Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ምዕራፍ አንድ ትምህርተ ክርስትና ፍ የክርስትና ትምህርትን ጀማሪው ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ፍ እርሱ ክርስቶስ ባይባል ኖሮ እኛም ክርስቲያን አንባልም ነበር የሐዋሥራ ፍ ክርስትና ተስፋ ነው ክርስቲያን ተስፋ አይቆርጥም የሚባለው ለዚህ ነው ክርስትና ራሱ ተስፋ ስለሆነ ክርስትና የሰማያዊት ርስት ዜግነት ነው ክርስትና አዲስ ሕይወት ነውይህ ብቻም አይደለም ክርስትና መከራ ነውክርስትና ፈተናም ነው ምክንያቱም ዘለዓለማዊ ህይወትን ለመውረስ መጋደል የግድ ነውና ቆሮ ፍ የዚህ ክርስትና መሠረቱ ደግሞ በቅድሚያ የዚህ ዓለም ፈጣሪና መጋቢ ማለትም አስገሂ አስተዳዳሪ ተቆጣጣሪ አለ ብሎ ማመመን ሲሆን ቀጥሎም የፈጠረው የሰው ልጅ በበደለው ጊዜ የሰውን ሥጋ ለብሶ ዓለምን ማዳኑን ማመን ያስፈልጋልይህም ነገረ ድኅነት የድኅነት ትምህርት ተብሎ ይጠራል እነዚህ ሁለቱ ዋና የክርስትና መሠረቶች ናቸው ነገረ ድኅነት ቀሩ ነገረ ድኅነት ስንል የድኅነት ትምህርት ማለታችን ነው የድኅነት ትምህርት የሚጀምረው ደግሞ ከሰው ልጅ አወዳደቅ ወይም በደል ነው ሩ ምክንያቱም በነገረ ድኅነት ትምህርት ሦስት ዋና ዋና አካላት አሉ ፅእግዚአብሔር የሰው ልጅ ኃጢአት እነዚህን ሦስቱን በነገረ ድኅነት አንፃር ስንመለከታቸው በሽታው ኃጢአት በደል ሲሆን ፈውስ ድኅነትመዳን ተብሎ ይጠራልየዳነው መላው የአዳም ዘር ሁሌ የሰው ልጅ ሲሆን ያዳነው ደግሞ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው ሰው ምን ሆኖ ነበር ከዕለተ እሁድ አንስቶ እስከ ዕለተ ዓርብ ከተፈጠሩት ፍጥረታት መካከል ሰው አዳም በዕለተ ዓርብ የተፈጠረ አራተኛ ፍጥረት ነውዘፍ ይህ የዕለተ ዓርብ ፍጥረት ብቻውን መሆን እንደሌለበት ፈጣሪው አስቦ ረዳት የምትሆነው ሔዋንን ከጎኑ አንዲት አጽምን አጥንት በመውሰድ ሥጋን አልብሶ ፈጠረለትዘፍ ሁለቱም በተድላ ሥጋና በተድላ ነፍስ በገነት ሰባት ዓመት ኖሩ ይሔ የሰው ልጅ ምዕራፍ አንድ የህይወት ጉዞ ነበርከሰባት ዓመት በኋላ ግን ይህ ምዕራፍ በራሱ በሰው ልጅ ተዘጋ የሰው ልጅ ብላ የተባለው አላጠግብህ ግዛ ንዳ የተባለው አላረካህ ብሎት የሰይጣንን ትዕዛዝ ከፈጣሪው ትዕዛዝ አስበልጦ አትብላ የተባለውን በልቶ በአምላኩና በእሱ መካከል ሆና የፍጡርና የፈጣሪን ድንበር የለየችውን ፍሬ ቆርጦ በላበዚህም ፈጣሪውን አሳዘነ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ የሰውን ልጅ ለሰባት ዓመት ከኖረበት ገነት አስወጣው መርገመ ሥጋና መርገመ ነፍስ ጣለበትዘፍ በዚህም ምክንያት የሰው ልጅ ለ ዘመን ክብሩ ተገፎ ከእግዚአብሔርና ከመላእክት ጥበቃ ርቆ የሥጋ ሞትና የነፍስ ሞት ሰልጥኖበት የጨለማና የቁሳቁስ ኑሮ ተጭኖበት ኖረ በአጠቃላይ የሰው ልጅ አታድርግ የተባለውን በማድረጉና በክፍ ምኞቱ የዲያብሎስን ዓይነት ስህተት ስለተሳሳተ የዲያብሎስን ዓይነት አወዳደቅ ወደቀ ስለዚህም ሁሉንም ዓይነት ሞት ሞተ ሞተ ኅሊናሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስ ላ ፈ ዒ ሏፈ ዒ ሞቲ ኅሊናየኅሊና ሞት ማለት የንጽሐ ልቡናየልብ ንጽሕና እጦት ማለት ነው አዳም ይህንን የኀሊና ሞት ሲሞት የክፉ አሳብ ተገዥ ሆነ ማለት ነውምድር ካንተ የተነሳ እሺህና አሜከላ ታበቅላለች የሚለው እርግማን በስሙ ብቻ የሚታይ አይደለምምድር የተባለው የአዳም ሰውነት ሲሆን እሾህና አሜከላ የተባሉት ደግሞ ፍትወታትና ልዩ ልዩ የክፋ አሳብ ዓይነቶች ናቸውዘፍ ሞተ ሥጋየሥጋ ሞት ማለት የነፍስ ከሥጋ መለየትና ወደ አፈርነት መመለስ ማለት ነው ሞተ ነፍስየነፍስ ሞት ማለት ከሥጋ ሞት በኋላ የነፍስ ተጓዘው ወደ ሲኦል ኋላም ወደ ገሃነም የዘለዓለም እሳት መጣልና መወርወር ማለት ነውይህም ዘለዓለማዊ ፍርድ ይባላል እንግዲህ የሰው ልጅ ሁለተኛው የሕይወት ምዕራፍ ደግሞ ይኹነው በዚህ የህይወት መስመር በመከራና በስቃይ በጨለማና በሞት ውስጥ ዘመን ኖረ ከዚህ ዘመን በኋላ ለሰው ልጅ በተሰጠው ተስፋ መሠረት የዘመኑ ፍጻሜ በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር ወልድ ሰው ሆነና የሰውን ልጅ አዳነው ገላ የእግዚአብሔር ሰው መሆን ይህንን ምስጢር ለማጥናት ሦስት ጥያቄዎችን መጠየቅና እነሱን ማብራራት በቂ ነው እግዚአብሔር አምላክ ሰው ሆነ ስንል በአጭር አገላለጥ የእኛን ሥጋ ተዋሕዶ ማለታችን ነውይህ የተፈጸመው ደግሞ በድንግል ማርያም ምክንያት ሲሆን ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል እግዚአብሔር ወልድ በተለየ አካሉ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ ሰው ሆነ ማለታችን ነው ይህም የሆነው የሰውን ልጅ ለማዳን ነውዕብ የሰውን ልጅ ከምንድነው የሚያድነው ብለን ከጠየቅን ደግሞ ከላይ ሰው ምን ሆኖ ነበር ስንል የዘረዘርነው ምላሽ ይሆናል እንዴት ሰው ሆነ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው የሆነው ሥጋን የተዋሐደውበመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል ብስራት ከቅድስት ድንል ማርያም ነውሉቃ ታዲያ ሰው ሲሆን በተዋሕዶ ነው ይህም ማለት በመለወጥ በመጠፋፋት ማለትም መለኮት ሥጋን ሥጋም መለኮትን በመዋጥና በመለወጥ አይደለም ማለት ነውበመሆኑም መለኮትና ትስብእት ሥጋ ከተዋሐዱ በኋላ አንድ አካል አንድ ባሕርይ አንድ ፈቃድ አንድ አገዛዝ ብለን ሁለት አንልም ስለዚህ እግዚአብሔር ወልድ በተዋሕዶ ነው ሰው የሆነው ስንል አምላክነቱን ሳይለቅ ነው ማለታችን ነው መቼ ነው ሰው የሆነው ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው የሆነው ከላይ እንደተጠቀሰው ሆኖ ዘመኑ ዘመነ ማቴዎስ ሲሆን ወሩ ወርኃ ታኅሣሥ ኛ ቀን ነው ዕለቱም ዕለተ ማክሰኞ ከሌሊቱ በኛው ሰዓት በቤተልሔም በከብቶች በረት ተወለደሉቃ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ እግዚአብሔር ወልድ ሁለት ልደታት እንዳላት የምናምነውና የምናስተምረው ይህንን ይዘን ነው በነገረ ድኅነት የሰው ልጅ ድርሻ ይህንን ርዕስ ከማብራራት በፊት የሚቀድም አለበቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ሁለት ገጽታዎች አሉት የተፈጸመ ድኅነትና ያልተፈጸመ ድኅነት ብለን በቀላሉ ማስቀመጥ እንችላለን አንድ ሰው ድነሃል ተብሎ ሲጠየቅ አዎ ወይም አልዳንኩም ከማለቱ በፊት ስለየትኛው ድኅነት የምንለው የሰው ልጅ ለ ዘመን በአዳም በደል ሲጠየቅ ከነበረበት ህይወቱበክርስቶስ መከራና ሞት ነጻ መውጣቱን ነውሮሜ አሁን ማንም ሰው በአዳም ኃጢአት አይጠየቅም የተዘጋው ገነት ተከፍቷልየተከፈተው ሲኦልም ተዘግቷልማንም ያለፈቃዱ እንደ ኦሪቱ ጊዜ ወደ ዚያ አይጣልም ያልተፈጸመ ያልነው ደግሞ መንግሥተ ሰማያትን ገንዘብ ማድረግ መውረስ ማለታችን ነው ምንም ሰውን መንግሥተ ሰማያትን ተስፋ ያደርጋልእንጂ አልወርሳትም ማለትም መንግሥተ ሰማያት ለሰዎች ሰጥታለች እንጂ አልተወረሰችም ሥለዚህ ነው ታገኙ ዘንድ ሩጡ በርቱና ተጋደሉ እያለ መጽሐፍ ቅዱስ የሚመክረን የሐዋ ኛ ቆሮ እነዚህ በነገረ ድኅነት የሰው ልጅ ድርሻ ያለው በመጀመሪያው ድኅነት ሳይሆን በሁለተኛው ድኅነት መሆኑን ማተዋል ይገባል አሁን እነዚህን ድርሻች በየተራ እንያቸው ሃይማኖት የሰው ልጅ የተሰጠውን ድኅት አምኖ ለመቀበል ኋላም በእጁ ለማድረግ ሃይማኖት ያስፈልገዋል ያለ ሃይማኖት ማመንም ሆነ ተስፋ ማድረግ የማይቻል ነውዕብ ሃይማኖት የሁሉ ነገር መሠረት ነው ቀጥሎ በዝርዝር የምናያቸው ድርጊቶች ሁሉ የሚከናወኑት በሃይማኖት ብቻ ነው ሃይማኖት በቀጥታ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር የሚገኝበት መንገድ ነውኤር ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚጠይቀውም መንገድ ስለሆነ ነው መንገድ ከተሳሳተ ደግሞ ወደፈለግነውና ወደ አስበነው ሳይሆን የሚያደርሰን ወደፈለግነውና ወደ አላሰብነው ቦታ ነው ስለዚህም ሰው የቀድሞውንና የተሰጠውን ድኅት አምና ለመቀበልና በዚህ ድኅነት የተተወላትንና የተቸረውን ገንዘብ ለማድረግ ለመረከብትክክለኛ ሃይማኖት ያስፈልገዋል ማለት ነው ጥምቀት መጽሐፍ ቅዱስ ያመነ የተጠመቀ ይድናል ያለው ለዚህ ነው መጠመቅ ማለት መወለድ ማለት ነው እኛ ስንጠመቅ ከሥላሴ የጸጋ የባሕርይ ያልሆነ ልጅነትን እናገኛለን ይህንን መወለዳችንንም በእምነት ሃይማኖት እንቀበለዋለን የሃይማኖትና የጥምቀት ትስስር ከዚህ ይጀምራልማር እግዚአብሔር ርስቱን መንግሥቱን ሊያወርሰን ሲፈልግ ዳግመኛ ልጁ እንድንሆን ጥምቀትን ሠራልን በዚህ ዓለም ሕግ ልጅ መሆን ለወራሸነት ያበቃልስለዚህ ልጅ እያለ ሌላ አካል አይወርስም ያለ ጥምቀት ልጅነት የለም ያለ ልጅነት መውረስ የለም መዳን መውረስ መንግስተ ሰማያትና እጅ ማድረግ ከሆነ መጠመቅ ወሳኝ ነው ማለት ነው የጥምቀትን አመሠራረትና አፈጻጸም በቱ አዕማደ ምሥጢርና በሃቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ትምህርቶች መመልከት የግድ ይላል ቁርባን ቁርባን በሁለት ወገን ይፈጸማል አንደኛው ማንኛውም ክርስቲያን ከእግዚአብሔር የጸጋ ልጅነትን ለመቀበል ከተጠመቀ በኋላ ሲሆን ሁለተኛው ከ ዓመት በኋላ በንስሐ አባቱ ምክርና ስርየተ ኃጢአት እየታገዘ ከንስሐ በኋላ በየጊዜ እየተቀበለ የሚኖርበት ህይወት ነው ቁርባን የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው ያለዘሂህ ደግሞ የዘለዓለም ህይወትን ገንዘብ ማድረግ እንደማይቻል እራሱ ክርስቶስ በግልጥ አስተምሯልዮሐ መልካም ምግባር አንድን ክርስቲያን ከሌሎቹ ሰዎች ለየት የሚያደርገው በማኅበራዊ ህይወት ባለው በጎ ተሳትፎ ነው ይህም ማለት ከቅን ልቡና በመነጨ የሚያከናውናቸው መልካም ምግባራት ናቸው እነዚህ ደግሞ ሰውን ሁሉ እኩል ማየትና ማክበር ለታላላቆች ብቻ ሳይሆን ለታናናሾችም መታዘዝ በኑሮ በሥራ በትምህርት ቦታ ሁሉ ለሰዎች መልካም አርአያ መሆንን ሁሉ ያጠቃልሳሌሉ ክርስቲያን ሌሎቹ እንዝረፍ ሲሉ እሱ እንስጥ ይላል ሌሎቹ እንጣላ ሲሉ እሱ እንታረቅ ይላል እግዚአብሔርን ብቻ ተስፋ አድርጎ በትክክለኛው የሕይወት ጎዳና ይጓዛልበዚህም በትዳሩ በሥራ ቦታው በቤተሰብ አመራሩ በልጆችም አስተዳደጉ በአጠቃላይ በምድራዊ ኑሮው ከዚህች ምድር ሳይለይ አሱ ግን ልዩ ነው ይህን ሁሉ የሚያደርገውም ዘለዓለማዊ ድኅነትን በእጁ ለማስገባት ነው መንፈሳዊ ተጋድሎ ክርስትና ተጀመረች እንጂ አልተፈጸመችም ተጋድለን የምንወርሳት መንግሥት ነች የተሰጠችን መጋደል ማለት ምን ማለት ነው ስንል በአጭሩ መቀበል መጠበቅና ማስረከብ ነው ከላይ በዝርዝር እንዳየነው ሰው በሃይማኖት የተሰጠውን ድኅነት ይቀበላልያንን ደግሞ ተገቢውን እየሠራ ይጠብቃል በኃላም ለሚቀጥለው ትውልድ ያስረክባልለእኛ አባቶቻችን እንዳስረከቡን ማለት ነው መጋደል ማለት በአጭሩ ይሔ ነውስንጋደል የምናከናውናቸው ነገሮች አሉ እነዚህ ሃይማኖቱ የሚፈቅድልንና ወሳኝ የሆኑ ነገሮች ምግባራት ናቸው ሥነ ምግባር የምንላቸው ማለት ነው እነሱም ጸም ጸሎትስግደትምጽዋት ወዘተ ብለን በዝርዝር ልናስቀምጣቸው የምንችላቸው ናቸው ቤተ ክርስቲያናችን ደግሞ እነዚህን ታሳቢ ያደረገ ሥርዓት አላት ለምሳሌ አጽዋማትን ብንወስድ በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ማንኛውም ክርስቲያን ከ ዓመት ዕድሜ ጀምሮ እንደየአቅሙ ከንስሐ አባቱ ጋር እየተማከረ የሚጾማቸው አጽዋማት አሉ እነዚህን መጸም ለሁሉም ክርስቲያን ግዴታ ነው ሃይማኖት ያለ ምግባር ዋጋ እንደሌላት የሚነግረን ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ ነውያዕ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በነገረ ድኅነት ከሌሎች የዕምነት ተቋማት ያላት ልዩነት ። የተዋሕዶ ጽንሰ አሳብ ላይ ፍ ተዋሕዶ ማለት የመለኮትና የትብስእት ሥጋ ፍፁም መዋሐዱ ሲሆን ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ መሆን ማለት ነው ፍ ተዋሕዶ ማለት ከተዋሕዶ በኃላ ሥጋ የሥጋን ሥራ መለኮት የመለኮትን ሥራ ይሠራል ማለት አይደለም ፍ ተዋሕዶ ማለት የሥጋና የመለኮት መዋሐድ ቱሳሔሚጠትርባ የነገረ ድኅነትን እናበስራለንም እንሰብካለንም ከላይ እንዳየነው ድኅነት ሁለት ገጽታ ስላለው በመጀመሪያው ገጽታው የምስራችን ነው የምናውጀው ማለትም ድነናል ድናችኋል እንላለንበሁለተኛው ገጽታው ደግሞ ዳኑ ለመዳንም ይህንና ያንን አድርጉ ብለን እንደብካለንሌሎች የሃይማኖት ድርጅቶች ግን ይህንን አጥርተው ስላሳስቀመጡ አንድ ጊዜ ድነናል ስሊዚህ ጾም ጸሎት ስግደት ወዘተበአጠቃላይ ሥራ አያስፈልግም እንዲሁ በጸጋው ድነናል እያሉ ያተምራሉ ለዚሁም መጽሐፍ ቅዱስን ይጠቅሳሉሮሜ ይህ ማለት ግን በፊት የተደረገውን የአዳምን በደልና ከዚያም ያለ እኛ ሥራ በክርስቶስ ፍቅር ብቻ እንዲያው በጸጋው የመዳናችንን ነገር ነው የሚነግረን በዚሁ ምዕራፍ ዝቅ ብሎ ይህም በፊት የተደረገውን ኃጢአት በእግዚአብሔር ችሎታ ስለመታው ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው ይለናልቁ እኛ ሁላችን ከአዳም ኃጢአት የዳነው በሥራችን አይደለም ስለዚህም የሚያስመካን ነገር የለምኤፌ ይህ ማለት ግን ለሁለተኛው ድህነት መንግሥተ ሰማይን ለመውረስ ነሥራ ተጋድሎአያስፈልግም ማለት አይደለም ከላይ እንደተዘረዘረው ማመንመጠመቅመቁረብ መንፈሳዊ ተጋድሎ ያስፈልጋል ጥበብ ይሉሃል እውቀት ይሉሃል እግዚአብሔርን መፍራት ነው ፈቃዱም ምግባርና ሃይማኖት ነውመጽ ሲራክ ሯሥራ በሃይማኖት ወሳኝ ነው ማቴ ራዕ ማቴ ራፅ ዮሐ ማቴ ራዕ መዝ ምሳ ማቴ ሮሜ ማጠቃኃቃለያ ሌሎች ዝርዝር ሁኔታዎች እንዳሉ ሆነው እኛ ከሌሎች ዕምነት መሰል ተቋማት የምንለይበት የነገረ ድኅነት አስተምህሮ የሚያጠነጥነው በዋናነት በሁለቱመሠረተ አሳቦች ላይ ነው ማለት ነው እነዚህም ከላይ የተጠቀሱት ሲሆኑ የተዋሕዶ ትርጓሜና ጽንሰ አሳብ አንደኛው ሲሆን ሁለተኛውም የነገረ ድኅነት ትርጓሜና ጽንሰ አሳብ ይሆናልእነዚህን ማዕከል ያደረጉ ሌሎች በርካታ ጉዳዮችንም እንዳሉ መዘንጋት የለበትም ምዕራፍ ሁለት መንፈሳዊ ሕይወት በከፍተኛ ትምህርት ተቋም መንፈሳዊነት ትርጉም መንፈሳዊ የሚለው ቃል መነሻው መንፈስ የሚለው ቃል ነው ያለ መንፈስ ቅዱስ መንፈሳዊ መሆን አይታሰብም ፍ ኢትዮሏያ ኢትዮሏያ ተብላ እኛን ኢትዮሏያዊያን እንዳስባለችን ሁሉ እግዚአብሔርም መንፈስ ተብሎ ነው እኛን መንፈሳዊ ያስባለን እግዚአብሔር መንፈስ በው እንዲል ዮሐ ብ ፍ ሥለዚህ መንፈሳዊ ለመባል በመጀመሪያ መንፈስ ቅዱስን ገንዘብ ማድረግ ያስፈልጋል በእና በ ቀናችን ከሥላሴ በተወለድን ጊዜ መንፈስ ቅዱስን ገንዘብ ስናደርግ ያኔ መንፈሳዊ እንባላለን ቻ ቻ መንፈሳዊ ማነው ፍ መንፈስ ቅዱስ ያደረበትመንፈስ ቅዱስን ገንዘብ ያደረኘገ በረቂቅነት ጠጠለቀ ከግዙፍ ዓለም ስሜትና አሳብ የራቀ ፍ ሥጋዊ ፈቃድን ሥጋዊ ሥራን የሸሸ ከሥጋ ብቻ ያልተወለደ ዮሐ ፍ የጸጋ ሃይማኖት ያለው ፍፁም ፍቅር ያለው ፈሪሃ እግዚአብሔር ገንዘብ ያደረገ መንፈሳዊ ቅናት የሚና መንፈሳዊነትና ዕውቀት ሁ ሁለቱ የተለያዩ ግን ደግሞ ምንጫቸው አንድ የሆኑ ናቸው ሁለቱንም በአንድ ይዞ መጠቀም ይቻላል ሁ ዕውቀት ስንል ግን ለሁለት ከፍለን ማየት እንችላለን « ሥጋዊ ዓለማዊፀርሀዉሃ እውቀትና ቻ ቻ ቻ ቻ ቻ ላ ሏፌ ዒሏ ዒ ዷፌ ኗሪ ኗሪ ጻ መንፈሳዊ እውቀት መንፈሳዊውን ዓለም በዕውቀት መመርመር አይቻልም ይልቁንም በሥጋዊ ዕውቀት በመንፈሳዊነት ግን ሁሉን መመርመር ይቻላልኛ ቆሮ እግዚአብሔር በእውቀት ሳይሆን በመንፈሳዊነት ነው የሚገለጠው ዕውቀትና መንፈሳዊነት ፍፁም ተጻራሪ ነገሮች አይደለም የሚጣሉበት ሰዎች ናቸው ዕውቀትን ለመንፈሳዊነት ማዋል መንፈሳዊነትንም ለእውቀት ማሳለጫ መጠቀም ይቻላል መንፈሳዊነት ያለ እውቀት ዕውቀት ያለ መንፈሳዊ ጅልነት ነው ዕውቀትም ያለመንፈሳዊነት እብደት ነውብፁዕ አቡነ ዮሴፍ ሟቹ መንፈሳዊነትና ምርምር ከላይ እንደተቀመጠው ነው መንፈሳዊ ምርምር ያስፈላጋል ትርጓሜው ቅኔው ድጓው ይኹ ሁሉ ምርምር ነው ሥጋዌ ምርምርም ያስፈልጋል ዕውቀቱን የሰጠን እግዚአብሔር ነው ምርምሩን ግን ለምን ጥቅም እንደምናውለው ማወቅና መረዳት መጠንቀቅም ይገባል ሁሉን መርምሩ ሁሉን ፈትኑ የሚጠቅመውን ግን ያዙ ተብለናልኛ ተሰ ሁሉም ተፈቅዶልናል ሁሉም እንደማይጠቅመን ደግሞ ተናግረናልኛ ቆሮ በዚህ ሁሉ መጽሐፍ ቅዱስ በጥንቃቄ መመራመርን ይፈቅዳልኛ ቆሮ አዲስ ነገር በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አንድ ሰው ወደ ከፍተኛ ተቋም ሲገባ የሚያጋጥሙት በርካታ አዳዲስ ጉዳዮች ይኖራሉ እነዚህ ጉዳዮች ግን ለሁሉም አዲስ ላይሆኑ ይችላሉአዲስ የሚሆኑብን ጉዳዮች የሚወሰኑት እንደየ አስተዳደጋችንና እንደየምንኖርባቸው አካባቢዎች ነው ለምሳሌ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ለአንድ ከገጠር ለመጣ ተማሪና ከሞቀ ከተማ ለመጣ ተማሪ እኩል የሆነ አዲስ ነገር ላይኖራቸው ይችሳላልቢሆንም ግን የጋራ የሆኑ አዳዲስ ጉዳዮችም ሊኖሩን ይችላልለምሳሌ ከቤተሰብ መለየት ራሱን በራ እያስተማረ ከቆየው በስተቀር ሁላችንም ማለት ይቻላል በዚህ ሥፍራ ስንገኝ ከቤተሰቦቻችን ተለይተን ነው ይሔ በራሱ ሁለት ነገሮችን እንድንሆን ይጋብዘናል መፍራት ፍ ብቻዬን ነን ምን ያጋጥመኝ ይሆን ፍ ሁሉን የማደርገው እኔ ነኝ እንዴትስ እወጣው ይሆን ፍ አደራ ተቀብዬ ነው የመጣሁት ቤተሰቦቼን እንዴት አስደስት ይሖን ፍ ናፍቆቱን አሳቡን እንዴት እችለዋለሁ ነሃጻ መሆን ው ኡፋ ተገላገልኩኝ ከዚህ በኋላ ተቆጣጣሪ የለኝም ሁ የራሴ አለቃ ራሴ ነኝ ያሻኝን እንደልቤ ማድረግና መሆን አችላለሁ እነዚህ ሁለት ጽንፎች ማዕበል እየሆኑ ተማሪውን ሊያንገላቱት ይችላሉ ይሁን እንጂ ሁለቱም እንደንፋስ ፈጥነው ያልፋሉ የሚያዋጣው አብሮ መንፈስ ሳይሆን ጥግ ይዞ ማሳለፍ ነው ስብጥር ስብጥሩ በብዙ መልኩ ነው የሚፈጠረው የጾታ ስብጥር የአመለካከት የዕውቀት የሃይማኖት የቋንቋ የባሕል ወዘተ ይህንን ስብጥር ላ ዴ ሏ ዒ ላ እንደበጎ አጋጣሚ መጠቀም ያስፈልጋል ምክንያቱም ሰዎች ሆነን በዚህች ምድር ስንኖር በራሳችን ምሉዕ አይደለንም አንዳችን ከአንዳችን ወስደን ጉድለታችንን የምንሞላባቸው በርካታ ነገሮች አሉ አንዳንድ ስግብግቦች ይህንን መለያየትስብጥር እንደ ጥሩ አጋጣሚ ወስደው ልዩነቱን ብቻ እያሳዩንና እያሰፉት መጠቀሚያ ሊያደርጉን ያስቡ ይሆናል ግን ይህም እንዳለ አውቀን ልንጠነቀቅ ያስፈልጋል በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚገጥሙ ፈተናዎችና መፍትሔዎቻቸው ጻ ፈተና በየትም ቦታ አለ ይኑር እንጂ መውጪያ የሌለው ፈተና የለም ኛ ቆሮ « ያለፈተና ዋጋ ያለመከራ ጸጋ እንደሌለ ማወቅ ያስፈልጋል ፈተናው ከየት እንደሚነሳ መረዳት ያስፈልጋል ምክንያቱም ምንጩ ሁለት ነው ከውስጥና ከውጭ « ከውስጥ ሲባል ከሥጋ ፈቃድ ማለት ነው ከውጭ ሲባል ከሥጋ ፈቃድ ማለት ነው ከውጭ ሲባል ደግሞ ከአካባቢያችንና ከጓደኞቻችን ከውሎና አዳራችን ማለት ነው ፍጻሜው ግን ከሰይጣን ማለታችን ነው በዚህ መሠረት በግቢ ጉባኤ በብዛት የሚስተዋሉ ፈተናዎች የሚከተሉት ናቸውይህ ሲባል ግን በጎላውና በተረዳው ሁልጊዜም በሚታየው ለመናገር እንጂ ሌሎች የሉም ማለት አይደለም ፍ ወጣትነትና የጾታ ጉዳዮች ፍ ክፍ ባልጀርነት ፍ ጭንቀት ፍ ለሱስ ተገዥነት ፍ የመናፍቃን ቅስጣ ፍ የዘመናዊነት የተዛባ ትርጉም ፍ አስተዳደራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ፍ የጓደኛነት አዎንታዊና አሉታዊ ተጽዕኖዎች ወ ዘ ተ ከላይ የተጠቀሱትን ፈተናዎችና መፍትሔዎች አስመልክቶ አጠቃላይ የሆነ ነገር እናስቀምጥ ምርመራ በመጀመሪያ ደረጃ ከላይ የተዘረዘሩት ሁሉ በእርግጥ ፈተና ናቸው ብለን እንጠይቅ ማለተም በጥንቃቄ ብናደርጋቸው የማይጎዱንና ፈጽሞ አጠገባችን እንዳይደርሱ የምናርቃቸው የትኞቹ ናቸው ይህንን ለይቶ ማስቀመጥ በራሱ አንድ መፍትሔ ነው በመሆኑም ጻ የጾታ ጉዳይ « ጓደኝነት ዘመናዊነት ወጣትነት አስተዳደራዊና ፖለቲካዊ ጉዳይ ወዘተ እነዚህ አይነኬ ሳይሆኑ በከፍተኛ ትኩረትና ጥንቃቄ በሊጠገኑና ልናስኬዳቸው የሚችሉ ጉዳዮች ናቸው እሾኋ ተፈርቶ ጽጌረዳ አበባን አታስፈልግም አይባልምና እሾኋን ግን መጠንቀቅ ያስፈልጋል አንዳንዴም እየተወጉ መቻልና መጽናትም ግድ ይላልበሌላ መልኩ ጭንቀት የሱስ ተገዥ መሆን ሃሦ መናፍቅነት ክፍ ባልንጀራ ወዘተበፍፁም አይነኬ የሆኑ አጠገባችን እንዲደርሱ ልንፈቅድላቸው የማይገቡ ነገሮች ሲሆኑ ድኅነት ነገር ሊፈልጉን ሊደርሱብንእንደሚችሉ አውቀን እንደአመጣጣቸው ለመመለስ ቆርጠን መዘጋጀት ይኖርብናል መከላከያዎቹም ቀ የዓላማ ሰው መሆን ቀሩ ጊዜን በዕቅድና በአግባቡ መጠቀም ሩ ጓደኛ አለማብዛት ጓደኛ ማብዛት ወሬ ማብዛት ነው የሚል አባባል አለ ቀሩ በሌሎች መስመር በሳቱ ሰዎች አለመፍረድና ጣት አለመቀሰር ቀሩ ራስን እንደማይሳሳቱ አድርጎ አለመገመት ቀሩ የጸሎት ሰው መሆን ሩሩ ከቤተ ክርስቲያን ከመንፈሳዊ ወንድሞችና እህቶች አለመለየት ውጤታማነት በቀለም ትምህርት ሩ በቀለም ትምህርት ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ማሰብ ሩ የመጡበት እዘህ ቦታ የተገኙት ዋናው ምክንያት ይኹ መሆኑን መረዳት ቀደም ሲል በግቢው የቆዩ ተማሪዎች የሚያሳዩትን መንገድ የሚሰጡትን እገዛ ሳይንቁ መከታተል ሩ እኔ መንፈሳዊ ነኝ ብሎ አስቦ ፈተናን እንደ ጠንቋይ በግምት ለመስራት አለመሞከር ሩ መንፈሳዊ ብንሆንም እግዚአብሔር ቢረዳንም ድርሻችንን አውቀን መተግበር ይጠበቅብናል ሉላዊነትግሎባሳይዜሽን ከላይ ያነሳነውን በቀለም ትምህርት ውጤታማ እንዳንሆን እንቅፋት ከሚሆኑብን ጉዳዮች አንዱ ይህ ሉላዊነት ነው ሌላዊነት ሁለት ገጽታዎች አሉት ይህንን ከማኅራት በፊት ሉላዊነት ስንል ምን ማለታችን እንደሆነ እንይ ሌላዊነት ማለት ሁለቱ ገጽታዎች ጠቀሜታውና ጎጂው ነው እንደአጠቃቀማችን ይወሰናል ምዕራፍ ሦስት የግቢ ጉባዔያት ቦታ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ውስጥ የማኅበረ ቅዱሳን ቦታ ማኅበረ ቅዱሳን በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ተሰባስበው በገዛ ፈቃዳቸው መንፈሳዊ ተግባራትን እንደሚከውኑትና በቤተ ክርስቲያን ታዛም ሆነ በመንደር እንደሚሰባሰቡት የጽዋ ማኅበራት አይነት አይደለም ወይም መንግሥታዊ እንዳልሆኑት የእርዳታ ድርጅቶችክአይደለም ወይም እንዳንዶች እንደሚሉት የቅዱሳን ስብስብም አይደለም ማኅበረ ቅዱሳን በቅዱስ ሲኖዶስ መልካም ፈቃድ ደንብና መመሪያ ጻድቅነት የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ለማገዝ የተመሠረተ ማኅበር ነውማኅበረ ቅዱሳን መባሉም እግዚአብሔር ያከበራቸው የነቢያት የሐዋርያት የጻድቃን የሰማዕታት በአጠቃላይ የቅዱሳን ገድል ትሩፋትና አማላጅነት የሚዘከርበት በመሆኑ ነው በኢትዮሏያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰትቤት ማደራጃ መምሪያ የማኅበረ ቅዱሳን መዋቅር ቅዱስ ሲኖዶስ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽቤት ት የሰትቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኝ የማኅበረ ቅዱሳን ጠቅላላ ጉባዔ ሃ ኦዲትና ኢንስፔክሽን አገልግሎት ክፍል ሃ ሥራ አመራር ጉባዔ ኘ ኦዲቶርያል አገልግሎት ሃ ሥራ አስፈጻሚ ጉባዔ ሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት የሰው ኃይል አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል ጥናትና ምርምር ማዕከል ዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ክፍል ፍይናንስ አገልግሎት የሕግ አገልግሎት ፍ ኘ ና ኅትመትና የቅዱሳት መካናት የሀገር ውስጥ ሙያ የውጭ ልማት ኤሌክትሮኒክ ልማትና የጥናት ማዕከላት ግቢ አገልግሉትና ማዕከላት ተቋማት ስ ሚዲያ አገልግሎት ጉባዔያት አቅም ማደራጃና አስተዳደር ር ማስተባበሪያ ዋና ማጎልበቻ ዋና ማተባበሪያ ዋና ዋና ክፍል ክፍል ክፍል ክፍል ማዕከላት የማኅበረ ቅዱሳንና የግቢ ጉባዔያት ትስስር የሚለው ቃል የማኅበረ ቅዱሳንና የግቢ ጉባዔያትን ነገር ለመግለጽ ያንሳል ያለ ማኅበረ ቅዱሳን ግቢ ጉባዔያትን ያለ ግቢ ጉባዔያትም ማኅበረ ቅዱሳንን ማየትና መግለጽ አይቻልም ሁለቱ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው ማኅበረ ቅዱሳን ስለ ግቢ ጉባዔያትና ለግቢ ጉባዔያት የተመሠረተ ነው ግቢ ጉባዔያትም በማኅበረ ቅዱሳን ጫንቃ ላይ የሚኖሩ ናቸው ለዚህም ነው ማኅበረ ቅዱሳን አላማዬ ብሎ ካስቀመጣቸው ነጥቦች መሃል ቕዥቹቿዌ ቿቾ ጆቹ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚማሩ ወጣቶችን በማኅበሩ ሥር አደራጅቶ የኢትዮሏያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እምነት ሥርዓትና ትውፊት እንዲማሩ እና የአባቶች ተተኪ እንዲሆኑ ማድረግ የሚለውን በግንባር ቀደምትነት ያስቀመጠው የግቢ ጉባዔያት ውስጣዊ አደረጃጀትና የአባላቱ ሱታፌ ፍ የግቢ ጉባዔያቱን መዋቅር ዶክመንት ማየት መንፈሳዊ አገልግሎት በግቢ ጉባዔያት ፍ ይህ አገልግሎት በሁለት ተከፍሎ ሊቀመጥ ይችላል ራስን የሚያገለግሎበት ወደ ቤተ ክርስቲያን መሔድ ቃለ እግዚአብሔርን መማር ላ መጸምመጸለይማስቀደስመቁረብ ሌላውን ማገልገል የአገልግሎት ክፍሎችን በመቀላቀል « የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት የአብነት በመማር በዲቁናበቅድስና በሥርዓት ማገልገል።