Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
እውቅና ውጪ የተደረገና የጋራ እዳ መሆኑና የፍርድ ባለመብቶች ገንዘብ ተከፍሎ አለቀ ድረስ ወለድ እንዲታሰብ ማድረግ ተጠሪ ያለአግባብ እንዲበለጽግ አመልካች ደግሞ የመቃወም አመልካች ነበር አመልካች ያቀረበዉ የሰበር አቤቱታ ተመርምሮ በአመልካች ደንበኛና በአቃቤ ህግ መካከል በተመሳሳይ ጉዳይ ክስ ሊቀርብባቸዉ አይገባም በማለት አመልካች ያቀረቡት መቃወሚያ የክስ ክርክር የጥብቅና ሙያን የሚያጎድፍ ተግባር በደንበኛዉ ወይም በሌላ ሰዉ ላይ መፈጸም ከባድ የዲስፕሊን ጥፋት መሆኑን የሚደነግግ ነዉ።
ክርክሩ በመጀመሪያ የታየው በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ነው በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመልካች ተከሳሽ ተጠሪ ደግሞ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል የክሳቸው ይዘትምፁ ከአመልካች ጋር ጥር ቀን ዓም በባህላዊ መንገድ ጋብቻ ፈጽመው አብረው የቆዩ መሆኑን አሁን ግን በመካከላቸው በተፈጠረው አለመግባባት በትዳር መቀጠል የማይችሉበት ደረጃ ላይ ስለደረሱ ፍርድ ቤቱ የማሰላሰያ ጊዜ መስጠት ሳያስፈልጋቸው በመካከላቸው ያለው ጋብቻ ፈርሶ የፍቺ ውሳኔ አንዲወሰንላቸው አመልካች ላይ ክስ አቅርበዋል አመልካችም ለቀረበው ክስ የሰጡት መልስ ተጠሪ ጋር የፈጸሙት ጋብቻ አንደሌለ ነገር ግን ተጠሪ ጋብቻ ተፈጸመበት ባሉበት እለት ለተጠሪ ቀለበት ሲያደርጉ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የተዘጋጀው ዝግጅት የቀለበት ስነስርዓት አና ወደፊት እንደሚጋቡ ቃልኪዳን የገቡበት የመተጫጨት ስርዓት አለመሆኑን እና ይህ እውነትም ተጠሪ በራሳቸው ጥቅምት ቀን ዓም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወሳኝ ኩነቶች ጽቤት ቀርበው ያላገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል ይህም ማስረጃ አለማግባታቸውን የሚገልጽ በተጠሪ እጅ የሚገኝ ሲሆን በዚህ ማስረጃ የሚያረጋግጡ መሆኑን ሌሎች ማስረጃዎች የሚያሳዩት ከተጠሪ ጋር ያላቸውን ግንኙነት የመተጫጨት ግንኙነት መሆኑን ለመተጫጨት መፍረሱ ምክንያት ተጠሪ ስለሆኑ አግባብ ባለው ህግ መሰረት ለአመልካች ወጪና ኪሳራ ሊከፍሉ ይገባል በማለት የመከላከያ መልሳቸውን አቅርበዋል ጉዳዩን በመጀመሪያ የተመለከተው ፍርድ ቤትም የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማና ማስረጃ ከመዘነ በኋላ በቀን ዓም በዋለው ችሎት በአመልካችና ተጠሪ መካከል የትዳር ሁኔታ መኖሩን ስለተረጋገጠ በሁለቱም መካከል ጋብቻ አለ ብሎ ከወሰነ በላ ለዚህ ውሳኔ መነሻ የሆነው የፍቺ ጥያቄ በተመለከተ የአሁን አመልካች ከጅምሩ ምንም ጋብቻ የለንም ብለው የሚከራከሩ በመሆኑ የፍቺ ጥያቄው ላይ አዲስ መልስ እንዲሰጡበት ቀጠሮ መስጠት ሳያስፈልግ እንዲሁም የማሰላሰያ ጊዜ መስጠት ሳያስፈልግ በተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሰረት ጋብቻቸው በፍቺ እንዲፈርስ ሲል የሰጠው ውሳኔ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ግራ ቀኙ ክርክር ከሰማ በኋላ የስር ፍርድ ቤት ውሳኔ ስህተት የለበትም በማለት በውሳኔ አጽንቶታል የሰበር አቤቱታው የቀረበውም ይህንኑ የስር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው አመልካች ሰኔ ቀን ዓም በፃዓፉት አቤቱታ የስር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ መሰረታዊ የሆነ የሕግ ስሕተት ተፈጽሟል የሚሉባቸውን ምክንያቶችን ዘርዝረው አቅርበዋል የአመልካች የሰበር አቤቱታ ተመርምሮ ለሰበር ችሎት እንዲቀርብ በመደረጉ ተጠሪ መልስ እንዲሰጡበት በታዘዘው መሰረት ነሐሴ ቀን ዓም የተፃፈ መልስ አቅርበዋል አመልካችም አቤቱታቸውን በማጠናከር የመልስ መልስ በመስጠት ተከራክረዋል የጉዳዩ አመጣጥ እና የክርክሩ ይዘት ከላይ የተመለከተው ሲሆን እኛም አቤቱታ የቀረበበት ውሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት መሆን አለመሆኑን ለክርክሩ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ከተያዘው ጭብጥ አንፃር መርምረናል በመሠረቱ ጋብቻ ስለመፈፀሙ በቀዳሚነት ሊቀርብ የሚገባው የጋብቻ ምስክር ወረቀት ስለመሆነ የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ድንጋጌ ሲያስቀምጥ ጋብቻ ስለመኖሩ ይኸው ማስረጃ ከሌለ የጋብቻ ግንኙነት ስለመኖሩ በትዳር ሁኔታ ማረጋገጥ ስለመቻሉም የተጠቀሰው ሕግ በአንቀጽ ደንግጓል ይህ የጋብቻ መኖር አለመኖርን በተመለከተ ሊቀርብ የሚገባው የማስረጃ አይነትና ቅደም ተከተሉ ነው የትዳር ሁኔታ መኖር ማለት ምን ማለት እንደሆነም ሕጉ በአንቀጽ ስር አስቀምጧል በዚህም መሠረት የትዳር ሁኔታ ማለት አንድ ወንድና አንዲት ሴት የትዳር ሁኔታ አላቸው የሚባሉት ራሣቸውን እንደባልና ሚስት የሚቆጥሩና የሚኖሩ ከመሆናቸውም በላይ ቤተዘመዶቻቸውና ማህበረሰቡ እንደባልና ሚስት የሚቀበሏቸው ሁነው ሲገኙ መሆኑ ተደንግጓል ይህንኑ በሕጉ የተመለከተውን ትርጓሜ ማስረዳት ከተቻለ ፍርድ ቤቱ ጋብቻ ተፈጽሟል ሲል የሕግ ግምት እንደሚወሰድ ተጠቃሹ ሕግ በአንቀጽ ስር በግልጽ አስቀምጧል ይህ የሕግ ግምት በማስረጃ መረጋገጥ በሚገባቸው ፍሬ ነገሮች ላይ የተመሠረተ ነው በዚህ አግባብ የተወሰደውን የሕግ ግምት ሌላኛው ተከራካሪ ወገን ማፍረስ የሚችልበት አግባብም በዚሁ ሕግ በአንቀጽ ተመልክቷል የአሁን ተጠሪ በስር ፍርድ ቤት ያሰሟቸው ምስክሮች ጥር ቀን ዓም አመልካችና ተጠሪ በባህላዊ መንገድ ጋብቻ መፈጸማቸውጋብቻው ከመፈጸሙ በፊት አመልካች በአካባቢው ባህልና ወግ መሰረት መስከረም ቀን ዓም የአገር ሽማግሌዎችን ወደ ተጠሪ ቤተሰቦች በመላክ ሽማግሌዎቹ ልጃችሁን ለልጃችን ስጡ በማለት ጥያቄ አቅርበው የተፈቀደላቸውና የሰርጉ ቀን የተወሰነ መሆኑበሰርጉ ላይ ቀለበት የማድረግ ስነስርዓት ሲፈጸም አመልካች የዘላለም ሚስቴ ናት በማለት ቃልኪዳን ገብተው የተዘጋጀው ምሳ ከተበላ በኋላ አመልካች ወደ ተከራዩት ቤት መሄዳቸው ከዚያ ግዜ ጀምረው ከአሜሪካ ወደ አገር ቤት ሲመለሱም አብረው በዚሁ ቤት አንድ ላይ ይኖሩ እንደነበር በዝርዝር ያስረዱ ስለመሆናቸው ፍሬ ጉዳዩን የማጣራትና ማስረጃ የመመዘን ስልጣን የተሰጣቸው የስር ፍርድ ቤቶች ያረጋገጡት ጉዳይ ነው አመልካች አጥብቀው የሚከራከሩት ተጠሪ በቀን ዓም ከወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ጽቤት ያላገባ የሚል ማስረጃ መውሰዳቸው በራሱ በአመልካች እና ተጠሪ የጋብቻ ግንኙነት አለመኖሩን ያረጋግጣል የሚል ነው ነገር ግን ከጥቅምት ቀን ዓም በፊት በአመልካችና ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በተጠሪ የነበረውን የትዳር ሁኔታ ግንኙነት መኖሩን በማስረጃ የተረጋገጠውን የሚያስተባብል አይደለም በማለት የስር ፍርድ ቤቶች የደረሱበት ድምዳሜ የሚነቀፍበት ህጋዊ ምክንያት አልተገኘም በመሆኑም በዚህ ረገድ የአመልካች አቤቱታ ተቀባይነት የለውም ሲጠቃለል አቤቱታ የቀረበበት ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ሁኖ ስላልተገኘ ተከታዩን ውሳኔ ሰጥተናል ውሳኔ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመቁ ጥቅምት ቀን ዓም ተሰጥቶ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም በውሳኔ ያጸናው ውሳኔ በፍብሥሥሕ ቁጥር መሰረት ፀንቷል በዚህ ችሎት ለተደረገው ክርክር የወጣውን ወጪና ኪሳራ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ተዘግቷልወደ መዝገብ ቤት ይመለስ ብለናል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ማአ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ መስከረም ቀን ዓም ዳኞች አልማው ወሌ ሙስጠፋ አህመድ አብርፃ መሰለ ፈይሳ ወርቁ ጳውሎስ አርሺሶ አመልካች አቶ አህፈሮም ግርማይ ቀረቡ ተጠሪወሮ ሀበን ፍስሐዬ የቀረበ የለም መዝገቡ ተመርምሮ ቀጥሎ ያለው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ የነገሩ አመጣጥ የባልና ሚስት ንብረት ክርክርን የሚመለከት ነው ጉዳዩ የተጀመረው በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቂርቆስ ምድብ ችሎት ነው በአሁን አመልካች እና ተጠሪ መካከል ያለው ጋብቻ መፍረሱን ተከትሎ የአሁን ተጠሪ በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጽፈው ባቀረቡት የክስ አቤቱታ በአሁን ተጠሪ ስም ከተመዘገበው የአስመጪና ላኪ ንግድ በተገኘ ገቢ እንዲሁም በብድር በተገኘ ገንዘብ የተገዛ የሰሌዳ ቀጥር ኮድ አአ የሆነው መኪና እንዲሁም ሌሎች ንብረቶችን በመጥቀስ ክፍፍል እንዲደረግ ዳኝነት ጠይቀዋል የአሁን አመልካችም በበኩላቸው በሰጡት መልስ ከንግድ የተገኘውን ገቢ በተመለከተ ለትራንስፖርት ለግብር እና ለትዳር ጥቅም ወጪ ወጥቶ የሚተርፍ ነገር የለም ተሽከርካሪው እዳ ያለበት በመሆነ እዳው ታሳቢ ተደርጎና አመልካች የከፈሉት ግምት ውስጥ ገብቶ ክፍፍሉ ቢደረግ ተቃውሞ የሌላቸው መሆኑን ገልጸው ተከራክረዋል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቂርቆስ ምድብ ችሎት ግራ ቀኙን ክርክር ሰምቶ እንዲሁም አግባብ ካላቸው አካላት መግለጫዎችን ጠይቆ ከመረመራቸው በኃላ ከአስመጪነትና ላኪነት ተገኘ ከተባለው ገቢ ለትዳር ጥቅም እና ለተለያዩ ጉዳዮች ያወጡዋቸው ወጪዎች ተቀናሽ ተደርገው ሊከፈሉ የሚገባው ገቢ ምን ያህል እንደሆነ በግልጽ በአሁን ተጠሪ አቤቱታ ላይ ያልሰፈረ በመሆኑ ጥያቄው ታልፏል በሰሌዳ ቁጥር አዲስ አበባ ለሆነው መኪና በጋራ ከተከፈለው ብር አስራ አንድ ሺህ አምስት መቶ ሰላሳ ብር ከሰባ ሁለት ሳንቲም ውስጥ ብር አምስት ሺህ ሰባት መቶ ስልሳ አምስት ብር ከአስራ አምስት ሳንቲም የአሁን አመልካች ለአሁን ተጠሪ እንዲከፍሉ ሲል ወስኗል በዚህ ውሳኔ ላይ ቅሬታ የተሰማቸው የአሁን ተጠሪ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ አቅርበዋል ቅሬታቸውም መሠረት ያደረገው ከአስመጪነት እና ላኪነት የተገኘው ገቢ በአግባቡ ተጣርቶ ድርሻዬ አልተወሰነልኝም ተሸከርካሪውን በተመለከተ በትዳር ወቅት በጋራ በብድር የተገዛ ሲሆን የብድሩን አከፋፈል በትዳር ዘመናችን ጀምሮ የጋራ ንብረታችን ክፍፍል ሳናደርግ በቆየንባቸው ጊዜዎች ውስጥ ተከፍሉ ያለቀ በመሆነ መኪናው የጋራ ተብሎ ሊወሰን ሲገባው የሥር ፍርድ ቤት የፍቺ ውሳኔ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ የተከፈለውን ክፍያ የአሁን አመልካች የሥር መልስ ሰጭ ከግላቸው አንዲከፍሉ ያለአግባብ ግምት በመውሰድ ቀደም ሲል ከተከፈለው ገንዘብ ግማሽ ለአሁን ተጠሪ ለይግባኝ ባይ እንዲተካ በማለት መኪናውን ለአሁን አመልካች ለመልስ ሰጭ አንዲሆን የሰጠው ውሳኔ ተገቢነት የሌለው በመሆኑ ሊሻር ይገባል የሚል ነው የከፍተኛ ፍርድ ቤቱም የሥር ፍርድ ቤት ቅሬታ በቀረበባቸው ነጥቦች ላይ የሰጠው ውሳኔ በአግባቡ መሆን አለመሆኑን ለማጣራት ይግባኙ መልስ ሰጭን ያስቀርባል በማለት ክርክራቸውን የሰማ ሲሆን የአሁን አመልካች መልስ ሰጭ ጋብቻ ከፈጸምንበት ጊዜ ጀምሮ የፍቺ ውሳኔ እስከተሰጠበት ድረስ የአስመጪና ላኪ ንግድ ተሰርቶ የተገኘው የተጣራ ገቢ ብር አንድ መቶ ዘጠና ሰባት ሺህ አራት መቶ ፃምሳ ሶስት ብር ከሰባ ሰባት ሳንቲም መሆኑን ከገቢዎች ከቀረበው ማስረጃ ማረጋገጥ የሜቻል ሲሆን ለትዳር እና ተያያዥ ወጪዎች ይኸው ገንዘብ ወጥቷል በመሆኑም ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የአሁን ተጠሪ ይግባኝ ባይ ያቀረቡት ቅሬታ ተቀባይነት የለውም መኪናውን በተመለከተ የአሁን አመልካች መልስ ሰጭ ከፍቺ በኃላ ከፍተኛውን እዳ የከፈልኩና በመኪናው ላይ እዳ የሌለበት ስለሆነ የሥር ፍርድ ቤት ይህንኑ ግምት ውስጥ በማስገባት መኪናውን ለአሁን አመልካች ለመልስ ሰጭ ይገባል ማለቱ በአግባቡ ነው የአሁን ተጠሪ ይግባኝ ባይ መኪናውን በጋራ ልካፈል ይገባል የሚሉ ካሆነ ከፍቺ በኃላ በግል የከፈልኩትን ብር ሁለት መቶ ሰላሳ ሰባት ሺህ አራት መቶ ዘጠና ሰባት ብር ከአስራ ስድስት ሳንቲም ተመላሽ አድርገውልኝ መኪናው ተሸጦ ብንካፈል ተቃውሞ የለኝም በማለት ተከራክረዋል የይግባኝ ሰሚው ክፍተኛ ፍርድ ቤትም ግራ ቀኙ ያሰሙትን ክርክራቸውን ከመረመረ በኃላ ከአስመጪነትና ላኪነት ጋር የተያያዘውን ክርክር በተመለከተ በአግባቡ ሳይጣራ የተሰጠ ውሳኔ ስለሆነ በመልስ ሰጭ በአሁን አመልካች ስም ተመዝግቦ ከሚገኘው የአስመጪና ላኪ ንግድ ተገኘ የተባለውን ገቢ በተመለከተ የተጣራ ገቢው ምን ያህል አንደሆነ ከተጣራው ገቢ ላይ የወጣ ወጪ መኖር አለመኖሩን አለ ከተባለ መጠኑ ምን ያህል እንደሆነና ግራ ቀኙ ሊከፍሉት የሚችሉት ተራፊ ገንዘብ ንብረት መኖር አለመኖሩን የግራ ቀኙ ቀኙን ክርክር የተሰበሰበውን ማስረጃ አንዲሁም እንደ አግባብነቱ ሌላ ተጨማሪ ማስረጃ በማስቀረብ ጭምር ተገቢ ነው ያለውን ውሳኔ እንዲወሰን ጉዳዩን በፍትሓብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር መሠረት መልሶታል መኪናውን በተመለከተ ደግሞ መልስ ሰጭ የአሁን አመልካች ከፍቺ በኃላ የመኪናውን የብድር አዳ የከፈሉ ከመሆነ ውጭ ይኸው የገንዘብ ምንጭ ከግራ ቀኙ የጋራ ሀብት ያልተገኘ ይልቁንም መልስ ሰጭ የአሁን አመልካች በግላቸው ከሌላ የገንዘብ ምንጭ በተገኘ ገቢ የተከፈለ መሆኑን በማንሳት ያቀረቡት ክርክርም ሆነ ማስረጃ የለም። የሚል ጭብጥ ተይዞ ጉዳዩ እንደሚከተለው ተመርምሯል ለክርክሩ ምክንያት የሆነው መኪና አመልካችና ተጠሪ በትዳር ውስጥ አብረው እያሉ በብድር በተወሰደ ገንዘብ የተገዛ መሆኑ ግራ ቀኙን አላከራከረም ግራ ቀኙን እያከራከረ ያለው ከመኪናው እዳ አከፋፈል ጋር የተያያዘ ነው የአሁን አመልካች መኪናውን ለመግዛት ከተወሰደው እዳ ከፍተኛው የተከፈለው የአመልካችና ተጠሪ ጋብቻ በፍቺ ከፈረሰ በኃላ በመሆኑ መኪናው ለአመልካች የግል ሊባል ይገባል የግል የማይባል ከሆነ ደግሞ ተጠሪ አዳውን ተጋርተው መኪናው የጋራ ሊሆን ይችላል በማለት የሚከራከሩ ሲሆን ተጠሪ ደግሞ ፍቺ ከተፈጸመ በኃላ የንብረት ክፍፍል ሳይደረግ ባለበት ሁኔታ ከአስመጪነትና ላኪነት ከተገኘው ገቢ እዳው ተከፍሎ ያለቀ በመሆኑ ተጠሪ የሚጋሩት እዳ የለም መኪናው የጋራ ነው በማለት ተከራክረዋል ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን የሰሌዳ ቁጥር ኮድ አአ የሆነ ተሽከርካሪ በተመለከተ አበዳሪ አዲስ ብድርና ቁጠባ ተቋም አመልካችና ተጠሪ ተለያይተው መኖር ከጀመሩበት ከጥር ቀን ዓም ጀምሮ ከጠቅላላ ብድር ምን ያህል እንደተከፈለ ተጠይቆ በቁጥር አብቁተአ ሚያዚያ ቀን ዓም በሰጠው ማስረጃ ከ ዓም በኃላ በጥቅሉ ብር ሁለት መቶ ሰላሳ ስምንት ሺህ አራት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ብር ከፃያ ዘጠኝ ሳንቲም መከፈሉን የገለጸ መሆኑን ተያይዞ ከቀረበልን የሥር ፍርድ ቤት የውሳኔ ግልባጭ ለመመልከት ተችሏል ይህ የመኪና ብድር ገንዘብ የተከፈለው የንብረት ክፍፍል ውሳኔ ከመሰጠቱ አስቀድሞ ነው በዚህ ጊዜ የአመልካችና የተጠሪ የንግድ ሥራ የሚሠራበት የአስመጪነትና ላኪነት የንግድ ሥራ እንቅስቃሴ በአሁን አመልካች አማካይነት ሲከናወን የነበረ መሆኑን አመልካች አይክዱም ይህ ከሆነ የከፍተኛ ፍርድ ቤት በውሳኔው ላይ እንዳስቀመጠውም እዳው የተከፈለው የባልና ሚስት የጋራ ከሆነው ከንግድ ሥራው ነው ተብሎ ግምት የሚወሰድ ነው አመልካች አዳው የተከፈለው ከንግድ ሥራው አይደለም ከግል ንብረቴ ወይም ገንዘብ ነው የሚል ክርክር አላቀረቡም ከዚህ አንጻር አላስረዱም አንድ ተከራካሪ ወገን ስለሚከራከርበት ፍሬ ነገር የማስረዳት ግዴታ እንዳለበት የፍትሓብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር እና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች ያስረዳሉ ከዚህ ጋረ በተያያዘ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ሰሚ ችሎትም በሰበር መዝገብ ቁጥር ላይበፍትሐብሔር ክርክር አንድ መብት ወይም ግዴታ አለ ብሎ የሚከራከር ወገን መብቱ ወይም ግዴታው ስለመኖሩ የማስረዳት ሸክም ያለበት ስለመሆኑ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል ይህም ትርጉም በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት በየትኛውም ደረጃ በሚገኙት ፍርድ ቤቶች ላይ አስገዳጅነት አንዳለው በግልጽ ተደንግጎ አንመለከታለን ስለሆነም አመልካች የመኪናው የብድር ገነዝብ ከፍቺ በኃላ የተከፈለ በመሆነ ተጠሪ የተከፈለውን ገንዘብ እስካልተኩ ድረስ መኪናው የጋራ ሊሆን አይገባም በማለት የሚከራከሩት ክርክር ከላይ በዝርዝር ከተመለከተው አንጻር ሲታይ ተቀባይነት ያለው ሆኖ አልተገኘም የሰበር አጣሪውም አእዳው በዚህ መልክ የተከፈለ መሆኑን ከሥር ፍርድ ቤት ክርክርና ይዘት በአግባቡ ሳይመለከት ከፍቺ በኃላ አመልካች የግል ገንዘብ እንደከፈሉ አድርጎ ተጠሪ አዳውን ሳይከፍሉ መኪናውን እንዲካፈሉ መባሉ ተገቢ እንዳልሆነ አድርጎ የያዘው ጭብጥ አግባብነት ያለው ሆኖ አልተገኘም ይህ በእንዲህ እንዳለ የባልና ሚስት ፍቺ ተፈጽሞ የንብረት ክፍፍል አስከሚደረግ ድረስ በጋብቻ ውስጥ ያፈሩት ንብረትም ሆነ ከዚህ ንብረት የሚገኝ ገቢ የጋራ ሆኖ አንደሚቆይ ከተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ እና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች ይዘትና መንፈስ የምንረዳው ነው ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በሌላ በኩል አመልካች ከአስመጪነትና ላኪነት ጋር በተያያዘ የተገኘውን ገቢ በተመለከተ ጉዳዩ ተጣርቶ እንዲወሰን ወደ ሥር ፍርድ ቤት መመለሱ አግባብ እንዳልሆነ በሰበር ቅሬታቸው ያነሱትን አጣሪው በጭብጥነት ያልያዘ ሲሆን ይህ ችሎት ይህን ቅሬታ እንደተመለከተው ከሆነ በከፍተኛ ፍርድ ቤት ጉዳዩ ተጣርቶ አንዲወሰን መመለሱ በአግባቡ ነው በሚል ታልፏል ሲጠቃለልም የክፍተኛ ፍርድ ቤቱ የሰጠው ውሳኔም ሆነ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የሰጠው ትዕዛዝ የሚነቀፍ ሆኖ ስላላገኘነው የተፈጸመ መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የለም ብለን የሚከተለውን ውሳኔ ሰጥተናል ውሳኔ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ እንዲሁም የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፍብይመቁ በቀን ዓም የሰጠው ትፅዛዝ በፍትሓብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር መሠረት ፀንቷል ክርክር ለተነሳበት መኪና የተወሰደ ብድር ገንዘብ ከአመልካችና ከተጠሪ ገቢ የተከፈለ በመሆኑ መኪናው የጋራ ነው ተብሎ የተወሰነው ውሳኔ ላይ የተፈጸመ መሠረታዊ የህግ ስህተት የለም ተብሎ ተወስኗል የቪህን ችሎት ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ የውሳኔው ግልባጭ ለሥር ፍርድ ቤቶች ይድረሳቸው ጉዳዩ ውሳኔ ስላገኘ መዝገቡ ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ማአ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰበር መቁ ግንቦት ቀን ዓም ዳኞች አልማው ወሌ ሙስጠፋ አህመድ አብርፃ መሰለ ፈይሳ ወርቁ ጳውሎስ ኦርሺሶ አመልካች ወሮ ጃኖ ተሰማ ቀረቡ ተጠሪ አቶ አሊ ሰይድ ቀረቡ መዝገቡ መርምረን ተከታዩን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ የአባትነትና የሞግዚትነት ጥያቄን የሚመለከት ክርክር ሲሆን ጉዳዩ የተጀመረው የአሁን ተጠሪ በአሁኗ አመልካች ላይ በመቁ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በዛፃብሩ ወረዳ ፍርድ ቤት ጥር ቀን ዓም ባቀረቡት ክስ መነሻነት ነው የተጠሪ ክስ ይዘትም ባጭሩ አመልካች በሀብሩ ወረዳ ፍርድ ቤት በፍመቁጥር በ ዓም በዋለው ችሎት የወራሽነትና የሞግዚነት እንዲሁም የሚስት ማስረጃ ያገኙ መሆኑን ይሁን እንጂ ኢብራሂም መሐመድ በሚል ወራሽነት ያሳወጁለት ከአሁኗ አመልካች ጋር በጸና ጋብቻ ውስጥ ሆነው የወለዱትና እያሳደጉ የነበሩ መሆኑን ይህ ሁኖ እያለ አመልካች ህጻኑ ከመሐመድ ሁሴን እንደተወለደና ወራሽ መሆኑን የሌላ ሰው ሚስት መሆናቸውን የህጻኑ ሞግዚት መሆናቸውን የሚያሳይ ማስረጃ የሚይዙበት አግባብ የሌለ መሆኑንና አመልካች እነዚህን ሁኔታዎችን የሚያሳይ ውሳኔ ያገኙ መሆኑን በሌላ ክርክር ጊዜ ማወቅ የቻሉ መሆኑን ጠቅሰው በመቁጥር በ ዓም የተሰጠው ውሳኔ ውድቅ እንዲሆንላቸው ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው የአሁኗ አመልካች ለክሱ በሰጡት መልስም ጉዳዩ ቀድሞ ታይቶ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ችሎት ጭምር የመጨረሻ ፍርድ የተሰጠበት መሆኑን በጉዳዩ ላይ ተጠሪ መብትና ጥቅምም የሌላቸው መሆኑንና ሕጻኑ የሐጂ መሀመድ ሐሰን ልጅ መሆኑን ጠቅሰው ተከራክረዋል የሥር ፍርድ ቤትም የአመልካችን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ነጥቦችን ውድቅ አድርጎ ከአለፈ በኋላ ክርክሩን መርቶ ተጠሪ ማስረጃዎቻቸውን ያሰሙ ሲሆን የአሁኗ አመልካች ግን በተደጋጋሚ ጊዜ ማስረጃዎቻቸውን እንዲያቀርቡ አድሉ ተሰጥቶአቸው ማስረጃዎቻቸውን በራሳቸው ጉድለት ሊያቀርቡ ባለመቻላቸው ይህንኑ መብታቸውን በማለፍ ጉዳዩን መርምሮ የአሁኗ አመልካች ህጻኑን ከሟች አቶ መሐመድ ሀሰን የወለዱት ሳይሆን ከአሁኑ ተጠሪ ጋር በጋብቻ ተሳስረው በነበሩበት ጊዜ የወለዱት መሆኑ ተረጋግጦአል በጋብቻ ውስጥ ለተወለደ ህጻን ደግሞ የደም ምርመራ የሚደረግበት የሕግ አግባብ የለም ሲል ወስኗል በቪህ ውሳኔ አመልካች ቅር በመሰኘት ይግባኛቸውን ለዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቢያቀርቡም ተቀባይነት አላገኙም አመልካች የሠበር አቤቱታቸውን ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አቅርበውም በጉዳዩ ላይ በተሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት የለም ተብሎ ተሰርዞባቸዋል የአሁኑ የሠበር አቤቱታ የቀረበውም ይህንኑ ውሳኔ በመቃወም ለማስለወጥ ሲሆን የአመልካች የሠበር አቤቱታ መሰረታዊ ይዘትም ጉዳዩ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመቁጥር በሆነ የመጨረሻ ፍርድ ያገኘ መሆኑን የአመልካች የማስረጃ ማሰማት መብት የታለፈውም ያላግባብ መሆኑ የሚዘረዝርና ህፃኑ የሟች ሀጂ መሐመድ ሀሰን ልጅ እንጂ ከተጠሪ የወለዱት ያለመሆኑን ጠቅሰው የበታች ፍርድ ቤቶች ውሳኔ ተሽሮ በመቁጥር በ ዓም የተሠጠው ውሳኔ እንዲፀናላቸው ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው አቤቱታው ተመርምሮም ግራ ቀኙ የሚከራከሩበት ጉዳይ አመልካች ልጃቸው ኢብራሂም መሀመድ ወይም አቡበከር መሀመድ የሟች ሼህ መሀመድ ሀሰን ልጅ ነው ልጁ የማን እንደሆነ የማውቀው እኔ እናቱ ነኝ ሲሉ ተጠሪ ደግሞ ልጁ የእኔ ነው ከአመልካች ጋር በነበረን ጋብቻ ውስጥ የተወለደ ነው የሚል ሲሆን ይህንን ለመለየት የዲኤንኤ ምርመራ ሳይደረግ በጋብቻ ውስጥ በመወለዱ ብቻ የሕግ ግምት ወስዶ ልጁ የተጠሪ ነው የመባሉን አግባብነት ለመመርመር ተብሎ ጉዳዩ በዚህ ችሎት እንዲታይ የተደረገ ሲሆን ተጠሪ ቀርበውም ግራ ቀኙ በጽሑፍ እንዲከራከሩ ተደርጓል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የጉዳዩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለመልኩ ከላይ የተገለፀው ሲሆን ይህ ችሎትም የግራ ቀኙን ክርክር ለሰበር አቤቱታው መነሻ ከሆነው ውሳኔ እና አግባብነት ካላቸው ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ ጉዳዩን ለዚህ ችሎት ሲቀርብ ከተያዘው ጭብጥ አንጻር አንደሚከተለው መርምሮታል ከክርክሩ መገንዘብ የተቻለው ተጠሪ በአመልካች ላይ ክሱን ሊመሰርቱ የቻሉት ከአመልካች ጋር ሕዳር ቀን ዓም ተጋብተው በመርሳ ከተማ ቀበሌ ይኖሩ እንደነበር በጋብቻ ወቅት ስሙ አቡበከር አሊ ኢብራሒም አሊ የተባለ ወንድ ልጅ ነፃሴ ቀን ዓም እንደወለዱ ይህ ሁኖ እያለ አመልካች ህጻኑ የሟች ሼህ መሀመድ ሀሰን ልጅ ነው በማለት የወራሽነትና የሚስትነት ማስረጃ መውሰዳቸው አግባብ ያለመሆኑን ጠቅሰው በዚህ ረገድ በመቁጥር በቀን ዓም በወረዳው ፍርድ ቤት የተሰጠው ውሳኔ እንዲሻርላቸው መሆኑን ይህን ክስ ሲያቀርቡና ዳኝነት ሲጠየቁም አለኝ የሚሉትን ማስረጃ ከመቁጠራቸውም በላይ የዲኤንኤ ምርመራም ተደርጎ የልጁ አባትነታቸው እንዲረጋግጥላቸው መከራከራቸውን አመልካች ህፃኑን ከተጠሪ አንዳልወለዱት የሕፃኑ ትክክለኛ አባትም ተጠሪ ሳይሆኑ ሟች መሐመድ ሀሰን መሆናቸውን ጠቅሰው የሚከራከሩ መሆኑን ነው እንዲሁም በሰመቁጥር በሆነው ይህ ሰበር ሰሚ ችሎት ሚያዚያ ቀን ዓም በዋለው ችሎት የሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ ይዘቱም አመልካች ከተጠሪ ጋር የአስልምና ሃይማኖት በሚያዘው አግባብ በኒካ መጋባታችን አልተረጋገጠም በማለት ያቀረቡት ክርክር የስር ፍርድ ቤቶች በሐይማኖቱ ስርዓት በፍሬ ነገር ደረጃ አጣርተው ውድቅ ያደረጉት በሐይማኖት ስርዓት ላይ የተመሰረተ በመሆኑ በሰበር ችሉቱ ተቀባይነት እንዳላገኘየሕፃን አቡበከር ኢብራሒም አባትነት በተመለከተ የሟች ፃጅ መሐመድ ሀሰን ልጅና ወራሽ መሆኑን የሚያረጋግጥ አስቀድሞ የተሰጠው ማስረጃ በሕጉ አግባብ መቃወሚያ ቀርቦበት ሳይሰረዝ የተጠሪ ልጅ ነው በማለት መወሰኑ ስነ ስርዓታዊ አይደለም በማለት በዚህ ረገድ በክልሉ ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት በፋመቁ በ ዓም ተሰጥቶ በአብክመ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰመቁ ሰኔ ቀን ዓም የጸናው የውሳኔ ክፍል የተሻረ መሆኑን የሚያሳይ መሆኑን ተመልክተናል ከዚህ አንጻር ሲታይ አመልካች ከተጠሪ ጋር ጋብቻ መስርተው የቆዩ መሆኑ በዚህ ሰበር ሰሚ ችሎትም በመቁጥር ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የመጨረሻ ፍርድ የተሰጠበት ጉዳይ ሲሆን አመልካች በዚህ መዝገብ ልጁ የተወለደው ከተጠሪ ሳይሆን ከሟች ሐጅ መዛመድ ሁሴን ነው በማለት ያቀረቡት ክርክር ስነ ስርዓታዊ በሆነ አግባብ በዚህ ሰበር ችሎት ተቀባይነት ያገኘ ከመሆኑ ውጪ ጉዳዩ የመጨረሻ አልባት ያገኘ አይደለም ይህ ሰበር ሰሚ ችሎት በሰመቁጥር በዚህ ረገድ የሰጠው ውሳኔ ህጻነ የሟች ዛጅ መሐመድ ሁሴን ልጅና ወራሽ መሆኑን የሚያረጋግጥ አስቀድሞ የተሰጠው ማስረጃ በሕጉ አግባብ መቃወሚያ ቀርቦበት ሳይሰረዝ የተጠሪ ልጅ ነው በማለት መወሰኑ ስነ ስርዓታዊ አይደለም በማለት በዚህ ረገድ የተሰጠውን ውሳፄ ከመሻሩ ውጪ ተጠሪ በሕጉ አግባብ የሚያቀርቡትን መቃወሚያ ወይም ክርክር የገደበ አይደለም በመሆኑም አመልካች በዚህ ረገድ ያቀረቡትን ክርክር ይህ ችሎት በሰመቁጥር የሠጠውን ውሳኔ መሰረታዊ ይዘት የፍብሥሥሕቁጥር ድንጋጌ ሙሉ ይዘትና ተጠሪ በሕጉ አግባብ ሊያቀርቡ የሚችሉትን መቃወሚያ ክርክር ያላገናዘበ በመሆነ አልተቀበልነውም ሌላው አመልካች አጥብቀው የሚከራከሩት ነጥብ የማስረጃ የማሰማት መብታቸው ያላግባብ ታልፏል የሚል ነው ይሁን እንጂ አመልካች የሰው ምስክሮች እንዲያሰሙ መብታቸው የተጠበቀላቸው መሆኑን ይህንነ መብታቸውን ምስክር እስከመቀየር ድረስ ፍርድ ቤቱ ጠብቆላቸው ምስክሮችን እንዲያቀርቡ በተደጋጋሚ ታዘዘው በራሳቸው ጉድለት የተነሳ ሳያቀርቡ በመቅረታቸው የታለፈ መሆኑን የውሳኔው ግልባጭ የሚሳይ በመሆኑና አመልካችም ሕጋዊ ምክንያት ያላቸው ስለመሆኑ ያቀረቡት ማስረጃ ሳይኖር የስር ፍርድ ቤት በዚህ ረገድ ስሀተት መፈፀሙን በመጥቀስ የሰበር ቅሬታ ማቅረባቸው ተቀባይነት የሚያገኝበትን የሕግ አግባብ አላገኘንም በመሆኑም የማስረጃ ማሰማት መብት በሕጉ በተዘረጋው ስርዓት የሚከናወንና ይህንኑ በህጉ የተዘረጋውን ስርዓት መሰረት ተደርጎ የተከራካሪ ወገን መብት በፍርድ ቤት ሲጠበቅ ተከራካሪ ወገነ ሕጋዊ ምክንያትና ማስረጃ በሌለበት ሁኔታ በራሱ ጉድለት ማስረጃውን ሳያቀርብ የቀረ ተከራካሪ ወገን ማስረጃ የማሰማት መብት አልተጠበቀልኝም በማለት ቅሬታ የሚያቀርብበት የሕግ አግባብ የለም በመሆኑም አመልካች በስር ፍርድ ቤት በተሰጣቸው በቂ ጊዜ ምስክሮቻቸውን ለማቅረብ ያልቻሉት በራሳቸው ጉድለት ስለመሆኑ ተረጋግጦ የማስረጃ ማሰማት መብታቸው የታለፈ መሆኑን የክርክሩ ሂደት የሚያሳይ በመሆኑ በዚህ ረገድ ያቀረቡትን ቅሬታ ይህ ችሎት ሊቀበል የሚችልበትን የሕግ አግባብ ሳላላገኘ አልፈነዋል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ወደ ዋናው ጉዳይ ስንመጣም አመልካች ከአብራካቸው የወለዱት ህጸን ኢብራሒምአቡበከር የተባለ ከሟች ሐጂ መሐመድ እንጂ ከአሁኑ ተጠሪ የወለድኩት አይደለም በማለት የሚከራከሩ ቢሆንም ተጠሪ በበኩላቸው አመልካች ጋር በፀና ጋብቻ ውስጥ ሁነው ህጻኑን የወለዱ መሆኑን በመጥቀስ በሕጉ ግምት የሕጻኑ አባት አኔ ነኝ በማለት የሚከራከሩ መሆኑን በአመልካችና በተጠሪ መካከል ከሕዳር ቀን ዓም እስከ ነሐሴ ቀን ዓም ድረስ ጋብቻ የነበራቸው መሆኑን በመቁጥር በሆነው አመልካች እስከ ሰኔ ቀን ዓም ድረስ ከሟች ሐጂ መሐመድ ሁሴን ጋር በጋብቻ ውስጥ የነበሩ መሆኑ መረጋገጡንና ህጻኑ ከሐጂ መሐመድ ሁሴን ሞት በላ አንድ አመት ቆይቶ ነሐሴ ቀን ዓም የተወለደ መሆኑን በፍሬ ነገር ደረጃ መረጋገጡን ተገንዝበናል የበታች ፍርድ ቤት ህጻኑ የተጠሪ ልጅ ነው ወደሚለው ድምዳሜ የደረሱትም አነዚህን ፍሬ ነገሮችን መሰረት በማድረግና የደም ምርምራ አባት አለመሆኑን ለማረጋገጥ እንጂ አባትነትን ለማረጋገጥ በሕግ የተፈቀደ መንገድ አይደለም በጋብቻ ውስጥ የተወለደ ልጅ አባት ነው ተብሎ የሚገመተው እናትዬውን ያስቀመጠው ባል ነው የሚሉትን ምክንያቶችን በመያዝ መሆኑን ከውሳኔው ግልባጭ ተገንዝበናል በመሰረቱ የአንድ ሰው አባትነት የሚረጋገጥባቸው መንገዶች በክልሉ የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር በአንቀጽ ስር የተመለከቱ ሲሆን ከእነዚህም አንዱ በፍርድ ቤት በሚሰጥ ውሳኔ አባትነት እንዲታወቅ ማድረግ መሆኑ በተጠቀሰው አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ስር ተመልክቷል አባትነትን እንዲታወቅ ለማድረግ ከሚያስችሉ ሁኔታዎች መካከልም አንዱ በሕግ የታወቀ ግንኙነት መኖር መረጋገጡ እንደሆነ በቤተሰብ ሕጉ በአንቀጽ ስር ተመልክቷል የወረዳው ፍርድ በሰጠው ውሳኔ ላይ የአመልካቹን አባትነት በፍርድ ለማረጋገጥ መሰረት ያደረገውን የክልሉን የቤተሰብ ሕግ ሲሆን ፍርድ ቤት በተጠሪው ምስክሮች በሰመቁጥር እንዲሁም በሌሎች የሰነድ ማስረጃዎች ከተረጋገጠው ፍሬ ነገር አንጻር የተጠሪ አባትነት በሕግ ግምት የሚወሰድበትና በዲኤንኤ ምርመራም የሚስተባበልበት አግባብ የለም በሚል ምክንያት መሆኑን ከወረዳው ፍርድ ቤት የውሳኔ ግልባጭ ተገንዝበናል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አመልካች የስር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ነው በማለት አጥብቀው ከሚከራከሩባቸው ነጥቦች መካከል አንዱ እና ዋነኛው ህጻኑ ከሐጂ መሀመድ ሁሴን የተፀነሰ እና ከመወለዱ ጊዜም ሆነ ከተፀነ በኋላ ከአመልካች ጋር በጋብቻ ተሳስረው በመኖር ላይ ያልነበሩ መሆኑን በመጥቀስ ነው ይሁን እንጂ ክርክራቸውን በማስረጃ ያላስደገፉ ከመሆኑም በላይ ከተጠሪ ጋር የነበራቸውን የጋብቻ ግንኙነት ጊዜ ያላገናዘበ መሆኑን የመዝገቡ ግልባጭ ያመለክታል በመሰረቱ በጋብቻ ውስጥ የተፀነሰ ወይም የተወለደ ልጅ አባቱ ነው የሚባለው ባልየው ስለመሆኑ በክልሉ የቤተሰብ ሕግ በአንቀጽ እና ስር ተመልክቷል ህጻነ የተፀነሰው ወይም የተወለደው አመልካች አንደሚከራከሩት ከሌላ ሰው ጋር በጋብቻ ውስጥ ባሉበት ጊዜ መሆኑ አልተረጋገጠም ይልቁንም ከተጠሪ ጋር ጋብቻ ውስጥ የነበሩ መሆኑ በሚገባ የተረጋገጠ ጉዳይ ነው አባትነትን በሕግ ግምት ወይም በመቀበል መንገዶች ለመወሰን ክርክር ሲነሳ የባህሪ ወሳኝ ቅንጣት አክላ ውጤት አንደ መከላከያ ማስረጃ እንዲቀርብ በሕጉ በግልጽ የተቀመጠ ድንጋጌ የሌለ በመሆኑነ ዳኝነት ሰጪ የሆነው ፍርድ ቤት በሕጉ የተረዘረጋውን ስርዓት ተከትሎና ለትክክለኛ ፍትህ አሰጣጥ አስፈላጊ መሆኑን ሲያምንበት ተግባራዊ ሊያደርገው የሚችለው መሆኑን ከክልሉ የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር አንቀፅ እና ሀ ድንጋጌዎች ይዘት የምንረዳው ጉዳይ ነው ከዚህ አንጻር ስንመለከተው የዘር የባህሪ ወሳኝ ቅጣት ዐዘል ምርመራ ውጤት በሕጉ በተመለከተው አግባብ በሕጋዊ ምክንያቶች ለማስረጃነት የሚቀርብ እንጂ በሕግ የተቀመጠውን ግምት እናት ስለካደች ብቻ ለማስረጃነት የሚቀርብ ማስረጃ ነው ብሎ ድምዳሜ የሚያዝበት አይደለም በተያዘው ጉዳይ አመልካች የዘር የባህሪ ወሳኝ ቅጣት ዐክል ምርመራ ውጤት ለማስረጃነት አንዲቀርብ በስር ፍርድ ቤት ያልጠየቁ ከመሆኑም በላይ በዚህ ሰበር ሰሚ ችሉት ባቀረቡት የሠበር አቤቱታ ላይም ይህንነ በቅሬታ ነጥብነት ጠቅሰው የጠየቁት ዳኝነት ካለመኖሩም በላይ ይህ ችሎት ግራ ቀኙን በቃል ሲያነጋግራቸውም ተጠሪ ወጣ ገባ ይል ነበር የሚል ቃል ለችሎቱ በማስታወቅ የምራመራ ሄዛደቱ እንዲከናወን ፍላጎት የሌላቸው መሆኑን የገለፁ ሲሆን ተጠሪ ግን ፈቃደኝነታቸውን የገለፁ መሆኑ ችሎቱ ተገንዝቧል በዚህም ምክንያት የዘር የባህሪ ወሳኝ ቅጣት ሀክል ምርመራ ሳይደረግ በጉዳዩ ላይ ውሳኔ የመሰጠቱን ጉዳይ በተመለከተ አጣሪው ችሎት በጭብጥነት የያዘው የክርክሩን ሄደት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ያላገናዘበ ከመሆኑም በላይ የህፃኑን በሕግ ግምት የተጠሪ ልጅ መሆኑን መሰረት ያላደረገ በክልሉ የቤተሰብ ህግም በአንቀፅ እና ድንጋጌዎች በተመለከተው አግባብ ምርመራው አንዲደረግ የሚያስገድዱ ሕጋዊ ምክንያቶች ስለመኖራቸው ያለመረጋገጡን መሰረት ያላደረገ ሁኖ ተገኝቷል የስር ፍርድ ቤት አመልካች ከሟች ሐጂ መሀመድ ሁሴን ጋር እስከ ሰኔ ቀን ዓም ድረስ ጋብቻ ውስጥ አንደነበሩ ማስረጃ እንዳላቸው ከተጠሪ ጋርም ከህዳር ቀን ዓም ጀምሮ ሕጋዊ ጋብቻ የነበራቸው መሆኑን የጊዜ መደራረብ መኖሩን ተገንዝቦ ሕጻኑ ከሟች ሐጂ መሀመድ ሁሴን ሊወለድ አይችልም ወደሚለው ድምዳሜ የደረሰው በሕጉ የተመለከተውን የእርግዝና ጊዜ መሰረት አድርጎ ስለመሆኑ ከውሳኔ ይዘት ተገንዝበናል በእርግጥ የልጀ አባት ነህ ተብሎ በሕግ አባትነት የሚሰጠው ሰው ልጁ ከመወለዱ በፊት በኛውና በኛው ቀናት መካከል ባለው ጊዜ ውስጥ ከልጁ እናት ጋር የሩካቤ ስጋ ግንኙነት ላለመፈፀሙ በማያጠራጥር ሁኔታ ያስረዳ እንደሆነ የተባለውን ልጅ ልጄ አይደለም ለማለት እንደሚቻል በክልሉ የቤተሰብ ሕግ አንቀፅ ስር የተመለከተ ሲሆን የተጠቃሹ ቤተሰብ ሕግ አንቀፅ በአንጻሩ ጋብቻ ከተፈጸመ ከ በኋላ ወይም ጋብቻው ከፈረሰ በ ቀናት ውስጥ የተወለደ እንደሆነ ልጁ በጋብቻው ውስጥ እንደተፀነሰ ይቀጠራል በሚል በንኡስ ቁጥር አንድ ስር ከመንደንገጉም በላይ ለዚህ ተቃራኒ የሆነ የማስረጃ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ጭምር አስገዳጅነት ባለው ሁኔታ በንዑስ ቁጥር ሁለት ስር በግልጽ አስፍሯል ከዚህ አንጻር ሲታይ አመልካች ከሟች ሐጂ መሀመድ ሁሴን ጋር የነበራቸው ጋብቻ ሰኔ ቀን በሞት ከፈረሰ በጊላ ህፃኑን ጋብቻው ከፈረሰ በኛው ቀን ውስጥ የወለዱት ሳይሆን ይህ በሕጉ የተመለከተው ጊዜ ከአለፈ በላ ነሐሴ ቀን ዓም የወለዱ መሆኑ በፍሬ ነገር ደረጃ የተረጋገጠ በመሆኑ በተጠቃሹ የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ ድንጋጌ አግባብም ተቃራኒ ማስረጃ ለማቅረብ የሚችሉበት የሕግ አግባብ የለም አመልካች የሕጻኑን ከተጠሪ መወለድ ክደው የሚከራከሩ መሆኑ ሲታይም የመካድ ክርክር እያቀረቡ ያሉ መሆኑን የሚያስገነዝብ ሁኖ ከተጠሪ ጋር በጋብቻ ተሳስረው በነበሩበት ሁኔታ ልጁ የተጠሪ ልጅ አይደለም በማለት የሚያቀርቡት ተገቢነት የሌለው መሆኑን ከክልሉ የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር አንቀፅ እአና ድንጋጌዎች ጣምራ ንባብ የምንረዳው ጉዳይ ሆኖ አግኝተናል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ሲጠቃለልም በእነዚህ ሁሉ ምክንያቶች ተጠሪ ከአመልካች ጋር በጋብቻ ተሳስረው በነበሩበት ጊዜ ህፃን አቡበከር አብራሒም ከአመልካች ወልደዋል ተብሎ የህጻኑ አባት ናቸው ተብሎ የተሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት ያለበት ነው ለማለት የሚቻልበትን የሕግ አግባብ ስላላገኘን ተከታዩን ወስነናል ውሳኔ በሐብሩ ወረዳ ፍርድ ቤት በመቁጥር በ ዓም ተሰጥቶ በሰሜን ወሎ መስተዳድር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁጥር በ ዓም በአብክመ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ አጣሪ ችሎት በሰመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የፀናው ውሳኔ በፍብሥሥሕቁጥር መሰረት ፀንቷል የስር ፍርድ ቤቶች ሕፃን አቡበከር ኢብራሒም የተጠሪ ልጅ ነው በማለት በሰጡት ውሳኔ የተፈፀመ መሰረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት የለም ብለናል በዚህ ፍቤት ለተደረገው ክርክር ግራ ቀኙ ያወጡት ወጪና ኪሳራ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መቤት ይመለስ ብለናል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የመቁጥር መስከረም ቀን ዓም ዳኞች አልማው ወሌ ሙስጠፋ አህመድ አብርፃዛ መሰለ ፈይሳ ወርቁ ጳውሎስ ኦርሺሶ አመልካች ወሮ ብርቱካን ታደሰ ቀረቡ ተጠሪ ወሮ የሺእመቤት ታደሰ ከጠበቃ አበበ ማስረሻ ጋር ቀረቡ መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ለሰበር አቤቱታው መነሻ የሆነው ጉዳይ ተጠሪ የአመልካችን የሻለቃ ታደሰ በላይነህ ልጅነትን በመቃወም ለፌዴራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ያቀረቡትን ክርክር መሠረት በማድረግ የተሰጠውን ውሳኔ የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀረመው የአሁኗ አመልካች በፌዴራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጥር ቀን ዓም ባቀረቡት ክስ ነው የአመልካች የክስ ይዘት ሲታይም ወላጅ አባታቸው ሻለቃ ባሻ ታደሰ በላይነህ ከወላጅ እናታቸው ከወሮ ሙሉነሽ አበበ ጋር በጋብቻ ውስጥ ሁነው በ ዓም የወለዷቸው መሆኑን የልደት ምስክር ወረቀትም ያላቸው ከቤተሰቦቻቸው አሳድገው አስተምረው የዳራቸው መሆኑን በሰፈር በቤተዘመድ እና በወረዳም ልጅ ለመሆናቸው የሚታወቁ መሆኑን ወላጆቻቸው ሲሞቱም ወራሽነታቸውን ሲያረጋግጡ የአሁኗ ተጠሪ በመቃወማቸው የወራሽነት ማስረጃውን የሰጠው ፍርድ ቤት አመልካችን ልጅነታቸውን አረጋግጠው እንዲቀርቡ በማዘዙ ምክንያት ክሱን ለማቅረብ የተገደዱ መሆኑን ጠቅሰው ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሁለቱም ሟቾች ልጅ መሆናቸው በፍርድ ተረጋግጦ የልጅነት ውሳኔ አንዲሰጣቸው ዘንድ ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው ተጠሪም ወደ ክርክሩ ጣልቃ ገብተው እንዲከራከሩ እንዲፈቀድላቸው በ ዓም በተጻፈ ማመልከቻ ጠይቀው ከተፈቀደላቸው በላ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትእዛዝ መነሻ አሻሸለው ባቀረቡት ክርክር ሟቾች ባልና ሚስት ቢሆኑም መፃን መሆናቸውን አመልካች የሟች ወሮ ሙሉነሽ አበበ የወንድም ልጅ መሆናቸውን ሟቾች ለተጠሪ ኑዛዜ ትተውላቸው ተጠሪ በፍርድ ቤት እንዲፀድቅ ማድረጋቸውንና አመልካች የሟቾች ተወላጅ ባልሆኑበት ሁኔታ ተጠሪ በሟቾች ኑዛዜ ወራሽነት ተጠቃሚ የሆኑበትን የውርስ ንብረት የሚጠይቁበት የሕግ አግባብ የለም በማለት ተክራክረዋል ለዚህ ክርክራቸው አሉኝ የሚሏቸውን የሠውና የሠነድ ማስረጃ ዘርዝረው ከማቅረባቸውም በተጨማሪ በ ዓም በተዛፈ ማመልከቻም የዲኤንኤ ምርምራ እንዲደረግ ትዕዛዝ እንዲሰጣቸው አመልክተው ፍርድ ቤቱም በ ዓም በዋለው ችሎት የተጠሪን የዲኤንኤ ምርመራ ጥያቄ ስነ ስርዓታዊ አይደለም በሚል ምክንያት ውድቅ አድርጎ ብይን ሰጥቷል ከዚህም በኋላ ጉዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ የተመለከተው ፍርድ ቤት የግራ ቀኙን ክርክርና ማስረጃ ከሰማና ተገቢ ነው ባለው መንገድ ሁሉ ከአጣራ በኋላ ጉዳዩን መርምሮ አመልካች የሟቾች ልጅ መሆናቸውን በሰውና በሰነድ ማስረጃ ሲያስረዱ ተጠሪ ይህንኑ አላስተባበሉም በሚል ምክንያት አመልካች የሟች ሻለቃ ባሻ ታደሰ በላይነህና የሟች ወሮ ሙሉነሽ አበበ ልጅ ናቸው በማለት ወስኗል በዚህ ውሳኔ የአሁኗ ተጠሪ ቅር በመሰኘት ይግባኛቸውን ለፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርበው ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤትም ግራ ቀኙን ከአከራከረ በኋላ ጉዳዩን መርምሮ የተጠሪ የዲኤንኤ ምርመራ የታለፈው ሕጋዊ ባልሆነ ምክንያት ነው በማለት የስር ፍርድ ቤት በፍሬ ነገሩ ላይ የሰጠውን ውሳኔ ሙሉ በሙሉ ሽሮ የአሁኗ አመልካች ከአቶ ገዛኽኝ በቀለ ጋር የዘረመል ክል ምርመራ እንዲያደርጉ የስር ፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዲሰጥና የምርመራ ውጤቱ ሲቀርብለት የመሰለውን እንዲወስን በማለት ጉዳዩን መልሶለታል በዚህ ውሳኔ የአሁኗ አመልካች ቅር በመሰኘት ይግባኛቸውን ለፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ቢያቀርቡም ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ይግባኛቸው በፍብሥሥሕቁጥር መሰረት ተሰርዞባቸዋል የአሁኑ የሠበር አቤቱታ የቀረበው ይህንኑ ውሳኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው የአመልካች የሠበር አቤቱታ መሰረታዊ ይዘትም ተጠሪ የዲኤንኤ ምርምራ ጥያቄ መጀመሪያ በሕጉ አግባብ ያላቀረቡና ጥያቄውን ከአቀረቡ በኋላም ምራመራው ከማን ጋር አንደሚከናውን የተለያዩ አቋም ይዘው ሲከራከሩ የቆዩ ከመሆናቸውም በላይ ከአመልካች ጋር ምርመራ አንዲያደርግ የታዘዘው ግለሰብም ፍርድ ቤቱ በምስክርነት የሰማውና የአመልካችን ተወላጅነት ያረጋገጠ ሁኖ እያለ ተገቢ ባልሆነ ስነ ስርዓትና ምክንያት የስር ፍርድ ቤት ውሳኔ መሻሩ ያላግባብ ነው የሚል ሲሆን አቤቱታው ተመርምሮም በዚህ ችሎት አንዲታይ የተደረገ ሲሆን ተጠሪ ቀርበውም ግራ ቀኙ በፅሑፍ እንዲከራከሩ ተደርጓል የጉዳዩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለመልኩ ከላይ የተገለጸው ሲሆን ይህ ችሎትም የግራ ቀኙን ክርክር ለሰበር አቤቱታው መነሻ ከሆነው ውሳኔ እና አግባብነት ካላቸው ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ ጉዳዩ ለዚህ ችሎት ሲቀርብ ከተያዘው ጭብጥ አንጻር እንዲሚከተለው መርምሮታል ጉዳዩ ለዚህ ችሎት ሲቀርብ የተያዘው ጭብጥም ተጠሪ ባቀረቡት የጣልቃ ገብ አቤቱታ ላይ የዘረ መል ምርመራ እንዲደረግ ባልጠየቁበት ሁኔታና እንዲሁም አመልካች የዘረ መል ምርመራ አብረው እንዲያደርጉ የተባለው ግለሰብ ከሟች ጋር ያለው የቅርብ ዝምድና ሳይጣራ የዘረመል መርምራ እንዲደረግ የመታዘዙን አግባብነት የሚመለከት ነው ከክርክሩ ሂደት መገንዘብ የተቻለው የአሁኑ አመልካች በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ያቀረቡት ከሟች ሻለቃ ባሻ ታደሰ በላይነህና ከወሮ ሙሉነሽ አበበ በጋብቻ ውስጥ ተወልጄአለሁ በሚል ይኬኹው በፍርድ እንዲረጋገጥላቸው መሆኑንና የአሁኗ ተጠሪ ወደ ክርክሩ ጣልቃ እንዲገቡ ተደርጎ ሟቾች ልጅ መውለድ የማይችሉና አመልካችም ከሟቾቹ ያልተወለዱ መሆኑን ተጠሪ ከሟቾቹ የኑዛዜ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልፀው የሚከራከሩ መሆኑን ግራ ቀኙ አሉን የሚሏቸውን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎቻቸውን ከማቅረባቸውም በተጨማሪ ፍርድ ቤቱ ፍሬ ነገሩን ተገቢ ነው ባለው መንገድ ያጣራ መሆኑን የአመልካች የሰው ምስክሮችም ሆኑ በተጠሪ በፍርድ ቤት ማጣሪያነት ቀርቦ እንዲመሰክር የተጠየቀው ምስክርም በማጣሪያ ምስክርነት ቀርቦ አመልካች የሟቾች ልጅ መሆናቸውን እንደሚያውቁ የመሰከሩ ሲሆን አመልካች በሰነድ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ማስረጃነት በ ዓም የተሰጣቸውን የልደት ምስክር ወረቀት ሟች ወሮ ሙሉነሽ አበበ አባል መሆናቸው ከተረጋገጠው ከምስራቅ በር እድር የቀረበው ሰነድም አመልካችን የአድርተኛ አብራክ ልጅ በሚል ተመዝገበው የሚገኙ መሆኑን እንደሚያሳይ ከክፍሉ ቀበሌ የቀረበው የቤተሰብ ቅጽም አመልካች ልጅ ተብለው የተመዘገቡ መሆኑን እንደሚያሳይ ከኮሪያ ዘማቾች የቀረበው ቅጽም አመልካችና ተጠሪ ልጅ ተብለው የተመዘገቡ መሆኑን እንደሚያሳዩ በአመልካች በኩል የተሰሙት አራት የሰው ምስክሮች አመልካችን ሟቾች ያሳደጓቸው እንጂ ያልወለዲቸው መሆኑን አመልካች አሉኝ የምትላቸው የኑዛዜ ተጠቃሚነት ሰነዶች ሲታይም ሻለቃ ባሻ ታደሰ በላይነህ በ ዓም አደረጉ የተባለው ኑዛዜ በመቁጥር በ ዓም በፍርድ ቤት የጸደቀ መሆኑን ሟች ወሮ ሙሉነሽ አበበ በ ዓም አደረጉ የተባለው ኑዛዜ ደግሞ በመቁጥር በ ዓም ፀድቆ የነበረ ቢሆንም በአመልካች ተቃዋሚነት በ ዓም የተሻረ መሆኑን የሚያስገነዝቡ መሆኑን የስር ፍርድ ቤት በውሳኔው ላይ በግልጽ ማስፈሩን ነው ተጠሪ የአመልካችን የሟቾች ልጅነት ተረጋግጦ ማስረጃ ይሰጠኝ ጥያቄን ጣልቃ ገብተው ሲቃወሙ የዲኤንኤ ምርመራ ጥያቄ ያላቀረቡ መሆኑን በ ዓም በስር ፍርድ ቤት ፅፈው ባቀረቡት አቤቱታም በሟች ሻለቃ በሻ ታደሰ በላይነህ እና በአመልካች መካከል የዘረ መል ምርመራ እንዲካሄድ የሜል ሲሆን በዚህ የተጠሪ ጥያቄ ላይ አመልካች አስተያየት እንዲሰጡበት ተደርጎ አመልካች በ ዓም በሰጡት አስተያየት ተጠሪ ጣልቃ ለመግባት በጠየቁበት ማመልከቻ ያልጠየቁትና ስነ ስርዓታዊ ያልሆነ ጥያቄ መሆኑን ሐምሌ ቀን ዓም አቀረብኩ ላሉት አቤቱታም አቶ ገዛኽኝ በቀለ በምስክርነት እንዲሰሙና ከአመልካች ጋር የዘረመል ምርምራ እንዲያደርጉ በማለት የጠየቁት ጥያቄም ግለሰቡ በማስረጃነት የተሰሙ በመሆኑና ግለሰቡ ከአመልካች ጋር የዘረመል ምርመራ ለማድረግ የሚያስችል ሕጋዊ ምክንያት ያለመኖሩን ገልጸው የተከራከሩ መሆኑን ከክርክሩ ሂደት ተገንዝበናል በመሰረቱ አንድ ሰው ከአንድ አባትና እናት መወለዱን በሕግ አግባብ በፍርድ ቤት እንዲረጋገጥ የሚቀርበውን ክስ መቃወም የሚቻለው በሕጉ በተዘረጋው ስርዓት ነው በአባት በኩል ያለውን መቃወም የሚቻለው የመካድ ክስ ወይም ክርክር በሚቀርብበት አግባብ ስለመሆኑ ከተሸሻለው የፌዴራል የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ከአንቀጽ ድንጋጌዎች ይዘትና መንፈስ የምንረዳው ጉዳይ ነው ከእነዚህ ድንጋጌዎች ይዘትና መንፈስ መረዳት የሜቻለው የመካድ ክሱ የሚቀርበው አባት ነህ የተባለ ሰው ራሱ መሆኑ የቤተሰብ ህጉ አንቀጽ ያስቀመጠ ሲሆን እርሱ የሞተ ወይም ችሉታ ያጣ ከሆነ ደግሞ በቤተሰብ ህጉ አንቀጽ የተጠቀሱት ሰዎች እንደቅደም ተከተላቸው መሆኑን ነው በሕጉ ከተመለከቱት ከእነዚህ ሰዎች ውጪ የመካድ ክስ ሌላ ሰው ሊያቀርብ የማይችል መሆኑን በሕጉ የተፈቀደላቸው ሰዎች የመካድ ክስ ለማቅረብ የሚችሉትም የቤተሰብ ህጉ አንቀጽ መሰረት የፍርድ ቤት ፍቃድ ሲያገኙ ነው በመሆኑም ይህ በሕጉ የተመለከተው ፈቃድ የማግኘት ጉዳይ አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታ ነው ህጉ በአናትና በልጁ ያለው ግንኙነት እናትነት ለማረጋገጥ በመወለድ ብቻ እንደሆነ ነገር ግን ይህን ሊሰተባበል አይቻልም ለማለት እንደማይቻል በተሻሻለው የፌዴራሉ የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ይደንግጋል ፍርድ ቤቱም ይህን ለማስረዳት ተጨባጭነት ያለው ተግባር መኖሩን ካልረተጋገጠ በቀር ሊፈቅድ እንደማይቻል በተጠቃሹ ሕግ ስር በግልጽ ተመልክቷል ወደተያዘው ጉዳይ ስንመለስም አመልካች ሟች ሻለቃ ባሻ ታደሰ በላይነህ አና ሟች ወሮ ሙሉነሽ አበበ በጋብቻ ውስጥ እያሉ የተወለዱ መሆኑን አመልካች ገልፀው ተከራክረው በስር ፍርድ ቤት የቀረቡት ምስክሮቻቸው ይህንኑ የመሰከሩላቸው ከመሆኑም በላይ ሌሎች የሰነድ ማስረጃዎች የቀረቡ ሲሆን ይህንን የሚያስተባብል ማስረጃ ተጠሪ ያለማቅረባቸውን የክርክሩ ሂደት ያሳያል በጋብቻ ውስጥ የተወለደ ልጅ አባት ባልየው ስለመሆናቸው የሕግ ግምት መኖሩን ከተሻሻለው የፌዴራሉ የቤተሠብ ሕግ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ድንጋጌ መረዳት ይቻላል በሕግ የልጁ አባት ነው የተባለው ሠው የልጁ አባት ሊሆን አንደማይችል በማያጠራጥር አኳን በማስረዳት ለመካድ አንደሚችልና በዚህ መሠረት የሚቀርበው የመካድ ክስ ግን ፍቤት ካልፈቀደና ሊቀርብ አንደማይችል ከተሻሻለው የቤተሠብ ሕግ አንቀጽ እና ድንጋጌ በግልጽ መረዳት ይቻላል የተሻሻለው የፌዴራሉ የቤተሠብ ሕግ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ የአኔ ልጅ አይደለም የሚል የመካድ ክስ የልጁን መወለድ ካወቀበት ወይም ማወቅ ከሚገባው ቀናት ውስጥ መቅረብ አለበት የሚል ይዘት ያለው ሲሆን በድንጋጌው በተለይ ማወቅ ከሚገባው የሚለው የድንጋጌው አገላለጽ የልጁን መወለድ ማወቅ ከሚገባው ቀን ጀምሮ ተብሎ የሚተረጐም መሆኑን ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የድንጋጌው ይዘትና መንፈስ የሚያስገነዝበው ጉዳይ ነው በመሆኑም ልጁ በሕጉ ግምት መሰረት አባት የተባለው ሰው ልጅ ያለመሆኑን በማናቸውም ጊዜ ወሬ ከሠማበት ወይም ጥርጣሬ ከተፈጠረበት ቀን ጀምሮ በሚል የተቀመጠ ባለመሆኑ የመካድ ክስ በማናቸውም ጊዜ የሚቀርብ ነው ተብሎ የማይወሰድ መሆኑን ሕጉ ያሳያል በጋብቻ ውስጥ የተወለደን ልጅ ባልየው አባት ነው ብሎ የተወሠደው የሕግ ግምት ጥብቅ ድንጋጌ በመሆኑ አባት አይደለም የሚል ጥያቄ ሲነሣ ይህንን በሚያጠራጥር አኳን ማስረዳት አንደሚጠበቅበትና የመካድ ክስ ለማቅረብ እንኳ የፍቤት ፈቃድ አንደሚያስፈልግ መደንገጉ ሲታይ ሕጉ በጋብቻ ውስጥ የተወለደን ልጅ በማናቸውም ጊዜ ማንኛውንም ምክንያት በማቅረቡ መካድ እንዳይኖር ከፍተኛ ጥበቃ ያደረገ መሆኑን መረዳት ይቻላል ይህ የሕጉ ጥብቅ ድንጋጌ እና ጥበቃ ያስፈለገበት ዋና ምክንያት ልጆች በወላጆቻቸው ተገቢ ባልሆነ ምክንያት ተክደው ወላጅ አልባ ሆነው እንዳይቀሩ ለተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ እንዳይዳረጉ በቤተሠብ መካከል የሚፈጠረውም ያለመተማመን ማህበራዊ ምስቅልቅሎች እንዳይፈጥር በወላጆችና በተወላጆች መካከል ለሚፈጠሩ መብቶችና ግዴታዎችን በአግባቡ ለማስተናገድ ሥርዓት ለማስያዝ ጭምር ነው ተብሎ ይታሰባል ከዚህ አንጻር ጉዳይ በፅጃችን የተያዘው ጉዳይ ሲታይም የአሁኑ ተጠሪ አመልካች የሻለቃ ታደሰ በላይነህ ልጅ አይደሉም በማለት ተቃውሞአቸውን ለስር ፍርድ ቤት ሲያቀርቡ ከላይ በተጠቀሰው ህግ መሠረት አስቀድሞ የፍርድ ቤት ፍቃድ አላገኙም በተጨማሪም ተጠሪ የኑዛዜ ተጠቃሚ ከመሆናቸው ውጪ በቤተሰብ ህጉ አንቀፅ እና ውስጥ ከተዘረዘሩት የመካድ ክስ ለማቅረብ ከተፈቀደላቸው ሰዎች ውስጥ የሜካቱ አይደሉም አመልካች የሟች ወሮ ሙሉነሽ አበበ ልጅ ነኝ በማለት ያቀረቡትን ክርክር ተጠሪ የሚቃወሙበትን አግባብ ስንመለከተውም እናትነትን ለማስረዳት በተጠቃሹ አዋጅ ውስጥ ከአንቀጽ ስር ስርዓቱ ተዘርግቷል ይዘታቸውም በሚከተለው መልኩ የተቀመጠው ነው በእናት በኩል ያለው ተወላጅነት በማንኛውም ባለጉዳይ በማንኛውም ጊዜ ሁሉ ክርክር ሊደረግበት እንደሚችል ህጉ በግልጽ የሚያሳይ ሲሆን የተጠቃሹ ህግ አንቀጽ ድንጋጌ በተለይ ሲታይም በተወላጅነት ላይ ስለሚደረገው ክርክር የሚቀርበው ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ክስ ፍርድ ቤት ካልፈቀደ በስተቀር ሊቀርብ የማይችል መሆኑን በንዑስ ቁጥር አንድ ድንጋጌ ስር ሲያስቀምጥ በንዑስ ቁጥር ሁለት ድንጋጌ ስር ደግሞ በተወላጅነት ላይ ክርክር ለማድረግ ለሚቀርበው ክስ ፈቃድ የሚሰጠው ፍርድ ቤቱ ክሱን እንዲቀበል የሚያደርጉት ተጨባጭነት ካላቸው የሚመነጩ ግምቶች ወይም ምልክቶች ሲኖሩ ብቻ ነው በሚል አስገዳጅነት ባለው መልኩ አስቀምጦ ይገኛል የአዋጁ አንቀጽ ድንጋጌም ልጁ ተወላጅነቱን የሚያረጋግጥ የልደት ምስክር ወረቀትና ከዚህ ጋር የሚስማማ የልጅነት ሁኔታ ያለው እንደሆነ በተወላጅነቱ ላይ ለመከራከር ፈቃድ አይሰጥም በሚል በኃይለ ቃል ደንግጓል እንዲሁም የአዋጁ አንቀጽ ንዑስ ቁጥር አንድ በተወላጅነት ምክንያት የሚቀርበው ክስ በተወላጅነቱ ላይ ክርክር በተነሳበት ሰው ላይ ወይም በወራሾቹ ላይ ሊመሰረት እንደሚችል ያሳያል ከእነዚህ ድንጋጌዎች አቀራረፅ ይዘት አና መንፈስ መገንዘብ የሚቻለው የአንድ ልጅ እናት እገሊት አይደለችም ወይም እኔ ነኝ የሚለው ክርክር የሚነሳው የመወለድ የምስክር ወረቀት ከሌለ ወይም የልጅነት ሁኔታ በሌለ ወይም ይህ ሁኔታ ክርክር የቀረበበት እንደሆነ ስለመሆኑ ነው እንግዲህ ከላይ የተጠቀሱት የሕጉ ድንጋጌዎች ተወላጅነት ላይ የሚነሳን ክርክር የሚገዙ ሲሆን በተሻሻለው የቤተሰብ ሕጉ አንቀፅ እስከ ድረስ ያሉት ድንጋጌዎች ስለልጅነት ማስረጃ ዞኮር ዉከበ የሚገዙ እና ተወላጅነት ላይ ስለሚነሳ ክርክር አግባብነት ካላቸው ከላይ ከተጠቀሱት ድንጋጌዎች የተለዩ ስለመሆኑ መገንዘብ የሚቻል ነው በመሠረቱ ስለልጅነት ቀዳሚ ማስረጃ የልደት ምስክር ወረቀት ስለመሆኑ የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ የሚያስገነዝብ ሲሆን የልደት ምስክር ወረቀት በሌለ ጊዜ የልጅነት ሁኔታ በመኖሩ ልጅነት እንደሚረጋገጥ በተጠቀሰው አዋጅ በአንቀጽ ስር የተመለከተ ሲሆን የልጅነት ሁኔታ መኖር የሚለው ትርጉም ደግሞ አንድ ሰው በማህበረሰቡ ዘንድ የእርሱ ወይም የእርሷ ልጅ ነው እየተባለ የሚገመት ሲሆን ስለመሆኑ በአዋጁ አንቀጽ ስር በግልጽ ተቀምጧል በዚህ አኳኋን የልጅነት ሁኔታ መኖሩን ለማስረዳት የተቻለ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ልጅ ነው ሲል የሕግ ግምት እንደሚወስድ የሕግ ግምቱ ልጁ የተባለው ሰው ልጅ ሊሆን እንደማይችል ሊፈርስ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ እንደሚችል በአዋጅ አንቀፅ ንዑስ ቁጥር አንድና ንዑስ ሁለት ስር እንደቅደም ተከተሉ ተመልክቷል የደም ምርመራ ሀአክል አንድ ሰው የልጁ አባት ወይም እናት አይደለም ለማለት የሚቀርብ ማስተባባያ ማስረጃ ሊሆን የሚችል ቢሆንም ይህ የሚከናወነው ደግሞ አባትነትን በሚመለከት የመካድ ክስ ለማቅረብ የሚያስችሉ ቀዳሚ ሁኔታዎች ሲሟሉ ነው አናትነትን በተመለከተም በተጠቃሹ ህግ ከአንቀፅ እስከ ድረስ የተዘረጋው ስርዓት የሚፈቅድ ሁኖ በፍትፃ ብሔር ስነ ስርዓት ሕጉ የተመለከቱትን የማስረጃ አቀራረብ ስርዓቶችን መሰረት በማድረግ ሊቀርብ የሚገባ ነው እንግዲህ በሕጉ የተዘረጋውን ስርዓት ይዘን ወደ ተያዘው ጉዳይ ስንመለስም ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች የተነሳ የስር ፍቤት አመልካች ሕግ ጥበቃ በሚያደረገው ጋብቻ ውስጥ የተወለዱ መሆኑንና ሟች ሻለቃ ባሻ ታደሰ በላይነህና ሟች ወሮ ሙሉነሽ አበበ በጋብቻ ውስጥ ሁነው አመልካችን መወለዳቸውን በአረጋገጠበት ሁኔታና በዚህ ግንኙነት ውስጥ የሚወለድ ልጅ አባት ተብሎ በሕጉ ግምት የሚወሰድበት ከልጁ እናት ጋር የተቀመጠው ወንድ መሆኑ ይህ የህግ ግምት የሚፈርስበት አግባብም የመካድ ክስን በማቅረብ ሁኖ ክሱን ወይም መቃወሚያውን ለማቅረብ የሚችሉ ወገኖች ማንነትና ማቅረቢያ ጊዜውም በህጉ ተለይቶ ከመቀመጡም በላይ የመካድ ክስ እንዲቀርብ የሚፈቀደው በማያጠራጥር ሁኔታ ልጁ ከተወለደበት ወደላ ሲቆጠር በ እና ቀናት ዉስጥ ከልጁ እናት ጋር ሩካቤ ሥጋ ግኙኝነት ያለመፈጸሙን ሲረጋገጥ ወይም በሌላ ማስረጃ የልጅ አባት መሆን አለመቻሉም ሲያሰረዳ አባት መሆኑ በሕጉ ጥብቅ በሆነ አግባብ ተመልክቶ እያለ አንዲሁም ሟች ወሮ ሙሉነሽ አበበም በሕጉ ከአንቀፅ እስከ አግባብ ተጠሪ መቃወሚያ ለማቅረብ የሚያስችሉ ሁኔታዎች ተገኝተው ፍርድ ቤቱ ፈቃዱን ባልሰጠበት ሁኔታ ከማስረጃ አቀራረብ ስርዓት ውጪ አመልካች ምርመራ እንዲያደርጉ የታዘዘው ግለሰብም በፍርድ ቤት ቀርቦ የአመልካችን ተወላጅነት ባረጋገጠበትና የዚህ ግለሰብ ዝምድናም ከሁለቱም ሟቾች ጋር ስለመሆኑ ባልተረጋገጠበት ሁኔታ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ያለምንም መነሻ የባህሪ ወሳኝ ቅጣት ሀዌዘለላ ምርመራ እንዲደረግ ተጠሪ ጥያቄ በሕጉ አግባብ አቅርበዋል ወደሚል ድምዳሜ ደርሶ የደም ምርመራ እንዲረግ ማዘዙ ከመነሻውም በሕጉ የተመለከተውን ስርዓት ያልተከተለ በመሆኑ በሕጉ ከተዘረጋው ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ስርዓት ውጪ እንዲከናውን ተደርጎ የነበረው ምርመራ ታልፎ በጉዳዩ ላይ በቀረቡት የሰውና የሰነድ ማስረጃ የአመልካች የሟቾች መሆናቸው በፌዴራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት መወሰኑ ከውጤት አንጻር የሚነቀፍበትን አግባብ አላገኘንም ከዚህ አንጻር ሲታይ የይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ውሳኔ መሰረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት ያለበት የስር ፍርድ ቤት ግን በጉዳዩ ላይ የቀረቡትን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን መዝኖ አመልካች የሟቾች ልጅ ናቸው በማለት የሰጠው ውሳኔ በመሆኑ መሰረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት የሌለበት ሁኖ ስለተገኘ ተከታዩን ወስነናል ውሳኔ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁጥር ጥቅምት ቀን ዓም የሠጠው እና በፌጠፍቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመቁ በ ዓም የፀናው ውሳኔ በፍብሥሥሕቁጥር መሰረት ተሽሯል በፌዴራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመቁጥር በ ዓም የሠጠው ብይንና ውሳኔ በፍብስስቁጥር መሠረት ጸንቷል በዚህ ችሎት ለተደረገው ክርክር የወጣውን ወጪና ኪሳራ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል ትእዛዝ ዓም ተሰጥቶ የነበረው እግድ ተነስቷል ይጻፍ መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ ብለናል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ማአ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ መስከረም ቀን ዓም ዳኞች አልማው ወሌ ሙስጠፋ አህመድ አብርሃ መሰለ ፈይሳ ወርቁ ጳውሎስ ኦርሺሶ አመልካች ሲር ሐምዚያ ሱለይማን ቀረቡ ተጠሪ አቶ አያሌው በቀለሉጠበቃ ኩራባቸው ጎሳ ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ የቀረበው አመልካች የኦሮሚያ ብክመጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሉት የሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ እንዲታረምልኝ በማለት ያቀረቡትን የሰበር አቤቱታ አጣርቶ ለመወሰን ነው ክርክሩ በመጀመሪያ የታየው በኦሮሚያ ብክመ አዳማ ልዩ ዞን በአዳማ ወረዳ ፍርድ ቤት ነው በሥር ፍርድ ቤት አመልካች ከሳሽ ተጠሪ ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል የአሁን አመልካች በቀን ዓም ባቀረቡት አቤቱታ ከተጠሪ ጋር በ ዓም ጀምሮ በባህል ተጋብተው ሲኖሩ አራት ልጆች ማፍራታቸው በመግለጽ አመልካች በቅርብ ጊዜ ውስጥ ባህሪያቸው ስለቀየረ በተለያዩ ጊዜያት የሚደበድቧቸውየሚሰድቧቸው አንዲሁም የማያከብራቸው በመሆኑ ጋብቻው ፈርሶ በጋራ አብረው ያፈሩት ንብረት ድርሻቸው እንዲወስነላቸው ዳኝነት ጠይቀዋል ተጠሪም ራሷ ባህሪዋን ለውጣ እፄ ያልፈጸምኩት ድርጊት ፈጽመዛል በማለት እኔን መክሰሷ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ትክክል አይደለም በማለት ትዳራችን በአመልካች ጥያቄ እና ፍላጎት በመሆኑ በእርሷ ምክንያት የሚፈርስ መሆኑ ተቆጥሮልኝ የሞራል ካሳ እንድትከፍለኝ በማለት ለአቤቱታው መልስ በመስጠት ተከራክረዋል ነገር ግን አመልካች የፍቺ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት መዝገቡ ለጊዜው እንዲዘጋ በማመልከታቸው ምክንያት የማንቀሳቀስ መብታቸው በመጠበቅ ተዘግቶ የነበረ ሲሆን አመልካች የተዘጋው መዝገብ እንዲንቀሳቀስ በቀን ዓም በተፃፈ ስለአመለከቱ ፍርድ ቤቱም ተዘግቶ የነበረው መዝገብ እንዲቀሳቀስ በማድረግ የግራ ቀኙ ክርክር ከሰማና ማስረጃ ከመዘነ በላ በቀን ዓም በዋለው ችሎት በግራ ቀኙ የነበረው ጋብቻ በፍቺ እንዲፈርስ ካደረገ ለጋብቻው መፍረስም ተጠሪ ምክንያት በመሆኑ በጋራ አፍርተው ካላቸው ንብረት ውስጥ ከተጠሪ ድርሻ በመቶ ለአመልካች እንዲያካፍል እንዲሁም የሁለት ልጆች ቀለብ በወር ብር አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር አንዲከፍል ሲል ወስኗል የአሁን ተጠሪ የስር ፍርድ ቤት ውሳኔ በመቃወም ለአዳማ ልዩ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ይግባኝ ቢያቀርቡም ተቀባይነት ሳያገኝ በትአዛዝ ሰርኮታል በመቀጠል ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሉት አቤቱታ አቅርበዋል ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን አስቀርቦ ካከራከረ በላ የስር ፍርድ ቤቶች የሰጡት ውሳኔ በማሻሻል በተከራካሪዎች መካከል የነበረው ጋብቻ በተጠሪው ጥፋት በመፍረሱ በጋብቻ ውስጥ በመቶ ለአመልካች እንዲያካፍል በማለት የተሰጠው ወሳኔ ውድቅ በማድረግ የልጆች ቀለብ በማጽናት ወስኗል የሰበር አቤቱታው የቀረበውም ይህንነ የስር ፍርድ ቤት ውሳኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው አመልካች ጥር ቀን ዓም በፃፈው አቤቱታ በስር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ መሰረታዊ የሆነ የሕግ ስሕተት ተፈጽሟል የሚሉባቸውን ምክንያቶችን ዘርዝረው አቅርበዋል የአመልካች የሰበር አቤቱታ ተመርምሮ ለሰበር ችሎት እንዲቀርብ በመደረጉ ተጠሪ መልስ እንዲሰጡበት በታዘዘው መሰረት ሚያዚያ ቀን ዓም የተፃፈ መልስ አቅርበዋል አመልካችም አቤቱታቸውን በማጠናከር የመልስ መልስ በማቅረብ ተከራክረዋል የጉዳዩ አመጣጥ ባጭሩ ከላይ እንደተገለፀው ሲሆን ይህ ችሎትም የግራ ቀኙን ክርክር ለሰበር አቤቱታው መነሻ ከሆነው ውሳኔ እና አግባብነት ካላቸው የሕግ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ ጉዳዩን ለሰበር ችሎቱ ሲቀርብ ከተያዘው ጭብጥ አንፃር በሚከተለው መልኩ መርምሮታል እንደመረመረውም የአመልካች ጥያቄ ልጆችን ለማሳደግ ደፋ ቀና ብዬ አንዲሁም በአሁኑ ወቅት አካል ጉዳተኛ ልጅ በሰው እርዳታ የሚኖር አሸብር አያሌው የሚባለውን ለማሳደግ በጥረት ላይ አያለሁ እና አቅመ አዳም ያልደረሱ አዳን እና ኢለያላ አያሌው የሚባሉትን ለማሳደግ እና ለማስተማር በጥረት ላይ አያለሁ ይህ ተጠሪ በየጊዜው ረብሻ እየፈጠረ አፀያፊ ቃላት እየተናገረ ለዚህ ሁሉ ለትዳር መበተን ዋና ተዋናይ እራሱ ሆኖ እአያለአንዲሁም ከአኔ ከአመልካች ጋር በጋብቻ ተሳስረን ወይም ተጋብተን እየኖርን እያለን ከትዳር ውጭ ከሌላ ሴት ጋር በፈጸመው የግብረ ስጋ ግንኙነት አንድ ልጅ የወለደ ለመሆኑ በስር ፍርድ ቤት በማያሻማ ተመስክሮበት መከላከል ያልቻለ ስለሆነ በገንዘብ መቀጮ ተቀጥቶ እያለ ምንም አይነት ጥፋት እንዳልፈጸመ ሰው ንብረቱን አኩል እንድንካፈል የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ ሊታረም ይገባል የሚል ሲሆን ተጠሪ በበኩላቸው የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሉት የስር ፍርድ ቤት የተካሄደውን ክርክር እና ያቀረብኩትን አቤቱታ መርምሮ ከተጠሪ ድርሻ ፃያ በመቶ ለአመልካች ሊከፍል ይገባል የተወሰነው የህግ መሰረት የሌለው በመሆኑ ውድቅ መደረጉ ምንም አይነት መሰረታዊ የህግ ስህተት የሌለበት በመሆነ ሊፀና ይገባል በማለት ተከራክረዋል የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር እንደተሻሻለው አዋጅ ቁጥር የፍቺው ምክንያት ለፍቺው አስፈላጊ ባይሆንም ለውጤቱ በተለይም ለጋራ ንብረት ክፍፍሉ ግን ግምት ውስጥ ሊገባ ይችላል ለምሳሌ ለፍቺው የተጠየቀው አንደኛው ወገን በፈፀመው ዝሙት ወይም ድብደባ ምክንያት ከሆነ ፍቺው ተወስኖ በሚደረገው የንብረት ክፍፍል ወቅት ንብረቱ በእኩል መከፋፈሉ ቀርቶ ይህንኑ ጥፋት ግምት ውስጥ ያስገባ ክፍፍል ማድረግ ይቻላል ምክንያቱም በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር እንደተሻሻለው አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ከባልና ከሚስት ባንዱ የተፈጸመውና ለፍቺው ምክንያት ሆኖ የተገኘው ጥፋት በሌላው ተጋቢ ላይ ጉዳት አስከትሎ ከተገኘ በዳዩ ላደረሰው ጉዳት ተመጣጣኝ የሆነ ካሳ እንዲከፍል ፍርድ ቤቱ ይወስናል ፍርድ ቤቱ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ መሰረት ከጋራ ንብረት በካሳ መልክ ያንደኛውን ተጋቢ ድርሻ አብዛኛውን ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ወይም ሙሉውን በደል ለተፈጸመበት ወገን እንዲከፈል ሊወሰን ይችላል በማለት ተደንግጎ ይገኛል በርግጥ በፍቺ ወቅት የሚኖረው የጋራ ሀብት ክፍፍል በአንጽ እንደተመለከተው የጋራ ሀብቱ ለሁለቱም እኩል የሚከፋፈል ነው ከዚህ አንባር ሲታይ አንቀጽ የአንቀጽ ልዩ ሁኔታ መሆኑ ግንዛቤ ሊወሰድበት ይገባል ወደያዝነው ጉዳይ ስንመለስ የአሁን አመልካች የፍቺ ውሳኔ እንዲሰጥ አቤቱታ ሲያቀርቡ እንደምክንያት ያቀረቡት ተጠሪ ባህሪያቸው በመቀየር በተለያዩ ጊዜያት የሚደበድቧቸው የሚሰድቧቸው እና የማያከብሯራቸው ከመሆናቸውም በላይ ከትዳር ውጭ ከሌላ ሴት ጋር በፈጸሙት የግብረ ስጋ ግንኙነት አንድ ልጅ የወለዱ መሆናቸው በዚህ ተግባራቸውም በአፋር ክልል ሎጊያ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም በዋለው ችሎት ጥፋተኛ በማለት በገንዘብ መቀጮ የቅጣት ውሳኔ የተወሰነባቸው መሆኑን በተጠሪ ከመታመኑም በላይ ፍሬ ነገሩን የማጣራትና የመመዘን ስልጣን የተሰጣቸው የስር ፍርድ ቤቶችም ያረጋገጡት ጉዳይ ነው ስለሆነም ከላይ በዝርዝር እንደተመለከትነው በአመልካችና ተጠሪ መካከል የነበረው ጋብቻ መፍረስ በተጠሪ ጥፋት መሆኑና በአመልካች ጉዳት ስለመድረሱ ተረጋግጦ እያለ ተጠሪ ለአመልካች ካሳ የማይከፍሉበት ህጋዊ ምክንያት የለም ሲጠቃለል የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሉት የስር ፍርድ ቤቶች በማሻሻል የሰጠው ውሳኔ በከፊል መሰረታዊ የሕግ የህግ ስህተት ያለበት ሆኖ ስለተገኘ ተከታዩን ውሳኔ ሰጥተናል ው ሳ ኔ የኦሮሚያ ብክመጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመቁ መጋቢት ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ በፍብስስሕቁ መሰረት ተሻሸሏል በአመልካችና ተጠሪ የነበረው ጋብቻ በፍቺ እንዲፈርስ እና ተጠሪ ለልጆች ቀለብ በወር ብር አንድ ሺህ አምስት መቶ ብርአንዲከፍል የተሰጠ ውሳኔ ክፍል ፀንቷል ተጠሪ ለአመልካች ካሳ ሊከፍል አይገባም ሲል የሰጠው ውሳኔ ክፍል ተሽሯል በአዳማ ወረዳ ፍርድ ቤት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም በዋለው ችሎት በሰጠው ውሳኔ ውስጥ በተከራካሪዎቹ መካከል የነበረው ጋብቻ በተጠሪ ጥፋት በመፍረሱ በጋብቻ ውስጥ በጋራ ከተፈራው ንብረት ውስጥ ተጠሪ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ከድርሻው ውስጥ በመቶ ለአመልካች እንዲከፍል በማለት የተሰጠው ውሳኔ በአዳማ ልዩ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ ሰኔ ቀን ዓም በትእዛዝ ያጸናው ውሳኔ በፍብስስሕቁ መሰረት ፀንቷል በዚህ ችሎት ለተደረገው ወጭ እና ኪሳራ የግራ ቀኙን ተከራካሪ ወገኖች የየራሳቸውን ይቻሉ በቀን ዓም የተሰጠው እግድ ተነስቷል ይፃፍ መዘገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ፋዘ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመ ቁጥር ቀን ዓም ዳኞች አልማው ወሌ ሙስጠፋ አህመድ አብርፃዛ መሰለ ፈይሳ ወርቁ ጳውሎስ ኦርሺሶ አመልካች ወሮ ሰብለ ታምራት ከጠበቃ ቤተልፄም አያሌው ቀርበዋል ተጠሪ አቶ ግሩም ግዛቸው የቀረበ የለም መዝገቡ ተመርምሮ የሚከተለው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ለዚህ ሰበር መዝገብ ክርክር መነሻ የሆነው ጉዳይ የቀረበው አመልካች መስከረም ቀን ዓም በተፃፈ አቤቱታ የፌደራል ከፍተኛ ፍቤት በመቁጥር ሐምሌ ቀን ዓም በዋለው ችሎት የሰጠው ትእዛዝ እና የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁጥር ህዳር ቀን ዓም በዋለው ችሎት የሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ በሰበር ታይቶ እንዲታረምልኝ በማለት ቅሬታዋን በማቅረቧ ነው ቅሬታዋም አቤት የተባለበትን ውሣኔ አመልካች የምትቃወምባቸውን ምክንያቶች የሚዘረዝርና በሰበር ሰሚው ችሎት በኩል ሊታይልኝ ይገባል የምትለውን ዳኝነት የሚጠይቅ ሲሆን የስር ፍቤቶች በጋብቻ ውስጥ ስለተፈራው መኪና ገቢ በተመለከተ በማስረጃ አረጋግጩ እያለ መታለፉ ተገቢ አይደለም በጋብቻ ውስጥ የተደረገ የብድር ውል ከአሁን አመልካች እውቅና ውጪ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የተደረገ በመሆኑ ውድቅ መደረግ ሲገባው የጋራ እዳ መባሉ ስህተት በመሆኑ ይታረምልኝ የሚል ነው በስር ፍቤት የነበረው ክርክር የጀመረው ከፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ሲሆን ከሳሽ የአሁን አመልካች ባቀረበችው ክስ ከተከሳሽ የአሁን ተጠሪ ጋር ያለን ጋብቻ ፈርሷል በጋራ ያፈራነው ንብረት መኪና የሰቁጥር ኦሮ የመኪና ገቢ በቀን በወር የሾፌር ተቀንሶ ከ ዓም ጀምሮ ያለው የቤቶች ፕሮግራም በንግድ ባንክ የተቆጠበ ገንዘብ ብር በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተቆጠበ የአቁብ ገንዘብ ያካፍለኝ ስትል ጠይቃለች ተከሳሽም መኪና የሰቁጥር ኦሮ የሆነ በብድር ገንዘብ የተገዛ በመሆኑ ብድሩ የጋራ እዳ ይሁን ብር የተበደርነውን እዳ ያልከፈልን ስለሆነ የጋራ እዳ ነው ይባልልኝ የቤት ቁሳቁስ ጠቅሶ የየግላቸው የሆነውን ለይቶ መካፈል እንደሌለበት መልስ ሰጥተዋል የስር የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁጥር ህዳር ቀን ዓም በዋለው ችሎት የሰጠው ውሳኔ መኪና የሰሌዳ ቁጥር ኦር በትዳር ውስጥ የተገዛና ከአዳም ነጻ መሆኗን በምስክሮች በሚገባ የተረጋገጠ በመሆኑ የጋራ ንብረት ነው የመኪና ገቢ አመልካች ለግል ጥቅሙ ያዋለው መሆኑን ከሳሽ ያላስረዳች በመሆኑ ታልፏል ለኮንዶሚንየም ቤት የተጠራቀመ ገንዘብ የጋራ መሆኑን በተማመኑት መሰረት ይካፈሉ የአቁብ ብር መኖሩ ተረጋግጧል እኩል ይካፈሉ ተከሳሽ ብር የብድር እዳ የጋራ ይባልልኝ ያለው በተመለከተ በሰው ምስክሮች ብድሩ መኖሩ በመረጋገጡ የጋራ እዳ ነው የቤት ቁሳቁስ ተዘርዝሮ የጋራ የሆኑትን የጋራ የግል ናቸው ያለውን የግል ነው ሲል ወስኗል ከሳሽ የአሁን አመልካች ለፌደራል ከፍተኛ ፍቤት የይግባኝ ቅሬታ አቅርባ በመቁጥር ሐምሌ ቀን ዓም በዋለው ችሎት የሰጠው ትእዛዝ በፍብሥሥህግ ቁጥር መሰረት አያስቀርብም ሲል መዝገቡን ዘግቶታል የአሁን አመልካችም ይህን ውሳኔ በመቃወም ቀርበዋል መዝገቡም ተመርምሮ በስር ፍቤት በዚህ ጉዳይ የብድር ውሉ በአበዳሪው ብቻ ምስክር አመልካች ስለ ብድሩ ያውቁ ነበር መባሉ የብድሩ ድንጋጌዎች መስፈርት ያሟሉ መሆን አለመሆኑን እና የመኪናው ገቢም ሙሉ በሙሉ መኪናው ካልተሸጠ አይከፈልም ተብሉ የመወሰኑን አግባብነት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ለመመርመር ሲባል ቀርቧል መልስና የመልስ መልስም ተሰጥቶበታል ተጠሪ ታህሳስ ቀን ዓም በተጻፈ መልስ የመኪና ገቢ በተመለከተ መኪናው የተሸጠው በ ዓም ሲሆን የሽያጭ ውሉ የፈረሰው በ ዓም መሆኑን አመልካች ገልጻ እያለ ከ ዓም ጀምሮ የመኪና ገቢ ያካፍለኝ ብላ መጠይቋ ተገቢ አይደለም በጋብቻ ውስጥ የተበደርነው ብድር ለትዳር ጥቅም የዋለ መሆኑ የቤተሰብ ህጉ ግምት የሚያስቀምጥ ሆኖ እያለ እና አመልካች ለትዳር ጥቅም ያልዋለ መሆኑን ባለማስረዳቷ የተሰጠው ውሳኔ ስህተት የተፈጸመበት ባለመሆኑ ይጽናልኝ ሲል ተከራክሯል አመልካችም ጥር ቀን ዓም በተጻፈ የመልስ መልስ አቤቱታቸውን በማጠናከር ተከራክረዋል የጉዳዩ አመጣጥ ከላይ የተመለከተውን ሲመስል እኛም የቀረበውን አቤቱታ መልስ አና የመልስ መልሱን እንዲሁም የስር ፍርድ ቤት ውሣኔዎችን እና ከጉዳዩ ጋር አግባብነት ያላቸውን የሕግ ድንጋጌዎችን መሠረት በማድረግ በጉዳዩ ላይ የተሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት መኖር አለመኖሩን ከተያዘው ጭብጥ አንጻር መርምረናል እንደመረመርነውም ኛ የሰሌዳ ቁጥር ኦሮ የመኪና ገቢ በተመለከተ በስር ፍቤት በማስረጃ የተረጋገጠው መኪናዋ ተሸጣ እንደነበረና የተሸጠችውም በ ዓም መሆኑን የዚች መኪና የሽያጭ ውሉ ደግሞ በ ዓም የፈረሰ መሆኑን ነው የአሁን አመልካች የዚች መኪና ገቢ ግማሹ እንዲከፈለኝ ሲሉ የጠየቁት ከ ዓም ጀምሮ ያለውን በቀን ብር ትከራያለች በሚል ሲሆን መኪናውን የተከራየው ራማ ኮንስትራክሽን ከ ዓም ጀምሮ ብር ከአቶ ዳንኤል ቱፋ ላይ የተከራየ መሆኑን አሳውቋል በመሆኑም የአሁን አመልካች የመኪናዋ ገቢ ይከፈለኝ ስትል በጠየቀችበት ቀን በፊት በ ዓም ጀምሮ መኪናዋ የተሸጠችና የሽያጩም ውል በ ዓም ከፈረሰ በኋላ አመልካችና ተጠሪ መኪናዋን ያስመለሱ ስለመሆኑ የተረጋገጠ ነገር አለመኖሩና የአሁን ተጠሪ የመኪናዋን ገቢ መሰብሰቡ ባለመረጋገጡ የመኪናዋ ገዥ የነበረው ገቢዋን ሰብስቦ ከሆነም ከውሉ ጋር በተያያዘ የሚታይ ከሚሆን በቀር የስር ፍቤት የአሁን አመልካችን ጥያቄ ሳይቀበለው ማለፉ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ አልተገኘም ኛ በስር ፍቤት ብር የብድር ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አዳ የጋራ እዳ ነው የተባለበትን ውሳኔ በተመለከተ ከ የኢትዮጵያ ብር በላይ የብድር ውል በጽሁፍ ወይም በፍርድ ቤት በተደረገ የአምነት ቃል ወይም በመሐላ ካልሆነ በስተቀር ማስረዳት እንደማይቻል በፍብህግ ቁጥር ላይ ተደንግጎ ይገኛል የአሁን ተጠሪ ብር ብድር የአሁን አመልካችና ተጠሪ አብረን ተበድረናል ሲል ለማስረዳት ያቀረበው የሰነድ ማስረጃ በብድሩ ውል ላይ ያለው ፊርማ የአሁን አመልካች ፊርማ እንዳልሆነ በፎረንሲክ ምርመራ ተረጋግጧል በብድር ውሉ ላይ ያሉት ሁለት ምስክሮችም ስለመመስከራቸው አያመለክትም እንዲሁም የአሁን ተጠሪ መጀመሪያ ባቀረበው ክስ ጋር ያላቀረበውን ማስረጃ ባሻሻለው ክስ ጋር አያይዞ ማቅረቡም የብድር ውል ሰነዱን ህጋዊነት የማያሳይ ነው ሌላው የአሁን ተጠሪ ብር ከአቶ ገናናው ተናገር ተበደርኩ የሚለው በ ዓም ሲሆን የአሁን አመልካች ከቤት የወጣችው በ ዓም መሆኑና በ ዓም በመሀላቸው ጋብቻ በፍቺ መፍረሱ አላከራከረም ተጠሪ ገንዘቡን ተበድሬያለሁ ከሚልበት ከ ዓም ጀምሮ አመልካች ከ ቀን በኋላ በ ዓም ከቤት ወጥታለች ተጠሪ ገንዘቡን የተበደረው ለመኪና ማስጠገኛ መሆኑን ገልጾ ለመኪናዋ ማስጠገኛ ስለማዋሉ ግን ያቀረበው ማስረጃ የለም በመሆነም በአመልካችና በተጠሪ መሀከል አለመግባባት በተፈጠረበት ጊዜ ውስጥ የአሁን ተጠሪ የተበደረው የ ብር ብድር ለትዳር ጥቅም ስለመዋሉ መረጋገጥ አለበት በዚሁ መሰረት የስር ፍቤት ብድሩ ስለመኖሩ የአሁን ተጠሪን ማስረጃ አበዳሪውን የሰው ምስክር ብቻ ሰምቶ የአሁን አመልካችና ተጠሪ ብድሩን ስለመበደራቸው አረጋግጫለሁ ሲል የጋራ እዳ ነው በማለት የሰጠው ውሳኔ ፍሬነገር የማጥራትና ማስረጃን የመመዘን መርህ ባለመከተል የተሰጠው ውሳኔ በመሆነ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነው ብለናል ውሳኔ የፌደራል ከፍተኛ ፍቤት በመቁጥር ሐምሌ ቀን ዓም በዋለው ችሎት የሰጠው ትእዛዝ እና የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁጥር ህዳር ቀን ዓም በዋለው ችሎት የሰጠው ውሳኔ በፍብሥሥህግ ቁጥር መሰረት ተሻሽሏል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ቅሀ የብር ብድር እዳ የባልና ሚስት የጋራ እዳ መሆኑ ባለመረጋገጡ የአሁን አመልካችን የሚመለከታት አይደለም ብለናል ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ የየራሣቸውን ይቻሉ የዚህ ውሳኔ ትክክለኛ ግልባጭ ለስር ፍቤት ይድረሳቸው ብለናል መዝገቡ ተዘግቶ ወደ መቤት ተመልሷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ግንቦት ቀን ዓም ዳኞች አልማው ወሌ ሙስጠፋ አህመድ አብርሃ መሰለ ፈይሳ ወርቁ ጳውሎስ ኦርሺሶ አመልካች ወሮ አመለወርቅ ፍቅሬ ጠበቃ ለገሰ ማሞ ቀረቡ ተጠሪ አቶ ተስፋሁን ታፈሰ የቀረበ የለም መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ የቀረበው አመልካች የወላይታ ሰዶ ከፍተኛ ፍርድ ቤት እና የደብብሕክመ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የሰጡት ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ እንዲታረምልኝ በማለት ያቀረቡትን የሰበር አቤቱታ አጣርቶ ለመወሰን ነው ክርክሩ በመጀመሪያ የታየው በወላይታ ሰዶ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው አመልካች በተጠሪ ላይ ያቀረቡት ክስ ከተጠሪ ጋር በቀን ዓም በተፈጸመ ጋብቻ በቁጥር በቀን ዓም በብሔራዊ የጋብቻ ስነስርዓት መሰረት ከሶዶ ከተማ ማዘጋጃ ቤት የጋብቻ ምስክር ወረቀት ወስደው ጋብቻ ከፈጸሙ በላ እንደማንኛውም ባለትዳር በአንድ ጣራ ስር መኖር ሳይጅምሩ ወደ አሜሪካን አገር መፄዳቸው በመግለጽ ለአለፉት አራት ዓመታት ከተጠሪው ጋር ምንም ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ዓይነት ግንኙነት ሳይኖር በተለያየ ቦታ የሚኖሩ መሆናቸውና ልጆች ሆነ የጋራ ሀብት ያላፈሩ በመሆኑ በመካከላቸው ያለው ጋብቻ ፈርሶ የፍቺ ውሳኔ እንዲወሰንላቸው ተጠሪው ላይ ክስ አቅርበዋል ተጠሪም ለቀረበው ክስ የሰጡት መልስ በአመልካችና በተጠሪ መካከል በህግ የፀና ጋብቻ ስለመኖሩ ሳይክዱ በጋብቻ ውስጥ መኖራችን ጥያቄ ማንሳት የሚችሉት ተጋቢዎች ወይም አንዳቸው እንጂ ሌላ ሰው የሚያነሳው ሀሳብ የህግ ድጋፍ የሌለው በመሆኑ ስለተጋቢዋ ሆኖ ጠበቃ የፍቺ ጥያቄ ማቅረብ የማይችል ስለሆነ ክሱ ወድቅ እንዲደረግ ይህ መቃወሚያ የሚታለፍ ከሆነ በህጉ መሰረት የሞራል ካሳ ተወስኖ የወጪና ኪሳራ የመጠየቅ መብት ተጠብቆ እንዲወሰንላቸው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያና አማራጭ መከላከያ መልሳቸው በማቅረብ ተከራክረዋል ጉዳዩን በመጀመሪያ የተመለከተው ፍርድ ቤትም በቀረበው መቃወሚያ የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በላ በቀን ዓም በዋለው ችሎት የአመልካች ወንድም አስቀድሞ የተጻፈ ሕጋዊ ውክልና ሰነድ ሳይኖር አመልካችን ወክሎ የአመልካች ጋብቻ እንዲፈርስ ጠበቃን የመወከል መብት በህጉ አልተሰጠውም ስለሆነም በተጠሪ የቀረበው መቃወሚያ ተገቢ ሁኖ ስለአገኘን በፍብስስህቁ እና መ መሰረት የአመልካች ተወካይ ነኝ ባይ ክሱን ለማቅረብ መብት የለውም ሲል ብይን ሰጥቷል ይህንን ብይን በመቃወም የአመልካች ተወካይ ይግባኛቸውን ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሉት ያቀረቡ ቢሆንም ተቀባይነት ሳያገኝ በፍብስስህቁ መሰረት ሰርዞታል የሰበር አቤቱታው የቀረበውም ይህንኑ የስር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው አመልካች ታህሳስ ቀን ዓም በፃፉት አቤቱታ የስር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ መሰረታዊ የሆነ የሕግ ስሕተት ተፈጽሟል የሚሉባቸውን ምክንያቶችን ዘርዝረው አቅርበዋል የአመልካች የሰበር አቤቱታ ተመርምሮ በዚህ ጉዳይ አመልካች ለወንድማቸው የሰጡት ውክልና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተረጋግጦ ቀርቦ ባለበት የተሟላ ውክልና አልቀረበም በሚል ውድቅ መደረጉ ያላግባብ ነው በማለት በአመልካች የቀረበው አቤቱታ ከውክልና አንፃር ለመጣራት ለሰበር ችሎት እንዲቀርብ በመደረጉ ተጠሪ መልስ እንዲሰጡበት በታዘዙት መሰረት የካቲት ቀን ዓም የተፃፈ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ መልስ አቅርበዋል አመልካች ጠበቃ በተጠሪ የቀረበው መልስ ላይ የመልስ መልስ መስጠት የማይፈልጉ መሆኑን በመግለጻቸው ምክንያት የቀረበ የመልስ መልስ የለም የጉዳዩ አመጣጥ እና የክርክሩ ይዘት ከላይ የተመለከተው ሲሆን እኛም አቤቱታ የቀረበበት ውሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት መሆን አለመሆኑን ለክርክሩ ከተያዘው ጭብጥ አንፃር መርምረናል በመሰረቱ በመርህ ደረጃ የግራ ቀኙ ጋብቻ በፍቺ እንዲፈርስ መጠየቅ የሚገባው ከባልና ሚስቱ አንደኛው ተጋቢ ወይም ሁለቱም ቢሆንም በህግ አግባብ ተቀባይነት ያለው ውክልና ማስረጃ ጋር የሚቀርብ የፍቺ ጥያቄ በህግ የተከለከለ አይደለም ከባልና ሚስት አንዳቸው የፍቺ ጥያቄ እስካቀረቡ ድረስ ፍቺው ሊከለከል እንደማይቻልና ፍቺ ሊወሰን አይገባም የሚለውን ነጥብ መሰረት በማድረግ ብቻ የይግባኝ አቤቱታ ማቅረብ አንደማይቻል በተሻሻለው ፌዴራል ቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ሆነ በደብብሕክመ የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ድንጋጌዎች መገንዘብ ይቻላል በሌላ በኩል ፍርድ ቤት የባልና ሚስትን ክርክር በሚያይበት ጊዜ አንደነገሩ ሁኔታ አስፈላጊ ሁኖ ካገኘው ባልና ሚስቱን በአንድነት ወይም በተናጠል ሲያነጋግር ወይም ጉዳዩን ሲመረምርና ምስክር ሲሰማ በዝግ ችሎት ያስችላል የሚለውን የቤተሰብ ህጉ ድንጋጌአንቀጽ በመጥቀስ ጋብቻና ጋብቻ ፍቺ በውክልና ሊቀርብ አይችልም በማለት በተጠሪ የሚቀርበው ክርክር ተቀባይነት የለውም ምክንያቱም ፍርድ ቤቱ ተጋቢዎችን የሚያነጋግራቸው አስፈላጊ ሁኖ ሲገኝ እንጂ የግድ ማናጋገር አንዳለበት የሚደነግግ ባለመሆነጋብቻ በእንደራሴ መፈጸም በመርህ ደረጃ የማይቻል ቢሆንም ከተጋቢዎች አንደኛው ጋብቻው ለመፈጸም ፈቃዱን በማያሻማ ሁኔታ በመግለጽ በግንባር ለመገኘት የማያስችለው ከባድ ምክንያት ሲያጋጥመው ጉዳዩ ለፍትህ ሚኒስትሩ ቀርቦ ሲረጋገጥ ጋብቻውን በእንደራሴ አማካኝነት መፈጸም እንደሚቻል በግልጽ በተሻሻለው ፌዴራል ቤተሰብ ህግ አንቀጽ ተደንግጓል ጋብቻ ለመፈጸም በልዩ ሁኔታ በውክልና እንደሚቻል ህጉ እየፈቀደ የፍቺ ጥያቄ በውክልና ሊቀርብ አይችልም በማለት በተጠሪ በኩል የሚቀርበው ክርክር ተቀባይነት ያለው ሁኖ አልተገኘም እዚህ ሊታይ የሚገባው ነጥብ የውክልናው ማስረጃ ህጋዊነት ነው ጉዳይ በስር ፍርድ ቤት የአመልካቹ ወኪል ሆነው የቀረቡት ሰው በፍርድ ቤት በሚደረግ ክርክር በተሟጋችነት ሊቆሙ ስለሚችሉ ሰዎች በሕጉ የተመለከተውን መስፈርት የሚያሟሉ ናቸው ወይስ አይደሉም። የሚሉ ነጥቦች በግራ ቀኙ ማስረጃ ከተጣሩ በጊላ ውሳኔ እንዲሰጥበት በፍብስስህቁ መሰረት ለወረዳ ፍርድ ቤት መልሶታል ፍርድ ቤቱም የተዘጋው መዝገብ አንቀሳቅሶ በተመለሱት ነጥቦች ላይ የግራ ቀኙ ክርክር ከሰማና ማስረጃ ከመዘነ በኋላ ተጠሪ ያለ አመልካቾች ፈቃድ አነሱ ሳያውቁ በይዞታቸው ላይ በሀይል ቤት የሰራ ስለሆነ በተጠሪ ወጪ በክሱ ተራ ቁጥር ኛ ላይ የሚገኝበት ቦታ እና አዋሳኙ በተገለጸው ይዞታ ላይ የተሰራውን ቤት በማፍረስ ለከሳሾችአመልካቾች ይዞታውን እንዲለቅበክሱ ከኛ እስከ ኛ እና ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ይዞታዎች የወላጅ አባታቸው መሆናቸውና ከሳሾች የይዞታዎቹ አዋሳኝ የማያውቁ መሆናቸውና አናታቸው ጋር በመሁክ ጡሪ ከተማ ያደጉ ስለሆነ ማወቅ አለመቻላቸውን እና የተደበቀ መሆኑን ስለተረጋገጠ የፍብህቁ በመጠቀስ ወራሾች እኩል እንዲካፈሉ ሲል ወስኗል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የአሁን ተጠሪ በዚሁ ውሳኔ ቅር በመሰኘት አቤቱታቸው ለሰሜን ሽዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርበዋል ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙ ክርክር ከሰማ በላ የስር ፍርድ ቤት የሰጠው ውሳኔ ስህተት ያለበት ሁኖ አልተገኘም በማለት በውሳኔ አጽንቶታል በመቀጠል ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አቤቱታቸው አቅርበዋል ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን አስቀርቦ ካከራከረ በኋላ የስር ፍርድ ቤቶች የሰጡት ውሳኔ በማሻሻል በክሱ ተራ ቁጥር ኛ እና ኛ የተጠቀሱት ይዞታዎች በተመለከተ የተሰጠ ውሳኔ በማጽናት በክሱ ተራ ቁጥር እና ኛ የተመለከቱት ይዞታዎች ላይ የስር ፍርድ ቤቶች የሰጡት ውሳኔ በመሻር ተጠሪ ለአመልካቾች ሊያካፍል አይገባም ሲል ወስኗል አመልካቾች ያቀረቡት አቤቱታ ተመርምሮ የስር ፍርድ ቤት የጉዳዩ አከራካሪ የሆነው የውርስ ይዞታ ተረስተው የታለፉና በድጋሚ መጠየቁ አግባብነት ያለው ነው ብለው የወሰነውን የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት መሬት የማይረሳ ነው ልጠይቁ አይገባም ያለበት አግባብነት ተጠሪው ባሉበት ለማጣራት ይቻል ዘንድ ጉዳዩ ለሰበር ክርክር እንዲቀርብ በመደረጉ ግራ ቀኙ የጽሁፍ ክርክር ተለዋውጠዋል የጉዳዩ አመጣጥ እና የክርክሩ ይዘት ከላይ የተመለከተው ሲሆን እኛም አቤቱታ የቀረበበት ውሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት መሆን አለመሆኑን ለክርክሩ ከተያዘው ጭብጥ አንፃር መርምረናል ከክርክሩ ሂደት መገንዘብ የተቻለው አመልካቾችና ተጠሪ የሟች ወላጅ አባታቸው አቶ ደበላ የመጀመሪያ ደረጃ ወራሾች መሆናቸውአመልካቾች በተጠሪ እጅ የሚገኙትን የውርስ ንብረትና ይዞታዎች ክፍፍል እንዲደረግ ዳኝነት በመጠየቃቸው ምክንያት ግራ ቀኙ በስምምነት ክፍፍል ማድረጋቸው በመግለጽ ነገር ግን ከውሳኔ በኋላ ለአመልካቾች በደረሳቸው ይዞታ ላይ ተጠሪ በሀይል ቤት በመስራቱ እንዲሁም የተረሱ ይዞታዎች ድርሻቸው እንዲያካፍላቸው ዳኝነት በመጠየቃቸው ምክንያት የግራ ቀኙ ክርክር ከተደረገ በኋላ ተጠሪ በአመልካቾች ድርሻ ላይ ቤት መስራቱን በማረጋገጥ የሰራውን ቤት በራሱ ወጪ አፍርሶ ይዞታው ለአመልካቾች እንዲለቅ መስጠቱን ተገንዝበናል በዚህ ረገድ የቀረበ አቤቱታ የለም አከራካሪ የሆነው አመልካቾች በክሳቸው ከኛ እስከ ኛ እንዲሁም ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱትን ይዞታዎችን በሚመለከት ነው አመልካቾች ከውሳኔ በኋላ ክስ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ለማቅረብ በምክንያትነት የጠቀሱት የውርስ ይዞታዎች የሆኑትን መኖራቸው ባለማወቅቸው መሆኑን የተረሱ የውርስ ሀብት መጠየቅ እንደሚቻል የፍብህቁ ስለሚፈቅድ በዚሁ አግባብ የቀረበ ክስ መሆነን በመግለጽ የተከራከሩ ሲሆን ጉዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ የተመለከተው ፍርድ ቤትም በተጠሪ አጅ የሚገኙትን ክፍፍል ሳይደረግባቸው የቀሩትን አኩል እንዲከፋፈሉ የሰጠው ውሳኔ በመቃወም ጉዳዩ አስከ ክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ደርሶ ተጠሪ ጉዳዩ ውሳኔ ካገኘ በኋላ በድጋሚ የቀረበ ነው በማለት ያቀረቡት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ውድቅ በማድረግ የስር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ በመሻር በፍሬ ነገር ዳግም ተጣርቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት ጉዳዩን በፍብስስህቁ መሰረት ለስር ፍርድ መልሶታል የተመለሰለት ፍርድ ቤትም የተዘጋው መዝገብ አንቀሳቅሶ የግራ ቀኙ ክርክርና ማስረጃ ከመዘነ በላ ለክርክር ምክንያት የሆኑት ይዞታዎች ግራ ቀኙ እኩል እንዲካፈሉ ሲል የሰጠው ውሳኔ በይግባኝ ሰሚ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የፀና ቢሆንም የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ጉዳዩን ከፍብስስህቁ አንጻር ተመልክቶ የስር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ በመሻር በክሱ ከኛ አስከ ኛ እና ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ይዞታዎች ተጠሪ ለአመልካቾች ሊያካፍል አይገባም ሲል ወስኗል የአመልካች አቤቱታ መሰረት ያደረገው በስር ፍርድ በተጠሪ ያልተነሳ ጉዳይ በማንሳት የተሰጠ ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ስለሆነ ሊታረም ይገባል የሚል ሲሆን በተጠሪ በኩል ደግሞ የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሉት ጉዳዩን በአግባቡ አጣርቶ የሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የሌለበት በመሆነ ሊፀና ይገባል በማለት ተከራክረዋል በመሰረቱ አንድ ተከራካሪ ወገን ከአንድ የክስ ምክንያት የመነጨ የመብት ጥያቄ ካለው አና በአንድ ክስ የሚጠቃለል የክስ ምክንያት ሆን ብሎ በመቀነስ ያስቀረ ከሆነ በድጋሚ በተመሳሳይ ጉዳይ አዲስ ክስ ማቅረብ እንደማይችል ከፍብስስህቁ ድንጋጌ መሰረታዊ ይዘት የምንገነዘበው ነው የአንድ ክስ ምክንያት መከፋፈል ባለጉዳዮች ጊዜ ወጪና ጉልበት አላስፈላጊ ጫና እና የማጉላላት ውጤት እንዳለው መረዳት ይቻላል የፍብስስስህግዓይነተኛ ዓላማ ጠሟበ ዐህበ ጉዳዮችን በህግ አግባብ በመምራት በተቻለ አጭር ጊዜ ውጤታማ ኢኮኖሚያዊ እና ፍትሃዊ ውሳኔ መስጠት ስለመሆኑ ከአጠቃላይ የህጉ ድንጋጌዎች የምንረዳው ነው ከአንድ ጉዳይ የመነጨ የመብት ጥያቄ የሚያቀርቡ ተከራካሪ ወገኖች ክሱን ለመመስረት መነሻ የሆነባቸው ጉዳይ አጠቃልለው ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው ተከራካሪ ወገኖች ከአንድ የክስ ምክንያት የሚመነጭ ክርክር ከፋፍለው ከቀረቡ ዐሀበ ጩጠ በድጋሚ በተመሳሳይ ጉዳይ ሌላ ክስ የማቅረብ መብት የሚሰጣቸው አይደለም ወደ ተያዘው ጉዳይ ስንመለስ የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሉት ጉዳዩን የፍብስስህቁ መሰረት በማድረግ የሰጠው ውሳኔ በአግባቡ ነው ወይስ አይደለም የሚለውን ጭብጥ መመርመሩ ተገቢ ሁኖ አግኝተነዋል የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ በሁለት ምክንያት ተገቢ ሁኖ አልተገኘም አንደኛው ይህ ጉዳይ ለክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የቀረበው ሁለት ጊዜ መሆኑን ከክርክሩ ሂደትና ከውሳኔ ግልባጭ ተገንዝበናል በስር ፍርድ ቤት አመልካቾች ያቀረቡት ክስ ላይ በተጠሪ የፍብስስህቁ መሰረት በማድረግ ያቀረቡት ክርክር ካለመኖሩም በላይ ጉዳዩ ክልል ሰበር ሰሚ ችሎት ደርሶ ጉዳዩ አንደገና ወደ ፍሬ ነገር ገብቶ እንዲጣራ በፍብስስህቁ መሰረት ሲመልስ የፍብስስህቁ ጥያቄ አልነበረም አንድ ተከሳሽ ለቀረበለት ክስ በዝርዝርና በግልፅ መቃወምና መካድ አንደለበት በፍብስስህቁ ተመልክቷል በይግባኝ ደረጃም ፍብስስህቁ በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ያልተነሳወን ክርክርና ያልቀረበውን አዲስ ነገር ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት መቀበል አንደማይችል ተደንግጓል እንዲሁም ፍብስስህቁ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተከራካሪዎቹ በዝርዝር ባላቀረቡት ወይም በግልፅ ባላመለከቱት ጉዳይ ላይ ፍርድ መስጠት እንደማይቻል ይደነግጋል ስለሆነም በዚህ ረገድ የክልሉ ሰበር ውሳኔ ተገቢ ሆኖ አልተገኘም በሌላ በኩልም የውርስ ንብረት ክፍያው ከተደረገ በኋላ በክፍያ ውስጥ ያልገቡ በውርሱ ንብረት ውስጥ ገብተው የሚቆጠሩ አዲስ ሀብቶች የተገኙ እንደሆነ አዲስ የክፍያ ስርዓት መፈጠም አንደሚቻል ከፍብህቁ አና ድንጋጌዎች መገንዘብ ይቻላል ሲጠቃለል አቤቱታ የቀረበበት ውሳኔ በከፊል መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ስለሆነ ተከታዩን ውሳኔ ሰጥተናል ውሳኔ በወጫሌ ወረዳ ፍርድ ቤት በመቁ ሚያዚያ ቀን ዓም እና በሰሜን ሸዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም ፍርድ ቤት ተሰጥቶ በኦሮሚያ ብክመጠቅላይ ፍርድ ቤት በመቁ ህዳር ቀን ዓም በውሳኔ የተሻሻለው ውሳኔ በፍብስስህቁ መሰረት ተሻሽሏል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በክሱ በኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሰውን የይዞታ መሬት ተጠሪ ለአመልካቾች እንዲለቅ የተሰጠ ውሳኔ ክፍል ፀንቷል በክሱ ከኛ አስከ ኛ አንዲሁም ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ይዞታዎች የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠው ውሳኔ በመሻር የወረዳ ፍርድ ቤትና ከፍተኛ ፍርድ ቤት በክሱ ከኛ እስክ ኛ እንዲሁም ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ይዞታዎች አመልካችና ተጠሪ እኩል እንዲካፈሉ በማለት የሰጡት ውሳኔ በፍብስስህቁ መሰረት ፀንቷል በዚህ ችሎት ለተደረገው ክርክር የወጣውን ወጪና ኪሳራ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ተዘግቷልወደ መዝገብ ቤት ይመለስ ብለናል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰበር መቁ ህዳር ቀን ዓም ዳኞች አልማው ወሌ ሙስጠፋ አህመድ አብርሃ መሰለ ፈይሳ ወርቁ ጳውሎስ ኦርሺሶ አመልካች አቶ እንደገና ተሾመ የቀረበ የለም ተጠሪ አቶ ረታ መልካ ታልፏል መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ በዚህ መዝገብ ለቀረበው የሰበር አቤቱታ መነሻ የሆነው ጉዳይ ኑዛዜን መሠረት በማድረግ የቀረበውን ክርክር የሚመለከት ነው ክርክሩ በተጀመረበት በአዳማ ወረዳ ፍቤት የአሁኑ አመልካች ሟች አማሆይ ውቢቱ ኃማሪያም በ ዓም አድርገውት ያለፉት ኑዛዜ መሠረት ተደርጉ የወራሽነት ማስረጃ ይሰጣቸው ዘንድ ዳኝነት ጠይቀው ሶስት ምስከሮችን አቅርበው አሰምተዋል ከዚህም በኋላ የአሁኑ ተጠሪ ወደ ክርክሩ ጣልቃ እንዲገቡ ጠይቀው ሟች ወላጅ አናታቸው መሆናቸውን የሟች የመጀመሪያ ደረጃ ወራሽ መሆናቸውን በፍርድ ቤት ያረጋገጡ መሆኑን አመልካች አለኝ የሚሉት ኑዛዜም ሕጋዊ አይደለም የሚሉበትን ምክንያት ጠቅሰው ተከራክረዋል በዚህ ተጠሪ ጣልቃ ገብተው በአቀረቡት መከራከሪያም የአሁነ አመልካች አለኝ የሚሉትን መከራከሪያ ነጥብ አቅርበዋል የስር ፍርድ ቤትም ጉዳዩን መርምሮ በፍትፃ ብሔር ሕጉ መሰረት ኑዛዜ ይመዝገብልኝ ይሻርልኝ እንዲሁም መጠኑ ይቀነስልኝ በማለት ዳኝነት ከሚጠየቅ በስተቀር ይረጋገጥልኝ መባሉ የህግ ድጋፍ የለውም በሚል ምክንያት የአመልካችን አቤቱታ ውድቅ አድርጎታል በዚህ ላይ ከአሁኑ አመልካች ይግባኝ የቀረበለት የአዳማ ልዩ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም በስር ፍርድ ቤት ብይን ላይ ጉድለት የለውም በማለት በትእዛዝ የአመልካችን ይግባኝ የሰረዘ ሲሆን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር አጣሪ ችሎትም በበታች ፍርድ ቤቶች ዳኝነት ላይ መሰረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት የለም ሲል የአመልካችን የሰበር አቤቱታ ሳይቀበለው ቀርቷል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም በዚህ ላይ ሲሆን የአመልካች የሰበር አቤቱታ መሰረታዊ ይዘትም የስር ፍርድ ቤት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አመልካች የነዛዜ ወራሽነት እንዲረጋገጥላቸው ያቀረቡትን አቤቱታ ተቀብሎ ምስክሮችን ከሰማ በላ በተጠሪ ጣልቃ ገብነት መነሻ የነዛዜ ወራሽነት ይረጋገጥልኝ ተብሎ ዳኝነት አይጠየቅም ሲል መዝገቡን መዝጋቱም ሆነ የክልሉ የበላይ ፍርድ ቤቶችም ይህንኑ የስር ፍርድ ቤት ትፅዛዝ ሳያርሙ መቅረታቸው መሰረታዊ የሆነ የሕግ ስህትት ያለበት ነው በማለት መከራከራቸውን የሚያሳይ ነው አቤቱታቸው ተመርምሮም በዚህ ችሉት አንዲታይ የተደረገ ሲሆን ተጠሪ ጥሪ ተደርጎላቸው መጥሪያ ደርሷቸው ባለመቅረባቸውም በጽሑፍ መልስ የመስጠት መብታቸው እንዲታለፍ ተደርጎአል የክርክሩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለመልኩ ከላይ የተገለጸው ሲሆን ይህ ችሎትም የግራ ቀኙን ክርክር ለሰበር አቤቱታው መነሻ ከሆነው ዳኝነት አና አግባብነት ካላቸው ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ ጉዳዩን እንደሚከተለው መርምሮታል እንደመረመረውም የበታች ፍርድ ቤቶች የአመልካች የኑዛዜ ወራሽነት ይረጋገጥልኝ ጥያቄ ፍርድ ቤት የሚቀርብ አይደለም በማለት የሰጡት ዳኝነት የሕግ መሰረት ያለው መሆን ያለመሆኑን የሚመለከተው ነጥብ በጭብጥነት ሊታይ የሚገባው ሁኖ አግኝቶታል ከክርክሩ ሂደት መረዳት የታቻለው አመልካች ክስ ሊመሰርቱ የቻሉት ሟች አደረጉ በተባለው ኑዛዜ መሠረት በማድረግ የወራሽነት ማስረጃ የምስክር ወረቀት ይሰጠኝ የፍብሕግ ቁጥር በማለት መሆኑን ይኹው መነሻ ተደርጎም የአመልካች ምስክሮች ሁሉ ተሰምተው የነበሩ መሆኑን ከዚህ በኋላም የአሁኑ ተጠሪ ወደ ክርክሩ ጣልቃ ገብተው የአመልካችን የዳኝነት ጥያቄ ሕጋዊ አይደለም የሚሉባቸውን ምክንያቶች ዘርዝረው የተከራከሩ መሆኑን ነው በመሰረቱ በፍትሐብሔር ሕጉ በግልጽ አንደተመለከተው ኑዛዜ ፈራሽ ነው ይባል በሚል የሚቀርበው ክስ የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዲሰጥ ከሚቀርበው ጥያቄ አቤቱታ የተለየ መሆኑ ይታወቃል ጥያቄዎቹ የተለያዩ በመሆናቸውም የተለያዩ ውጤት ነው ያላቸው በፍሥሥሕግ ቁ እንደተደነገገው ወራሽ ነኝ የሚል ማንኛውም ሰው የወራሽነት ምስክር ወረቀት ይሰጠው ዘንድ ለፍቤት ሊያመለክት ይችላል ፍቤቱም ጥያቄውን ከመቀበሉ በፊት ጠያቂው ማስረጃዎቹን ሁሉ እንዲያቀርብ በማድረግ አና አስፈላጊ መስሎ የታየውን ዋስትና እንዲሰጥ በማስገደድ ጭምር ዋስትናውን ካገኘ በኋላ የተጠየቀውን የምስክር ወረቀት ሊሰጥ እንደሚችል በፍብሕግ ቁ ተመልክቷል በሌላ በኩል ደግሞ ፍቤቱ የአመልካቹን ጥያቄ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ መሠረት በማድረግ ሰጥቶት የነበረው የወራሽነት የምስክር ወረቀት ሊሰረዝው እንደሚችል በፍብሕግ ቁ የተቀመጠው ድንጋጌ ያመለክታል ይህ ሊሆን የሚችለው ደግሞ ማስረጃው ከተሰጠ በኋላ ማስረጃው የተሰጠው ከህግ ውጪ ነው የሜል ወገን ክርክሩን ከአቀረበ ነው ከዚህ እንግዲህ መገንዘብ እንደሚቻለው የምስክር ወረቀቱ በጠያቂው አቤቱታ መነሻነት የሚሰጥ ቢሆንም የተሰጠው ያለአግባብ ነው የሚል መቃወሚያ ሊቀርብ የሚችልበት ሁኔታ መኖሩንና መቃወሚያው ተገቢ ሆኖ ከተገኘም የምስክር ወረቀቱ የሚሰረዝ መሆኑን ነው ወደ ያዝነው ጉዳይ ስንመለስ የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዲሰጥ ጥያቂ የቀረበበት ፍቤት ጥያቄውን ተቀብሎ የምስክር ወረቀቱን ከመስጠቱ በፊት ይኹው ማስረጃ እንዳይሰጥ ተጠሪ ተቃውሞ አቅርበዋል በሕግ አግባብ የተደረገ ኑዛዜ በፍርድ ቤት እንዲረጋገጥ የፍርድ ቤትን ቡራኬ የማያስፈልገው መሆኑን ይህ ችሎት በሰመቁጥር እና በሌሎች መዝገቦች አስገዳጅ የህግ ትርጉም መስጠቱን ይታወቃል ይህ የሚሆነው ግን ኑዛዜው ሕጋዊ አይደለም የሚል ተከራካሪ ወገን በቀረበበት አግባብ አይደለም ይህ ችሎት በሰመቁጥር የሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም የኑዛዜውን ህጋዊነት የሚቃወም ወገን በንብረት ክርክር ጊዜ ክርክሩን ሊያነሳ የሚችል መሆኑን የሚያመላክት ነው ይህም የተከራካሪ ወገኖችን የመሰማትና ፍትህ የማግኘት መብትን ሁሉ ያገናዘበ ነው ሊባል የሚችል ነው በመሆኑን ለፍርድ ቤት የሚቀርብ ጥያቄ በፍርድ ቤት ስልጣን ስር የሚወድቅ እስከሆነ ድረስ የተከራካሪ ወገኖችን የመሰማት መብትን ባከበረና የሥነ ስርዓት ሕጉን መሰረታዊ አላማ ባገናዘበ መልኩ ሊስተናገድ ይገባል በሌላ በኩል የኑዛዜ ወራሽነት እንዲረጋገጥለት አቤቱታ አቅርቦ ማስረጃ ያሰማ ወገን ማስረጃውን ከማግኘቱ በፊት ማስረጃው እንዳይሰጥ የሚል ተከራካሪ ወገን ከቀረበ ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር በሕጉ አግባብ ተመልክቶ ተገቢውን ዳኝነት ሊሰጥበት የሚገባው እንጂ ከመነሻውም የኑዛዜ ወራሽነት ይረጋገጥልኝ የሚል አቤቱታ መቅረብ አልነበረበትም በማለት መዝገቡን ሊዘጋው የሚገባው አይደለም ምክንያቱም ማስረጃው እንዳይሰጥ የሚል ወገን ቀርቦ ስለኑዛዜው ፎርማሊቲ ሳይሆን ስለኑዛዜው ሕጋዊነት ኑነኮዛዜው የሚሻርባቸውን ወይም ውድቅ የሚሆንባቸውን ምክንያቶች በሚመለከት ክርክር ከአነሳ በዚህ ረገድ ጭብጦችን ይዞ ተገቢውን ዳኝነት መስጠትን የሚጠይቅ ጊ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ነውና ስለሆነም የኑዛዜ ወራሽነት ይረጋገጥልኝ የሚለው ጥያቄ በፍርድ ቤት አንዲቀርብ ሕጉ የግድ አይልም ሲባል ከኑዛዜ ፎርማሊቲ ጋር ተያይዞ የሚታይ እንጂ ስለነዛዜው ሕጋዊነት ጭምር ነው ሊባል የሚችል አይደለም የኑዛዜ ወራሽነት ይረጋገጥልኝ በሚል አቤቱታ በተከፈተ መዝገብ ላይ ኑዛዜው ሕጋዊ አይደለም የሚል ተከራካሪ ወገን ከቀረበ ደግሞ ፍቤቱ ወደ ኑዛዜው ይዘት እና ሕጋዊነት ሁኔታ ገብቶ ውሳሄ መስጠትን የግድ የሚል በመሆኑ በጉዳዩ ላይ ግራ ቀኙን በሕጉ አግባብ በመስማትና በሚገባ በማጣራት ተገቢውን ዳኝነት መስጠት ስነ ስርዓታዊ እንጂ በንብረት ክርክር ጊዜ የሚታይ ነው ተብሉ የሜታለፍ አይደለም ክርክሩ በንብረት ክርክር ጊዜ የሚታይ ነው ብሎ መዝገቡን መዝጋትም ክርክሮች በአነስተኛ ወጪ በተፋጠነ ጊዜና ፍትፃዊ በሆነ መልኩ መሰጠት አለባቸው ከሚለው የስነ ስርዓት ሕጉ መሰረታዊ ዓላማ ጋርም አብሮ የማይሄድ በመሆኑ ተገቢነት የለውም ሲጠቃለል የስር ፍቤቶች በጉዳዩ ላይ የሰጡት ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ሆኖ ስለአገኘን ተከታዩን ወስነናል ውሳኔ በአዳማ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት በመቁጥር በ ዓም ተሰጥቶ በአዳማ ልዩ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁጥር በ ዓም በኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር አጣሪ ችሎት በመቁጥር በ ዓም በትእዛዝ የፀናው ብይን በፍብሥሥሕግ ቁጥር መሠረት ተሽሯል የአዳማ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ክርክሩን በመቁጥር ቀጥሎ የግራ ቀኙን ክርክርና ማስረጃ በመስማት እንዲሁም አስፈላጊ ሁኖ ሲያገኘው ለጉዳዩ አግባብነት ያላቸውን ማስረጃዎች በማስቀረብና ክርክሩን ስነ ስርዓቱ በሚፈቅደው አግባብ ጭምር በመመራት በጉዳዩ ላይ ተገቢውን ዳኝነት እንዲሰጥበት ጉዳዩን በፍብሥሥሕቁጥር መሰረት መልሰን ልከንለታል ይጻፍ ወጪና ኪሣራ በተመለከተ ግራ ቀኙ ወገኖች የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ውል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁጥር ቀንግንቦት ቀን ዓም ዳኞች ብርሃኑ አመነዉ በዕዉቀት በላይ እንዳሻዉ አዳነ ኃይሉ ነጋሽ አትመት አሰፋ አመልካች ወሮ ዘቢባ ሙሳ ተጠሪ አቶ አማን በሪሶ መዝገቡ ተመርምሮ የሚከተለዉ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ለዚህ ሰበር ክርክር መነሻ የሆነው የከተማ ቦታ ይዞታ ጉዳይ ሲሆን የተጀመረው በኦሮሚያ ክልል በአዳማ ወረዳ ፍርድ ቤት ነው በዚሁ ፍቤት የአሁኑ አመልካች በተጠሪ ላይ ያቀረቡት ክስ ይዘት በአዳማ ከተማ ቀበሌ ዉስጥ የሚገኘዉን የካርታ ቁጥሩ የሆነዉ ካሜ የመኖሪያ ቤት ቦታ በአዳማ ከተማ መስተዳድር ተሰጥቶ በስሜ ተመዝግቦ የሚገኘዉን ተጠሪ ምንም መብት ሳይኖረዉ ቦታዉ ላይ ቤት መስራቱን አይቼ ግንባታዉን እንዲያቆም ብጠይቀዉም ፈቃደኛ ስላልሆነ ግንባታዉን በራሱ ወጪ አፍርሶ ይዞታዉን ይልቀቅልኝ የሚል ነዉ ተጠሪ በበኩላቸዉ በሰጡት መልስ ለክርክሩ መነሻ የሆነዉ መሬት አስመልክቶ አመልካች መንግስት አካል ጋር በመቅረብ በዉክልና ቁጥር በቀን ዓም ለአቶ ፋአድ ጀማል ሙሳ ይዞታዉንና ንብረቷን እንዲሸጥ እንዲለዉጥ ለኛ ወገን በማንኛዉም ሁኔታ እንዲያስተላልፍ ዉክልና ሰጥታዉ አሱም ዉክልና አቶ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አህመድ ለሚባል አሳልፎ ሰጥቶ ዉክልናዉ ሕጋዊ መሆኑን አረጋግጩ በቀን ዓም በተጻፈ የግዥ እና ሽያጭ ዉል በብር ተስማምቼ ገዝቼ ዉሉም ስልጣን ባለዉ አካል ጸድቆ የሊዝ ዉሉ ወደ ስሜ ተዛዉሮ የይዞታ ማረጋገጫ ተሰጥቶኝ ባለይዞታ የሆንኩበትና አመልካች ሳይቃወሙ የገነባሁት ቤት ስለሆነ ክሱ ተቀባይነት የለዉም በማለት ተከራክረዋል የወረዳዉ ፍቤት የግራቀኙን ክርክር ከሰማ በኃላ መርምሮ ተጠሪ ክርክር ያስነሳዉን ይዞታ አመልካች ስልጣን ባለዉ አካል ፊት ለመሸጥ ዉክልና ከተሰጠዉ ሰዉ ጋር ተዋዉሎ የገዛና በአመልካች ስም የነበረዉ ወደ ተጠሪ ተዘዋዉሮና ተመዝግቦ የሚታወቅ በመሆኑ አንዲሁም አመልካች ከኢሜግሬሽን እና የዜግነት ጉዳዮች ጽቤት ያቀረቡት ማስረጃም ቢሆን ከአመልካች ጋር ሳይሆን ከአመልካች ተወካይ ጋር ዉሉ የተደረገ በመሆኑና ተጠሪ አመልካች ከአገር መኖር አለመኖራን የማወቅ ግዴታ የሌለዉ በመሆኑ አመልካች ተጠሪ ይዞታዬን በሕገወጥ መንገድ ይዚል በማለት ያቀረቡት ክስ ተቀባይነት የለዉም በማለት ወስኗል በዚህ ዉሳኔ ቅር ተሰኝተዉ አመልካች ባቀረቡት ይግባኝ መነሻ ጉዳዩን የተመለከተዉ የአዳማ ከፍተኛ ፍቤት ግራ ቀኙን ካከራከረ በኃላ የስር ፍቤትን ዉሳኔ በማጽናት ወስኗል በመቀጠል አመልካች የሰበር አቤቱታ ለክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ቢያቀርቡም አቤቱታዉ ተቀባይነት አላገኘም ይህ የሰበር አቤቱታ የቀረበው በዚሁ ውሳኔ ላይ አመልካች ቅር በመሰኘታቸዉ ዉሳኔዉን ለማስለወጥ ነው አመልካች ያቀረቡት የሰበር አቤቱታ ይዘት ለክርክሩ ምክንያት የሆነዉ የመኖሪያ ቤት ቦታዬ እንዲሸጥም ሆነ እንዲለወጥ የሰጠሁት ሕጋዊ ዉክልና እንደሌለ እየተከራከርኩ አና ዉክልናዉ ተሰጥቶኛል በተባለበት ወቅትም ሀገር ዉስጥ ያልነበርኩ መሆኔን በመግለጽ የኢሚግሬሽን እና የዜግነት ጉዳዮች ቢሮ በቀን ዓም ለአዳማ ወረዳ ፍቤት በመግለጽ ተጽፎ እያለ ጉዳዩ በሚገባ ሳይጣራ ሀሰተኛ በሆነ ዉክልና ስሙ ከአመልካች ጋር የሚመሳሰል በመሆኑ ብቻ ተጠሪ በዚህ ዉክልና መሠረት በግዢ ዉል የያዘዉ ነዉ በማለት የሰጠዉ ዉሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ነዉ የምስራቅ ሸዋ ዞን ፍትህ ቢሮ በቀን ዓም ለወረዳዉ ፍቤት በጻፈዉ ደብዳቤ አመልካች በአካል ቀርባ የዉክልና ቁጥሩ የሆነ በቀን ዓም ዉክልና ሰጥታለች በማለት ስለገለጸ ብቻ የወረዳዉ ፍቤት ዉሳኔ መስጠቱ ተገቢ አይደለም ምክንያቱም ዉክልና ሰጥታለች በተባለበት ቀን በአገር ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ያልነበርኩ መሆኔን ስልጣን ከተሰጠዉ አካል በተጻፈ ደብዳቤ ተረጋግጧል ስለሆነም ዉሳኔዉ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ ይሻርልኝ የሚል ነዉ የአመልካች አቤቱታ ተመርምሮ አመልካች ዉክልናዉ ተሰጠ በተባለበት ጊዜ በሀገር ዉስጥ አልነበርኩም በማለት ከኢሚግሬሽን የተጻፈ መግለጫ ያቀረበችዉና በዉክልናዉ ላይ ያለዉ ፊርማ በፎረንሲክ እንዲመረመር የጠየቀችዉ በስር ፍቤት የታለፈበትና ዉድቅ የተደረገበትን አግባብነት ለማጣራት ሲባል ጉዳዩ ለሰበር ያስቀርባል የተባለ ሲሆን ግራቀኙ መልስ እና የመልስ መልስ በጽሁፍ በማቅረብ ተከራክረዋል የተጠሪ መልስ ይዘት በአጭሩፁ ከኢሚግሬሽን የመጣ ደብዳቤ እና የፎረንሲክ ምርመራን ከፍትሕ ቢሮ ከመጣዉ ደብዳቤ ጋር አመዛዝኖ ዉሳኔ መስጠት የስር ፍቤት ማስረጃን የመመዘን ስልጣን አንጂ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ስላልሆነ አቤቱታዉ ዉድቅ ይደረግልኝ አመልካች በስር ፍቤት ያቀረቡት ክስ በሕገወጥ መንገድ ያለእኔ ፈቃድ የተደረገ የሽያጭ ዉል ይፍረስልኝ የሚል እስካልሆነ ድረስ የሚያዘዉ ጭብጥ ከቀረበዉ ክስ አንጻር ተጠሪ ንብረቱን የያዘዉ በሕገወጥ መንገድ ነዉ ወይስ በሕጋዊ መንገድ የሚለዉ ነዉ ለዚህ በማስረጃነት ያቀረብኩት አመልካች እራሷ ለወንድሟ የሰጠችዉን ዉክልና ወንድሟ ለአቶ አህመድ የሰጠዉን ዉክልና በእኔና በኛ ተወካይ መካከል የተደረገ ሕጋዊ የሽያጭ ዉል እንዲሁም የሊዝ ዉል በስሜ የተሰጠኝ ካርታና ፕላን እና የግንባታ ፈቃድ ነዉ ዉክልናዉ ሕጋዊ ስለመሆኑ የፍትህ ቢሮ እና ማዘጋጃ ቤቱ ተጠይቆ በስር ፍቤት ተረጋግጧል ይህ መሠረት ተደርጎ ማስረጃ ተመዝኖ የተሰጠ ዉሳኔ በመሆኑ መሠረታዊ የሕግ ስህትት ተፈጽሞበታል የሚባል አይደለም ኢሚግሬሽን መስሪያ ቤት በ ዓም በጻፈዉ ደብዳቤ ላይ በግልጽ እንዳመለከተዉ አመልካች በአካል ቀርባ አገር ዉስጥ ስለመኖሯ አረጋግጦ ሳይሆን ካላቸዉ ዳታ ዉስጥ ባደረገዉ ማጣራት መሆኑን ገልጽዋል ይህ ማስረጃ በአካል ቀርባ ከሰጠችዉ ዉክልና ጋር ተመዝኖ የተሰጠዉ ዉሳኔ ተገቢ ነዉ በ ዓም በተጻፈዉ ደብዳቤ አመልካች በ ወደ ሮም መሄዷን የገለጸ ሲሆን በ ዓም በጻፈዉ ደብዳቤ ላይ ደግሞ አመልካቿ በ ወደ አገር ዉስጥ ገብታ በ ከአገር መዉጣቷን ወይም ካናዳ መሄፄዷንና አገር ዉስጥ ተመልሳ ያልገባች መሆኑን ይገልጻል ይህም እርስ በርሱ የሚጋጭ ነዉ በፎረንሲክ ፊርማዉ መጣራት ነበረበት የሚለዉም ቢሆን ዉክልናዉ የመንደር ዉል ሳይሆን ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ስልጣን ከተሰጠዉ የመንግስት አካል ተረጋግጦ የቀረበ በመሆነ ክርክሩ ተገቢነት የለዉም ስለሆነም የስር ፍቤቶች ዉሳፄ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ባለመሆኑ ይጽናልኝ የሚል ነዉ አመልካች በሰጡት የመልስ መልስ የሰበር አቤቱታቸዉን በሚያጠናክር መልኩ ተከራክረዋል የግራ ቀኙ ክርክር በአጭሩ ከላይ የተመለከተዉን የሚመስል ሲሆን ከስር ፍቤት ዉሳኔ እና ጉዳዩ ለሰበር ያስቀርባል ተብሎ ከተያዘዉ ጭብጥ ጋር በማገናዘብ መርምረናል መርምረን አንደተረዳነዉ በስር ፍቤት አመልካች ክስ ያቀረቡት ተጠሪ በሕገወጥ መንገድ ይዞታዬን በመያዝ የገነባዉን ግንባታ በራሱ ወጪ እንዲያፈርስ የሚጠይቅ ሲሆን ተጠሪ በበኩሉ ይዞታዉ አስቀድሞ የአመልካች የነበረ ቢሆንም በሕጋዊ መንገድ የዉክልና ስልጣን ካለዉ ሰዉ ጋር ተዋዉሎ መግዛቱንና ሕጋዊ ባለይዞታ መሆኑን በመግለጽ ክሱ ዉድቅ እንዲደረግለት በመጠየቅ ተከራክሯል የስር ፍቤትም አመልካች ስልጣን ባለዉ የመንግስት አካል ጋር ቀርባ የዉክልና ቁጥሩ በሆነ ጥቅምት ቀን ዓም ለአቶ ፉአድ ጀማል ሙሳ ይኮዞታዉንና ንብረቱን አእንዲሸጥ አንዲለዉጥና ለኛ ወገን በማንኛዉም መንገድ እንዲያስተላልፍ ዉክልና መስጠቷን ተወካይዋ ደግሞ በተሰጠዉ ዉክልና መሠረት ለአቶ አህመድ በሪሶ ቁጥሩ በቀን ዓም ምስራቅ ሸዋ ፍትሕ መምሪያ ቀርቦ ዉክልና መስጠቱን አንዲሁም አቶ አህመድ በሪሶ ደግሞ መጋቢት ቀን ዓም ከተጠሪ ጋር ባደረገዉ የሽያጭ ዉል ይዞታዉን ለተጠሪ ሸጦለት ቅድመ ሁኔታዎቹ ተሟልቶ የሊዝ ዉሉ ወደ ተጠሪ ስም መዛወሩንና የይዞታ ማረጋገጫና የግንባታ ፈቃድ የተሰጠዉ መሆኑ አረጋግጧል ዉክልናዎቹ ትክክለኛ መሆናቸዉ እና በአግባቡ ሽያጭና የስም ዝዉዉር ተደርጎ ይዞታዉ ለተጠሪ መተላለፉን የምስራቅ ሸዋ ፍትሕ መምሪያና በአዳማ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቤት ተጠይቀዉ አረጋግጠዋል አመልካች አጥብቃ የምትከራከረዉ ዉክልና ሰጥታለች በተባለችበት ወቅት አገር ዉስጥ ያልነበረች መሆኑን ኢሚግሬሽንና የዜግነት ጉዳዮች መስሪያ ቤት አረጋግጦልኛል አንዲሁም በዉክልናዉ ላይ ያለዉ ፊርማ የእኔ አይደለም በፎረንሲክ ይመርመርልኝ በሚል ነዉ በመሠረቱ አንድ የዉክልና ሰነድ ሰነዶችን ለማረጋገጥና ለመመዝገብ ስልጣን በተሰጠዉ አካል ፊት እንዲሰጥና እንዲመዘገብ ያስፈለገበት ዋናዉ ምክንያት ዉክልናዉ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ትክክለኛ አና በወካዩ አማካይነት የተሰጠ መሆኑን በማረጋገጥ ዉክልናን መሠረት ተደርገዉ የሚፈጸሙ ሕጋዊ ተግባራት የተሳለጡ እንዲሆነ ለማስቻልና ዉክልናዉ በወካይ አልተሰጠም የሚል አላስፈላጊ ክርክርና ጥርጣሬዎችን ለማስወገድ ነዉ በዚህ ረገድ በአዋጅ ቁ አንቀጽ ላይ እንደተደነገገዉ በሰነድ መዝጋቢዉ አካል የተረጋገጠዉ ሰነድ ሙሉ እምነት የሚጣልበት ማስረጃ ሆኖ ቅቡልነት ያለዉ ነዉ ይህንን ሰነድ ቅቡልነት መቃወም የሚቻለዉም በበቂ ምክንያት ፍርድ ቤት ሲፈቅድ ብቻ አንደሆነ በዚሁ አንቀጽ ንኡስ ሁለት ስር ተመልክቷል ስለሆነም አመልካች ሰነዱን የሚቃወሙበት በቂና ህጋዊ ምክንያት ካላቸዉ ሰነዱ እንዲሰረዝ በህግ አግባብ ከሚጠይቁ በስተቀር በሚመለከተዉ አካል የተረጋገጠ የዉክልና ሰነድ ቅቡልነት ሊኖረዉ አይገባም የሚለዉ ክርክር ስለሰነዶች ምዝገባ የወጣዉን አዋጅ ይዘትና ዓላማ ያላገናዘበ እንደሆነ መረዳት ይቻላል ከዚህ አንጻር ከተወካይ ጋር ዉል የሚገባ ሰዉ ዉክልናዉ በተወካይ የተሰጠና ተመዝግቦ የሚገኝ መሆኑን ከማረጋገጥ ባለፈ ወካይ ውክልናዉ በተሰጠበት ወቅት በአገር ዉስጥ መኖር አለመኖራቸዉንና ፊርማዉ የወካይ መሆን አለመሆኑን የሚያጣራበት አግባብ የለም በተያዘዉ ጉዳይ አመልካች ተጠሪ ይዞታዉ በሽያጭ ዉል ተላልፎልኛል ያለበት ዉክልና በአመልካች ያልተሰጠና የሀሰት ነዉ በማለት የሚከራከሩት የኢሚግሬሽንና የዜግነት ጉዳዩች መስሪያ ቤት አመልካች ከአገር የወጣችበትና ወደ አገር የገባችበትን ቀን የገለጸ በመሆነ ዉክልና በተሰጠበት ጊዜ በአገር ያልነበርኩ በመሆኔ ዉክልናዉን ልሰጥ አልችልም ፊርማዉ የእኔ ባለመሆኑ በፎረንሲክ ይመርመርልኝ የሚል ነዉ ዉክልናዉ ሰነዶችን ለማረጋገጥና ለመመዝገብ ስልጣን በተሰጠዉ አካል ፊት ተሰጥቶ ተመዝግቦ የሚገኝ መሆኑ እስከተረጋገጠ ድረስ አመልካች ከአገር የወጡበትና ወደ አገር የገቡበትን ጊዜ በማረጋገጥ እንዲሁም በዉክልናዉ ላይ ያለዉ ፊርማ በፎረንሲክ ቢመረመርና ልዩነት አለዉ ቢባል አንኳ ዉክልናዉ በአመልካች አልተሰጠም የሚል ድምዳሜ ላይ የሚያደርስ አይሆንም ስለሆነም አመልካች ከአገር የወጡበትን አና ወደ አገር የገቡበትን ጊዜ በማስረዳት እንዲሁም በዉክልና ሰነዱ ላይ ያለዉ ፊርማ ከአመልካች ከተለመደዉ ፊርማ ጋር ልዩነት ያለዉ መሆን ያለመሆኑን በማስመርመር ዉክልናዉ በአመልካች አልተሰጠም የሚል ድምዳሜ ላይ መድረስ የሚቻል ባለመሆኑ የስር ፍቤት ዉክልናዉ በአመልካች የተሰጠና ተመዝግቦ የሚገኝ መሆኑን ሰነዶችን ለመመዝገብና ለማረጋገጥ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ስልጣን ተሰጥቶት ዉክልናዉን የመዘገበዉን አካል በመጠየቅና በማረጋገጥ እንዲሁም በዉክልናዉ መሠረት የሽያጭ ዉል ተፈጽሞ ይዞታዉ ወደ ተጠሪ ስም በሕግ አግባብ ተላልፎ ተጠሪ ባለይዞታ የሆነበት መሆኑን በማረጋገጥ የአመልካችን ክስ ዉድቅ ማድረጉ የሚነቀፍ ሆኖ አልተገኘም ሲጠቃለል ተጠሪ ክርክር ያስነሳዉ ይዞታ በሕግ አግባብ ተላልፎለት የባለይዞታነት መብት መፍጠሩን በማረጋገጥ አመልካች ተጠሪ በሕገወጥ መንገድ የያዘብኝን ይዞታ ይልቀቅልኝ በማለት ያቀረቡትን ክስ ዉድቅ በማድረግ የወረዳዉ ፍቤት የሰጠዉም ዉሳኔ ሆነ በየደረጃዉ ጉዳዩን የተመለከቱት የስር ፍቤቶች ዉሳኔዉን ማጽናታቸዉ የሚነቀፍበት በቂ ምክንያት ባለመኖሩ ዉሳኔዉ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል ለማለት አልተቻለም በመሆኑም የሚከተለዉ ዉሳኔ ተሰጥቷል ዉሳኔ በአዳማ ከተማ ወረዳ ፍቤት በመቁ ታሕሳስ ቀን ዓም ተሰጥቶ በአዳማ ልዩ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በመቁ የካቲት ቀን ዓም በተሰጠ ዉሳኔ እና በክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት በሰመቁ ግንቦት ቀን ዓም በተሰጠ ትዕዛዝ የጸናዉ ዉሳኔ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ጸንቷል የሰበር ክርክሩ ያስከተለዉን ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ የየራሳቸዉን ይቻሉ መዝገቡ ዉሳኔ ያገኘ ስለሆነ ተዘግቷል ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ሰጌ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ቀን ዓም ዳኞች ተኽሊት ይመሰል ተፈሪ ገብሩ ሀቦር ቀነዓ ቂጣታ ተሾመ ሽፈራዉ አብዬ ካሳሁን አመልካች አቶ ቶዉፊቅ ላሉ ቀርበዋል ተጠሪ አቶ ስራጅ ጀማል ቀርበዋል መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ክርክሩ የተጀመረዉ በስልጤ ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች ከሳሽ ተጠሪ ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል የአመልካች ክስም በአጭሩ በ ዓም ወደ አረብ አገር ስፄድ ዋጋቸዉ በድምሩ ብር የሚያወጣዉን አንድ በሬ አንዲት ላም ከነጥጃዋ እና አንዲት ሴት አህያ ተከሳሽ እንዲጠብቅልኝ አደራ ሰጥቻቸዋለሁ እንዲሁም መኖሪያ ቤት እና ንግድ ቤት እንዲገዙልኝ አረብ አገር ሆፔ ብር የላኩላቸዉ ቢሆንም ተከሳሽ ብር መልሰዉልኝ ቀሪዉን ገንዘብ ለመመለስ ፊቃደኛ አልሆኑም በመሆኑም ከብቶቹን እንዲሁም ቀሪዉን ገንዘብ ብር ተከሳሽ እንዲመልሱ ይወሰንልኝ የሚል ይዘት ያለዉ ነዉ ተጠሪ ለቀረበባቸዉ ክስ በሰጡት መልስ በክሱ የተጠቀሱትን ከብቶች ከከሳሽ በአደራ አልተቀበልኩም ከሳሽ ቤት እንዲገዛላቸዉ ዉጭ አገር ሆነዉ የላኩልኝ ገንዘብ የለም ተከሳሽ ተከፍሎኛል ያሉት ብር ብድር የሰጠሁት ነዉ በማለት የቀረበባቸዉ ክስ ዉድቅ እንዲሆን በማለት ተከራክረዋል በበኩላቸዉ ባቀረቡት የተከሳሽ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ከሳሽነት ክስ በብድር መልክ በባንክ ሂሳባቸዉ ገቢ ያደረግኩትን ገንዘብ ብር ከሳሽ እንዲከፍሉኝ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት የጠየቁ ሲሆን አመልካች በበኩሉ ከተጠሪ የተበደርኩት ገንዘብ የለም በማለት ተከራክረዋል ጉዳዩ በመጀመሪያ የቀረበለት የወረዳ ፍርድ ቤትም በዚህ መልኩ ከግራ ቀኝ የቀረበዉን ክርክር እንዲሁም ማስረጃ ከሰማ በኋላ አመልካች ከብቶቹን ለተጠሪ አደራ መስጠቱን ለማስረዳት ቀርበዉ የተሰሙት የሰዉ ምስክሮች ቃል የተለያየ እና እርስ በርሱ የሚጋጭ በመሆኑ በግራ ቀኝ መካከል በህግ አግባብ የተደረገ የአደራ ዉል ስለመኖሩ አለመረጋገጡን እንዲሁም ከብር በላይ የሆነ ጥሬ ገንዘብን በአደራ የመስጠት ዉል ስለመኖሩ ማስረዳት የሚቻለዉ በጽሑፍ በተደረገ ዉል መሆኑን እና አመልካች በዚህ መልኩ ያቀረቡት ማስረጃ አለመኖሩን የፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ እና በዋቢነት በመጥቀስ የአመልካችን ክስ ዉድቅ ያደረገ ሲሆን ተጠሪ ለአመልካች ብር አበድሬያለሁ ያሉትንም በተመለከተ በፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ መሠረት ይህን የሚያስረዳ በጽሑፍ የተደረገ የብድር ዉል አለመኖሩን ጠቅሶ የተከሳሽ ከሳሽነት ክሱንም ዉድቅ በማድረግ ወስኗል አመልካች ይህን ዉሳኔ ባለመቀበል ለስልጤ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ያቀረበ ቢሆንም የዞነ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የስር ፍርድ ቤቱን ዉሳኔ በማጽናቱ አመልካች ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር አቤቱታ ያቀረበ ቢሆንም የክልሉ ሰበር አጣሪ ችሉት የቀረበዉን የሰበር አቤቱታ ሰርዞታል ይህ የሰበር አቤቱታ የቀረበዉም በዚህ ዉሳኔ ቅር በመሰኘት ለማስለወጥ ሲሆን አመልካች በቀን ዓም ተዘጋጅቶ በቀረበ የሰበር አቤቱታ በስር በክልሉ በየደረጃዉ ባሉት ፍርድ ቤቶች የተሰጡት ዉሳኔዎች እና ትዕዛዝ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመባቸዉ ናቸዉ የሚሉባቸዉን ምክንያቶች በመዘርዘር ታርሞ ይወሰንላቸዉ ዘንድ ዳኝነት ጠይቀዋል አቤቱታዉ ተመርምሮ ያስቀርባል በመባሉም ተጠሪ በተደረገላቸዉ ጥሪ መሠረት ቀርበዉ ግራ ቀኝ ክርክራቸዉን በጽሑፍ ተለዋዉጠዋል የጉዳዩ አመጣጥ በአጭሩ ከላይ የተገለጸዉ ነዉ እኛም የስር ፍርድ ቤቶች የአመልካችን ክስ ዉድቅ በማድረግ የሰጡትን ዉሳኔ አግባብነት ከግራ ቀኝ ክርክር እና ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ለጉዳዩ አግባብነት ካላቸዉ ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ መዝገቡን እንደሚከተለዉ መርምረናል ከክርክሩ ሄደት መገንዘብ የተቻለዉ አመልካች በስር ፍርድ ቤት ላቀረቡት ክስ መሠረት ያደረጉት ተጠሪ የተለያዩ ከብቶችን ሊጠብቁላቸዉ በአደራ መቀበላቸዉን እንዲሁም ቤት እንዲሰሩላቸዉ አመልካች የላኩትን ገንዘብ ተቀብለዉ አለመመለሳቸዉን ነዉ ተጠሪ በበኩላቸዉ ከብቶቹንም ሆነ ገንዘቡን ከአመልካች በአደራ አለመቀበላቸዉን ገልጸዉ የተከራከሩ መሆኑን የስር ፍርድ ቤት ዉሳኔ ግልባጭ ያሳያል በመሆኑም አመልካች በክሱ የተመለከቱትን ከብቶችም ሆነ ገንዘቡን ለተጠሪ በአደራ መልክ የሰጣቸዉ ስለመሆኑ በቅድሚያ የማስረዳት ግዴታ ይኖርባቸዋል ከብቶቹን በአደራ መስጠታቸዉን በተመለከተ አመልካች የሰዉ ምስክሮችን አቅርበዉ ያሰሙ ሲሆን የወረዳዉ ፍርድ ቤትም አመልካች ያቀረቧቸዉን የሰዉ ምስክሮች ቃል በመመዘን የቀረቡት የሰዉ ምስክሮች ቃል የተለያየ እና እርስ በእርሱ የሚጋጭ መሆኑን ጠቅሶ የአደራ ዉል በመካከላቸዉ ስለመደረጉ አላስረዱም በሚል ድምዳሜ ላይ መድረሱን ተመልክተናል በሌላ በኩል በኢፌዲሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ ለ እንዲሁም በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት የዚህ ሰበር ሰሚ ችሎት ስልጣን መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተትን በማረም ላይ የተገደበ በመሆኑ ከፍሬ ነገር ጋር በተያያዘ በስር ፍርድ ቤቶች የቀረቡትን ማስረጃዎች ድጋሚ ሊመዝን የሚችልበት ህጋዊ ምክንያት አይኖርም ስለሆነም አመልካች በክሱ የተመለከቱትን ከብቶች ለተጠሪ በአደራ ስለመስጠቱ አልተረጋገጠም በሚል የስር ፍርድ ቤት የደረሰበት ድምዳሜ መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነዉ ለማለት የማይቻል በመሆኑ አመልካች በዚህ ረገድ ያቀረቡት ክርክር ተቀባይነት ያለዉ አይደለም ከዉጭ አገር የተላከ ገንዘብን በተመለከተ አመልካች የሚከራከሩት ተጠሪ የንግድ እና የመኖሪያ ቤት አንዲሰሩላቸዉ ገንዘቡን መላካቸዉን ነዉ ከላይ እንደተመለከተዉ ተጠሪ የተላከላቸዉ የአደራ ገንዘብ አለመኖሩን ገልጸዉ ተከራክረዋል የስር የወረዳዉ ፍርድ ቤት በዉሳኔዉ እንዳመለከተዉም በአደራ የተሰጠ ገንዘብ መኖሩን ለማስረዳት ተቀባይነት የሚኖረዉ ማስረጃ በጽሑፍ የተደረገ የአደራ ዉል ስለመሆኑ በፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ እና ድንጋጌዎች ጣምራ ንባብ መረዳት ይቻላል ይሁንና አመልካች በዚህ መልኩ ያቀረቡት ማስረጃ የለም በሌላ የሰዉ ወይም የሰነድ ማስረጃ ደግሞ ይህን ማረጋገጥ አይቻልም ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በአጠቃላይ የስልጤ ወረዳ ፍርድ ቤት የአመልካችን ክስ ዉድቅ በማድረግ የሰጠዉ ዉሳኔ እንዲሁም የስልጤ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት እና የክልሉ ሰበር ችሎት የወረዳዉን ፍርድ ቤት ዉሳኔ በማጽናት በቅደም ተከተል የሰጡት ፍርድ እና ትዕዛዝ በህግ አግባብ ነዉ ከሚባል በስተቀር መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ አላገኘንም በመሆኑም ተከታዩ ተወስኗል ዉሳኔ የደቡብ ብብሕክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም በዋለዉ ችሎት የስልጤ ወረዳ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም በዋለዉ ችሎት እንዲሁም የስልጤ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም በዋለዉ ችሎት የሰጠዉን ዉሳኔ በማጽናት የሰጠዉ ትዕዛዝ በፍሥሥህጉ አንቀጽ መሠረት ፀንቷል በዚህ ችሎት በተደረገ ክርክር ምክንያት የወጣዉን ወጪ እና ኪሳራ ግራ ቀኝ የየራሳቸዉን ይቻሉ በዚህ ችሎት በቀን ዓም ተሰጥቶ የነበረዉ ዕግድ ተነስቷል ይፃፍ መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት አጐ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ታህሳስ ቀን ዓም ዳኞች ተኽሊት ይመስል ተፈሪ ገብሩ ዶር ቀነአ ቂጣታ ተሾመ ሽፈራው ፀሐይ መንክር አመልካች አቶ ሰለሞን መርደኪዮስ ቀረቡ ተጠሪ አቶ ሲሳይ ለበኔ አልቀረቡም በዚህ መዝገብ የተያዘውን ጉዳይ ከሰመቁ ጋር በማጣመር መርምረን የሚከተለውን ውሳኔ ሰጥተናል ፍርድ ለሰበር አቤቱታዎቹ መቅረብ ምክንያት የሆነው ክርክር የተጀመረው ተጠሪ በአመልካች ላይ በደቡብ ክልል አርባ ምንጭ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ባቀረቡት ክስ ነው ተጠሪ ባቀረቡት ክስ ከገኔ ዩናይትድ የመኪና አስመጪ ኃየተየግማህበር ጋር በነበረን ውል መሰረት ቅድመ ክፍያ ብር መቶ ስድሳ ሺህ በመክፈል ሚኒባስ መኪና ለመውሰድ ስጠባበቅ ድርጅቱ የኢኮኖሚ ችግር ገጥሞት ሊፈጽም ባለመቻሉ የአሁኑ አመልካች ለድርጅቱ ከሚከፍለው ብር ሁለት መቶ ሃምሳ አራት ሺህ ውስጥ የእኔን ገንዘብ ሊከፍል የዕዳ ማስተላለፍ ውል አድርገናል ነገር ግን አመልካች ብር አራት ሺህ ብቻ ከፍሎ ሌላውን ስልላከፈለ ቀሪውን ብር መቶ ሃምሳ ስድስት ሺህ ከህጋዊ ወለድ ጋር እንዲሁም በውሉ ከተመለከተው ብር ፃምሳ ሺህ መቀጮና ክርክሩ ካስከተለው ወጪና ኪሳራ ጋር አንዲከፍል ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው አመልካች ለክሱ በሰጡት መልስ በውሉ መሰረት የዕዳ መክፈያ ጊዜ ገና ወደፊት ነው በየሳምንቱ ብር ሁለት ሺህ ለመክፈል የተስማማን ሲሆን የሁለት ሳምንት ብር አራት ሺህ እንደከፈልኩ ውሉ እንደተቋረጠ አድርጎ መክሰሱ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ያላግባብ ነው ዕዳው በአንድ ጊዜ የሚከፈል ሳይሆን በ ሳምንታት የሚከፈል ነው መኪናዬ ላይ የደረሰው ብልሽት ለውሉ አለመፈፀም ምክንያት መሆኑን እያወቀ ክስ መመስረቱም ያላግባብ ነው ስለሆነም በየሳምንቱ ብር ሁለት ሺህ አየከፈልኩ ዕዳውን እንድጨርስ ይወሰን በማለት ተከራክረዋል ጉዳዩ በዚህ መልኩ የቀረበለት የስር ፍርድ ቤት ክርክርና ማስረጃውን መርምሮ አንደውሉ ግዴታውን ያልተወጣ ተከሳሽ ስለመሆነ በማስረጃ ስለተረጋገጠና ተከሳሽ በመኪናው መበላሸት ምክንያት አንደውሉ አለመፈጸሙን የገለፀ ቢሆንም ስለመኪናው መበላሸት በውሉ ላይ ያልተገለፀ በመሆነ መከላከያ ሊሆን አይችልም በሌላ በኩል በውሉ አንቀጽ መሰረት መቀጮ ብር ሊከፍል እንደሚገባ የተመለከተ ቢሆንም ይህ የመቀጮ ገንዘብ የተጋነነ እና ለህግና ለሞራል ተቃራኒ በመሆኑ ሊሻሻል ይገባል በማለት ተከሳሽ የአሁን አመልካች ያልከፈሉትን ብር ከ ወለድ ጋር እንዲከፍሉ እንዲሁም ከሳሽ የወጪና ኪሳራ ዝርዝር እንዲያቀርቡ በማለት ወስኗል በዚህ ውሳኔ ላይ የአሁን ተጠሪ በውል የተመለከተው የመቀጮ ገንዘብ እንዲከፈል አለመወሰኑን በመቃወም የይግባኝ ቅሬታቸውን ለጋሞ አካባቢ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርበዋል ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ተከሳሽ የውል ግዴታውን በአግባቡ አለመወጣቱ በማስረጃ ከተረጋገጠ በኋላ በውል የተመለከተው መቀጮ ሊከፈል አይገባም መባሉ አላግባብ ነው በማለት የስር ፍርድ ቤት ያሳለፈውን ውሳኔ አሻሽሎ በውላቸው የተቀመጠውን ብር አመልካች ለተጠሪ እንዲከፍል ወስኗል አመልካች ይህን ውሳኔ በመቃወም ቅሬታቸውን ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት አቅርበው ችሎቱም ጉዳዩን መርምሮ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ያሳለፈውን ውሳኔ በመሻር የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ውሳኔን አጽንቷል በዚህ ውሳኔ ላይ የአሁን ተጠሪ ቅሬታቸውን ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት አቅርበዋል የሰበር ችሎቱ የግራቀኙን ክርክር መርምሮ የሥር ፍርድ ቤቶችን ውሳሄ በማሻሻል አመልካች ዋናውን ገንዘብ ብር አና በውላቸው የተስማሙበትን ብር ለተጠሪ ሊከፍሉ ይገባል መቀጮ እንዲከፍሉ የተወሰነ በመሆኑ ወለድ ሊከፍሉ አይገባም በማለት ወስኗል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰበር አቤቱታው ለዚህ ፍርድ ቤት የቀረበው ይህን በመቃወም ነው አመልካች ነሓሴ ዓም ባቀረቡት አቤቱታ ገና ወደፊት ሰማንያ ሳምንት የክፍያ ጊዜ ላለው ዕዳ መቀጮ እንድከፍል መወሰኑ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት በመሆኑ የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠው ውሳኔ ተሽሮ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሉት የሰጠው ውሳኔ እንዲፀና ይወሰንልኝ በማለት ጠይቀዋል ጉዳዩ ለሰበር ችሎት እንዲቀርብና ተጠሪ መልስ አንዲሰጡበት የተደረገ ሲሆን ተጠሪ ጥቅምት ዓም በተዛፈ መልስ ውሳኔ የተሰጠው በመካከላችን የተደረገውን ውል እና የቀረበውን ማስረጃ መሰረት በማድረግ በመሆኑ አንዲሁም የሰበር ቅሬታው የተፈጸመውን የህግ ስህተት የሚያሳይ ባለመሆኑ ውድቅ ተደርጎ ውሳኔው አንዲፀና በማለት ተከራክረዋል አመልካችም የመልስ መልስ አቅርበዋል በሌላ በኩል በሰመቁ የተያዘው ጉዳይ የወጪና ኪሳራን የተመለከተ ነው ተጠሪ በአርባ ምንጭ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የወጪ ዝርዝር አቅርበው ፍርድ ቤቱ ዝርዝሩን መርምሮ ውሳኔ ባገኘው አጠቃላይ ብር ላይ የጠበቃ አበል ብር የዳኝነት ብር የምስክር አበል ብር የቴምብር ብር በድምሩ ብር አስራ ዘጠኝ ሽህ አራት መቶ ፃያ ሁለት የአሁን አመልካች ለተጠሪ እንዲከፍሉ ወስኗል ይግባኙ የቀረበለት የጋሞ አካባቢ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጠበቃ አበል አሻሽሎ ብር ሊሆን ይገባል በማለት ሌላውን ዝርዝር ተቀብሎ በአጠቃላይ ብር አስራ አምስት ሽህ ሶስት መቶ ሁለት ወጪ እንዲተካ ወስኗል የክልሉ ሰበር ችሎትም ይህን ውሳኔ ተቀብሉሎታል በዚህ ውሳኔ ላይ አመልካች ነዛሴ ዓም ለዚህ ፍርድ ቤት ባቀረቡት ቅሬታ የሥር ፍርድ ቤቶች የመቀጮውን ብር አካተው የጠበቃ አበል እንዲታሰብበት ማድረጋቸው ስህተት ስለሆነ የጠበቃ አበል መታሰብ ያለበት ከዋናው ዕዳ ብር ላይ ብቻ መሆን አለበት ተብሉ እንዲታረም ጠይቀዋል ተጠሪ ውሳኔው እንዲፀና በመከራከር መልስ ሰጥተዋል ጉዳዩ ለምርመራ የተቀጠረው በዚህ ሁኔታ ሲሆን በበኩላችን ቅሬታ በቀረበባቸው ውሳኔዎች የተፈፀመ የህግ ስህተት መኖር አለመኖሩን መርምረናል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ እንደመረመርነው የዕፅዳ ማስተላለፍ ውል መደረጉና ስምምነት ከተደረገበት ገንዘብ ውስጥ አመልካች ብር አራት ሺህ ብቻ ከፍለው ቀሪውን ብር መቶ ሃምሳ ስድስት ሺህ ያልከፈሉ መሆኑ ግራ ቀኙን አላከራከረም አመልካች በስር ፍርድ ቤት ለክሱ በሰጡት መልስ ዕዳው በአንድ ጊዜ የሚከፈል ሳይሆን በ ሳምንታት የሚከፈል መሆኑንና በየሳምንቱ ብር ሁለት ሺህ እየከፈልኩ ዕዳውን እንዲያጠናቅቁ እንዲደረግ ተከራክረው የነበረ ቢሆንም የስር ፍርድ ቤት ማስረጃውን ተመልክቶ ዕዳውን በአንድ ጊዜ እንዲከፍሉ ሲወስን የበኩላቸውን ይግባኝ ለበላይ ፍርድ ቤቶች አላቀረቡም ለይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ቅሬታ ያቀረቡት የአሁን ተጠሪ ሲሆኑ ቅሬታቸውም በውል የተመለከተው የመቀጮ ገንዘብ አንዲከፈል አለመወሰኑን የተመለከተ ነበር ስለሆነም የአሁን አመልካች ገና ወደፊት ሰማንያ ሳምንት የክፍያ ጊዜ ያለው ዕዳ ነው በማለት በዚህ ፍርድ ቤት ያቀረቡትን ክርክር የምንቀበለው አይሆንም ይልቁንም የዚህን ፍርድ ቤት ውሳኔ የሚጠይቀው ቀዳሚ ጭብጥ እንደውሉ አንዲፈፀም እንዲሁም የመቀጮ ገንዘብ እንዲከፈል የተሰጠው ውሳኔ ህጉን የተከተለ መሆን አለመሆኑ ነው ተጠሪ በሥር ፍርድ ቤት ባቀረቡት የዳኝነት ጥያቄ ያልተከፈላቸው ቀሪ ብር መቶ ፃምሳ ስድስት ሺህ ከህጋዊ ወለድ ጋር አንዲሁም በውሉ ከተመለከተው ብር ፃምሳ ሺህ መቀጮ እንዲከፈላቸው ጠይቀዋል የሥር ፍርድ ቤቶች የተለያየ ውሳኔ የሰጡ ሲሆን ጉዳዩን በመጨረሻ የተመለከተው የክልሉ ሰበር ችሎት አመልካች ዋናውን ገንዘብ ብር እና በውላቸው የተስማመበትን ብር መቀጮ ለተጠሪ ሊከፍሉ ይገባል ነገር ግን መቀጮ እንዲከፍሉ የተወሰነ በመሆኑ ወለድ ሊከፍሉ አይገባም ብሏል የገደብ የመቀጫ ስምምነት በተደረገ ጊዜ ባለገንዘቡ ተቃራኒ ስምምነት ከሌለ በቀር ውሉ እንዲፈፀም አንዲሁም የመቀጮ ገንዘብ እንዲከፈል ለመጠየቅ የሚችል ስለመሆኑ በፍብህቁ ሥር የተደነገገ ሲሆን በዚህ ረገድ ባለገንዘቡ ያለው መብት ግን የተገደበ መሆኑን ከፍብህቁ መገንዘብ ይቻላል በፍብህቁ እንደተመለከተው ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ኪሳራው የተወሰነው ለሥራው አፈፃፀም መዘግየት ብቻ ወይም ለተጨማሪ ግዴታዎች አለመፈፀም ካልሆነ በቀር ባለገንዘቡ ውሉ እንዲፈፀምና ገደቡን መቀጮውንም እንዲቀበል ሁለቱንም በአንድ ጊዜ ለመጠየቅ አይችልም የድንጋጌው የእንግሊዝኛ ቅጅም ጠጺሃ በ። መኪናውን ከሣሽ ከገዛ በኋላ ወጪ አጥቷል ወይንስ አላወጣም የሚሉ ጭብጦችን በመያዝ የግራ ቀኙን ምስክሮች ሰምቷል አጠቃላይ ክርክሩን ከተመለከተ በኋላም በግራ ቀኙ መሐከል የመኪና ሽያጭ ውል መኖሩ አለማከራከሩን በሽያጭ ውሉ ላይ ጉድለት አለ ወይንስ የለም የሚለው በቅድሚያ መለየት የሚገባ መሆኑን አና የተሰጠው መኪና ሻንሲ አና ቁጥር የተመታ በመሆኑ መሸጥ መለወጥ የማይቻል መሆኑ በመንገድ ትራንስፖርት ፅቤትም ከኮድ ወደ ኮድ መለወጥ አንደማይቻል መከልከሉን በመያዝ የተሰሙ ምስክሮችን ቃል ሲመረመርም መኪናው ከመሸጡ በፊት በባለሙያመካኒክ የተመረመረ ቢሆንም መካኒክ ሲመረምር ሻንሲው የተመታ መሆኑን መለየት ይችላል ብለው ተከሣሽም ያነሱት ክርክር የሌለ እና የተረጋገጠም ባለመሆኑ ከቀረበው የማስረጃ ክብደት አንፃር የሠቁ ኮድ አአ የሻንሲ ቁጥር ሃአ የሞተር ቁጥር ነ በማስመሰል የተመታው ከሽያጭ ውሉ በፊት በተከሣሽ እጅ ላይ እያለ የነበረ ጉድለት መሆኑን ፍቤቱ ግንዛቤ መውሰዱን ገልዷል ይህ ጉድለት ውል እንዲፈርስ ምክንያት ይሆናል ወይ የሚለውን በተመለከተ በፍብሕቁ ሻጭ ዋቢ ሊሆንባቸው የሚገባቸው ጉድለቶች የሸጠው ነገር ለደንበኛው አገልግሎት ወይም ለንግድ ሥራ ጥራትነት የሌለው ዕቃ ከሆኑ በማለት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሚደነግግ በመሆኑ በተያዘው ጉዳይ ሻጭ ዋቢ ሊሆንለት የሚችል ጉድለት የተገኘበት ስለሆነ ሊፈርስ የሚገባው ውል ነው በሚል ወስኗል ወጪን በተመለከተ ግን ከሣሽ ወጪዎችን ያስረዱልኛል ብለው ያቀረቧቸውን ደረሰኞች እያንዳንዳቸውን በመመልከት የቀረበውን ወጪ ያስረዱም በማለት ውድቅ አድርጐ መኪናው የተሸጠበትን ገንዘብ ብር ዐዐዐዐዐዐ አንድ መቶ አስር ሺ ብር እና ብር ዐዐ አምስት ሺ ሰባት መቶ ዘጠና ስምንት ብር በመጨመር ተከሣሽ ለከሣሽ አንዲመልስ ከሣሽ ደግሞ የሀቁ አአ የሆነውን ተሽከርካሪ አሁን ባለበት ሁኔታ ለተከሣሽ እንዲያስረክቡ መሆኑን በመቁ ግንቦት ቀን ዐዐ ዓም የሰጠው የውሣኔ ግልባጭ ያመለክታል አመልካች ይግባኝ ቢሉም ይግባኝ ቅሬታውን የመረመረው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግራ ቀኙን አስቀርቦ እና አከራክሮ በመቁ ህዳር ቀን ዐዐ በዋለው ችሎት የስር ፍርድ ቤት ውሣኔ ጉድለት የለበትም በሚል ሙሉ በሙሉ አጽንቶታል አመልካች በስር ፍርድ ቤት ውሣኔ ላይ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት በመሆኑ በሰበር ታይቶ እንዲታረምላቸው የካቲት ቀን ዐዐ ዓም የተፃፈ የሰበር አቤቱታ አቅርበዋል ይዘቱም በአጭሩ ክርክር ያስነሳውን ተሽከርካሪ እዳ እና እገዳ የሌለበት መሆኑ ተረጋግጦ ከሣሽ በስማቸው አዛውረዋልየባለቤትነት ደብተርም ተጠሪ በስማቸው አውጥተዋል ተጠሪ መኪናውን ሲገዙ በተለመደው አሰራር የራሳቸውን ባለሙያ አምጥተው አስመርምረዋል ውሉ ከተደረገ ከ ወር በኋላ በዐዐ ዓም የመኪናውን አገልግሎት ከኮድ ወደ ኮድ ለመቀየር ጥያቄ በሚያቀርቡበት ጊዜ የመኪናው ሞተርና ሻንሲ የተመታ መሆኑን የተገለፀላቸው ቢሆንም አመልካች ይህ ጉድለት ስለመኖሩና መቼ እንደተከሰተም የሚያውቁት ነገር የለም ከቅን ልቦና ውጭ ያቀረቡት ጥያቄ ውሉ በመሳሳት የተደረገ ነው ሊባል አይችልም ሽያጩ የተደረገው በታህሳስ ዐ ቀን ዐዐ ዓም ሲሆን ተጠሪ መኪናውን እስካሁን ድረስ እየተጠቀሙበት የሚገኙ ከመሆኑ አኳያ የመኪና ሽያጭ ውሉ በመፍረስ ወደነበርንበት እንዲመለሱ ቢደረግ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አፈፃፀሙ አዳጋች ነው በሚል የስር ፍርድ ቤቶች ውሣኔ ላይ የተፈፀመው ስህተት እንዲታረምላቸው ጠይቀዋል አቤቱታውን የመረመረው የሰበር አጣሪ ችሎት ሊጣራ የሚገባውን ጭብጥ በመያዝ መዝገቡ ለችሎቱ እንዲቀርብ በማድረጉ ሊቀርብ ችሏል አቤቱታው ከማስቀረቢያ ነጥቡ ጋር ለተጠሪ ደርሶ መልስ እንዲያቀርቡ ከመጥሪያ ጋር የተላከላቸው በመሆኑ ጥር ቀን ዐ ዓም የተፃፈ መልስ አቅርበዋል ይዘቱም ከማስቀረቢያ ነጥቡ አኳያ ካቀረቡት በጥቂቱ ውል እንዲፈርስ ክስ ያቀረብኩት ውሉ ከተደረገ እና መኪናውን ከተረከብኩ ከ ቀን በኋላ ነው በመሆኑም መኪና ከተረከብኩ ከ ዓመት በኋላ ውል እንዲፈርስ ክስ አላቀረብኩም መኪናውን በትራንስፖርት ቅርንጫፍ ባለሙያ አስመርምረው አላስረከቡኝም በመኪናው ላይ ጉድለት ያለበት መሆኑ የታወቀው ተጠሪ መኪናውን ከቤት አገልግሎት ወደ ንግድ ተሽከርካሪነት ለመለወጥ አስቤ መኪናው በትራንስፖርት ቅርንጫፍ ጽቤት ባለሙያ በተመረመረበት ጊዜ ነው በዚህ መሠረት የስር ፍርድ ቤቶች ውሣኔ አግባብ በመሆኑ የተፈፀመበት የህግ ስህተት የለውም ተብሎ አቤቱታው ውድቅ እንዲሆን ጠይቋል አመልካችም የመልስ መልስ አቅርበዋል የጉዳዩ አመጣጥ ከላይ የተመለከተውን የሚመስል ሲሆን እኛም አጠቃላይ የቀረበውን ጉዳይ አግባብነት ካለው የህግ ድንጋጌ ጋር በማገናዘብ መርምረናል እንደመረመርነውም ከላይ በስር የቀረበው ክስ ላይ ታህሳስ ዐ ቀን ዐዐ ዓም ክርክር ያስነሳውን ተሽከርካሪ ሽያጭ ውል ግራ ቀኙ በማድረግ የሽያጭ ገንዘቡንም ብር ዐዐዐዐዐዐ ሻጭ መቀበላቸውን ገዢም መኪናውን መረከባቸውን የተካደ ባለመሆኑ አለማከራከሩን ተመልክተናል ሆኖም መኪናው በተገቢው ርክክብ ከተደረገ በኋላ ስመ ሀብትም ከዞረ በኋላ የመኪናውን አገልግሎት ለመቀየር ለትራንስፖርት ባለሥልጣን ጥያቄው ቀርቦ ሲፈተሽ ግን የሻንሲው ቁጥር የተመታ መሆኑ በመረጋገጡ በቀይ ሰሌዳ ላይ የተመዘገበ በመሆኑ አገልግሎቱን ማግኘት እንደማይቻል ለተጠሪ የተገለፀላቸው በመሆኑ ውሉ ጉድለት ባለበት ንብረት ላይ የተፈፀመ በመሆኑ ውሉ እንዲፈርስ ጠይቀዋል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አሁን እያከራከረ ያለው ጭብጥ መኪናው ከሻጭ ወደ ገዢ ከመተላለፉ በፊት በመካኒክ ተፈትሾ የተላለፈ በመሆነ ኃላፊነት ለገዢ ተላልፏል ሊባል ይገባል ወይንስ አይገባም የሚለው ነጥብ ላይ ይሆናል በስር ፍርድ ቤት መኪናው በአግባቡ ተጠሪ ራሣቸው ባመጡት ሜካኒክ ተፈትሾ እና ተነድቶ ጉድለት የሌለበት መሆኑ ተረጋግጦ ገዢ የተረከቡ መሆኑ በፍሬ ነገር ደረጃ ተረጋግጧል ነገር ግን ይህ የመካኒክ ፍተሻ የሻንሲ እና የሞተር ቁጥር ኦርጅናልነት ጨምሮ የሚያረጋግጥ ነው ወይንስ አይደለም የሚለው በአመልካች በስር ክርክር የተደረገበት ባይሆንም በይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ግን ተነስቶ የነበረ በመሆኑ በዚህ መልኩ አመልካች መኪናው ተፈትሾ ለገዢ መተላለፉን ስለማስረዳታቸው የተቀመጠ ነገር የለም በኑሮ ልማድ አውቀት እንደሚታወቀው መካኒክ የሚፈትሸው ጉድለት ከመኪናው ጤነኝነት ማለትም አገልግሎት መስጠት እና አለመስጠት ጋር በተያያዘ እንጂ የሻንሲን እና የሞተርን ቁጥር ኦርጅናልነትን የሚጨምር አይደለም ይህ ማለት አመልካች መኪናውን ሲሰጡ ይህ ጉድለት መኖሩን ያውቁ ነበር ለማለትም አስቸጋሪ ነው ምክንያቱም አመልካችም በአቤቱታቸው እንደገለፁት መኪናው የተላለፈላቸው ከሌላ ሰው መሆኑን የገለፁ በመሆኑ ይህን ምርመራ የመካኒክ ምርመራ የሚያካትት ቢሆን ኑሮ ቀድመው የሚያውቁበት አድል ይኖራቸው ነበር ሆኖም አመልካች ጉድለቱ መኖሩን በፍፁም አላውቅም በማለት ይከራከሩ እንጂ ጉድለቱ የለም አላሉም እያነሱ ያሉት ርክክብ ከተፈፀመ በኋላ ከእጄ ወጥቶ በተጠሪ እጅ ገብቷል ስለሆነም ኃላፊነት ተላልፏል የሚል ሆኖ ተገኝቷል ኃላፊነት ተላልፏል ጉድለቱ አይመለከተኝም ለማለት ደግሞ ቀድሞ ጉድለቱ ያለመኖሩን በእርግጠኝነት ማረጋገጥ የሚገባው ኃላፊነቱ ከተላለፈ በኋላ ነው ጉድለቱ የደረሰው የሚለው ወገን መሆን ይኖርበታል እንዲህ ከሆነ ጉድለቱ መኖሩ የተረጋገጠ በመሆኑ ይህ ጉድለት ደግሞ ገዢን አንድ የንብረት ባለቤት ሊያገኝ የሚችለውን መብት የሚቀንስ ወይም ጨርሶ የሚያሳጣ ከሆነ ውሉ የተፈፀመው በመሳሳት በመሆኑ የማይፈርስበት ምክንያት አይኖርም ይህን ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ተሽከርካሪ ተጠሪ የአገልግሎት ዘርፍ በመቀየር ሥራ ላይ ለማዋል የማይችሉ እና በትራንስፖርት ባለሥልጣን አባባል ቀይ ሰሌዳ ላይ የተመዘገበ በመሆኑ የገዙትን ንብረት ስም ብቻ ማዛወራቸው ንብረቱን ህግ በሚፈቅደው መልክ በመቀየር ሊጠቀሙ የማያስችላቸው አዳጋች ነገር ተፈጥሮባቸዋል ስለሆነም የገዙትን ንብረት በፈለጉት መልኩ መጠቀም የማያስችል ሁኔታ መፈጠር ደግሞ ውሉ ከመደረጉ በፊት ችግሩጉድለቱ እንዳለ ቢያውቁ ኩሮ ውሉን አይፈጽሙም ነበር የሚያሰኝ በመሆኑ ጉድለት ያለበት ውሉ ነው ተብሎ በስር ፍርድ ቤት እንዲፈርስ መወሰኑ እና በፍብሕቁ መሠረት ተዋዋይ ወገኖች ወደ ነበሩበት እንዲመለሱ በሚል የተሰጠው ውሣኔ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ነው ሊያስብል የሚችል ምክንያት አልተገኘም በመሆኑም የስር ፍርድ ቤትን ውሣኔ በማጽናት አቤቱታውን አልተቀበልነውም ስለሆነም ተከታዩ ውሣኔ ተሰጥቷል ው ሣ ኔ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሉት በመቁ ህዳር ቀን ዐዐ ዓም በዋለው ችሎት የስር ፍርድ ቤትን ውሣኔ በማጽናት የሰጠው ፍርድ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ሆኖ ባለመገኘቱ በፍብሕሥሥቁ መሠረት ፀንቷል በዚህ ፍርድ ቤት ግራ ቀኙ ያወጡት ወጪ ካለ የየራሣቸውን ይቻሉ የውሣኔው ትክክል ግልባጭ ለስር ፍርድ ቤት ይድረስ መዝገቡ ውሣኔ ስላገኘ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ሠአ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ቀን ዳኞች ተኽሊት ይመሰል ተፈሪ ገብሩ ዶር ቀነዓ ቂጣታ ተሾመ ሽፈራዉ አብዬ ካሳሁን አመልካች ወሮ አሻ ፋራህ ጠበቃ ጣሂር ሼህ አብዱላህ ተጠሪዎች አቶ አብዱራህማን ጣሂር ዮሱፍ አሊ ዩሱፍ ሀሰን አሊ ዩሱፍ ሳላህ ኢብራሂም አልቀረቡም ሮዉዳ አሊ ዩሱፍ ረሺድ አሊ ዩሱፍ ኢስማሃን አሊ ዩሱፍ በድሪያ ኢብራሂም ግራድ ሀሰን ኢብራሂም ኢጋል መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ወመ መወቓይወዕጅው ፍርድ ክርክሩ የተጀመረዉ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል መንግስት በፋፈን ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን ተጠሪዎች ከሳሽ አመልካች እና በዚህ ችሎት የክርክሩ ተካፋይ ያልሆነዉ አቶ ሰኢድ አሊ በቅደም ተከተል ኛ እና ኛ ተከሳሾች በመሆን ተከራክረዋል የተጠሪዎች ክስ ይዘትም በአጭሩ እናቶቻችን ከአያታችን የወረሱት እና በዉርስ ሊተላለፍልን የሚገባ ቦታ ኛ ተከሳሽ በህገ ወጥ መንገድ ለኛ ተከሳሽ በሽያጭ በማስተላለፉ ዉሉ ፈርሶ ቦታዉ ይመለስልን የሚል ነዉ ተከሳሾች ለፍርድ ቤቱ ቀርበዉ በሰጡት መልስ ቦታዉ ለኛ ተከሳሽ በተለይ ከእናቱ የተሰጠዉ መሆኑን ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ከሳሾች ከቦታዉ የዉርስ ድርሻ የሌላቸዉ መሆኑን ቦታዉን ኛ ተከሳሽ ቆርቆሮ ቤት ሰርቶበት በህጋዊ መንገድ ለኛ ተከሳሽ የሸጠ በመሆኑ ዉሉ ሊፈርስ አይገባም በማለት ተከራክረዋል ጉዳዩ በመጀመሪያ የቀረበለት የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ከግራ ቀኝ በዚህ መልኩ የቀረበዉን ክርክር እና ማስረጃ ከሰማ በኋላ ለክርክሩ ምክንያት የሆነዉ እና ቆርቆሮ የተሰራበት ቦታ ከስር ኛ ተከሳሽ ጋር ባደረጉት የሸያጭ ዉል መሠረት በአመልካች እጅ እንደሚገኝ በማስረጃ መረጋገጡን ገልፆ ቤትና ቦታዉ የአመልካች ነዉ በማለት የተጠሪዎችን ክስ ዉድቅ በማድረግ ወስኗል ተጠሪዎች በዚህ ዉሳኔ ባለመስማማት ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ያቀረቡ ሲሆን ይግባኝ ሰሚዉ ፍርድ ቤት በበኩሉ ለክስ ምክንያት የሆነዉ ዉል በሚመለከተዉ አካል ዘንድ የተመዘገበ አና የተፈረመም አለመሆኑን ተጠሪዎች ወራሾች መሆናቸዉን አና ለስር ኛ ተከሳሽ ለብቻዉ የተሰጠ መሆኑን የሚያሳይ ማስረጃ ባለመቅረቡ ንብረቱ ለተጠሪዎች ሊመለስላቸዉ ይገባል አመልካች በቦታዉ ላይ ቤት ለሰራችዉ ቤት ግምቱን ተጠሪዎች ለአመልካች እንዲከፍሉ አመልካች በዉሉ ምክንያት ያጣችዉ መብት ካለ በስር ኛ ተከሳሽ ላይ ክስ የማቅረብ መብት አላት በማለት የስር ፍርድ ቤትን ዉሳኔ በመሻር ወስኗል አመልካች ይህን ዉሳኔ ባለመቀበል ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር አቤቱታ ያቀረበች ሲሆን ሰበር ሰሚዉ ችሎት የስር ኛ ተከሳሽ በሽያጭ ዉሉ መሠረት የወሰደዉን ገንዘብ ለአመልካች ሊመለስ ይገባል በሚል ይግባኝ ሰሚዉ ችሎት በዚህ ረገድ የሰጠዉን የዉሳኔ ክፍል ብቻ በመሻር ቀሪዉን በማጽናት ወስኗል አመልካች በቀን ዓ ም ተዘጋጅቶ በጠበቃዋ አማካይነት በቀረበ አምስት ገጽ የሰበር አቤቱታ ተጠሪዎች ወራሾች መሆናቸዉ ባልተረጋገጠበት ሁኔታ እንዲሁም በግራ ቀኝ መካከል የተደረገዉ ዉል ተገቢዉን ፎርም ያሟላ መሆን አለመሆኑን በተመለከተ የቀረበዉ ክርክር በሌለበት ሁኔታ የስር የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ እና ሰበር ሰሚ ችሎቶች በፋፈን ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተሰጥቶ የነበረዉን ዉሳኔ በመሻር የሰጡት ዉሳኔ መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነዉ በማለት ተከራክራለች አቤቱታዉ ተመርምሮ ያስቀርባል በመባሉም ተጠሪዎች በተደረገላቸዉ ጥሪ መሠረት ቀርበዉ ግራ ቀኝ ክርክራቸዉን በጽሑፍ ተለዋዉጠዋል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የጉዳዩ አመጣጥ በአጭሩ ከላይ የተመለከተዉ ሲሆን ይህ ችሎትም ለአቤቱታዉ ምክንያት የሆነዉን ዉሳኔ ከግራ ቀኝ ክርክር እና ለጉዳዩ አግባብነት ካላቸዉ ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ መዝገቡን እንደሚከተለዉ መርምሮታል ከክርክሩ ሄደት መገንዘብ የተቻለዉ ለክርክሩ ምክንያት የሆነዉ ቤት እና ቦታ በአመልካች እጅ ሊገባ የቻለዉ ከስር ኛ ተከሳሽ ጋር ባደረጉት የሽያጭ ዉል መሠረት ስለመሆነ ግራ ቀኝን ያከራከረ ጉዳይ አይደለም ተጠሪዎች የሚከራከሩት ቤትና ቦታዉ ከአያታቸዉ በዉርስ ሊተላለፍላቸዉ የሚገባ መሆኑን ሲሆን አመልካች እና የስር ኛ ተከሳሽ በበኩላቸዉ ቤትና ቦታዉ ለስር ኛ ተከሳሽ ሸያጭ በግል የተሰጠዉ እንጂ የዉርስ ሀብት አለመሆኑን ገልጸዉ የተከራከሩ መሆኑን መዝገቡ ያስረዳል ይሁንና ቤትና ቦታዉ ቀደም ሲል የተጠሪዎች አያት የነበረ ሆኖ ለተጠሪዎች በዉርስ የተላለፈላቸዉ እንጂ ለስር ኛ ተከሳሽ በግል የተሰጠዉ ያለመሆነን ማስረጃን መዝኖ ፍሬ ነገርን የማጣራት ስልጣን በተሰጣቸዉ በስር ፍርድ ቤቶች ተረጋግጧል በፍሬ ነገር ደረጃ የተረጋገጠዉ ይህ ከሆነ በአመልካች እና በስር ኛ ተከሳሽ መካከል የተደረገዉ እና ለክርክሩ መነሻ የሆነዉ ዉል ህጋዊ ዉጤት የሚያስከትል መሆን ያለመሆኑን ስለ ጉዳዩ ከሚደነግገዉ የፍትሐብሔር ህጉ ድንጋጌ ጋር አገናዝቦ ማየቱ ተገቢ ሆኖ ተገኝቷል እንደሚታወቀዉ የማይንቀሳቀስ ንብረት ካለዉ ልዩ ባህርይ አንፃር ንብረቶቹን ከአንድ ወደ ሌላ ሰዉ ለማስተላለፍ የሚደረጉ አሠራሮች እና ስርዓቶች ጥብቅ መሆን አንዳለባቸዉ ይታወቃል የማይንቀሳቀስ ንብረትን ከአንዱ ወደ ሌላ ሰዉ ማስተላለፍ ስለሚቻልበት ሁኔታ በተመለከተ በፍትሐብሔር ህጋችን የተለያዩ አንቀፆች የተደነገጉ ድንጋጌዎችም ይህኑን የሚያሳዩ ናቸዉ ከእነዚህም ድንጋጌዎች ዉስጥ አንዱ በህጉ አንቀጽ ስር የተመለከተዉ ድንጋጌ ነዉ በዚህ ድንጋጌ መሠረት የማይንቀሳቀስ ንብረትን በሸያጭ ለሌላ ሰዉ ለማስተላለፍ የሚደረግ ዉል በሦስተኛ ወገን ላይ ህጋዊ ዉጤት ያስከትል ዘንድ ንብረቱ በተመዘገበበት መዝገብ ላይ መመዝገብ አለበት የተያዘዉን ጉዳይ በተመለከተም ተጠሪዎች ከቤቱ ላይ መብት ያላቸዉ መሆኑ አስከተረጋገጠ ድረስ አመልካች ከስር ኛ ተከሳሽ ጋር ያደረገችዉ ዉል ህጋዊ ዉጤት ያስከትል ዘንድ የሽያጭ ዉሉ በህግ አግባብ የተመዘገበ መሆኑን የማስረዳት ግዴታ አለባት ሆኖም ለክርክሩ ምክንያት የሆነዉ ዉል በሚመለከተዉ አካል ዘንድ ያልተመዘገበ መሆኑ በስር ፍርድ ቤት ተረጋግጧል ስለሆነም ለክርክሩ ምክንያት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሆነዉ ዉል የሚጸናበት የህግ ምክንያት የሌለ በመሆኑ ዉሉ ሊፈርስ ይገባል በማለት የስር የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ እና ሰበር ሰሚ ችሉቶች የደረሱበት ድምዳሜ የሚነቀፍበት ምክንያት የለም ሽያጩ ሊፈርስ ይገባል የሚባል ከሆነ ደግሞ የስር ኛ ተከሳሽ ሻጭ ሰዒድ አሊ ዩሱፍ በዉሉ ምክንያት የተቀበለዉን ገንዘብ የመመለስ ግዴታ ያለበት ሲሆን ይህን እንዲያደርግ ሌላ ክስ ማቅረብ ሳያስፈልግ በዚሁ መዝገብ ላይ መወሰን የሚቻል በመሆኑ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዚህ ረገድ የሰጠዉን የዉሳኔ ክፍል በመሻር የደረሰበት ድምዳሜም በአግባቡ ሆኖ ተገኝቷል በአጠቃላይ ለክርክሩ ምክንያት የሆነዉ ቤትና ቦታ የተጠሪዎች የዉርስ ድርሻ ያለበት መሆኑ እስከተረጋገጠ እና አመልካች ቤትና ቦታዉን ለመግዛት ያደረጉት ዉልም በህግ አግባብ በሚመለከተዉ አካል ዘንድ ያልተመዘገበ በመሆኑ ዉሉ ሊፈርስ ይገባል በማለት የስር ኛ ተከሳሽ የሽያጩን ገንዘብ ለአመልካች እንዲመልስ በሚል የተሰጠ ዉሳኔ በአግባቡ ነዉ ከሚባል በስተቀር በዚህ ችሎት ሊታረም የሚችል መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ ስላልተገኘ ተከታዩ ተወስኗል ዉሳኔ የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሉት በመቁ በቀን ዓም በዋለዉ ችሎት የሰጠዉ ዉሳኔ በፍሥሥርዓት ህጉ አንቀጽ መሠረት ጸንቷል በዚህ ችሎት የተደረገዉ ክርክር ያስከተለዉን ወጪ እና ኪሳራ ግራ ቀኝ የየራሳቸዉን ይቻሉ አመልካች ቦታዉን ከተረከቡ በኋላ ላካሄዱት ተጨማሪ ግንባታ ያወጡትን ወጪ በተመለከተ ወጪዉ እንዲመለስላቸዉ ሊያቀርቡ የሚችሉትን ክስ ይህ ዉሳኔ አይከለክልም መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት መይ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ቀን ዓም ዳኞች ዳጌ መላኩ ተኸሊት ይመስል ተፈሪ ገብሩ ዶር ቀነዓ ቂጣታ አብዬ ካሳሁን አመልካች ብርሃን ኢንተርናሽናል ባንክ አክሲዮን ማሕበር ነገረ ፈጅ ቤተልሔም ማትዎስ ቀረቡ ተጠሪዎች ኛ አቶ እዮብ ሙሉጌታ ቱሳና ኛ ወሮ መድሃኒት ሙሉንታ ቱሳና የቀረበ የለም መዝገቡ መርምረን ተከታዩን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ ዋስትናን መሰረት ያደረገ ክርክር ሲሆን የጀመረው በኦሮሚያ ክልል ምፅራብ አርሲ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው በስር አመልካች ከሳሽ ተጠሪዎች እና በዚህ መዝገብ የክርክሩ ተካፋይ ያልሆነውን አቶ ፈቃዱ ሙሉጌታ ተከሳሾች በመሆን ተከራክረዋል አመልካች በስር ፍርድ ቤት ባቀረበው ክስ የስር ኛ ተከሳሽ የነበረው አቶ ፈቃዱ ሙሉጌታ የአመልካች ሠራተኛ በመሆን በወላይታ ቅርንጫፍ ተመድቦ አየሰራ በነበረበት ጊዜ ከባንኩ አሠራር ውጭ የአቶ ጀመሬ መጃ ሎጊሶን ከሆነው ሂሣብ ቁጥር የባለ ሂሣቡን ስምና ፊርማ በማስመሰል ፈርሞ ወደ አመልካች ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ባንክ ሻሸመኔ ቅርንጫፍ በማዛወር ብር በህገወጥ መንገድ በመውሰዱ ገንዘቡን አንዲከፍል የአሁነ ተጠሪዎች ዋስ በመሆናቸው ገንዘቡን በአንድነትና በነጠላ እንዲከፍሉ ይወሰን ዘንድ ዳኝነት ጠይቋል የስር ተከሳሾች ባቀረቡት የመከላከያ መልስ በስር ኛ ተከሳሽ ስምና ፊርማ የተደረገ የገንዘብ ዝውውር የለም በማለት ተከራክረዋል በዚህ አግባብ ክርክሩ የቀረበለት የስር ፍርድ ቤትም በክሱ የተጠቀሰው ገንዘብ በስር ኛ ተከሳሽ ወጭ ተደርጐ መወሰዱን ተረጋግጦ በወንጀል የተቀጣ መሆኑን የአሁኑ ተጠሪዎችም ዋስ ስለመሆናቸው ያልተካደ መሆኑን በመግለጽ ብር በአንድነትና በነጠላ ይክፈሉ ሲል ፍርድ ሰጥቷል የአሁነ ተጠሪዎች በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኘት ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ይግባኝ ቅሬታ አቅርበው ፍርድ ቤቱም ግራቀኙን ከአከራከረ በኃላ የስር ኛ ተከሳሽ ድርጊቱ የፈፀመው ለደንበኞች አገልግሎት እየሰጠ ሳይሆን ለራሱ የአመልካች ደንበኛ በመሆን እንደሆነ የሻሸመሄፄ ቅርንጫፍም ባለመብት ባለማጣራት የከፈለው በመሆነ ዋሶቹ ተጠያቂነት የለባቸውም በማለት የስር ፍርድ ቤት ውሳኔ ሽሯል አመልካች በውሳኔው ቅር በመሰኘት ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ይግባኝ ቢያቀርብም ተቀባይነት አላገኘም አመልካች ሐምሌ ቀን ዓም ባቀረበው የሰበር አቤቱታ በስር ፍርድ ቤቶች ተፈፀመ ያለውን የህግ ስሕተት በዝርዝር ያቀረበ ሲሆን መሰረታዊ ይዘቱ ሲታይም የአሁኑ ተጠሪዎች በስር ፍቤት ያላነሱት ክርክር ይግባኝ ሰሚ ችሎት ለውሳኔ መነሻ ማድረጉ ተገቢ አለመሆኑን የስር ኛ ተከሳሽ ገንዘቡ የወሰደው ከሥራው ጋር በተያያዘ ሁኔታ መሆኑን በመግለጽ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አና የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የሰጡት ውሳኔና ትዕዛዝ እንዲሻር አመልክቷል ጉዳዩን የመረመረው አጠሪ ችሎትም የአሁን ተጠሪዎች ኃላፊነት የለባቸውም ተብሎ የተወነበት አግባብ ባሉበት ማጣራት ይቻል ዘንድ ጉዳዩ ለዚህ ችሎት ያስቀርባል ተብሏል የአሁኑ ተጠሪዎች ዓም የተፃፈ መልስ አቅርበው የስር ፍቤቶች ውሳኔ እንዲጸና ጠይቋል የመልስ መልስም ቀርቧል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ከሥር የጉዳዩ አመጣጥ አጠር ባለመልኩ ከላይ የተገለጸው ሲሆን እኛም የስር ፍርድ ቤቶች የሰጡት ፍርድና ትዕዛዝ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት መሆን አለመሆኑን አንደሚከተለው መርምረናል እንደመረመረነውም የአሁኑ ተጠሪዎች በስር ኛ ተከሳሽ ለነበሩት አቶ ፈቃዱ ሙሉንታ ዋስ ስለመሆናቸው የገንዘብ መጠኑም እስከ ብር ስለመሆነ ያከራከረ ጉዳይ አይደለም ከስር ፍቤት መዝገብ መረዳት የተቻለው ተጠሪዎች ከባንክ ገንዘብ አልወጣም የሚል ክርክር ሳያቀረቡ ነገር ግን ገንዘቡ ሥርዓቱን ጠብቆ ያልወጣ በመሆኑ ልንጠየቅ አይገባም በማለት ተከራክረዋል በስር ፍርድ ቤት በፍሬ ነገር የተረጋገጠው የስር ኛ ተከሳሽ የአቶ ጀመሬ መጃን ፊርማ ለማስመሰል ብር በህገወጥ መንገድ ማውጣቱን ገንዘቡም ከሻሸመኔ ቅርንጫፍ ወጭ አደረጎ መውሰዱን ነው የስር የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ተጠሪዎች ተጠያቂ ሊሆኑ አይገባም ለማለት እንደምክንያት የጠቀሰው ድርጊቱ የተፈፀመው አገልግሎት እየሰጠ ሳይሆን አንደደንበኛ ቀርቦ ገንዘብ ሲያወጣ ተገቢ ማጣራት አልተደረገም በሚል ነው ከመዝገቡ እንደተረዳነው የስር ኛ ተከሳሽ በአመልካች ባንክ የወላይታ ቅርንጫፍ ሰራተኛ በመሆን ሲሰራ እንደነበር ከዚህ ቅርንጫፍ ባንክ ደንበኛ ገንዘብ በሕገወጥ መንገድ ወጭ አድርጎ ወደ ሻሸመኔ ቅርንጫፍ በማስተላለፍ ወጭ አድርጎ መወሰዱን ነው ከዚህ የምንረዳው የስር ኛ ተከሳሽ ከሚሰራበት ቅርንጫፍ ባንክ ያለው የደንበኛ ሂሣብ ቁጥር በሕገወጥ መንገድ ገንዘብ በመወሰድ ወደ ሌላ ቅርንጫፍ በማስተላለፍ ገንዘቡን ለግል ጥቅሙ ማዋሉን ነው የስር ኛ ተከሳሽ ድርጊት ከሻሸመኔ ቅርንጫፍ ገንዘብ ማውጣት ብቻ ተነጥሎ የሜታይ ሳይሆን የወላይታ ቅርንጫፍ ሰራተኛ በመሆን ከህግ ውጭ ከደንበኛ ሂሣብ ገንዘብ ቀንሶ ማስተላለፍንና ወጪ አድርጎ መወሰዱን አብሮ መታየት ያለበት ጉዳይ ነው የአሁነ ተጠሪዎች የስር ኛ ተከሳሽ ዋሶች መሆናቸው አልተካደም ይህ ከሆነ ደግሞ ተጠሪዎች የስር ኛ ተከሳሽ በሥራው አጋጣሚ ያገኘው የደንበኛ ገንዘብ ከህግ ውጭ ቀንሶ በማስተላለፍና በማውጣት መውሰዱ በተረጋገጠበት ሁኔታ ከኃላፊነት ነፃ የሚያደርጋቸው ሆኖ አልተገኘም የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት እና የፌዴራል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የሰጡት ውሳኔና ትዕዛዝ የስር ኛ ተከሳሽ ድርጊት ህጋዊ ውጤት እና የተጠሪዎች የግዴታ አድማስ መሰረት ያላደረገ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ነው የአሁኑ ተጠሪዎች የስር ኛ ተከሳሽ የወሰደው ብር በአንድነትና በነጠላ ሊከፍሉ ይገባል በመሆኑም የስር ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቶች ተጠሪዎች ከስር ኛ ተከሳሽ ጋር በአንድነትና በነጠላ ገንዘቡን የመክፈል ግዴታ እያለባቸው ከኃላፊነት ነፃ ማድረጋቸው የፍሕቁ እና ድንጋጌዎች መሰረታዊ ይዘትና መንፈስ ያላገናዘበ ነው ብለናል በዚሕም ተከታዩን ወስነናል ውሳኔ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የደቡብ ችሎት በመቁ ዓም የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ በ ዓም የሰጠው ውሳኔ በመሻር የተሰጠው ፍርድ እና የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሉት በፍብይመቁ በ ዓም የሰጠው ትዕዛዝ ተሽሯል ተጠሪዎች ከስር ኛ ተከሳሽ አቶ ፈቃዱ ሙሉንታ ጋር በአንድነትና በነጠላ በዋስትና ውሉ የተመለከተውን ብር የመክፈል ግዴታ አለባቸው በማለት ወስነናል የምፅራብ አርሲ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ በ ዓም የሰጠው ፍርድ ጸንቷል ወጭና ኪሳራ ግራቀኙ የየራሳቸው ይቻሉ ብለናል የዚህ ፍቤት ውሳኔ ግልባጭ ለስር ፍቤቶች ይተላለፍ ብለናል መዝገቡ ተዘጋ ወደ መዝገብ ቤት ተመለሰ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት አጐ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞች አልማው ወሌ ሙስጠፋ አህመድ አብርፃ መሰለ ፈይሳ ወርቁ ጳውሎስ ኦርሺሶ አመልካች ቻን ቹን ያን ኃላፊነቱ የተየግማህበር ተጠሪ ወሪት ሞሚና ሁሴን ጠበቃ ፈለቀ ዋጎ ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ የቀረበው አመልካች የስር ፍርድ ቤቶች የሰጡት ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ እንዲታረምልን በማለት ያቀረቡትን የሰበር አቤቱታ አጣርቶ ለመወሰን ነው ክርክሩ በመጀመሪያ የታየው በፌዴራል የመደ ፍርድ ቤት ነው በፌመደ ፍርድ ቤት የአሁን አመልካች ተከሳሽ ተጠሪ ደግሞ ከሳሽ ነበሩ የአሁን ተጠሪ ያቀረቡት የክስ አቤቱታ በአመልካችና ተጠሪ መከካል የመጋዝን ኪራይ መኖሩን በመግለጽ አመልካች የተከራየውን መጋዝን ከውሉ ጊዜ መጠናቀቅ በላ መጋዘኑን ሳይለቅልኝ ማሽኑን በማስቀመጡ መጋዘኑን በወር ብር ፃያ ሺህ ብር ላከራየው እችል የነበረ ሲሆን በዚሁ ስሌት እስኪያስረክበኝ ድረስ ታስቦ እንዲከፍለኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል የአሁን አመልካች ለቀረበበት ክስ መልስ የሰጠ ሲሆን በበኩሉ የብር አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሰላሳ ሰባት ሺህ ሶስት መቶ ዛያ ሁለት ብርየተከሳሽ ከሳሽነት ክስ አቅርበዋል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ጉዳዩን በመጀመሪያ የተመለከተው ፍርድ ቤትም የግራ ቀኙ ክርክር ከሰማና ማስረጃ ከመዘነ በኋላ ተጠሪ ከሰኔ ቀን ዓም አስከ ሚያዚያ ዓም ድረስ አመልካች ማሽኑን እንዳያወጣ የከለከሉ በመሆነ የጠየቁት የዚህ ወቅት ኪራይ ሊከፈል አይገባቸውምሆኖም ከመስከረም ዓም ጀምሮ አመልካች ማውጣት እየቻለ ስላላወጣ ከዚሁ ጊዜ ጀምሮ እስከ የካቲት ቀን ዓም ላለው ጊዜ በወር ብር አስር ሺህ ብርሒሳብ የሶስት ዓመት ከአምስት ወር ብር አራት መቶ አስር ሺህ ብር ሊከፍል ይገባል እንዲሁም ተጠሪ የወጪና ኪሳራ ዝርዝር እንዲያቀርቡ በአመልካች በኩል የተከሳሽ ከሳሽነት ክስ በተመለከተ ተጠሪ የባትሪ ድንጋይ ማምረቻ ማሽኑን ለአመልካች ሊያስረክቡ ይገባል ቀሪዎቹ የአመልካች ጥያቄ ውድቅ በማድረግ የሰጠው ውሳኔ አመልካች በመቃወም ይግባኛቸውን ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ይግባኝ ሰሚ ችሎት ቢያቀርቡም ተቀባይነት ሳያገኝ በፍብስስህቁ መሰረት በትእዛዝ ሰርዞታል የሰበር አቤቱታው የቀረበውም ይህንነ የስር ፍርድ ቤት ውሳኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው አመልካች ሰኔ ቀን ዓም በፃፈው አቤቱታ በስር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ መሰረታዊ የሆነ የሕግ ስሕተት ተፈጽሟል የሚሉባቸውን ምክንያቶችን ዘርዝረው አቅርበዋል የአመልካች የሰበር አቤቱታ ተመርምሮ አመልካች እስከ ሚያዚያ ዓም ድረስ ከመጋዝኑ ፅቃውን ሊያወጣ ያልቻለው በተጠሪ ጥፋት ስለመሆኑ በክርክር ሂደት የስር ፍርድ ቤት በፍሬ ነገር ደረጃ ያረጋገጠው ጉዳይ መሆኑ ከታወቀ የአሁን አመልካች ክስ ከቀረበበትን የኪራይ ገንዘብ የመክፈል ኃላፊነት አለበት ወይስ የለበትም እንዲሁም የአሁን ተጠሪ ከዚሁ መጋዝን ኪራይ ጋር በተያያዘ በአመልካች ላይ የኪራይ ገንዘብ ይከፈለኝ ክስ አቅርበው ብር በመቁ ማስወሰናቸውን እራሳቸው በክሳቸው ላይ ያረጋገጡት ጉዳይ በመሆኑ ከሳሽ በዚህ የሰበር ጉዳይ መነሻ የሆነ ክስ ማስቀረት ይቻል ዘንድ ከኪራይ ገንዘቡ ክስ ጋር በመጋዝን ያለውን ዕቃ አውጥቶ መጋዝኑን እንዲያስረክብኝ ይወሰንልኝ በማለት የተጠቃለለ ክስ በማቅረብ ጉዳቱን የመቀነስ ግዴታውን አልተወጣም በማለት አመልካች በቀረበው ክርክር ላይ ዳኝነት ሳይሰጥበት በዝምታ የመታለፉን አግባብነት ለመመርመር ሲባል ለሰበር ችሎት እንዲቀርብ በመደረጉ ተጠሪ መልስ እንዲሰጡበት በታዘዘው መሰረት ህዳር ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ቀን ዓም የተፃፈ መልስ አቅርበዋል አመልካችም አቤቱታቸውን በማጠናከር የመልስ መልስ በማቅረብ ተከራክረዋል የጉዳዩ አመጣጥ ባጭሩ ከላይ እንደተገለፀው ሲሆን ይህ ችሎትም የግራ ቀኙን ክርክር ለሰበር አቤቱታው መነሻ ከሆነው ውሳኔ እና አግባብነት ካላቸው የሕግ ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ ጉዳዩን ለሰበር ችሎቱ ሲቀርብ ከተያዘው ጭብጥ አንፃር በሚከተለው መልኩ መርምሮታል እንደመረመርነው አመልካች የ ዓመት ከ ወር የኪራይ ገንዘብ ሊከፍል ይገባል ወይስ አይገባም። የሚለው ነጥብ ምላሽ የሚያስፈልገው ሆኖ አግኝቶታል ከክርክሩ ሂደት መገንዘብ የተቻለው በአመልካችና ተጠሪ መካከል የመጋዝን ኪራይ ውል የተደረገው ለተወሰነ ጊዜ ከሐምሌ ቀን ዓም እስከ ሰኔ ቀን ዓም ድረስ ለሶስት ዓመት መሆኑተጠሪ የውሉ ጊዜ ከማብቃቱ በፊት ሰኔ ቀን ዓም ያልተከፈላቸው የኪራይ ገንዘብ እንዲከፈላቸው ክስ መሰርተው አመልካች ብር ሁለት መቶ አርባ ሺህ ብርለተጠሪ እንዲከፍል የተወሰነ መሆነበዚሁ ክስ መጋዝኑን እንዲያስረክባቸው ዳኝነት ያልጠየቁ መሆናቸውይህ ውሳኔ ከተሰጠ በላ ለዚህ ክርክር መነሻ የሆነው ሚያዚያ ቀን ዓም ክስ ማቅረባቸውተጠሪ የኪራይ ገንዘብ ካልተከፈለኝ በሚል ምክንያት አመልካች ተከራይቶ ከነበረው መጋዝን ውስጥ ያለውን ዕቃ እንዳያወጣ የከለከሉ ስለመሆናቸው በስር ፍርድ ቤቶች የተረጋገጡ ጉዳዮች ናቸው ተጠሪ የመጋዝኩኑ የኪራይ ዋጋ ይታሰብልኛል በሚል ብቻ መጠበቅ ሳይኖርባቸው መጋዘነ እንዲለቀቅላቸው ምክንያታዊ በሆነ ጊዜ መጠየቅ ነበረባቸው በፍብህቁ እንደሚደነግገው ተጠሪ የጉዳት ኪሣራ የመቀነስ ግዴታ ነበረባቸው አመልካችም ዕቃዎቹ ከመጋዝኑ እንዲያወጣ በህግ አለመጠየቁ ለደረሰው የጉዳት ኪሣራ አስተዋጾ አላቸው በመሆኑም ለደረሰው የጉዳት ኪሣራ ዛላፊነት የአመልካች ብቻ አለመሆኑን መገንዘብ ይቻላል የጉዳት ኪሣራ አመልካች ብቻ እንዲከፍል መወሰኑ ከፍብህቁ እና እንዲሁም ተበዳዩ የሚካሰው ለጉዳቱ ተመዛዛኝ የሆነ ኪሣራ መሆን ስለሚገባው ለደረሰው ጉዳት ዛላፊነት ያለበት ሰው ታውቆ የተጎዳው ወገን ከደረሰበት ጉዳት ጋራ ተመጣጣኝ የሆነ ካሳ መከፈል ሲለሚገባው ከፍብህቁ እና መሰረት ሲመዘን ህጋዊ ውሳኔ ነው ለማለት የሚቻል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አይደለም ለደረሰው የጉዳት ኪሣራ ምክንያቶቹ ከላይ እንደተገለጸው አመልካችም ተጠሪም በመሆናቸው ለደረሰው የጉዳት ኪሣራ ሁለቱም ዛላፊነቱን መሸከም አለባቸው በመሆኑም በስር ፍቤት በተጣራው የኪራይ ዋጋ በብር አስር ሺህ ብር ታስቦ የስድስት ወር አመልካች ለተጠሪ ሊከፍል ይገባል የስር ፍቤት በዚህ መሰረት አመዛዝኖ መወሰን ሲገባው የተጠሪ ጉዳት የመቀነስ ዛላፊነት ግምት ውስጥ ሳይገባ አመልካች ብቻ ሙሉውን የጉዳት ኪሣራ እንዲከፍሉ መወሰኑ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነው በዚህም ምክንያት ተከታዩን ውሳኔ ሰጥተናል ውሳኔ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ መጋቢት ቀን ዓም ተሰጥቶ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም በትአዛዝ ያፀናው ውሳኔ በፍብስስሕቁ መሰረት ተሻሳጓሏል አመልካች ከመስከረም ዓም እስከ የካቲት ቀን ዓም ድረስ ያለውን የ ዓመት ከ ወር የኪራይ ሂሳብ በድምሩ ብር አራት መቶ አስር ሺህ ብር ለተጠሪ አንዲከፍል በማለት የተሰጠ ውሳኔ ክፍል ተሽራል የስድስት ወር ብር ስልሳ ሺህ ብር አመልካች ለተጠሪ እንዲከፍል ተብሎ ተወስኗል የተቀሩት የስር ፍርድ ቤቶች ውሳኔዎች አልተነኩም በቢህ ችሎት ለተደረገው ወጭ እና ኪሳራ የግራ ቀኙን ተከራካሪ ወገኖች መይ የየራሳቸውን ይቻሉ መዘገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ጥር ቀን ዓም ዳኞች ተኽሊት ይመስል ተፈሪ ገብሩ ዶር ቀነአ ቂጣታ ተሾመ ሽፈራው ፀፃይ መንክር አመልካች ጅማ ዩኒቨርሲቲ ነፈጅ ጌታቸው ነጋሽ ቀረቡ ተጠሪ ቢሊሱማ ሚአ የዕፀዋት ዘር አቅራቢ ድርጅት አቶ ቢሊሱት ሚአ ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ የሰበር አቤቱታው የቀረበው የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያሳለፈውን ውሳኔ በመቃወም ሲሆን ክርክሩ የጀመረው የአሁን ተጠሪ በምስራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባቀረበው ክስ ነው በሥር ፍርድ ቤት ኛ ተከሳሽ አቶ ካሳሁን መሰለ ኛ ተከሳሽ ደግሞ የአሁን አመልካች ነበሩ ተጠሪ ያቀረበው ክስ ይዘት የተለያዩ ችግኞችን ለማቅረብ ከኛ ተከሳሽ ጋር ውል የፈፀምኩ ሲሆን ስራውን መስራት ስለበዛብኝ ኛ ተከሳሽ ይህን ሥራ እንዲሰራልኝ በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ አነሱም የችግኝ ዘር መቅረብን አስመልክቶ ጨረታ ላይ አንዲሳተፍ የጨረታ ሰነድ እንዲገዛ እንዲያስገባ ገንዘብ ፈርሞ እንዲወስድ የወሰደውንም ገንዘብ በድርጅቱ ሥም በቢሊሱማ ሚአ በኢትጵያ ንግድ ባንክ አዳአ ቅርንጫፍ ሂሳብ ቁጥር ገቢ እንዲያደርግ ውክልና ስልጣን ሰጥቸዋለሁ ይሁን እንጂ ኛ ተከሳሽ የሰጠሁትን ውክልና ስልጣን በህገወጥነት በመጠቀም ከኛ ተከሳሽ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጅማ ቅርንጫፍ ሂሳብ ቁጥር ከሆነው ብር አራት መቶ ፃያ ሺህ ሰባት መቶ ስድሳ ሶስት በቀን ዓም ወጪ በማድረግ ወደራሴ ሂሳብ ገቢ ማድረግ ሲገባቸው ኛ ተከሳሽ በቀጥታ ወደ ግሉ ሂሳብ ቁጥር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቢሾፍቱ ቅርንጫፍ ሂሳብ ቁጥር አዙሮ ወስዷል ኛ ተከሳሽ ባለው ውክልና ስልጣን መሰረት ይህን ገንዘብ ወደራሴ ሂሳብ እንዲመልስ ብጠይቀውም ፍቃደኛ ስላልሆነ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ገንዘቡን ሊከፍለኝ ይገባል ከኛ ተከሳሽ ጋር ችግኞች ለማቅረብ ስንስማማ የገንዘብ ክፍያ ሊከፈለኝ የሚገባውን ገንዘብ በሂሳብ ቁጥር ገቢ አንዲያደርጉ ተስማምተን እያለ ከውሉ ውጪ ሆነ ብለው እኔን ለመጉዳት ገንዘቤን ወደ ኛ ተከሳሽ ሂሳብ በማስገባታቸው የአንድነት ተጠያቂነት አለባቸው ስለሆነም ተከሳሾች ብር አራት መቶ ፃያ ሺህ ሰባት መቶ ስድሳ ሶስት እንዲከፍሉኝ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው የሥር ኛ ተከሳሽ በሰጡት መልስ ብዙ ወጪ አውጥቼ ከቢሸፍቱ ከተማ እስከ ጅማ ከተማ ተመላልሼ ጨረታውን አሸንፌ ውል ተዋዉዬ የተለያዩ እፅዋቶችን ከተለያየ ቦታ ገዝቼ አቅርቤያለሁ ከሳሽ ገንዘብ ለመክፈልም ሆነ አፅዋቶችን ለማቅረብ ያደረገው አስተዋፅኦ የለም ከጅማ ዩንቨርሲቲ የተከፈለውን የሽያጭ ዋጋ ከከሳሽ ጋር ተስማምተን ለተለያዩ የግዥ ዋጋዎች ክፍያ ውሏል የጽሁፍ ደብዳቤ እኔ አየፈረምኩ የከሳሽ ባለቤት የድርጅቱን ማህተም መታልኝ ኛ ተከሳሽ ገንዘቡን በስሜ ባለው ሂሳብ አንዲያስገባ ጠይቄ ገንዘቡ እንዲገባ ተደርጎ ያለብን አዳ የተከፈለ ሲሆን የቀረው ትርፍ ጥቂት ስለሆነ ከከሳሽ ጋር ሂሳብ እንድንሰራ እና የሚከፈለኝን ክፍያ ከፍሎኝ እንዲያጠናቅቅ ከሳሽን ስጠይቀው ፈቃደኛ አልሆነም ስለሆነም በሂሳብ ባለሙያ ተጣርቶ ያወጣሁት ገንዘብ አንዲቻቻል በማለት ተከራክረዋል የአሁን አመልካች በበኩሉ በሰጠው መልስ ከከሳሽ ጋር በተደረገው ውል መሰረት ለቀረበው ችግኝ በውሉ የተገለፀውን ብር ከፍያለሁ ከሳሽ ስራውን የሚሰራው በተወካዩ ኛ ተከሳሽ በኩል ነው ኛ ተከሳሽ ገንዘቡን መውሰድ አንደሚችል የውክልና ሰነዱ ይገልፃል ይህ በመሆኑ ገንዘቡን ለኛ ተከሳሽ ለመክፈል የህግ መሰረት ያለኝ ሲሆን በተሰጠው ውክልና ላይ የተመሰረተ ነው የሚከፈለው ገንዘብ ወደተወካዩ ሂሳብ አንዳይገባ በሚል በውክልና ሰነዱ አልተገለፀም በፌዴራል ገንዘብ ክፍያ መመሪያ ቁጥር አንቀፅ መሰረት ከብር የሚበልጥ ክፍያ ወደሚከፈለው ሰው ባንክ ሂሳብ ቁጥር በማሳለፍ ክፍያ መፈፀም አንዳለበት ይደነግጋል በዚሁ መሰረት ተወካይ የሂሳብ ቁጥር አቅርበው ገንዘቡ ተላልፏል የከሳሽ ተወካይ ክፍያ እንዲፈፀምለት የጠየቀበት ደብዳቤ በከሳሽ ማህተም ተደግፎ የቀረበ ነው ስለሆነም ከሳሽ እኔን መክሰሱ ተገቢ አይደለም ብሏል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ክርክሩ በዚህ መልኩ የቀረበለት የዞነ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የግራ ቀኙን ክርክር እና ማስረጃ መርምሮ ኛ ተከሳሽ ሂሳብ እንዲሰራ እና እንዲቻቻሉ ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት የለውም ከሳሽ የሰጠው ውክልና ገንዘብ ወደራሱ ሂሳብ ቁጥር እንዲያስገባ የሚል አይደለም ስለሆነም ወደራሱ ሂሳብ ገንዘቡ እንዲገባ ማዘዙ ከውክልና ስልጣኑ በላይ አልፎ ለራሱ ጥቅም እንደሰራበት የሚያረጋግጥ በመሆኑ የወሰደውን ገንዘብ ሊመልስ ይገባል ኛ ተከሳሽን አመልካችን በተመለከተም ገንዘቡን ወደ ኛ ተከሳሽ ሂሳብ ያስተላለፈ መሆኑን ያልካደ በመሆነ ይህን ያደረኩት በተፃዓፈልኝ ደብዳቤ ተመስርቼ ነው ይበል እንጂ ኛ ተከሳሽ በውክልና ስራውን እየሰራ መሆኑን ከውክልናው መረዳት የሚቻል ሲሆን የተሰጠው ውክልና ደግሞ ከችግኝ ሽያጭ የሚገኝ ገንዘብ ወደ ከሳሽ ሂሳብ ቁጥር መግባት አንዳለበት ተገልጾ የሂሳብ ቁጥሩም በውክልናው ላይ የተጠቀሰ በመሆኑ ውክልናው ገንዘብ መግባት ያለበትን የባንክ ሂሳብ ቁጥር ኛ ተከሳሽ መቀየር የሚችል ስለመሆኑም የተገለፀ ነገር ባለመኖሩ ኛ ተከሳሽ ገንዘቡን በራሴ ሂሳብ አስገባው በማለት ያቀረበው ደብዳቤ ላይ የተመታው ማህተም መጀመሪያ ከሳሽ ፕሮፎርማ ሲያስገባ በፕሮፎርማው ላይ ካለው ማህተም የተለየ መሆኑን መረዳት ሲችል ገንዘቡን ወደ ኛ ተከሳሽ ማስገባቱ ስህተት ነው ኃላፊነትም አለበት ብሏል በአጠቃላይ ሁለቱም ተከሳሾች ከችግኝ ሽያጭ የተገኘውን ገንዘብ በከሳሽ ባንክ ሂሳብ ማስገባት እያለባቸው ይህን ባለማድረጋቸው የአንድነትና ነጠላ ግዴታ አለባቸው በማለት ብር ከ የጠበቃ አበል እና ልዩ ልዩ ወጪዎች ጋር እንዲከፍሉ በማለት ወስኗል ይግባኙ የቀረበለት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ክርክሩን ሰምቶ የአሁን አመልካች በተወካዩ ደብዳቤ ሲቀርብለት በደብዳቤው መሰል ትዕዛዝ ለመስጠት ሙሉ ስልጣን አንዳለው ማየትና ለተጠሪ ደውሎ ማጣራት ነበረበት የሚል ምክንያት በመጨመር የሥር ፍርድ ቤት ያሳለፈውን ውሳኔ አጽንቷል የሰበር አቤቱታው የቀረበው በዚህ ነው አመልካች ህዳር ዓም ያቀረበው የሰበር ማመልከቻ ተመርምሮ ተጠሪ ለስር ኛ ተከሳሽ አቶ ካሳሁን መለሰ ችግኝ እንዲያቀርብ በጨረታ ላይ እንዲሳተፍ የግዢ ትዕዛዝ አንዲቀበል ገንዘብ እንዲቀበል እና የተቀበለውን ገንዘብ በተጠሪ የባንክ ሂሳብ ቁጥር ገቢ እንዲያደርግ ውክልና በሰጡበት ሁኔታ ተወካዩ ለአሁን አመልካች ችግኝ አቅርቦ የተከፈለውን ብር ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ወደ ተወካዩ የባንክ ሂሳብ ገቢ በማድረጉ አመልካች ከሥር ኛ ተከሳሽ ጋር ለክስ ምክንያት የሆነውን ገንዘብ በአንድነትና በነጠላ ክፈል የመባሉን አግባብ ከግራ ቀኙ የውል ግንኙነት አንጻር ለማጣራት ሲባል ጉዳዩ ለሰበር ችሎት እንዲቀርብ ተደርጓል ግራ ቀኙም የሥር ክርክራቸውን በማጠናከር በጽሁፍ ተለዋውጠዋል ከፍ ሲል ባጭሩ የገለጽነው የጉዳዩን አመጣጥ ሲሆን በበኩላችን ጉዳዩን እንደሚከተለው መርምረናል እንደመረመርነው ተጠሪ በአመልካች ላይ ክስ የመሰረቱት ችግኝ የማቅረብ ስራውን መስራት ስለበዛብኝ የሥር ኛ ተከሳሽ ይህን ሥራ እንዲሰራልኝ የችግኝ ዘር መቅረብን አስመልክቶ ጨረታ ላይ እንዲሳተፍ የጨረታ ሰነድ አንዲገዛ እንዲያስገባ ገንዘብ ፈርሞ እንዲወስድ የወሰደውንም ገንዘብ በድርጅቱ ሥም ገቢ እንዲያደርግ ውክልና ስልጣን ሰጥቸዋለሁ ይሁን አንጂ ከአመልካች ጋር ችግኞች ለማቅረብ ስንስማማ የገንዘብ ክፍያ በሂሳብ ቁጥሬ ገቢ እንዲያደርጉ ተስማምተን እያለ ከውሉ ውጪ ገንዘቤን ወደ ኛ ተከሳሽ ሂሳብ በማስገባታቸው ተጠያቂነት አለባቸው ገንዘቡን ብር አራት መቶ ፃያ ሺህ ሰባት መቶ ስድሳ ሶስት እንዲከፍሉኝ ይወሰንልኝ በማለት ነው አመልካች በበኩሉ ከተጠሪ ጋር በተደረገው ውል መሰረት ለቀረበው ችግኝ በውሉ የተገለፀውን ብር ከፍያለሁ ተጠሪ ስራውን የሚሰራው በተወካዩ በኩል ነው ተወካዩ ገንዘቡን መውሰድ እንደሚችል በውክልና ሰነዱ ተገልዷል በዚሁ መሰረት ተወካይ የሳብ ቁጥር አቅርበው ገንዘቡ ተላልፏል ተወካይ ክፍያ አንዲፈፀም የጠየቁበት ደብዳቤ በተጠሪ ማህተም ተደግፎ የቀረበ ነው በማለት ተከራክሯል የሥር ፍርድ ቤቶች በተጠየቀው ዳኝነት መሰረት አመልካች ገንዘቡን ለመክፈል ከተወካዩ ጋር የአንድነትና የነጠላ ኃላፊነት አለበት በማለት የወሰኑት የአመልካች መከራከሪያ ተቀባይነት የለውም በማለት ነው ከፍሲል እንደተገለፀው በአመልካች እና በተጠሪ መካከል በተደረገው ውል መሰረት ለቀረበው ችግኝ በውሉ የተመለከተው የብር ክፍያ አመልካች ለተጠሪ ተወካይ መክፈሉ ተጠሪ ስራውን የሚሰራው በተወካዩ በኩል መሆኑ እንዲሁም ተወካዩ ገንዘቡን መውሰድ እንደሚችል በውክልና ሰነዱ ስልጣን የተሰጠው መሆኑ ግራ ቀኙን አላከራከረም ተጠሪ በውሉ ላይ የገንዘብ ክፍያ በሂሳብ ቁጥሬ ገቢ እንዲያደርጉ ተስማምተን እያለ ከውሉ ውጪ አመልካች ገንዘቤን ወደ ተወካይ ሂሳብ በማስገባቱ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ተጠያቂነት አለበት በማለት የተከራከሩ ቢሆንም ከውሉ በኋላ ነፃሴ ዓም ለተወካዩ በሰጡት ውክልና ገንዘቡን እንዲቀበል እና የተቀበለውን ገንዘብ በድርጅቱ የባንክ ሂሳብ ገቢ አንዲያደርግ ውክልና መስጠታቸውን አላስተባበሉም የውክልና ሰነዱም ይህን የሚያሳይ ነው ይልቁንም የሥር ኛ ተከሳሽ ተወካይ በተሰጠው ውክልና መሰረት ገንዘቡን መውሰዱን ሳይክድ ከአሁን ተጠሪ ጋር የመቻቻል እና የሂሳብ አናድርግ ጥያቄ ማቅረቡ ለክሱ መነሻ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል ይህ ደግሞ ለውክልናው ኛ ወገን የሆነውን የአሁን አመልካችን ሳይሆን በወካይ እና ተወካይ መካከል የተፈጠረን የጥቅም ግጭት የሚመለከት ነው ከፍብህቁ እና ተያያዥ ድንጋጌዎች መገንዘብ እንደሚቻለው ውክልናው በላዩ ተዘርዝረው የተመለከቱትን ጉዳዩችና የነዚሁ ተከታታይ እና ተመሳሳይ የሆነውን እንደ ጉዳዩ አይነትና አንደ ልማድ አሰራር አስፈላጊ የሆነውን ማከናወን የሚያስችል ሲሆን ተወካዩ የፈፀመው ተግባር የወካይና ተወካይ ጥቅሞችን ግጭት የሚያስከትል በሆነ ጊዜ ኛው ወገን ይህን ሁኔታ ያወቀና ሊያውቅ የሚገባ መሆኑ ካልተረጋገጠ በቀር ኃላፊነት የሚኖርበት አይሆንም በተያዘው ጉዳይ ተጠሪ ከአመልካች ጋር ውል ካደረገ በኋላ ለወኪሉ የሰጠው ውክልና ችግኝ እንዲያቀርብ በጨረታ ላይ እንዲሳተፍና የግዢ ትዕዛዝ እንዲቀበል የሚል ብቻ ሳይሆን ገንዘብ አንዲቀበል እና የተቀበለውን ገንዘብ በተጠሪ የባንክ ሂሳብ ቁጥር ገቢ እንዲያደርግ ስልጣን የሚሰጥ ነው አመልካች በውል ግዴታው መሰረት ብር ብር ለተጠሪ ተወካይ ከፍሏል ስለሆነም አመልካች ገንዘቡን ለተጠሪ ተወካይ መክፈሉ በባንክ ሂሳቡ ማስገባቱ ውሉን እና የውክልና ሰነዱን መሰረት ያደረገ አይደለም የሚባልበት ምክንያት የለም ከዚህ በቀር አመልካች ውክልናውን ተከትሎ ክፍያ ለተወካይ የፈፀመው በወካይ አና ተወካይ መካከል ያለውን የጥቅም ተቃርኖ አያወቀ ወይም ማወቅ እየተገባው ነው የሚሰኝ ስለመሆኑ ክርክር እና ማስረጃ አልቀረበም በአጠቃላይ የስር ፍርድ ቤቶች አመልካች የውሉን ገንዘብ ለተጠሪ ተወካይ በመክፈሉ ከተወካዩ ጋር የአንድነትና የነጠላ ኃላፊነት አለበት በማለት የደረሱበት መደምደሚያ በክርክሩ የተረጋገጠውን ፍሬነገር እና ከፍ ሲል የተጠቀሱትን የህጉን ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ድንጋጌዎች ይዘት መሰረት ያደረገ ባለመሆኑ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ነው ብለን በአብላጫ ድምጽ ተከታዩንም ወስነናል ውሳኔ የምስራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ ሰኔ ዓም የሰጠው ውሳኔ እንዲሁም የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ይግባኝ ሰሚ ችሉት በመቁ ህዳር ዓም ያሳለፈው ውሳኔ በፍብሥሥህቁ መሰረት በአብላጫ ድምፅ ተሻሸሏል የአሁን አመልካች ከተጠሪ ጋር ያደረገውን ውል እና ተጠሪ ለተወካያቸው የሰጡትን የውክልና ስልጣን መሰረት በማድረግ የውሉን ገንዘብ ለተወካይ የከፈለ በመሆነ ኃላፊነት የለበትም ብለናል ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የሶስት ዳኞች ፊርማ አለበት የሐሳብ ልዩነት እኛ ስማችን በአራተኛ እና በአምስተኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሰው ዳኞች አመልካች በተጠሪ ተወካይ ሂሳብ ቁጥር ገቢ በማድረጉ ከተወካዩ ጋር በአንድነት እና በነጠላ ለተጠሪ ዛሃላፊነት የለበትም በሚለው በአብላጫው ድምጽ ድምዳሜ ስለማንስማማ በዛሳብ ተለይተናል አቶ ካሳሁን መሰለ የተጠሪ ተወካይ በመሆን ከአመልካች ጋር ያደረገው የችግኝ ሸያጭ ውል በፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ እና መሰረት አመልካች እና ተጠሪ መካከል እንደተደረገ ስለሚቆጠር አመልካች ችግኙን ስረከብ ተጠሪ ገንዘቡን የማግኘት መብት ያለው ሲሆን አመልካችም ገንዘቡን ለተጠሪ የመክፈል ተነጻጻሪ ግዴታ እንደሚኖርበት ይታወቃል ተጠሪ ለተወካዩ በሰጠው የውክልና ስልጣን ተወካዩ ገንዘብ ፈርሞ እንዲወስድ ጭምር ስልጣን የሚሰጥ ቢሆንም በአመልካች እና በተጠሪ መካከል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በተደረገ የችግኝ አቅርቦት ውል አመልካች ገንዘቡን በተጠሪ የባንክ ሂሳብ ገቢ ማድረግ አንዳለበት ተስማምቶ የተጠሪ የባንክ ሂሳብ ቁጥር የተሰጠው ሲሆን አመልካች ይህ ስለመሆኑ ክዶ አልተከራከረም አመልካች በዚህ መልኩ መስማማቱን ሳይክድ ገንዘቡን በተወካዩ ሂሳብ ቁጥር ገቢ ለማድረግ የቻለው ተወካዩ ይህን እንዲያደርግ በደብዳቤ የገለጸለት መሆነን በመጥቀስ መሆኑን ተገንዝበናል በሌላ በኩል ገንዘቡ በተጠሪ የባንክ ሂሳብ ገቢ እንዲሆን ግራቀኝ ሲስማሙ በምክንያት ነው ተብሉ ስለሚታመን አመልካች ይህን ስምምነት የማክበር ግዴታ አለበት ተጠሪ ለተወካዩ የሰጠው ውክልና ገንዘብ እንዲቀበል ጭምር የሚያካትት ቢሆንም ገንዘቡ በተወካዩ ሂሳብ ገቢ እንዲደረግ ግራቀኝ በተለየ ሁኔታ ያደረጉት ግልጽ ስምምነት በውክልና ሰነድ ላይ ከተመለተው የውክልና ስልጣን በልዩ ሁፄታ መታየት ያለበት በመሆኑ የማይፈጽምበት ምክንያት የለም በመሆኑም አመልካች ገንዘቡን በተጠሪ የሂሳብ ቁጥር ገቢ ለማድረግ ከተጠሪ ጋር ባደረገው ስምምነት ግዴታ ገብቶ እያለ ከስምምነቱ ውጪ በሆነ ሁኔታ በተጠሪ ሂሳብ ገቢ ማድረግ ያለበትን ገንዘብ በተወካዩ የባንክ ሂሳብ ገቢ በማድረጉ ገንዘቡን ከተጠሪ ተወካይ ጋር በአንድነት እና በነጠላ ለተጠሪ የማይከፍልበት ምክንያት የለም በዚህም ምክንያት ከባልደረቦቻችን በፃሳብ ተለይተናል የማይነበብ የሁለት ዳኞች ፊርማ አለበት መይ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ግንቦት ቀን ዓም ዳኞች ዳ መላኩ ተኽሊት ይመስል ተፈሪ ገብሩዶር ቀነአ ቂጣታ አብዬ ካሳሁን አመልካች አቶ በትግሉ ከበደ ተጠሪ ሽሬ እንዳስላሴ ማረሚያ ቤት መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ የሰበር አቤቱታው የቀረበው የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት በመቁ በ ዓም ያሳለፈውን ትዕዛዝ በመቃወም ሲሆን ክርክሩ የጀመረው በሽረ እንዳስላሴ ወረዳ ፍርድ ቤት የአሁን አመልካች በተጠሪ ላይ ባቀረቡት ክስ ነው አመልካች ያቀረቡት ክስ ይዘት በተጠሪ ተቋም ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች መንግስት በመደበላቸው በጀት መሰረት ከቀን ዓም ጀምሮ ለአንድ ዓመት ምግብ አብስዬ ለማቅረብ ከተጠሪ ጋር ውል አድርገናል በዛደት ደግሞ በቀን ዓም በውሉ መሰረት እየመገብኩ እንደነበር በማረጋገጥ ከቀን ዓም ጀምሮ ከሽንኩርት አቅርቦት ተቀንሶ ወደ በርበሬ ስኳር እና ስጋ እንዲሸጋሸግ በዚህ መሰረት የስጋ አቅርቦት ከነበረበት በተጨማሪ አንድ ጊዜ በወር ከተሸጋሸገው ዋጋ ስጋ እንዳቀርብ ውል ከመሻሻሉ በፊት ሳይቀርቡ የቀሩ ውዝፍ አቅርቦት በማጣጣም በቀጣይ በስጋ መልክ እንዳቀርብ ተስማምተናል ነገር ግን ተጠሪ ከተሻሻለው ስምምነት ውጪ ስጋ አላቀረብክም በማለት መክፈል የሚገባውን ብር አላግባብ የቀነሰብኝ በመሆኑ እንዲሁም በትርፍ ያቀረብኩት የሥጋ ዋጋ ብር ስላልከፈለኝ እንዲከፍለኝ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ተጠሪ ለክሱ በሰጠው መልስ ያላቀረቡት አስቤዛ አና ስጋ በስምምነቱ መሰረት በግራሙ ተለክቶ ባላቀረቡት ልክ ክፍያው የተቀነሰ እንጂ ከውል ውጭ ያስቀረሁት ገንዘብ የለም በማለት ተከራክራል ጉዳዩ በዚህ መልኩ የቀረበለት የወረዳው ፍርድ ቤት የግራቀኙን ክርክርና የምስክሮቻቸውን ቃል እንዲሁም የሰነድ ማስረጃውን መርምሮ በግራቀኙ መካከል የተደረገው የተሻሻለ ውል በወር አንድ ጊዜ አምስተኛ ሆኖ የሚቀርብ ስጋ ለአንድ ታራሚ ግራም ከሳሽ እንዲያቀርብ የሚያስገድድ ስለሆነ ውሉ ከመሻሸሉ በፊት የነበሩ ውዝፍ አቅርቦቶች በስጋ መልክ እንዲቀርቡ ተስማምተው ውዝፍ የስጋ አቅርቦት በተሻሻለው ውል መሰረት ማቅረብ የነበረበትን አመልካች ስላላቀረበ እንዲሁም ሌሎች ለክስ ምክንያት የሆኑ አቅርቦቶች አልቀረቡም ተብሎ በተጠሪ የተቆረጠው ገንዘብ ከሳሽ ግዴታውን ባለመፈፀሙ ምክንያት መሆኑ ተረጋግጧል ስለሆነም አመልካች በውሉ መሰረት መቅረብ የነበረባቸውን ስላላቀረበ ለክስ ምክንያት የሆነው ገንዘብ ተጠሪ ቆርጦ ማስቀረቱ ውሉን መሰረት ያደረገና አግባብነት ያለው ነው በማለት የክሱን ገንዘብ ተጠሪ የመክፈል ግዴታ የለበትም በማለት ወስኗል አመልካች ይህን ውሳኔ በመቃወም ቅሬታቸውን ለሰሜን ምዕራብ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት እና ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ቢያቀርቡም ተቀባይነት አላገኙም የሰበር አቤቱታው ለዚህ ፍርድ ቤት የቀረበው ይህን ውሳኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው አመልካች መስከረም ዓም ያቀረቡት ማመልከቻ በአጣሪ ችሉቱ ተመርምሮ በግራ ቀኙ መካከል የተፈፀመው የመጀመሪያ ውል በሌላ ውል ተሻሽሎ እያለ ክፍያው ግን በመጀመሪያው ውል መሰረት እንዲፈፀም በሥር ፍርድ ቤቶች የመወሰኑን አግባብነት ከፍብህቁ እና ተከታዮች አኳያ ለመመርመር ሲባል ጉዳዩ ለሰበር ችሎት እንዲቀርብ እና ተጠሪ መልስ እንዲሰጥበት ተደርጓል በዚህ መሰረት ግራ ቀኙ ክርክራቸውን በማጠናከር በፅሁፍ ተለዋውጠዋል ከፍሲል ባጭሩ የተመለከትነው የጉዳዩን አመጣጥ ሲሆን ለሰበር ችሉቱ የተያዘውን ጭብጥ ከግራ ቀኙ ክርክርና አግባብነት ካላቸው የህግ ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ በስር ፍርድ ቤቶች በተላለፈው ውሳኔ የተፈፀመ የህግ ስህተት መኖር አለመኖሩን መርምረናል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ከክርክሩ መረዳት አንደሚቻለው የአሁን አመልካች ባቀረቡት ክስ ተጠሪ ከተሻሻለው ስምምነት ውጪ ስጋ አላቀረብክም በማለት መክፈል የሚገባውን ገንዘብ አላግባብ የቀነሰብኝ በመሆኑና በትርፍ ላቀረብኩት የሥጋ ዋጋም ስላልከፈለኝ እንዲከፍለኝ ይወሰንልኝ በማለት የጠየቁ ሲሆን ተጠሪ በበኩሉ ያላቀረቡት አስቤዛ እና ስጋ በስምምነቱ መሰረት በግራሙጮ ተለክቶ ባላቀረቡት ልክ ክፍያው የተቀነሰ እንጂ ከውል ውጭ ያስቀረሁት ገንዘብ የለም በማለት ተከራክሯል ግራ ቀኙ በዚህ መልኩ የተካካዱበትን ፍሬ ነገር በማስረጃ ያጣራው የወረዳው ፍርድ ቤት አመልካች ስምምነት ባደረጉባቸው ውሎች መሰረት ማቅረብ የነበረባቸውን ስላላቀረቡ የክሱን ገንዘብ ተጠሪ ቆርጦ ማስቀረቱ ውሉን መሰረት ያደረገና አግባብነት ያለው ነው በማለት ክሱን ውድቅ አድርጓል ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤትም ይህንኑ የፍሬ ነገር መደምደሚያ ተቀብሉታል በሌላ በኩል ጉዳዩ ለሰበር ችሎት አንዲቀርብ የተደረገው የመጀመሪያው ውል በሌላ ውል ተሻሽሎ እያለ ክፍያው በመጀመሪያው ውል መሰረት እንዲፈፀም በሥር ፍርድ ቤቶች የመወሰኑን አግባብነት ከፍብህቁ እና ተከታዮች አኳያ ለመመርመር በሚል ሲሆን መዝገቡ እንደሚያሳየው የቀደመው ውል መሻሻል የተደረገበት በአቅርቦት እንጂ በዋጋ ጉዳይ አይደለም በቀደመው ውል ከነበረው የቀይ ሽንኩርት ቲማቲም እና አትክልት አቅርቦቶች ላይ በመቀነስ በምትኩ ወደ በርበሬ ስኳርና ስጋ አቅርቦት እንዲጨመር መስማማታቸውን የሚያሳይ ነው የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔ የሰጠውም አመልካች ማቅረብ የነበረባቸውን አንዳላቀረቡ ተረጋግጧል በሚል እንጂ ጉዳዩ ከክፍያ ልዩነት አንፃር ታይቶ አይደለም ከዚህም ሌላ ጉዳዩ ከውል መተካት አንፃር እንዲታይ ይተካል በተባለው አና ተተክቷል በሚባሉት ውሎች መካከል ያለው የውለታ ጉዳይም ሆነ የውለታው ምክንያት በይዘቱ አዲስ መሆን አንዳለበትና ይህንኑ በውለታውም አይነት ሆነ ከውለታው ምክንያት አንፃር ታይቶ አዲስ የሆነው ውል ከዚህ ቀደም ተደርጎ በነበረው ውል ላይ የተመለከቱትን ግዴታዎች በማያጣራጥር አኳኋን ሊያስቀር የሚችል ፈቃድ ከተዋዋይ ወገኖች እንዲኖር አስፈላጊ ስለመሆኑ በፍብሕቁ አና የተደነገገ ሲሆን ውልን የማሻሻል ጉዳይ ግን ከዚህ አንፃር ሊታይ እንደማይገባ መገንዘብ ይቻላል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሥር ፍርድ ቤት ከፍሲል እንደተገለፀው አመልካች በውሎቹ መሰረት ማቅረብ የነበረባቸውን ስላላቀረቡና ግዴታቸውን አለመፈፀማቸው በማስረጃ ተረጋግጧል ለክስ ምክንያት የሆነውን ገንዘብ ተጠሪ የመክፈል ግዴታ የለበትም በማለት የወሰነው ፍሬ ነገሩን ለማጣራት እና ማስረጃ ለመመዘን ባለው ስልጣን መሰረት ነው ይህ ሰበር ሰሚ ችሎት በተሰጠው ውሳኔ የተፈፀመ የህግ ስህተት ካለ ከሚመለከት በቀር መሰል የፍሬ ነገር ክርክርን መርምሮ አና ማስረጃ መዝኖ ውሳኔ የሚሰጥም አይደለም በአጠቃላይ አመልካች በገቡት ውል መሰረት አለማቅረባቸውና ባጎደሉት አቅርቦት ልክ ተጠሪ ክፍያ መቀነሱ በፍሬ ነገር ደረጃ ተረጋግጦ የአመልካች የዳኝነት ጥያቄ ውድቅ መደረጉ ውሉን እና ህጉን የተከተለ ነው ከሚባል በቀር ውሳኔው የህግ ስህተት የተፈፀመበት ነው የሚሰኝ ሆኖ አላገኘነውም ስለሆነም ተከታዩን ወስነናል ውሳኔ በትግራይ ብክመንግስት የሽረ እንዳስላሴ ወረዳ ፍርድ ቤት በመቁ ህዳር ዓም የሰጠው ውሳኔ አንዲሁም የሰሜን ምዕራብ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ መጋቢት ዓም እና የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት በመቁ በ ዓም የተላለፈው ትዕዛዝ በፍሥሥህቁ መሠረት ፀንቷል በዚህ ችሎት ስለተደረገው ክርክር በግራ ቀኙ ለደረሰው ወጪና ኪሣራ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤፍ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ቀን ዓም ዳኞች ተኽሊት ይመሰል ተፈሪ ገብሩ ዶር ቀነዓ ቂጣታ ተሾመ ሽፈራው አብዬ ካሳሁን አመልካች አቶ አክሊሉ ጌታሁን ጠበቃ ክፍለ ታደሰ ቀረቡ ተጠሪ ወሮ ፍሬህይወት አሰፋ ጠበቃ ቸርነት ተገኝ ቀረቡ መዝገቡ መርምረን ተከታዩን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ የብድር ዉል መነሻ ያደረገ ክርክር ሲሆን የጀመረዉ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት አመልካች በተጠሪ ላይ ባቀረቡት ክስ መነሻ ነዉ አመልካች በመዝገብ ቁጥር ሚያዝያ ቀን ዓም ባቀረቡት ክስ የአሁን ተጠሪ በብድር የወሰዱት ብር እንዲመለስላቸዉ ዳኝነት ጠይቋል ተጠሪ በዓም በሰጡት መልስ ከአመልካች የወሰዱት ብድር አለመኖሩን ለተጠሪ እናት የተላከዉ ብር ፈርመዉ የተቀበሉት ብድር አለመሆኑን በመግለጽ ክሱ ዉድቅ አንዲሆን አመልክቷል በዚህ አግባብ ክርክሩ የቀረበለት የስር ፍቤትም በተጠሪ ተፈረመ የተባለዉ ሰነድ በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ ዘርፍ እንዲመረመር የተደረገ ሲሆን በዉሉ ላይ ያለዉን ፊርማ የተጠሪ ተከሳሽ አለመሆኑን መረጋገጡን በመግለጽ አመልካች ከተጠሪ ጋር ያደረጉት የብድር ዉል የለም ተጠሪ በክሱ የተጠቀሰዉ ገንዘብ ሊከፍሉ አይገባም በማለት ወስኗል አመልካች በስር ፍቤት ዉሳኔ ቅር በመሰኘት ለፌከፍቤት ይግባኝ ያቀረበ ሲሆን ፍቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር ከመረመረ በኃላ በአመልካች እና ተጠሪ መካከል የተደረገ የብድር ዉል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የለም ተከፈለ የተባለዉ ብር ከብድር ዉሉ ጋር ግንኙነት የለዉም በማለት የስር ፍቤት ዉሳኔ በማጽናት ወስኗል የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበዉም የስር ፍቤቶች ዉሳኔና ትእዛዝ በመቃወም ለማስለወጥ ነዉ አመልካች መጋቢት ቀን ዓም ባቀረቡት የሰበር አቤቱታ የብድር ስምምነት መኖሩን የሚያስረዱ ተጨማሪ ምስክሮች አንዳያቀርቡ እንደተከለከሉ የብድር ዉል ለማስረዳት የቀረበዉ ሰነድ ባልተካደበት ለምርመራ መላኩ የምርመራ ዉጤቱም እንደ መጨረሻ ብቸኛ መረጃ ተደርጎ መዉሰዱ በህጉ አግባብ አይደለም የሚል ክርክር አቅርቧል የአመልካች አቤቱታ የመረመረዉ አጣሪ ችሎትም የብድር ዉል ሲፈረም የነበሩ ምስክሮች ሳይሰሙ ተጠሪ ሊጠይቁ አይገባም በማለት በስር ፍቤቶች የተሰጠዉ ዉሳኔ ከሰመቁ አንፃር እንዲመረመር በድምጽ ብልጫ ለዚህ ችሎት አስቀርቦታል ተጠሪ ሰኔ ቀን ዓም በሰጡት መልስ በስር ፍቤት የብድር ዉል የሌለ መሆኑን ተረጋግጦ የተሰጠዉ ዉሳኔ እንዲጸና አመልክቷል አመልካች አቤቱታቸዉን የሚደግፍ የመልስ መልስ ሰኔ ቀን ዓም አቅርቧል ከስር የጉዳዩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለመልኩ ከላይ የተገለጸዉ ሲሆን አኛም የሥር ፍቤቶች በሰጡት ፍርድ ላይ ሊታረም የሚችል መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት መሆን አለመሆኑን እንደሚከተለዉ መርምረናል እንደመረመርነዉም የአመልካች መሰረታዊ የዳኝነት ጥያቄ በብድር የተወሰደዉ ብር እንዲመለስላቸዉ የሚያመለክት ነዉ ተጠሪ ብድር አለመዉሰዳቸዉን በመግለጽ ተከራክሯል የስር ፍቤቶች በህጉ አግባብ የተቋቋመ የብድር ዉል ከሚል መደምደሚያ ላይ የደረሱ መሆኑን መዝገቡ ያሳያል አመልካች እና ተጠሪ እያከራከረ ያለዉ ብድር ዉል ነዉ አመልካች ከሳሽ የብድር ዉል መኖሩን ለማስረዳት ተጠሪም የተበደሩ መሆኑን ከተረጋገጠ ክፍያ መፈፀማቸዉን ለማስተባበል መቅረብ ያለበት የማስረጃ ዓይነት ምን መሆን እንዳለበት በፍብህቁ ላይ በግልጽ ተመልክቷል በብድር የተሰጠዉ ገንዘብ ከብር በላይ ከሆነ ብድሩን ለማስረዳት የብድር ዉል መቅረብ ያለበት ሲሆን የብድር ዉሉ ካልቀረበ ደግሞ ተበዳሪዉ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በፍቤት ካላመነ ወይም በቃለ መሀላ ስር ሆኖ ቃሉን ካልሰጠ በስተቀር በሌላ አግባብ ማስረዳት እንደማይቻል ድንጋጌዉ ያመለክታል አመላለሱ በተመለከተም ተመሳሳይ የማስረጃ መርህ የሚከተል ስለመሆነ የፍብሕቁ ደንግጓአል በተያዘዉ ጉዳይ አመልካች ብር ማበደራቸዉ በመግለጽ ክስ ቢያቀርቡም የብድር ዉሉ በተጠሪ አልታመነም የብድር ዉል የተባለዉ ሰነድ በፎረንሲክ ምርመራ የተደረገለት ሲሆን በሰነድ ላይ ያረፈዉ ፊርማ የተጠሪ አለመሆኑን ተረጋግጧል አንዲሁም ተጠሪ ወሰዱት የተባለዉ ብር ብድር ክርክሩ የተያያዘ አለመሆኑን የስር ፍቤት ማረጋገጡን መዝገቡ ያሳያል አመልካች አጥብቀዉ የሚከራከሩት በሰነድ ላይ የተመለከቱ ምስክሮች ሳይሰሙ ዉሳኔ መስጠቱ ተገቢ አይደለም በሚል ነዉ በመሰረቱ ዉሉ በጽጉፍ አንዲሆን በህጉ በተመለከተበት ሁኔታ ሰነድ ራሱ አስረጂ መሆኑን ነገር ግን ሰነድ የተቀደደ የተሰረቀ የጠፋ ስለመሆኑ ከተረጋገጠ ዉሉ በምስክሮች ማስረዳት የሚቻልበት ስርዓት ተመልክቷል በተያዘዉ ጉዳይ ሰነድ ቀርቧል። የሚለው ጥያቄ ምላሽ ሊያገኝ የሚገባው ነው የአመልካች አባት ድርሻቸውን በሥጦታ ለአመልካች መስጠት ይችላሉ እንጂ የባለቤታቸውን ማለትም የግራ ቀኙን እናት ድርሻ ሊሰጡ የሚችሉበት የህግ አግባብ አይኖርም በፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ ከንብረቶቹ አንዱን የሚለቅበት በማለት የተደነገገውም ይህንነ የሚያሳይ ነው እንዲሁም የፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ የተመለከተው ጽንሰ ሀሳብም አስተላላፊው ሰጭ የራሱ የሆነን ሀብት ብቻ ሊያስተላልፍ እንደሚገባ የሚያስገነዝብ ነው በያዝነው ጉዳይ ሟች ደሴ ካሳ ለአሁን አመልካች ሥጦታ ያደረጉት የአሁን ተጠሪዎችን ወላጅ እናት ድርሻ መሬት ነው ይህም ደግሞ ከፍ ሲል ከተመለከተው የፍትሐብሔር ህግ ቁጥር አንጻር ሲታይ አግባብነት ያለው አይደለም በመጨረሻም ለአሁን አመልካች በሥጦታ ሊተላለፍላቸው የሚገባው የወላጅ አባታቸው ድርሻ የሆነው ሁለት ቀዳ መሬት ብቻ እንጂ የወላጅ እናታቸው ድርሻ የሆነው ሁለት ቀዳ መሬት ሊሆን ስለማይችል ግራ ቀኙ እንደየድርሻቸው ሊካፈሉት ይገባል በማለት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰጠው ውሳኔም ሆነ ይህ ውሳኔ በአቤቱታ የቀረበለት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በትፅዛዝ መዝጋቱ ሲታይ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ አልተገኘም በመሆኑም ተከታዩ ውሳኔ ተሰጥቷል ውሳኔ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ እንዲሁም የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰአመቁ በቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር መሠረት ፀንቷል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አለበት የአመልካች አባት ከድርሻቸው ውጪ ያለውን የአርሻ መሬት ለአሁን አመልካች በሥጦታ ሊሰጡ አይችሉምየሟች እናታቸውን ድርሻ የሆነው ሁለት ቀዳ የእርሻ መሬት ለግራ ቀኙ ሊሆን ይገባል ተብሎ በተሰጠው ውሳኔ ላይ የተፈጸመ መሥረታዊ የህግ ስህተት የለም ተብሎ ተወስኗል የዚህን ችሎት ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ የውሳኔው ግልባጭ ለሥር ፍርድ ቤቶች ይድረሳቸው መዝገቡ ውሳኔ ስላገኘ ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ ቅሀ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ቀን ዳኞች ተኽሊት ይመሰል ተፈሪ ገብሩ ዶር ቀነዓ ቂጣታ ተሾመ ሽፈራዉ አብዬ ካሳሁን አመልካች ያዳኒ ራባ አልቀረቡም ከተባለ ተወካይ ሰመረ ገህይወት ቀርበዋል ተጠሪ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንዋር መስጊድ ቅርንጫፍ አልቀረቡም መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ክርክሩ የተጀመረዉ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች በተጠሪ ላይ ባቀረቡት ክስ በመጋቢት ወር ዓም የባንክ ደብተራቸዉን ይዘዉ ባደሩበት አልጋ ላይ ረስተዉ መሄዳቸዉን ተከትሎ ተጠሪ በባንክ ደብተራቸዉ ላይ ያለዉን ገንዘብ ማንነቱ ላልታወቀ ሰዉ በመክፈል የገንዘብ እና የሞራል ጉዳት ያደረሰባቸዉ መሆኑን ጠቅሰዉ ተጠሪ ያላግባብ የከፈለዉን ብር እንዲሁም የሞራል ካሳ ብር እንዲከፍል ይወሰንላቸዉ ዘንድ የጠየቁትን ዳኝነት መነሻ ያደረገ ነዉ ተጠሪ በበኩሉ ለክሱ በሰጠዉ መልስ ገንዘቡ የተከፈለዉ አመልካች ከሞሉት ፎርም እአና ከፊርማቸዉ ናሙና ጋር በማመሳከር ተገቢዉ ጥንቃቄ ተደርጎ ለአመልካች ለአእራሳቸዉ የተከፈለ መሆኑን አንዲሁም ደብተሩ ጠፍቶ አራት ወር ሲቆይ አመልካች ደብተሩ ስለመጥፋቱ ለፖሊስ አመልክተዉ ሂሳቡ እንዲታገድላቸዉ አለማድረጓጋቸዉን በመጥቀስ ኃላፊነት የለብኝም ሲል ተከራክሯል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ጉዳዩ በመጀመሪያ የቀረበለት የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትም ከግራ ቀኝ በዚህ መልኩ የቀረበዉን ክርክር ከሰማ በኋላ አመልካች ደብተሩ የጠፋባቸዉ ስለመሆኑ ለተጠሪ የማሳወቅ ግዴታ እያለባቸዉ ይህን ባለማድረግ የሂሳብ ደብተሩ ሦስተኛ ወገን አጅ ገብቶ ገንዘቡን ሌላ ሰዉ እንዲያወጣ ምክንያት በመሆናቸዉ ተጠሪ ገንዘቡን እንዲከፍል የሚገደድበት ምክንያት የለም በማለት የቀረበዉን ክስ ዉድቅ በማድረግ ወስኗል አመልካች ይህን ዉሳኔ ባለመቀበል ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያቀረቡት ይግባኝም ተቀባይነት አላገኘም አመልካች በቀን ተዘጋጅቶ በተወካያቸዉ አማካይነት በቀረበ የሰበር አቤቱታ ተጠሪ ተገቢዉን ማጣራት እና ጥንቃቄ ሳያደርግ ከአመልካች የሂሳብ ደብተር ወጪ አድርጎ ለሌላ ሰዉ ከፍሎ እያለ እና ገንዘቡን የከፈለዉ የባንኩ ሠራተኛም በዚህ ጉዳይ ላይ በወንጀል ተከሶ ጥፋተኛ ሆኖ እያለ አመልካች ደብተሩ መጥፋቱን ሪፖርት የማድረግ ግዴታቸዉን አልተወጡም የሚል ምክንያት በመጥቀስ ተጠሪ ኃላፊነት የለበትም በሚል በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተሰጥቶ በከፍተኛ ፍርድ ቤት ፀንቶ የተወሰነዉ ዉሳኔ መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነዉ በማለት ታርሞ ይወሰንላቸዉ ዘንድ ዳኝነት ጠይቀዋል አቤቱታዉ ተመርምሮ የስር ፍርድ ቤት የአመልካችን ክስ ዉድቅ ያደረገዉ በአግባቡ መሆን ያለመሆኑን ግራ ቀኝ በተገኙበት አጣርቶ ለመወሰን ሲባል ያስቀርባል በመባሉ ተጠሪ በተደረገለት ጥሪ መሠረት ቀርቦ ግራ ቀኝ ክርክራቸዉን በጽሑፍ ተለዋዉጠዋል ከስር ጀምሮ የክርክሩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለ መልኩ ሲታይ ከፍ ሲል የተመለከተዉ ሲሆን ይህ ችሎትም አቤቱታዉን ለማስቀረብ የተያዘዉን ጭብጥ ከግራ ቀኝ ክርክር እና ለጉዳዩ አግባብነት ካላቸዉ ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ መዝገቡን እንደሚከተለዉ መርምሮታል ከክርክሩ ሂደት መገንዘብ የተቻለዉ አመልካች በተጠሪ ላይ ባቀረቡት ክስ ለጠየቁት ዳኝነት መሠረት ያደረጉት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሂሳብ ቁጥር ያስቀመጡትን ገንዘብ የያዘ የባንክ ደብተር መጥፋቱን እና ባንኩ በሂሳብ ደብተሩ ላይ የተመለከተዉን ገንዘብ ለኛ ወገን መክፈሉን ሲሆን ተጠሪም የባንክ ደብተር ላይ የተመለከተዉን ገንዘብ ወጪ አድርጎ የከፈለ ስለመሆኑ ክዶ አልተከራከረም የተጠሪ ክርክር የነበረዉ ተገቢዉን ጥንቃቄ አድርጎ ለአመልካች አራሷ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ መክፈሉን እና የሂሳብ ደብተሩ ስለመጥፋቱ አመልካች ለተጠሪ የማሳወቅ ግዴታቸዉን አለመወጣታቸዉን ሲሆን የስር የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትም የአመልካችን የዳኝነት ጥያቄ ተቀባይነት የለዉም በሚል ድምዳሜ ላይ የደረሰዉ አመልካች ደብተሩ ስለመጥፋቱ ለተጠሪዉ ባንክ ሪፖርት የማድረግ ግዴታቸዉን አለመወጣታቸዉን ስለመሆኑ የዉሳኔዉ ይዘት ያስገነዝባል በመሠረቱ በግራ ቀኝ መካከል ተደርጎ ለዚህ ክርክር ምክንያት የሆነዉ ግንኙነት መሠረቱ በንግድ ህጉ አንቀጽ እና ስር የተመለከተዉ ገንዘብ በአደራ የማስቀመጥ ዉል ሀቪ በ ነዉ በዚህ ዉል መሠረትም ተጠሪ አደራ አስቀማጭ አንደመሆኑ የአመልካችን ገንዘብ የመጠበቅ አመልካች ሲጠይቁ ወጪ አድርጎ የመክፈል እና ከአመልካች ዉጪ ለሌላ ሰዉ ያለመክፈል ከዉል የመነጨ ግዴታ ይኖርበታል ይህን የማድረግ ግዴታዉን ባለመወጣት በአመልካች ላይ ሊደርስ ለሚችል ጉዳት ከዉል የመነጨ ኃላፊነት አንደሚኖርበትም ይታወቃል በመሆኑም ማንኛዉም ባንክ የሚቀርብለትን የክፍያ ጥያቄ ሲያስተናግድ ገንዘብ እንዲከፈለዉ ጥያቄዉን ያቀረበ ሰዉ በርግጥም አደራ አስቀማጩ መሆን አለመሆኑን በቅድሚያ የማረጋገጥ ግዴታ ይኖርበታል የተያዘዉን ጉዳይ በተመለከተ ተጠሪ በአመልካች የባንክ ሂሳብ ላይ የሚገኘዉን ለክርክሩ ምክንያት የሆነዉን ገንዘብ ወጪ አድርጎ ክፍያ የፈጸመ ስለመሆኑ ክዶ እስካልተከራከረ ድረስ ከኃላፊነት ሊድን የሚችለዉ ገንዘቡን የከፈለዉ በባንኩ በተዘረጋዉ ደንብና አሰራር መሠረት አስፈላጊዉን ጥንቃቄ ሁሉ አድርጎ ተከፋይ አመልካች መሆኑን በማረጋገጥ ክፍያዉን የፈጸመ ስለመሆኑ ማረጋገጥ ሲችል ብቻ ነዉ በርግጥ አመልካች ደብተሩ ስለመጥፋቱ ለተጠሪ ባንክ የማሳወቅ ግዴታ እንዳለባቸዉ ይታወቃል ይሁንና ተጠሪ የአመልካችን ገንዘብ በአደራ የመጠበቅ ባለበት ግዴታ መሠረት ተገቢዉን ጥንቃቂ ባለማድረግ ገንዘቡን ለሌላ ሰዉ በመክፈሉ ምክንያት በአመልካች ጉዳት መድረሱ ከተረጋገጠ አመልካች ደብተሩ ስለመጥፋቱ ለተጠሪ አለማሳወቃቸዉ የተጠሪን ኃላፊነት ሊያስቀር የሚችል አይሆንም በመሆኑም በስር ፍርድ ቤት በፍሥሥርዓት ህጉ አንቀጽ መሠረት ተይዞ በማስረጃ ተጣርቶ እልባት ሊሰጠዉ የሚገባዉ ትክክለኛ ጭብጥ ተጠሪ ለክርክሩ ምክንያት የሆነዉን ገንዘብ የከፈለዉ አስፈላጊዉን ጥንቃቁ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በማድረግ ተከፋዩ አመልካች መሆኑን በማረጋገጥ መሆን አለመሆኑ ነዉ ከዚህ አንፃር ሲታይ የስር የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመልካች ደብተራቸዉ ስለመጥፋቱ ለተጠሪ የማሳወቅ ግዴታቸዉን አልተወጡም በሚል የፍሕጉን አንቀጽ ድንጋጌ ያለቦታዉ በመጥቀስ የቀረበዉን ክስ ዉድቅ በማድረግ የሰጠዉ ዉሳኔ እንዲሁም የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ይህኑን በማጽናት የሰጠዉ ትዕዛዝ መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ አግኝተናል በመሆኑም ተከታዩ ተወስኗል ዉሳኔ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በኮመቁጥር በቀን ዓም በዋለዉ ችሎት የሰጠዉ ዉሳኔ እንዲሁም የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁጥር በቀን ዓም በዋለዉ ችሎት የሰጠዉ ትዕዛዝ በፍሥሥርዓት ህጉ አንቀጽ መሠረት ተሽረዋል የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተዘግቶ የነበረዉን መዝገብ በማንቀሳቀስ ተጠሪ ለክርክሩ መነሻ የሆነዉን ገንዘብ ከአመልካች የባንክ ሂሳብ ወጪ አድርጎ ሲከፍል በባንኩ በተዘረጋዉ ደንብና ስርዓት መሠረት ክፍያዉ ለአመልካች የተከፈለ መሆኑን ማረጋገጥ በሚያስችል ደረጃ አስፈላጊዉን ጥንቃቂ በማድረግ መሆን አለመሆኑን በተመለከተ የግራ ቀኝን ማስረጃ እንዲሁም እንዳስፈላጊነቱ ሌሎች ተጨማሪ ማስረጃዎችን ጭምር አስቀርቦ በመመርመር ባንኩ አደራ አስቀማጭ ከመሆኑ አንፃር ክፍያን በመፈጸም ረገድ እንዲያደርግ ከሚጠበቅበት ጥንቃቄ አንፃር በማገናዘብ ተገቢዉን ዉሳኔ እንዲሰጥበት መዝገቡ በፍሥሥርዓት ህጉ አንቀጽ መሠረት ተመልሶለታል በዚህ ችሎት የተደረገዉ ክርክር ያስከተለዉን ወጪ እና ኪሳራ ግራ ቀኝ የየራሳቸዉን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ግንቦት ቀን ዓም ዳኞች ተኽሊትይመሰል ተፈሪ ገብሩ ዶር ቀነዓ ቂጣታ ተሾመ ሽፈራዉ አብዬ ካሳሁን አመልካችየኢትዮጵያና የጅቡቲ ምድር ባቡር ድርጅትጠበቃ ዶር ዘዉድነህ በየነ አና ነፈጅ አቶ አስራት መኮንን ቀርበዋል ተጠሪፁ ኮንስታ ጆይንት ቬንቸርጠበቃ አቶ ወሰንየለህ ትጉህ ቀርበዋል ይህ መዝገብ የተቀጠረዉ ለምርመራ ሲሆን ተመርምሮ የሚከተለዉ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ ክርክር የተጀመረዉ በዓለም አቀፍ የግልግል ዳኝነት ጉባኤ ኔዘርላንድ ፄግ የሚገኘዉ ቋሚ የግልግል ዳኝነት ፍቤት የሚያስተዳደረዉ መቀመጫዉ አዲስ አበባ ከተማ ኢትዮጵያ የሆነዉ ሲሆንየአሁን አመልካች ተከሰሽየአሁን ተጠሪ ደግሞ ከሳሽ ሁኖ ሲከራከሩ ነበርጉዳዩ ለዚህ ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ የግልግል ዳኝነት ጉባኤዉ በመቁ ሚያዚያ ቀን ዓም እኤአ ግንቦት ቀን የሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ እንዲታረምልን በማለት አመልካች ያቀረበዉን የሰበር አቤቱታ መርምሮ ለመወሰን ነዉ የጉዳዩየአመጣጥሲታይከሳሽ ኮንስታ ጆይንት ቬንቸር ባቀረበዉ ክስ ከተከሳሽ የኢትዮጵያና የጅቡቲ ምድር ባቡር ድርጅት ጋር የባቡር መስመር ጥገና ዉል ህዳር ቀን ዓም ክዕህከ። ተጠሪ አጥብቆ የሚከራከረው የተሻሻለው መመሪያ ቁጥር ዓንቀፅ ሐመ ውሉ ከኔ ጋር እንዲቀጥል ይደግፈኛል በማለት ሲሆን ከመዝገቡ ይዘት ለመረዳት እንደቻልነው በነበረው መመሪያ መሰረት ወላጅ አባት ሲሞት የተከራይ መብት ወደ እናት ሚስት እንዲተላለፍ የሚፈቅድ መሆኑ በዚህ መሰረትም የቤቱ ተከራይ የነበሩት አቶ ወልዴ ብራሮ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ ባለቤታቸው የሆኑት ወሮ ፈለቀች ጫካ ህጋዊ ተከራይ እና የኪራይ ገንዘቡም በስማቸው የሚከፈል መሆኑ ተጠሪ ግን ቤቱ ውስጥ መኖሩ እንጂ ከአመልካች ጋር ህጋዊ ውል የሌለው መሆኑ የተሻሻለው መመሪያ ቁጥር ም ሆነ ከዚሁ ከተሻሻለው መመሪያ በፊት የነበረው መመሪያ የቤት ተከራይነት መብት ለልጅ የሚተላለፈው ህጋዊ ተከራይ የሆነው ወላጅ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለይ አንጂ ኮንደሚኒየም ደርሶት ቤቱ ሲለቅ ባለመሆኑ በተያዘው ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ጉዳይ ህጋዊ ተከራይ የነበሩት የተጠሪ እናት ወሮ ፈለቀች ጫካ ኮንደሚኒየም ቤት አግኝተው ከተከራዩት ቤት ከለቀቁ ቤቱ በመመሪያው መሰረት አከራይ ለሆነው አመልካች መመለስ አለባቸው ስለሆነም አከራካሪ የሆነውን የመንግስት ቤት ህጋዊ ተከራይ የሆኑት የተጠሪ አናት በመሆናቸው እሳቸው የኮንደሚኒየም ቤት ከደረሳቸው ከመንግስት የተከራዩት ቤት ለመንግስት የማስረከብ ግዴታ ያላቸው በመሆኑ እና ተጠሪ አከራካሪው ቤት በተመለከተ መብት ያለው መሆኑ ማስረጃ ያልቀረበ በመሆነ አመልካች ለከሳሽ አከራካሪውን ቤት ለቀው አንዲወጡ ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ህጋዊ ተግባር ነው ሲጠቃለል የስር ፍርድ ቤቶች አመልካች ማስጠንቀቂያ መስጠቱ የሁከት ተግባር ነው በማለት የሰጡት ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ስለሆነ የሚከተለዉ ተወስኗል ዉሳኔ የአዲስ አበባ ከተማ ይግባኝ ሰሚ ሰበር ችሎት በመቁጥር ታህሳስ ቀን ዓም የስር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ በማዕናት የሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ በፍብሥሥሕቁ መሰረት ተሽሯል አመልካች አከራካሪውን ቤት በተመለከተ የሰጠው ማስጠንቀቂያ የሁከት ተግባር አይደለም ብለናል ግራ ቀኛቸዉ በዚህ ችሎት የደረሰባቸዉ ወጪና ኪሳራ የየራሳቸዉን ይቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ ብለናል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ማአ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞችአልማው ወሌ ሙስጠፋ አህመድ አብርፃዛ መሰለ ፈይሳ ወርቁ ጳውሎስ ኦርሺሶ አመልካች ወሮ አድና መላኩ ተጠሪ የወልዲያ ከተማ አገልግሎት ጽቤት ከክልሉ ፍትህ ቢሮ ፍሬህይወት አበባ ቀረቡ መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ የሰበር አቤቱታ ሊቀርብ የቻለው አመልካች የወልዲያ ወረዳ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም ጉዳዩ በቀጥታ ክስ በፍርድ ቤት የሚታይ አይደለም በማለት የሰጠውን ብይን የሰሜን ወሎ መስተዳድር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም በፍርድ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ አጣሪ ችሎት በመቁጥር በ ዓም በትእዛዝ በማጽናታቸው መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት በሆኑ በሰበር ታይቶ ይታረምልኝ በማለታቸው ነው ጉዳዩ የዳኝነት ሥልጣንን የሚመለከት ሲሆን በስር ፍቤት አመልካች ከሳሽ ተጠሪ ደግሞ ተከሳሽ ነበሩ የክሱ ይዘትም በወልዲያ ከተማ ቀበሌ ክልል ውስጥ የሚገኘውና አዋሳኙ በክሳቸው የተጠቀሰው ቦታ እንዳላቸውና በዚህ ቦታ ላይ ቤት ያላቸው ባህር ዛፍና ሁለት አግር ጽድ ያፈሩ መሆኑን ይዞታውን ለረዥም ጊዜ ይዘው ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በሚገኙበት ሁኔታ ተጠሪ ህግና መመሪያን መሰረት ሳያደርግ ለአመልካችም ካሜትር ይዞታ ሳይጠብቅላቸው ቦታውን እየሸነሸነ ለግለሰቦች እየሰጠ እንደሚገኝ በቦታው ላይ የሰሩትን ቤት ያለምንም ምክንያት በዶዘር መጋቢት ወር ዓም ያፈረሰባቸውና አቤቱታቸውን ለሚመለከተው አካል አቅርበው የሚመለከታቸው አካላት አንደማንኛውም ባለይዞታ ካሜትር ይዞታ ለአመልካች እንዲጠበቅላቸው አስተዳደራዊ ውሳኔ የሰጡ መሆኑንና በዚህ አግባብ እንዲወሰንላቸው ለተጠሪም ሆነ ለሚመለከተው አካል አመልክተው መፍትሔ ያላገኙ መሆኑን ገልጸው ለክሱ ምክንያት ከሆነው ነባር ይዞታ ላይ ካሜት እንዲጠበቅላቸው ከሕግ ውጪ በዶዘር ለፈረሰባቸው ቤት ግምት ብር አንድ መቶ ሺህ ብር የባህር ዛፉና የፅዱ ግምትም እንዲከፈላቸው እንዲሁም ከ ካሜትር በላይ ላለው ይዞታም ካሳ አእንዲከፈላው ይወሰን ዘንድ ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው የአሁነ አመልካችም ጉዳዩ በአዋጅ ቁጥር እና በአዋጅ ቁጥር መሰረት በፍርድ ቤት በቀጥታ ክስ የሚታይ ያለመሆኑን አመልካች በቦታው ላይ መብት የሌላቸው መሆኑንና ሌሎች የክርክር ነጥቦችን በማንሳት ተከራክሯል የሥር ፍርድ ቤትም ስልጣንን መሰረት አድርጎ የተነሳውን የተጠሪን መቃወሚያ መርምሮ አመልካች የከተማ ቦታ ይዞታን እንዲለቁ የተደረጉ በመሆኑ ጉዳዩ መታየት ያለበት በከተማ አስተዳደሩ ስር ለተቋቋመ የመሬት ነክ አቤቱታ ሰሚ አካል ነው እንጂ ለፍርድ ቤት አይደለም የሚል ምክንያት አስፍሮ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን በቀጥታ ክስ የማየት የስረ ነገር ስልጣን የለውም ሲል በብይን የአመልካችን ክስ ውድቅ አድርጎታል በዚህ ብይን የአሁነ አመልካች ቅር በመሰኘት ይግባኛቸውን ለሰሜን ወሎ መስተዳድር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርበው ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን አከራክሮ የሥር ፍርድ ቤት የሰጠውን ብይን ተገቢ ነው በማለት አጽንቶታል በመጨረሻም አመልካች የሠበር አቤቱታቸውን ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አቅርበው በአጣሪው ችሎት ተሰርኮዞባቸዋል የአሁኑ የሠበር አቤቱታ የቀረበውም ይህንነ በመቃወም ለማስለወጥ ነው የአመልካች የሰበር አቤቱታ መሰረታዊ ይዘትም የአመልካች ክስ መሰረታዊ ይዘት ከሕግ ውጪ የተወሰደው ቦታና የወደመው ንብረት በሕጉ አግባብ ታይቶ ባለይዞታነታቸው መብት እንዲጠበቅላቸውና ለወደመው ንብረት ደግሞ ካሳ እንዲከፈል የሚያሳይ ሁኖ እያለ የክሱን መሰረታዊ ይዘት ሳይገነዘቡ ጉዳዩ በቀጥታ ክስ በፍርድ ቤት የሚታይ አይደለም ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በማለት መወሰናቸው ያላግባብ ነው የሚል ሲሆን አቤቱታቸው ተመርምሮም አመልካች በሕገ ወጥ መንገድ ቦታዬ ተወስዶአል ንብረቴም ወድሟል በማለት ያቀረቡት ክስ በአስተዳደራዊ መልኩ ብቻ የሚታይ ነው በማለት የሥር ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር እና የሊዝ ደንብ ቁጥር በመጥቀስ የመወሰናቸውን አግባብነት ለመመርመር ሲባል ጉዳዩ ለዚህ ችሎት የቀረበ ሲሆን ተጠሪ ቀርቦም ግራ ቀኙ በፅሁፍ እንዲከራከሩ ተደርጎአል የጉዳዩ አመጣጥ አጠር ባላመልኩ ከላይ የተመለከተው ሲሆን ይህ ችሎትም የግራ ቀኙን ክርክር ለሰበር አቤቱታው መነሻ ከሆነው ውሳኔ አና አግባብነት ካላቸው ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ ጉዳዩን ለዚህ ችሎት ያስቀርባል ሲባል ከተያዘው ጭብጥ አንጻር በሚከተለው መልኩ መርምሮታል ከከርክር ሂደት መገንዘብ የሚቻለው አመልካች ከነባር ይዞታቸው ውስጥ በሕጉ አግባብ ሊጠበቅላቸው የሚገባው ይዞታ መብት ያልተጠበቀላቸው መሆኑንና በይዞታው ላይ የነበሩ ንብረቶችም ኪሳራ ሳይከፈላቸው በዶዘር የወደሙባቸው መሆኑን ጠቅሰው ክስ የመሰረቱ መሆኑን ተጠሪ የሚከራከረው ደግሞ ጉዳዩ ከህግ ውጪ የተያዘውን የከተማ ቦታ የማስለቀቅ ጉዳይ በመሆኑ ለተጠሪ በሕጉ ከተሰጠው ስልጣን አንፃር ጉዳዩ የከተማ ቦታን ማስለቀቅ ጉዳዮች አቤቱታ ሰሚ አካል ከሚቀርብ በስተቀር በቀጥታ ክስ በፍርድ ቤት የሚታይ አይደለም በማለት የሚከራከር መሆኑን ነው ፍርድ ቤቶች በህግ የሚቋቋሙ በመሆናቸው የዳኝነት ስልጣናቸው የሚመነጨውም ከህግ ነው የማንኛውም ፍርድ ቤት ስልጣን በህግ ተወስኖ የሚሰጥ በመሆኑ ፍርድ ቤት የቀረበለትን ጉዳይ ተቀብሎ ከማስተናገዱ በፊት ጉዳዩን ክሱን ለማየት በህግ የተሰጠ የዳኝነት ስልጣን ያለው መሆኑን የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት በህግ የዳኝነት ስልጣን ሳይኖረ የሚሰጥ ውሳኔ የህግ መሰረት ያለው ነው ለማለት አይቻልም ወደ ያዝነው ጉዳይ ስንመለስ አመልካች በስር ፍርድ ቤት የጠየቁት ዳኝነት ከነባር ይዞታቸው ውስጥ ካሜትር እንዲጠበቅላቸውና በይዞታው ላይ የነበረው ንብረትም ከሕግ ውጪ በመወደሙ ካሳ ሊከፈለኝ ይገባል በማለት ነው ተጠሪም ይዞታውን ከሕግ ውጪ በመያዙ መውሰዱንና አመልካች በሕግ አግባብ የያዙት ይዞታ ደግሞ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የተጠበቀላቸው መሆኑን ገልጾ ጉዳዩ የከተማ ቦታን ከማስተዳደር ስልጣኑ ጋር የተያያዘና በከተማ ቦታ ማስለቀቅ ጉዳዮች አቤቱታ ሰሚ አካል ቀርቦ ሊታይ ይገባል በማለት የሚከራከር መሆኑን ተገንዝበናል በመሰረቱ ካሳን አስመልክቶ የሚቀርቡ አቤቱታዎችና ይግባኝ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ በግልጽ ተደንግጓል በከተማ አስተዳደር የከተማ መሬት ማስለቀቅ ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ ካለ ካሳውን አስመልክቶ የሚቀርበው ቅሬታ ለዚህ አስተዳደራዊ አካል የሚቀርብ ስለመሆነ ሕጉ የሚደነግግ ሲሆን የከተማው አስተዳደራዊ አካል ካሳውን አስመልክቶ በሚሰጠው ውሳኔ ላይ ቅሬታ ያለው ወገን ለመደበኛ ፍርድ ቤት ይግባኙን ማቅረብ እንደሚችልም ሕጉ ደንግጎ ይገኛል እንዲሁም ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የሚሰጠው ውሳኔ የመጨረሻ ስለመሆኑም ሕጉ ይደነግጋል ሆኖም በአዋጁ መሰረት ይዞታው የተወሰደው ያለአግባብ ነው በሚል መሬት እንዲለቀቅ በተላለፈው ውሳኔ ላይ ቅሬታ ማቅረብ የሚቻልበት ሁኔታ በአዋጁ ውስጥ አልተካተተም የሊዝ አዋጅ ቁጥር በአንቀፅ ስር አግባብ ያለው አካል ከቦታው ለሚነሳው ንብረት ተመጣጣኝ ካሳ በቅድሚያ እንዲከፈል በማድረግ የከተማ ቦታ ይዞታን ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የማስለቀቅና የመረከብ ስልጣን እንደሚኖረው ሲደነግግ በተጠቃሹ ድንጋጌ ንዑስ ቁጥር አራት ስር ደግሞ አግባብ ያለው አካል በሕገ ወጥ መንገድ የተያዘን የከተማ ቦታ በአዋጁ አንቀጽ መሰረት የማስለቀቂያ ትፅዛዝ በመስጠትና ካሳ መክፈል ሳያስፈልግ የሰባት ቀናት የፅሑፍ ማስጠንቀቂያ ብቻ ለባለይዞታው በአካል በመስጠት ወይም በቦታው በሰፈረው ንብረት ላይ በመለጠፍ የማስለቀቅ ስልጣን እንደሚኖረው ተመልክቶአል የማስለቀቂያ ትዕዛዝን ወይም ማስጠንቀቂያ የሚመለከቱ አቤቱታዎች አቀራረብን በተመለከተም አዋጁ በአንቀጽ ስር ያሰፈረ ሲሆን በአቤቱታዎች ላይ ስለሚኖረው ይግባኝም በአዋጁ አንቀፅ ስር ሰፍሮ ይገኛል በመሆኑም አዋጅ ቁጥር በሕገ ወጥ መንገድ የተያዙ የከተማ ቦታዎችን እንዲለቀቁ የሚደረግበት ስርዓት በግልጽ የተመለከተ ሲሆን አግባብ ያለው አካል በሚሰጠው ውሳኔ ላይ ቅሬታውን ለይግባኝ ሰሚው ጉባኤው ማቅረብ እንደሚችል ሕጉ መደንገጉ ጉዳዩ በቀጥታ ወደ ፍርድ ቤት የሚሄድበት አግባብ የሌለ መሆኑን የሚያሳይ ነው ይግባኝ ሰሚው አካል ጉዳዩን የሚያስተናግደውም አቤቱታው በቅድሚያ መሬቱን እንዲለቅ ትዕዛዝ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ለሰጠው አካል ቀርቦ መስተናገዱ ሲረጋገጥ መሆኑን በአዋጁ የከተማ ቦታን ማስለቀቅ ጋር በተያያዘ የሚነሱ ክርክሮችን በተመለከተ የተዘረጋው ስርዓት ያስገነዝበናል ወደ ተያዘው ጉዳይ ስንመለስም አመልካች ክሱን የመሰረቱት የነባር ይዞታ ባለመብትነት እንዲጠበቅላቸውና በተጠሪ የወደመ ንብረት ካሳ እንዲከፈላቸው ሲሆን የክሳቸው መሰረታዊ ይዘት የሚያስገነዝበውም የነባር ይዞታ መብትን የሚመለከቱ ህጎች የጠበቁላቸው መብቶች ሳይከበሩላቸው ሕጉቹ ተጥሰው ይዞታው የተወሰደባቸው መሆኑንና ይዞታው ሲወሰድም በላዩ ላይ የሰፈረው ንብረት የወደመባቸው መሆኑን በመሆኑ ነባር ይዞታን የሚመለከቱ ሕጎችንና የፍብሕቁጥር ድንጋጌን መሰረት በማድረግ ጥያቄአቸውን መመርመርን የግድ የሚል ነው ተጠሪ የከተማ ይዞታን የማስተዳደር ስልጣን በሕጉ አግባብ የተሰጠው ቢሆንም ስልጣንን እና ኃላፊነቱን በሕጉ አግባብ አልተወጣም የሜል ክርክር ያለው ወገን ግን ጉዳዩን በፍርድ ቤት ወስዶ መብቱን ከማስከበር የሚከለከል ያለመሆኑን ከኢፌዲሪፐብሊክ ሕገ መንግስት አንቀፅ እና ድንጋጌዎች ጣምራ ንባብ የምንረዳው ጉዳይ ነው አመልካች ክሳቸውን ለመደበኛ ፍርድ ቤት ሊያቀርቡ የቻሉትም የሚመለከታቸው የከተማው አስተዳደር አካላት የነባር ይዞታ ባለመብትነታቸው እንዲጠበቅላቸው አስተዳደራዊ ውሳኔ ሰጥተው እያለ ተጠሪ ውሳኔውን ባለማክበሩ ምክንያት መሆኑን ከክሳቸው መግለፃቸው ሲታይ በአዋጅ ቁጥር አንቀፅ ከ እና ድንጋጌዎች በተመለከተው አካል በሚመለከተው አካል በተሰጠው ውሳኔ ቅሬታ አላቸው ለማለት የማያስችል በመሆኑ በተጠቃሹ አዋጅ በተዘረጋው የይግባኝ ጉባኤ መብታቸውን ማስከበር አለባቸው ሊባሉ የሚችሉበት የሕግ አግባብ የለም ይልቁንም እሚመለከተው አካል መስኖባቸው እያለ በተጠሪ ለጉዳዩ አግባብነት ያላቸው ሕጎቹ ተጥሰው የይዞታና የንብረት መብታቸው እንደተነካባቸው አመልካች በክሳቸው መጥቀሳቸውና ተጠሪም በሕጉ አግባብ ስልጣኑን በመጠቀም የወሰደው አርምጃ መሆኑን ጠቅሶ መከራከሩ በፍብሥሥሕቁጥር እና ድንጋጌዎች አግባብ የተጠሪ እርምጃ ሕጉን ተከትሎ የተከናወነ መሆን ያለመሆኑን የሚመለከት ጭብጥ በመያዝ ጉዳዩን ማጣራትን የግድ የሚል በመሆኑ በአዋጅ ቁጥር ወይም አዋጅ ቁጥር ድንጋጌዎች አግባብ በተዘረጋው ስርዓት መሰረት በቀጥታ ለፍርድ ቤት ሊቀርብ የሚችል አይደለም ወደሚለው ድምዳሜ የሚያደርስ አይደለም ስለሆነም ከአመልካች ክስ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ መሰረታዊ ይዘት ስንነሳ በስር ፍርድ ቤት የተሰጠው ብይንም ሆነ በክልሉ የበላይ ፍርድ ቤቶች ይህንኑ ብይን በማጽናት የተሰጠው ዳኝነት መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ አግኝተናል በዚሁ መሰረት ተከታዩን ውሳኔ ሰጥተናል ውሳኔ በወልዲያ ወረዳ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም ተሰጥቶ በሰሜን ወሉ መስተዳድር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም በፍርድ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ አጣሪ ችሎት በመቁጥር በ ዓም የጸናው ብይን በፍሥሥሕቁ መሰረት ተሸሯል የወልዲያ ወረዳ ፍርድ ቤት በመቁ ክርክሩን አንዲቀጥል በማድረግ ከስልጣን ውጪ የቀረቡትን የግራ ቀኙን ሌሉች የክርክር ነጥቦችን በመመርመርና በማጣራት ተገቢውን ዳኝነት እንዲሰጥበት ጉዳዩን በፍብሥሥሕቁጥር መሰረት መልሰን ልከንለታል ይጻፍ በዚኅ ችሎት በተደረገው ክርክር ግራ ቀኙ ያወጡትን ወጪና ኪሳራ የየራሳቸውን ይቻቻሉ ብለናል መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ ብለናል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞች ብርሃኑ አመነዉ በዕዉቀት በላይ እንዳሻዉ አዳነ ፃይሉ ነጋሽ እትመት አሰፋ አመልካች ኢትዮቴሌኮም የሰሜን ምስራቅ ሪጅን ተጠሪ ወሮ በለጡ ወልደ ተገኝ መዝገቡ ለምርመራ የተቀጠረ በመሆኑ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ በዚህ መዝገብ የቀረበዉ ጉዳይ አመልካች በተጠሪ ይዞታ ላይ የተከለዉን ኮንቴነር እንዲያነሳ የቀረበዉን ክስ መነሻ በማድረግ የአማራ ክልል ጠ ፍርድ ቤት አመልካች የተጠሪ ይዞታ ለተጠቀመበት ተገቢዉን ካሳ እንዲከፍል መወሰኑን ተከትሎ ዉሳኔዉ መሰረታዊ የህግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል እንዲታረም የቀረበ አቤቱታ ነዉ የጉዳዩ አመጣጥ ባጭሩ ሲታይ ክርክሩ የተጀመረዉ በደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን ተጠሪ ያቀረበችዉ ክስ ይዘት ባጭሩ ያለተጠሪ ፈቃድ ለጊዜዉ ነዉ በሚል አመልካች በተጠሪ ይዞታ ዉስጥ ገብቶ የቴሌ ሳጥንኮንቴነር በመትከሉ ይዞታየን ለመጠቀም አልቻልኩም በሜል ያጣሁትን ጥቅም ግምት ብር ከፍሎ ሳጥኑን እንዲያነሳ እንዲወስን በማለት ዳኝነት የጠየቀች ሲሆን አመልካች በበኩሉ ፍርድ ቤት ጉዳዩን የመዳኘት ስልጣን የለዉም የሚልና ሌሎች የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሚላቸዉን መከራከሪያዎች አንስቶ በፍሬነገር ረገድም ሳጥኑ የተተከለዉ በከተማ አስተዳደር ተፈቅዶ ስለመሆኑ ገልጾ ክሱ ዉድቅ እንዲደረግ ተከራክሯራል ጉዳን በመጀመሪያ የዳኝነት ስልጣን ያከራከረዉ የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአመልካችን የመጀመሪያ መቃወሚያ ዉድቅ ካደረገ በላ ስለጉዳዩ ከከተማዉ አስተዳደር መግለጫ ጠይቆ ከተማዉ አስተዳደር አመልካች የተጠሪ ይዞታ ዉስጥ ገብቶ ካሜ ተጠቅሞ የቴሌ ሳጥን መትከሉንና በዚህ ይዞታ ላይ እንዲተክል ከተማ አስተዳደሩ አንዳልፈቀደለት ስላላረጋገጠ አመልካች ለተጠቀመዉ ቦታ በአካባቢዉ የሊዝ ዋጋ ለተጠሪ እንዲከፍል ዉሳኔ ሰጥቷልአመልካች በዚህ ዉሳኔ ቅር ተሰኝቶ ለክልሉ ጠፍርድ ቤት ይግባኝ አቅርቦ ፍቤቱም ግራቀኙን ካከራከረ በኋላ አመልካች ለተጠሪ በአዋጅ እና መሰረት ካሳ የመክፈል ግደታ አለበት በሚል ካሳ መጠን ላይ የስር ፍርድ ቤት አጣሪቶ እንዲወስን መልሶለታል ለዚህ ሰበር ችሎት አቤቱታ የቀረበዉ በዚህ ላይ ሲሆን የአመልካች አቤቱታ ይዘት ባጭሩ የዳኝነት ስልጣን አስመልከቶ በስር ፍርድ ቤት የቀረበዉ መቃወሚያ መታለፉ ተገቢ አለመሆነክሱ በይርጋ የሚታገድ ስለመሆኑ እና በፍሬነገር ረገድ አመልካች ክስ ያቀረበችበት ይዞታ ለመሰረተ ልማት ዝርጋታ የተፈቀደ ሆኖ አመልካች ኋላ ላይ በቆርቆሮ አጥር ወደ ይዞታዋ ያስገባች ስለመሆነ የተተከለዉ ሳጥን በከተማ አስተዳደር ተፈቅዶ በቋሚነት የሚቀመጥ እንጂ በጊዜያዊነት አለመሆኑንና ተጠሪ ኮንቴነሩ እንዲነሳ ያቀረቡት ጥያቄ ተገቢነት እንደሌለዉ በመዘርዘር በመጨረሻም ተጠያቂዉ የከተማዉ አስተዳደር መሆን አለበት በሚል የስር ፍርድ ቤት ዉሳኔ አንዲታረም ጠይቋልየአመልካች ሰበር አቤቱታ ተመርምሮ አከራካሪዉ መስመር የተዘረጋዉ ከ ዓመት በፊት መሆኑንና ተጠሪ ይዞታዉን ከዚያ በኋላ አስፋፍተዉ የያዙት ነዉ በማለት አመልካች ያቀረበዉ ክርክር በስር ፍርድ ቤት መታለፉን አግባብነት ለመመርመር ጭብጥ ተይዞ ተጠሪ መልስ እንዲትሰጥ ተደርጓልተጠሪ መጥሪያ ተልኮላት መልስ አላቀረበችምበዚሁ መልስ የማቅረብ መብት ታልፎ መዝገቡ ተመርምሯል መዝገቡን መርምረን እንደተገነዘብነዉ አመልካች ክስ በቀረበበት ይዞታ ላይ ኮንቴነር መትከሉ አልተካደምአመልካች አጥብቆ የሚከራከረዉ በአዋጅ ቁ መሰረት ጉዳዩ መታየት ያለበት በራሱ በአመልካቹ ድርጅት መሆን እንዳለበትና ድርጊቱም የህግ ድጋፍ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ያለዉ ስለመሆኑ ነዉ በመሰረቱ ማንኛዉም የቴሌኮሙንኬሽን ድርጅት የቴሌኮሙንኬሽን መስመር ሲዘረጋ የከተማዉን ፕላን ተከትሎ የመዘርጋት ዛላፊነት እንዳለበት የቴሌኮሙንኬሽን አዋጅ ቁ አንቀጽ በግልጽ ያስገነዝባልከዚህ ባሻገር መስመሩ የባለይዞታን ወይም የሌላ ህንጻ ላይ የሚዘረጋበት አስገዳጅ ሁኔታ ሲኖር አስቀድሞ ለባለይዞታዉ ወይም ለባለህንጻዉ በማስታወቅ የባለይዞታዉ ወይም የባለህንጻዉ ተቃዉሞ እንዳለ ሰምቶ ተገቢዉን የመወሰን ስልጣን ለኤጀንሲዉ የተሰጠ ስለመሆኑ በአዋጁ አንቀጽ በዝርዝር ተመልክቷል በተያዘዉ ጉዳይ አመልካች በተጠሪ ይዞታ ዉስጥ ገብቶ ኮንቴነር መትከሉና ይዞታዉ የተጠሪ ህጋዊ ይዞታ ስለመሆኑ ደግሞ የከተማዉ አስተዳደር ያረጋገጠ ስለመሆኑ በስር ፍርድ ቤት የተረጋገጠ ፍሬነገር ነዉ ። ስለሆነም አመልካች ኮንቴነር ከተከለ በኋላ ተጠሪ ቦታዉን አስፋፍተዉ በመያዝ ወደ ይዞታዋ አስገብታለች የሚለዉ ነጥብ የፍሬነገር ክርክር በስር ፍርድ ቤት ያልተነሳና በማስረጃ ያልተረጋገጠ ፍሬነገር በመሆኑ በዚህ ረገድ የቀረበዉ ክርክር ተገቢነት ያለዉ ሆኖ አላገኘንም አመልካች በአዋጁ መሰረት ጉዳዩ በኤጄንሲዉ በኩል አንዲታይ ለማድረግም አስቀድሞ ለተጠሪ የሰጠዉ ማስታወቂያ ስለመኖሩ ካለማስረዳቱም በተጨማሪ ጊዜያዊ ነዉ እያለ ተጠሪ እንዲጠባበቁ ያደረገ ስለመሆኑ በስር ፍቤት ክርክር የተቀረበበት ነዉ በመሆኑም አመልካች በተጠሪ ይዞታ ላይ የተከለዉ ኮንቴነር በቋሚነት የሚቀጥል እስከሆነ ድረስ በአዋጁ አንቀጽ መሰረት ተገቢዉን ካሳ ለተጠሪ የመክፈል ግዴታ አለበት ስለዚህም የአማራ ክልል ጠፍቤት በስር ፍርድ ቤት የተረጋገጠዉን ፍሬነገር መሰረት በማድረግ አመልካች ለተጠቀመበት የተጠሪ ይዞታ ተገቢዉን ካሳ እንዲከፍል ዉሳኔ መስጠቱና የካሳዉ መጠን ተጣርቶ እንዲወሰን ለስር ፍርድ ቤት መመለሱ በአዋጅ ቁ አንቀጽ እና አዋጅ ቁ አንቀጽ መሰረት ተገቢ ሆኖ ስላገኘን ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ዉሳኔዉ መሰረታዊ ህግ ስህተት የተፈጸመበት ነዉ የሚባልበት ምክንያት አላገኘንምበዚህ አግባብ ተከታዩን ዉሳኔ ሰጥተናል ዉሳኔ ኛየአማራ ብክጠፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመቁ በ ዓም የሰጠዉ ፍርድ በፍብስስህግ ቁ መሰረት ጸንቷል ኛበዚህ መዝገብ ላይ በጥር ቀን ዓም ተሰጥቶ የነበረዉ እግድ ትአዛዝ ተነስቷልይጻፍ መዝገቡ ተዘግቷልይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ሰጌ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የፍትሐብሔር ሥነሥርዓት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ የካቲት ቀን ዓም ዳኞች ዳሜመላኩ ተፈሪ ገብሩ ዶር ቀነዓ ቂጣታ ተሾመ ሽፈራዉ ፀሐይ መንክር አመልካች አቶ መሀመድ ከማል ቀርበዋል ተጠሪ አቶ በቀለ ወልዴ ከጠበቃ አቶ ምስጋኑ ሙለታ ጋር ቀርበዋል ይህ መዝገብ የተቀጠረዉ ለምርመራ ሲሆን ተመርምሮ የሚከተለዉ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ይህ የሰበር ጉዳይ በሌለሁበት የተሰጠ ፍርድ እንዲነሳልኝ የሚል አቤቱታ መነሻ ያደረገ ክርክር ሲሆን ለዚህ ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ የአሁን አመልካች የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመቁ በ ዓም የሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ እንዲታረምልኝ በማለት ያቀረበዉን አቤቱታ መርምሮ ለመወሰን ነዉ የጉዳዩ መነሻ ሲታይ በሆሳዕና ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት የአሁን ተጠሪ ከሳሽየአሁን አመልካች ደግሞ ኛ ተከሳሽበዚህ ችሎት የክርክሩ ተካፋይ ያልሆኑት ወሮ ዘምዘም ኑሪ ኛ ተከሳሽ ሁኖ ሲከራከሩ ነበር ከሳሽ ባቀረበዉ ክስ ታህሳስ ቀን ዓም የተደረገዉ የድርጀት ሽያጭ ዉል እንዲፈጸምልኝ በማለት በጠየቀዉ ዳኝነት ኛ ተከሳሽ ጉዳዩ በሌለበት እንዲታይ ተደርጎ ኛ ተከሳሽ እንደዉሉ ቢፈጸም አልቃወምም በማለታቸዉ ፍቤቱ ጉዳዩን በመመርመር በመቁ በ ዓም በሰጠዉ ዉሳኔ በ ካሜ ቦታ ላይ ያረፈዉ የዱቄት ፋብሪካ ከነመገልገያ ማሽኖቹ ጭምር ታህሳስ ቀን ዓም በተደረገ የሽያጭ ዉል መሰረት ለከሳሽ አንዲፈጸም በማለት ወስኗል ይህን ዉሳኔ ተከትሎ ኛ ተከሳሽ የአሁን አመልካች ባቀረበዉ አቤቱታ የፍቤቱ መጥሪያ እንዲደርሰኝ ተገቢ ጥረት አልተደረገም መጥሪያ አልደረሰኝም ክርክሩን ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ስላልሰማሁት ተከሳሽ በሌለሁበት በጋራ ንብረት ላይ የተሰጠዉ ዉሳኔ በፍብሥሥሕቁ መሰረት እንዲነሳልኝ በማለት አመልክቷል በዚህ አቤቱታ ላይ ከሳሽ ባቀረበዉ መልስ ተከሳሽ በቀበሌ በኩል መጥሪያ ተልኮለት በቀበሌዉ እንደሌለ አረጋግጦ ጽፏል በአዲስ ዘመን ጋዜጣም ጥሪ ተደርጎለታል የፍቤቱ መጥሪያ ለኛ ተከሳሽ ሚስት ለሆነችዉ ለኛ ተከሳሽ ደርሷት ቀርበ ስለተከራከረች መጥሪያ ለእርሱም እንደደረሰ ይቆጠራል ተከሳሽ በፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ከሳሽ ላይ ላቀረበዉ ክስ ከመልስ ጋር የሆሳዕና ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት የሰጠዉ ዉሳኔ በማያያዝ ግንቦታ ቀን ዓም ስለተሰጠ ተከሳሽ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ዉሳኔዉን ያወቀ ስለሆነ አቤቱታ ያቀረበዉ በ ዓም ስለሆነ ዉሳኔዉን ካወቀ ከ ወር በኋላ ስለሆነ አቤቱታዉ ተቀባይነት የለዉም በማለት ተከራክሯል የሥር የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ጉዳዩን በመመርመር በሰጠዉ ብይን ኛ ተከሳሽ መጥሪያ በቀበሌ በኩል ቢላክለትም በቀበሌዉ እንደማይኖር ቀበሌዉ ደብዳቤ ጽፏል በጋዜጣም ጥሪ ተደርጎለት አልቀረበም በዚህ ጉዳይ የተከሳሽ ባለቤት የሆነችዉ ወሮ ዘምዘም ኑሪ ቀርባ ስለተከራከረች ተከሳሽም ክርክሩን እንደሰማ የሕግ ግምት ያስወስዳል ተከሳሽ ክርክሩን የሰማሁበት በፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ከመልስ ጋር በቀረበዉ የሰነድ ማስረጃ ነዉ የሚባል ከሆነ ግንቦት ቀን ዓም አዉቋል ስለሚያስብል ኛ ተከሳሽ በፍብሥሥሕቁ መሰረት አቤቱታዉን ያቀረበዉ ሰኔ ቀን ዓም ስለሆነ ይህ ደግሞ ከሁለት ወር በላይ ስለሆነ አቤቱታዉ በፍብሥሥሕቁ መሰረት በአንድ ወር ይርጋ የሚታገድ ነዉ በማለት ዉድቅ በማድረግ ወስኗል የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍቤት እና የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የቀረበላቸዉን ቅሬታ ዉድቅ በማድረግ የሥር ዉሳኔ በማጽናት ወስኗል የአሁን የሰበር አቤቱታ የቀረበዉ በዚህ ዉሳኔ ቅር በመሰኘት ለማስለወጥ ነዉ የአሁን አመልካች የካቲት ቀን ዓም በተጻፈ አቤቱታ አመልካች በፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ላይ በነበረን ክርክር በሌለሁበት ዉሳኔ መሰጠቱን ያወቅኩት ግንቦት ቀን ዓም ሳይሆን ግንቦት ቀን ዓም ትዕዛዙ በደረሰኝ ጊዜ ነዉ እኔ በሌለሁበት ዉሳኔ መሰጠቱን እንዳወቅኩኝ ሰኔ ቀን ዓም በሌለሁበት የተሰጠዉ ዉሳኔ እንዲነሳልኝ ለሆሳዕና ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት አቤቱታ ያቀረብኩኝ ቢሆንም የፍቤቱ ሰራተኞች እስከ ሰኔ ቀን ዓም ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በስብሰባ ላይ የነበሩ በመሆነ በዚህ ምክንያት ሊዘገይ መቻሉን እየተከራከርኩኝ የሥር ፍቤቶች ይህን ሳይቀበሉ መወሰናቸዉ ተገቢ አይደለም አመልካች በባለቤቱ በኩል ክርክር አንዳለ ያዉቃል ለተባለዉ ከባለቤቴ ጋር ተጣልቼ የነበረ እና ባለቤቴ ይህን ድርጅት አሳግዳዉ የነበረ ሲሆን ከተጠሪ ጋር በመመሳጠር እግድ እንዲነሳ በማድረግ ስም ዝዉዉር እንዲደረግ አድርጓል የሥር ፍቤቶች አመልካች ክርክር እንዳለ ያዉቃል በማለት የጠቀሱት በማስረጃ ባልተረጋገጠ ጉዳይ በመሆኑየሥር ዉሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ እንዲሻርልኝ በሌለሁበት የተሰጠዉ ዉሳኔ ተነስቶ ተገቢ መከራከሪያ አቅርቤ ዉሳኔ እንዲሰጥ በማለት አመልክቷል የሰበር አጣሪ ችሎት ጉዳዩን በማየት አመልካች ከሚስቱ ጋር በጋብቻ ፍቺ ክርክር ጋር ባለበት ሚስቱ መጥሪያዉ ደርሷታል ጉዳዩን ታዉቃለች በመሆኑም አመልካችም ጉዳዩን ያዉቃል ተብሎ ግምት ተወስዶ በፍብሥሥሕቁ መሰረት የቀረበዉን የአመልካች ጥያቄ ዉድቅ የመደረጉን አግባብነት ለመመርመር ሲባል አቤቱታዉ ያስቀርባል በማለት ተጠሪ መልስ እንዲሰጥ ባዘዘዉ መሰረት በ ዓም የተጻፈ መልስ አቅርቧል የመልሱም ይዘት በአጭሩ በዚህ ጉዳይ የሥር ፍቤቶች የሰጡት ዉሳኔ የሕግ ስህተት ያልተፈጸመበት ስለሆነ አመልካች ያቀረበዉ በማስረጃ ያልተረጋገጠ እና አዲስ የፍሬ ነገር ክርክር ተቀባይነት የሌለዉ ስለሆነ ዉድቅ ሆኖ የሥር ዉሳኔ አእንዲጸናልኝ ወጪና ኪሳራ እንዲወሰንልኝ በማለት በዝርዝር ተከራክሯል የአሁን አመልካች የመልስ መልስ አቅርቧል የጉዳዩ አመጣጥ ከላይ የተመለከተዉ ሲሆን ይህ ችሎት የግራ ቀኛቸዉን ክርክር አግባብነት ካላቸዉ የሕግ ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ እንዲሁም አቤቱታዉ ያስቀርባል ሲባል ከተያዘዉ ጭብጥ አንጻር እንደሚከተለዉ መርምሮታል የሥር ፍቤት የአሁን አመልካች መጥሪያ ሳይደርሰኝ በሌለሁበት የተሰጠዉ ዉሳኔ እንዲነሳልኝ በማለት ያቀረበዉን አቤቱታ ዉድቅ ያደረገዉ በቀበሌዉ እንደሌለ ተረጋግጧል በጋዜጣ ጥሪ ተደርጎለት አልቀረበም በሚስቱ ቀርባ ስለተከራከረች ክርክሩን እንደሰማ በሕግ ግምት ይወሰዳል ዉሳኔዉን ካወቀዉ ከአንድ ወር በላይ ስለሆነ አቤቱታዉ ተቀባይነት የለዉም በሚሉት ምክንያቶች መሆኑን የሥር ዉሳኔ ግልባጭ ያሳያል እንደሚታወቀዉ ስለመጥሪያ አደራረስ ሥርዓት በተመለከተ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ አንቀጽ ድንጋጌዎች ሥር ተመልክቷል ከአነዚህ ድንጋጌዎች ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አቀራረጽና ይዘት መገንዘብ እንደሚቻለዉ የመጥሪያ አደራረስ ሂደት በቅድም ተከተል አራት ደረጃዎች እንዳሉት የሚያሳይ መሆኑን ነዉ እነዚህም አንደኛ መጥሪያዉን ለተከሳሹ ለራሱ ማድረስ የፍብሥሥሕቁ ሁለተኛ መጥሪያዉን ለተከሳሹ ሊሰጥ ይችላል ተብሎ ለሚገመት ሰዉ ማድረስ አንቀጽ ሶስተኛ በፖስታ በኩል ለተከሳሽ እንዲደርሰዉ በማድረግ አንቀጽ አራተኛ በምትክ የመጥሪያ አደራረስ ዘዴን በመጠቀም ለተከሳሹ እንዲደርሰዉ ማድረግ እንደሚቻል አንቀጽ ያሳያል ስለሆነም የመጥሪያ አደራረስ ዘዴዉ ወይም ሥርዓት በዚህ ቅደም ተከተል ካልተፈጸመ ለተከሳሹ መጥሪያዉ በሕጉ አግባብ ደርሶታል ለማለት የሚያስችል አይደለም በዚህ አግባብ አሁን ወደ ተያዘዉ ጉዳይ ስንመለስ የሥር የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ለአመልካች መጥሪያ እንዲደርሰዉ የወሰደዉን እርምጃ ማየቱ አስፈላጊ ነዉ የአሁን አመልካች ቀድም ሲል ሲኖርበት የነበረዉን ቀበሌ ዉስጥ እንደማይኖር የተረጋገጠ በመሆኑ እና ከተጠሪ ጋር በፌዴራል ፍቤት ክርክር ላይ እንደነበሩ የሚታወቅ ስለሆነ የሥር ፍቤት ተጠሪ የፍቤቱን መጥሪያ ለአመልካች በአድራሻዉ እንዲደርሰዉ ተገቢዉን ጥረት እንዲያደርግ ማድረግ ነበረበት ፍቤቱ የመጀመሪያ ደረጃ የመጥሪያ አደራረስ ዘዴ በአግባቡ ሳይፈጸም አራተኛ ደረጃ የመጥሪያ አደራረስ ዘዴ ማለትም ምትክ የመጥሪያ አደራረስ ዘዴ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግለት ማድረጉን የሥር ዉሳኔ ግልባጭ ያመለክታል ይህ ደግሞ የሥር ፍቤት የፍብሥሥሕቁ በሚደነግገዉ መሰረት የአሁን አመልካች ክርክሩን አዉቀዉ ቀርበዉ መከራከሪያዉን እንዲያቀርብ ተጠሪ መጥሪያዉን ለአመልካች ለራሱ እንዲያደርስ ተገቢዉን ጥረት እንዲያደርግ ማድረግ ሲገባዉ ይህ ሳይደረግ በጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግለት ማድረጉ ከላይ የተመለከቱትን የሥነሥርዓት ሕጎችን የተከተለ ሆኖ አልተገኘም ስለሆነም የፍቤቱ መጥሪያ ለአመልካች እንዲደርሰዉ ተገቢዉ ጥረት ሳይደረግ በጋዜጣ ጥሪ መደረጉ በሕግ የተመለከተዉን የመጥሪያ አደራረስ ዘዴን ያልተከተለ መሆኑን ያስገነዝባል በመሆኑም የፍቤቱ መጥሪያ በሕጉ አግባብ ለአመልካች ደርሶታል ክርክሩን አዉቆታል የሚያስብል አይደለም በሌላ በኩል የሥር ፍቤት በሰጠዉ ዉሳኔ የአሁን አመልካች ሚስት የነበረችዉ የሥር ኛ ተከሳሽ ወሮ ዘምዘም ኑሪ በዋናዉ ጉዳይ ቀርባ እስከተከራከረች ድረስ አመልካች ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ክርክሩን እንዳወቀ የሕግ ግምት ያስወስዳል የሚል ድምዳሜ ላይ በመድረስ የአመልካችን አቤቱታ ዉድቅ አደርጓታል ከፍ ሲል እንደተጠቀሰዉ በዚህ ጉዳይ አመልካች እና ወሮ ዘምዘም ኑሪ ሁለቱም ተከሳሾች የነበሩ ስለሆኑ የፍብሥሥሕቁ መሰረት ለእያንዳንዳቸዉ መጥሪያ እንዲደርሳቸዉ መደረግ እንዳለበት ይደነግጋል የሥር ፍቤት በዚህ አግባብ ትዕዛዝ በመስጠት የሥር ኛ ተከሳሽ ወሮ ዘምዘም ኑሪ ለአመልካች የተላከዉን መጥሪያ ፈርማ መቀበሏን የሥር ዉሳኔ የሚያመለክተዉ ነገር የለም የሥር ፍቤት በሰጠዉ ዉሳኔ ለአሁን አመልካች የተላከዉን መጥሪያ ለወሮ ዘምዘም ስለመሰጠቱ ሳያረጋግጥ ወሮ ዘምዘም ራሳቸዉ ተከሳሽ ስለነበሩ መጥሪያ ደርሷቸዉ ቀርበዉ ስለተከራከሩ አመልካችም ክርክሩን እንደሚያዉቅ የሕግ ግምት እንደሚያስወስድ በመግልጽ መወሰኑ የዉሳኔዉ ግልባጭ ያሳያል በፍብሥሥሕቁ ሥር እንደተመለከተዉ የፍቤት መጥሪያ የተላከለትን ተከሳሽ ማግኘት ያልተቻለ ወይም መጥሪያ ተቀባይ የሚሆን ወኪል የሌለዉ እንደሆነ ከተከሳሹ ጋር አብሮት ከሚኖረዉ አካላ መጠን ከደረሰ ቤተሰቡ ላንዱ መስጠት እንደሚቻል ያመለክታል በዚህ ረገድ የተያዘዉ ጉዳይ ሲታይ የሥር ፍቤት የሥር ኛ ተከሳሽ የነበሩት ወሮ ዘምዘም ኑሪ ለአመልካች የተላከዉን መጥሪያ ፈርሞ ስለመቀበላቸዉ ያረጋገጠዉ ነገር ካለመኖሩም በላይ በወቅቱ የአሁን አመልካች ከሚስቱ ጋር በፍቤት የፍቺ ክርክር እንደነበራቸዉ እና በግንኙነታቸዉ መካከል ችግር እንዳጋጠመዉ መገንዘብ ተችሏል ይህ ከሆነ ደግሞ በአመልካች እና በሚስቱ መካከል በነበረዉ የፍቺ ክርክር ላይ ዉሳኔ ባይሰጥም የፍቺ ክርክር በመኖሩ በመካከላቸዉ ሰላማዊ ግንኙነት ይኖራቸዋል ተብሎ አይገመትም በመሆኑም በዚህ ሁኔታ ወሮ ዘምዘም ኑሪ የፍቤቱን መጥሪያ ለአመልካች በአግባቡ ያደርሳሉ ተብሎ የሕግ ግምት ለመዉሰድ የሚያስደፍር አይደለም የሥር ፍቤት ይህን ሁኔታ በመገንዘብ ተጠሪ የፍቤቱን መጥሪያ ለአመልካች ለማድረስ ተገቢዉን ጥረት እንዲያደርግ ማድረግ ሲገባዉ ይህን ሳያደርግ ለሚስቱ መጥሪያ ደርሷት ቀርበ ስለተከራከረች ለአመልካችም መጥሪያ እንደደረሰ ግምት በመዉሰድ አመልካች ያቀረበዉን አቤቱታ ዉድቅ ማድረጉ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ነዉ ብለናል በመጨረሻም የሥር ፍቤት የአመልካች በሌለሁበት የተሰጠዉ ዉሳኔ እንዲነሳልኝ በማለት ያቀረበዉን አቤቱታ ዉድቅ ያደረገበት ምክንያት በፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በነበረዉ ክርክር ተጠሪ ከተሰጠዉ መልስ ጋር በቀረበ የሰነድ ማስረጃ ነዉ ያወቅኩኝ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሚል ከሆነ በዛ ክርክር መልስ የተሰጠዉ ግንቦት ቀን ዓም ስለሆነ አመልካች አቤቱታዉን የቀረበዉ ሰኔ ቀን ዓም በመሆኑ የአንድ ወር ጊዜ አልፎበታል በማለት ነዉ የአሁን አመልካች ባቀረበዉ ክርክር አርሱ በሌለበት ዉሳኔ መሰጠቱን ግንቦት ቀን ዓም እንዳላወቀ እና ግንቦት ቀን ዓም በችሎት ጸሐፊ በኩል ትዕዛዝ ሲደርሰዉ እንዳወቀ በዚህ መነሻነትም ለሥር ፍቤት በጊዜ አቤቱታዉን እንዳቀረበ በመግልጽ እየተከራከረ ይገኛል በዚህ ረገድ ተጠሪ በቀረበዉ ክርክር አመልካች ግንቦት ቀን ዓም ችሎት ቀርበዉ የመከላከያ መልስና የሰነድ ማስረጃ ተቀብሎ ዉሳኔ መሰጠቱን አዉቋል የሚል ሳይሆን አመልካች የዉሳኔ ግልባጭ መጠበቅ ሳያስፈልገዉ ማወቅ ይችል ነበር የሜል ነዉ የሥር ፍቤት አመልካች ግንቦት ቀን ዓም እርሱ በሌለበት ዉሳኔ መሰጠቱን ያወቀ መሆኑን የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት መዝገብ በማስቀረብ ወይም በሌላ አግባብ በማጣራት ያረጋገጠ ነገር መኖሩን የሥር ዉሳኔ አያመለክትም ከሥር ፍቤት ዉሳኔ ግልባጭ እና ከግራ ቀኛቸዉ ክርክር መገንዘብ አንደሜቻለዉ የአሁን አመልካች ግንቦት ቀን ዓም በፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በችሎት ቀርበዉ ተጠሪ ያቀረበዉን የመከላከያ መልስና የሰነድ ማስረጃ በመቀበል አርሱ በሌለበት ዉሳኔ መሰጠቱን ግንቦት ቀን ዓም አዉቆታል ለማለት የሚያስችል ነገር የለም የሥር ፍቤት በእርግጠኝነት የአሁን አመልካች ግንቦት ቀን ዓም አርሱ በሌለበት ዉሳኔ መሰጠቱን ማወቁን አግባብነት ባለዉ ማስረጃ ባላረጋገጠበት አርሱ በሌለበት ዉሳኔ መሰጠቱን በግምት በዚህ ቀን መሰጠቱን አዉቆታል አመልካች በአንድ ወር ጊዜ ዉስጥ አቤቱታዉን ስላላቀረበ ዉድቅ ነዉ በማለት የደረሰበት ድምዳሜ የፍብሥሥሕቁ ዓላማ የሚቃረን ስለሆነ ተቀባይነት የለዉም በመሆኑም የሥር ፍቤት የአሁን አመልካች በሕግ አግባብ መጥሪያ የደረሰዉ መሆኑን አና አርሱ በሌለበት ዉሳኔ መሰጠቱን በእርግጠኝነት ያወቀበት ቀን እስካልተረጋገጠ ድረስ የመከላከያ መልስና ክርክር በማቅረብ የመሰማትና ፍትሕ የማግኘት መብት ሕገ መንግስታዊ መብት ስለሆነ አሳማኝና በቂ ባልሆነ ምክንያት ሊነፈግ አይገባም በዚህ ረገድ በኢፌዴሪሕገ መንግስት አንቀጽ ፍትሕ የማግኘት መብት ሕገ መንግስታዊ መብት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል ሲጠቃለል የሥር ፍቤቶች የአሁን አመልካች በሕግ አግባብ መጥሪያ የደረሰዉ እና አርሱ በሌለበት ዉሳጌ መሰጠቱን ማወቁን አግባብነት ባለዉ ማስረጃ ባላረጋገጡበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አመልካች በሌለሁበት የተሰጠዉ ፍርድ ተነስቶ የመከላከያ መልስ እንዳቀርብ በማለት የቀረበዉን አቤቱታ በአንድ ወር ጊዜ ዉስጥ አልቀረበም በሚል ምክንያት ዉድቅ በማድረግ የሰጡት ዉሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ የሚከተለዉ ተወስኗል ዉሳኔ የሆሳዕና ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁ በዓ ዓም የሰጠዉ ዉሳኔ እና ይህን ዉሳኔ በማጽናት የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በመቁ በ ዓም የሰጠዉ ትዕዛዝ አና የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ሰሚችሉሎት በመቁ በ ዓም የሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመባቸዉ ስለሆነ በፍብሥሥሕቁ መሰረት ተሽሯል የአሁን አመልካች በሕግ አግባብ መጥሪያ የደረሰዉ እና አርሱ በሌለበት ዉሳኔ መሰጠቱን ያዉቅ እንደነበር ባልተረጋገጠበት በሌለሁበት የተሰጠዉ ዉሳኔ አእንዲነሳልኝ በማለት ያቀረበዉ አቤቱታ በአንድ ወር ጊዜ ዉስጥ አልቀረበም በማለት ዉድቅ ማድረጉ በሕግ አግባብ ሆኖ ስላልተገኘየመከላከያ መልስ የመቅረብ የመከራከርና ፍትሕ የማግኘት መብቱ ሊነፈግ ስለማይገባ የሆሳዕና ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁ በ ዓም አመልካች በሌለበት የሰጠዉ ዉሳኔ በፍብሥሥሕቁ መሰረት ሊነሳ ይገባል ብለናል የሆሳዕና ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት የዘጋዉን መዝገብ በማንቀሳቀስ የአሁን ተጠሪ የቀረበዉ ክስና ማስረጃ ለአመልካች እንዲደርሰዉ በማድረግ አመልካች የመከላከያ መልስ እንዲያቀርብ በማድረግ በሕጉ አግባብ ተከራካሪ ወገኖቹን በማከራከርና በማጣራት ተገቢ ነዉ ያለዉን ዉሳኔ አንዲሰጥበት በፍብሥሥሕቁ መሰረት ተመልሶለታል የዚህ ዉሳኔ ግልባጭ ለሥር ፍቤቶች ይድረስ ብለናል ግራና ቀኛቸዉ በዚህ ችሉት የደረሰባቸዉን ወጪና ኪሳራ የየራሳቸዉን ይቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ግንቦት ቀን ዓም ዳኞችዳሜ መላኩ ተኽሊት ይመሰል ተፈሪ ገብሩ ዶር ቀነዓ ቂጣታ አብዬ ካሳሁን አመልካች አቶ መስፍን ዘርዓብሩክ ጠበቃ ዘበነ ፍቅሬ ቀረቡ ተጠሪ ወሮ የወርቅዉፃ አለማየሁ ወሮ ኤልሳቤጥ ጥላሁን አቶ አሰግድ ጥላሁን ጠበቃ ያሬድ ዘርይሁን ቀረቡ ወሮ አደይ አፈወርቅ ወት ሜሮን አፈወርቅ አቶ ዳንኤል ተቀባ አልቀረቡም ወሮ ኤልሳቤጥ ለማ አልቀረቡም አቶ ሩዶለፍ ጆርዳኖ አልቀረቡም ወሮ መዓዛ ዘዉዴ አልቀረቡም የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስትያን ጠበቃ በሬሳ በየነ ቀረቡ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ለክርክሩ መነሻ የሆነው ጉዳይ የተጀመረው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነበር በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአሁኑ አመልካች ከሳሽከኛ እስከ ኛ ተጠሪዎች ተከሳሾች እንዲሁም ኛ ተጠሪ ጣልቃ ገብ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል በዚህ መዝገብ የተያዘው ጉዳይ የቤት ሽያጭ ዉል ፈርሶ ቤት ለመረከብ የቀረበ የዳኝነት ጥያቄን የሚመለከት ነው አመልካች ለከፍተኛ ፍርድ ቤት ያቀረቡት ክስ ይዘት በአጭሩ በአዲስ አበባ ከተማ በአሁነ አጠራር ቄርቆስ ክፍለ ከተማ ቀበሌ ውስጥ የሚገኝ በካርታ ቁጥር ር ተመዝግቦ የሚገኝ በ ካሬ ሜትር ይዞታ ላይ የተገነባ ቁጥሩ የሆነ ቤት ግንቦት ቀን ዓም በተደረገ የሽያጭ ውል አቶ ጥላሁን ልዑልሰገድ ከተባሉት አሁን በህይወት ከሌሉት ከኛ ተጠሪ ባለቤት ከኛ እስከ ኛ ያሉ ተጠሪዎች አውራሽ በብር አራት መቶ ሺህ ብር መግዛታቸውንከገዙም በኋላ ከፍተኛ ገንዘብ በማውጣት ማሻሻያ ማድረጋቸውንስመዛፃብቱ ወደ ገዥው ሳይዞር አመልካች በኢትዮኤርትራ ግጭት ምክንያት ከአገር ውስጥ መውጣታቸውንይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ሟች ጥላሁን ልዑልሰገድ በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ክስ አቅርበው የካቲት ቀን ዓም በተሰጠ ውሳኔ ከአመልካች ጋር አድርገውት የነበረው የሽያጭ ውል እንዲፈርስ በማስወሰንና ካርታ እንደጠፋባቸው በማስመሰል አዲስ ካርታ አውጥተው ሰኔ ቀን ዓም ለኛው ተጠሪ በሽያጭ በብር አራት መቶ ፃምሳ ሺህ ብር ማስተላለፋቸውንከዚህ በኋላ ኛው ተጠሪ ባለቤታቸው ከሆኑት ኛ ተጠሪ ጋር ሆነው ነሐሴ ቀን ዓም በተፃፈ የሽያጭ ውል ለኛና ኛ ተጠሪዎች በብር አምስት ሚሊዮን አንድ መቶ ሺህ ብር በሽያጭ ያስተላለፉት መሆኑን ጠቅሰው ከዚህ ሁሉ በኋላ አመልካች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በመዝገብ ቁጥር ከሟች ጥላሁን ልዑልሰገድ ጋር በመከራከር ግንቦት ቀን ዓም የተደረገው ውል ሊፈርስ አይገባም ተብሎ ነሐሴ ቀን ዓም የተወሰነ በመሆኑ ሟች ጥላሁን ልዑልሰገድ ሰኔ ቀን ዓም ከኛ ተጠሪ ጋር ያደረጉት የሸያጭ ውል እንዲሁም ኛው ተጠሪ ከባለቤታቸው ኛ ተጠሪ ጋር በመሆን ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ለኛና ኛ ተጠሪዎች ነሐሴ ቀን ዓም ያረጉት የቤት ሽያጭ ውል ፈርሶ ኛና ኛ ተጠሪዎች አከራካሪውን ቤት ለአመልካች እንዲያስረክቡአመልካች ከቤቱ ያገኙ የነበረውን ጥቅም ወደፊት አስልተው የመጠየቅ መብታቸው እንዲጠበቅላቸውና የክርክሩ ወጭና ኪሳራ እንዲታሰብላቸው ዳኝነት በመጠየቅ ያቀረቡት ክስ ነው ከኛ እስከ ኛ ያሉት ተጠሪዎች ጥር ቀን ዓም በተፃፈ መልስ አመልካች ቤት ልረከብ በማለት ክስ ያቀረቡ ቢሆንም በአከራካሪው ቤት መብት ያላቸው ለመሆኑ የሚያሳይ ማስረጃ አላቀረቡምህገ ወጥና ለህሊና ተቃራኒ የሆነ ውል ለማስፈረስ የሚቀርብ ክስ በሁለት ዓመት ይርጋ ቀሪ ነውአመልካች አከራካሪውን ቤት ከአገር ውስጥ ሲወጡ በአደራ የሰጡት ሰው ካለ መክሰስ እየተገባቸው ተጠሪዎችን መክሰሳቸው ተገቢ አይደለም በማለት በመቃወሚነት ጠቅሰው በፍሬ ጉዳዩም ላይ ግንቦት ቀን ዓም የተደረገው ውል በአዋዋይ ፊት የተደረገ አለመሆኑን አመልካች አቤቱታ አቅርበው ውሉ ሊፈርስ አይገባም ቢባልም ይግባኝ ማቅረባቸውን ገልፀው አመልካች ካሳ ከሚጠይቁ በስተቀር ውሉን አስመልክቶ የሚያቀርቡት ክርክር ተቀባይነት እንደሌለው መልስ አቅርበዋል በሌላ በኩል ኛ ተጠሪ ሰኔ ቀን ዓም በተፃፈ መልስኛ ተጠሪ ነሐሴ ቀን ዓም በተጻፈ መልስ እንዲሁም ኛና ኛ ተጠሪዎች ጥር ቀን ዓም በተጻፈ መልሳቸውን ያቀረቡ ሲሆን የሁሉም መልስ በይዘት ደረጃ ተመሳሳይነት ያለው ሆኖ አከራካሪውን ቤት ህጉን ተከትለው እና ተገቢውን ጥንቃቄ አድርገው የገዙ መሆናቸውን ገልፀው ቤቱም ወደ ሌላ ወገን ተላልፎ እንደሚገኝ በመጥቀስ ክሱ ውድቅ እንዲሆንላቸው ያቀረቡት ነበር የአሁን ኛ ተጠሪ ከኛና ኛ ተጠሪዎች ቤቱ የተላለፈላቸው መሆኑን ጠቅሰው ወደ ክርክሩ ጣልቃ ገብተው ግንቦት ቀን ዓም የተፃፈ መልሳቸውን አቅርበው ተከራክረዋል ጉዳዩ በመጀመሪያ ደረጃ የቀረበለት የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረቡ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚዎችን ጥቅምት ቀን ዓም በብይን ውድቅ በማድረግ አልፎ በዋናው ጉዳይ የግራቀኙን ተከራካሪዎች ክርክርና ማስረጃ አግባብነት ካላቸው ህጎች ጋር አገናዝቦ በመመርመር በመዝገብ ቁጥር ሰኔ ቀን ዓም በዋለው ችሎት አመልካች ከሟች ጥላሁን ልዑልሰገድ ጋር ያደረጉት የቤት ግዥ ዉል ሶስተኛዉ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ወገን በሆኑት ከኛ እስከ ኛ ባሉት ተጠሪዎች ላይ መቃወሚያ ሊሆን የሚችለዉ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር መሠረት በመዝገብ ተመዝግቦ ሲገኝ ብቻ ስለመሆኑና በዚሁ ረገድ ሦስተኛ ወገን ገዥዎች ተገቢዉን ማጣራትና ጥንቃቄ አድርገዉ ቤቱን ከባለሀብት የገዙ ስለሆነ በቅን ልቦና የተደረገ ዉል ከመሆኑ አኳያ ኛ ተጠሪ ከሟች ጋር ያደረጉት ውልም ሆነ ኛና ኛ ተጠሪዎች ከኛና ሃኛ ተጠሪዎች ጋር ያደረጉት የቤት ሽያጭ ዉል ሊፈርስ አይገባም በማለት ወስኗል አመልካች በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አቅርበው ሲከራካሩ የቆዩ ሲሆን ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ይግባኝ የተባለበትን ፍርድ ለማስለወጥ የሚያስችል በቂ እና አሳማኝ የህግም ሆነ የፍሬ ነገር ምክንያት አልተገኘም ሲል የከፍተኛ ፍርድ ቤቱን ውሳኔ አፅንቶታል ይህ የሰበር አቤቱታ የቀረበው ጉዳዩን የተመለከቱት ፍርድ ቤቶች የፈፀሙትን መሠረታዊ ህግ ስህተት ለማሳረም ነው አመልካች በሥር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ ላይ ተፈፅሟል ያሉትን መሠረታዊ የህግ ስህተት በመዘርዘር አቤቱታቸው አቅርበዋል በሰበር አጣሪው ችሎት ትዕዛዝ መሠረት የሥር ፍርድ ቤቶችን ውሳኔ አግባብነት ለማጣራት ተጠሪዎች ቀርበው መልሳቸውን እንዲያቀርቡ ተደርጓል አመልካችም የመልስ መልስ አቅርበዋል ክርክሩ በዚህ አግባብ ተጠናቋል እኛም መዝገቡን መርምረናል እንደመረመርነውም አመልካች በመሠረታዊነት የሚከራካሩት ከኛ ተጠሪ ባለቤት እንዲሁም ከኛ እስከ ኛ ተጠሪዎች አውራሽ ከሆኑት አቶ ጥላሁን ልዑልሰገድ ጋር ባደረግነው የቤት ሽያጭ ውል የገዛሁትን ቤት ሟች አቶ ጥላሁን ልዑልሰገድ ከኛ ተጠሪ ጋር ያደረጉት የሽያጭ ውል እንዲሁም ኛ ተጠሪ ከባለቤታቸው ኛ ተጠሪ ጋር ሆነው ከኛና ኛ ተጠሪዎች ጋር ያደረጉት የቤት ሽያጭ ውል ፈርሶ ቤቱን እንዲያስክቡኝ ይወሰንልኝ የሚል ነው ከመዝገብ ምርመራው መገንዘብ እንደተቻለው አከራካሪውን ቤት አመልካች ለመግዛት ሟች ጥላሁን ልዑልሰገድ ለመሽጥ ግንቦት ቀን ዓም ስምምነት አድርገው ነበር ከቪዚህ ስምምነት በኋላ ሟች ጥላሁን ልዑልሰገድ በመዝገብ ቁጥር ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በፌዴራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ክስ አቅርበው የካቲት ቀን ዓም በተሰጠ ውሳኔ ግንቦት ቀን ዓም የተደረገው የሽያጭ ውሉ ስምምነት አንዲፈርስ አስወስነዋል ከዚህ ውሳኔ በኋላ አዲስ ካርታ አውጥተው ሰኔ ቀን ዓም ለኛው ተጠሪ በሽያጭ በብር ማስተላለፋቸውም ተረጋግጧል ኛው ተጠሪ ባለቤታቸው ከሆኑት ኛ ተጠሪ ጋር ሆነው ነሐሴ ቀን ዓም በተፃፈ የሽያጭ ውል ለኛና ኛ ተጠሪዎች በብር በሽያጭ ማስተላለፉቸውም ግልፅ ነው አመልካች ይህ ሁሉ ከተከናወነ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በመዝገብ ቁጥር ከሟች ጥላሁን ልዑልሰገድ ጋር በመከራከር ግንቦት ቀን ዓም የተደረገው የቤት ሽያጭ ውል ሊፈርስ አይገባም ተብሎ ነሐሴ ቀን ዓም አስወስነዋል በመሆኑም ሊነሳ የሚገባው ጥያቄ አመልካች ከሟች ጥላሁን ልዑልሰገድ ጋር ያደረጉት የሽያጭ ውል ሊፈርስ እንደማይገባ ነሐሴ ቀን ዓም የተሰጠው ውሳኔ የሽያጭ ውሉ ፈርሷል የሚል ተፈፃሚነት ያለው ውሳኔ በነበረበት ጊዜ ማለትም በ ዓም እና በ ዓም በቤቱ ላይ የተደረጉ የሽያጭ ውሎች ላይ የሚያስከትለው የህግ ውጤት ምንድን ነው። የሚል ነው በመሆኑም ተጠሪ ኑዛዜ ፀድቆአል በማለት ያቀረቡት መቃወሚያ የሕግ ድጋፍ ያለው አይደለም በአመልካች የእናት ድርሻ እንካፈል በሚል ለቀረበው የዳኝነት ጥያቄ በመከሪከሪያነት ያቀረቡት የክርክሩንና የሟች አቶ በየነ ተማሪያም ነዛዜ የሚተረጎምበትን አግባብ መሰረት ያላደረገ በመሆኑ አመልካች ከእናታቸው ሊያገኙት የሚገባው የሐብት ድርሻ በተመለከተ የሥረ ነገር ክርክር ቀድሞ ታይቶአል ሊባል የሚችልበት የሕግ አግባብ የለም እንዲሁም አመልካች ኑዛዜው ከፀደቀ በኋላ በቀረበው ክፍፍል ውስጥ ከአናታቸው በውርስ ሊያገኙት ከሚገባው ድርሻ ተገቢውን ያላገኙ መሆኑን ገልጸው የሚከራከሩ በመሆኑ ይህም ፍሬ ነገሩ ተጣርቶ ከሚለይ በስተቀር ኑዛዜው ፀድቆአል በሚል ምክንያት ብቻ ከወዲሁ ውድቅ ሊሆን የሚችልበት የስነ ስርዓት ሕግ አግባብ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የለም ሲጠቃለልም በእነዚህ ሁሉ ምክንያቶች የበታች ፍርድ ቤቶች አመልካች ከተጠሪ ጋር ሊካፈሉ ስለሚገባው የእናታቸው የውርስ ንብረት ላይ ያቀረቡትን ክርክር ውድቅ ማድረጋቸው የክርክሩን ይዘትና በፍብሥሥሕቁጥር ድንጋጌ ስር የተመለከቱትን መመዘኛዎችን ያላሟላ በመሆኑ አቤቱታ የቀረበበት የውሳኔ ክፍል መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ሁኖ አግኝተናል በዚህም መሰረት ተከታዩን ወሰነናል ሠአ ውሳኔ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመቁጥር በ ዓም ተሰጥቶ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁጥር በ ዓም የጸናው ውሳኔ በፍብሥሥሕቁ መሰረት ተሻሽሎአል አመልካች የእናታቸውን ድርሻ በተመለከተ ያቀረቡት የክፍፍል ጥያቄ ውድቅ የተደረገው ያላግባብ ነው ብለናል የፌዴራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመልካች የሟች ወሮ የሺ ብሩን የውርስ ሃብት በተመለከተ ያቀረቡትን ክርክር በፍርድ ሐተታው ላይ በተመለከተው አግባብ ተመልክቶና በሚገባ አጣርቶ ተገቢውን ዳኝነት እንዲሰጥበት ጉዳዩን በፍብሥሥሕቁጥር መሰረት መልሰን ልከንለታል ይጻፍ በዚህ ችሎት ለተደረገው ክርክር መጪና ኪሣራ ግራ ቀኝ ወገኖች የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ቀን ዳኞች ተኽሊት ይመሰል ተፈሪ ገብሩ ዕር ቀነዓ ቂጣታ ተሾመ ሽፈራዉ አብዬ ካሳሁን አመልካቾች አቶ ቡልቻ ቱሉ ቀርበዋል ወሮ ወርቄ አብዲሳ ቀርበዋል ተጠሪ አቶ ተመስገን ሙላቱ አልቀረበም መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ጉዳዩ የተጀመረዉ በኦሮሚያ ብክልላዊ መንግስት መስተዳደር በጉቶ ጊዳ ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን ኛ አመልካች በፍሥሥህጉ አንቀጽ መሠረት ያቀረቡትን የመቃወም አቤቱታ መሠረት ያደረገ ነዉ ኛ ተጠሪ ያቀረቡት መቃወሚያ ይዘትም በአጭሩ በኡኬ ከተማ ቀበሌ የሚገኘዉን እና አዋሳኞቹ በአቤቱታዉ ላይ የተመለከቱትን ቤት እና ይዞታ በተመለከተ የወረዳዉ ፍርድ ቤት በመቁ የሰጠዉ ዉሳኔ መብታቸዉን የሚነካ መሆኑን ጠቅሰዉ ወደ ክርክሩ ገብተዉ ተከራክረዉ እንዲወሰንላቸዉ መጠየቃቸዉን የሚያሳይ ነዉ የወረዳዉ ፍርድ ቤትም በዚህ መልኩ በቀረበዉ አቤቱታ መነሻነት የግራ ቀኝ ክርክር ከሰማ በኋላ ቀደም ሲል ሰጥቶ የነበረዉን ዉሳኔ በመሻር ለክርክሩ መነሻ የሆነዉ ቤት እና ይዞታ አመልካቾች በጋራ የሰሩት ነዉ በማለት ወስኗል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ተጠሪ ይህን ዉሳኔ ባለመቀበል ለምሥወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያቀረቡ ሲሆን ይግባኝ ሰሚዉ ፍርድ ቤት የይግባኝ መዝገቡን አስቀርቦ የግራ ቀኝ ክርክር ከሰማ በላ በወረዳዉ ፍርድ ቤት የተሰጠዉን ዉሳኔ በማጽናት ወስኗል ተጠሪ ይህ ዉሳኔ መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት መሆኑን ጠቅሶ ለኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አቤቱታዉን ያቀረበ ሲሆን ሰበር ሰሚዉ ችሉት በበኩሉ ተጠሪዎች ባልና ሚስት መሆናቸዉን እና ኛ ተጠሪ ጉዳዩ መብቴን ይነካል የሚትል ከሆነ ክርክርሩ በሂደት ላይ በነበረበት ወቅት ጣልቃ ገብታ መከራከር እየቻለች ይህን ሳታደርግ ቀርታ ዉሳኔ ከተሰጠ በኋላ ያቀረበችዉን የመቃወም አቤቱታ በመቀበል የወረዳዉ እና የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የሰጡት ዉሳኔ መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነዉ በማለት ሽራል ይህ የሰበር አቤቱታ የቀረበዉም ይህኑን ዉሳኔ በመቀበል ለማስለወጥ ሲሆን አመልካቾች በቀን ዓም ተዘጋጅቶ በጠበቃቸዉ አማካይነት በቀረበ ገጽ የሰበር አቤቱታ በኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የተሰጠዉ ዉሳኔ መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነዉ የሚሉባቸዉን ምክንያቶች በመዘርዘር ታርሞ ይወሰንላቸዉ ዘንድ ዳኝነት ጠይቀዋል አቤቱታዉ ተመርምሮ ያስቀርባል በመባሉም ተጠሪ በተደረገለት ጥሪ መሠረት ቀርቦ ግራ ቀኝ ክርክራቸዉን በጽሑፍ ተለዋዉጠዋል የጉዳዩ አመጣጥ በአጭሩ ከላይ የተገለጸዉ ሲሆን ይህ ችሎትም ለአቤቱታዉ ምክንያት የሆነዉን ዉሳጌፄ ከግራ ቀኝ ክርክር አና ለጉዳዩ አግባብነት ካላቸዉ ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ መዝገቡን እንደሚከተለዉ መርምሮታል ከፍ ሲል እንደተመለከተዉ ኛ አመልካች ለወረዳዉ ፍርድ ቤት ላቀረቡት የመቃወም አቤቱታ መሠረት ያደረገችዉ የወረዳዉ ፍርድ ቤት በኛ አመልካች እአና በተጠሪ መካከል የተደረገዉን ክርክር መሠረት በማድረግ በመቁ በቀን ዓም በዋለዉ ችሎት የሰጠዉ ዉሳኔ መብቴን ይነካል በማለት ነዉ የክርክሩ መነሻ ተጠሪ በኛ አመልካች ላይ ያቀረበዉ ክስ ሲሆንተሰጥቶ የነበረዉ ዉሳኔም ኛ አመልካች ቤትና ቦታዉን ለተጠሪ ይልቀቅ የሚል ስለመሆኑ ከግራ ቀኝ ክርክር መገንዘብ ይቻላል ይሁንና ኛ አመልካች ይህን ዉሳኔ ባለመቀበል ለምሥወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያቀረበዉ ይግባኝ ተቀባይነት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ባለማግኘቱ ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ያቀረበ ሲሆንይግባኝ ሰሚዉ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም በዋለዉ ችሎት በወረዳዉ እና በከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የተሰጡትን ዉሳጌዎች በመሻር መወሰኑን ተመልክተናል አመልካቾች በዚህ ችሎት ባቀረቡት የሰበር አቤቱታ አጥብቀዉ ከሚከራከሩባቸዉ ነጥቦች ዉስጥ አንዱ ለመቃወም አቤቱታዉ ምክንያት የሆነዉ ዉሳኔ መሻሩን ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሉት አቅርበን እያለ ችሎቱ ይህን ሳያጣራ ዉሳኔ መስጠቱን ሲሆን ተጠሪም በጽሑፍ በሰጠዉ መልስ ቀደም ሲል በስር ፍርድ ቤት ተሰጥቶ የነበረዉ ዉሳኔ በይግባኝ መሻሩን በተመለከተ ክዶ ካለመከራከሩም በላይ ይህ ችሎትም የዉሳኔዉን ግልባጭ አስቀርቦ ተመልክቶታል በሌላ በኩል አንድ ሰዉ ዉሳኔ ከተሰጠ በሏላ የመቃወም አቤቱታ መቅረብ የሚችለዉ መብቱን የሚነካ ዉሳኔ ሲኖር ብቻ ስለመሆኑ በፍሥሥርዓት ህግ አንቀጽ ስር በግልጽ ተመልክቷል ይህም ማለት የመቃወም አመልካች አቤቱታ ተቀባይነት ያለዉ መሆን አለመሆኑን በመወሰን ረገድ ፍርድ ቤቶች ግምት ዉስጥ እንዲያስገቡ ከሚጠበቅባቸዉ ሁኔታዎች ዉስጥ አንዱ የመቃወም አመልካችን መብት የሚነካ ዉሳኔ መኖር አለመኖሩን ነዉ የተያዘዉን ጉዳይ በተመለከተ ኛ አመልካች ለክርክሩ መነሻ የሆነዉን የመቃወም አቤቱታ ለወረዳዉ ፍርድ ቤት አቅርባ ጉዳዩ በክርክር ባለበት ወቅት ለመቃወም አቤቱታዉ ምክንያት የሆነዉ ዉሳኔ በኛ አመልካች ይግባኝ ባይነት በዞን አና በጠቅላይ ፍርድ ቤት በሄደት ላይ የነበረ መሆኑን ነዉ ጉዳዩ በከፍተኛ ወይም በጠቅላይ ፍርድ ቤት በይግባኝ በሂደት ላይ እያለ በጎን ለወረዳዉ ፍርድ ቤት የቀረበዉ የመቃወም አቤቱታ ከመነሻዉም ተቀባይነት ያለዉ አይደለም ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ ለዚህ ሰበር አቤቱታ ምክንያት የሆነዉ ጉዳይ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከመቅረቡ በፊት ለመቃወም አቤቱታዉ ምክንያት የሆነዉ ዉሳኔ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ተሽሯል አመልካቾች ይህን ለሰበር ሰሚዉ ችሎት ገልፀዉ መከራከራቸዉን ከክርክሩ መገንዘብ ተችሏል በመሆኑም የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የኛ አመልካችን መብት ነክቷል ተብሎ ለመቃወም አቤቱታዉ ምክንያት የሆነዉ ዉሳኔ የተሻረ መሆን አለመሆኑን ማጣራት ነበረበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በበኩላችን እንደተመለከትንዉ ኛ አመልካች ላቀረቡት የመቃወም አቤቱታ ምክንያት የሆነዉ ዉሳኔ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተሽሯል በመሆኑም ለመቃወም አቤቱታ ምክንያት የሚሆን ዉሳኔ የለም የተሻረን ዉሳኔ መነሻ በማድረግ የሚቀርብ የመቃወም አቤቱታ አይኖርም ስለሆነም የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ለመቃወም አቤቱታዉ ምክንያት የሆነዉ ዉሳኔ መሻሩን እና የኛ አመልካቸን መብት ሊጎዳ የሚችል ዉሳኔ አለመኖሩን አረጋግጦ የቀረበን የሰበር አቤቱታ ባለመቀበል እንዲሁም ይህኑን መሠረት በማድረግ በስር ፍርድ ቤቶች የተሰጡትን ዉሳኔዎች በመሻር መወሰን ሲገባዉ ይህን ባለማድረግ የኛ አመልካች የመቃወም አቤቱታ አቀራረብ ስነ ስርዓታዊ አይደለም በሚል መንፈስ የሰጠዉ ዉሳኔ መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ ተገኝቷል በመሆኑም ተከታዩ ተወስኗል ቅሀ ዉሳኔ የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም በዋለዉ ችሎት የሰጠዉ ዉሳኔ እንዲሁም የጉቶ ጊዳ ወረዳ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም በዋለዉ ችሎት እና የምስወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም በዋለዉ ችሎት የሰጡት ዉሳኔ በፍሥሥህጉ አንቀጽ መሠረት ተሽራል ኛ አመልካች መብቴን ይነካል በሚል የመቃወም አቤቱታ ያቀረቡበት ዉሳኔ በሌላ አግባብ ስለተሻረ እና መብቷን ሊነካ የሚችል ዉሳኔ ስለሌለ የኛ አመልካች የመቃወም አቤቱታ ተቀባይነት የለዉም የሰበር አጣሪ ችሎት በቀን ዓም የሰጠዉ የዕግድ ትዕዛዝ ተነስቷል በዚህ ችሎት የተደረገዉ ክርክር ያስከተለዉን ወጪ እና ኪሳራ ግራ ቀኝ የየራሳቸዉን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ተዘግቷልወደ መዝገብ ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ቀን ዳኞች ዳ መላኩ ተኽሊት ይመሰል ተፈሪ ገብሩ ዶር ቀነዓ ቂጣታ ተሾመ ሽፈራዉ አመልካች ናይል ትራንዚት ኃየተየግማህበር ተጠሪዎች ኒያላ ኢንሹራንስ ኩባኒያ አጉል ትራንዚት አቶ ኑሩ ኡመር መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ጉዳዩ የኢንሹራንስ ዉልን መሠረት በማድረግ በመድን ሰጪዉ የተከፈለን የጉዳት ካሳ መድን ሰጪዉ በመድን ገቢዉ ተተክቶ በተጠየቀ የመዳረግ መብት ጋር በተያያዘ የቀረበን ክርክር መሠረት በማድረግ የስር የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የስር ኛ ጣልቃ ገብ የነበሩት አቶ ኪዳኔ ታረቀኝ እና የአሁን ኛ ተጠሪ በክርክሩ ጣልቃ ሊገቡ አይገባም በማለት የሰጠዉ ዉሳኔ መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነዉ በማለት አመልካች ያቀረበዉ አቤቱታ ነዉ አመልካች በቀን ዓም ተዘጋጅቶ ባቀረበዉ የሰበር አቤቱታ ስር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ኛ እና ኛ ተጠሪዎች ወደ ክርክሩ እንዲገቡ ትዕዛዝ ከሰጠ በኋላ አመልካች ከፈለገ ከእነርሱ ላይ ክስ መስርቶ ካሳ መጠየቅ ይችላል በሚል ከክሱ እንዲሰናበቱ መወሰኑ መሠረታዊ የህግ ስህተት ነዉ የሚል ነዉ አቤቱታዉ ተመርምሮ ያስቀርባል በመባሉም ተጠሪዎች በየበኩላቸዉ በጽሑፍ በሰጡት መልስ የስር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዉሳኔ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት አይደለም የሚሉባቸዉንም ምክንያቶች ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በመዘርዘር መልስ ሰጥተዋል አመልካች ያቀረበዉ የመልስ መልስም ከመዝገቡ ጋር ተያይዛል የጉዳዩ አመጣጥ በአጭሩ ከላይ የተመለከተዉ ሲሆን እኛም የስር ፍርድ ቤት በዚህ ረገድ የሰጠዉን ብይን አግባብነት እንደሚከተለዉ መርምረናል ከክርክሩ ሂደት መገንዘብ የተቻለዉ የአሁን ኛ ተጠሪ በአመልካች ላይ በስር ፍርድ ቤት ባቀረበዉ ክስ አመልካች ከደንበኛዉ ጋር ባደረገዉ የዕፅቃ አስተላላፊነት ዉል መሠረት የሚጠበቅበትን ግዴታ ባለመወጣቱ ለደንበኛዉ የከፈለዉ የጉዳት ካሳ እንዲተካለት ሲሆን አመልካች በበኩሉ የተለያዩ የመጀመሪያ እና የፍሬ ነገር ክርክሮችን ካቀረበ በኋላ የማጓጓዝ ስራዉ የተከናወነዉ በስር ኛ ጣገብ በነበረዉ አቶ ኪዳኔ ታረቀኝ በክርክሩ ጣልቃ እንዲገባ የጠየቀ ሲሆን አቶ ኪዳኔ ታረቀኝም በክርክሩ ጣልቃ ገብቶ በመግባት በሰጠዉ መልስ ያሁን ኛ ተጠሪ መኪና በጭነቱ ቦታ የነበረ መሆኑን ጠቅሶ በክርክሩ ጣልቃ እንዲገባ በማለት መጠየቁን ነዉ የስር ፍርድ ቤት የስር ኛ ጣልቃ ገብ አቶ ኪዳኔ ታረቀኝ እንዲሁም የአሁን ኛ እና ኛ ተጠሪዎች በክርክሩ ጣልቃ እንዲገቡ በማድረግ ክርክር ከሰማ በላ ኛ ተጠሪ እና የስር ኛ ጣልቃ ገብ ከክርክሩ እንዲወጡ ብይን መስጠቱን ተገንዝበናል በመሠረቱ በሌሎች ሰዎች መካከል በመካፄድ ላይ ባለዉ ክርክር ጣልቃ መግባት ስለሚቻልበት ሁኔታ የፍሥሥርዓት ህጋችን ከአንቀጽ ባሉት ድንጋጌዎች የተመለከቱ ሲሆን ክርክሩን በመስማት ላይ ያለዉ ፍርድ ቤትም ሌላ ሦስተኛ ወገን በክርክሩ ጣልቃ እንዲገባ ትዕዛዝ ከመስጠቱ በፊት ሊገባ የሚገባ መሆን አለመሆኑን በመወሰን ረገድ በድንጋጌዎቹ ስር የተመለከቱትን ሁኔታዎች ግምት ዉስጥ የማስገባት ግዴታ የሚጠበቅበት ሲሆን ይህን የሚያደርገዉም ኛዉ ወገን ጣልቃ እንዲገባ ትዕዛዝ ከመስጠቱ በፊት ስለመሆኑ ከየድንጋጌዎቹ አጠቃላይ ይዘት መገንዘብ የሚቻል ነዉ ይህ መርህ እንደተጠበቀ ሆኖ ኛ ወገን ጣልቃ እንዲገባ ትዕዛዝ ከሰጠ በኋላ ጣልቃ ለመግባት የሚያስችል ህጋዊ ምክንያት አለመኖሩን ፍርድ ቤቱ ካመነበት ክርክሩ በየትኛዉም ደረጃ ላይ ቢሆን ጣልቃ ገቡ ከክርክሩ ዉጪ እንዲሆን ትዕዛዝ ከመስጠት የሚከለክለዉ ነገር የለም በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ተጠሪዎች በክርክሩ ጣልቃ እንዲገቡ ትዕዛዝ ከሰጠ በኋላ ወደ ኋላ ተመልሶ ከክርክሩ ዉጪ እንዲሆኑ ትዕዛዝ መስጠቱ ኢ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ስነስርዓታዊ ነዉ በማለት አመልካች እያቀረበ ያለዉ ቅሬታ ተቀባይነት ያለዉ አይደለም ወደ ክርክሩ እንዲገባ የተደረገዉ ኛ ተጠሪ በክርክሩ እንዳይቀጥል አለመደረጉ በአግባቡ ነዉ ወይስ አይደለም የሚለዉን ጭብጥ ስንመለከት የስር ኛ ጣልቃገብ አቶ ኪዳኔ ታረቀኝ ኛ ተጠሪ በክርክሩ ጣልቃ እንዲገባ ሲጠይቅ በምክንያትነት የጠቀሰዉ ጉዳት የደረሰበትን ማሽነሪ የጫነዉ የኛ ተጠሪ መኪና መሆኑን ነዉ ከፍ ሲል እንደተገለጸዉ በሌሎች ሰዎች መካከል በመካፄድ ላይ ባለዉ ክርክር ጣልቃ መግባት ስለሚቻልበት ሁኔታ የፍሥሥርዓት ህጉ አንቀጽ ይደነግጋል የተያዘዉን ጉዳይ በተመለከተ የስር ኛ ጣልቃ ገብ ያሁን ኛ ተጠሪ በክርክሩ ጣልቃ እንዲገባ ሲጠይቅ በህጉ አንቀጽ መሠረት ኛ ተጠሪ ከእርሱ ጋር በድርሻ ካሳዉን ለመክፈል የሚገደድበትን የዉል ወይም የህግ ምክንያት ስለመኖሩ አልገለጸም አሊያም በአመልካች እና በተጠሪ መካከል ሲደረግ በነበረዉ ክርክር መሠረት ፍትሐዊ ዉሳኔ ለመስጠት የተጠሪዎች በክርክሩ ጣልቃ መግባት በፍትሥሥርዓት ህጉ አንቀጽ መሠረት የግድ መሆኑን የሚያሳይ የህግ ምክንያት አልቀረበም ከዚህ አንፃር ሲታይ ተጠሪዎችን ከክርክሩ ዉጪ በማድረግ በስር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተሰጥቶ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በትዕዛዝ የፀናዉ ብይን በዚህ ችሎት ሊታረም የሚችል መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ ባለመገኘቱ ተከታዩ ተወስኗል ዉሳኔ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም በዋለዉ ችሎት የሰጠዉ ብይን እንዲሁም የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁ በቀን ዓም በዋለዉ ችሎት የሰጠዉ ትዕዛዝ በፍሥሥርዓት ህጉ አንቀጽ ፀንቷል በዚህ ችሎት በቀን ዓም የተሰጠዉ የእግድ ትዕዛዝ ተነስቷል በዚህ ችሎት የተደረገዉ ክርክር ያስከተለዉን ወጪ እና ኪሳራ ግራ ቀኝ የየራሳቸዉን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ሠአ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰበር መዝገብ ቁጥር መስከረም ቀን ዓም ዳኞች አልማው ወሌ ሙስጠፋ አህመድ አብርፃ መሰለ ፈይሳ ወርቁ ጳውሎስ ኦርሺሶ አመልካች ወሮ ካሰች በቀለ ወሮ ባንቻየሁ በቀለ ቀረቡ ተጠሪ ውቢት ዘውዴ ቀረቡ ትግስት ዘውዴ ወኪል ደሳለኝ ታምራት ቀረቡ ልቡ በቀለቀረበ መዝገቡ ተመርምሮ የሚከተለው ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ጉዳዩ የቀረበው አመልካቾች ከወላጅ አባታቸው ከሟች ቄስ በቀለ ሀወልድ በውርስ ሊያገኙ የሚገባውን ይዞታና ግምታቸው ብር የሚሆኑ ከብቶችን በ ዓም በተደረገ ኑዛዜ መሰረት የነቀሏቸው መሆኑን ጠቅሰው ኑዛዜው ፈርሶ ድርሻቸውን እንዲያካፍሏቸው ይወሰን ዘንድ የአቀረቡትን የዳኝነት ጥያቄ የሱልልታ ወረዳ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር በ ዓም በይርጋ ውድቅ አድርጎ ብይን ሰጥቶ በፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁጥር በ ዓም በውሳኔ የኦሮሚያ ብሔረዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር አጣሪ ችሎት በመዝገብ ቁጥር በዓም በትዕዛዝ ማጽናታቸው ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በማለት አመልካቾች በ ዓም የተፃፈ የሰበር አቤቱታ በማቅረባቸው ነው አመልካቾች በ ዓም ያቀረቡት ክስ መሰረታዊ ይዘቱ ሲታይም የአመልካቾችና የኛ ተጠሪ ወላጅ አባታቸው ሟች ቄስ በቀለ ሀወለድ መሆናቸውን ሟች በሕይወት እያለ በ ዓም ባደረጉት ኑዛዜ አመልካቾችን ከውርስ የነቀሉ መሆኑን ጠቅሰው ኑዛዜው ፈርሶ አመልካቾች ከሟቹ የገጠር መሬት ይዞታና ከብቶች ድርሻቸውን እንዲያገኙ ይወሰን ዘንድ ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው የአሁኑ ኛ አና ኛ ተጠሪዎች ለክሱ በሰጡት መከላከያ መልስም ክሱ በይርጋ የሚታገድ መሆኑን የኑዛዜ ወራሽነታቸውም ቀድሞ በፍርድ ያለቀ በመሆኑ አመልካቾች አዲስ ክስ ማቅረባቸው ተገቢ ያለመሆኑን ጠቅሰው የተከራከሩ ሲሆን ኛ ተጠሪ ግን የአመልካቾችን ክስ ተገቢ መሆኑን በማመን ተከራክረዋል ጉዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ የተመለከተው ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ምስክሮች በመስማትና ለጉዳዩ ተያያዥነት አላቸው ያላቸውን የመቁጥር እና ን አስቀርቦ ከተመለከተ በኋላ ጉዳዩን መርምሮ አመልካቾች ኑዛዜው እንዲፈርስ የጠየቁት ከሶስት አመት በኋላ መሆኑ ተረጋግጧ በማለት ክሱን ውድቅ አድርጓል አመልካቾች በወላጅ አባታቸው ኑዛዜ ከውርስ የነቀለ መሆነን ጠቅሰው ያቀረቡት ክስ በይርጋ የታገደ ነው ተብሎ በተሰጠው የብይን ክፍል ቅር በመሰኘት ይግባኛቸውን ለዞነ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሠበር አቤቱታቸውን ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ቢያቀርቡም ተቀባይነት አላገኙም የአሁነ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም ይህንኑ ብይን በመቃወም ለማስለወጥ ነው የአመልካቾች የሠበር አቤቱታ መሰረታዊ ይዘትም በአባታቸው በ ዓም የተደረገው ኑዛዜ ከውርስ የነቀላቸው መሆኑን ይዞታውንም በስምምነት ተካፍለው ሲጠቀሙ የነበረ ከመሆኑም በላይ ክርክሩም እኩል ደረጃ ላይ በማይገኙ ወራሾች መካከል ሁኖ እያለ የበታች ፍርድ ቤቶች ክሱ በይርጋ የታገደ ነው በማለት ብይን መስጠታቸው ያላግባብ ነው የሜል ነው አቤቱታቸው ተመርምሮም አመልካቾች አከራካሪውን የውርስ ንብረት መጋቢት ቀን ዓም ተደረገ በተባለ ስምምነት ተካፍለው ሲጠቀሙ የነበረ ከመሆኑነ አንጻር ክሱ በይርጋ የታገደ ነው ተብሎ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የመወሰኑን አግባብነት ለመመርመር ተብሎ ጉዳዩ ለዚህ ችሎት እንዲቀርብ የተደረገ ሲሆን ተጠሪዎች በመቅረባቸውም ግራ ቀኙ በፅሑፍ እንዲከራከሩ ተደርጓል የጉዳዩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለመልኩ ከላይ የተገለጸው ሲሆን ይሀ ችሎትም የግራ ቀኙን ክርክርና ለሰበር አቤቱታው መነሻ የሆነውን ብይን አግባብነት ካላቸው ድንጋጌዎች አንጻር እንደሚከተለው መርምሮታል እንደመረመረውም የችሎትን ምላሽ የውርስ ንብረት በስምምነት ክፍፍል ተደርጎበት የነበረ መሆን ያለመሆኑና በተለያዩ መዝገቦች በክርክር ላይ የቆዩት ወገኖች በይርጋው አቆጣጠር ላይ የሚኖረው ሕጋዊ ውጤት ሳይለይ ክሱ በይርጋ የታገደ ነው ተብሎ ብይን መሰጠቱ ተገቢ ነው። በመቁጥር እና ሲካሄዱ በነበሩት ክርክሮች ሲሳተፉ የነበሩ ተከራካሪ ወገኖች እነማን እንደሆኑና በጉዳዮቹ ላይ የተሰጠ የፍርድ ቤት ውሳኔ ይዘቱ ምን እንደሚል እንዲሁም በይርጋው ላይ የሚኖረው ሕጋዊ ውጤት ምን እንደሆነ በመመርመርና በግራ ቀኙ እና አግባብነት ባላቸው ማስረጃዎች ሁሉ እንዲጣሩ ካደረገ በኃላ ኛ እና ኛ ተጠሪዎች ባቀረቡት የይርጋ መቃወሚያ ላይ ተገቢውን ብይን እንዲሰጥ እና ክሱ በይርጋ ቀሪ የሚሆን አይደለም የሚባል ከሆነም በፍሬ ጉዳዩ ረገድ የቀረበለትን ክርክር በአግባቡ አጣርቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት ጉዳዩ ለሱልልታ ወረዳ ፍርድ ቤት በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር መሰረት መልሰናል ይጻፍ በዚህ ችሎት ለተደረገው ክርክር የወጣውን ጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ ብለናል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ መስከረም ቀን ዓም ዳኞች ብርሃኑ አመነዉ በዕዉቀት በላይ አንዳሻዉ አዳነ ፃይሉ ነጋሽ እትመት አሠፋ አመልካች አቶ መሀመድ በሀዲንአልቀረበም ተጠሪ ዘምዘም አሊአልቀረበም መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ጉዳዩ የይግባኝ ጊዜን የሚመለከት ነው የፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍቤት የአሁን አመልካች ያቀረበው ታሕሳስ ቀን ዓም ላቀረበው የይግባኝ ቅሬታ የይግባኝ ማስፈቀጃ ምክንያት ያቀረበ ቢሆንም የይግባኝ ማስፈቀጃ ምክንያቱ በቂ አይደለም በማለት በፍብሥሥሕቁ መሠረት መዝገቡን ዘግቶታል የሰበር አቤቱታው የቀረበው ይህንኑ ትዕዛዝ በመቃወም ነው የአመልካች የሰበር አቤቱታ መሠረታዊ ይዘትም የፌዴራሉ ከፍተኛ ሸሪዓ ፍቤት በመቁ በቀን ዓም የሰጠውን ውሳኔ በመቃወም አመልካች የይግባኝ ማመልከቻ አቅርቤ ግልባጩ የተሰጠኝ በቀን ዓም በእለተ አርብ ነውአመልካች ቅዳሜ እና እሁድ የመንግሥት ሥራ ዝግ ስለሆነ ታሕሣሥ ቀን ዓም የይግባኝ ቅሬታዬን ለፍቤቱ ያቀረብኩ ቢሆንም ፍቤቱ የይግባኝ ጊዜው አልፏል በማለት የሰጠው ትዕዛዝ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ሥሕተት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል የሚል ነው የአመልካች የሰበር አቤቱታ ተመርምሮ የጠቅላይ ሸሪዓ ፍቤቱ አመልካች ይግባኙን በቀን ዓም ማቅረቡን በገለጸበት ሁኔታ የይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜው አልፏል በማለት የሰጠውን ትዕዛዝ አግባብነት ለመመርመር ሲባል ጉዳዩ በዚህ ችሎት እንዲታይ ተደርጓል ለተጠሪ ጥሪ ተደርጎም ግራቀኙ በጽሑፍ እንዲከራከሩ ተደርጓል የተጠሪ መልስ ይዘት በአጭሩ ይግባኝ የተጠየቀበት ውሳኔ የተሰጠው በቀን ዓም ሲሆን አመልካች ይግባኙን ያቀረበው በቀን ዓም በመሆኑ በራሱ ቸልተኝነት የይግባኝ ጊዜው ያለፈበት መሆኑን የሚያሳይ ነውየይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ የሚቆጠረው ቀኖቹን በተከታታይ በመቁጠር እንጂ ቅዳሜ እና እሁድን በመተው አይደለምአመልካች በበቂ ምክንያት የተደገፈ የይግባኝ ማስፈቀጃ ያላቀረበ በመሆኑ አቤቱታው ውድቅ ሊደረግ ይገባል የሚል ነው የጉዳዩ አመጣጥ በአጭሩ ከላይ የተገለጸው ነው ይህ ችሎትም እንዲጣራ የተያዘውን ነጥብ ከግራቀኙ ክርክርለሰበር አቤቱታው መነሻ ከሆነው ውሳኔ እና ለጉዳዩ አግባብነት ካላቸው ሕጎች ጋር በማገናዘብ እንደሚከተለው መርምሮታል ይግባኝ የተጠየቀበት ውሳኔ የፌዴራሉ ከፍተኛ ሸሪዓ ፍቤት በመቁ በቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ መሆኑ አመልካች ግልባጭ እንዲሰጠው የጠየቀው በቀን ዓም መሆኑንአመልካች የመዝገብ ግልባጭ የተሰጠው በቀን ዓም በአለተ አርብ መሆኑ እና ይግባኙን ያቀረበው በቀን ዓም መሆኑን የድሬዳዋ ፌዴራል ከፍተኛ ሸሪዓ ፍቤት በቀን ዓም የጻፈው መሸኛ ደብዳቤ ያሳያል ከደብዳቤው ይዘት መገንዘብ የሚቻለው ታሕሣሥ ቀን ዓም እና ታሕሣሥ ቀን ዓም የሆኑን ሁለቱ ቀናት በአመልካች ጥፋት ያልባከኑ መሆኑን ነው በመሠረቱ የይግባኝ አቤቱታ አቀራረብ የሚመራው በሥነሥርአት ሕጉ በተዘረጋው ሥርአት መሠረት ነው የፍብሥሥሕቁ ድንጋጌ የመጀመሪያ ደረጃው ፍርድ ቤት በሰጠው ውሳኔብይን ወይም ትእዛዝ ቅር የተሰኘ ተከራካሪ ወገን የይግባኙን አቤቱታ ለይግባኝ ሰሚው ፍቤት ማቅረብ ያለበት ይግባኝ በሚባልበት ጉዳይ ላይ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በተፈረደ በ ቀን ውስጥ መሆኑን ይደነግጋልፎ በዚህ ጊዜ ውስጥ ይግባኙን ያላቀረበ ተከራካሪ ወገን ይግባኙ እንዲከፈት ይግባኝ ማስፈቀጃ ማቅረብ እንዳለበት የዚሁ ሕግ ቁጥር ያስገነዝበናል የይግባኝ ማስፈቀጃ የቀረበለት ፍቤትም በዚሁ ሕግ ቁጥር መሠረት ይግባኝ ጠያቂው ይግባኙን በጊዜው ለማቅረብ ያልቻለበትን ምክንያት በቂ መሆን አለመሆኑን መርምሮ ይግባኙ እንዲከፈት ሊፈቅድ ወይም ሊከለክል እንደሚችል ከድንጋጌው ይዘት መገንዘብ ይቻላል በያዝነው ጉዳይ ይግባኝ አመልካች የፌዴራሉ ከፍተኛ ሸሪዓ ፍቤት በመቁ በቀን ዓም በሰጠው ውሳኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ መጠየቅ ይችል ዘንድ ግልባጭ እንዲሰጠው የጠየቀው የ ቀኑ የይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ ሳያልፍ በቀን ዓም ሲሆን የመዝገብ ግልባጭ የተሰጠው ደግሞ በቀን ዓም በአለተ አርብ በመሆነ ይግባኙ የሚቀርብበት የመጨረሻው ቀን የመንግስት ሥራ ዝግ በሆነበት ቀን ላይ አርፏልአመልካችም በቀጣዩ ቀን ታሕሳስ ቀን ዓም ይግባኙን አቅርቧል የሥር ፍቤት አመልካች ያቀረበው ምክንያት በቂ አይደለም በማለት በፍብሥሥሕቁ መሠረት መዝገቡን የዘጋው ቢሆንም የይግባኝ አቤቱታ ማቅረቢያ ጊዜ ከሆኑት ስልሳ ቀናት ውስጥ ሁለቱ ቀናት በአመልካች ችግር የባከኑ ካለመሆናቸው ባሻገር ይግባኝ የማቅረቢያው የመጨረሻ ቀን የመንግስት ስራ ዝግ በሆነበት ቀን ላይ ያረፈ በመሆኑየፍብሕቁ ግዴታው የሚፈጸምበት ቀን ከአንድ የበአል ቀን ጋር ከገጠመ በዓል ባልሆነበት በማግስቱ ባለው የሥራ ቀን እንደሚተላለፍ በሚደነግገው አግባብ በተመሣሣይ ሁኔታ አመልካችም ጊዜ ሳያባክን በቀጣዩ የሥራ ቀን ይግባኙን አዘጋጅቶ ያቀረበ ከመሆኑ እና ይግባኝ ሕገ መንግስታዊ ዋስትና ያለው መብት ከመሆኑ አኳያ አመልካች ይግባኙ እንዲከፈት ያቀረበው ምክንያት በቂ ነው ተብሎ ይግባኙ እንዲከፈት መፍቀድ ሥነሥርዓታዊ ሆኖ አግኝተነዋል የስር ፍቤትም ጉዳዩን በዚህ አግባብ በማየት ይግባኙ እንዲከፈት መፍቀድ ሲገባው አመልካች ይግባኙ እንዲከፈት ያቀረበው ምክንያት በቂ አይደለም በማለት መዝገቡን መዝጋቱ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ሥሕተት የተፈጸመበት ሆኖ አግኝተነዋል በዚህም ምክንያት ተከታዩን ውሳኔ ሰጥተናል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ፋዘ ውሳኔ የፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት በመቁ ታሕሳስ ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ ውሳኔ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ተሸራል አመልካች ይግባኙ እንዲከፈት ያቀረበው ምክንያት በቂ ምክንያት ስለሆነ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ይግባኙን እንዲያቀርብ ተፈቅዶለታል አመልካች የዚህ ውሳኔ ግልባጭ ከደረሰው ቀን ጀምሮ በሚቆጠር በአሥር ቀን ጊዜ ውስጥ ይግባኙን ያቅርብ ብለናል በዚህ ችሎት ለተደረገው ክርክር የወጣውን ወጪ ግራቀኙ የየራሣቸውን ይቻሉ መዝገቡ ውሳኔ ስላገኘ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ መጋቢት ቀን ዓም ዳኞች ዳ መላኩ ተኽሊት ይመስል ተፈሪ ገብሩ ዶር ቀነአ ቂጣታ ፀሃይ መንክር አመልካች የኢትዮጵያ አየር መንገድ አልቀረቡም ተጠሪዎች ኛ ወሮ መሰረት ፍቃዱ ተወካይ አበበች ዘመድኩን ቀረቡ ኛ ገልፍ አየር መንገድ ጠ ዮዲት ጉርጂ ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ የቀረበው የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እና በይግባኝ የተመለከተው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያሳለፉት ውሳኔ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት በመሆኑ በሰበር ታይቶ ይታረምልኝ በማለት አመልካች ያቀረበውን የሰበር አቤቱታ አጣርቶ ለመወሰን ነው በስር ፍርድ ቤት ኛ ተጠሪ ከሣሽ ሲሆኑ አመልካች እና ኛ ተጠሪ ደግሞተ ከሣሽ በመሆን ተከራክረዋል ኛ ተጠሪ ያቀረቡት ክስ ይዘት በታህሳስ ወር ዓም ከሳውዲ አረቢያ ወደ ኢትዮጵያ በአየር መንገዱ ተሳፍሬ ግምታቸው ብር ሰላሳ ሺህ የሚያወጡ ልብሶች እና ቁሳቁሶች በመያዝ የመጣሁ ሲሆን የመጣው ዕቃ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ ሴክሽን ከሌላ ዕቃ ጋር በመለዋወጡ ጠፍቷል እነሱ ደግሞ ኛ ተጠሪን ጠይቂ እያሉ እያመላለሱኝ ይገኛሉ በመሆኑም ንብረቴ በመጥፋቱ የንብረቱ ግምት ይከፈለኝ በማለት ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው አመልካች ለክሱ በሰጠው መልስ ዕቃውን ሊረከብ የቻለው ከኛ ተጠሪ ጋር ባለው የማመቻቸት ስምምነት መሰረት ነው በዚህ ስምምነት የአመልካች ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ኃላፊነት ዕቃው መጥፋቱን ለኛ ተጠሪ ማሳወቅ ብቻ ነው በዚህም መሰረት አመልካች ለኛ ተጠሪ አሳውቋል ስለሆነም ኃላፊነት የለብኝም በሌላም በኩል የዕቃው ግምት ብር ስለመሆኑ የቀረበ ማስረጃ የለም በማለት ተከራክሯል ኛ ተጠሪ በበኩሉ በሰጠው መልስ ከአመልካች ጋር ባላቸው ስምምነት መሰረት አመልካች የኛ ተጠሪ የካርጎ ወኪል ነው የኛ ተጠሪ ኃላፊነት ፅቃውን የማጓጓዝ ብቻ ነው እንጂ ዕቃዎቹ በአግባቡ መጫናቸውን አና መውረዳቸውን በሚመለከት የአመልካች ኃላፊነት ነው አመልካች ለኛ ተጠሪ ስለጉዳዩ ያሳወቀው ነገር የለም ዕቃው የጠፋው በአመልካች ካርጎ ሴክሽን ውስጥ ከሌላ ፅቃ ጋር በመቀያየሩ ነው ስለሆነም ዕቃው የጠፋው በአግባቡ ከተጓዓጓዘ በኃላ በመሆነ ኛ ተጠሪ ምንም ኃላፊነት የለበትም በማለት ተከራክሯል ክርክሩ በዚህ መልኩ የቀረበለት የስር ፍርድ ቤት ጉዳዩን መርምሮ ለክርክር ምክንያት የሆነው ንብረት የጠፋው በኛ ተጠሪ ጥፋት ሳይሆን በአመልካች ካርጎ ክፍል ዕቃ ተቀያይር መሆኑ የታመነ ፍሬ ነገር በመሆኑ የመካስ ኃላፊነት ያለበት አመልካች ነው ሊከፍል የሚገባውን የገንዘብ መጠን በተመለከተም አመልካች ፅቃው በጠፋ ጊዜ ከሳሽን ያስፈረማቸው ሰነድ ላይ የጠፋው ዕቃ የዋጋ ግምት በማለት ያሰፈሩት የሳውዲ ሪያል ወይም ብር ሃያ ስድስት ሺህ አራት መቶ ፃያ ስድስት በመሆኑ ይህንኑ ገንዘብ ከነወለዱ ሊከፍል ይገባል በማለት ወስኗል በዚህ ውሳኔ ላይ ይግባኙ የቀረበለት የፌከፍተኛ ፍርድ ቤት በበኩሉ የይግባኝ ክርክሩን ከሰማ በኃላ አመልካች ኃላፊ ነው ተብሎ ገንዘቡን እንዲከፍል መወሰኑን የተቀበለው ሲሆን ኛ ተጠሪን በተመለከተ ውል የፈፀመ በመሆነ ገንዘቡን የመክፈል ግዴታ ቢኖርበትም ከሳሽ ባቀረቡት ክስ ላይ ስሙ ከመጠቀሱ ውጪ የዳኝነት ጥያቄ ያልቀረበበት በመሆነ ከፍብሄር ስነ ስርዓት አንፃር በግልፅ ባልተጠየቀ ዳኝነት የካሳ ገንዘቡን ኛ ተጠሪ እንዲከፍል የሚወሰንበት አግባብ የለም የስር ፍርድ ቤት ያሳለፈው ውሳኔ በውጤት ደረጃ ሊፀና ይገባል በማለት ወስኗል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰበር ቅሬታው ለዚህ ፍርድ ቤት የቀረበው በዚህ ነው አመልካች መጋቢት ዓም ባቀረበው የሰበር ማመልከቻ ዕቃው ከሳውዲ አረቢያ ወደ አዲስ አበባ የመጣው በኛ ተጠሪ እና ኛ ተጠሪ መካከል ባለው የማጓጓዝ ውል መሰረት በመሆኑ በዋርሶው ስምምነት አንቀጽ መሰረት አጓኙ ዕቃውን አጓጉዞ መብት ላለው ሰው እስከሚያስረክብ ድረስ ኃላፊነት ያለበት ስለመሆኑ የሚደነግግ በመሆኑ አመልካች ዕቃውን ሊረከብ የቻለው ዕቃውን ከኛ ተጠሪ ተረክቦ ኛ ተጠሪን በመወከል ለኛ ተጠሪ ለማስረከብ በገቡት የማመቻቸት ውል ከመሆኑ ወጪ በኛ ተጠሪ እና በአመልካች መካከል የውልም ሆነ የህግ ግንኙነት ባለመኖሩ አመልካች ኃላፊነት አለበት ተብሎ በስር ፍርድ ቤቶች የተሰጠው ውሳኔ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ነው ተብሎ አመልካች ኃላፊነት የለበትም በሚል እንዲወሰን ጠይቋል ጉዳዩ በሰበር አጣሪ ችሎቱ ተመርምሮ ኛ ተጠሪ የንብረቱ አጓዥ ሆኖ እያለ ከኃላፊነት ውጪ የመደረጉን አግባብነት ለመመርመር ሲባል መዝገቡ ለሰበር ችሎት እንዲቀርብ እና ተጠሪዎች መልስ እንዲሰጡበት ተደርጓል ኛ ተጠሪ ሚያዚያ ዓም በተፃፈ መልስ አመልካች የኛ ተጠሪን የንብረት ግምት ከፍሎ ከኛ ተጠሪ ጋር ባላቸው ግንኑነት መሰረት ኛ ተጠሪን ከሶ ከመጠየቅ ውጪ የኛ ተጠሪን ንብረት አልከፍልም በማለት ያቀረበው አቤቱታ የህግ መሰረት የሌለው በመሆኑ ተቀባይነት ሊኖረው አይገባም በማለት ተከራክረዋል ኛ ተጠሪ በበኩሉ ሚያዚያ ዓም በተፃፈ መልስ ፅቃው የጠፋው በአመልካች አየር መንገድ ካርጎ ሴክሽን ክፍል ውስጥ ከሌላ ዕቃ ጋር ተቀያይሮ መሆኑ በአመልካች በራሱም የታመነ በመሆኑ አመልካች በቸልተኝነት ከሌላ እቃ ጋር በማቀያየር እንዲጠፋ ማድረጉ አመልካችን በኃላፊነት ከሚያስጠይቀው ውጪ ከኛ ተጠሪ ጋር ግንኙነት የለውም ኛ ተጠሪ ዕቃውን አላጓጓዘም አንጂ አጓጉዚል ቢባል አንኳ ዕቃው የጠፋው በአግባቡ ከተራገፈ በላ በአመልካች ካርጎ ሴክሽን ክፍል ውስጥ በመሆኑ ኛ ተጠሪ ምንም አይነት ኃላፊነት የለበትም በማለት ተከራክሯል አመልካቹም ክርክሩን በማጠናከር የመልስ መልስ አቅርቧል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ከፍሲል ባጭሩ የገለፅነው የጉዳዩን አመጣጥና በሰበር የተደረገውን ክርክር ሲሆን በበኩላችን ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ኛ ተጠሪ ውል የፈፀመ በመሆኑ ገንዘቡን የመክፈል ግዴታ እንደሚኖርበት ወስኖ ነገር ግን ከሳሽ ባቀረቡት ክስ ላይ ስሙ ከመጠቀሱ ውጪ የዳኝነት ጥያቄ አልቀረበበትም በሚል ገንዘቡን ኛ ተጠሪ እንዲከፍል የሚወሰንበት አግባብ የለም በማለት መወሰኑ ተገቢ መሆን አለመሆኑን መርምረናል ይህን ጭብጥ ለመወሰን የሥር ፍርድ ቤቶች በፍሬ ነገር ደረጃ የተቀበሉትን እና ለጉዳዩ ተፈፃሚነት ያለው የዋርሶ ስምምነት በሞንትሪያል ፕሮቶኮል ቁጥር እንደተሻሻለ ተገቢ ድንጋጌዎችን ይዘትና ትርጉም እንዲሁም የፍብሥሥህግ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ የሚሆንበትን ሁኔታ መርምረናል ከክርክሩ መገንዘብ እንደሚቻለው የሥር ሁለቱም ተከሳሾች ዕቃው ስለመጥፋቱ ያቀረቡት ክርክር የለም ይልቁንም የየበኩላቸውን ክርክር በማቅረብ ኃላፊነት እንደሌለባቸው ተከራክረዋል አመልካች አከራካሪውን ንብረት መረከቡን እና ከአጁ የጠፋ መሆኑን ሳይክድ ኃላፊ ሊሆን የሚገባው ከከሳሽ ጋር የማጓጓዝ ውል ያደረገው ኛ ተጠሪ ሊሆን እንደሚገባና ዕቃውን ሊረከብ የቻለው ከኛ ተጠሪ ጋር ባለው የማመቻቸት ስምምነት መሰረት መሆኑን በመግለጽ ተከራክሯል ነገር ግን አመልካች ንብረቱን የተረከበ መሆኑና የጠፋውም በአመልካች ዕቃ ማስቀመጫ ካርጎ ሴክሽን ውስጥ የመሬት መስተንግዶ ስራ ግዴታውን በሚፈጽምበት ጊዜ ከሌላ ዕቃ ጋር ተቀያይሮ መሆኑ ያልተካደ በመሆኑ በዚህ መልኩ በአመልካች ጥፋት ለጠፋው ንብረት አመልካች ኃላፊ የማይሆንበት የህግ ምክንያት የለም በሌላ በኩል ኛ ተጠሪ ዕቃውን አላጓጓዝኩም እንጂ አጓጉዘሃል ብባል እንኳ ፅቃው የጠፋው በአመልካች እጅ በመሆኑ ኃላፊነት የለብኝም በማለት የተከራከረ ቢሆንም ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ኛ ተጠሪ ዕቃውን በውል በማጓጓዙ ከውል የመነጨ ኃላፊነት እንዳለበት ወስኗል በዚህ ውሳኔ ላይ በኛ ተጠሪ በኩል የቀረበ ቅሬታ የለም ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ኛ ተጠሪ ካሳውን ሊከፍል አይገባም በማለት የወሰነው በቀረበው ክስ በግልጽ ዳኝነት አልጠየቀበትም ከፍብሥሥርዓት ድንጋጌዎች አንጻር በግልጽ ባልተጠየቀ ዳኝነት ኛ ተጠሪ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ካሳውን እንዲከፍል የሚወሰንበት ምክንያት የለም በሚል ነው ይሁን እንጂ የአሁን ኛ ተጠሪ የአሁን አመልካችን እና ኛ ተጠሪን በተከሳሽነት በመሰየም ኃላፊነት ያለበት ወገን ተለይቶ እንዲወሰንላቸው ባቀረቡት ክስ ተጓጉዞ የመጣው ፅቃ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ ሴክሽን ከሌላ ፅቃ ጋር በመለዋወጡ የጠፋ በመሆኑና አመልካችም ኛ ተጠሪን ጠይቂ እያለ እያመላለሳቸው መሆኑን ጠቅሰው የንብረቱ ግምት እንዲከፈላቸው መጠየቃቸውን ከክሱ መረዳት ይቻላል በፍብሥሥህቁ እንደተደነገገው ከሳሽ መብቱን ማግኘት የሚገባው ከየትኛው ተከሳሽ ላይ እንደሆነ ለይቶ ለማወቅ የሚያጠራጥር ሁኔታ ያጋጠመው ሲሆን አንዱን ወይም ከአንድ በላይ የሆኑትን ሰዎች በህብረት በመክሰስ አላፊነቱ የሚመለከተው የትኛው አንደሆነ ተለይቶ እንዲወሰንለት ለማመልከት ይችላል ስለሆነም ኛ ተጠሪ በዚህ አግባብ በሁለቱ ተከሳሾች ላይ ክስ ማቅረባቸው የሚነቀፍ ባለመሆነ ይግባኝ ሰሚው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ኛ ተጠሪ በክሱ ስሙ ከመጠቀሱ ውጪ የዳኝነት ጥያቄ አልቀረበበትም በማለት የደረሰበት መደምደሚያ የቀረበውን የዳኝነት ጥያቄ እና ህጉን የተከተለ ባለመሆኑ ተቀባይነት የለውም በአጠቃላይ ኛ ተጠሪ ባቀረቡት ክስ ኛ ተጠሪን በተከሳሽነት ስሙን ከማስገባት ውጪ በሱ ላይ ዳኝነት ስላልጠየቁ ኛ ተጠሪ ካሳ ሊከፍል አይገባም በማለት የተደረሰበት መደምደሚያ የቀረበውን ክስ እና ከፍሲል የተጠቀሰውን የፍብስስህግ ድንጋጌ መሰረት ያደረገ ባለመሆኑ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነው ብለናል ተከታዩንም ወስነናል ውሣኔ የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመቁ ሀምሌ ቀን ዓም ያሳለፈው ውሳኔ አንዲሁም የፌከፍተኛ ፍርድ ቤት በኮመቁ መጋቢት ዓም የሰጠው ውሳኔ በፍብሥሥህቁ መሰረት ተሻሸሏል በኛ ተጠሪ ላይ ለደረሰው ጉዳት ኛ ተጠሪ ከውል የመነጨ ኃላፊነት ያለበት መሆኑ ተረጋግጦ ከተወሰነ በላ የዳኝነት ጥያቄ አልቀረበበትም ገንዘቡን ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ሊከፍል አይገባም ተብሎ የተሰጠው ውሳኔ የዳኝነት ጥያቄውን እና ህጉን የተከተለ ባለመሆኑ ተሽሯል አመልካች ኃላፊነት ያለበት ስለመሆኑ የተሰጠው ውሳኔ ፀንቷል አመልካች እና ኛ ተጠሪ ባልተነጣጠለ ኃላፊነት ብር ሃያ ስድስት ሺህ አራት መቶ ፃያ ስድስት ክስ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ከሚታሰብ ወለድ ጋር ለኛ ተጠሪ ሊከፍሉ ይገባል በማለት ወስነናል መጋቢት ዓም በዋለ ችሎት በሥር ፍርድ ቤት በመቁ የተጀመረው አፈፃፀም እንዲታገድ የተሰጠው ትዕዛዝ ተነስቷል ይጻፍ የሰበር ክርክሩ ያስከተለውን ወጭና ኪሣራ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤፍ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ መስከረም ቀን ዓም ዳኞች አልማው ወሌ ሙስጠፋ አህመድ አብርሃ መሰለ ፈይሳ ወርቁ ጳውሎስ አርሺሶ አመልካች ወሮ ፈይዛ ከሚል ጠበቃ ልሣነወርቅ ተኪ ቀረቡ ተጠሪ አቶ አብዲ አህመድ ቀረቡ መዝገቡን መርምረን ቀጥሉ ያለውን ፍርድ ሰጠተናል ፍርድ የክርክሩ ምክንያት የፍቺ ውጤት የሆነው የንብረት ክርክር ነው የአሁኗ አመልካች የካቲት ቀን ዓም ጽፈው ባቀረቡት ክስ ከተጠሪ ጋር የነበራቸው ጋብቻ በ ዓም በተሰጠ የፍቺ ውሳኔ መፍረሱ በትዳር ውስጥ ከሚያዚያ ዓም ጀምሮ ከቤት እስከወጡበት የካቲት ዓም ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ ንስላክከተማ ወረዳ ክልል ውስጥ ባለአንድ ፎቅ ዘመናዊ ቪላ ቤት የቤት ቁጥር አዲስ የሆነ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ ል የሆነና ግምቱ ብር የሚያወጣ ያሪስ መኪና በሀሰን ላውንደሪ ንግድ ቤት ውስጥ በአቶ ሰኢድ ሙዘይን ዳኝነትና በአቶ ኤልያ ሰይድ ጸሓፊነት ብር የእቁብ ገንዘብና የቤት ቁሳቁሶችን ያፈሩ መሆኑን ዘርዝረው ክፍፍሉ እንዲደረግ ይወሰንላቸው ዘንድ ዳኝነት ጠይቀዋል የአሁኑ ተጠሪ መጋቢት ቀን ዓም በተፃፈ መልስ ዳኝነት የተጠየቀበት ቤት የተሰራው በ ዓም ሆኖ አመልካችና ተጠሪ ደግሞ በሸሪዓ ህግ መሰረት የተጋቡት ጥር ቀን ዓም በመሆኑ ንብረቱ የተፈራው ከጋብቻ በፊት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ መሆኑን ቤቱን ለመስራት የሚያሥችላቸው ገቢ ስላልነበራቸውም አባታቸውን በላውንደሪ ስራ ስለሚረዱ ቤቱን ከጋብቻ በፊት ወላጅ አባታቸው አቶ አህመድ መፃመድ ሰርተው የሰጧቸው መሆኑን የእቁብ ገንዘብ በጋብቻ እያሉ ታህሳስ ቀን ዓም ደርሶአቸው ለትዳራቸው ለጋራ ጥቅም ያዋሉት መሆኑን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ቀበሌ ክልል ውስጥ በቤት ቁጥር በአቶ መሃመድ ይማም ዳኝነት በአቶ እንድሪስ አለሙ ጸሐፊነት በአቶ ወንድሜነህ አለሙ ሰብሳቢነት የነበረው እቁብም ለመክፈል ባለመቻላቸውም በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመቁጥር ክስ ቀርቦባቸው ገንዘቡን እንዲከፍሉ ታህሳስ ቀን ዓም ተወስኖባቸው ከወጪ ኪሳራ ጋር ብር እንዲከፍሉ በመገደድ መኪናውን ሽጠው እዳውን ከከፈሉ በኋላ ቀሪውን ገንዘብ ለትዳር ጥቅም ያዋሉ መሆኑን አመልካች ከቤት የወጡት የካቲት ቀን ዓም ሳይሆን ሰኔ ቀን ዓም መሆኑን በአቶ ሀሰን ላውንደሪ በአቶ ሰይድ መዘይን ዳኝነት በአቶ ኤልያስ ሰይድ ጸሐፊነት በሚሰበሰብ እቁብ ውስጥ የሌሉበት መሆኑን እና የቤት ቁሳቁሶችን ቢካፈሉ ተቃውሞ የሌላቸው መሆኑን ዘርዝረው ተከራክረዋል ጉዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ የተመለከተው የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትም ለጉዳዩ አግባብነት አላቸው ያላቸውን ሰባት ጭብጦችን በመመስረት የግራ ቀኙን ምስክሮች ቃል ሰምቶና ጉዳዩን መርምሮ በአመልካችና በተጠሪ መካከል የነበረው ጋብቻ በፍቺ ውሳኔ ሲፈርስ በሚያዚያ ወር ዓም የተደረገ ጋብቻ ፈርሷል የተባለ ቢሆንም ተጠሪው የጋብቻ ሰርተፊኬት ጋብቻው በሐይማኖት ስርዓት ጥር ቀን ዓም ተፈፅሞ በውልና ክብር መዝገብ ሹም አገልግሉት በ ዓም ተመዝግቦ ህጋዊ መረጃ እንደተሰጣቸው የሚያሣይ ማስረጃ ያቀረቡና አመልካችም ይህንን ማስረጃ አልካዱም ወደሚለው ድምዳሜ ደርሶ እና ቀድሞ በፍቺ ጊዜ ጋብቻው የተፈጸመበት ጊዜ ሚያዚያ ወር ዓም ነው ተብሎ የተሰጠውን በፍብሥሥሕቁጥር ስር የሚወድቅ ስህተት ነው በማለት ይህንኑ ስህተት ነው ያለውን ጊዜ አርሞ በአመልካችና በተጠሪ መካከል ጋብቻው የተፈጸመው ጥር ቀን ዓም ነው ቤቱ የተሰራውም ከዚህ በፊት መሆኑ ስለተረጋገጠ የተጠሪ የግል ፃብቱ ነው አመልካች ከቤት የወጣችው ከየካቲት ዓም በፊት ነው በጋብቻ ጊዜ የጋራ አዳ የነበራቸው መሆኑ ተረጋግጧል ኮድ ቁጥር ል መኪና ለጋራ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ እዳ የተሸጠ መሆኑ ስላልተረጋገጠ መኪናው የጋራቸው ነው እቁቡን በተመለከተም የወጣላቸው መሆን ያለመሆኑንና የገንዘብ መጠን ምን ያህል እንደሆነ አመልካች ያላስረዱና ተጠሪ ለግል ጥቅማቸው ያዋሉ መሆኑም ያልተረጋገጠ በመሆኑ አመልካች ያቀረቡት ጥያቄ ተገቢነት የሌለው መሆኑን የቤት ዕቃዎችን በተመለከተ በተጠሪ በታመነው መሰረት እንዲካፈሉ ሲል ወስኗል ከዚህ ውሰኔ ውስጥ በጋብቻ ጊዜ በቤቱና በእቁቡ ላይ በተሰጠው የውሳኔ ክፍል የአሁኗ አመልካች ቅር በመሠኘት ይግባኛቸውን ለፌዴደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርበው ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን ከአከራከረ በኋላ የሥር ፍርድ ቤት በፍብሥሥሕቁጥር መሰረት የጋብቻውን ጊዜ ማረሙ ፍፁም የሥነ ስርዓት ህጉንና መሰረታዊ የዳኘነት አሰራር መርህን ያልተከተለ መሆኑን ከገለጸ በኋላ በውጤት ደረጃ ግን ለጋብቻ መኖር መቅረብ ያለበት የጋብቻ ምስክ ወረቀት በመሆኑ ይኹው ሰነድ መቅረቡ ተገቢ አንደሆነ ዘርዝሮ ጋብቻው የተፈፀመው ጥር ቀን ዓም ተብሎ የተሰጠውን የውሳኔ ክፍልና ከዚሁ ጋር ተያይዞ በቤቱ ላይ ተሰጠውን ውሳኔ ሙሉ በሙሉ አጽንቶታል የአሁኑ የሠበር አቤቱታ የቀረበውም ይህንኑ የበታች ፍርድ ቤቶች ውሳኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው የአመልካች የሰበር አቤቱታ መሠረታዊ ይዘትም የሥር ፍርድ ቤት በአመልካችና በተጠሪ መካከል የነበረውን ጋብቻ እንዲፈርስ ውሳኔ በሰጠበት ጊዜ ጋብቻው በሚያዚያ ወር ዓም መሆኑን በግልጽ አስፍሮ ውሳኔ በሰጠበት እና በዚህ ረገድ የተሰጠው ውሳኔም በይግባኝ ባልተለወጠበት ሁኔታ በንብረት ክርክር ጊዜ ተጠሪ ያቀረቡትን ክርክርና ማስረጃ ተቀብሎ ጋብቻው ጥር ቀን ዓም የተፈጸመ ነው በማለት መወሰኑ ከፍብሥሥሕቁጥር ጋር አብሮ በማይሄድ ምክንያት ከመሆኑም በላይ አመልካችና ተጠሪ ከ ዓም ጀምሮ ግንኙነት ፈጥረው በ ዓም አመልካች አርግዘው በ ዓም ልጅ የወለዱ መሆኑና ቤቱም ተጠሪ በ ዓም በጨረታ ባገኙት ቦታ ላይ በትዳር ውስጥ መሰራት ተጀምሮ ቤቱ ተሰርቶ የተጠናቀቀው በ ዓም መሆኑ ከሚመለከተው አካል ለስር ፍርድ ቤት በተላከው ማስረጃ የተረጋገጠ ሆኖ እያለ ይኹው ማስረጃና በጉዳዩ ላይ የተሰሙት ምስክሮች ቃል በአግባቡ ሳይታይ መታለፉን የአቁብ ገንዘብን በተመለከተ አመልካች የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ፈጽመው ምስክሮችን አላቀረቡም የተባለው አመልካችም መጥሪያውን ለእቁቡ ዳኛና ሰብሳቢ ለማድረስ ጥረት አድርገው ምስክሮቹ አውቀው እየተደበቁ ስላስቸገሩኝ በሚኖሩበት ወረዳ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አስተዳደር በኩል እንዲደርሳቸው በማለት በቃለ መፃላ አቤቱታ አመልካች አቅርበው አያሉ ፍርድ ቤቱ ይህንኑ በማየት ተገቢውን ትዕዛዝ መስጠት ሲገባው ምስክሮቹ በአመልካች ጉድለት እንዳልቀረቡ በመቁጠር ውሳኔ መስጠቱ ያላግባብ ነው የሚሉ ናቸው አቤቱታው ተመርምሮም በዚህ ችሎት እንዲታይ የተደረገ ሲሆን ተጠሪ ቀርበውም ግራ ቀኙ በጽሑፍ እንዲከራከሩ ተደርጎአል እንዲሁም የሥር ፍርድ ቤትና የይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት መዛግብትም እንዲመጡ ተደርጎ የይግባኝ ሠሚው ፍቤት መዝገብ መጥቶ የሥር ፍቤት የመዝገብ ግልባጭ የያዘ መሆኑ ተረጋግጧል የጉዳዩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለመልኩ ከላይ የተገለፀው ሲሆን እኛም የግራ ቀኙን ክርክር ለሰበር አቤቱታው መነሻ ከሆነው ውሳኔ እና አግባብነት ካላቸው ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ ጉዳዩን አንደሚከተለው መርምረናል እንደመረመርነውም የዚህን ችሎት ምላሽ የሚያሥፈልጋቸው አበይት ጭብጦች የሥር ፍርድ ቤት በፍቺ ውሳኔ የለየውን የጋብቻ ጊዜ በንብረት ክርክር ጊዜ በመመልከት በፍብሥሥሃሕቁጥር መሰረት ማረሙ ከዚሁ ጋር ተያይዞ ለክርክሩ ምክንያት የሆነው ቤት የተጠሪ የግሉ ነው በማለት የወሰነበት አግባብና እቁቡን በተመለከተ የተሰጠው ዳኝነት ተገቢ መሆን ያለመሆኑን የሚመለከቱ ናቸው በዚህም መሰረት እያንዳንዳቸውን ነጥቦች በሚከተለው መልኩ ተመልክተናል የመጀመሪያውን የጋብቻ ጊዜውን በተለመከተ ሲሆን የሥር ፍርድ ቤት በዚህ ረገድ ሁለት ጊዜ ውሳኔ የሰጠ መሆኑን የክርክ ሄደት ያስገነዝባል ይቬኹውም አንዱ በፍቺ ውሳኔ ጊዜ ሲሆን በዚህ ጊዜ ጋብቻው በሚያዚያ ወር ዓም የተፈጸመ መሆኑን ማረጋገጡን አምኖ ጋብቻው እንዲፈርስ መወሰትን በ ዓም የሰጠው ውሳኔ ያስገነዝባል ሁለተኛው ውሳኔ በንብረት ክርክር ጊዜ የተሰጠ ሲሆን በዚህ ጊዜ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ሊሰጥ የቻለው ተጠሪው ጋብቻው የተፈፀመው ጥር ቀን ዓም ነው በማለት ተከራክረው በዚህ ረገድም የጋብቻ ምስክር ወረቀት ለማስረጃነት አቅርበው ይኹው የሰነድ ማስረጃ ጥር ቀን ዓም የተፈፀመው ጋብቻ ግንቦት ቀን ዓም በውልና ክብር መዝገብ ስም አገልግሎት መመዝገቡን የሚያሳይ መሆኑን ጠቅሶና ቀድሞ በፍቺ ውሳኔ ጊዜ ጋብቻው ሚያዚያ ወር ዓም የተፈፀመ ነው የተባለው በፍብሥሥሕቁ ድንጋጌ መሠረት ሊታረም ይገባዋል በማለት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሠጠው ውሳኔ ነው ። የሚለዉ ነጥብ መሆኑን ተገንዝበናል በዚህ መሰረት የስር የዞን ከፍተኛ ፍቤት ዉሳኔ ግልባጭ ሲታይ የአሁን አመልካች የፍቤቱ መጥሪያ ደርሶት ያለ በቂ ምክንያት መልሱን ይዞ እንዳልቀረበ በመግለጽ መልስ የመስጠት መብቱን ማለፉን ያሳያልጹ በሌላ በኩል ከስር የጠቅላይ ፍቤት ዉሳኔ መገንዘብ እንደሚቻለዉ የአሁን ተጠሪ ባቀረበዉ ክርክር በፖሊስ በኩል የፍቤትን መጥሪያ ለአመልካች በ ዓም የሰጠሁት ስለሆነ ለ ዓም ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ መልሱን ይዞ ለመቅረብ በቂ ጊዜ እንደነበረዉ ገለጾ ተከራክሯል አመልካች በበኩሉ ባቀረበዉ ክርክር በ ዓም መጥሪያ ቢመጣለትም አንብቡልኝ ብላቸዉ ሊያነቡልኝ ፈቃደኛ አልሆነም አመልካች በ ዓም ፍቤት ቀርቦ በመታመሜ ምክንያት መልስ ለማዘጋጀት አልቻልኩም ስለዚህ ከባለሙያ ተማክሬ መልሴን እንዳቀርብ ብሎ እንዳመለከቱ አመልካች መጥሪያዉን ቢቀበል ኖሮ ለ ዓም መልስ አዘጋጅቶ ለመቅረብ እንደሚችል በመግለጽ መታለፉ ተገቢ መሆኑን በመግለጽ የስር ዉሳኔ በማጽናት ወስኗል ስለዚህ የአሁን ተጠሪ ባቀረበዉ ክርክር እንኳን ቢሆን አመልካች መልሱን ይዞ እንዲቀርብ እየተደረገ ያለዉ በስምንት ቀናት ዉስጥ እንደሆነ አና አመልካች ከባለሙያ ተማክሮ መልሱን ለማቅረብ ጊዜ እንዳልበቃዉ በመግለጽ ፍቤቱ ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጠዉ እንዳመለከተ ማየት ይቻላል አመልካች የቀረበበትን ክስና ማስረጃ በመመርመር ተገቢ ነዉ ያለዉን መልስ ለማቅረብ ከተሰጠዉ ቀጠሮ ከ ቀን በፊት ሊደርሰዉ እንደሚገባዉ የፍብስስሕቁ ያስገነዝባል ከዚህ አንጻር የአሁን አመልካች መልሱን እንዲያቀርብ የታዘዘዉ አና ቀጠሮ የተሰጠዉ ከ ቀን ባነሰ ጊዜ ዉስጥ መሆኑን ያሳያል ይህ ደግሞ አመልካች በሕግ በተመለከተ ጊዜ ዉስጥ ተገቢዉን ዝግጅት በማድረግ መልሱን አዘጋጅቶ እንዲቀርብ የሚያስችለዉ ጊዜ ሆኖ አይገኝም ይህ ደግሞ በኢፌዴሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ መሰረት የተጠበቀዉን መብት የሚነፍግ ነዉ ስለሆነም የስር ፍቤቶች የአሁን አመልካች በሕጉ አግባብ ተገቢዉን የመከላከያ መልሱን እንዲያቀርብና ሙሉ ክርክሩን እንዲያቀርብ ማድረግ ሲገባቸዉ የመከላከልና የመከራከር መብቱን በመንፈግ ዉሳኔ መስጠታቸዉን መገንዘብ ተችሏል ሲጠቃለል የስር ፍቤቶች የአሁን አመልካች የመከላከያ መልሱን ሳያቀርብ እና ክርክሩን አቅርቦ ሳይሰማ የሰጡት ዉሳኔ የመከላከልና የመከራከር የመሰማት መብቱን የነፈገ በመሆኑ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ ተገኝቷል በዚህ ምክንያት የሚከተለዉ ተወስኗል ዉሳኔ በትግራይ ክልል የሰሜን ምዕራብ ዞን ከፍተኛ ፍቤት በመቁ በ ዓም የሰጠዉ ዉሳኔ እና ይህን ዉሳኔ በማጽናት የትግራይ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ክልል ጠቅላይ ፍቤት መደበኛ ችሎት በመቁ በ ዓም የሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ በናብስስሕቁ መሰረት ተሽሯል በትግራይ ክልል የሰሜን ምዕራብ ዞን ከፍተኛ ፍቤት የተዘጋዉን መዝገብ በማንቀሳቀስ በፍርድ ሐተታዉ በተመለከተዉ መሰረት የአሁን አመልካች የመከላከያ መልሱን እና ክርክሩን እንዲያቀርብ በማድረግ ግራ ቀኛቸዉን በማከራከር ጉዳዩን በማጣራት ተገቢ ነዉ ያለዉን ዉሳኔ እንዲሰጥበት በፍብስስሕቁ መሰረት ተመልሶለታል የዚህ ዉሳኔ ግልባጭ ለስር ፍቤት ይድረስ ግራ ቀኛቸዉ በዚህ ችሎት የደረሰባቸዉን ወጪና ኪሳራ የየራሳቸዉን ይቻሉ ይህ ዉሳኔ ታህሳስ ቀን ዓም ተነብቧል አጐ መዝገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ መጋቢት ቀን ዓም ዳኞች መዓዛ አሸናፊ ሰለሞን አረዳ ተኽሊት ይመስል ተፈሪ ገብሩ ዶር ቀነአ ቂጣታ ተሾመ ሽፈራው ፀሃይ መንክር አመልካቾች ኛ ወሮ ሶፊያ መሐመድ ኛ አቶ አህመድ መሐመድ ኛ ወሮ ዘብይዳ መሐመድ ተጠሪ አቶ እንድሪስ ጋሹ መዝገቡን መርምረን ተከታዩን ውሳኔ ሰጥተናል ፍርድ ጉዳዩ የቤት ሽያጭ ውልን መሠረት ያደረገ ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው ተጠሪ በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በአመልካቾች ላይ ባቀረቡት ክስ ነው ተጠሪ ያቀረቡት ክስ ይዘትፁ ከሟቾች ሐጂ መሐመድ ሰይድ እና ወሮ ፋጡማ መሐመድ የአሁን አመልካቾች ወላጆች ጋር ሚያዚያ ቀን ዓም በተፃፈ የቤት ሽያጭ ውል በቀድሞው ወረዳ ቀበሌ የቤቁጥር የሆነ ቤት በብር ህያ ሺህ ገዝተው በውሉ መሰረት ባለመፈፀሙ ምክንያት ስም አእንዲዛወርላቸው በተዋዋዩቹ ላይ ነሃሴ ዓም ክስ መስርተው በክልል መስተዳደር ወረዳ ፍርድ ቤት በትዕዛዝ መቁ ታህሳስ ዓም ስም እንዲዛወር ውሳኔ ተሰጥቷል ይህን ውሳኔ ለማስፈፀም በቀድሞ ተከሳሾች ወራሾች የአሁን አመልካቾች ላይ አቤቱታ አቅርበው በፍብመቁ በ ዓም በተሰጠ ትዕዛዝ ሊፈጸም የማይችል ውሳኔ ነው ተብሉ መዝገቡ መዘጋቷል ስለሆነም ተከሳሾች የሻጮች ወራሾች ስለሆኑ ቤቱን እና ለስም ማዛወር የሚጠቅሙ የቤቱን ሰነዶች እንዲያስረክቡኝ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው አመልካቾች ለክሱ ባቀረቡት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ጉዳዩ ከዚህ በፊት ውሳኔ ያገኘ በመሆኑ ክሱ በድጋሚ የቀረበ ነው ተብሎ በፍብሥሥህቁ መሰረት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ውድቅ እንዲደረግ ውሉን መሰረት በማድረግ በሟቾች ላይ መስርተውት በነበረው ክስ በፍብሥሥህቁ እና ሁሉንም ጥያቄ አጣምረው ሊያቀርቡ ይገባ ነበር እንዲሁም ጉዳዩ በፍብህቁ መሰረት በ ዓመት ይርጋ እና በፍብህቁ መሰረት በአንድ ዓመት ይርጋ የታገደ ነው እንዲባል ጠይቀዋል በፍሬ ጉዳዩም በሰጡት መልስ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ በ ላይ በግልጽ እንደሰፈረው የከተማ ቤት በሽያጭ የሚተላለፍ ከሆነ መንግስት የግዥ ቀዳሚነት መብት አለው ይህም በመሆኑ በ ዓም የሚደረግ የቤት ሽያጭ ፍጹም አልነበረም ከሳሽ ውልን አደረኩ ባሉበት ጊዜ አውራሻችን በሚኒስቴሩ የፀደቀ ንብረት የላቸውም በዚህም መሰረት የተከሳሾች አውራሽ ንብረቱን ለማስተላለፍ መብት አልነበራቸውም ስለሆነም ውሉ ሐሰተኛ ወይም ህገወጥ ነው በአጠቃላይ የቀረበው ክስ በህጉ አግባብ ተቀባይነት የለውም ተብሎ ውድቅ ይሁንልን በማለት ተከራክረዋል ጉዳዩ በዚህ መልኩ የቀረበለት የሥር ፍርድ ቤት በአመልካቾች የቀረበውን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ እና ዝርዝር ክርክር ውድቅ በማድረግ ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን ቤት እና ሰነዶችን እንዲያስረክቡ ወስኗል አመልካቾች መቃወሚያዎቹ መታለፋቸውን እና በፍሬ ጉዳዩ የተሰጠውን ውሳኔ በመቃወም ጉዳዩን በይግባኝ ለፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርበው ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎችን በተመለከተ የሥር ፍርድ ቤት ያሳለፈው ውሳኔ ተገቢ መሆኑን ነገር ግን ፍሬ ጉዳዩ ባግባቡ ተጣርቶ አለመወሰኑን በመጥቀስ በድጋሚ አጣርቶ እንዲወስን ወደ ስር ፍርድ ቤት ጉዳዩን መልሷል በዚህ መልኩ የተመለሰለት የሥር ፍርድ ቤት ማስረጃዎችን ተመልክቶ የቀደመ ውሳኔውን በድጋሚ አሳልፏል ይህ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ አመልካቾች መቃወሚያዎቹ የታለፉት አላግባብ መሆኑን እና በፍሬ ጉዳዩ የተሰጠውን ውሳጌ በመቃወም ይግባኝ ለከፍተኛው ፍርድ ቤት አቅርበዋል ፍርድ ቤቱም መቃወሚያዎችን በተመለከተ አስቀድሞ ውሳኔ የሰጠባቸው በመሆኑ በጊዜው ይግባኝ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ሊጠይቁባቸው ይገባ እንደነበር በፍሬ ጉዳዩ ተጣርቶ የተሰጠው ውሳኔም ግድፈት እንደሌለበት ወስኗል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰበር አቤቱታው የቀረበው ይህን በመቃወም ነው አመልካቾች ህዳር ዓም በተፃፈ የሰበር ማመልከቻ መቃወሚያዎቹ በመታለፋቸውም ሆነ በፍሬ ጉዳዩ ተፈፀሙ የሚሏቸውን የህግ ስህተቶች ዘርዝረው አቅርበዋል አቤቱታው በሰበር አጣሪ ችሎት ተመርምሮ አከራካሪው ቤት በአመልካቾች እጅ ስለመኖሩ ባልተካደበት የቤት ሽያጭ ገንዘቡም አልተከፈለም ተብሎ ቀደም ሲል በመቁ በተሰጠ ፍርድ ላይ በተመለከተበት እና በአፈፃፀም መዝገብ ቁጥር ስመሃብት ይዛወር ተብሎ የተሰጠው ውሳኔ ሊፈፀም የማይችል ነው ተብሎ አፈፃፀሙ በተዘጋበት የስር ፍርድ ቤቶች ክሱን ዳግም በ ዓም በተከፈተ መዝገብ አስተናግደው የቤት ሽያጭ ውሉ ህጋዊ ስለሆነ አመልካቾች ቤቱን እና ኦሪጅናል ካርታውን ለተጠሪ ያስረክቡ በማለት የመወሰናቸውን አግባብነት ለመመርመር ሲባል አቤቱታው ለሰበር ችሎት እንዲቀርብ እአና ተጠሪ መልስ እንዲሰጡበት ተደርጓል ተጠሪ በሰጡት መልስ በቅድሚያ የሰበር አቤቱታውን አቀራረብ በተመለከተ መቃወሚያዎችን አትቅርበዋል የመቃወሚያው ይዘት አመልካቾች ለሰበር አቤቱታ መነሻ ያደረጉት ቀደም ሲል የከፍተኛው ፍርድ ቤት በመቁ በ ዓም ክርክር አድርጎ ውሳኔ የሰጠባቸው ነጥቦች ላይ ማለትም በፍብሥሥህቁ መሰረት የቀረበውን መቃወሚያ የይርጋ ክርክሩን የሽያጩን ገንዘብ ክፍያ አንዲሁም በህግ የታወቀ መብት አና የሥም ዝውውር ጥያቄን በተመለከተ ያቀረቡት የሰበር አቤቱታ ስለሆነ በፍብሥሥህጉ አግባብ በወቅቱ ይግባኝ አልተባለበትም የሰበር አቤቱታ አልቀረበበትም ተብሎ ውድቅ እንዲደረግ ጠይቀዋል ይህ ከታለፈም በጉዳዩ ላይ ፍርድ የተሰጠው በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመቁ በ ዓም እና በከፍተኛው ፍርድ ቤት በ ስለሆነ አቤቱታ የማቅረቢያ ጊዜ ያለፈበት ነው ተብሉ ውድቅ አንዲደረግ ብለዋል በፍሬ ጉዳዩም ዝርዝር መልሳቸውንም አቅርበዋል አመልካቾች ባቀረቡት የመልስ መልስ ቅሬታቸውን በማጠናከር ለሰበር ችሉቱ ከተሰጠው ስልጣን አንፃር በተለይም የህግ ድንጋጌዎችን ወጥነት ባለው መልኩ እንዲተረጎሙ ከማድረግ አኳያ የህግ ጥያቄዎች ለችሎቱ መቅረባቸው የሚነቀፍበት ምክንያት ሊኖር እንደማይገባ በመግለፅ በሰበር አቤቱታው አቀራረብ ላይ የተነሳው ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ መቃወሚያ ተቀባይነት የለውም እንዲባል ጠይቀዋል በሌሎች ነጥቦች ላይም የሥር ክርክራቸውን በማጠናከር አቅርበዋል የጉዳዩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለ መልኩ ከላይ የተመለከተው ሲሆን በበኩላችን ጉዳዩን መርምረናል አንደመረመርነው ተጠሪ የሰበር አቤቱታው አቀራረብ በተመለከተ ያነሱት መቃወሚያ ይህ ሰበር ችሎት በጉዳዩ ላይ አስቀድሞ የሰጣቸውን አስገዳጅ ትርጉሞች መሰረት በማድረግ የቀረበ በመሆኑ ከዚህ አንፃር ሰበር ችሎቱ አስቀድሞ በተመሳሳይ ጉዳዮች ያሳለፋቸው ገዥ ትርጉሞች በአዋጅ ቁጥር መሰረት በድጋሚ ሊታዩ የሚገባ መሆን አለመሆኑን መመልከቱ ተገቢ ሆኖ ተገኝቷል ተጠሪ ባቀረቡት መልስ አመልካቾች ለሰበር አቤቱታ መነሻ ያደረጉት ቀደም ሲል የከፍተኛው ፍርድ ቤት በይግባኝ አይቶ ፍሬ ጉዳዩ በአግባቡ ተጣርቶ እንዲወሰን ወደስር ፍርድ ቤት ሲመልስ በመቃወሚያዎቹ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ሰጥቶበት የነበረ በመሆኑ በመቃወሚያዎቹ ላይ በዚህ መልኩ በተሰጠው የመጨረሻ ውሳኔ ላይ በወቅቱ የሰበር አቤቱታ አልቀረበበትም ተብሎ ውድቅ እንዲደረግ ተከራክረዋል አመልካቾች በበኩላቸው ለሰበር ችሎቱ ከተሰጠው ስልጣን አንባር የህግ ጥያቄዎች ለችሎቱ መቅረባቸው የሚነቀፍበት ምክንያት ሊኖር እንደማይገባ በመግለፅ መከራከሪያው ውድቅ አንዲደረግ ጠይቀዋል ስለሆነም ውሳኔ የሚሻው ጉዳይ በእንዲህ አይነቱ ክርክር በመቃወሚያው ላይ የተሰጠውን ውሳኔ መነሻ ያደረገ የሰበር ቅሬታ መቅረብ ያለበት መቼ ነው። የሚለው በአግባቡ ሊታይ ይገባል ከፍብሥሥህቁ ንዑስ ቁጥር እና ግልጽ ድንጋጌ መገንዘብ እንደሚቻለው ይግባኝ የተባለበትን ፍርድ የወሰነው የበታች ፍርድ ቤት ጠቃሚ የሆነውን ጭብጥ ሳይዝ ወይም ጉዳዩን ሳይመረምርና ሳይረዳ ያለፈው መሆኑን ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ካረጋገጠ የተዘለሉለትን ጭብጦችና ፍሬ ነገሮች ለይቶ እንደገና እንዲመረምርና እንዲያጣራው ለመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት መልሶ ይልክለታል በዚህ መልኩ እንደገና እንዲያይ የተላከለት ፍርድ ቤትም በትዕዛዙ መሰረት ዳኝነቱን ካየ በኃላ ያጣራውን ነገር ለይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት መልሶ ይልካል በማለት ይደነግጋል ከድንጋጌው መገንዘብ አንደሚቻለው በይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት በፍብሥሥህቁ መሰረት ጉዳዩ ለመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተመልሶ የሚላከው ተጣርቶ ለይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት እንዲመለስ በመሆኑ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የተዘለሉለትን ጭብጦችና ፍሬ ነገሮች ለይቶ እንደገና እንዲመረምርና እንዲያጣራው ሲመልስ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ሰጥቷል የሚባልበት የህግ አግባብ አይኖርም የመጨረሻ ውሳኔ ባልተሰጠበት ጉዳይ ላይ ደግሞ የሰበር አቤቱታ እንዲቀርብ ማድረግ ከፍሲል የጠቀስናቸውን የህጉን ድንጋጌዎች መሰረት ያደረገ ባለመሆኑ ተቀባይነት የለውም ከዚህም ሌላ መቃወሚያውን መሰረት ያደረገ የይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ውሳኔ ላይ የሚኖረው ቅሬታ ተከራካሪው ወገን ወደስር ፍርድ ቤት በተመለሰው ክርክር አሸናፊ ከሆነ ቀሪ ሊሆን የሚችልበት አድል በመኖሩ ስህተቱ ሊታረም የሚገባው ወዲያውኑ በሚቀርብ የሰበር አቤቱታ ብቻ ነው ሊባል የሚችልበት ምክንያት አይኖርም በተጨማሪም ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የስር ፍርድ ቤት በመቃወሚያው ላይ የሰጠውን ብይን በማጽናት ነገር ግን በፍሬ ነገሩ ላይ የተሰጠውን ውሳኔ ሽሮ ተጣርቶ እንዲወሰን ጉዳዩን ሲመልስ በመቃወሚያው ላይ የተሰጠውን ውሳኔ የሚመለከት የሰበርይግባኝ ቅሬታ ወዲያውነ ካልቀረበ ተቀባይነት ሊኖረው አይገባም የተባለበት አግባብ በአንድ በኩል በስረ ነገሩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ያልተሰጠበት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የሰበር ችሎቱ ተያያዥነት ያላቸውንና ተጠቃለው ቢቀርቡ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በአንድ መዝገብ ውሳኔ ሊያገኙ የሚችሉ ጉዳዮችን በተነጣጠለ መልኩ ውሳኔ እንዲሰጥባቸው ያደርጋል ይህም በተከራካሪዎች ላይ ተጨማሪ እንግልትና ወጪን እንዲሁም በችሎቱ ላይ አላስፈላጊ የሥራ ጫናን የሚፈጥር ነው በተለይ እንዲህ አይነት ክርክሮች ከክልል ፍርድ ቤቶች የሚነሱ ሲሆን ተከራካሪዎች በአንድ መዝገብ በተነሱ ክርክሮች ሁለት እና ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ ወደ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት መመላለስ እንዲኖርባቸው የሚያድርግ ነው ይህም ብቻ ሳይሆን ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ተጣርቶ እንዲወሰን ወደስር ፍርድ ቤት ጉዳዩን መመለሱን ተቀብለው የጉዳዩን መጠናቀቅ በቅን ልቦና ሲጠባበቁ በመቃወሚያው ላይ በተሰጠው ውሳኔ የተፈፀመ የህግ ስህተትን ወዲያውኑ አላቀረባችሁም በሚል በሰበር ለማሳረም እንዳይችሉ የተደረጉት ባለጉዳዩች በርካቶች መሆናቸውንና በዚህ ምክንያት ፍትህ መጓዓደሉን መገንዘብ ይቻላል ስለሆነም አስቀድሞ በሰበር ችሉቱ የተያዘው አቋም የሥነ ሥርዓት ህጉን መንፈስ በተለይም የፍብሥሥህቁ አና ድንጋጌዎችን ይዘት እና የሰበር ስርዓቱን አላማ የተከተለ ሆኖ አላገኘነውም በእነዚህ ምክንያቶች ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ወደ ሥር ፍርድ ቤት በመለሰው ክርክር ላይ የሚሰጠውን ውሳኔ ውጤት ጠብቆ በፍሬ ነገሩ ውሳኔ ከተሰጠ በላ በመቃወሚያውም ሆነ በፍሬ ነገሩ ላይ የተጠቃለለ የሰበር አቤቱታ መቅረቡ ህጉን የተከተለ ከመሆኑም በላይ በአንድ ጉዳይ በተለያዩ ፍርድ ቤቶች በተበታተነ ሁኔታ ክርክር እንዳይካፄድ የሚያደርግ የተከራካሪዎችን መብት በተሻለ የሚያስከብር እና የህግ ስህተት የተፈፀመበት ውሳኔ ፀንቶ እንዳይቀር የሚያደርግ በመሆኑ አስቀድሞ የተሰጠው ትርጉም ሊለወጥ ይገባል ብለናል ስለሆነም የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን አዋጅ እንደገና ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሰረት ቀደም ሲል በዚህ ፍርድ ቤት በሰመቁ እና ሌሎችም በርካታ መዛግብት ተሰጥቶ የነበረውን ትርጉም ለውጠናል ይኸውም ጉዳዩ በፍብሥሥህቁ መሰረት ወደስር ፍርድ ቤት በተመለሰበት ሁኔታ ለክሱ በቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ላይ በይግባኝ ሰሚ ችሎት የተሰጠ ውሳኔን በመቃወም የሰበር አቤቱታ መቅረብ የሚገባው ወዲያውኑ ማለትም ውሳኔው ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በህግ በተደነገገው የሰበር ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ማቅረቢያ ጊዜ ውስጥ ከሚሆን በቀር በፍሬ ጉዳዩ ረገድ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ወደ ሥር ፍርድ ቤት በመለሰው ክርክር ላይ የሚሰጠውን ውሳኔ ውጤት ጠብቆ ተጠቃሎ የሚቀርብበት ምክንያት የለም ተብሎ የተሰጠው ትርጉም ተለውጧል ወደስር ፍርድ ቤት ጉዳዩ ተመልሶ በፍሬ ነገሩ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ በመቃወሚያው ላይ አስቀድሞ በተሰጠው ብይን ላይ ተጠቃሎ የሚያቀርበው አቤቱታ ህጉን መሰረት ያደረገ በመሆኑ ተቀባይነት የለውም ሊባል አይገባም ብለናል በተያዘውም ጉዳይ አመልካቾች ለክሱ ያቀረቡት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ በሥር ፍርድ ቤቶች ውድቅ በመደረጉ የህግ ስህተት ተፈጽሟል በማለት ለዚህ ሰበር ችሎት ያቀረቡት ቅሬታ በወቅቱ የሰበር አቤቱታ አልቀረበበትም ተብሎ ውድቅ እንዲደረግ በተጠሪ በኩል የቀረበው መከራከሪያ ተቀባይነት የለውም ብለናል ከፍሲል እንደተገለፀው ተጠሪ ባቀረቡት ክስ ከአመልካቾች ወላጆች ጋር ሚያዚያ ቀን ዓም በተደረገ የቤት ሽያጭ ውል አከራካሪውን ቤት ገዝተው በውሉ መሰረት ባለመፈፀሙ ምክንያት ስም እንዲዛወርላቸው ክስ መስርተው በትዕዛዝ መቁ ታህሳስ ዓም ስም እንዲዛወር ውሳኔ አሰጥተው እንደነበር ይህን ውሳኔ ለማስፈፀም አቤቱታ አቅርበው በፍብመቁ በ ዓም በተሰጠ ትዕዛዝ ሊፈጸም የማይችል ውሳኔ ነው ተብሎ ውድቅ መደረጉን በመጥቀስ አመልካቾች የተዋዋዮች የሻጮች ወራሾች ስለሆኑ ቤቱን እና ለስም ማዛወር የሚጠቅሙ የቤቱን ሰነዶች እንዲያስረክቡኝ ይወሰንልኝ በማለት ጠይቀዋል አመልካቾች በበኩላቸው ለክሱ ባቀረቡት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ጉዳዩ ከዚህ በፊት ውሳኔ ያገኘ በመሆኑ ክሱ በድጋሚ የቀረበ ነው ተብሉ ውድቅ እንዲደረግ ውሉን መሰረት በማድረግ በሟቾች ላይ መስርተውት በነበረው ክስ ሁሉንም ጥያቄ አጣምረው ሊያቀርቡ ይገባ ነበር እንዲሁም ጉዳዩ በይርጋ የታገደ ነው እንዲባል የተከራከሩ ሲሆን በፍሬ ጉዳዩም በህጉ አግባብ የተደረገ ውል ባለመኖሩ ቤቱንም ሆነ ሰነዶችን ልናስረክብ አይገባም የሚሉበትን መከራከሪያ በማንሳት ተከራክረዋል በበኩላችን አመልካቾች ካቀረቧቸው መቃወሚያዎች መካከል ለክሱ መቅረብ ምክንያት የሆኑት ነገሮች ላይ ሁሉ በሙሉ ተጠቃሎ መቅረብ ይገባው ነበር በሚል የቀረበውን ክርክር መርምረናል በፍብሥሥህቁ እንደተደነገገው ከሳሽ ክስ ሲያቀርብ ለክሱ ምክንያት የሆኑትን ነገሮች በሙሉ በክሱ ማመልከቻ ላይ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አጠቃሎ ማቅረብ አንደሚገባው የሚደነግግ ሲሆን የፍብሥሥህቁ ደግሞ ከሳሹ ሊከስበት ሲችል ሆነብሎ በመቀነስ ባስቀረው ነገር እንደገና ሌላ ክስ ለማቅረብ አንደማይችል ይደነግጋል የማይንቀሳቀስ ንብረትን ለማስመለስ ተጣምረው ስለሚቀርቡ ክሶችም በፍብሥሥህቁ ሥር ተደንግጓል በመሆኑም ከሳሽ ክስ ሲያቀርብ ክሱን ለማቅረብ ምክንያት የሆኑት ነገሮች በሙሉ አጠቃሎ ማቅረብ የሚጠበቅበት ሲሆን ማቅረብ ሲችል ቀንሶ ባስቀረው ጉዳይ ላይ ድጋሚ ክስ ሊያቀርብ እንደማይችል ከድንጋጌዎቹ መገንዘብ ይቻላል በተያዘው ጉዳይም ተጠሪ የሽያጭ ውል ነው ያሉትን መሰረት በማድረግ የቤቱ ስም አእንዲዛወርላቸው ክስ መስርተው በትዕዛዝ መቁ ታህሳስ ዓም ስም እንዲዛወር ውሳኔ አሰጥተው ነበር በሌላ በኩል ለአሁኑ ክርክር ምክንያት የሆነውን ክስ በማቅረብ አመልካቾች የተዋዋዮች የሻጮች ወራሾች ስለሆኑ ቤቱን አና ለስም ማዛወር የሚጠቅሙ የቤቱን ሰነዶች እንዲያስረክቡኝ ይወሰንልኝ በማለት መጠየቃቸውን ተገንዝበናል በሁለቱም ክስ የዳኝነት ጥያቄ የቀረበው ውሉን መሰረት በማድረግ እንደውሉ ተፈጽሞ ስመሃብቱ እንዲዞርና ቤቱንና የቤቱን ሰነዶች ለመረከብ ነው ስለሆነም ተጠሪ የቀደመው ውሳኔ በአፈጻፀም ውድቅ ሲደረግባቸው አንደገና በሁለተኛው ክስ ያቀረቡት ጥያቄ በመጀመሪያው ክስ ተጠቃሎ ሊጠየቅ የሚገባው ነበር በመጀመሪያው ክስ አጠቃለው ሊያቀርቡት ሲገባ ሁለተኛ ክስ ማቅረባቸው በፍብሥሥህቁ አንጻር የማይቻል በመሆኑ የሥር ፍርድ ቤቶች የአመልካቾችን የክስ መቃወሚያ ተቀብለው ክሱን ውድቅ ሊያደርጉት ሲገባ ይህን አልፈው ፍሬ ጉዳዩን በመመልከት አመልካቾች ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን ቤት እና ሰነዶችን እንዲያስረክቡ በማለት ያሳለፉት ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ አግኝተነዋል ስለሆነም ተከታዩን ወስነናል ውሳኔ በዚህ ሰበር ችሎት በሰመቁ እና ሌሎችም ተመሳሳይ መዛግብት በይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ወደ ስር ፍርድ ቤት የተመለሰው ፍሬ ጉዳይ የመጨረሻ ውሳኔ ከማግኘቱ በፊት በመቃወሚያዎቹ ላይ በተሰጠ ውሳኔ የሰበር አቤቱታ ወዲያውኑ ካልቀረበ የፍሬ ጉዳዩን የመጨረሻ ውሳኔ ጠብቆ የሚቀርበው አቤቱታ ተቀባይነት አይኖረውም ተብሎ የተሰጠው አስገዳጅ ትርጉም የሰበር ችሎቱ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የተቋቋመበትን ዓላማ ዳር የሚያደርስ ሆኖ ስላላገኘነውና ህጉንም መሰረት ያደረገ ባለመሆኑ አስቀድሞ የተሰጠው ይህ ትርጉም የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን አዋጅ እንደገና ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር አንቀፅ መሰረት ተለውጧል በዚህ መዝገብ የተሰጠው ውሳኔ ለጉዳዩ ገዥ ይሆናል ብለናል በፍብሥሥህቁ መሰረት ጉዳዩ ወደስር ፍርድ ቤት ተመልሶ በፍሬ ነገሩ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ በመቃወሚያው ላይ አስቀድሞ በተሰጠው ብይን ላይ ተጠቃሎ የሚያቀርበው የሰበር አቤቱታ ህጉን መሰረት ያደረገ በመሆኑ ተቀባይነት የለውም ሊባል አይገባም ብለናል ተጠሪ በመጀመሪያው ክስ አጠቃለው ሊያቀርቡት ሲገባ ሁለተኛ ክስ ማቅረባቸው በፍብሥሥህቁ አንጻር የማይቻል በመሆኑ የሥር ፍርድ ቤቶች የአመልካቾችን የክስ መቃወሚያ ተቀብለው ክሱን ውድቅ ሊያደርጉት ሲገባ ይህን አልፈው ፍሬ ጉዳዩን በመመልከት አመልካቾች ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን ቤት እና ሰነዶችን እንዲያስረክቡ ያሳለፉት ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆነ የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በኮመቁ ሚያዚያ ዓም እንዲሁም የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በኮመቁ ጥቅምት ቀን ዓም የሰጡት ውሳኔ በፍብሥሥህቁ መሰረት በአብላጫ ድምፅ ተሽሯል ከሥር ፍርድ ቤቶች የተላኩት መዛግብት በመጡበት አግባብ ይመለሱ በዚህ ፍርድ ቤት ስለተደረገው ክርክር ግራቀኙ ወጪና ኪሳራ ይቻቻሉ በዚህ ፍርድ ቤት መጋቢት ቀን ዓም የተሰጠ የአግድ ትአዛዝ ተነስቷል መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የስድስት ዳኞች ፊርማ አለበት የልዩነት ሀሳብ እኔ ስሜ በተራ ቁጥር አምስት ላይ የተጠቀሰዉ ዳኛ የአብላጫዉ ድምጽ ከሰጠዉ ዉሳኔ በሚከተሉት ምክንያቶች በመለየት የልዩነት ሀሳብ አስቀምጫለሁ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የጉዳይ አመጣጥ ሲታይ በክልል መስተዳደር ወረዳ ፍርድ ቤት በመቁ ታህሳስ ቀን ዓም በሰጠዉ ዉሳኔ በአሁን ተጠሪ ሳሽ እና በሟቾች ሐጂ መሐመድ ሰይድ እና ወሮ ፋጡማ መሐመድ ተከሳሾች መካከል ሚያዚያ ቀን ዓም በተደረገዉ የቤት ሽያጭ ዉል በቀድሞ ወረዳ ቀበሌ ክልል ዉስጥ የሚገኘዉን የቤት ቁጥር ሆነዉ ስመ ሀብቱ ወደ ከሳሽ እንዲዛወር በማለት ወስኗል የአሁን ተጠሪ ይህ ዉሳኔ እንዲፈጸምላቸዉ የአፈጸጸም ክስ ያቀረቡት ቢሆንም በመቁ በ ዓም በተሰጠ ዉሳኔ ዉሳኔዉ ሊፈጸም አይችልም ተብሉ ተወስኗል ከዚህ በኋላ የአሁን ተጠሪ የሥር ከሳሽ በአሁን አመልካቾች በሥር ተከሳሾች ላይ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ባቀረበዉ ክስ ተከሳሾች በቤት ሽያጭ ዉሉ መሰረት ቤቱን እና ቤቱን የሚመለከቱትን ሰነዶች እንዲያስረክቡኝ እንዲወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቋል የአሁን አመልካቾች የሥር ተከሳሾች በዚህ ክስ ላይ በሰጡት መልስ ይህ ጉዳይ ከዚህ ቀደም ታይቶ ዉሳኔ ያገኘ በመሆኑ አሁን የቀረበዉ ክስ ድጋሚ የቀረበ በመሆኑ ተቀባይነት የለዉም ከሳሽ ከዚህ ቀደም ክስ ሲያቀርቡ ጉዳያቸዉን በአንድ ላይ አጠቃልሉ ማቅረብ ሲገባቸዉ በመከፋፈል አሁን ያቀረቡት ክስ ተቀባይነት የለዉም ክሱ በይርጋ የሚታገድ ነዉ በማለት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎችን በማንሳት የተከራከሩ ሲሆን በዋናዉ ጉዳይ ላይ ክርክራቸዉን አቅርበዋል ከዚህ በኋላ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ጉዳዩን በመመርመር በሰጠዉ ዉሳኔ አመልካቾች ያቀረቡትን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎችን ዉድቅ በማደረግ በፍሬ ጉዳይ አመልካቾቹ ቤቱን እና ቤቱን የሚመለከቱትን ሰነዶች ለተጠሪ እንዲያስረክቡ በማለት ወስኗል የአሁን አመልካቾች በዚህ ዉሳኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ያቀረቡ ሲሆን ፍቤቱም ግራ ቀኛቸዉን በማከራከር በሰጠዉ ዉሳኔ የሥር ፍቤት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎችን ዉድቅ በማድረግ የሰጠ ዉሳኔ በሕጉ አግባብ ነዉ በማለት በማጽናት ዋናዉን ጉዳይ በተመለከተ ግን በአግባቡ ተጣርቶ ዉሳኔ የተሰጠበት ባለመሆኑ ጉዳዩን ድጋሚ ተጣርቶ ዉሳኔ ሊሰጥበት ይገባል በማለት ለሥር ፍቤት መልሶታል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በዚህ ዉሳኔ መሰረት የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በዋናዉ ጉዳይ የግራ ቀኛቸዉን በማከራከርና በማጣራት የቀደመዉን ዉሳኔ በማጽናት ወስኗል ከዚህ በኋላ የአሁን አመልካቾች በዚህ ዉሳኔ ቅር በመሰኘት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎች መታለፋቸዉ ተገቢ እንዳልሆነ በመግለጽ እና በዋናዉ ጉዳይ ላይ የተሰጠዉንም ዉሳኔ በመቃወም ይግባኝ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ያቀረቡ ሲሆን ፍቤቱም ግራ ቀኛቸዉን በማከራከር በሰጠዉ ዉሳኔ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎች ስለመታለፋቸዉ የቀረበዉን ቅሬታ በተመለከተ ይህ ፍቤት አስቀድሞ ዉሳኔ የሰጠባቸዉ በመሆኑ በጊዜዉ ይግባኝ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍቤት ሊጠይቁባቸዉ ሲገባቸዉ አሁን ያቀረቡት ቅሬታ ተቀባይነት የለዉም የሥር ፍቤት በፍሬ ጉዳይ የሰጠዉ ዉሳኔ ሲታይ ተጣርቶ የተወሰነ በመሆኑ ግድፈት የለዉም በማለት በማጽናት ወስኗል የአሁን የሰበር አቤቱታ የቀረበዉ ይህን ዉሳኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነዉ የአሁን አመልካቾች ባቀረቡት የሰበር አቤቱታ የሥር ፍቤቶች አመልካቾች ያነሷቸዉን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎች ማለፋቸዉ ተገቢ አይደለም እና በዋናዉ ጉዳይ ዝርዝር ቅሬታቸዉን በማቅረብ የሥር ፍቤቶች ዉሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነዉ ተብሎ አእንዲሻርልን በማለት አመልክቷል ይህ ችሎት የሰበር አቤቱታዉ ያስቀርባል በማለት ተጠሪ መልስ እንዲሰጥ ባዘዘዉ መሰረት ተጠሪ ባቀረበዉ መልስ የአሁን አመልካቾች የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎችን በተመለከተ የተሰጠዉን ዉሳኔ አሁን ለዚህ ችሎት ቅሬታ ሊያቀርቡ አንደማይችሉ እና በዋናዉ ጉዳይም የሥር ፍቤት መሰረታዊ የህግ ስህተት ያልተፈጸመበት ስለሆነ እንዲጸናልኝ በማለት በዝርዝር ተከራክሯል አመልካቾች የሰበር አቤቱታቸዉን በማጠናከር የመልስ መልስ አቅርበዋል አኔ ይህ ጉዳይ በሚከተለዉ አግባብ መታየት አለበት ብዬ የልዩነት ሀሳቤን አስቀምጣለሁ ሀ አስገዳጅ ሕግ ትርጉም የሚለወጥበት አግባብ በተመለከተ ይህ ሰበር ሰሚ ችሎት ከዚህ ጉዳይ ጋር ተመሳሳይ የሆኑትን ጉዳዮች በተመለከተ በሰመቁ እና በሌሎች በርካታ መዛግብት ላይ አስቀድሞ በሰጠዉ አስገዳጅ የህግ ትርጉም የይግባኝ ሰሚ ፍቤት የቀረበለትን ይግባኝ ተከትሎ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎች ላይ የሰጠዉ ዉሳኔ የመጨረሻ ዉሳኔ በመሆኑ ዉሳኔዉን በመቃወም የሰበር አቤቱታ መቅረብ የሚገባዉ ዉሳኔዉ ከተሰጠ ቀን ጀምሮ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በሕጉ በተቀመጠ የሰበር አቤቱታ የሚቀርብበት ጊዜ ገደብ ዉስጥ መሆን አለበት እንጂ በፍሬ ጉዳይ ወደ ሥር ፍቤት የተመለሰዉን ዉሳኔ ዉጤት ጠብቆ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ላይ ቅሬታ ማቅረብ እንደማይቻል ዉሳኔ ሰጥቶበታል በዚህ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም መሰረት ፍቤቶች የዳኝነት ሥራቸዉን ሲያከናዉኑ መቆየታቸዉ ግልጽ ነዉ። የሚለው ጥያቄ ደግሞ ራሱን የቻለ የፍርድ አፈጻጸም ጥያቄ እንጂ ተመሳሳይ ጉዳይን ከሚገዙ የተለያዩ አገሮች ሕጎች ግጭት ወይም ተቃርኖ ጋር በቀጥታ የሚያያዝ ጉዳይ አይደለምእንደ ስር ፍርድ ቤቶች አቋም ጉዳዩ የግል ዓለም አቀፍ ሕግ ተፈጻሚነት ጉዳይን የሚያስነሳ ነው ተብሎ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የመጀመሪያ ደረጃ ስልጣን ተስተናግዶ ውሳኔ ቢሰጥ እንኳ በአሜሪካን አገር ይገኛሉ የተባሉትን ገንዘብ እና ንብረት አስመልክቶ የፍርድ አፈጻጸም ጉዳይ ራሱን ችሎ የሚነሳ ጥያቄ መሆኑን ማስቀረት የሚችል አይደለም ቀደም ሲል እንደተገለጸው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጉዳዩን ለማየት የሚያስችል የሥረ ነገር ሥልጣን የለኝም ከሚል ድምዳሜ ላይ ደርሶ መዝገቡን በብይን የዘጋው በመዝገብ ቁጥር የተሰጠውን የሰበር ገዥ ውሳኔ በአስረጂነት በመጥቀስ ነውበመሰረቱ አስቀድሞ በቀረበለት ጉዳይ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት የሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ቀጥለው በሚቀርቡ ጉዳዮች ላይ ተፈጻሚነት ሊኖረው የሚችለው በሁለቱ ጉዳዮች ለክርክር የቀረቡት የሕግ እና የፍሬ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ነገር ነጥቦች ተመሳሳይነት ያላቸው በሆነ ጊዜ መሆኑ የሚታወቅ ነውበመዝገብ ቁጥር የተሰጠው ገዥ ውሳኔ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክርክሩ ቀድሞውኑ በአንድ መዝገብ ተስተናግዶ ውሳኔ ማግኘት የነበረበት ነው በሚል ክሱን አልቀበልም ማለቱ ተገቢ አለመሆኑ ተገልጾ ጉዳዩ እንዲታይ የተመለሰበት እንጂ በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ነው የተባለ ንብረት ከፊሉ ከኢትዮጵያ ውጪ የሚገኝ መሆኑ የግል ዓለም አቀፍ ሕግ ተፈጻሚነት ጉዳይን የሚያስነሳ ነው ተብሎ ትርጉም የተሰጠበት አይደለምበውሳሄኔው የመጨረሻ ፓራግራፍ የሰፈረው የውሳኔው ክፍልም በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የተያዘውን አቋም ለማመላከት ታስቦ የሰፈረ ነው የሚባል እንጂ ሰበር ችሎቱ እራሱ ጉዳዩን በጭብጥነት ይዞ ገዥ ውሳኔ ያሳረፈበት አይደለምበመሆኑም የስር ፍርድ ቤቶች ተጠቃሹን የሰበር ችሎት ውሳኔ በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ነው የተባለ ንብረት ከፊሉ ከኢትዮጵያ ውጪ የሚገኝ መሆኑ የግል ዓለም አቀፍ ሕግ ተፈጻሚነት ጉዳይን የሚያስነሳ ነው ተብሉ ትርጉም እንደተሰጠበት አድርገው በመውሰድ የያዙት አቋም የውሳኔ ትክክለኛ ዓላማ እና ይዘት መሰረት ያደረገ ነው ለማለት የሚቻል አይደለም ሲጠቃለል አቤቱታ የቀረበበት የስር ፍርድ ቤቶ ውሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት እና ሊታረም የሚገባው ሆኖ በመገኘቱ የሚከተለው ውሳኔ ተሰጥቷል ውሳኔ ጉዳዩን የማየት የስነ ነገር ስልጣን የለኝም በሚል መዘገቡን ዘግቶ በመመለስ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር በ ዓም ተሰጥቶ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር በ ዓም በትዕዛዝ የጸናው ብይን በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር መሰረት ተሽሯል ግራ ቀኙ በጋብቻቸው ጊዜ ካፈሩት ገንዘብና ንብረት ከፊሉ በአሜሪካን አገር ይገኛል መባሉ ብቻውን የግል ዓለም አቀፍ ሕግን ተፈጻሚነት ጉዳይን የሚያስነሳ አይደለም በማለት ወስነናል የተከሳሽ ከሳሽነት ክስ የቀረበበትን ጉዳይ ጭምር የማየት የሥረ ነገር ሥልጣን የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ነው በማለት ወስነናል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ መዝገቡን አንቀሳቅሶ ክርክሩን ቀጥሎ በማየት ተገቢውን ውሳኔ ይሰጥበት ዘንድ ጉዳዩ በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር በ መሰረት ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እንዲመለስ ወስነናል የውሳኔ ግልባጭ ተገቢውን መፈጸም ያስችለው ዘንድ ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትእንዲያውቀው ደግሞ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይላክ የሰበር ክርክሩ ያስከተለውን ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ ውሳኔ ያገኘ ስለሆነ መዘገቡ ተዘግቷል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ግንቦት ቀን ዓም ዳኞች ተኽሊት ይመስል ተፈሪ ገብሩ ዶር ቀነአ ቂጣታ ተሾመ ሽፈራው አብዬ ካሳሁን አመልካች አቶ ገዛህኝ አየለ አልቀረቡም ተጠሪዎች ኛ አቶ ኑረዲን ዓሊ ቀረቡ ኛ አቶ አይደር ከድር አልቀረቡም መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል ፍርድ የሰበር አቤቱታው የቀረበው የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ድሬዳዋ ምድብ ችሉት የአሁን ኛ ተጠሪ አላግባብ ተይዞብኛል የሚሉት በከተማው ቀበሌ አስተዳደር ክልል የሚገኘውን ቁጥሩ የሆነ የቀበሌ የንግድ ሱቅ እንዲመለስላቸው ያቀረቡትን ክስ ተመልክቶ የአሁን አመልካች ሱቁን ለከሳሽ ኛ ተጠሪ እንዲያስረክቡ ያሳለፈውን ውሳኔ እና ይግባኙ የቀረበለት የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔው ግድፈት አልተገኘበትም በማለት የቀረበለትን አቤቱታ ባለመቀበል ትዕዛዝ በመስጠቱ መሰረታዊ የህግ ስህተት ተፈጽሟል በሚል ነው አመልካች ሰኔ ዓም ያቀረቡት የሰበር ማመልከቻ ተመርምሮ አከራካሪው ጉዳይ የቀበሌ ቤት ሆኖ ዕያለ የስር ፍርድ ቤት የዳኝነት ስልጣኑ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ነው በማለት ክርክሩን አይቶ የመወሰኑን አግባብነት ለመመርመር ሲባል ጉዳዩ ለሰበር ችሎት እንዲቀርብና ተጠሪዎች መልስ አንዲሰጡበት ተደርጓል በዚህ መሰረት ግራ ቀኙ ክርክራቸውን በጽሁፍ ተለዋውጠዋል በበኩላችን አመልካች በዳኝነት ስልጣን ረገድ ያቀረቡትን ክርክር ቅሬታ ከቀረበበት ውሳኔ እና ለጉዳዩ አግባብነት ካላቸው የህጉ ድንጋጌዎች አንፃር መርምረናል አንደመረመርነው ክሱ የቀረበው የድሬደዋ ከተማ ቀበሌ አስተዳደር በሚያስተዳድረው በቀበሌው ክልል የሚገኘውን ቁጥሩ የሆነ የንግድ ሱቅ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ለማስመለስ ሲሆን ከክሱ ይዘት መረዳት እንደሚቻለው ዳኝነት የተጠየቀው የሥር ኛ ተከሳሽ የአሁን ኛ ተጠሪ በከሳሽ ከተሰጠው የውክልና ስልጣን ውጪ በቤቱ በራሱ ሥም የንግድ ፍቃድ ከማውጣቱም በላይ ለኛ ተከሳሽ አሁን አመልካች በአደራ ሰጥቶት የሚገኝ በመሆኑ እንዲመልስልኝ ብጠይቀውም ለመመለስ ፈቃደኛ ስላልሆነ ከመንግስት የተከራየሁትን የንግድ ሱቅ እንዲያስረክቡኝ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት መጠየቁን የሚያሳይ ነው የሥር ፍርድ ቤትም ወደ ፍሬ ጉዳይ ክርክሩ በመግባት የውሉን ይዘት መርምሮ ቤቱ ለከሳሽ እንዲመለስ ወስኗል በድሬዳዋ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ሪ እንደተደነገገው የከተማው አስተዳደር የሚያስተዳድራቸው ሆኖ ለንግድ ለመኖሪያ ወይም ለሌላ አገልግሎት በመስጠት ላይ ካሉ የመንግስት ቤቶች ጋር በተያያዘ የሚነሱ ክሶችን ተመልክቶ ለመወሰን የድሬደዋ ከተማ ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ስልጣን እንዳላቸው ተመልክቷል ነገር ግን በተያዘው ጉዳይ ለክሱ ምክንያት የሆነው በግለሰቦች መካከል የተደረገ ውል ሲሆን ዳኝነት ተጠይቆበት ውሳኔ የተሰጠውም ከውሉ ጋር በተያያዘ በቀረበው ክርክር ላይ ነው ስለሆነም ከፍ ሲል በተጠቀሰው ድንጋጌ የሚሸፈን አይሆንም በፍብሥሥህቁ ሥር አንደተመለከተውም በቀጥታ ወይም በግልፅ ካልታገዱ በቀር መደበኛ ፍርድ ቤቶች ሁሉ የፍትሐ ብሔርን ክስ ተቀብለው ለማከራከር ሥልጣን አላቸው በአጠቃላይ ጉዳዩ በፌዴራሉ ፍርድ ቤቶች ሳይሆን በከተማ አስተዳደሩ ፍርድ ቤቶች ሊታይ ይገባል በሚል በአመልካች የቀረበው መከራከሪያ ዳኝነት የተጠየቀበትን ጉዳይ እና ከፍ ሲል የተጠቀሱትን ህጎች ይዘት ያገናዘበ ባለመሆነ ክርክሩ ተቀባይነት የለውም ብለናል ተከታዩንም ወስነናል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ውሣኔ በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁ ሚያዚያ ቀን ዓም የተሰጠው ውሳኔ እንዲሁም የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቁጥር ሰኔ ቀን ዓም ያሳለፈው ትዕዛዝ በፍብሥሥህቁ መሰረት ፀንቷል በዚህ ፍርድ ቤት ህዳር ዓም የተሰጠው የዕግድ ትዕዛዝ ተነስቷል ይፃፍ። የአሁኑ ተጠሪ የዉፃ አገልግሎት መስጠቱ አመልካቾች ደግሞ ተጠቃሚዎች ከመሆናቸዉ አንባር የተገለገሉበት ሂሳብ የመክፈል ግዴታ ያላቸዉ መሆኑን ተጠቅሶ የቀረበዉ ክርክር መነሻዉ ዉል እንጂ የሁለት ተቋማት ክርክር ስለመሆኑ መዝገቡ አያሳይም ይህ ከሆነ ደግሞ የሥር ይግባኝ ሰሚ ችሎት በዉሳኔዉ እንደገለፀዉ ክርክሩ ዉል መነሻ ያደረገ ያልተከፈለ ገንዘብ ለማስከፈል የቀረበ ክስ ከመሆነ አንፃር የአዲስ አበባ ከተማ ፍቤቶች የስረ ነገር ስልጣን ያላቸዉ ስለመሆኑ የሚሳይ አንዳችም የህግ መሰረት ያለዉ ክርክር አልቀረበም በሌላ በኩል የከተማዉ ሰበር ሰሚ ችሎት አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ሠ የተረጎመበት አግባብ የድንጋጌዉ መሰረታዊ ይዘትና መንፈስ ያልተከተለ ነዉ የስረ ነገር ስልጣን ክርክር ጉዳይ ፍቤቱ በራሱ ጊዜ የሚያነሳ ስለመሆኑም የፍሕስስሕቁ እና ድንጋጌዎች መሰረታዊ ይዘት ያስገነዝቡናል በመሆኑም የከተማዉ ሰበር ሰሚ ችሎት ክርክሩ ዉል መነሻ ያደረገ መሆኑን መገንዘብ እየተገባዉ ጉዳዩ በከተማዉ ፍቤቶች የሚታይ ነዉ በማለት የደረሰበት መደምደሚያ አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ያላገናዘበ ነዉ ብለናል በዚህም ተከታዩን ወስነናል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ዉሳኔ የአዲስ አበባ ከተማ ፍቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመቁ ሰኔ ቀን ዓም በዋለዉ ችሎት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመቁ በ ዓም የሰጠዉ ዉሳኔ በመሻር የሰጠዉ ዉሳኔ ተሽራል የአዲስ አበባ ከተማ ፍቤቶች ለክርክሩ መነሻ የሆነዉ የዉል ጉዳይ የመዳኘት የስረ ነገር ስልጣን የላቸዉም በማለት ወስነናል የአዲስ አበባ ከተማ ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመቁ በ ዓም በአብላጫ ድምጽ የሰጠዉ ዉሳኔ ጸንቷል ወጪና ኪሳራ ይቻቻሉ የዉሳኔዉ ግልባጭ ለስር ፍቤቶች ይተላለፍ መዝገቡ ተዘጋ ወደ መቤት ተመለሰ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ቤፍ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ቀን ዳኞች ተኽሊት ይመሰል ተፈሪ ገብሩ ዶር ቀነዓ ቂጣታ ተሾመ ሽፈራዉ አብዬ ካሳሁን አመልካቾችአቶ ያሲን ኢብራሂም ቀርበዋል አቶ ጌቱ አሸቱ ቀርበዋል ተጠሪ አቶ ኃይሉ ታዬ ቀርበዋል መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ጉዳዩ የተጀመረዉ በኦሮሚያ ብክመንግስት መስተዳደር በሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን ተጠሪ ከሳሽ አመልክቾች ደግሞ ተከሳሾች በመሆን ተከራክረዋል የተጠሪ ክስ ይዘትም በአጭሩ በጉንዶ መስቀል ከተማ ቀበሌ ዉስጥ ያለኝን ካሜትር መሬት ተከሳሾች ያላግባብ የያዙብኝ በመሆኑ ይህኑን መሬት እንዲለቁ ይወሰንልኝ የሚል ነዉ አመልካቾች በበኩላቸዉ ከሳሽ በቦታዉ ላይ የነበራቸዉን መብት በ ዓም ለእህቱ አሰገደች ታዬ መስጠቱን አና አሰገደች ይዞታዉን ለሌላ ሰዉ በሽያጭ ዉል ካስተላለፉላቸዉ ሰዉ ገዝተዉ የያዙት እንጂ የከሳሽ አለመሆኑን ገልፀዉ ተከራክረዋል ጉዳዩ በዚህ መልኩ የቀረበለት የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤትም በዚህ መልኩ ከግራ ቀኝ የቀረበዉን ክርክር እና ማስረጃ ከሰማ በኋላ አመልካቾች ለክርክሩ ምክንያት የሆነዉን ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ቦታ በህገ ወጥ መንገድ የያዙ መሆኑ መረጋገጡን ጠቅሶ በላዩ ላይ የሰሩትን ቤት አፍርሰዉ ይዞታዉን ለተጠሪ እንዲለቁ ሲል ወስኗል አመልካቾች ይህን ዉሳኔ ባለመቀበል ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያቀረቡት ይግባኝ ተቀባይነት ባለማግኘቱ አቤቱታቸዉን ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያቀረቡ ሲሆን ሰበር ሰሚዉ ችሎት መዝገቡን አስቀርቦ ከመረመረ በላ ጉዳዩን የማየት የስረ ነገር ስልጣን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በመሆኑ የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ጉዳዩን ለማየት ስልጣን የለዉም በሚል ተጠሪ ያቀረበዉን ክርክር ዉድቅ በማድረግ የፍሬ ነገር ክርክሩን በተመለከተ በክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተሰጥቶ በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በትዕዛዝ የፀናዉን ዉሳኔ በማጽናት ወስኗል ይህ የሰበር አቤቱታ የቀረበዉም በዚህ ዉሳኔ ቅር በመሰኘት ለማስለወጥ ሲሆን አመልካቾች በቀን ዓም በጠበቃቸዉ አማካይነት ተዘጋጅቶ በቀረበ ሦስት ገጽ የሰበር አቤቱታ በኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የተሰጠዉ ዉሳኔ መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነዉ የሚልባቸዉን ምክንያቶች በመዘርዘር ታርሞ ይወሰንለት ዘንድ ዳኝነት ጠይቀዋል አቤቱታዉ ተመርምሮ ያስቀርባል በመባሉም ተጠሪ በተደረገላቸዉ ጥሪ መሠረት ቀርበዉ ግራ ቀኝ ክርክራቸዉን በጽሑፍ ተለዋዉጠዋል የጉዳዩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለ መልኩ ሲታይ ከፍ ሲል የተመሰለከተዉ ነዉ ይህ ችሎትም የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ይህን ጉዳይ ተቀብሎ የማየት ስልጣን ያለዉ መሆን አለመሆኑን በጭብጥነት በመያዝ መዝገቡን አንደሚከተለዉ መርምሮታል እንደመረመረዉም የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን ስልጣን ለመወሰን የወጣዉ አዋጅ ቁጥር የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን የፍትሐብሔር የዳኝት ስልጣን በሚደነግገዉ አንቀጽ ስር መደበኛ ነዋሪነታቸዉ በተለያዩ ክልሎች ዉስጥ በሆነ ሰዎች መካከል የሚነሱ ክርክሮችን የማየት ስልጣን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ስለመሆነ ይደነግጋል በሌላ በኩል የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች የሰበር ስልጣን የመጨረሻ ዉሳኔ በተሰጠባቸዉ የክልል ጉዳዮች ላይ እንደሆነ በኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀጽ ሐ ስር ተመልክቷል ለተያዘዉ ጉዳይ አግባብነት ያለዉ የኦሮሚያ ክልል ፍርድ ቤቶችን ስልጣን ለመወሰን የወጣዉ አዋጅ ቁጥር ሲሆን የዚህ አዋጅ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አንቀጽ ሠ የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሉት የዳኝነት ስልጣን የክልል ጉዳዮችን በተመለከተ በክልሉ ፍርድ ቤቶች የመጨረሻ ዉሳኔ ባገኙ ጉዳዮች ላይ የተገደበ ስለመሆነ ይደነግጋል ከዚህ የምንረዳዉ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የክልሉ ፍርድ ቤቶች ባላቸዉ የዉክልና ስልጣን መሠረት የፌዴራል ጉዳዮችን አይተዉ የሚሰጧቸዉ የመጨረሻ ዉሳኔዎችን ተቀብሉ ለማየት ስልጣን የሌለዉ መሆኑን ነዉ ከዚህ አንፃር የተያዘዉን ጉዳይ ስንመለከት የአመልካቾች አድራሻ በኦሮሚያ ክልል ደራ ወረዳ ጉንዶ መስቀል ከተማ ቀበሌ ሲሆን የተጠሪ አድራሻ አዲስ አበባ ከተማ አራዳ ክከተማ ወረዳ መሆኑ ተረጋግጧልፎ ይህም የሚያሳየዉ ተከራካሪ ወገኖች በተለያዩ ክልሎች የሚኖሩ መሆኑን ነዉ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ጉዳዩን ለማየት ስልጣን አለዉ ለማለት ሁለት ምክንያቶችን የጠቀሰ ሲሆን የመጀመሪያዉ ምክንያት በኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀጽ መሠረት አዲስ አበባ ክልል አይደለም የሚል ነዉ በእኛ በኩል እንደተመለከትንዉ የኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀጽ የፌዴሬሽኑ አባላት የሆኑትን ዘጠኙን ክልሎች በመዘርዘር በአንቀጽ ሁሉም ክልሎች የራሳቸዉ አስተዳደር እንደሚኖራቸዉ ይደነግጋል በተመሳሳይ ሁኔታ በአንቀጽ ስር አዲስ አበባ ከተማ ራሱን በአራሱ የማስተዳደር ሙሉ ስልጣን እንዳለዉ እና ዝርዝሩ በህግ እንደሚወሰን ይደነግጋል በዚህም መሠረት የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁጥር እንዲሁም ይህን አዋጅ አሻሽሎ በወጣዉ አዋጅ ቁጥር መሠረት አዲስ አበባ ከተማ ራሱን በእራሱ በማስተዳደር ላይ ይገኛል ከዚህም የምንረዳዉ ኦሮሚያ እና አዲስ አበባ የየራሳቸዉ የሆነ የአስተዳደር ስልጣን ክልል ያላቸዉ መሆኑን ነዉ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ ስር በተለያዩ ክልሎች በሚል የተመለከተዉም በተለያዩ የአስተዳደር ክልሎች ዉስጥ የሚኖሩ ሰዎችን ለማለት እንደሆነ መገንዘቡ ተገቢ ነዉ በመሆኑም የዚህ ድንጋጌ አፈፃፀም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስልጣን ክልል ዉስጥ የሚኖሩትን አያጠቃልልም ሊባል የሚችልበት ህጋዊ ምክንያት የለም የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የጠቀሰዉ ሁለተኛዉ ምክንያት ለክርክሩ መነሻ የሆነዉ ንብረት የሚገኘዉ በኦሮሚያ ክልል ዉስጥ አና ዉሉም የተደረገዉ በኦሮሚያ ክልል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ዉስጥ መሆኑን ነዉ በመሠረቱ ንብረቱ የሚገኝበትን ወይም ድርጊቱ የተፈጸመበትን ቦታ ግምት ዉስጥ በማስገባት የሚወሰነዉ የአካባቢ ስልጣን እንጂ የስረ ነገር ስልጣን አለመሆኑን ከፍሥሥርዓት ህጉ አንቀጽ እና ድንጋጌዎች ይዘት እና መንፈስ መገንዘብ ይቻላል በመሆኑም ተከራካሪ ወገኖች በተለያዩ ክልሎች ዉስጥ የሚኖሩ መሆናቸዉ እስከተረጋገጠ ድረስ ለክርክሩ ምክንያት የሆነዉ ዉል ወይም ንብረቱ የሚገኘዉ በክልሉ ዉስጥ መሆኑ ጉዳዩን የማየት የስረ ነገር ስልጣኑ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች መሆኑን አያስቀርም ጉዳዩን ለማየት የስረ ነገር ስልጣን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ሆኖ ግን የአካባቢ ስልጣኑ በክልሎች ስር የሚወድቅ ሲሆን በኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀጽ እና መሠረት እንደነገሩ ሁኔታ የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወይም የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዉክልና ጉዳዩን የማየት ስልጣን ይኖራቸዋል በዚህም መሠረት ለክርክሩ ምክንያት የሆነዉ ንብረት እንዲሁም ዉሉ የተደረገዉ በኦሮሚያ ደራ ወረዳ ጉንዶ መስቀል ከተማ ቀበሌ መሆነ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ስልጣንን በዉክልና ለማየት ስልጣን ባለዉ በሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንዲታይ የማድረግ ዉጤት ሊያስከትል የሚችል ቢሆንም የስረ ነገር ስልጣኑን የፌዴራል ከመሆን አያስቀርም ስለሆነም የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በዚህ ረገድ የጠቀሰዉ ምክንያት የህግ መሠረት ያለዉ አይደለም በአጠቃላይ ተከራካሪ ወገኖች በተለያዩ የአስተዳደር ክልል ዉስጥ የሚኖሩ መሆናቸዉ ተረጋግጦ እያለ እና በዚህም ምክንያት ጉዳዩን የማየት የስረ ነገር ስልጣን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ሆኖ እያለ የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በህግ ተቀባይነት የሌላቸዉን ምክንያቶች በመጥቀስ ጉዳዩን ተቀብሎ በማከራከር የሰጠዉ ዉሳኔ መሠረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ ተገኝቷል በመሆኑም ተከታዩ ተወስኗል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ዉሳኔ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመቁ በቀን ዓም በዋለዉ ችሎት የሰጠዉ ዉሳኔ በፍሥሥርዓት ህግ አንቀጽ መሠረት ተሽሯል የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ይህን ጉዳይ ተቀብሎ ለማየት ስልጣን የለዉም ብለናል አመልካቾች የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በሰጠዉ ዉሳኔ ላይ ቅሬታ ካላቸዉ በህግ ስልጣን ላለዉ ፍርድ ቤት ለማቅረብ ያላቸዉን መብት ይህ ዉሳኔ አያስቀርም ይህ ችሎት በቀን ዓም በዋለዉ ችሉት የሰጠዉ ዕግድ ተነስቷል በዚህ ችሎት የተደረገዉ ክርክር ያስከተለዉን ወጪ እና ኪሳራ ግራ ቀኝ የየራሳቸዉን ይቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ማአ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ መጋቢት ቀን ዓም ዳኞች መዓዛ አሸናፊ ሰለሞን አረዳ ተኽሊት ይመስል ተፈሪ ገብሩ ዶር ቀነአ ቂጣታ ተሾመ ሽፈራው ፀፃይ መንክር አመልካቾች ኛ ወሮ አለምሸዋ አባተ አበበ ኛ ወሮ ስንታየሁ አበራ መኮንን ጠበቃ መታሰቢያ ሐይልዬ ቀረቡ ኛ አቶ አንተነህ አበራ መኮንን ኛ አቶ በሐይሉ አበራ መኮንን ተጠሪዎች ኛ አቶ ሚሊዮን አባተ አበበ ኛ ተጠሪ በራሳቸውና ስለ ኛ ተጠሪ ቀረቡ ኛ ወሮ ፍሬህይወት ፀጋ መዝገቡን መርምረን ተከታዩን ወስነናል ፍር ድ ጉዳዩ የቀረበው የሐረሪ ክልል ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ህዳር ቀን ዓም የሰጠውን ውሳኔ የሐረሪ ክልል ጠቅላይ ፍሃቤት በይመቁ መጋቢት ቀን ዓም በዋለው ችሎት በመሻር ባሳለፈው ውሳኔ ላይ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመ በመሆኑ ጉዳዩ በዚህ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ታይቶ በክልሉ ይግባኝ ሰሚ ችሎት ውሳኔ የተፈፀመው ስህተት ይታረምልን በማለት አመልካቾች የሰበር አቤቱታ በማቅረባቸው ነው ከመዝገቡ መረዳት አንደሚቻለው የአሁን አመልካቾች በተጠሪዎች ላይ በክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባቀረቡት ክስ በሐረር ከተማ ቀበሌ ውስጥ የሚገኘውንና በይዞታችን ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ባቆየነው ቦታ ላይ የሰራነውን ግምቱ ብር ስድሳ ሽህ የሆነ ሶስት ክፍል ሰርቪስ ቤቶች ተጠሪዎችን አስጠግተናቸው እንደ ኪራይ የሜታሰብ ብር አምስት መቶ እየከፈሉ ይኖሩበት ነበር ይሁን አንጂ በይዞታችን ላይ በገንዘባችን የሰራነውን ይህን ሶስት ክፍል ቤት ስመ ዛብት ወደራሳቸው ለማዞር እንቅስቃሴ አያደረጉ መሆኑን ስለደረስንባቸው ቤቱን ለቀው እንዲያስረክቡን ይወሰንልን በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል ተጠሪዎች ለክሱ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ እና የበኩላቸውን መከራከሪያ አቅርበዋል ጉዳዩን በቅድሚያ የተመለከተው የከፍተኛው ፍርድ ቤት መቃወሚያውን ውድቅ በማድረግ የግራቀኙን ክርክርና ማስረጃ መርምሮ አከራካሪውን ቤት አመልካቾች በራሳቸው ይዞታ በህጋዊ የግንባታ ፈቃድ መሰረት የሰሩት ስለመሆኑ በሰውና በሰነድ ማስረጃ የተረጋገጠ በመሆኑ ተጠሪዎች በቤቱና ቤቱ በተሰራበት ይዞታ ላይ ምንም ዓይነት መብት የላቸውም በማለት ተጠሪዎች ቤቱን ለቀው ለአመልካቾች እንዲያስረክቡ ወስኗል ተጠሪዎች ይህን ውሳኔ በመቃወም የይግባኝ ቅሬታቸውን ለሐረሪ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያቀረቡ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ጉዳዩ በክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ባለስልጣን ተጣርቶ እንዲቀርብ ካደረገና የግራቀኙን የይግባኝ ክርክር ከሰማ በኋላ ውሳኔ ሰጥቷል በሰጠው ውሳኔ ክርክር ያስነሳው ቤትና ቦታ ከአሁን አመልካቾች ህጋዊ ይዞታ ውጪ በመሆኑና ይኸው ቦታም በመንግስት ይዞታነት ሥር ያለ በመሆኑ አመልካቾች በህጋዊ መንገድ ካርታ ተሰጥተውበት ካለው ይዞታ ውጪ በሆነ የመንግስት ይዞታ ላይ በጨረቃ ቤትነት ተገንብቶ ባለው ሰነድ አልባ ቤት ላይ ክስ የማቅረብ መብት የላቸውም በማለት የስር ፍርድ ቤት ያሳለፈውን ውሳኔ ሽራል የሰበር አቤቱታው በቀጥታ ለዚህ ፍርድ ቤት የቀረበው ይህን በመቃወም ነው አመልካቾች ሚያዚያ ቀን ዓም በተጻፈ የሰበር ማመልከቻ የሐረሪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የሰጠው ውሳኔ ተሸሮ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ውሳኔ አንዲፀና ጠይቀዋል ጉዳዩ ለሰበር ችሎት እንዲቀርብና ተጠሪዎች መልስ እንዲሰጡበት የተደረገ ሲሆን ተጠሪዎች ሰኔ ዓም በተጻፈ መልስ ውሳኔው በህጉ አግባብ የተሰጠ ነው ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ተብሉ እንዲፀና ተከራክረዋልአመልካቾችም ክርክራቸውን በማጠናከር የመልስ መልስ አቅርበዋል መዝገቡም ለምርመራ የተቀጠረው በዚህ ሁኔታ ነው የጉዳዩ አመጣጥ አጠር ባለ መልኩ ከላይ የተመለከተው ሲሆን ይህ ችሎትም ጉዳዩን መርምሯል እንደመረመርነው ጉዳዩ የፌዴራል ጉዳይ ነው የሚባልበት ምክንያት የሌለ ሲሆን የክልል ጉዳይ መሆኑ ግራቀኙን አላከራከረም የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት ያለበትን በክልል ጉዳዮች የተሰጠ የመጨረሻ ውሳኔ ለማረም በሰበር ችሉት የማየት ስልጣን ያለው መሆኑም ይታወቃል ነገር ግን የተያዘው ጉዳይ በክልሉ ሰበር ችሉት ሳይታይ በቀጥታ ለዚህ ፍርድ ቤት የቀረበው ይህ ሰበር ሰሚ ችሎት አስቀድሞ በተመሳሳይ ጉዳዩች በሰጠው ትርጉም ምክንያት መሆኑን መገንዘብ ይቻላል ስለሆነም የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት አስቀድሞ ያሳለፋቸው ገዥ ትርጉሞች በአዋጅ ቁጥር መሰረት በድጋሚ ሊታዩ የሚገባ ሆኖ ተገኝቷል ይህ ሰበር ሰሚ ችሉት በሰመቁ ሚያዚያ ዓም በዋለው ችሎት በሰጠው ውሳኔ የሰበር ችሎት በህግ አግባብ ሳይቋቋም የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ጉዳዩን በሰበር አቤቱታ ስርዓት ሊያስተናግዱ የሚችሉበት አግባብ ሊኖር እንደማይችል በሐረሪ ክልል የሰበር ስርዓት በዝርዝር ህጎች በግልጽ ያልተቀመጠና ያለው አሰራርም በክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ያለመኖሩን የሚያስገነዝብ በመሆኑ በውስን ጉዳዮች ላይ ብቻ በክልሉ ሰበር ችሎት ተቋቁሟል እየተባለ የሰበር ስርዓት ተግባራዊ የሚሆንበት አግባብ ተገቢ ሆኖ አልተገኘም በማለት የክልሉ ሰበር ችሎት ሰጥቶት የነበረውን ውሳኔ በመሻር የክልሉ ይግባኝ ሰሚ ችሎት በሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ነው የሚል ወገን አቤቱታውን ሊያቀርብ የሚገባው በቀጥታ ለፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ነው በማለት ወስኗል በተመሳሳይም በሰመቁ ህዳር ዓም በተሰጠ ውሳኔ በሐረሪ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ በክልሉ ሰበር ሰሚ ችሉት ያልተቋቋመ መሆኑን በሐረሪ ክልል የሰበር ስርዓት በዝርዝር ህጎች ያልተቀመጠና ያለው አሰራርም በክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ያለመኖሩን የሚያስገነዝብ መሆኑን በመግለጽ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ጉዳዩን ተቀብሎ መወሰኑ ተቀባይነት የለውም በማለት ጉዳዩ ሊቀርብ የሚገባው በቀጥታ ለፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ስለመሆኑ ተወስኗል በነዚህና በመሰል መዛግብት በተሰጠው ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አስገዳጅ ትርጉም ምክንያት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጉዳዮችን በሰበር ማየቱን አንዳቆመ ተገንዝበናል በተያዘው ጉዳይም የሰበር አቤቱታው ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ሳይቀርብ በቀጥታ ለዚህ ፍርድ ቤት የቀረበው በዚህ ምክንያት ነው ስለ ፍርድ ቤቶች ጣምራነት እና ስልጣን በሚደነግገው የኢፌዴሪ ህገ መንግስት አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ለ ሥር እንደተመለከተው የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበትን በክልል ጉዳዮች የተሰጠ የመጨረሻ ውሳኔ ለማረም በሰበር ችሎት የማየት ስልጣን አንደሚኖረውና ዝርዝሩ በህግ እንደሚወሰን ይደነግጋል በተመሳሳይ የሐረሪ ክልል ህገ መንግስት አንቀጽ ሀ በማንኛውም የክልሉ ፍርድ ቤት የተሰጠ የመጨረሻ ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ሲሆን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰበር የማየት ሥልጣን እንዳለውና ዝርዝሩ በህግ እንደሚወሰን ይደነግጋል በዚህ መልኩ በህገመንግስታቱ የተቋቋመው እና ሥልጣኑ የተለየውን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት የተመለከቱ ዝርዝር ህጎች መውጣታቸውን ከክልሉ ፍርድ ቤቶች የማቋቋሚያ አዋጆችና ማሻሻያቸው መገንዘብ ይቻላል የሐረሪ ሕዝብ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፍርድ ቤቶችና የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር ምዕራፍ ሁለት ስለመደበኛ ፍርድ ቤቶች መቋቋምና ስለዳኝነት ስልጣናቸው የሚደነግግ ሲሆን በአንቀጽ ሥር የሐረሪ ህዝብ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት መቋቋሙ ተመልክቷል የችሎቶቹን አሰራር በሚደነግገው አንቀጽ ሥር ደግሞ በማንኛውም ደረጃ የሚገኙ የክልሉ ፍርድ ቤቶች ለሥራቸው አስፈላጊ የሆነ ችሎቶች እንደሚኖራቸው ተመልክቷል የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤት የዳኝነት ሥልጣን የሚዘረዝረው የአዋጁ አንቀጽ በንዑስ ቁጥር ስር ደግሞ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት ያለበትን በየትኛውም ደረጃ በሚገኝ የክልሉ ፍርድ ቤት የተሰጠን የመጨረሻ ፍርድ ወይም ውሳኔ በሰበር ችሎት የማየት ሥልጣን እንዳለው ይደነግጋል ከዚህም በቀር የሐረሪ ህዝብ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፍርድ ቤቶችና የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር እና ማሻሻያ አዋጆች ቁጥር አና እንደገና ለማሻሻል የወጣው አዋጅ ቁጥር ማሻሻያ ካደረገባቸው ጉዳዮች አንዱ የክልሉን ሰበር ችሎት የተመለከተ ነው በዚህ መሰረት በቀዳሚው አዋጅ ቁጥር አንቀጽ የተመለከተው ተሰርዞ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበትን በየትኛውም ደረጃ በሚገኝ የክልሉ ፍርድ ቤት የተሰጠን የመጨረሻ ፍርድ ወይም ውሳኔ በሰበር ችሎት የማየት ስልጣን ይኖረዋል የሰበር አቤቱታ አቀራረብ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት እና በወንጀለኛ መቅጫ ህግ ሥነስርዓት ስለ ይግባኝ አቀራረብ በተደነገጉት መሰረት ነው በሚል ተተክቷል ከፍሲል የተጠቀሱት የፌዴራሉም ሆነ የክልሉ ህገመንግስቶች እንዲሁም የሐረሪ ህዝብ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፍርድ ቤቶችና የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ማቋቋሚያ አዋጅ አና ማሻሻዎች ሁሉ የክልሉ ሰበር ችሎት መቋቋሙን የሰበር ችሎቱን ሥልጣን እና ለሰበር ችሎቱ አቤቱታ የሚቀርብበትን ስርዓት ሁሉ በህግ መደንገጉን የሚያሳዩ ናቸው የሰበር ችሎቱን ዝርዝር አደረጃጀትና አሰራር ሥርዓት መደንገጉ ለክልሉ ህግ አውጭ አካል የተተወ በመሆኑ በዚህ መልኩ ዝርዝር ህጎች እንዲወጡ ማድረግ ተገቢ ሲሆን እስካሁን በክልሉ ህግ አውጭ አካል በወጡት አዋጆ መሰረት የክልሉ ሰበር ችሎት በአግባቡ ተደራጅቶ አገልግሎት የማይሰጥበት የህግ ምክንያት የለም ሥራ ላይ ባሉት ህጎች አግባብ ችሎቱ እንዲደራጅና አገልግሎት እንዲሰጥ ማድረግም ከፍርድ ቤቱ ኃላፊዎች የሚጠበቅ ነው ይህ ከሆነ ደግሞ ሥራ ላይ ባሉት ህጎች መሰረት በክልሉ ሰበር ችሎት ታይተው ውሳኔ የተሰጠባቸው ጉዳዮች ላይ ለዚህ ሰበር ችሎት አቤቱታ ሲቀርብ በክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት አልተቋቋመም እንዲሁም በክልሉ የሰበር ስርዓት በዝርዝር ህጎች አልተቀመጠም በማለት ውድቅ መደረጉና የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ጉዳዩን ተቀብሎ እንዳይወሰን መደረጉ እንዲሁም ጉዳዩች ሊቀርቡ የሚገባው በቀጥታ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ስለመሆኑ የተሰጠው ትርጉም ከፍሲል የተጠቀሰውን የህገመንግስቱንና የፍርድ ቤቱን ማቋቋሚያ አዋጆች የተከተለ ባለመሆኑ አስቀድሞ የተሰጠው ትርጉም ሊለወጥ ይገባል ብለናል ስለሆነም የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን አዋጅ እንደገና ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሰረት ቀደም ሲል በዚህ ፍርድ ቤት በሰመቁ ሚያዚያ ዓም በሰመቁ ህዳር ዓም እንዲሁም በሌሎች ተመሳሳይ መዛግብት ሰጥቶት የነበረውን ትርጉም ለውጠናል በዚህ መዝገብ የተሰጠው ውሳኔ ለጉዳዩ ገዥ ይሆናል ብለናል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ በዚህ ምክንያት አመልካቾች የሐረሪ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔን በመሻር ባሳለፈው ውሳኔ ላይ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመ በመሆኑ በሰበር ችሎት ታይቶ ይታረምልን በማለት ያቀረቡትን የዳኝነት ጥያቄ በቅድሚያ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ሊያቀርቡ ይገባል በማለት ተከታዩን ወስነናል ውሳኔ በዚህ ፍርድ ቤት በሰመቁ ሚያዚያ ዓም በሰመቁ ህዳር ዓም እንዲሁም በሌሎች ተመሳሳይ መዛግብት ሰጥቶት የነበረው ትርጉም የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን አዋጅ እንደገና ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሰረት ከላይ በፍርዱ በተመለከተው መሰረት ለውጠናል አመልካቾች የሐረሪ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔን በመሻር ባሳለፈው ውሳኔ ላይ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመ በመሆኑ በሰበር ችሎት ታይቶ ይታረምልን በማለት ያቀረቡት አቤቱታ በሐረሪ ህዝብ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሉት ሊስተናገድና ውሳኔ ሊሰጥበት የሚገባ ነው ብለናል መስከረም ዓም የተሰጠው የዕግድ ትዕዛዝ ተነስቷል ይጻፍ በዚህ ፍርድ ቤት ስለተደረገው ክርክር ወጪና ኪሳራ ይቻቻሉ መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ብግ አፈፃፀም ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁጥር ቀንሕዳር ቀን ዓም ዳኞች ብርሃኑ አመነዉ በዕዉቀት በላይ አንዳሻዉ አዳነ ኃይሉ ነጋሽ እትመት አሰፋ አመልካች የአብክመ ገቢዎች ባለስልጣን ዐሕግ ተጠሪ አቶ መስፍን ጥላሁን ይህ መዝገብ አመልካችና ተጠሪ አቶ በላይ አካለ ከሚከራከሩበት የሰመቁ ጋር ከአንድ የስር ፍቤት ዉሳኔ የተነሱ ጉዳዮች በመሆናቸዉ መዝገቦቹ ተጣምረዉ ተመርምሮ የሚከተለዉ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ለዚህ ሰበር ክርክር መነሻ የሆነው የአፈጸጸም ጉዳይ ሆኖ የተጀመረዉ በአማራ ክልል በባህር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍቤት ነዉ። በሌላ በኩል ስለኮንስትራክሽን መሣሪያዎች ምዝገባና ቁጥጥር በወጣ አዋጅ ቁጥር እና በአዋጁ መሠረት በሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር የኮንስትራክሽን መሳሪያዎች ቁጥጥርና ምዝገባ እንዲሁም የባለቤትነት ደብተር አሰጣጥ አስመልክቶ በወጣዉ መመሪያ አንቀጽ ለ መሰረት ክሬሸር እንደአስፓልት ሚክሲንግ ፕላንትና ክሬን ሁሉ ከቦታ ወደ ቦታ እየተወሰደና አየተተከለ የሚሠራ ምዝገባና የባለቤትነት ደብተር የሚሰጠዉ ልዩ ተንቀሳቃሽ ንብረት መሆነ ተመላክቷል በዚሁ አዋጅ አንቀጽ መሰረት ከምዘገባና ቁጥጥሩ ዓላማዎች ዉስጥ አንዱ መሳሪያዎቹ ለዋስትና መያዣና ለተመሳሳይ አገልግሎቶች የሚዉልበትን ሁኔታ ማመቻቸት መሆኑ ተመልክቷል ከተጠቀሱት የአዋጁና የመመሪያዉ ድንጋጌዎች ይዘት መገንዘብ የሚቻለዉ ክሬሸር ወደ ኛ ወገን አንዳይተላለፍ ወይም አንዳይሸጥ የሚታገደዉ ክሬሸሩ ለሚገኝበት ቀበሌ ወይም የአስተዳደር አካል ደብዳቤ በመጻፍ ሳይሆን ክሬሸሩን ለሚመዘግበዉና የስም ዝዉዉር በማድረግ የባለቤትነት ደብተር ከሚሰጠዉ አካል ዘንድ ፅገዳዉ እንዲመዘገብ በማድረግ ነዉ በተያዘዉ ጉዳይ አመልካች ክሬሸሩ ለሚገኝበት ቀበሌ ደብዳቤ በመጻፉ ብቻ ንብረቱ በሕግ ፊት የጸናና ንብረቱ ወደ ኛ ወገን አንዳይተላለፍ የሚያግድ ዕግድ ነበረበት ለማለት አይቻልም ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ከላይ ከተገለጸዉ አንጻር የድንጋይ ወፍጮዉ ወይም ክሬሸሩ የማይንቀሳቀስ ንብረት ሳይሆን ልዩ ተንቀሳቃሽ ንብረት ነዉ የተባለ በመሆነ በፍብሥሥሕቁ መሠረት የጨረታዉ ማስታወቂያዉ ተለጥፎ ለ ቀናት የቆየ መሆኑ በስር ፍቤቶች የተረጋገጠ በመሆኑ የጨረታዉ ሄደት ጉድለት አለበት ሊባል የሚችል አልሆነም በሌላ በኩል አመልካች በፍብሥሥሕቁ መሰረት የመቃወም አቤቱታ ያቀረበዉ ንብረቱ በሀራጅ ጨረታ ከተሸጠና ገንዘቡም ለፍርድ ባለገንዘቦች ከተከፈለ በኋላ የቀረበ በመሆኑ አመልካች በክልሉ የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት ያለዉን የቀዳሚነት መብት ሊጠቀም አይችልም ስለሆነም የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የአመልካችን አቤቱታ ዉድቅ በማድረግ መወሰነ የሚነቀፍበት በቂ ምክንያት የለም ሲጠቃለል ከላይ በተገለጸዉ አግባብ አመልካች በፍብሥሥሕቁ መሠረት የመቃወም አቤቱታዉን ያቀረበዉ ክርክር ያስነሳዉ ክሬሸር በጨረታ ከተሸጠና ገንዘቡም ለፍርድ ባለገንዘብ ከተከፈለ በኋላ በመሆኑ በጨረታዉ ሂደትም ጨረታዉን ሊያስፈርስ የሚችል ጉድለት ባለመገኘቱ አንዲሁም ንብረቱ ለኛ ወገን አንዳይተላለፍ የተሰጠ ዕግድ በሕግ አግባብ ያልተመዘገበ በመሆነ የአመልካችን አቤቱታ ዉድቅ በማድረግ የተሰጠዉ ዉሳኔ የሚነቀፍበት በቂ ምክንያት ባለመኖሩ የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ነዉ ለማለት አልተቻለም በመሆኑም የሚከተለዉ ዉሳኔ ተሰጥቷል ውሳኔ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰመቁ ጥር ቀን ዓም እና የካቲት ቀን ዓም የሰጣቸዉ ዉሳኔዎች በፍብሥሥሕቁ መሠረት ጸንተዋል የቪህ ፍርድ ትክክለኛ ግልባጭ ከዚህ መዝገብ ጋር ተጣምሮ ከተወሰነዉ የሰመቁ ጋር ይያያዝ ተብሏል የሰበር ክርክሩ ያስከተለዉን ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ የየራሳቸዉን ይቻሉ መዝገቡ ዉሳኔ ያገኘ ስለሆነ ተዘግቷል ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ሩለ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁጥር መስከረም ቀን ዓም ዳኞች ብርሃኑ አመነዉ በዕዉቀት በላይ አንዳሻዉ አዳነ ኃይሉ ነጋሽ አትመት አሰፋ አመልካች ወሮ እድገት ፎጊ ጠበቃ መሐመድ ሲራጅ ቀረቡ ተጠሪ ምኢር አሻግሬ ወማሪያም አልቀረቡም መዝገቡ ተመርምሮ የሚከተለዉ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ለዚህ ሰበር ክርክር መነሻ የሆነው አፈጸጸምን የሚመለከት ጉዳይ ሲሆን የተጀመረው በደቡብ ብብሕክልል በየም ልዩ ወረዳ ፍርድ ቤት ነው በግራ ቀኙ መካከል የነበረዉ ጋብቻ በፍቺ መፍረሱን ተከትሉ የነበራቸዉ ቤት ግምቱ ብር ሆኖ ከቀረበ በኃላ ተጠሪ ብር ጨምሮ በብር ለማስቀረት የጠየቀ ሲሆን አመልካች በበኩላቸዉ በብር ለማስቀረት ጠይቀዉ ሁለቱም ገንዘብ ለማምጣት በሚል ሄደዉ ተጠሪ ገንዘብ ይዞ ቢመለስም አመልካች ሳይቀርቡ ቀርተዋል ሀራጅ ጨረታ ወጥቶ በሁለተኛዉ ጨረታ መር አብነት ወልዴ በብር ብር ያሸነፈ ሲሆን ተጠሪ አመልካች ከፍዬ አስቀራለሁ ባሉት መሠረት ድርሻዉን ብር በአንድ ጊዜ ከፍለዉ የሚያስቀሩ ቢሆን የማይቃወም መሆኑን የገለጸ ሲሆን አመልካች ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ብር ይዘዉ መቅረባቸዉንና ልጆች ስላሏቸዉ ቀሪዉን ለመክፈል ጊዜ እንዲሰጣቸዉ በመጠየቅ ተከራክረዋል የስር ፍቤት ጉዳዩን መርምሮ ግራ ቀኙ ያቀረቡት የቅድሚያ ግዥ መብት የሕግ ድጋፍ የለዉም በማለት የጨረታ አሸናፊ የሆነዉ መር አብነት ወልዴ ብር ከፍሎ ቤቱን እንዲረከብ የአፈጻጸም ትዕዛዝ ሰጥቷል አመልካች በዚህ የአፈጻጸም ትዕዛዝ ቅር ተሰኝተዉ ቅሬታ በየደረጃዉ ላሉ ፍቤቶች ቢያቀርቡም ተቀባይነት አላገኘም ይህ የሰበር አቤቱታ የቀረበው በዚሁ ዉሳኔ አመልካች ቅር በመሰኘታቸዉ ነው አመልካች ያቀረቡት የሰበር አቤቱታ ይዘት በወረዳዉ ፍቤት ትዕዛዝ ማዘጋጃ ቤት መጋቢት ቀን ዓም በባለሙያ ገምቶ ያቀረበዉ ግምት ሲሆን በቀጠሮ ከተጠሪ ድርሻ ዉስጥ ይዢ ብቀርብም ተጠሪ ሳይቀርብና እንደፍርዱ እንዲፈጸምለት ሳይጠይቅ ከሰባት ዓመት በኃላ እንሰትና የጓሮ አትክልት አልምቼበት እያለሁ በ ዓም እኔ ባላወቅኩበት ሁኔታ ብር ነዉ ተብሎ ተገምቶ በላዬ ላይ መሸጡ ተገቢ ባለመሆኑ የአፈጻጸም ትዕዛዙ ይሻርልኝ አንድ መኖሪያ ቤት ያለአግባብ ሦስት ዙር መገመቱ ስህተት ነዉ ከፍቺ በኃላ ያለማሁትን የጓሮ አትክልት በብር የተገመተ ቢሆንም ሳይታሰብልኝ ቀርቷል በአጠቃላይ በቤቴ የመኖር መብቴ እንዲከበርልኝ በቀደምትነት የመግዛት መብቴ ይጠበቅልኝ የሚል ነወ የአመልካች አቤቱታ ተመርምሮ የጨረታ መነሻ ዋጋ ከታወቀ በኃላ ግራቀኙ ይሸጥ የተባለዉን ንብረት ይህንኑ ዋጋ በማጣቀስ ያስቀሩት እንደሆነ የቅድሚያ መብት መብታቸዉን በማረጋገጥ ረገድ ስርዓቱን ከተከተለ በኃላ የቅድሚያ መብት ሊሰጥ አይገባም በሚል የደረሰበት መደምደሚያ አግባብነት ከሁሉም በላይ ንብረቱ የባልና ሚስት የጋራ ሀብት ከመሆኑ እአና አመልካች ከሐራጅ መሸጫ ዋጋ የተሻለ ዋጋ ላቅርብ እያሉ ጥያቄያቸዉ የመታለፉን አግባብነት ከፍብሕቁ ድንጋጌ አፈጻጸም አንጻር ለማየት ሲባል ጉዳዩ ለሰበር ያስቀርባል የተባለ ሲሆን ግራ ቀኙ መልስና የመልስ መልስ በጽሁፍ በማቅረብ ተከራክረዋል የተጠሪ መልስ ይዘትፁ በሕጋዊ መንገድ በማዘጋጃ ባለሙያ ተገምቶ የጓሮ አትክልት ግምት ብር መሆኑንን የአመልካችም መብት በቅድሚያ ተጠብቀላት አኔን ድርሻ ሰጥታ አንድትጠቀም ቢፈቀድላትም በቀጠሮ ሳትቀርብ ቀርታለች በስር ፍቤት አመልካች የእኔን መብት በመጋፋቷና በተደጋጋሚ መሰናክል በመፍጠሯ በሀራጅ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ጨረታ ቤቱ ተሸጦ ድርሻዬ ብር ተረክቤ የአሷን ድርሻ በሥር ፍቤት ተቀምጦላት እያለ ባለቀ ጉዳይ ያቀረበችዉ ቅሬታ ተገቢነት የሌለዉ በመሆኑ የሰበር አቤቱታዋ ዉድቅ ይደረግልኝ የሚል ነዉ የጉዳዩ አመጣጥና የግራ ቀኙ ክርክር ከላይ የተመለከተዉን የሚመስል ሲሆን ከስር ፍቤት ዉሳኔ እና ጉዳዩ ለሰበር ያስቀርባል ተብሎ ከተያዘዉ ጭብጥ ጋር በማገናዘብ መርምረናል መርምረን አእንደተረዳነዉ ግራ ቀኙ በጋራ በጋብቻ ዉስጥ ያፈሩትን ቤት ፍቺን ተከትሎ እንዲከፋፈሉ ዉሳኔ የተሰጠ ሲሆን በአፈጻጸም ሂደት ቤቱ በማዘጋጃ ቤት ብር ተገምቶ ቀርቧል ተጠሪ ብር ጨምሮ ለመግዛትና የአመልካችን ድርሻ ከፍሎ ለማስቀረት የጠየቀና ገንዘብ ይዞ የቀረበ ሲሆን አመልካች በብር ለማስቀረት ጠይቃ ተጠሪም ፈቃደኛ ቢሆንም አመልካች ብር ይዛ በመቅረብ ቀሪዉን ለመክፈል ጊዜ ከመጠየቅ በቀር ግዥዉን ለመፈጸምና የቅድሚያ ግዥ መብት ልትጠቀም አልቻለችም ከዚህም በኃላ የስር ፍቤት ቤቱን ሁለት ጊዜ ጨረታ ወጥቶ ጨረታዉን በብር ያሸነፈዉ መር አብነት ወልዴ ገንዘቡን ከፍሎ ቤቱን በአፈጻጸም እንዲረከብ ትፅዛዝ ተሰጥቷል ተጠሪ ከሽያጭ ገንዘቡ ድርሻዉን የወሰደ ሲሆን አመልካች ድርሻዋን ባለመዉሰዷ በአደራ በመስሪያ ቤቱ ግዥና ፋይናንስ ክፍል እንዲቀመጥ ተደርጓል አመልካች አጥብቃ የምትከራከረዉ በ ዓም በማዘጋጃ ቤት ተገምቶ በቀረበዉ ግምት መሠረት ብር ለመክፈል ይዢ ቀርቤና ሌላዉን በሂደት ለመክፈል ጠይቄ ባለሁበት ከቤቱ ተፈናቅዬ ቤቱን ገዥዉ እንዲረከብ ትዕዛዝ መሠጠቱ ስህተት ነዉ በሚል ነዉ በመሠረቱ አመልካች ክርክር ያስነሳዉን ቤት የቅድሚያ ግዥ መብት ጠይቃ አልተከለከለችም እንዲሁም በፍብሥስሕቁ መሠረት በሀራጅ ጨረታዉ ለመሳተፍ ጠይቃ አልተከለከለችም አመልካች ለመግዛት በጠየቀችዉ ብር እንድታስቀር ተጠሪ ስምምነቱን ገልጾ የነበረ ሲሆን አመልካች የተጠሪን ድርሻ ለመክፈል ይዛ የቀረበችዉ ገንዘብ ብር ብቻ በመሆነ ቤቱን ልታስቀር አልቻለችም ጊዜ ተሰጥቶኝ በሂደት ልክፈል የሚለዉ ክርክርም ቢሆን ባለገንዘብ በሆነዉ በተጠሪ ፈቃድ ላይ የሚመሠረት በመሆኑ ጊዜ እንዲሰጥ ሊገደድ አይችልም በሌላ በኩል አመልካች ግምት መክፈል የነበረብኝ በ ዓም በነበረዉ ግምት ነዉ የሚለዉ ክርክሯም የሕግ መሠረት የለዉም ምክንያቱም ፍርዱ እስካልተፈጸመ ድረስ ቤቱ በአመልካች አጅ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ቢቆይም የጋራ ሀብት በመሆኑ በቆይታ የሚመጣዉ የግምት ጭማሪ ሁለቱንም የሚጠቅም በመሆኑ ነዉ ሌላዉ አመልካች ከቤቱ ልፈናቀል አይገባም በማለት ብትከራከርም ቤቱን በሀራጅ ጨረታ ተሳትፎ ግዥ የፈጸመዉ ተጠሪ ሳይሆን መር አብነት ወልዴ በመሆኑ ገዥዉ ተከራካሪ ባልሆነበትና በተጠሪነት ወደ ክርክሩ እንዲገባ ባልተደረገበት ሁኔታ የሀራጅ ሽያጩ ሊሠረዝ ወይም የአመልካች የቅድሚያ ግዥ መብት ሊጠበቅ የሚችልበት አግባብ የለም ስለሆነም አመልካች አቤቱታ ተገቢነት የለዉም ሲጠቃለል አመልካች ካቀረቡት የሰበር አቤቱታ አንጻር የስር ፍቤት ዉሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል ለማለት አልተቻለም በመሆኑም የሚከተለው ውሳኔ ሰጥተናል ውሳኔ ኛ በየም ልዩ ወረዳ ፍቤት በመቁ መስከረም ቀን ዓም ተሰጥቶ በከፍተኛ ፍቤት በመቁ ጥቅምት ቀን ዓም በተሰጠ ትዕዛዝ አና በደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍቤት ሰበር ሰሚ ችሉት በሰመቁ ታሕሳስ ቀን ዓም በተሰጠ ትዕዛዝ የጸናዉ ዉሳኔ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ጸንቷል ኛ በስር ፍቤት የተጀመረዉ አፈጻጸም ለጊዜዉ ታግዶ እንዲቆይ ጥር ቀን ዓም የተሰጠዉ የእግድ ትዕዛዝ ተነስቷል ይጻፍ ኛ በዚህ ችሎት ለተደረገው ክርክር የወጣውን ወጪና ኪሳራ ግራቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ተመላሽ ብለናል የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት አጐ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ መስከረም ቀን ዓም ዳኞች ብርሃኑ አመነዉ በዕዉቀት በላይ አንዳሻዉ አዳነ ፃይሉ ነጋሽ እትመት አሠፋ አመልካች የቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማት እና ማኔጅመንት ጽቤት ተጠሪ አቶ ደገፉ ምሰኔ መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ለሰበር አቤቱታው መነሻ የሆነው ጉዳይ የአፈጻጸም ክርክርን የሚመለከት ነው ለአፈጻጸሙ መነሻ የሆነው ፍርድ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁ አመልካች ለተጠሪው የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ አዘጋጅቶ እንዲሰጣቸው በማለት የሰጠው ውሳኔ ነው የአሁን ተጠሪ ይህን ውሳኔ መነሻ በማድረግ ለከፈቱት የአፈጻጸም ክስ አመልካች በሰጠው መልስ ካርታው ሊሰጣቸው የሚገባው በአዋጅ ቁጥር መሠረት ወደ ሊዝ ስሪት በማስገባት በመሆኑ ተጠሪ ሊከፍሉት የሚገባ ክፍያ አለ በማለት ገልጂል ተጠሪ በበኩላቸው ጉዳዩ ሳይፈጸም የቆየው በአመልካች ችግር መሆኑን እና ከአዋጁ በፊት የተጀመሩ ጉዳዮች በቀድሞ ሕግ መሠረት ሊስተናገዱ የሚገባ መሆኑን በመግለጽ ተከራክረዋል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አፈጻጸሙን የመራው የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በግራቀኙ መካከል ያለውን የአፈጻጸም ክርክር መርምሮ ተጠሪ በተለያየ ጊዜ አዋጅ ቁጥር ከመውጣቱ በፊት አመልካች የይዞታ ማረጋገጫ አንዲሰጣቸው የጠየቁ መሆኑን አና ሊፈጸምላቸው እንዳልቻለ በመቁ ከተሰጠው ውሳኔ መገንዘብ የሚቻል በመሆኑ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታው ሊሰጣቸው የሚገባው በአዋጁ አንቀጽ መሠረት ሳይሆን በአንቀጽ መሠረት ነው ሲል ትዕዛዝ ሰጥቷል አመልካች በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኘት ለፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የይግባኝ አቤቱታ ያቀረበ ቢሆንም ይግባኙ የቀረበለት ፍቤት ግራቀኙን አከራክሮ የስር ፍቤት የሰጠውን ውሳኔ አጽንቷል የሰበር አቤቱታው የቀረበው ይህን ውሳኔ በመቃወም ሲሆን ይዘቱም ተጠሪ ካርታ የወሰዱበት ጊዜ እንጂ የጠየቁበት ጊዜ ወደ ሊዝ ስሪት ገብተው የሚስተናገዱበትን ጊዜ የማይወስን መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የካርታ መስተንግዶ ጠየቅኩ ያሉበት ጊዜ በአዋጅ ቁጥር ጊዜ ሲሆን በዚህ ወቅት አዋጅ ቁጥር እና የከተማ አስተዳደር መመሪያ ቁጥር በሰነድ አልባ የሚስተናገዱ አካላት ወደ ሊዝ ስሪት ስለሚገቡበት ሁኔታ እና የካርታ መስተንግዶ ስለሚያገኙበት አግባብ የተደነገገ ሆኖ ሳለ የስር ፍቤቶች ይህን አልፈው ተጠሪ ያለ ሊዝ ክፍያ እና ስሪት ካርታ እንዲሰጣቸው የሰጡት ውሳኔ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ሥሕተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል የሚል ነው የአመልካች የሰበር አቤቱታ ተመርምሮ የስር ፍቤት የሰጠው ውሳኔ ከአዋጅ ቁጥር አተገባበር አኳያ ለመመርመር ሲባል ጉዳዩ በዚህ ችሎት እንዲታይ ተደርጓል ለተጠሪ ጥሪ ተደርጎም ግራቀኙ በጽሑፍ እንዲከራከሩ ተደርጓል የተጠሪ መልስ ይዘት በአጭሩፁ አመልካች የገዛሁት እና ውሉ ተመዝግቦ ማስረጃ እንዲሰጠኝ የጠየቅኩት ንብረት ሰነድ አልባ አይደለምቤቱ በፍቃድ እና በፕላን የተሰራ እና በሻጭ ስም የተመዘገበ ነውአመልካች መስሪያ ቤት ጉዳዩ እንዳይፈጸም በማድረግ ሊዝ እስኪታወጅ አቆይቶታልጊዜው የተራዘመው በአመልካች ጥፋት እንጂ በተጠሪ ጥፋት አይደለምአመልካች ውሉን ያስገባሁት እና እንዲመዘገብልኝ የጠየቅኩት ከአዋጁ በፊት ስለሆነ ሊፈጸምልኝ የሚገባው ውሉን ባስገባሁበት ወቅት በነበረው ሕግ መሠረት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ነው በማለት መልስ ሰጥተዋል አመልካችም የሰበር አቤቱታውን በማጠናከር የመልስ መልስ ሰጥቷል የጉዳዩ አመጣጥ በአጭሩ ከላይ የተገለጸው ነው እኛም እንዲጣራ የተያዘውን ነጥብ ከግራቀኙ ክርክርለሰበር አቤቱታው መነሻ ከሆነው ውሳኔ እና ለጉዳዩ አግባብነት ካላቸው ሕጎች ጋር በማገናዘብ እንደሚከተለው መርምረነዋል ተጠሪ ንብረቱ በስማቸው ተመዝግቦ የባለቤትነት ማስረጃ እንዲሰጣቸው በማለት በአመልካች ላይ ክስ ያቀረቡት በመስከረም ወር ዓም መሆኑንጉዳዩ የቀረበለት የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁ በሰጠው ውሳኔ ተጠሪ ከ ዓም ጀምሮ ይፈጸምልኝ በማለት ሲመላለሱ የቆዩ በመሆኑ አመልካች ለተጠሪው የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ አዘጋጅቶ እንዲሰጣቸው በማለት ውሳኔ የሰጠ ቢሆንም ተጠሪ በየትኛው ሕግ መሠረት ሊስተናገዱ እንደሚገባ በውሳኔው ላይ ለይቶ ያላስቀመጠ መሆኑንተጠሪ ይህንኑ ውሳኔ መሠረት በማድረግ የአፈጻጸም ክስ የከፈቱ መሆኑን እና የስር ፍቤቶችም ተጠሪ ሊስተናገዱ የሚገባው በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት ነው በማለት የአፈጻጸም ትዕዛዝ የሰጡ መሆኑን ከክርክሩ ሒደት መገንዘብ ችለናል የከተማን ቦታ በሊዝ ስለመያዝ የወጣው አዋጅ ቁጥር አንቀጽ በነባር ይዞታ ላይ የሰፈረ ንብረት ባለቤትነት ከውርስ በስተቀር በማናቸውም መንገድ ለሌላ ሰው ከተላለፈ ንብረቱ የተላለፈለት ሰው የቦታው ባለይዞታ መሆን የሚችለው በሊዝ ስሪት መሰረት ነው በማለት ይደነግጋል የዚሁ አዋጅ አንቀጽ ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ቀደም ሲል ቀርበው በእንጥልጥል ላይ ያሉ የከተማ ቦታ ጥያቄዎችን በሚመለከት አዋጅ ከጸናበት ቀን ጀምሮ ባሉት ሦስት ወራት ጊዜ ውስጥ በቀድሞ ሕግ መሠረት ውሳኔ መስጠት አለባቸው በማለት ይደነግጋል የስር ፍቤቶች ተጠሪ አዋጅ ቁጥር ከመውጣቱ በፊት አመልካች የይዞታ ማረጋገጫ እንዲሰጣቸው የጠየቁ በመሆኑ እና ሊፈጸምላቸው ያልቻለ በመሆኑ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታው ሊሰጣቸው የሚገባው በአዋጁ አንቀጽ መሠረት ሳይሆን በአንቀጽ መሠረት ነው ከሚል መደምደሚያ ላይ የደረሱ ቢሆንም ተጠሪ አስተዳደሩ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ጥያቄዬን አልተፈጸመልኝም በማለት በመደበኛው ፍቤት ክስ ያቀረቡ በመሆነ የተጠሪ ጉዳይ ከአስተዳደሩ እጅ መውጣቱን የሚያሳይ እንጂ በአዋጁ አንቀጽ በተገለጸው አግባብ ቀደም ሲል ቀርቦ በእንጥልጥል ላይ እንደነበረ ሊወሰድ የሚገባ ሆኖ አላገኘነውም በሌላ በኩል ተጠሪ ክስ ያቀረቡት አዋጅ ቁጥር ከወጣ በላ በ ዓም ሲሆን ጉዳዩ የቀረበለት ፍቤት ውሳኔ የሰጠውም ተጠቃሹ አዋጅ በስራ ላይ እያለ በመሆኑ የተጠሪ ጉዳይ ሊስተናገድ የሚገባው በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት ሳይሆን በአዋጁ አንቀጽ በሊዝ ስሪት መሠረት ነው የስር ፍቤቶችም ጉዳዩን በዚህ አግባብ በማየት መወሰን ሲገባቸው ተጠሪ ሊስተናገዱ የሚገባው በአዋጁ አንቀጽ መሠረት ነው በማለት የሰጡት ውሳኔ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ሥሕተት የተፈጸመበት ሆኖ አግኝተነዋል በዚህም ምክንያት ተከታዩን ውሳኔ ሰጥተናል ውሳኔ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍቤት በመቁ መጋቢት ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔየፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመቁ ጥቅምት ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔ በፍብሥሥሕቁ መሠረት ተሽሯል ከላይ በፍርድ ሐተታው ላይ በተገለጸው ምክንያት አፈጻጸሙ ሊቀጥል የሚገባው በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት ሳይሆን በአዋጁ አንቀጽ በሊዝ ስሪት መሠረት ነው ብለናል በዚህ ችሎት ለተደረገው ክርክር የወጣውን ወጪ ግራቀኙ የየራሣቸውን ይቻሉ ጥር ቀን ዓም በመዝገቡ የተሰጠው የዕግድ ትዕዛዝ ተነስቷል ይጻፍ መዝገቡ ውሳኔ ስላገኘ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ካየ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ሕዳር ቀን ዓም ዳኞች ብርሃኑ አመነዉ በዕዉቀት በላይ አንዳሻዉ አዳነ ፃይሉ ነጋሽ እትመት አሠፋ አመልካች ኢትዮ ቴሌኮም ሠራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር የሕብረት ሥራ ማሕበር ተጠሪዎች እነ ሰለሞን እሸቴ ሰዎች መዝገቡ ለምርመራ የተቀጠረ ነው። ተጠሪ አሁን ጥፋተኛ የተባለበት የህግ ድንጋጌ በቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር የወንጀል ደረጃና እርከን የወጣለት ስለሆነ የገንዘብ መጠት ብር አራት ሚሊዮን አምስት መቶ አስራ ሰባት ሺህ አንድ መቶ አስራ ሰባት ብር ከሰማንያ አንድ ሳንቲም በመሆነ የእስራት ቅጣት መነሻ አርከነኑ የገንዘብ መቀጮ መነሻ አርከኑ ይሆናል በከሳሽ አመልካች በኩል የቀረበ እና በስር ፍርድ ቤት በማስረጃ የተረጋገጠ ማክበጃ ስለሌለ የቅጣት እርከኑ ከተያዘው መነሻ እርከን ከፍ አላለም በሌላ በኩል ተጠሪ የቀድሞ ሪከርድ የሌላቸው መሆኑ እና ቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆናቸው ሁለት የቅጣት ማቅለያ የተያዘላቸው በመሆኑ የእስራት ቅጣት መነሻ እርከኑ ከእርከን ወደ እርከን እንዲሁም የገንዘብ መቀጮ መነሻ እርከኑ ወደ እርከን ዝቅ ያደርገዋል ስለሆነም በአርከን ስር ባለው ፍቅድ ስልጣን ከ አመት እስከ አመት ስለሆነ ተጠሪ ጥፋተኛ በተባለበት የህግ ድንጋጌ ያስተምረዋል የተባለውን የአምስት አመት ፅኑ እስራት እና የአራት ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ሊቀጣ ይገባል ብለናል ሲጠቃለል የስር ፍርድ ቤቶች ተጠሪ ላይ የሰጡት የጥፋተኝነት እና የቅጣት ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት በመሆኑ የሚከተለው ውሳኔ ተሰጥቷል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ሠአ ውሳኔ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር ሰኔ ቀን ዓም በዋለው ችሎት ውሳኔ ተሰጥቶ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር መስከረም ቀን ዓም የፀናው የጥፋተኝነት እና የቅጣት ውሳኔ በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር ለወ መሰረት ተሻሸሏል ተጠሪ ክስ በቀረበበት የህግ ድንጋጌ ጥፋተኛ የተባለ በመሆኑ የስር ፍርድ ቤቶች የሰጡት የቅጣት ውሳኔ በማሻሻል ተጠሪ በዚህ ጉዳይ የታሰሩበት ጊዜ ሁሉ የሚታሰብላቸው ሆኖ በአምስት አመት ፅኑ እስራት እና በአራት ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እአንዲቀጡ ወስነናል የፌዴራል ፖሊስ ተጠሪ በሚገኙበት በመያዝ ለሚመለከተው ማርሚያ ቤት እንዲያሰረክብ ማረሚያ ቤቱም ከፌዴራል ፖሊስ ተረክቦ ተጠሪን በጉዳዩ ላይ ቀድሞ የታሰሩበት ጊዜ ካለ ታሳቢ በማድረግ የተወሰነውን የአምስት ዓመት ጽኑ አስራት ቅጣትን ተከታትሎ እንዲያስፈጽም ብለናል የገንዘብ ቅጣቱ የሚመለከተው የፋይናንስ ክፍል ያስፈፅም ብለናል ይፃፍ መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰመቁ ሐምሌ ቀን ዓም ዳኞች ብርሃኑ አመነዉ በዕዉቀት በላይ አንዳሻዉ አዳነ ፃይሉ ነጋሽ እትመት አሠፋ አመልካች በትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፍትሕ ቢሮ ዓቃቤሕግአልቀረቡም ተጠሪ አቶ ንጉስ ሀይሉአልቀረበም መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ ጉዳዩ ወንጀል ነው የአሁን አመልካች ተጠሪው የአዋጅ ቁጥር አንቀጽ ለ ድንጋጌን በመተላለፍ ማንም ሳይፈቅድለት በቀን ዓም ከቀኑ ሠዓት በሐወልቲ ክፍለከተማ ቀጠና ስፋቱ ሜ የሆነ የመንግሥት መሬት ጨምሮ ቤት ስለሰራበት በፈጸመው የከተማ ቦታ ያለአግባብ መያዝ ወንጀል ተከሷል በማለት ያቀረበውን ክስ የተመለከተው በትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የሐወልቲ ፍቤት ተጠሪን በተከሰሰበት የሕግ አንቀጽ ጥፋተኛ ሆኖ ስላገኘው ቅጣቱን በቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር በማስላት በሠባት ዓመት ጽነ እሥራት እና በብር አርባ ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ሲል ወስኗል ተጠሪ በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኘት ለመቐለ ከተማ ከፍተኛ ፍቤት ይግባኝ ሰሚ ችሉት የይግባኝ አቤቱታ አቅርቧል ይግባኙ የቀረበለት ፍቤት ግራቀኙን ካከራከረ በኋላ ተጠሪ የሰሩትን የድንጋይ አጥር እንዲያፈርሱ በቃል የተነገራቸው ከመሆኑ በቀር የተሰጣቸው ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የ ቀን የጽሑፍ ማሥጠንቀቂያ የለምአዋጁ የሰባት ቀን የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ መሰጠት እንዳለበት የሚደነግግ ሆኖ ሳለ እና ተጠሪ በቃል በተሰጣቸው ማስጠንቀቂያ መሠረት የሰሩትን የድንጋይ አጥር አፍርሰው ሳለ የሥር ፍቤት በአዋጁ የተቀመጠው ማሥጠንቀቂያ የመስጠት ቅድመሁኔታ ባልተሟላበት ሁኔታ የሰጠው የጥፋተኝነት እና የቅጣት ውሳኔ ተገቢ አይደለም በማለት የሥር ፍቤት የሰጠውን ውሳኔ በመሻር ተጠሪን በነጻ አሰናብቷል አመልካች በበኩሉ በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኘት በየደረጃው ላሉ የክልሉ ፍቤቶቸ አቤቱታ ያቀረበ ቢሆንም አቤቱታው የቀረበላቸው ፍቤቶች የሥር ይግባኝ ሰሚው ከፍተኛ ፍቤት የሰጠውን ውሳኔ አጽንተዋል የሰበር አቤቱታው የቀረበው ይህን ውሳኔ በመቃወም ነው የአመልካች የሰበር አቤቱታ መሠረታዊ ይዘትም አስቀድሞ የመሬት ወረራ ወንጀል ለመስራት አስቦ መሬትን የወረረ ሰው ማሥጠንቀቂያ ካልተሰጠው በቀር በወንጀል ጥፋተኛ ሊባል አይገባም የሚል ድንጋጌ በአዋጁ ባልተቀመጠበት ሁኔታ ይግባኝ ሰሚው የሥር ፍቤቶች ለተጠሪ ማሥጠንቀቂያ አልተሰጠም በሚል ምክንያት ተጠሪን በነጻ በማሰናበት የሰጡት ውሳኔ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ሥሕተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል የሚል ነው የአመልካች የሰበር አቤቱታ ተመርምሮ የአሁን ተጠሪ የከተማ ይዞታውን የያዘው ከሕግ ውጪ መሆኑ በተረጋገጠበት ሁኔታ በአዋጅ ቁጥር አንቀጽ መሠረት ማሥጠንቀቂያ ባልተሠጠበት ሁኔታ ጥፋተኛ ሊባል አይገባም በማለት የመወሰኑን አግባብነት ለመመርመር ሲባል ጉዳዩ በዚህ ችሎት እንዲታይ ተደርጓል ለተጠሪ ጥሪ ተደርጎም ግራቀኙ በጽሑፍ እንዲከራከሩ ተደርዓጓል የተጠሪ መልስ ይዘት በአጭሩፁ በአዋጁ አንቀጽ እና የተቀመጠው ማስጠንቀቂያ የመስጠት ግዴታ በአዋጁ አንቀጽ ለ የተቀመጠው ቅጣት ክብደት አኳያ ተጠሪን የመሰሉ ሰዎች ማስጠንቀቂያ በመስጠት አሥተዳደራዊ መፍትሔ ለማምጣት እና በማስጠንቀቂያ ከተግባሩ አንዲቆጠብ በመሆኑ የሥር ፍቤቶች ይህንኑ በመገንዘ ተጠሪን በነጻ ማሰናበታቸው ተገቢ ነውይህ የሚታለፍ ከሆነም ተጠሪ ለጊዜው የሰራሁትን አጥር ያፈረስኩ እአና የፈጸምኩት ተግባርም ቀላል ስለሆነ ጥፋተኛ ልባል የሚገባው በወንጀል ሕግ አንቀጽ ከመግሥት ፈቃድ ውጪ የመንግሥትን ቦታ መያዝ ወንጀል በሚል ሊሆን ይገባልይህ የሚታለፍ ከሆነም ይዞታው ከባለቤቴ ይዞታ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ አጠገብ የሚገኘውን ቦታ ክረምቱ እስኪያልፍ በሚል ለማገዶ የተሰራ እንጂ ቦታውን ለማካተት ስላልሆነ የአመልካች አቤቱታ ውድቅ ሊደረግ ይገባልቅጣቱም ቀሉ ሊወሰን ይገባል የሚል ነው የጉዳዩ አመጣጥ በአጭሩ ከላይ የተገለጸው ነው ይህ ችሎትም ጉዳዩ ለሰበር ይቅረብ ሲባል እንዲጣራ የተያዘውን ነጥብ ከግራቀኙ ክርክርለሰበር አቤቱታው መነሻ ከሆነው ውሳኔ እና ለጉዳዩ አግባብነት ካላቸው ሕጎች ጋር በማገናዘብ እንደሚከተለው መርምረነዋል ተጠሪ የአዋጁን አንቀጽ ከአዋሳኛቸው ጎን ያለውን የመንግሥት ቦታ ወደ ራሣቸው ይዞታ በመቀላቀል የድንጋይ አጥር የሰሩበት መሆኑ በወረዳው ፍቤት የተረጋገጠ ፍሬነገር ነው የከተማን ቦታ በሊዝ ስለመያዝ የወጣው አዋጅ ቁጥር አንቀጽ ለ ማንም ሰው አዋጁን ወይም በአዋጁ መሠረት የወጡ ደንቦችን ወይም መመሪያዎችን በመተላለፍ የከተማ ቦታን አጥሮ ከያዘ ግንባታ ካካሄደበት ወይም ከአዋሳኝ ይዞታው ጋር ከቀላቀለ ከሠባት እሥከ አሥራ አምሥት ዓመት በሚደርስ ኑ አሥራት እና ከብር እሥከ በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል በማለት ይደነግጋል የአዋጁ አንቀጽ አግባብ ያለው አካል ከቦታው ለሚነሳው ንብረት ተመጣጣኝ ካሣ በቅድሚያ እንዲከፈል በማድረግ የከተማ ቦታ ይዞታን ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የማስለቀቅ እና የመረከብ ሥልጣን ይኖረዋል በማለት ይነግጋል የዚሁ አንቀጽ ንዑስ ቁጥር አግባብ ያለው አካል በሕገወጥ መንገድ የተያዘን የከተማ ቦታን በአዋጁ አንቀጽ መሠረት የማስለቀቂያ ትዕዛዝ መስጠት እና ካሣ መክፈል ሳያስፈልግ የሠባት የሥራ ቀናት የጽሑፍ ማሥጠንቀቂያ ብቻ ለባለይዞታው በአካል በመስጠት ወይም በቦታው በሰፈረው ንብረት ላይ በመለጠፍ የማስለቀቅ ሥልጣን ይኖረዋል በማለት ይደነግጋል የሥር ይግባኝ ሰሚው ፍቤቶች ተጠሪ የሰሩትን የድንጋይ አጥር እንዲያፈርሱ በቃል የተነገራቸው ከመሆኑ በቀር የተሰጣቸው የ ቀን የጽሑፍ ማሥጠንቀቂያ የለምበአዋጁ አንቀጽ ላይ የተቀመጠው የሰባት ቀናት የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ የመስጠት ግዴታ ባልተሟላበት ሁኔታ እና ተጠሪ በቃል በተሰጣቸው ማስጠንቀቂያ መሠረት የሰሩትን የድንጋይ አጥር ባፈረሱበት ሁኔታ ጥፋተኛ መባላቸው ተገቢ አይደለም ከሚል ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ መደምደሚያ ላይ የደረሱ ቢሆንም በአዋጁ አንቀጽ ላይ አግባብ ያለው አካል በሕገወጥ መንገድ የተያዘን የከተማ ቦታን በአዋጁ አንቀጽ መሠረት የማስለቀቂያ ትፅዛዝ መስጠት እና ካሣ መክፈል ሳያስፈልግ የሠባት የሥራ ቀናት የጽሑፍ ማሥጠንቀቂያ ብቻ ለባለይዞታው በአካል በመስጠት ወይም በቦታው በሰፈረው ንብረት ላይ በመለጠፍ የማስለቀቅ ሥልጣን ይኖረዋል በማለት የተቀመጠው ሀሳብ በአዋጁ አንቀጽ መሠረት በሕጋዊ መንገድ ለተያዙ የከተማ ቦታዎችን ለማስለቀቅ የተቀመጠውን የማስለቀቂያ ትዕዛዝ የመስጠት እና ካሣ የመክፈል ሥርዓት ማሟላት ሳያስፈልግ በሕገወጥ መንገድ የተያዘን የከተማ ቦታን ማስለቀቅ የሚቻልበትን ሥርዓት የሚደነግግ እንጂ የከተማ ቦታን ወሮ ለያዘ ሰው የወንጀል ሀላፊነትን የሚያስቀር አይደለም በመሆኑም የሥር ይግባኝ ሰሚ ፍቤቶች የአዋጁን አንቀጽ ድንጋጌን ያለአግባብ በመተርጎም ለተጠሪ የተሰጠው የሰባት ቀናት የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ በሌለበት ሁኔታ ተጠሪ ጥፋተኛ ሊባል አይገባም በማለት የሰጡት ውሳኔ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ሥሕተት የተፈጸመበት ሆኖ አግኝተነዋል በዚህም ምክንያት ተከታዩን ውሳኔ ሰጥተናል ውሳኔ በትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የመቐለ ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ሐምሌ ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔየክልሉ ጠቅላይ ፍቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመቁ ግንቦት ቀን ዓም የሰጠው ውሳኔየክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት በመቁ ጥቅምት ቀን ዓም የሰጠው ትዕዛዝ በወመሥሥሕቁ ለሪ መሠረት ተሽራል ከላይ በፍርድ ሐተታው ላይ በተገለጸው ምክንያት የሐወልቲ ወረዳ ፍቤት በመቁ ሠኔ ቀን ዓም የሰጠው የጥፋተኝነት ውሳኔ በወመሥሥሕቁ ለ መሠረት ጸንቷል የመቐለ ከተማ ከፍተኛ ፍቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት አመልካችን በነጻ በማሰናበት የሰጠው ውሳኔ የተሻረ መሆኑን አውቆ የቅጣት ውሳኔውን በተመለከተ መርምሮ ተገቢውን እንዲወስን ጉዳዩ ተመልሶለታል መዝገቡ ውሳኔ ስላገኘ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ የማይነበብ የአምስት ዳኞች ፊርማ አለበት ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ የሰበር መቁ ጥቅምት ቀን ዓም ዳኞችብርፃኑ አመነዉ በዕዉቀት በላይ እንደሻዉ አዳነ ፃይሉ ነጋሽ እትመት አሰፋ አመልካች አማረ ረታ ተጠሪ የፌደራል ጠአቃቤ ህግ መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል ፍርድ በዚህ መዝገብ የቀረበዉ ጉዳይ በወንጀል ጉዳይ ፍርድ ከተሰጠ በጊላ አዲስ የወጣዉ ህግ ተከሳሹን የሚጠቅም በሆነ ጊዜ እንዴት ይፈጸማል የሜል ነዉለዚህ ሰበር አቤቱታ ምክንያት የሆነዉ ጉዳይ አመልካች በጉሙሩክ አዋጅ ቁ ስር ጥፋተኛ ተብሎ የቅጣት ዉሳኔ ተላልፎበት በማረሚያ ቤት ቅጣቱን እየፈጸመ እያለ አዲስ የወጣዉ የጉሙሩክ አዋጅ ቁ ለተመሳሳይ ጥፋት የደነገገዉ ቅጣት አመልካችን የሚጠቅም ስለሆነ በአዲሱ አዋጅ መሰረት ቅጣቱ እንዲታይለት ለፌዴራል የመደረጃ ፍርድ ቤት አቤቱታ አቅርቦ ተቀባይነት ባለማግኘቱና ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ይህንኑ በማጽናቱ ነዉ የአመልካች ሰበር አቤቱታ ይዘት ባጭሩ አመልካች አዋጅ ቁ አንቀጽ ሐእና በመተላለፍ እሽጎችን መፍታትና ምልክቶችን ማንሳት እንዲሁም አንቀጽ በመተላለፍ የማጓጓዝ ፃላፊነት ባለመወጣት ጥፋተኛ ተብሎ በፌዴራል የመደረጃ ፍርድ ቤት በብር እና ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ስለመወሰኑና በዚህ ቅር ተሰኝቶ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ አቅርቦ ፍርድ ቤቱ ቅጣቱን ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ብቻ በማሻሻል ዓመት ጽኑ አስራት እንዲቀጣ መወሰኑን ይህንኑ ቅጣት እየፈጸመ አያለ አዲስ የወጣዉ አዋጅ ቁ በዚህ ጉዳይ ከቀድሞ አዋጅ ያነሰ ቅጣት የሚያስቀጣ በመሆኑ በኢፌዲሪ ሕግ መንግስት አንቀጽ መሰረት አዲሱ አዋጅ ተፈጻሚ እንዲሆን አቤቱታ ማቅረቡንና የስር ፍርድ ቤቶች ይህንኑ ተቀብለዉ ቅጣቱን ማሻሻል ሲገባቸዉ አቤቱታዉን አናስተናግድም ማለታቸዉ የህግ ስህተት ስለሆነ እንዲታረም የሚል ነዉ የአመልካች አቤቱታ ተመርምሮ ጉዳዩን ከህገ መንግስቱ አንቀጽ እና ከወንጀል ህጉ አንቀጽ አና እንዲሁም ከአዋጅ ቁ አንቀጽ እና አንጻር ለመመርመር እንዲቻል ጭብጥ ተይዞ አቃቤ ህግ መልስ እንዲሰጥ ተደርጓልበአቃቤ ህግ በኩል የቀረበዉ መልስ ባጭሩ በአዲሱ አዋጅ መሰረት መነሻ ቅጣቱ ተከሳሽን የሚጠቅም መሆኑ ታይቶ ማሻሻያ ቢደረግለት ተቃዉሞ እንደሌለዉ ገልዷጂል የጉዳዩ አመጣጥ ከላይ ባጭሩ የተገለጸ ሲሆን እኛም አቤቱታዉ ለሰበር ያስቀርባል ሲባል የተያዘዉን ጭብጥ መሰረት በማድረግ አግባብነት ካለዉ ህግ ጋር በማገናዘብ መርምረናልመዝገቡን መርምረን እንደተገነዘብነዉ በወንጀል ጉዳይ የወንጀል ህግ ወደ ኋላ ተመልሶ እንዲሰራ የሚደረገዉ መቼ ነዉ እንዲህ ዓይነት አቤቱታስ እስከ መቼ መቅረብ ይችላል የሚሉት ነጥቦች መታየት ያለባቸዉ ሆኖ አግኝተናል በመሰረቱ የወንጀል ህግ ወደኋላ ተመልሶ የማይሰራ መሆነ በሀገራችን ህገ መንግስት አና በወንጀል ህግ በግልጽ የተደነገገ ከመሆኑም በተጨማሪ በዓለም አቀፍ ስምምነቶች ተደንግጎ የሚገኝ አለም አቀፍ ቅቡልነት ያለዉ መርሆ መሆኑ ይታወቃልየኢፌዲሪህገ መንግስት አንቀጽ የኢፌዲሪየወንጀል ህግ አንቀጽ እንዲሁም ዓለም አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ስምምነት አንቀጽይመለከታልከዚህ መርህ ልዩ ሁኔታ ተብሎ የተደነገገዉ ድርጊቱ ከተፈጸመ በሏላ የወጣዉ ህግ ለተከሳሹ ወይም ለተቀጣዉ ሰዉ ጠቃሚ ሆኖ ከተገኘ ከድርጊቱ በኋላ የወጣዉ ህግ ተፈጻሚ እንዲሆን የማድረግ ጉዳይ ነዉ የኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀጽየወንጀል ህጉ አንቀጽ እንዲሁም የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች አለም አቀፍ ስምምነት አንቀጽ ሁለተኛ ፓራግራፍ ይመለከታል ይህም የሚያሳየዉ ህጉ ተከሳሽን መብትና ጥቅም በተሻለ ሁኔታ ማስከበርን መሰረት ያደረገ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ስለመሆኑና በወንጀል ጉዳይ ህግ መተርጎም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ተከሳሽን በሚጠቅም አኳኋን ሊተረጎም ይገባል የሚለዉን ቅቡልነት ያለዉ የወንጀል ህግ አተረጓጎም መርህ የተከተለ አንደሆነ መገንዘብ ይቻላል ስለዚህም ቅጣትን በሚመለከት አዲሱ የወንጀል ህግ ከመውጣቱ በፊት በተፈፀመ ወንጀል ከተፈረደበት እና ሆኖም ግን ወንጀሉ በተፈፀመበት ጊዜ ስራ ላይ ከነበረው ወንጀል ህግ ይልቅ አዲሱ ህግ ለተከሳሹ ቅጣትን የሚያቀልለትና ተከሳሹን የሚጠቅም ሆኖ ከተገኘ ይፄው በአዲሱ ህግ ላይ ያለው ቅጣት የሚፈጽምበት ስለመሆኑ ከወንጀል ህጉ ቁ ድንጋጌ ይዘት የሚያስገነዝብ ስለመሆኑ ሰበር ችሎቱ በመቁ ዉሳኔ ሰጥቷልበሌላ በኩል አዲስ የወጣዉ ህግ የቀድሞዉን ህግ የሻረዉ እንደሆነና በቀድሞ ህግ ወንጀል የነበረዉ ድርጊት በአዲሱ ህግ ይኸዉ ድርጊት ወንጀልነቱ ቀሪ ከሆነ ወይም የማያሥቀጣ ከሆነ በቀድሞ ህግ ተፈርዶበት ቅጣቱ እንደማይፈጸም ወይም እየተፈጸመ ከሆነም ቅጣቱ አፈጻጸም ወዲያዉኑ እንደሚቋረጥ የወንጀል ህግ አንቀጽ በግልጽ ደንግጓል ስለሆነም ከእነዚህ ድንጋጌዎች ይዘት መገንዘብ የሚቻለዉ ጊላ የወጣዉ የወንጀል ህግ ተከሳሹን ወይም የተቀጣዉን ሰዉ የሚጠቅም መሆን አለመሆኑ መመዘኛ ተደርጎ መታየት ያለበት ስለመሆኑ ነዉኋላ የወጣዉ ህግ የቀድሞዉን ህግ በመሻር የድርጊቱን ወንጀልነት ቀሪ በማድረጉ በቀድሞ ህግ የተሰጠዉ ፍርድ ቀሪ ነዉ በሚል በግልጽ ህጉ ደንግጎ እያለ ኋላ የወጣዉ ህግ ቅጣት ማቅለሉን መሰረት በማድረግ ተቀጪዉ ያቀረበዉ አቤቱታ ሊስተናገድ አይገባም የሚለዉ የስር ፍርድ ቤት ዉሳኔ የህገ መንግስቱን አንቀጽ እና የወንጀል ህጉን ልዩ ሁኔታ አንቀጽ ያላገናዘበ ሆኖ አግኝተናል በሁለተኛ ደረጃ መታየት ያለበት ጉዳይ እንዲህ ዓይነት ሁኔታ ሲያጋጥም ተከሳሹ ወይም ተቀጪዉ አቤቱታ ማቅረብ የሚጠበቅበት የጊዜ ገደብ መኖር አለመኖሩ ላይ ነዉበመሠረቱ የወመሕሥሥ ለይግባኝ ማቅረቢያና ተያያዥ ጉዳዮች የጊዜ ገደብ ቢያስቀምጥም ፍርድ አግኝቶ የተዘጋ መዝገብ በኃላ አንደገና መከፈቱ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በምን ያህል ጊዜ ዉስጥ አቤቱታ ሊቀርብበት እንደሚገባ በሕግ የጊዜ ገደብ አልተቀመጠም ይህ በሚሆንበት ወቅት የጊዜ ገደቡ የሚወሰነዉ የጉዳዩን ሁኔታዎችና የአቤቱታዉን ዓይነት በመመልከት እንጂ ከተወሰነ ጊዜ በኃላ የቀረበዉ አቤቱታ ህለ ፐ ፍር ዐዐሃ ፎቲ ተቀባይነት የለዉም በሚል ድምዳሜ ላይ በመድረስ አይደለምከዚህ በተጨማሪ አመልካች የኢፌዴሪ ሕገመንግስት አንቀጽ የወሕአንቀጽ እና ን መሠረት በማድረግ አቤቱታ ያቀረበበት ጉዳይ በባህሪዉ እንደመደበኛ የክርክር ጉዳይ የሚታይ ሳይሆን አቤቱታ በቀረበ ጊዜ ሊስተናገድ የሚችል መሆኑን ህጉ ግልጽ የጊዜ ገደብ አለማስቀመጡ የሚያሳይ ነዉ በዚህ መዝገብ በተያዘዉ ጉዳይ አመልካች በቀድሞ የጉምሩክ አዋጅ ቁ አንቀጽ ሐ እና እንዲሁም አንቀጽ በተደራራቢ ወንጀል ተከሶ ጥፋተኛነትና የቅጣት ዉሳኔ ተሰጥቶ ቅጣቱን በመፈጸም ላይ እያለ አዲስ የወጣዉ የጉምሩክ አዋጅ ቁ አንቀጽ እና የድርጊቱን አስቀጪነት እንዳለ ይዞ ነገር ግን ቅጣቱን በማሻሻሉ አመልካች የኋለኛዉ ህግ ይጠቅመኛል በሚል ለስር ፍርድ ቤት አቤቱታ ሲያቀርብ ፍርድ ቤቱ እንዲህ ዓይነት አቤቱታ ሊስተናገድ የሚችልበት አግባብ የለም በማለት የሰጠዉ ዉሳኔ ከላይ በዝርዝር የተመለከተዉን ህገ መንግስታዊ ድንጋጌ እና የወንጀል ህጉን ዓላማና ይዘት ያላገናዘበ ስለሆነ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል ብለናልበዚሁ አግባብ ተከታዩን ዉሳኔ ሰጥተናል ዉሳኔ ኛየፌዴራል የመደረጃ ፍቤት በመቁ ላይ በ ዓም የሰጠዉ ትእዛዝ አና ይህንኑ በማጽናት የፌዴራል ከፍተኛ ፍቤት በመቁ ላይ በ ዓም የሰጠዉ ዉሳኔ በመሰረዝ አመልካች ያቀረበዉ አቤቱታ ተመርምሮ ተገቢዉ ዉሳኔ እንዲሰጥ መዝገቡን በወመስስህግ ቁ ሀ መሰረት ለፌዴራል የመደረጃ ፍርድ ቤት መልሰናል ።