Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
በገይሪዐዐ«ፈበሪዕነዐሀ የአቤቶሁን ያዕቆብ ትውልድና አጭር ታሪክ። አዲስ አበባ ተብሎ የሚጠራው የኢትዮጵያ ዋና መናገሻ ከተማ በንጉሥ ሣህለ ሣላሴ ተቁርቁሮ በጋላ ፊንፊኔ ይባል ነበር። ሆኖም በየጊዜው ይህን ተረድረው ሲያስቡ እንደ አባቶቻቸው እንደነ አጹ ኢያሱ አድያም ሰገድ የአለምን ከንቱነት ተረድተው ገዳም ለመግባት ማሰባቻእው የሚያስመሰግናቸው ነው። አቤቶ ሥግወ ቃል። ግራኝ መሐመድ የአጹ ልብነ ድንግል ንጉሣዊ ሰውነት መንገላታትና መከራን የማይችል መስሎት በአነስተኛ ግምት ስለ ገመተው ልጅዎን ይዳሩልኝና እንታረቅ ሲል የዕርቅ ድርድር ቢልክባቸው ቁራጡ ንጉሠ ነገሥት ላንተ ልጄን ሰጥቼ ጦርነቱን ከማስቀረት በኅጢአታቸው የፈጠረን ጌታ ቢቀጣን ይሻላል ብለው እንደ መለሱትና እስከ መጨረሻውም ድረስ ተጋድለው በሰማዕትነት እንዳለፉ ጀግናው ልጃቸው አጹ ገላውዴዎስም የብዙ ጊዜ ጠላታቸውን ከተበቀሉላቸው በኋላ በትውስት ወታደር አዲስ ጉልበት ካላቸው ጋራ ተዋግተው መሞታቸውን ታሪክ ይመሰክርላቸዋል። ይህንንም ታሪክ ባጭሩ ለመጻፍ ያሳሰበኝ ምንም እንኳ የታወቀ ታሪክና የታሪክ ደራሲዎች ከጻፉት ያልተለየ ቢሆን ይበልጥ ጉልህ ሆኖ ከረጅሙ ባጭሩ ተጠቃሎ ግልጽ ማስረጃ ሆኖ የተጨበጠ እንዲሆንና ማናቸውም ኢትዮጵያዊ እንዲያውቀውና ለማጥናትም ቀላል ሆኖ እንዲገንለት በማለት ነው። ይህም አጻጻፍ ካለማወቅ የተነሣ ሳይሆን እኔ እንደማውቀው ሌላውም ያውቀዋል በማለትና እንዳውቀውም በመቀጠር ከታሪክ ደራሲዎች ስለሚዘለልና ቸል ስለሚባል ነው። በበኩሌም ለሆነው ግድፈት የአንባቢዎቹ የማረሚያ ርዳታ ተገኝቶበት ለወደፊቱ በሰፊው ታርሞ እንዲዘጋጅ ተስፋ በማድረግ ላሁኑ ጊዜ ከፍ ያለ አገልግሎት ተገኝቶበት ለሕዝቡ ጠቃሚ ይሆናል በማለት ይህን ታሪክ አዘጋጀሁ።
ነገር ግን የሕዝብ ድምፅ የእግዚአብሔር ድምፅ ነው እንደሚባለው በንጹሕ ሕዝብ የተነገረው ቃል አንድ ቀን ከወንድማቸው ከአቤቶ ፋሲል ገራም ከዕለታት አንድ ቀን ከወንድማቸው ከአቤቶ ሥግወ ቃል ተለይተው ወደ አጐታቸው ልጅ ወደ አጹ ሠርጸ ድንግል ቤት ወደ ጐን ደር ተሻግረው ሳለ ለእቴጌይቱ መድኀኒት ልቀምስ እፈልጋለሁ ስላሉዋቸው እቴጌይቱም ይሠጉበትና ይጨነቁበት የነበረውን በመዘንጋት ፋሲል የነጋ ልጅ ሆኖ በገረድ እጅ መድኀኒት ሊቀምስ አይገባምና ሐመልማል ታቅምሰው ሲሉ አዝዘው መድኀኒት የሚቀምሱበት የተለየ እልፍኝ ሰጥተዋቸው ስለ ነበር አቤቶ ፋሲል የጉልማሣነት ፈቃድ ስለ አሸነፋቸው ከወይዘሮ ሐመልማል ጋራ ተገናኝተው ኖሮ አጹ ሱስንዮስ በኋላን አቤቶ ልሳነ ክርስቶስ ተፀነሱ። አጹ ሠርጸ ድንግል ከሞቱ በኋላ ልጃቸው አጹ ያዕቆብ በነገሁ ጊዜ አጹ ሱስንዮስን በመልካም ዐይን አይመለከቱዋቸውም ነበር። የአጹ ያዕቆብ ልጅ አቤቶ ገላውዴዎስ ካገራቸው ሳይወጡ ሲቀሩ ወንድማቸው አቤቶ ጸጋ ክርስቶስ ያባታቸውን አልጋ ለመመለስ ሺ ወታደር ከአጹ ሱስንዮስ ጋራ ተዋግተው ድል ከሆኑ በኋላ በሰነዓር በኩል ሸሽተው ሲሄዱ ያገሩ ንጉሥ ኦርባት ያባትህን አልጋ ላስመልስልህ ከፈቀድህ ልጄን አግባና የጦር ሠራዊት ሰጥቼህ ከሱስንዮስ ጋራ እንደገና ተዋጋ ቢላቸው የኢትዮጵያ ነገሥታትና መሳፍንት ከጥንት ጀምሮ አገራቸውን ለማስወጋት አለመፍቀድ ልምዳቸው ስለ ሆነ የኦርባትን ምክር በመቃወም ወደ ኤሮፓ ሄደው ፈረንሳይ አገር በሺሄቋ ዓም በሕመም ሞተው ካርዲናል ሪቬሊዬ የተባለው የነገሥታት ልጆች ይቀበሩበት በነበረው ቦታ በታላቅ ክብር አስቀበራቸው። ለምሳሌ መርድ አዝማች አስፋ ወሰን ገና በሕይወታቸው ሳሉ ልጃቸው መርድ አዝማጅ ወሰን ሰገድ ከአፍቀራ ጐሌ ልጅ ከወይዘሮ ዘነበ ወርቅ ንጉሥ ሣህለ ሥላሴን ስለ ወለዱ የምሥራች ብለው ወደ አባታቸው ቢልኩ ስሙን ምኒልክ እንድትለው ብለው መክረዋቸው ነበር። ከዚህም ቀጥሎ መርድ አዝማች አስፋ ወሰን ልጃቸውን መርድ አዝማች ወሰን ሰገድን በብረት ይሞታሉ የሚል ንግር አባታቸው ስለ ሰሙ ይጠነቀቁላቸው ነበር ይባላል። ከዚህ በኋላ የአቤቶ ያዕቆብ የታላቁ ልጃቸው የአቤቶ ፋሲል ልጅ ከአጹ ሱስንዮስ ጀምሮ የኢትዮጵያ ነገሥታት እየተባሉ እስከ ነገሥታት እስከ አጹ ተክለ ጊዮርጊስ ድረስ መናገሻ ከተማቸውን ጐንደር ላይ አድርገው በሙሉ ኢትዮጵያን ገዝተዋል። አቤቶ ፋሲል ገራም አቤቶ ሥግወ ቃል አቤቶ ተዝካር ቃልና ወይዘሮ ወለተ ማርያም እግዚአብሔር ለመፈጸም ለሚፈቅደው ሁሉ ምክንያት ይፈጥርለታል የተባለበት የሸዋ ባላባቶች የርስ በርስ ውጊያ አጹ ኢያሱን ወደ ሸዋ እንዲመጡ የእግዚአብሔር መንፈስ መራቸው። ነገር ግን ከወይዘሮ አትሞች ሆኖ ልጅ ሳያገኙ ብዙ ዘመን ሲኖሩ ልጃቸው መርድ አዝማች አስፋ ወሰን ከትምህርት ቤታቸው ትምህርታቸውን ፈጽመው ወደ አባታቸው ቤት ሲመለሱ ወይዘሮ አትሞች ሆኖ በሚኖሩበት አገር በኩል ሲያልፉ እዚያው አገር መሽቶባቸው እወይዘሮ አትሞች ሆኖ ቤት በእንግድነት ሲያድሩ ያባታቸው ቁባት መሆናቸውን ባለማወቅና ሴቲቱም የባላቸው ልጅ መሆናቸውን ባለማወቅ በግብረ ሥጋ ተገናኝተው መርድ አዝማች ወሰን ሰገድ ተፀነው። መርድ አዝማች ወሰን ሰገድ ሲያድጉ በናታቸው በወይዘሮ አትሞች ሆኖ በኩል የላስታና የጐንደር ቤተ መንግሥት ዘር መሆናቸውን ሲያውቁ አባታቸው አስፋ ወሰን ከሞቱ በኋላ መርድ አዝማች አትበሉ ራስ በሉኝ ሲሉ ቁይተው እንደ ገና ንጉሥ በሉኝ ማለት ጀመሩ የሚገባቸው ሆኖም በመገኘቱ ንጉሥም ራስም እየተባሉ ይጠሩ ነበር። በዚሁ ምክንያት የአምኃየስ ልጅ መርድ አዝማች አስፋ ወሰን ወሰን ሰገድን የወለዱት ወደ አባታቸው ቤት ከትምህርት ቤት ሲመለሱ ወይዘሮ አትሞች ሆኖን እግዛታቸው ሰላ ድንጋይ ስለ አገኙዋቸው ነው። አስፋ ወሰን ሲሞቱ ልጃቸው ወሰን ሰገድ ተተኩ አባታቸው በሕይወታቸው ሳሉ የመንዝ ባላባት የአፍቀራ ጐሌ ልጅ ወይዘሮ ዘነበ ወርቅ ባላቸው ሰው ገድሎባቸው የኀዘን ልብስ እንደ ለበሱ ለአቤቱታ ሲመጡ የወሰን ሰገድ አገልጋዮች አይተዋቸው ኖሮ ለወሰን ሰገድ የሴቲቱን ውበትና መልክ ዘርዝረው ቢነግሩዋቸው ሴቲቱን አግብተው ከዚሁ ጋብቻ ሣህለ ሥላሴ ስለ ተወለዱ ልጅ ስለ መውለዳቸው የምሥራች ወደ አባታቸው ቢልኩ ኢትዮጵያን አንድ አድርጎ የሚገዛ ምኒልክ የሚባል ይነግሣል እየተባለ በዚያን ጊዜ ይነገር ስለ ነበር አስፋ ወሰንም ጊዜው የደረሰ መስሏቸው ልጁን ምኒልክ በለው ብለው ላኩባቸው። የንጉሥ ወሰን ሰገድ ልጆች አቤቶ በኩሩና አቤቶ ሣህለ ሥላሴ ናቸው። ልጆቻቸው ከወይዘሮ በዛብሽ የተወለዱ አቤቶ ኃይለ መለኮት አቤቶ ሰይፉ ወይዘሮ ወሰን የለሽ ወይዘሮ በለጥሻቸው ከወይዘሮ ይመኑሻል የተወለዱ ወይዘሮ ተናኘ ወርቅ መርድ አዝማች ኃይሌ ወይዘሮ ጠንፍየለሽ ከሌሎች ልዩ ልዩ የባላባት ልጆች የተወለዱ ራስ ዳርጌ ወይዘሮ ብርቅነሽ ወይዘሮ አያህሉሽም ወይዘሮ ሙላተ ወርቅ ሲሆኑ ከሚስታቸው ከወይዘሮ በዛብሽ የተወለዱት አቤቶ ኃይለ መለኮት ከእርሳቸው ሞት በኋላ ባባታቸው አልጋ ተተኩ። አቶ በዛብህ እንደራሴነቱን ከመሾማቸው በፊት አጹ ቴዎድሮስ አቤቶ ምኒልክን ይዘው ወደ ጐንደር ሲሄዱ የንጉሥ ሣህለ ሥላሴን ኛውን ልጅ መርድ አዝማች ኃይሌን ነበር የሾሙት መርድ አዝማች ኃይሌ ጀት ዓመት ያህል በሥልጣን እንደ ኖሩ ሊሸፍቱ ማሰባቸውን አጹ ቴዎድሮስ ስለ ሰሙ እርሳቸውን ሽረው አሰሯቸው በእርሳቸው ፈንታ የነገሥታት ዘር የሌላቸውን አቶ በዛብህን ሾሙና ተመልሰው ወደ ጐንደር ሊሄዱ ሱሉ አቶ በዛብህን ጠርተው እኔን የከዳውን ሰው ሁሉ አመልክተኝ ብለው አዘዚቸው። አቤቶ ምኒልክ ምንም እንኳ ባ ዓመት ዕድሜያቸው ወደ በጌምድር ደብረ ታቦርን ቢሄዱና እዚያው ዓመት ያህል ቢቁዩ የእርሳቸው ያሥር ዓመት መለየት ጊዜ የሸዋን ነገሥታት የገዥነት መሥመሩን ያቋረጠው ቢመስል ያባታቸው መንግሥት ለባዕድ እንዳያልፍ የእግዚአብሔር ፈቃድ ስለ ሆነ ከአጹ ቴዎድሮስ እጅ አምልጠው ወደ አገራቸው ሲገቡ አቶ በዛብህ እመንገድ ቁይተው ጋዲሎ ላይ ሐምሌ ኛ ቀን ዓም ቢዋጉዋቸውም ጠላታችውን ድል አድርገው ባባታችወ ዙፋን ለመቀመጥ በቁ። ይህ ሁሉ ሲሆን አጹ ምኒልክ ባባቶቻቸው አልጋ እንደ ገና ለመቀመጥ አብቅቷቸው ንጉሠ ሸዋ ተብለው ሦስት ዓመት እንደ ነገው አጹ ቴዎድሮስ በየጊዜው ከዳተኛ እየተነሣባቸውና የእንግሊዝም ጦር ስላወካቸው አጹ ምኒልክን ለመከታተልና ወደ ሸዋ ለመምጣት ጊዜው ሳይፈቅድላቸው ቀርቶ በነገሠው ባደዳ ዓመታቸው ባ ዓም መቅደላ ላይ ሞቱ። ከዚህም በኋላ ግርማዊ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ገና አልጋ ወራሽ ሳሉ አጹ ቴዎድሮስ በሞቱ በሄኛው ዓመት ባ ዓም የእንግሊዝን አገር ሊጐበኙ ሄደው ስለ ነገረ ያዴ ቴዎድሮስን ዘውድና ልብሰ መንግሥት ይዘው ተመለሱ። ሚ ይሠይጥ የተባለው ሚናስ በጦርነቱ ውስጥ ተማርከው ወደ የመን አገር ምርኮኛ ሆነው ሄደው ስለ ነበረ እንዲሁም የግራኝ ልጅ ከታላላቅ የጦር አዝማቾች ጋራ ባጹ ገላውዴዎስ እጅ ተማርከው ነበረና የምርኮ መመላለስ ሆኖ የግራኝም ልጅ ነከጓደኞቹ ወደ አገሩ ሚናስም ከነዘመዶቻቸው ወደ አገራቸው ተመልሰው ገብተው ከአጹ ገላውዴዎስ በኋላ አልጋውን ወርሰው ዓመት ነግሠው ካረፉ በኋላ ልጃቸው አጹ ሠርጸ ድንግል ዉ ዓመት ነግሠው መንግሥቱ ከልጅ ልጅ እየተወራረሰ እስከ አጹ ያዕቆብ ከደረሰ በኋላ ያ ይነበር የተባለው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ከአቤቶ ያዕቆብ ልጅ ከገራም ፋሲል የሚወለዱት አ ሱስንዮስ ዓመት ነግሠው ካረፉ በኋላ የአቤቶ ያዕቆብ ዘርፍ ተያይዞ እስካሁኑ የቤተ መንግሥት ዘርፍ ድረስ እየቀጠለ መጣ።