የአማራ ስርዓት ተመሰረተ በማለት አማራው ሌላ ጭፍጨፋ እንዲካሄድበት ያደረገ አደገኛ ሁኔታን ፈጥሯል በኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ፓርቲዎች ማዕቀፍ ውስጥ የአማራን ህዝብ ጥያቄ መመለስ ያልተቻለው ለምንድን ነው። ከህ የአዋጁ ተዛማጅ ትርጉም የአማራ ልሂቃንን ትንሹንም ትልቁንም መፍጀቱ በፍጥነት መከናወን ያለበት ነገር ነው ይህ ካልተደረገ የሚጠብቀን ነውጥ ነው ከዚህ አዋጅ የምንረዳው ትልቅ ቁምነገር ኢትዮጵያን ቅኝ ለመግዛትለማዳከምና ለመበታተን ቀድሞ አማራውን መፍጀትና ማዳከም በጣሊያን ተጀምሮ ለሃገራችን የዘውግ ብሄርተኞች የተላለፈ ቀመር መሆኑን ነውይህ ነገር የሚያስረዳን ሌላ ትልቅ ቁምነገር የአማራ ህልውና በእጅጉ ከኢትዮጵያ ህልውና ጋር የተሳሰረ ታሪካዊ መሰረት ያለው መሆኑ ነውየአማራ ንቅናቄ ለኢትዮጵያ ብሄርተኝነት አጋዥና አዳኝ ይሆናል እንጅ የሚጋጭ ነገር እንደሌለው የሚከራከረው የአማራ ንቅናቄ ወቅታዊ እሳቤ ተጨባጭ ታሪካዊ ድጋፍ ያለው ሙግት ነውበመሆኑም ይህ የግራዚያኒ አዋጅ የያዘው ቁምነገር በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው የአማራ ልህቃን ዘንድ አማራውን ከመሳደድ ለማስቆም ሲባል በግድ የተገባበትን የአማራ ንቅናቄ መደገፍ ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነትን መከዳት ወይም ለድርድር ማቅረብ ተደርጎ የሚወሰደውን ነገር የአላዋቂ ስጋት ያደርገዋል የአማራ ንቅናቄን መገንባትመደገፍና ማበረታታት ኢትዮጵያን መከዳት ነው ብሎ ከማሰብ ይልቅ ታሪካዊ ዳራዎችን አይቶ አካሄድን ማስተካከል ለአማራ ህዝብ መከራ መቆምም ሆነ ለኢትዮጵያ ህልውና ቀጣይነት ዋነኛውን ሚና የሚጫወት አካሄድ ነውይህን ለማጤን ደግሞ የአማራ ንቅናቄ እንዲፈጠር ያደረጉ አስገዳጅ ሁኔታዎችንአፍጥጠው የመጡ አደጋዎችና የአማራ ንቅናቄን ተፈጥሮ መርምሮ ማወቅ ያስፈልጋልየአማራ ብሄርተኝነት አንዲፈጠር ያደረጉት ምከንያቶች ደግሞ የብሄርተኝቱን ተፈጥሮ በእጅጉ ይወስናሉ የአማራ ህዝብ ለሰላሳ አመት የቆየበት ዘውግ ተኮር ጥቃትና አሁንም በአስፈሪ ሁኔታ ያንዣበበትን ተጨባጭ አደጋ ምከንያት አድርጎ ህልውናውን ያገኘው የአማራ ንቅናቄ ዋና ዓላማው አማራው በዘውጉ ተለይቶ የሚደርስበትን የህልውና ስጋት መቀልበስ ነውስለዚህ የአማራው ንቅናቄ ራስን የመከላከል ተከላካይ ንቅናቄ አንጅ ሌሎችን በጠላትነት ፈርጆ ለበቀል የመነሳሳት ወይም በሃገሪቱ ዋነኛ የስልጣን ቦታዎች ላይ የአማራ ዘውግ መቀመጥ አለበት የሚል ቅንጦት መሰል ጉዳይ አይደለምበተጨማሪም አማራውን ኢላማ ያደረገው ጥቃት መነሻው አማራን በማጥፋት ኢትዮጵያን መበታተን የሚለው የጣልያን አጀንዳ በመሆኑ አማራውን መታደግ ኢትዮጵያንም ከመታደግ ጋር የሚገናኝ አንጅ ኢትዮጵያን የማጥፋት ወይም የመከዳት ተልዕኮ የተሸከመ አይደለምየአማራ ንቅናቄ ከኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነት ጋር ይጋጭ ዘንድ ተፈጥሮውም አይፈቅድም የሆነው ሆኖ የአማራ ንቅናቄ አስፈላጊነቱ ከ ሚሊዮኑ የአማራ ህዝብ ህልውና አስፈላጊነት ጋር የሚተሳሰር ሆኗልከላይ በተደጋጋሚ እንደ ተገለፀው የአማራ ህዝብ በትርከት ላይ የተመሰረተ የጥላቻ ዘመቻ የተዘመተበትበህገመንግስት የፀና አደጋ የተጋረጠበት እና ስልጣን በያዘ አካል ጭምር የሚደገፍ የህልውና ስጋት የተጋረጠበት ህዝብ ነው የአማራ ንቅናቄ ይህን ስጋት መከላከልመቀልበስና ህልውናን የማስጠበቅ እንቅስቃሴ ነው በመሆኑም የአማራ ንቅናቄ ነፃአውጭ ግንባር መስርተው ከኢትዮጵያ ለመገንጠል አንደሚያልሙ ግራዘመም ብሄርተኝነቶች ያለ ተፈጥሮ ያለው አይደለምይልቅስ የአማራ ንቅናቄ ትግልን ግድ ያደረገው የአማራ ህዝብ በህይወት የመኖር መብትን መነጠቅን የጨመረ የህልውና አደጋ የተጋረጠበት መሆኑ ነውበመሆኑም የትግል ዘይቤውም በህልውናው ላይ የተቃጣውን አሰቃቂ ህይወት የሚቀማ አደጋ መከላከል በመሆኑ ባህሪው የተከላካይነት ነውበህይወት የመኖር መብቱን በተጨባጭ የተነጠቀ ህዝብ ራሱን መከላከል የሚያስችል የተከላካይነት ትግል ማድረጉ ደግሞ ህጋዊ ብቻ ሳይሆን ሞራላዊም ድጋፍ ያለው ተግባር ነው የአማራ ንቅናቄ ትግል ሁለት መንታ ተፈጥሮ ያለው ነውየመጀመሪያው በአማራ ህዝብ ላይ የተጋረጠውን ህልውናን የማጣት አደጋን መከላከልን ያለመ የተከላካይነት መልክ ያለው ፎበክህትግል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የአማራን ህዝብ ህልውና አደጋ ላይ የጣለውን አማራጠል ትርከት መቀልበስ ህ የሚያስችል አይነት ተፈጥሮ ያለው ትግል ነው የአማራ ህዝብ የመጣበትን ትርከት አዘል ግልፅ አደጋ እና በቀን ተቀን ህይወቱ እያስተናገደው ያለውን ዘውግ ተኮር ጥቃት ለመቀልበስ በዘውጉ ተደራጅቶ የሚያደርገው ትግል በማንኛውም ማህበረሰብ የሚስተዋል ተጠባዊ መልስርከክ እንደሆነ ታዋቂው የፈረንሳይ ፈላስፋ ፉኮት ይገልፃልይህን ተከትሎም የመቀልበስ እንቅስቃሴ አውድጸህ ሀርህ ይፈጠራል የአማራ ህዝብም በዓለም ላይ ካሉ ህዝቦች የተለየ ተፈጥሯዊ አወቃቀር የለውምና የተጋረጠበትን ግልፅ አደጋ የመቀልበስና የመከላከል ትግል ውስጥ ገብቷል የቆየውን ትርከት ለመቀልበስ በሚደረግ የአንድ ማህበረሰብ የትግል ጉዞ ውስጥ ዋነኛ ምዕራፍ የሚሆነው ትግሉን የሚያደርው ማህበረሰብ አንድ አሰባሳቢ የጋራ ማንነት ያለው መሆኑን ማስረገጥ ነውይህ ንድፈ ሃሳብ በአማራ ህዝብ ሁኔታ ሲታይ በአማራነቱ እየተሳደደ ያለው ኢትዮጵያዊነቱ ላይ ብቻ ትኩረት ሰጥቶ የኖረውአንዳንዴም አማራ የሚባል ማንነት የለም ሲባል የነበረው ህዝብ አማራ የሚባል ለመጠቃቱ ምከንያት የሆነ አሰባሳቢ ማንነት ያለው በመሆኑ ላይ እንዲግባባ ማድረግ ነው እንዲህ በማድረግ አማራነት ተመሳሳይ የጋራ የታሪከ ትዝታ አንድ አይነት አሁናዊ ስጋትዕድልና የወደፊት እጣ ፋንታ ያለው ህዝብ መጠሪያ ማንነት መሆኑ ላይ መግባባት ላይ መድረስ ነው የተከላካይነት ተፈጥሮ ያለው የአማራ ንቅናቄ የአማራን ህዝብ ከጥቃት የሚታደጉ ህጋዊና ፖለቲካዊ ማዕቀፎች በሃገሪቱ እንዲዘረጉ የማድረግ መዳረሻ ያለው ቀላል የማይባል ትግል የሚፈልግ የቤት ስራ ያነገበ ትግል ነው የአማራ ህዝብ በሃገሪቱ ዳርቻ በሰፊው ተበትኖ የሚኖር መሆኑ ደግሞ ትግሉን ከበርካታ የሃገሪቱ ፖለቲካዊ ሃይሎች ጋር መነጋገርንና መደራደርን የሚጠይቅ ውስብስብ ያደርገውልሌላው የአማራ ንቅናቄ ትግል ትርከትን የመቀልበስ መልከ ያለው ሲሆን ፖለቲካዊ መሰጠት ብቻ ሳይሆን ምሁራዊ ምርምሮችን አድርጎ የታሪከን አውነተኛ ገፅ ማሳየትን የሚጠይቅየብዙ የአማራ ሃይሎችን ርብርብ የሚፈልግ ትግል ነውወቅታዊውን የአማራ ንቅናቄ ትግል ከሌሎች ብሄርተኞች ትግል የተለየ አስቸጋሪ ገፅታ እንዲኖረው የሚያደርገው ይህ ነባሩን ተረከ የመቀልበሱ ትግል ነው ከአማራ ንቅናቄ ውጭ ያሉ የሃገራችን ዘውግ ብሄርተኝነቶች ትግላቸውን የሚያደርጉት በሰፊው ተነግሮ ተቀባይነት ባገኘ ትርከት ላይ ቆመው ሲሆን የሚቀለብሱት ሌላ ትርከት ደግሞ የለምበአንፃሩ የአማራ ንቅናቄ ነባሩን ትርክት የመቀልበስ ከባድ ትግል ይጠብቀዋልበተጨማሪም ነባሩን ትርከት ከመቀልበሱ ጎን ለጎን አዲስ የማታገያ ትርከት መፍጠር ይጠበቅበታልነባሩን አማራ ጠል ትርከት የመቀልበሱ ስራ አማራው እንደ ህዝብ የተሰጠው የጨቋኝነት መርገም በታሪክ አውነተኛ ገፆች ያልተፃፈ የሃሰት ከስ መሆኑን አስረግጦ ለማስረዳት ምሁራዊ ጥናቶችን ማድረግን ጨምሮ በርካታ የህዝብ ግንኙነት ስራዎችን መስራትን ይጠይቃል ከዚህ ጎን ለጎን ደግሞ አሁን ሃገራችን ያለቸበት ተጨባጭ ፖለቲካዊ ሁኔታ በአማራ ህዝብ ላይ የጋረጠውን አደጋ በሚያንፀባርቅ መልኩ አዲስ የማታገያ ትርከት ወደ ትግሉ ሜዳ ማምጣት ችላ የማይባል የቤት ስራ ነውበተመሰረተና ብዙ ዘመን ባስቆጠረ ትርከት ላይ ተመስርቶ ትግል ማድረግና በተጨባጭ ያለውን ፖለቲካዊ ሁኔታውን የሚያንፀባርቅ አዲስ ትርክት አስተዋውቆ በህዝብ ዘንድ እንዲሰርፅ አድርጎ የትግልን ግቦች ማሳካት ሁለንተናዊ መሰጠትን እና ትኩረትን የሚጠይቅ ነገር ነው የአማራ ንቅናቄ አማራውን ለተጠቂነት የዳረገውን የዘውግ ብሄርኞች ተረከ ለመቀልበስ ከመታገሉ ባሻር የህልውና አደጋ ላጠላበት የአማራ ህዝብ ማታገያነት ወቅቱን የጠበቀ የማታገያ ትርክት ሲያስተዋውቅ አይታይም ሆኖም አሁን የአማራ ህዝብ ካለበት ሁለንተናዊ ሁኔታ በመነሳት የማታገያ ትርከት ቀርፆ ማስተዋወቅ የአማራ ሃይሎች ትልቅ የቤት ስራ ነውይህም ከትህነግ መውደቅ በኋላ የመጡ አዲስ ፖለቲካዊ ተለዋዋጮችን በቅጡ ማጤንን ይፈልጋል በትህነግ ልሂቃን በሚመራው ስርዓት ውስጥ የነበረው ሁኔታ አማራውን በጨቋኝነት መውቀስና ማሳደድ ላይ ያተኮረ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን ራሷን ስሟን ለመጥራት እንኳን ያለመፈለግ ዝንባሌ የሚያሳይ አካሄድ ነበር ይህ አማራውም ሆነ ሌላው ህዝብ በግልጽ የሚረዳው የትህነግ አቋም በመሆኑ ኢትዮጵያ እንደ ሃገር እንድትቀጠል ይፈልግ የነበረው ህዝብ ሁሱ ትህነግን እንደ ሃገር ጠል አደገኛ ቡድን በመቁጠር ለውድቀቱ ተባብሮ ሰርቷል ከትህነግ ውድቀት በኋላ የመጣው ኦህዴድብልፅግና መራሹ አስተዳደር በመሰረታዊ ተፈጥሮው እንደ ትህነግ ዘወግ ተኮር ነውይህ ቡድን የኢትዮጵያን ቀጣይነት የሚበይነውም ለኦሮሞ ዘውግ ልሂቃን በምትሰጠው የስልጣን ድርሻ ነው ሆኖም ትህነግን ያስጠላውን ኢትዮጵያን የማጣጣል አካሄድ አሻሸሎ ጭራሽ የኢትዮጵያ ጠበቃ በመሆኑ ረገድ ከአማራ የበለጥኩ ነኝ ለማለት የሚቃጣው ሆኖ ታይቷልለዚህ አንድ ማሳያው ጠሚ አብይ ስልጣን ላይ በወጡ ሰሞን ወደ ባህርዳር ተጉዘው የአማራ ወጣቶችን ባናገሩበትመድረከ የአማራ ዘውግ ተኮር ንቅናቄ ማደግ አንደሚያሳስባቸው የገለፁበት ሁኔታ ነው ተጨማሪ መጥቀስ ካስፈለገ ኢትዮጵያዊነት ሱሴ ነው የሚለው የአቶ ለማ መገርሳን ንግግር እማኝ ማድረግም ይቻላል ከጅማሬው የለማ ቡድን ይባል የነበረው ይህ ቡድን በኦሮሞ ፖለቲከኞች ዘንድ ባልተለመደ ሁኔታ የኢትዮጵያዊ ብሄርኝነትን አጀንዳ ቀዳሚ አድጎ መምጣቱ በርካታ የአማራ ልሂቃንን ግራ ቀኝ ሳያገናዝቡ በጭፍን የለውጥ አመራር የተባለው ቡድን ደጋፊዎች አደረጋቸው ጊዜ እየገፋ ሲሄድ ይህ የለውጥ አመራር የተባለ ቡድን ሊመሰርታት የሚመኛት ኢትዮጵያ አማራውን እንዴት አድርጋ የምታስተናግድ ነች የሚለው ገሃድ አየወጣ መጣ ለዚህ ወሳኝ ጥያቄ መልስ ለማግኘት ለውጥ መጣ ከተባለ ወዲህ በአማራው ህዝብ ላይ የደረሰውን ያላባራ ጭፍጨፋ ለማስቆም ኢትዮጵያን አወዳለሁ የሚለው አዲስ አስተዳደር ምን እርምጃዎችን ወሰደ የሚለውን ማሰብ ነውለዚህ ጥያቄ የሚሰጠው መልስ የለውጥ አመራሩ እገነባታለሁ የሚላት ኢትዮጵያ ከትህነግ በባሰ አማራውን የምታሳድድየሞት የጣር ጩኸቱን እንደ ተዛባ ታሪከ ማስተካከያ የምትወስድአማራ መሆንን ቅጣት የሚገባው ወንጀል አድርጋ የምትወስድ መሆኗን ያሳያልየአማራው ንቅናቄ ለማታገያነት ሊያስተዋውቀው የሚገባው አዲስ ትርክትም መሰረቱን ማድረግ ያለበት እዚህ ላይ ነው የለውጥ አመራር ነኝ የሚለው ስልጣን ላይ ያለው አህዴድ መራሽ ቡድን የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ጠበቃ ነኝ ማለቱ ከአማራ ህዝብ አምነት ጋር የማይጋጭ ስለሆነ ተቀባይነት ያለው ነውሆኖም ይህ አመራር የሚላት ኢትዮጵያ አማራውን አንዴት የምታይና የምታስተናግድ ነች የሚለው የአማራ ንቅናቄ ለአማራ ህዝብ ሊያስተዋውቀው የሚገባው አዲስ የማታገያ ትርከት መሰረታዊ ነጥብ መሆን አለበትይህም ማለት አማራው የኢትዮጵያን ስም ከጠራ ጋር ወዲያው አብሮ መንጎዱን ትቶ ለረዥም ዘመን ሲከፋፋ ለኖረው ለአማራው ህዝብ እንዴት ያለች ኢትዮጵያ ነች የምትመሰረተው የሚለውን መጠየቅምበተግባር ከሚደረገው ድርጊት ተነስቶ ብያኔ መስጠትና የትግል አካሄዱን ማስተካከል አማራጭ የሌለው ነገ ዛሬ ሳይባል መተግበር ያለበት የፖለቲካ አተያይ ነው የአማራ ብሄርተኝነት ትግል ውስንነቶች የአማራ ንቅናቄ አዲስ እንደመሆኑ መጠን ውስንነቶች አያጡትምየመጀመሪያው ውስንነቱ በዚህ ጎራ የሚታገሉ ሃይሎች ፖለቲካዊ ግባቸውን በህዝባቸው ዘንድ ለማስረፅ የሚሰሩት ስራ አጥጋቢ አለመሆኑ ነውበዚህም ሳቢያ አማራው በህልውና ስጋት ውስጥ በመሆኑ ላይ ከመስማማት በቀር የአማራ ንቅናቄን የሚደግፉ አካላት የትግል ግባቸውን ጥርት አድርጎ በማወቁበማሳወቁ ረገድ ብዙ የሚቀራቸው ነገር አለ ሁለተኛው ውስንነቱ ከኢትዮጵያ ሃገረመንግስት ጋር ያለው መስተጋብር ምን እንደሆነ ማስቀመጥ ያልቻለ መሆኑ ነውበሃገራችን የሚንቀሳቀሱ ሌሎች ግራ ዘመም ብሄርተኞች ቀደም ሲል መገንጠልን የሚጠይቁየነበረ ቢሆንም አሁን በኢትዮጵያ ሃገረመንግስት ውስጥ ሲኖሩ እንደ ዘውግ ሊሟሉላቸው የሚፈልጓቸውን ጥያቄዎች መናገር የሚችሉ ናቸውወደ አማራ ንቅናቄ ሲመጣ ግን አማራ ከኢትዮጵያዊነት ባሻገር እንደ ዘውግ ከሃገረመንግስቱ የሚፈልጋቸውን ጉዳዮች እንደ ኢትዮጵያዊ ከሚጋራቸው ነገሮች በተለየ መንገድ ማቅረብ አልቻለምይህ የአማራ ህዝብ ከኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነት ጋር ከነበረው ጥብቅ ቁርኝት የመነጨ ነው ሶስተኛው ውስንነት የአማራ ህዝብን በተለየ ሁኔታ የሚያንገላቱ ትርከት ተኮር ችግሮችን በጥራት ነቅሶ አውጥቶ ወደ ትግሉ ሜዳ ከማውጣት ይልቅ የአማራ ህዝብ ችግር የሌሎችም የሃገራችን ዘውጎች ችግር የሆነ አድርጎ ማቅረብ ይስተዋላልየአማራ ዘውግ ከሌሎች ህዝቦች ጋር በጋራ የሚያስተናግዳቸው ችግሮች አንዳሉ ባይካድም የአማራ ህዝብ በዘውግ ማንነቱ የሚያስተናግደው ተግር ግን በአይነቱ የተለየየከበደ መሆኑ የሚያከራክር ጉዳይ አይደለም ስለዚህ የአማራ ህዝብ ከሌሎች ህዝቦች ጋር የሚጋራቸውን ችግሮች ጨቋኝ ዘውግ ተብሎ ከመፈረጁ የተነሳ ከሚገጥሙት የብቻ ችግሮቹ ለይቶ ማቅረብ ያስፈልጋል በአራተኛነት ሊነሳ የሚችለው የአማራ ንቅናቄ እንከን ተባብሮ መስራት ላይ ያለው ውስንነት ነውማንኛውንም የፖለቲካ ግብ ለማሳካት የተለያዩ አካላት ትብብር ያስፈልጋልየአማራ ንቅናቄ ዋነኛ ግቦችን ለማሳካትም ከፖለቲካ ፓርቲዎች በተጨማሪ የሲቪከ ማህበራትመገናኛ ብዙሃንበትግሱ አስፈላጊነት የሚያምኑ ታዋቂ ግለሰቦችምሁራን ወዘተ መሳተፍ አለባቸውእአነዚህ ወገኖች በትግሉ አካሄድ ላይ ልዩነቶች ቢኖሯቸውም በግቡ ላይ ተመሳሳይ አቋም የሚኖራቸው በመሆኑ ተባብረው መስራታቸው እጅግ አስፈላጊ ነው በአማራ ንቅናቄ ትግል ላይ ግን ተባብሮና ተደጋግፎ መስራቱ ብዙ ርቀት የሚቀረው ሲሆን አንዳንዴ እንደውም ከመተባበር ይልቅ መነቃቀፍና መጠላለፍ የሚስተዋልበት ጊዜም አለከዚህ ሲብስ ደግሞ ለትግሉ ተብሉ የተሰበሰበን ንብረት ለግል ጥቅም አውሎ ህዝብን በትግሉና በመሪዎቹ ተስፋ አንዲቆርጥ የሚያደርግ አጋጣሚም ታይቷል ግለሰቦች ትግሉ ለከቆመለት አላማ ስኬት ይልቅ የግል ተከለስብዕናቸውን ወደመገንባቱ ቁልቁለት የሚሄዱበት ሁኔታም ያጋጥማል ኢህዴንብአዴንአዴፓየአማራ ብልፅግና እያለ የመጣው የአማራን ህዝብ ለመወከል ሳይሆነ ለመቅጣት ዓላማ ሲባል በአማራ ህዝብ ጠላቶች ተቦከቶ የተጋገረውን ፓርቲ ሌላው የአማራ ንቅናቄ ፈተና ነው የዚህ ፓርቲ አመራሮችም ከድሮ እአስከዘንድሮ አማራውን ሲያስገርፉ የኖሩ እንደሆኑ የታወቀ ነገር ነውእነዚህን ለአማራው ስቃይ ግድ ብሏቸው የማያውቁ ለመጣው ሁሉ ተላላኪ አመራሮችን እውነተኛ ታጋይ አስመስሎ ማቅረብ አነሱ በቀደዱለት የመንደር ዘውገኝነት ቦይ በመፍሰስ አማራ ተብሎ በጅምላ የሚገደለውን ህዝብ በአማራነቱ ተደራጅቶ እንዳይታገል ጎጃምጎንደርወሎሸዋ በሚል በመንደር ለመከፋፈል መሞከር የአማራ ንቅናቄ ትልቅ ፈተና ነው ሌላው የአማራ ንቅናቄ ችግር በዘውጉ ምከንያት የሚደርስበትን ችግር በዘውግ ተደርጅቶ ለመታገል ለትግል ከተሰለፈ በኋላ በመንግስት በኩል ከልብም ይሁን ከአንገት በላይ ስለ የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ስለተወራየአብረን እንስራ ጥያቄ ስለቀረበና መጠነኛ የስልጣን ማጋራት ስራ ስለተሰራ ብቻ ለትግሉ ዋነኛ ምከንያት የሆኑ የአማራ ህዝብ አንገብጋቢ ጥያቄዎችን ችላ ብሎ መንግስትን የሚያስደስቱ የትግል መስመሮች ላይ መሰማራት ነውይህ የአማራ ንቅናቄ ደጋፊውችን በአጅጉ ተስፋ ያስቆረጠ እንከን ነው እንደ ዘውግ የሚያቀርበውን ጥያቄ እና እንደ ኢትዮጵያዊ ሃገረመንግስትን ለማስቀጠል ያለበትን ሃላፊነት ለይቶ አለማየት አንዱ የአማራ ንቅናቄ እንከን ነውየፖለቲካ ትግልን ለማሳካት የጨዋታውን ህግ ጠንቅቆ ማወቅና በህጉ መሰረት መንቀሳቀስ የፖለቲከኛ የመጀመሪያው ጥበብ ነው በአሁኑ ወቅት በሃገራችን ያለው የፖለቲካ መንፈስ የዘውግ ብሄርተኝነትን ዋነኛ ማጠንጠኛው ያደረገ በመሆኑ የኢትዮጵያ ሃገረመንግስት ቀጣይነት የሚወሰነውም ሃገረ መንግስቱ ለዘውጎች ጥያቄ በሚሰጠው መልስ አርኪነት ላይ ነው በመሆኑን በአሁኑ የሃገራቸን ፖለቲካዊ ሁኔታ ማንኛውም የህዝብ ጥያቄ የሚጠየቀውም የሚመለሰውም በዘውግ በኩል ነው በሌላ አባባል የአሁኑ የፖለቲካ ዘይቤ መጫወቻ ህግ የኢትዮጵያ ሃገረመንግስት ቀጣይነት አንዲኖረው ዘውጎች የሚያነሱት ጥያቄ በተገቢው መንገድ መመለስ አለበት የሚል ነው የአማራ ልሂቃን ደግሞ ይህን ህግ ገልብጠው የሚረዱት ሁኔታ ይበዛል ይህም ማለት የአማራ ሃይሎች በአብዛኛው የትግል መስመራቸው የአማራ ንቅናቄን ተመርኩዘው የአማራ ህዝብ አንደ ዘውግ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች ከማስተጋባት ይልቅ ጥያቄዎቹ አንዲመለሱ ጠንከር አድርጎ መጠየቅ የኢትዮጵያን ሃገረ መንግስት ቀጣይነት አደጋ ላይ ሊጥለው ይችላል በሚል የአማራ ህዝብን ጥያቄዎች ለማቅረብ ዳተኝነት ያሳያልበዚህም ሳቢያ የአማራ ህዝብ ሌላው ቀርቶ በህይወት የመኖር መብት ጥያቄዎቹን እንኳን ነገሬ ብሎ የሚያያቸው ጠፍቷል የአማራ ህዝብ አንደ ዘውግ የሚደርስበትን በደል የሚታገሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ እምነት ለማሳደር ዳተኛ መሆኑ ሌላው የአማራ ንቅናቄ የተፈለገውን ያህል እንዳይራመድ እንቅፋት የሆነ እንከን ነው በቅርቡ በሃገራችን በተደረገው ምርጫ የአማራ ንቅናቄ ዋነኛ መሪ የሆነው አብን በክልሉ ያገኘው የድምፅ መጠን አነስተኝት የአማራ ንቅናቄ በእጅጉ ሊሰራበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑን አመላከቶ ያለፈ ነውበአርግጥ የአማራ ህዝብ በምርጫው እምብዛም አምነት እንደሌለው ለምርጫው ለመመዝገብ የወጣው የህዝብ ቁጥር አናሳነት ጠቋሚ ነው ከምዝገባው ባሻገር የምርሜው ውጤትም የገዥው ፓርቲ እጅ የሌለበት ነው ብሎ ማሰብ አይቻልም ሆኖም የምርጫውን ውጤትየአማራ ህዝብ በፀጋ የተቀበለው መሆኑ ከበአዴን ለአማራ ህዝብ ያለመቆም ተፈጥሮ ጋር ሲደመር የሚነግረው ነገር አለ ይህ የምርጫ ውጤት የአማራ ህዝብ የአማራ ብልፅግናን እንደሚወድ የሚያሳይ አይደለም ይልቅስ የአማራ ብልፅግናን ባለመምረጡ ከብልፅግና መንግስት ሊመጣበት የሚቸልውን በቀል ለመከላከል ሲል ያደረገው የቢቸግር ምርጫ አንደሆነ መገመት ይቻላልሆኖም ይህ የአማራ ህዝብ ባለጋራን የመለማመጥ መፍትሄ ያልሆነ መፍትሄ ነውምከንያቱም የብልፅግና መንግስት የቆመበት ርዕዮት ዋነኛ ማጠንጠኛ አማራ ሌሎችን ዘውጎች ሲጨቁንሲበዘብዝሲገዛ የኖረ በቀል የሚገባው ህዝብ ነው የሚል ሲሆን ለትግል የተሰማራበት ዋነኛ ዓላማ ደግሞ አማራውን መበቀል ነው ይህ ትህነግ ዘመን በአፍ ሲነገር የነበረ በብልፅግና ዘመን ደግሞ በተግባር አየተተገበረ ያለ ጉዳይ ነው የፖለቲካ ስራ ድርድር ማድረግና ሰጥቶ በመቀበልም ይገለፃል ስለሆነም ማንኛውም የፖለቲካ ቡድን በፖለቲካዊ ጉዞው የሚደራደርባቸው ጉዳዮች ቢኖሩም የተፈጠረበትን የትግል ዓላማ ለድርድር የሚያቀርብ ብልህ ፖለቲከኛ የለምቀድሞ ኢህአዴግ አሁን ብልፅግና የተባለው ከዋለልኛዊ የዘውግ ብያኔ የተነሳው አሁንም ስልጣን ላይ ያለው ጎራየአማራ ብልፅግናን ጨምሮ አማራውን የመበቀል ተግባር በምንም ነገር ለድርድር የማያቀርቡት ዋነኛው የፖለቲካ ህይወት ግባቸው ነውስለዚህ የአማራ ህዝብ ብልፅግና ፓርቲን መምረጡ ይህ ቡድን ለአማራ ህዝብ ያለውን ፅይታ ቀይሮ የአማራን ህዝብ በወዳጅ አይን እንዲያየው አያደርገውምየአማራ ህዝብ ትንሽ ትልቅ ሳይል መረዳት ያለበት የብልህ አካሄድ ይህ ነው የዘውግ ፖለቲካው አንዴት እንደሚያየው። ርዐ ነው በዚህ የሞት ምልከት ላይ ደግሞ ትምክህተኛየድሮ ስርዓት ናፋቂሰፋሪ ቅኝ ገዥ የሚሉ ክብረነከና አሸማቃቂ ቅጥያዎች ተጨምረውበት ነው የአማራ ሃይሎች የሚያደርጉት ሃገራዊ ምከከርና ድርድር የአማራን ህዝብ በጅምላ በጨቋኝነት ፈርጆ የሚንቀሳቀሰው አማራ ጠል ትርከት በአማራ ህዝብ ላይ የጋረጠውን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ መሆን አለበትይህን ገቢራዊ ለማድረግ ደግሞ ትርከቱ ራሱ ልከ አለመሆኑን ግልፅ አድርጎ ማሳየት ያስፈልጋልለዚህ የመጀመሪያው አማራ ጠሉ ትርከር አእታገለዋለሁ የሚለው የአማራ ገዥ መደብ ማንእንደሆነ ግልፅ አንዲያደርግ አበከረው መጠየቅ አለባቸው ሁለተኛው ጉዳይ የምንታገለው የአማራ ህዝብን ሳይሆን ገዥ መደቡን ነው የሚለው አካሄድ ራሱ ሆን ተብሎ ለማደናገር የሚደረግ እንጅ በገቢር ትግላቸው የሚያደርጉት ከአማራ ደሃ ህዝብ ጋር እንደሆነ ተጨማጭ ማስረጃን ጠቅሶ ማስረዳት ያስፈልጋል ይህ ተጨባጭ ማስረጃ ከቱ የበደኖአርባ ጉጉቁንቁፍቱአሶሳ የአማራ ጭፍጨፋ እስከ ዛሬው ወለጋቤኒሻንጉል ጉራፈርዳ ድረስ እየተገደለ አየተሳደደ እየተጨፈጨፈ ንብረቱ እየተቃጠለ ያለው ደሃው አማራ መሆኑ ነው ከዚህ በተጨማሪም ነፍጠኛትምክህተኛሰፋሪ ቅኝ ገዥ የሚሉ የአማራው የመገደያ ስሞች በህግ አንዲታገዱ ማድረግም የድርድሩ አካል መሆን አለበትከ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በኢትዮጵያ አራቱም ማዕዘን ዘር ተኮር ጭፍጨፈ የተደረገበት የአማራ ህዝብን ለአሰቃቂ የግፍ ሞትመፈናቀልየንብረት ውድመት ተጠያቂ አካል እንዲኖር የሚሰራ ልዩ የወንጀል ምርመራ ፍርድቤት እንዲቋቋምና ለተጎዳው ህዝብ ካሳ እንዲከፈል መጠየቅ የአማራ ሃይሎች ድርሻ ነው በሃገራችን የታሪክ በደልና ቁርሾ እንዳለ መናገር የፖለቲካችን ዋነኛው መለያ ነው ሆኖም ይህ ንግግር አማራውን በዳይ አድርጎ የሚያቀርብ ነው እንጅ አማራው ከ ዓመት ወዲህ በተለይ በዘውጉ ተለይቶ የደረሰበት እጅግ አሰቃቂና ፈርጀ ብዙ በደል ይቅርታ ሊጠየቅበት እንደሚገባ በደል ሲቆጠር አይስተዋልምፎህ የሆነበት ዋናው ምከንያት አሁን በሃገሪቱ የረበበው አስተሳሰብ አማራው ተገቢውን ቅጣት አገኘ እንጅ ተበደለ ብሎ መቀበል ስለማይፈልግ ነውሁለተኛው ምከንያት አማራው እንደ ዘውግ ተለይቶ በሚደርስበት በደል በከፍተኛ በደልና ሰቆቃ የኖረ ቢሆንም ይህን በተገቢው መንገድ ጠቅሶ የሚሟገትለት አካል ባለመኖሩ ነውአሁን የአማራ ብሄርተኝነት ሃይሎች ለድርድርም ሆነ ለምከክር በሚቀርበበት ጊዜ ይህን የአማራውን በደል እንደ ዋዛ የማየቱን ዝንባሌም ሆነ የማድበስበስ ነገር ለማስቆም መታገል አለባቸው ህገመንግስታዊ ማሻሻያን መጠየቅ አሁን በሃገራችን በስራ ላይ ያለው ህገመንግስት የተፃፈበት መንፈስ የሃገሪቱ ዘውጎች አማራ በሚባል ዘውግ ጭቆናና ብዝበዛ ስር የነበሩ ናቸው የሚል ነውአማራው በሌሎች ዘውጎቾቸ ኪሳራ ሲጠቀም የኖረ ዘውግ እንደሆነ በህገመንግስቱ አርቃቂዎች ዘንድ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷልበመሆኑም በሃገራችን በስራ ላይ ያለው ህገመንግስት በመግቢያው የሚጀምረው በሃገራችን ባሉ ዘውጎች መካከል የተዛባ ታሪካዊ ግንኙነት ነበረ ብሎ ነው ይህ የተዛባ ግንኙነት አለ የሚለው እሳቤ ሲብራራ መዛባቱ የተፈጠረው አማራውን ተጠቃሚ ሌሎችን ተጎጅና ተጨቋኝ ባደረገ ሁኔታ ነው የሚል እሳቤ ያዘለ ነው ይህ አሳቤ ከዓም ጀምሮ በሃገራችን ስልጣን ላይ ያለው አስተሳሰብ ዋነኛ የፖለቲካ ዘይቤ ነው በመሆኑም በሃገራችን በተለያዩ ማዕዘኖች በአማራው ህዝብ ላይ የሚደረገው አሰቃቂ ጭፍጨፋየንብረት ዝርፊያመፈናቀል ሁሉ ህገመንግስታዊ መሰረት ያለውን የተዛባ ታሪካዊ ግንኙነት የማስተካከል ትከከለኛ እርምጃ ተደርጎ ይቆጠራልበመሆኑም የአማራ ሃይሎች በሚያደርጉት ትግል ውስጥ ገና ከመቅድሙ ጀምሮ የአማራን ህዝብ ለአደጋ የሚያጋልጠውን ህገመንግስት ማሻሻልንመቀየርን ያነገበ መሆን አለበት በአማራ ሃይሎችዘንድ የአማራን ህዝብ ፈርጀ ብዙ ሰቆቃዎች ለማስቀረት ሲባል በሚደረግ ትግል ውስጥ ህገመንግስታዊ ማሻሻያ እንደ አንድ የትግል አካል ሲነሳ በአብዛኛው ታሳቢ የሚደረገው የፌደራሉ ህገመንግስቱን ስለማሻሻል ነውሆኖም ከፌደራሉ ህገመንግስት ባላነሰ ሁኔታ የከልል ህገመንግስቶችም የአማራውን ህዝብ በህይወት የመኖር መብትን ጨምሮ በርካታ የሰብዓዊ መብቶች አደጋ ላይ የሚጥሱ አንቀፆችን ያዘሉ ናቸውእንደ ፌደራሉ ህገመንግስት ሁሉ የሃገራችን ከልሎች ህገመንግስቶችም የመቅድም ገፃቸውን የሚጀምሩት የጨቋኝ ተጨቋኝ ዘውግ ትርከትን በማስቀደም ነውሁሉም የከልል ህገመንግስቶች በሚባል ደረጃ በመግቢያቸውላይ የሚያትቱትየነበረባቸውን ብሄራዊ ጭቆና የነፍጠኛውን ስርዓት በትግላቸው አስወግደው ነፃ አንደወጡ ነውይህ የፌደራሉ ህገመንግስት በመቅድሙ ከገለፀው የተዛባ የዘውጎች ግንኙነት ነበር ከሚለው የሚቀዳ ሲሆን የፌደራሉ ህገመንግስት ደግሞ ከህወሃት የ ማኒፌስቶ የቀዳው ነው የአማራ ሃይሎች ከሌሎች የሃገሪቱ ዘውጎች የበለጠ ህገመንግስቱን ለማስቀየር ለማሻሻል መስራት ያለባቸው የከልልም ሆነ የፌደራል ህገመንግስቶች ከመቅድማቸው ጀምሮ ያስቀመጡት በዘውጎች መካከል የነበረ የሚሉት የተዛባ ግንኙነት ትርከት አማራውን የመብቶች ሁሉ ቁንጮ የሆነውን በህይወት የመኖር መብት የሚነፍግና የአማራው ያላባራ መከራ ዋነኛ መንስኤ በመሆኑ ነው የሚገርመው ደግሞ ጨዳቋኝ ነህ ተብሎ በግልፅም ሆነ በተዘዋዋሪ ሲፈረጅ የነበረውን የአማራ ህዝብ ለማስተዳደር የወጣው የአማራ ከልል ህገመንግስትም ይህንን የጨቋኝ ተጨቋኝ ትርክት ይዞ መገኘቱ ነውየአማራ ክልል ህገመንግስት በመግቢያው ላይ እኛ የአማራ ከልል ህዝቦች ለዘመናት ተንሰራፍቶ የቆየውን የጨቋኝ ስርዓት ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶቻችንን አፍኖ በተዛባ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፖሊሲዎች ለድህነትንና ኋላቀርነት ዳርጎን መቆየቱ በጠቅላላ እድገታችን ላይ ያደረሰውን አሉታዊ ተፅኖ ለማስወገድ በመሻት እንዲሁም በአብዛኛዎቹ የሃገራችን ብሄር ብሄረሰቦች ላይ ሲፈፀም በቆየው አስከፊ ብሄራዊ ጭቆና ምክንያት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የጉዳቱ ሰለባዎች ሆነን መቆየታችን በማያዳግም ሁኔታ መታረም እንዳለበት በማመን እያለ የጨቋኝ ተጨቋኝ ተርከቱን ያትታል ሌላው የከልል ህገመንግስቶች የሚያስቀምጡትና ከከልሉ ውጭ የሚኖረውን አማራ ሰብዓዊ መብቶች አደጋ ላይ የሚጥለው ሃሳብ ከአማራ ከልል በቀር ሁሉም የከልል ህገመንግስቶች በከልሉ ሉዓላዊ የስልጣን የሰጡት የከልሉ ባለቤት ብለው ለጠቀሷቸው ዘውጎች ነውይህ ለዘውጎች በከልላቸው ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤቶች እንደሆኑ የሚያትተው ህግ በተግባር ሲተረጎም እነዚህ የከልል ባለቤት የተባሉ ዘውጎቾ በተለምዶ መጤሰፋሪነፍጠኛ በሚሉት አማራ እና ሌሎች ዘውጎች ላይ በህይወት የመኖር መብትን እስከመንጠቅ የሚደርስ ስልጣን እንዳላቸው የሚያሳይ ነው በመሆኑም ባለቤት ባልተባለበት ክልል በብዛት የሚኖረው የአማራ ህዝብ የከልሉ ባለቤት በተባሉ ዘውጎች የሚደርስበት አሰቃቂ ጭፍጨፋንብረት ቅሚያሰብዓዊ ከብርን ያልጠበቀ ከሞት እስከ ቀብር የደረሰ እንግልት ከልሉን በሚያስተዳድሩ አስተዳዳሪዎች ላይምሆነ በፌደራል መንግስቱ መሪዎች ላይ አንዳች ጥያቄ አያስነሳም ሌላው ቀርቶ ባለቤት ባልተባሉበት ክልል የሚኖሩ አማራ ዘውግ ተወላጆች በአሰቃቂ ሁኔታ ከተገደሉ በኋላ አስከሬናቸው በአኛ ከልል አይቀበርም እስከማለት የተደረሰው ከዚሁ የባለቤትነት ህገመንግስታዊ አንቀፅ የተነሳ ነው ሌላው ከክልል ህገመንግስቶች ጋር ተያይዞ መነሳት ያለበት ጉዳይ ህገመንግስቶቹ የከልል ባለቤት ላሏቸው ዘውጎች በብቸኝን የሚሰጧቸው መብቶች ከመገንጠል መብት በቀር በተለያዩ የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ስምምነቶች የሰው ልጆች ሁሉ ሊኖሯቸው የሚገባ መሰረታዊ መብቶች ተብለው የተቀመጡ ናቸውበሃገራችን የከልል ህገመንግስቶች በአብዛኛው በአንቀፅ ላይ የተቀመጡና ለከልሉ ባለቤት ዘውጎች ብቻ የተሰጡ ነገር ግን በዓለም አቀፍ ስምምነቶች ሁሉም የሰውልጆች ሊኖሯቸው እንደሚገቡ ስምምነት ላይ የተደረሰባቸው ህጎች የሚከተሉት ናቸው ማንነትን የመጠበቅና የማስከበር መብትቅርስንና ታሪከን የማስጠበቅየማበልፀግና የመንከባከብ እንዲሁም ቋንቋውን የማሳደግና ባህሉን የመግለፅ መብት ራስን በራስ የማስተዳደር መብትበኢትዮጵያ ፌደራላዊ መንግስት ውስጥ በነፃነትና አድሎ በሌለበት ፍትሃዊ ሁኔታ ተሳትፎ የማድረግ መብትራሱን የሚያስተዳድርበት መንግስታዊ ተቋማት የማቋቋምና በፌደራላዊ አስተዳደሮች ውስጥ ሚዛናዊ ውክልና ማግኘት የሚሉ ናቸው እነዚህ የሰው ልጆች መሰረታዊ መብቶች ለከልል ባለቤት ለተባሉ ዘውጎች ብቻ የሚያድለው የክልሎች ህገመንግስት ባለቤት ያልተባሉ ዘውጎችን ከዚህ መብት የሚያገልሉ በመሆናቸው ከዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ጋር ይጋጫሉ በተለያዩ ከልሎች በብዛትና በስፋት የሚኖሩ የአማራ ዘውግ ተወላጆች ደግሞ እነዚህን መብቶች የመጠየቅ መብታቸውን በከልል ህገመንግስቶች ስለተነፈጉ የመገለሉ ጉዳት ግንባር ቀደም ተጠቂዎች ናቸው ለዚህም ነው የአማራ ሃይሎች ለህገመንግስታዊ መሻሻል ቀዳሚ ታጋዮች ሊሆኑ የሚገባው የአማራ ሃይሎች ህገመንግስቱ እንዲሻሻል የሚጠይቁበት ሌላው ዋነኛ ምክንያት በስራ ላይ ያለው ህገመንግስት ለማዘጋጀትም ሆነ ለማፅደቅ በነበረው ሂደት የአማራ ህዝብ እንደ ዘውግ ሃሳቡእምነቱና ፍላጎት በምንም ሁኔታ ያልተወከለበት በመሆኑ ነውአንድ ህዝብ ባልተሳተፈበት ባልመከረበት ሃሳቡ ፍላጎቱና እምነቱ ባልተንፀባረቀበት ህገመንግስት መተዳደር ስለማይኖርበት ህገመንግስቱ የኢትዮጵያ ህዝብ በስፋት በሚሳተፍበት ግልጽ ነፃና አሳታፊ በሆነ ሂደት እንደገና ሊሻሻል ይገባዋል ከዚህ ዉጭ ከፍተኛ ጥያቄ የሚነሳባቸዉን የመሬት ብሄር ተኮር ፌደራሲዝም ፓርላሜንታዊ ስርዓት የባንዲራ ጉዳይ የጠቅላይ ሚኒስትር የስልጣን ዘመን የራስን እድል በራስ መወሰን እስከ መገንጠል ጉዳይ የህዝብ ሉአላዊነት ጉዳይ የምርጫ ስርዓት የፌደራል እና የከልል መንግስታት የስልጣን ከፍፍል ህገመንግስቱን በፌደሬሸን ምክር ቤት የመተርጎም ጉዳይና መሰል አንኳር ጉዳዮች የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም የአማራ ህዝብ ያልመከረባቸዉ በወከላቸዉ ተወካዮቹ አማካኝነት ዉይይት ተደርጎባቸዉ ያልፀደቁ በመሆናቸዉና በሀገሪቱ ከፍተኛ ዉዝግብ እያስነሱ የሚገኙ ያልተፈቱ ጉዳዮች በመሆናቸዉ እነዚህ ጉዳዮች አንደገና ህዝባዊ ምከከር ተደርጎባቸዉ ሊሻሻሉ የሚገባ በመሆኑ የህገመንግስቱን መሻሻል አስፈላጊነት የሚያደርገዉ ሌላኛዉ ጉዳይ ነዉ በአጠቃላይ ህገመንግስቱ ህዝባዊ ተሳትፎ ያልተደረገበትና የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም የአማራ ህዝብ ያተወከለበት ብሎም የአንድ ጠባብ ቡድን ፍላጎት ለማሳካት ታስቦ የወጣ እና ሀገራችን አሁን ላለችበት ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊ አና ማህበራዊ ቀዉስ ዋነኛ ምንጭ በመሆኑ ከየትኛዉም እርምጃ በፊት የህገመንግስት ማሻሻል ጉዳይ ቅድሚያ ትኩረት ሊሰጠዉ የሚገባ ጉዳይ ነዉ የሰብዓዊ መብት ጥያቄዎች የአማራ ህዝብ ላይ የሚደርሰው አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሰላሳ አመት ያለፈው ቢሆንም ከዓለም አቀፍ እስከ ሃገር አቀፍ አውድ ለሰብዓዊ መብት ቆመናል በሚሉ ድርጅቶችንም ሆነ መንግስታዊ አካላትን ዘንድ ቁብ ተሰጥቶት አንደ ችግር የሚቃይ ነገር አልሆነምየዚህ ቸልታ ምከንያቱ አማራ ጠሉ እሳቤ ከተፀነሰበት ሁኔታ ጋር በአጅጉ የሚገናኝ ሲሆን አማራው በዘውጉ ምክንያት የሚደርስበትን በደል በዘውግ ተደራጅቶ ጠንከር ባለ ሁኔታ ስለማያጋልጥ ነው አማራ ጠሉ እሳቤ ምንጩ የጣሊያን የቅኝ አገዣዝ ህልም እንደሆነ ከፍ ብሎ ተገልጧልጣሊያን የአማራ ልሂቃንን ካላጠፋች የቅኝ አገዛዝ ጉዞዋ እጅግ ችግር የተሞላበት እንደሆነ በግራዚያኒ አዋጅ በግልፅ አውጃ ነው በአማራው ላይ አሰቃቂ ግድያዎችን የማድረጉን ጅማሬ ያስጀመረችው ቅኝ ገዥው የጣሊያን መንግስት አማራን የቅኝ አገዛዝ አቅዱ ዋነኛ ተግዳሮት አድርጎ ሲያስቀምጥ አማራውን መዋጋት የፈለገው በአዋጅ ብቻ አልነበረም ይልቅስ አማራውን የኢትዮጵያ በዝባዥ ዘውግ አድርጎ ሊበሉ ማስተካከሉን በምሁራን የጥናት ስራዎች ጭምር እንዲሰነድ የማድረግ ሁለንተናዊ ዘመቻ በማድረግ ጭምር ነበርበዚህ ምከንያት በውጭው አለም የምሁራዊ ከበብ ውስጥ አማራው የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ችግር መነሾ ተደርጎ ተበይኖ ቀርቷል በዚህ ላይ የጣሊያንን ፈለግ ተከትሎ በአማራው ላይ የመዝመቱ ዘይቤ በዎቹ አብዮተኞች ሲገፋበት በአማራው ላይ ቀደም ብሎ ተከፍቶ የነበረውን የማከፋፋት ዘመቻ ይበልጥ ውጤታማ አድርጎታልየአማራው ብሄርተኝነት ደግሞ ይህን ከዓለም አቀፍ እስከ ሃገር አቀፍ በሰፊው የተዘረጋውን አማራ ጠል ትርከት ለመስበር የሚያስችል ሁለንተናዊ ቁመና ላይ አይደለምበመሆኑም የአማራው ሞት በዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ ዝምታበሃገር ውስጥ ደግሞ በአማራ ጠል ድህረ አስተዳደሮች አስተናባሪነት እየተባባሰ የቀጠለ አሰቃቂ ትዕይነት ሆኗል በአማራ ህዝብ ላይ የሚደርሰው አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በአስቸኳይ እንዲቆም ማድረጉ የአማራ ሃይሎች ለመደራደር ሲቀመጡ ለመደራደሪያነት የሚያቀርቡት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ድርድር ውስጥ ለመግባት ራሱ እንደ ቅድመ ሁኔታ ጭምር ሊያነሱት የሚገባ እጅግ አንገብቢ ጉዳይ ነውየአማራ ሃይሎች በድርድር መድረከ ሲቀመጡ በአማራው ላይ የሚደርሰው የሰብዓዊ መብት ጥሰት አጀማመሩ ከጣሊያን ዘመን የጀመረና አሁን የአማራውን ግድያ የሚያሳልጠው አማራ ጠል የዘውግ ፖለቲካው ደግሞ የጣሊያንን እቅድ አያስፈፀመ እንደሆነ አበከረው ማሳወቅ አለባቸው ይህን ማድረግ የሚጠቅመው አማራውን መግደል ከአማራው ጨቋኝነት የተነሳ የመጣ ችግር አንደሆነ የሚያስቡ የዘውግ ፖለቲከኞች የአሳቤ ምንጫቸው ከፋሽስት ጣሊያን የቅኝ አገዛዝ አሳቤ መሆኑን ሊያውቁ ስለሚገባ ነው ይህን ማሳወቁ ደግሞ አማራው የሚገደለው በታሪከ ባጠፋው ጥፋቱ ነው የሚለውን እሳቤ አማራ የሚሞተው ለጣሊያን አገዛዝ የማይመች በመሆኑ ምከንያት በቅኝ ገዥዎቹ በተተከለበት የጥላቻ አርሾ ነው በሚለው ትከክለኛ አሳቤ ለመተካት ያግዛል የአማራ ንቅናቄ ትግል አሮጌውን ትርከር መዋጋትን ብቻ ሳይሆን በእውነት ላይ የቆመ አዲስ ትርከት ማስተዋወቅንም የሚጨምር ነው የአማራ ንቅናቄ ለአማራ ህዝብ ሰብዓዊ መብቱቶች በአስቸኳይ መከበር የሚደራደረው ድርድር ከዚህ በፊት በአማራው ህዝብ ላይ የተደረጉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችም ተጣርተው ፍትህ የሚያገኙበትን አና ካሳ የሚከፈልበትን ሁኔታ አንዲመቻች ማድረግንም የጨመረ መሆን አለበት የአማራው ህዝብ የሰብዓዊ መብት መጣስ ሰላሳ አመት ያስቆጠረ ብቻ ሳይሆን ከጣሊያን ዘመን ጀምሮ ሲካሄድ የቆየ ነገር ቢሆንም አሁን ስልጣን ላይ ያለው መንግስት ሃገራችንን በሚመራበት ወቅት በአማራ ህዝብ ላይ የደረሰው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ግን በአይነቱም በስፋቱም በአሰቃቂነቱም በከፋ ሁኔታ የቀጠለ ነውበመሆኑም አሁን ሃገራችንን የሚመራው መንግስት ይህ ሁሱ አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በአማራው ህዝብ ላይ ሲደረግ በማድረግ ወይም ባለማድረግ በመተባበሩ በህግ እንዲጠየቅ ማድረግ የአማራ ሃይሎች ድርድሩን ጨምሮ በማንኛውም የትግላቸው መንገድ ሊሰሩበት የሚገባ ጉዳይ ነው የአማራን ህዝብ ሰብዓዊ መብት በማስከበሩ ረገድ ከሁሉም ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው ሌላ ጉዳይ ደግሞ ከተለያዩ የሃገራችን ስፍራዎች የተፈናቀሱ የአማራ ዘውግ ተወላጆች በፍጥነት ወደ ቀያቸው የሚመለሱበትከተመለሱም በኋላ ተጨባጭ የሆነ የደህንነት ዋስና እንዲሰጣቸውኑሯቸውን የሚገፉበት መልሶ የማቋቋም አርዳታም ከመንግስትም ሆነ መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች የሚያገኙበት መንገድ በተጨባጭ ተግባራዊ አንዲሆን መታገል የአማራ ንቅናቄ ጊዜ የማይሰጠው ስራ መሆን አለበት ከላይ ከተጠቀሱት ተግባራዊ ድርጊቶችን ፀፎቨበ ልርከኪህፀ ከሚጠይቁ የድርድር ሁኔታዎች በተጨማሪ የአማራን ህዝብ ሰብዓዊ መብት በዘላቂነት ለማስጠበቅ አማራን በጨቋኝነት በሚከሰው አማራ ጠል የዘውግ ፖለቲካ እሳቤ መንፈስ የተፃፉት የፌደራል እና የከልል ህገመንግስታት አንዲሻሻሉ መሞገት መሰረታዊው የአማራ ንቅናቄ የትግል አቅጣጫ ነው ከዚህ ጎን ለጎን የአማራ ህዝብ ለ ዓመታት በአጠቃላይ እና በዚህ ሶስት አመት ደግሞ በተለይና በአሰቃቂ ሁኔታ አእያስተናገደው ባለው የሰብዓዊ መብት ጥሰትላይ ለሰብአዊ መብት መከበር ቆሜያለሁ የሚለው የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ፊቱን ያዞረበት ሁኔታ ሩዋንዳ ላይ በተደረገው የዘር ማጥፋት ላይ ሆን ብሎ ፊቱን ያዞረበትን እና አሁን ይቅርታ ከጠየቀበት ሁኔታ ጋር በማመሳሰል በዓለም አቀፍ መድረኮች ማስተጋባት ከአማራ ሃይሎች የሚጠበቅ ነውይህ እንቅስቃሴ በአጭር ጊዜ ለውጥ ሊያመጣ የሚችል ሲሆን በዲያስፖራው የአማራ ተወላጆች ቁጥር ብዙ መሆኑ ደግሞ ለውጤታማነቱ በጎ ተፅዕኖ የሚያበረከት ነገር ይሆናል የፖለቲካዊአስተዳደራዊ ውክልና ጥያቄ የአማራ ህዝብ በአማራ ጠሉ የዘውግ ፖለቲካ ትርከት ምክንያት ከአማራ ዘውግ የተወለደ ሰው አንደ ጠቅላይ ሚኒስትርነት በመሰሉ የፌደራሉ የስልጣን ዋነኛ አርከኖች ላይ አንዳይመጣ ከመጣም በሁለተኛ ሶስተኛነት መሆን እንዳለበት ባልተፃፈ ህግ ስምምነት ላይ የተደረሰ ይመስላል ይህ ትርከት የአማራ ተወላጆች በፌደራል ዋነኛ ስልጣን ላይ ቀርቶ እምብዛም የሃገሪቱ ፖለቲካ በማይወሰንባቸው ስፍራዎች ሳይቀር የአማራ ዘውግ ተወላጅ እንዲታይ አይፈልግም ትህነግ በተወገደበት ወቅት ማን ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናል። በ ጀርዐክዐክርሃ በ የዩዐበ በሚል በዓለም ባንከ ሪፖርት የተገለፀ ከልል ነውየሃገራችን ሁሉም ከልሎች እምብዛም ባልታደሉት የኢንዱስትሪ ግንባታም ቢሆን የአማራ ከልል ሁኔታ የከፋ እንጅ የተሻለ አይደለም በኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦትም ቢሆን በደርግ ስርዓት ከተሰራው አንድ የሃይል ማመንጫ ውጭ የተሰራ ነገር የለም በዚህም ምከንያት የከልሉ አብዛኛው ህዝብ የኤሌክትሪክ ብርሃን የማያገኝ ነው በከልሉ የአንደኛ ደረጃም ሆነ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የሚሰጥባቸው ከፍሎች የፈራረሱ ጎጆዎች ሲሆኑ አንዳንዴ ተማሪዎች በድንጋይ ላይ ቁጭ ብለው በዛፍ ስር የሚሰጥበት ሁኔታም አሰ የጤና አገልግሎት ሽፋን አነስተኛ በመሆኑ በከልሉ በአጠቃላይ በህይወት የመኖሪያ አድሜ እጅግ ዝቅተኛ ሲሆን ከአምስት አመት በታች የሚሞቱ ህፃናት ቁጥርም በሃገሪቱ ካለው መጠን ከፊተኞቹ ተርታ የሚመደብ ነው በህፃናት መቀንጨርም ከልሉ ቀዳሚ ተጠቃሽ ነው ሃገራችን እንደ አጠቃላይ በኢኮኖሚ እጅግ ኋላ የቀረች ብትሆንም የአማራ ከልል ይህን ኋላ ቀርነት ከፊት ሆኖ የሚመራ የሆነው ሃገራችን የምትመራበት ዘውግ ፖለቲካ አማራውን መበቀልን አንዱ የፖለቲካ ዘይቤው አድርጎ ስለሚያስብ ነው በዚህ ላይ ለአማራ ህዝብ የሚቆረቆሩ የአማራ ዘውግ ተወላጆች በሃገራዊ የስልጣን ከፍፍሉ ዋነኛ የውሳኔ ቦታዎችን እንዳይዙ ስለሚፈለግ ሃገራዊ ፕሮጀከቶች የሚንቀሳቀሱበት በጀት በተዛባ ሁኔታ እንዲከፋፈልና የአማራ ከልልን ድህነት ቀጠና አንዲሆን የራሱን ሚና ተጫውቷል በመሆኑም የአማራ ሃይሎች ይህን የተዛባ ተርከት ውጤት የሆነውን የአማራ ከልል የኢኮኖሚ ሁኔታ በመቀየር ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እንዲያገኝ መታገል ይኖርባቸዋል የአማራ ህዝብ ቁጥር ጉዳይ አሁን ሃገራቸን ባለችበት የዘውግ ፖለቲካ ለከልሎች የሚመደበው በጀት ከልሉ በያዘው ዘውግ ቁጥር ላይ የሚወሰን ነውየአማራን ዘውግ በሁሉም አቅጣጫ መበቀል የሚፈልገው ይሄው የዘውግ ስርዓት ታዲያ የአማራን ህዝብ ቁጥር በመቀነስ ከልሉ ከሃገሪቱ ብሄራዊ በጀት ሊያገኘው የሚገባውን ትከከለኛ ድርሻ አእንዳይጋራ አድርጓልኢህአዴግ በቆየበት ሩብ ምዕተ ዓመት የአማራን ህዝብ ቁጥር በሁለት ሚሊዮን በሚቆጠር ደረጃ የደረሰበት ጠፋ በማለት አማራ ጠል አላማውን በግልፅ ቢያሳይም ባለፉት ሩብ ምዕተ አመታት በተደረገው የህዝብ ቆጠራም የአማራ ህዝብ ትከከለኛ ቁጥር ስለመመዝገቡ አርግጠኛ መሆን አይቻልም የአማራ ህዝብ ትከከለኛ ቁጥር መታወቁ ከበጀት ባለፈ በሃገራዊ ፖለቲካ ውስጥ ህዝቡ ሊጫወት የሚገባውን ሚና እንዲጫወትም ያግዛል ስለሆነም የአማራ ሃይሎች የአማራ ህዝብ ትከከለኛ ቁጥር የሚታወቅበት አውነተኛ የህዝብ ቆጠራ እንዲደረግ መታገል ይገባቸዋል እንደሚታወቀው በዘውግ ፖለቲካ የጨዋታ ህግ የህዝብ ብዛት ወደ ዋነኛ ሃገራዊ የስልጣን እርከኖች የሚያስጠጋ መንገድ ነው በዘውግ ፖለቲካ ከሃገርኛ ፖለቲካው ዋነኛ የስልጣን አርከን ድርሻ ማግኘት ለአንድ ዘውግ ጥንካሬ በአጅጉ የሚጠቅም ጉዳይ እንደሆነ ህወሃት በአሁኑ ወቅት ያለበትን ሁለንተናዊ ጥንካሬ አይቶ መገንዘብ ይቻላል ህወሃት ሃገራዊ ስልጣን ላይ እያለ ለዘውጉ በሰራው ስራ ጠንካራ ሆኖ ለግማሽ ምዕተ አመታት መቆየትና ከዋናው የሃገራችን የስልጣን እርከን ገሸሽ የተደረገው የአማራ ዘውግ ደግሞ በሁሉም መለኪያ ከአርሱ በሚያንሰው የትግራይ ከልል ከፍተኛ ውድመት እንዲደርስበት አድርጓልአሁን ስልጣን ላይ ያለው የኦሮሞ ልሂቃን የሚመሩት ሃገራዊ አስተዳደርም ከህወሃት በተመሳሳይ ሁኔታ የወጣበትን ከልል ሁለንተናዊ እድገት ለማምጣት እየሰራ ይገኛል በእርግጥ በሃገር ብሄራዊ ስልጣን ላይ ወጥቶ ለአንድ ዘውግ ጥንካሬ መስራት ተገቢ ነገር ላይሆን ይችላል ሆኖም ሃገራችን በዘውግ ፖለቲካ የጨዋታ ህግ እስካለች ድረስ ይህ እሳቤ ተቀባይነት ያለው አይደለምበመሆኑም የጨዋታው ህግ በሚያዘው መሰረት ሄዶ መጫወት ግድ ነውና አማራውም ሃገራዊ ስልጣን ላይ ወጥቶ የዘውግ ፖለቲካ ህግ በሚያዘው መንገድ በሁለንተናዊ ጉስቁልና ላለው የአማራ ህዝብ ከሌላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ባላገለለ ሚዛናዊነት መስራት ይጠበቅበታል ከአማራ ህዝብ አንፃር ከህዝብ ቆጠራ ጋር ተያይዞ የሚመጣው ሌላ ቁምነገር በሃገራችን የህዝብ ቆጠራ ሲደረግ በተለያዩ የሃገራችን ከልሎች የሚኖሩ የአማራ ዘውግ ተወላጆች ቁጥር በትከከል የሚታወቅበት ሁኔታ እንዲኖር መታገል ነው አንደሚታወቀው የአማራ ዘውግ ተወላጆች በተለያዩ የሃገራችን ከልሎች በብዙ ቁጥር ተበትነው ይኖራሉ ሆኖም በሃገራችን ያለው ስርዓት አማራ መሆንን እንደ ወንጀል የሚያይ በመሆኑ በሌላ ክልል እየኖሩ አማራ ነኝ ማለት ደግሞ እጅግ አስፈሪ ጉዳይ እየሆነ ነውበተለይ በኦሮሚያ እና በቤኒሻንጉል ከልል እየኖሩ አማራ ነኝ ማለት አደጋ አዝሎ የሚመጣ ነገር ነው በመሆኑም በዚህ ከልል የሚኖሩ አማሮች ከደህንነት ስጋት የተነሳ በህዝብ ቆጠራ ሰዓት አማራ ነን ከማለት ይልቅ የሚኖሩበትን ከልል ዘውጋዊ ማንነት መጋራትን ይመርጣሉይህ በዋናነት የሚመጣው ከደህንነት ስጋት በመሆኑ የእነዚህ ሰዎች የደህንነት ስጋት እንዲነሳና ራሳቸውን በሚገልፁበት ትከከለኛ ዘውጋዊ ማንነታቸው እንዲቆጠሩ ማድረግ የአማራ ብሄርኛ ታጋዮች ድርሻ ነው በሌላ ከልል የሚኖሩ አማሮች ትክከለኛ ቁጥር መታወቁ ጥቅሞች አሉት የመጀመሪያው ልጆቻቸውን በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እንዲማሩ ለማድረግ ያስችላልበሁለተኝነት ከአማራ ከልል ውጭ ያሉ አማሮች በአስተዳደራዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ውከልና ያግኙ የሚለውን ትግል ገቢራዊ ለማድረግ ያግዛልከሁሉም በላይ ግን ሰዎች ማንነታቸውን ያለማጣት ሰብዓዊ መብት ያላቸው በመሆኑ ነኝ በሚሉት ማንነታቸው መታወቅ የሰው ልጆች መሰረታዊ መብት በመሆኑ ነው ይህ ሁሉ እንዲሆን ግን ሰዎቹ ማንነታቸውን በመግለፃቸው ሳቢያ ከሚመጣባቸው አደጋ አስተማማኝ የደህንነት ዋስትና ሊሰጣቸው ይገባልይህን ማድረግ ደግሞ በአማራ ብሄርተኝነት ሃይሎች በእጅጉ ሊሰራበት የሚገባ የትግል አቅጣጫ ነው የአዲስ አበባየድሬዳዋ ባለቤትነት ጉዳይ በአብዛኛው የኢትዮጵያ ከተሞች የሚኖረው ህዝብ ዘውጋዊ ስብጥር ያለው ነው በመሆኑም የአንድ አካባቢን አስተዳደራዊ ፈለግ በአንድ ወጥ ዘውግ የሚበይነው የዘውግ ፖለቲካ ከተሞችን የሚያስተዳድርበት ሁኔታ በውስጡ የሚኖሩትን ስብጥር ያላቸው ዘውጎች ፍላጎት በመወከሉረገድ ከፍተኛ ውስንነት ያለው ነው የዘውግ ፖለቲካው አስተዳደር በአንድ ዘውግ የበላይነት የማስተዳደር ዘይቤውን ለማሟላት ሲል ብቻ ከፍተኛ ስብጥር ያለውን የከተማ ነዋሪ ከገጠር በመጡ የዘውግ ፖለቲከኞች እንዲተዳደር ያደርጋልእነዚህ ከገጠር የሚመጡ አስተዳዳሪዎች ከተሞቹ የሚገኙበት ከልል ከሚጠራበት ዘውግ የሚመጡ ናቸው የዘውግ ፖለቲካው ከተሞችን ከገጠር በመጡ የዘውግ ፖለቲከኞች እንዲተዳደሩ ከማድረጉም በላይ በህገመንግስት በየትኛውም ዘውጋዊ ከልል ስር ያልተካለሉ እንደ አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ያሉ ከተሞችን ወደ አጎራባች የዘውግ ከልሎች ማጠቃልልን ይመኛሉለገቢራዊነቱም ይታገላሉ የአሮሞ ብሄርተኛ ልሂቃን በህገመንግስቱ በየትኛውም የዘውግ ከልል ስር ያልተካለሉትን አዲስአበባንአና ድሬዳውን በዙሪያቸው በሚገኘው የኦሮሚያ ከልል ለማስገባት ይታገላሉይህ ገቢራዊ ቢሆን በእነዚህ ከተሞች ያሉ የሌላ ዘውግ ህዝቦች በኦሮሚያ ከልል የሚኖሩ የሴሌላ ዘውግ ተወላጆች የሚያጋጥማቸው መገደልመፈናቀልመሰደድንብረትን መቀማትከአስተዳደራዊ ውከልና መገለል ማንነትን ማጣት እንደማይደርስባቸው አርግጠኛ መሆን አይቻልም የዘውግ ፖለቲካው እስካለ ድረስ ለዘውግ አስተዳደር የማይመቹት አነዚህ ከተሞች ቢያንስ በህገመንግስቱ ያላቸውን በከተማ አስተዳደር ምክርቤት የመተዳደር መብታቸው እንዲጠበቅ መታገል የሁሉም የሃገራችን ህዝብ ፋንታ ቢሆንም በእነዚህ ከተሞች በብዛት የሚኖሩት የአማራ ዘውግ አባላት በመሆናቸው የአማራ ብሄርተኞች በዋናነት ትግሉን መምራት አለባቸው ይህን ትግል ምቹ የሚያደርገው ህገመንግስታዊ ድንጋጌን በሻረ ሁኔታ ከተሞቹን በባለቤትነት ለመጠቅለል የሚፈልጉት የኦሮሞ ብሄርተኞች ህገመንግስቱንም የሚደግፉ አካላት መሆናቸው ነው በወቅታዊ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ጥያቄዎች በአሁኑ ወቅት የአማራ ከልል እጅግ ፈርጀ ብዙ ችግሮችን የተሸከመ ከልል ነው ከህወሃት ጋር የተደረገው ጦርነት በሃገር ደረጃ የተደረገ ነው ቢባልም ትልቁን የኢኮኖሚ እና የሰብዓዊ ኪሳራ የጣለው በአማራ ከልል ላይ ነው ጦርነቱ ሲጀመር የአማራ ክልል ቀድሞ ባልታቀደ መንገድ በቢሊዮን የሚቆጠር በጀት ለጦርነቱ እንዲያውል ቢደረግም የፌደራል መንግስቱ ይህን በጀት ለከልሉ ስለሚተካበት ሁኔታ አንስቶ አያውቅም በሰብዓዊ ኪሳራም ቢሆን የአማራ ከልል በርካታ ህዝብ ህይወቱን ያጣበት የተፈናቀለበትና የተዘረፈበት ጦርነት ነው ሆኖም ይህን ኪሳራ ማን ሲሸፍነው እንደሚችል የሚታወቅ ነገር የለም ሆኖም የዚህ ኪሳራ ተፅዕኖው ከልሉን ሰላሳ አመታት ለሚጠጋ ጊዜ ወደኋላ የሚጎትት እንደሆነ የክልሉ መንግስት ጥናት እንደሰራ ጠቅሶ አያስታወቀ ነውይህን ኪሳራ ለማካካስ ከመንግስት ጋር ከመነጋገር ባሻገር የአማራ ብሄርተኞች መንግስታዊ ካልሆኑ የበጀት ምንጮች በሚነሳ የኢኮኖሚ እገዛ ከልሱ ለማገገም ያስፈልገዋል ከተባለው ሰላሳ አመት ቀድሞ እንዲያንሰራራ መስራት ያስፈልጋቸዋል ይህም ማለት ከረጅ ድርጅቶች ከሚገኙ እርዳታዎች ውስጥ በጦርነት የደቀቀው የአማራ ከልልን መልሶ ለማቋቋም የተለየ ትኩረት ባለው መንገድ መመደብ አለበት በተጨማሪም በሃገር ውስጥም ሆነ ከሃገር ውጭ ያሉ የአማራ ተወላጆችና የከልሉ ህዝብ ጉዳት የሚሰማቸው ኢትዮጵያዊያን ሁሉ የቻሉትን የሚረዱበት መንገድ መመቻቸት አለበት ሌላው መታለፍ የሴለበት የአማራ ብሄርተኞች ያለመታከት መንግስትን መጠየቅ ያለባቸው በድርድር ወቅትም ማስተጋባት ያለባቸው ወቅታዊ አጀንዳ በደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ በመማር ላይ የነበሩና ከመንገድ ላይ ተጠልፈው ደብዛቸው የጠፋው የአማራ ተማሪዎች ጉዳይ ነውይህ ጉዳይ ቁርጡ መታወቅ ያለበት በመሆኑ መንግስት አውነተኛውን ነገር ለተማሪዎቹ ቤተሰቦችም ሆነ ለአማራ ህዝብ አንዲያሳውቅ ከፍተኛ ትግል ማድረግ አለባቸው በብሄራዊ ምከከሩ የአማራ ህዝብ በማን ይወከል። ሃገራዊ የምክከር መድረኩ ለድርድር የሚጋብዛቸው የህብረተሰብ ከፍሎች እና በውይይቱ የሚቀመጡ ተሳታፊ አካላት ብዛት ምን ያህል እንደሚሆን አስካሁን ባለው ሁኔታ ማወቅ አልተቻልም ሆኖም የሃገራችን ፖለቲካ ማጠንጠኛው ዘውግ በመሆኑ በሃገሪቱ ያሉ ዘውጎች ወኪሎች ናቸው በሚባሉ አካላት በዋናነት የድርድሩ ተካፋይ እንደሚሆኑ መገመት ይቻላል የአማራ ህዝብም በዘውጉ ወኪሎች አማካይነት እንደሚወከል ከግምት በዘለለ ሁኔታ መረዳት ይቻላል አዚህ ላይ መነሳት ያለበት ወሳኝ ጥያቄ የአማራ ዘውግ በማን ይወከል የሚለው ነው የአማራን ዘውግ ወክለው የሚገቡ አካላት ቁጥር ያልታወቀ ስለሆነ አነማን በምን መጠን ይግቡ የሚለውን አሁን ባለንበት ሁኔታ ማወቅ ያስቸግራል አሁን ላይ መናገር የሚቻለው የአማራን ህዝብ ጥያቄ በተገቢው መንገድ ለማቅረብ ምን መደረግ አለበት የሚለውን ስልት ነው አንደሚታወቀው የአማራ ህዝብ በዘውግ ፖለቲካው ሳቢያ የደረሰበት በደል ፈርጀ ብዙ እና በተለያየ መንገድ የሚገለፅ ነው ይህን ፈርጀ ብዙ ችግር በተገቢው ሁኔታ ለማቅረብ ደግሞ በተለያየ የህይወት መስመር የተሰለፉ የአማራ ዘውግ አባላት መካተት አለባቸው ከተለያየ የህይወት መስመር የተውጣጡ የአማራ ዘውግ አባላትን ማሳተፉ የሚጠቅመው አማራ በመሆናቸው የደረሰባቸውን ወይም በሌሎች ላይ ሲደርስ ያስተዋሉትን በደል እንደየ የህይወት መስመራቸው ሁኔታ የሚለያይ በመሆኑና ሁሉንም ተግዳሮቶች ይዞ ወደ ድርድሩ መግባት አስፈላጊ ስለሆነ የተለያዩ የህብረተሰብ ከፍሎችን ጥያቄ አንግቦ ወደ ድርድር መግባቱ ውጤታማ ድርድር ለማድረግ ይበጃልከእነዚህ የህብረተሰብ ከፍሎች በተጨማሪ ድርጅት መስርተው ለአማራው ህዝብ የሜታገሉ ፓርቲዎችና የሲቪከ ማህበራት መሳተፍ ይኖርባቸዋል የህይወት ልምዳቸው ያስተዋወቃቸውን የአማራ ህዝብ ተግዳሮቶች ለማስረዳት በውይይቱ ሊሳተፉ የሚችሉ የህብረተሰብ ከፍሎችን ለመጥቀስ ያህል የመጀመሪያዎቹ ተሳታፊዎች መሆን ያለባቸው ከአማራ ክልል ውጭ የሚኖሩ የአማራ ዘውግ ተወላጆች ናቸው እነዚህ የህብረተሰብ ከፍሎች በህይወት ልምዳቸው ካለፉበት ሁኔታ በመነሳት እዚህ ሰነድ ላይ ከተቀመጠው የአማራ ህዝብ ቸግር በተጨማሪ የሚያመጧቸው የመደራደሪያ ነጥቦች ይኖራሉሌሎች መሳተፍ ያለባቸው አካላት በአማራ ከልል ውስጥ የሚገኙ አማሮች ናቸውየአማራ ተማሪዎች ማህበርም በዚህ ድርድር መሳተፍ ያለበት ሌላው የህብረተሰብ ከፍል ነው ከአማራ ከልል ውጭ ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው የሚማሩ ተማሪዎች እገታን ጨምሮ በርካታ ዘውግ ተኮር የመብት ጥሰቶችንና አንግልቶችን የሚያስተናግዱ ስለሆነ በድርድሩ ውስጥ ተሳትፎ ሊኖራቸው ይገባልየአማራን ህዝብ ጥያቄ አንግበው የሜታገሉ የአማራ ዘውግ ተኮር ፓርቲዎች የድርድሩ አካል ሊሆኑ ይገባልበሃገራችን በተለያዩ ከልሎች በሚነሱ ዘውግ ተኮር ግጭቶች ንብረቶቻቸው የሚወድሙባቸውና ለከፍተኛ ኪሳራ የሚዳረጉ የአማራ ባለሃብቶችም የድርድሩ አካል መሆን አለባቸው የሃገራችን ፖለቲካ በከፍተኛ ሁኔታ የዲያስፖራውን ሚና የሚፈልግ በመሆኑ የአማራ ዲያስፖራዎች በድርጅትም ሆነ በግል ሊሳተፉ ይገባል ሆኖም መንግስት በድርድሩ የሚሳተፉ ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው ብቻ ናቸው ስላለ የዲያስፖራው ቀጥተኛ ተሳታፊነት አጠያያቂ ነው ሆኖም ዲያስፖራው በቀጥታ መሳተፍ ባይችል አንኳን ከሚሳተፉ አካላት ወደ ድርድር መድረኩ ከመግባታቸው በፊት ተገናኝቶ ሃሳቡ በእነሱ በኩል አንዲንፀባረቅ ሚያስቸሉ ውይይቶች ማድረግ ይቻላል ሌላው በድርድሩ መሳተፍ ያለበት አካል ከቅርብ ጊዜ ውዲህ የአማራ ብሄርተኝነት አይነተኛ ወኪል ተደርጎ እየተወሰደ ያለው ፋኖ ነው የአማራውን ጉዳይ ቀዳሚ አጀንዳቸው አድርገው የሚሰሩ የመገናኛ ብዙሃንና የማህበረሰብ አንቂዎችየአማራ ወጣቶች ማህበራትየአማራ ምሁራን መማከርት የውይይቱ ተሳታፊ መሆን ያለባቸው አካላት ናቸው የአማራ ምሁራን መማከርት የትርክት ቅልበሳውን ትግል በሙያዊ ጥናት በተደገፈ ተጨባጭ ጥናታዊ መረጃ ማስደገፍ የሚያስችል አቅም ስላላቸው ለድርድሩ የሚያበረከቱት አስተዋፅኦ የማይተካ ነው በድርድሩ የአማራ ሃይሎች ሊገጥሟቸው የሚቸሉ ግዳሮቶች እና የመፍትሄ አቅጣጫዎች የአማራውን በደል ለመስማት ያለመፈለግ ዝንባሌ አሁን በሃገራችን የሰፈነው አማራ ጠል የዘውግ ፖለቲካ አማራው በጅምላ ተገድሎ በስካቫተር ተዝቆ እስከመቀበር በደረሰ ሰብዓዊ ከብርን ባዋረደ ሁኔታ እየተበደለ እንደሆነ በግልፅ እየታየም አማራው በዳይ ሆኖ እንዲቀርብ አንጅ ተበድሏል ብሎ ማመን አይፈልግምይህ የሚሆንበት ዋነኛ ምከንያት ተበድያለሁ ብሎ ማመንና ሎችን ማሳመን መቻል በዘውግ ፖለቲካ ስልጣን ለመያዝ ዋናው ቅድመሁኔታ ስለሆነ ነውራሱ አማራ በድሎኛል እያለ ወደ ስልጣን የመጣው የድህረ አስተዳደር አማራው በደሉ ይቆምለት ዘንድ ብቻ በደሉን ሲያስረዳ አማራውም ስልጣን እየጠየቀ ይመስለዋልስለሆነም በደሉን መስማት አይፈልግም አማራው በአሁኑ ወቅት እየደረሰበት ያለው አይነት አልሰማም ቢሉት የማይቻል በደል ሲሆን ደግሞ በደሉን መካድ ስለማይቻል በደሉን ማቃለልን አንደ አማራጭ ይወስዳል በደሉን ከማቃለሉ በተጨማሪ ማስቀየስበሃገሪቱ በሁሉም ሰው ላይ የሚደርስ በደል አንደሆነ አስመስሎ ማስቀመጥ አናስቆማለን የሚል ከልብ ያልሆነ መልስ መስጠትንለድርጊቱ አማሮችን ራሳቸውን ተጠያቂ እስከማድረግ መሄድ ወዘተ መንገዶችን ይጠቀማል ከቅርብ አመት ወዲህ የታየውን እጅግ አሰቃቂ የአማሮች ዘውግ የተለየ ግድያ ከአንዳንድ ጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶች ጋር ማያያዝ ጭራሽ ግድያውን ያቀናበሩት በአካባቢው ወርቅ ለመቆፈር የፈለጉ የአማራ ባለሃብቶች ናቸውየሞቱት አማሮች ብቻ አይደሱም የሚል እጅግ አሳዛኝ መልስ ሲሰጥ ተሰምቷል የአማራ ሃይሎች ለድርድር ሲቀርቡም ይህንኑ አይነት የመካድ የማድበስበስ የማስቀየስናሃሰተኛ ተጓዳኝ ነገሮችን መፍጠር ዋናውን በደል ማስረሳት አይነት ችግሩን በደምብ አንዳያስረዱ የሚያደርግ ተግዳሮት ሊገጥማቸው ይትላል እንደዚህ አይነት ችግር ሲገጥም የመጀመሪያው ወሳኝ መፍትሄ እዚህ አባባሎች የዘውግ ፖለቲካው ጠላቴ የሚለውን አማራን ሲያሳድድ ለመኖር ሲል የሚጠቀምባቸው አደገኛ ዘዴዎች እንደሆኑ የአማራ ሃይሎች ጠንቅቀው የሚያውቁ መሆናቸውን በተገቢ መንገድ መግለፅ ያስፈልጋልከዚህ ቀጥሎ የአማራ ሃይሎች ግልፅ ሊያደርጉት የሚገባው ነገር የዘውግ ፖለቲካው የአማራውን በደል መስማት የማይፈልገው ወይም የሚያድበሰብሰው አማራው መበደሉን ሲገልፅ ስልጣን ስጡኝ እያለ አንደሆነ ስለሚያስብ እንደሆነ ገልፀው እውነታው ግን አሱ አንዳልሆነ ይልቅስ በህይወት የመኖር መብቴ ይከበርልኝ የሚል የህልውና ጥያቄ እያቀረበ እንደሆነ አስረግጦ መንገር ነው ይህ ማለት አማራው የስልጣን ጥያቄ አያነሳም ማለት አለመሆኑንይልቅስ በአሁኑ ወቅት የአማራው አንገብጋቢ ጥያቄ በህይወት የመኖር መብትመሆኑን ግልፅ ማድረግምይገባልአማራው በህይወት የመኖር መብቱን ካስከበረ በኋላ በሃገሩ ፖለቲካ የመሳተፍ ሙሉ መብት ስላለው የስልጣን ጥያቄን የማንሳት ሙሉ መብት እንዳለው ማስገንዘብ ያስፈልጋልይህን መንገር የሚያስፈልገው አማራው ተመልሶ መምጣት የሴለበት የድሮው ስርዓት ወኪል ስለሆነ ከሃገራዊ ስልጣን መገለል አለበት የሚለውን የዘውግ ፖለቲካውን ትርከት ለመታገል ነው በተጨማሪ ዲሞከራሲያዊ መብቱን መጠቀምም የዜግነት መብቱ ነው የአማራ ሃይሎች በሚገኙበት የድርድር መድረክ ሁሉ የአማራውን በደል ሲገልፁ አብረው ማንሳት ያለባቸው አሁን በአማራው ላይ እየተደረገ ያለው በደል እና የመንግስት ዝምታ የዘውግ ፖለቲካው አዲስ ሊፈጥራት እያሰባት ያለችው ኢትዮጵያ አማራውን የምታሳድድና የምትገድል ለመሆኗ ምልከት ሰጭ መሆኑን ነው በአማራው በኩል ደግሞ የኢትዮጵያ ስም ስለተነሳ ብቻ እንዲህ ባለው አደገኛ ሁኔታ መስማማትና ከአማራጠሉ የዘውግ ፖለቲካ ጋር መጓዝ እንደማይታሰብ መንገር ያስፈልጋል አማራ ጠሉ የዘውግ ፖለቲካ የአማራውን በደል ለመስማት ያለመፈለጉ ሌላ መልክ በአማራ ሃይሎች የሚነሳውን የህገመንግስት ማሻሻያ ጥያቄ የሚገፋበት መንገድ ነው የዘውግ ፖለቲከኞች አሁን ያለው የአማራውን መሳደድና መገደል ህጋዊ ያደረገውን ህገመንግስት ቀጣይነት በእጅጉ ይፈልጉታልበመሆኑም የአማራ ሃይሎች ህገመንግስቱ እንዲሻሸልአንዲቀየር የሚያቀርቡትን ጥያቄ ለማጣጣል በህገመንግስቱ አማራው ለይቶ ጠቅሶ የሚጎዳበት አንቀፅ አልተቀመጠም ይላሉየባሰው ደግሞ ለአንድ ከልል ስንል ህገመንግስት አንቀይርም የሚለው መልሳቸው ነው እንዲህ ያለ ተግዳሮት ሲገጥማቸው የአማራ ሃይሎ ማንሳት ያለባቸው ከርክር ህገመንግስት በአንቀፁ ብቻ ሳይሆን በተፃፈበት መንፈስ የሚበየን መሆኑን መግለፅ ነውይህ ህገመንግስት የተፃፈበት መንፈስ ደግሞ አማራ መቀጣት ያለበት ጨቋኝቅኝ ገዥና ትምከህተኛ ነው የሚል ሲሆንይህን የሚያምኑ የፖለቲካ ቡድኖች አማራውን አከርካሪውን ሰብረን ጨርሰናል በሚል የአሸናፊነት ስነልቦና ሰከረው አድራጊ ፈጣሪ በሆኑበት የአፃፃፍ ሂደት የተፃፈ እንጅ ትክከለኛውን መንገድ የተከተለ አልነበረምከሁሉም በላይ የአማራ ህዝብ በፍፁም ያልተወከለበት ነበረአማራው እንደዘውግ ተወክሎ አብሮ ባልፃፈው ህገ መንግስት የመገዛት ግዴታ እንደሌለበት አበከሮ ማስረዳት ይጠበቃል ይህ ሲባልም ኢህዴንን እንደ አማራ ወኪል አድርጎ የማቅረብ ዝንባሌ ይኖራል ይህን ተግዳሮትም የአማራ ሃይሎች እንዴት ማለፍ አንዳለባቸው በዚህ ሰነድ ከፍ ብሎ ተገልጧል የአማራ ህዝብን ጥያቄዎች የሌሎች ዘውጎችን መብቶች ለመንፈግ የሚደረግ ሙከራ አድርጎ ማየት የዘውግ ብሄርተኞች የአማራውን አከርካሪ መስበር አለብን በሚለው መርሃቸው አማራውን በእጅጉ የሚበድሉት አማራው ተጠናከሮ ታግሎ መብቱን ካስከበረ ሌሎች ብሄረሰቦች መብታቸውን ያጣሉ የሚል አደናጋሪ እሳቤ ስላላቸው ነውከምከንያታዊነት የተፋታ መከራከሪያን አንግቦ እንደ ትከከለኛ እሳቤ መከራከር የዘውግ ፖለቲካችን መለያ ስለሆነ የአማራው መብት መከበር ማለት የሌሎች ብሄረሰቦች መብት መነጠቅ አድርገው ያስባሉሆኖም የአማራው መብት መከበርን አንፈልግም የሚለውን በግልፅ መናገር ስለማይቻል አማራው ለፖለቲካዊ ውከልና የሚያቀርበውን ጥያቄ የተለያዩ ምክንያቶች በማቅረብ ሊያድበሰብሱ ይሞከራሉ የመጀመሪያው ማደድበስበሻ ከአማራ ከልል ውጭ የሚኖረው አማራ ተበታትኖ ስለሚኖር ራሱን በራሱ የሚያስተዳድርበት ፖለቲካዊ ሁኔታ መፍጠር አይቻልም ይላሉይህ በሁለት መንገድ ልከ አይደለም አንደኛው አማራው በብዛት ተሰባስቦ ብቻ ሳይሆን ብዙሃን በሆነባቸው ከ በላይ የህዝብ ቁጥር ይዞ በሚኖርባቸው ከአማራ ከልል ውጭ ያሉ ከተሞች ተገቢውን አስተዳደራዊ ውከልና እንዳያገኝ የኮታ ስርዓት በማምጣት በታሰበበት ሁኔታ ከአስተዳደራዊ ውከልና እንዲገለል ተደርጓልበተጨማሪም አንደ ደራወልቃይትመተከል ባሉ አማሮች ብዙሃን ሆነውም በአንድ አካባቢ ተሰብስበው በሚኖሩበት ሁኔታም በአስተዳደራዊ ውከልና ተነፍገዋል ሁለተኛው ሰዎች በሚኖሩበት ቦታ አስተዳደራዊ ውከልና የማግኘት መሰረታዊ መብታቸውን ለመጠቀም በአንድ ቦታ ላይ በርከት ብለው በዘውግ ተሰባስበው መገኘታቸው ግድ አይደለም ስለዚህ ሰዎች በርከት ብለው በሚገኙበት ሁኔታ በአማራ ከልል ኦሮሚያ ልዩ ዞን እንደሚደረገው በግዛታዊ ውከልናፐሸቪበ ጸፀርበዐበክ በአስተዳደራዊ መዋቅር የሚወከሉ ሲሆን ተበታትነው የሚኖሩ ከሆነ ደግሞ ግዛታዊ ባልሆነ የውከልናክዐክፐፎበበር ክዩፀየፎበበ በአስተዳደራዊ መዋቅሩ መወከል የሚገባቸው መሆኑን አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች የደነገጉት መብት ነውይህን ጠቅሶ መከራከር የአማራ ሃይሎች ዋኛው የትግል አቅጣጫ መሆን አለበት የአማራ ህዝብ እንደ ዘውግ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች ከኢትዮጵያ ብሄተኝነት ጭብጥ ጋር እያቀላቀሉ ማደናገር የአማራ ህዝብ የሚያነሳቸውን የግዛት እና የማንነት ጥያቄዎቸበመተከልበደራበወልቃይት ሁመራበራያ ግዛቶች ለማድበስበስ የዘውግ ፖለቲካው ግዛቶቹ የትም ቢሆኑ ኢትዮጵያ ውስጥ ስላሉ በዚህ ሁኔታ መታሰብ አለበት ሲሉ ለአማራ ህዝብ ስለኢትዮጵያዊነት እሴት ሊመከሩ ይሞከራቸዋልሆኖም የአማራ ህዝብ እነዚህን ግዛቶች ለማስመለስ የሚጠይቀው በስፍራዎች እንደ ኢትዮጵያዊ በአኩልነት ሳይስተናገድ ስለቀረጭራሽ አማራነቱ ወንጀል ሆኖ ህይወቱን አደጋ ላይ የጣለ ስጋት ስላንዣበበት ነው የአማራን ህዝብ ሌሎች ማንነት ተኮር ጥያቄዎች ከኢትዮጵያዊነት የመጉደል ወንጀል አድርገው የሚያነሱ የዘውግ ፖለቲከኞች በተግባራዊ ስራቸው በዘውጋቸው ተደራጅተው ስልጣን የያዙአማራውንም በዘውጉ ለይተው የሚያሳድዱ ናቸው ከሁሉም በላይ ስለኢትዮጵያ ብሄርተኝነት የሚወራው የሃገሪቱ አጠቃላይ ፖለቲካ በዜግነት ዛቢያ የሚዞር ሲሆን ነው እንጅ ለአማራው ሲሆን ብቻ የኢትዮጵያ ብሄርተኝነትን እንደ መሸሻ ማንሳት የሚያስኬድ ከርከር አይደለምየአማራ ህዝብ የግዛት ይገባኛል ጥያቄ የሚያነሳባቸውን ቦታዎች በህገመንግስቱ በሌላ ከልል የተካለሉ ስለሆኑ ማንሳት ልከ እንዳልሆነም ሲነገር ያጋጥማልይህን የሚሉ ወገኖች ራሳቸው ህገመንግስቱ ለዘውጋቸው ከልል ያልመደባትን አዲስ አበባን እና ድሬዳዋን በይገባኛል የሚያነሱ ቡድኖች ናቸው ለአነዚህ ወገኖች የሚመለሰው ቀላል ከርከር የአማራ ህዝብ ሲረቀቅ ባልተሳተፈበት ህገመንግስት የመገዛት ግዴታ እንደሌለበት ነው ሃገራዊ ድርድሩ ለአማራ ህዝብ ሊያመጣ የሚችለው ፋይዳ የአማራ ህዝብ የህልውና ስጋት የተጋረጠበት ህዝብ በመሆኑ ሃገራዊ የውይይትየድርድር የምከከር መድረኮች ላይ ተኝቶ ጥያቁዎችን ጥርት ባለ ሁኔታ ማስተጋባት መቻሉ በአማራው አለመደራጀትና አለመጠናከር ላይ ህልውናውን ለገነባው አማራ ጠል የዘውግ ፖለቲካ ጎራ ትርጉም ያለው መልዕከት የሚልክ ነውይህ መልዕከት አማራው ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ ህልውና ሲል ለዘውግ ፖለቲካው የስልጣን ላይ መወጣጫ መሰላል ሆኖ መቀጠሉን አንዳቆመ የሚያስረዳ ነው ይልቅስ አማራው በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ብሄርተኝት እና በአማራ ብሄርተኝነት መካከል ሚዛናዊ መስተጋብር ሰርቶ ሁለቱንም የማይጎዳ ግን የአማራውን የህልውና ስጋት የሚያስቀር የትግል መስመር እንደ ጀመረ ለደጋፊውቹም ሆነ በወንጀለኛነት ለሚከሱት ተገዳዳሪዎቹ ማሳየት ይትላል አማራ ጠሉ የዘውግ ፖለቲካ አድሜውን የሚያራዝመው ከዚህ ቀደም በዘውግ ተደራጅቶ ማንንም በድሎ የማያውቀውን አሁንም ቢሆን በዘውግ መደራጀቱን በተገቢው ሁኔታ ያላወቀበትን የአማራውን ዘውግ በማያውቀው የዘውግ ፖለቲካ ዘይቤ ግራ በማጋባት ነው የዘውግ ፖለቲካው የአማራው ግራ መጋባት ለስልጣኑ እድሜ መራዘም ዋስትናው ስለሆነ የአማራው ዘውግ በዘላለማዊ ግራ መጋባት ውስጥ እንዲኖር ይመኛልአማራው በዘወግ ተደራጅቶ እንደዚህ ባሉ ሃገራዊ የድርድርምከከር መድረኮች መገኘቱ አማራ ጠሉ የዘውግ ፖለቲካ ጎራ የሚፈልገው የአማራ ግራ መጋባት እያበቃ እንደሆነ ምልክት ይሰጣል ከዚህ ባለፈ የምከክር መድረኩ ለአማራ ህዝብም ሆነ ለሌሎች የሃገራችን ህዝቦች የመነጋገርን አድል የሚሰጥ ሊሆን ስለሚቸል የሃገራችንን ፈርጀብዙ የፖለቲካ ችግር ለማቃለል በጎ አስተዋፅኦ ይኖረዋል የአማራ ህዝብ ያለበት ወቅታዊ ሁኔታ የአማራ ህዝብ በአሁኑ ወቅት ያለበት ሁለንተናዊ ጉዳት ትህነግ አማራ ጠላቴ ነው ብሎ በቱ ማኒፌስቶ ከፃፈበት ጊዜ ጀምሮ የተሰራው አማራ ጠል ፕሮፖጋንዳ ውጤት ነው ከዓም ጀምሮ እስከ ዛሬ ያለው አስተዳደር የሰው ለውጥ አምጥቷል እንጅ የአማራ ህዝብን በተመለከተ ያለው የቂምየአውዳሚነትና የጥፋት አጀንዳ ተመሳሳይ ነው ሆኖም የአማራው ልሂቅ በአብዛኛው የአማራን ህዝብ በደል ከትህነግ ጋር ብቻ አቆራኝቶ የሚያይ በመሆኑ አሁንም በርካታ የአማራ ልሂቅ ከህወሃት በበለጠ አማራውን ለአዋራጅ ሞት የዳረገውን ኦህዴድ መራሹን የብልፅግና ፓርቲ አስተዳደር በመደገፉ ቀጥሏል በመሆኑም የአማራ ህዝብ በኦህዴድ መራሹ የብልፅግና አስተዳደር የሚደርስበት ፈርጀብዙ ፖለቲካዊ በደል በሌላው ብቻ ሳይሆን በራሱ በአማራው ልሂቅ ወይ እንደ ሌለ ይቆጠራል ወይ ለብልፅግናው መንግስት ይቅርታ ለማድረግ በሚመች መልኩ እጅግ ተዛብቶ እና ተቃሎ ይቀርባል የአማራ ህዝብ በአሁኑ ወቅት በሁለንተናዊ ከስረት ውስጥ ይገኛል በፖለቲካው ረገድ ሃገር ለማስቀጠል ሲል ከሰፊው የኦሮሞ ህዝብ የወጡ ልሂቃን ስልጣን መያዛቸውን በመደገፍ በቻለው ሁሉ ለመርዳት ያደረገው ቅንነት በኦሮሞ ልሂቃን ዘንድ ቁማር የመበላት ፖለቲካዊ አላዋቂነት ተደርጎ ተተርጉሟል በመሆኑም የአማራ ህዝብ ይህንኑ የመብላት መበላት ፖለቲካ አሜን ብለው በተቀበሉ ቁማር አሳላጭ ምስለኔዎች በመመራቱ ቀጥሷል በፀጥታና ደህንነት ረገድ ግዝፈቱን በሚመጥን መልኩ ሴሎች ከልሎች እንደሚያደርጉት በጊዜ የሰለጠነ የከልል ልዩ ሃይል እንዳያሰለጥ በአነዚሁ ምስለኔ መሪዎች በመከልከሉ ለህወሃት ወረራ አጥር የሌለው ቤት ሆኖ አንዲጠብቅ ተፈርዶበታልበዚህ ሳቢያ የደረሰበትን በትህነግ አጥፊ ቡድን የመውደም ከስረት ደግሞ በአማራው ራስን መከላከል ያለመቻል ፈሪነት የመጣ ችግር ተደርጎሴላ የስነልቦና ስብራት ዘመቻ ተከፍቶበታል ይህን ሆድ ሲያውቅ ሆነ የማጠልሸት አካሄድ ወደ ጎን ብሎ ራሱ መንግስት በጠራው የከተት ጥሪ በራሱ ስንቅና ትጥቅ ለመሳተፍ ሲሞከር ደግሞ የተለያዩ አሻጥሮችን በመስራት በቻለው አቅሙ ራሱን እንዳይከላከል ተደርጓል በዚህም ሳቢያ የአማራ ህዝብ በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ የደህንነት ስጋትና ግራ መጋባት ውስጥ ይገኛልበኢኮኖሚው ረገድ ድሮም በማያወላዳው አቅሙ ላይ ከትህነግ ጋር የተደረገው ጦርነት ባመጣው ውድመት መመለሻው በጣም ሩቅ በሆነ ውድመት ውስጥ ይገኛል የአማራ ንቅናቄ የወደፊት ትግል እንዴት መቃኘት አለበት።