Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ገበሬ ኔ ጫዴ ና እንዲሁም ለሥርዓተቅዳሴ የተዘጋጀውን ምግብና መጠጥ ለሙሽራይቱ ማቅረብ ነው የሥራ ድርሻው ሁለቱ ሚዜዎች ለሙሽራይቱ አባት በሙሽራው አማካይነት እንዲተዋወቁ ሲደረግ የከበቡሸሽ አባት «ሚዜዎችህ እነማን ናቸው። ባለ አንድ ዘርፍ የዘር ሐረግ አቆጣጠር እና አክራሪ ባሕርይ ከነበረው የጋብቻ ሥነሥርዓታቸው ጋር የተያያዘው ባህል የመኖር ሕልውናው ለረዥም ጊዜ እንደማይቆይ በግልጽ እየታዬ መጣ እኤአ በ ዓም አምስት መቶ ያህል አረማዋዊ ኦሪታዌ ቅማንቶች በዕምነታቸው ፀንተው የቆዩ ቢሆንም በሚቀጥሉት ሠላሣ ዓመታት ጊዜ ውስጥ በመርሳት በብዙ ሚሊዮን በሚቆጠረው የአማራው ብሔረሰብ ባህሳቸው ተውጦ ጠቅላሳ ውህደት እንደሚፈጠር አያጠራጥርም በአሁኑ ጊዜ በክርስትና ሃይማኖት የተጠመቁት «ቅማንት» አየተባሉ ቢጠሩም ይህ የመታወቂያ ስም ሙሉ በሙሉ ከአማራው ጋር በማኅበራዊ ኑሮ ረገድ መጠነኛ የሆነ ልዩነት አላቸው በባህል ግን ይህን ያህል የጐላ ልዩነት የላቸውም በክርስቲያን ቅማንቶችና በአማራው መካከል ዖለው አነስተኛ ማኅበሪዊ ልዩነት ባዕድ ያሆኑትን ሕዝቦች ከማግለል የባህል ባሕርይ የመነጨ ሳይሆን በጋብቻ ረገድ በሚያጋጥሙ ችግሮች ምክንያት ነው።
ቅማንቶች አርሶ አደሮች ናቸው ይህንን ሊያሰኝ ያስቻለው እርሻ እያረሱ ከሚያመርቱት የሚተርፋቸውን በገበያ ላይ በመሸጥ ግብር በመክፈል ከላይ እስከ ታች ለተዘረጋው የኢትዮጵያ የአስተዳደር መዋቅር እንዲንቀሳቀስ አስተዋጽኦ ስለሚያደርጉ ነው የኢትዮጵያ ሥልጣኑ በሚዲተራንያንና በቅርብ ምሥራቅ አካባቢ በቅድመ ኢንዱስትሪ ዘመን ከስድስት ሺህ ዓመት በፊት በምዕራብ እስያ የእርሻ አብዮት ከተከሰተ በኋላ ወደ ደቡብ ቀስ በቀስ እየተስፋፋ የመጣው የሥልጣኔ ተቀጽሳ አካል ነው ነገር ግን ይህ ዓይነት ሥልጣኔ ወደ ኢትዮጵያ ሊሰራጭ የቻለው ከሦስት ሺህ ዓመት በፊት ትንሽ ቀደም ብሎ አንደሆነ ይታወቃል በዚህና በሌሉች ምክንያቶች የቅማንት ሥልጣኔ እኛ ካለን ዘመናዊ የኢንዱስትሪያል ከተማ ሥልጣኔ አስቀድሞ የነበረውን የኀብረ ተሰብ ሥልጣኑ የሚወክል ነው ቅማንትን ማጥናት ማለት ብዙ ጥናት ያልተካሄደበትንና ባልታወቀችው ኢትዮጵያ የተካሄደውን የባህል ለውጥ ሂደት አንድናውቅ የሚረዳን ከመሆኑም በላይ በመካከለኛው ምሥራቅና በሰሜን አፍሪካ የአስልምና ሃይማኖት ከመምጣቱ በፊት የነበረው የክርስቲያን ሥልጣኒ ሳይጠፋ የቆየበትን ብቸኛ አካባቢ ለማወቅ የሚያስችለን ይሆናል ከሁሉም በላይ ደግሞ ቅማንትን ማጥናት ማለት ከብዙዎቹ ኀብረተሰቦች መካከል አነስተኛ አርሶ አደሮች በሚካሄደው ዓለም አቀፍ ዘመናዊ ሥልጣኔና የኢንዱስ ትሪዎች እድገት ተፅፅኖ ሳይለውጣቸው እንዴት አንደቆዩ ለማወቅ ይረዳናል አሁንም ቢሆን ቅማንት ጉልህ የሆነ የባህል ለውጥ እያደረገ መሆኑ ቢታወቅም ለውጡ የምዕራባውያንን የባህል ናሙና የተከተለ ሳይሆን በአካባቢያቸው የሚኖረው የአማራ ገበሬ የባህል ለውጥ ሂደቶችን የተከተለ ነው የቅድመ ኢንዱስትሪ ሥልጣዬ ማኅበራዊ ኑሮ የበለጠ ውስብስብና በቴክኖሎጅ ኋላቀር ከሆኑት አዳኞች ፍራፍሬ ለቃሚ ዎችና በጓሮ እርሻ ከሚተዳደሩት ማኅበረሰብ በጣም የላቀ ነው የከተሞች መቆርቆር የሥነጽሑኩኡፍ ማቆጥቆጥ በማረሻ ማረስ ብረት ማቅለጥ የመታሰቢያ ሕንፃዎች መገንባት ዓይነተኛ መገለጫዎች ሲሆኑ ቢያንስ ሁለት የኀብረተሰብ መደቦች ይኖሩታል የኀብረ ተሰብ መደቦች ይኖራሉ ስንል በአንድ በኩል ታላቅ ባሕል ያለው ኀብረተሰብ የተባለው ባህሉ ያደገውና የነቃው በከተማ ነዋሪ የሆነው ክፍል ሲሆን ሌላው ደግሞ አነስተኛ ባህል ያለው ገጠሬውን አርሶ አደር የእጅ ሙያተኛውን ወይም በሂደት በታለቁ ባህል ሊታቀፉ ያልቻሉትን የከተማ ነዋሪዎችን ያጠቃልላል በፖለቲካ የተደራጀ ሥልጣኔ ወደ መንግሥት ወይም መንግሥታት በሚለወጥበት ወቅት ሥልጣን የያዘውና የነቃው ክፍል ሌሎች ያልነቁትን እንደገበሬው ያሉትን ኅብረተሰቦች ኤሙ መመመ ጨ የጁ ተቆጣጥሮ ይመራል ያስተዳ ድራል በአፀፋው ደሣሞ ገበራ ከሀብቱና ከጉልበቱ ለገዥው መደብ ማበርከት ግደታ አለበት በፖለቲካ በኩል ቅማንት ባለፉት ስድስት መሥዮፐ ዓመታት የራሳቸው የሆነ የገበፊ መደብ ባላቸው በአማራና በትግሬው የገዥ መደብ ሥር ሲተዳደር ቢቆይም በማይናት ደረጃ የራሱ የሆነ የውስጥ የፖለቲካ ነፃነት ነበረው ይህም በመሆኑ የራሱ የሆነ በተለያየ እርከን የተደራጀ የሃይማኖትና የፖለቲካ ሥርዓት ይዞ እስከ ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሳይለወጥ ቆይ ቷል አሁንም ቢሆን ይኸ ሥርዓት በተመናመነ ሥልኩ ተጥሏሷል ቅማንትን አንድ ላይ አስተሳስሮና አቀራርቦ ያቆየው ሥርዓት በሦስት እርከን የተከፈለ ነው በትደም ተከተል ለመግለጽ ያህል የመጀመሪያው በዝቅተኛ ደረጃ የሚገኘው የአዛውንቶች ሸንጐ በመካከለኛ ደረጃ የሚገኘው ከፍተኛና ዝቅተኛ ቀሳውስት ስብስብ አና በመጨረሻ ደግሞ ቁንጮው ላይ የሚገኘው የሃይማኖትና የፖለቲካ የበላይ የሆነው «ወምበር» ናቸው በከፍተኛ ደረጃ የሚገኘው ወምበሩ የአማራውን ባላባታዊ አስተዳደር የበላይነት ይቀበላል በክርስቲ ያኒቱ ኢትዮጵያ የነበረው ባላባታዊ ሥርዓት በምንም ዓይነት ሳይለወጥ እስካሁን የቆየ ሲሆን በክርስቲያን አውሮጳ ተንሠራፍቶ ከቆየው ባላባታዊ ፊውዳል ሥርዓት ተመሳ ሳይነት ያለው ነው የኀብረተሰቡ ትስሰር ምክንያቶች የቅማንት መኖሪያ ቤቶች ተበታትነው የሚገኙ ቢሆንም የአነሱ ብቻ የሆነው ልዩ የፖለቲካ ሥርዓትና ከቤተሰብ አልፎ ከሌሎች ኅብረተሰብ ጋር ያላቸው የጠበቀ ግንኙነትና ዝምድና ሁሉም በአንድ ሳላይ ተሳስረውና ተቀራርበው አንዲኖሩ አድርጉአቸዋል የአያንዳንዱ ቤተሰብ የአባትን የዘር ሐረግ ተከትሎ የሚደረገው የዘር ቁጠራ ወደላይ እየተራዘመ ሄዶ የዋናው የዘር ግንዳቸውና አንዱን ከሌላው ጋር በመጨረቫሻ ከሚያገ ናኛቐው የጐሣ መሥራች ከሆነው ባህላዊ ጀግና አባት ላይ ይደርሳል የቅማንት ጐሣዎች ልዩ ልዩ ሐረግና ዘርፎች ሲኖሩ ዋቸው ወደላይ አየወጣ ሲሄድ ከሁለት ታላላቅ የዘር ክፋዮት ቡድኖች ላይ ያርፋል ይህም መሠረታዊ የሆነ ማኅበራዊ የጐሣ ኅብረተሰብ እንዲመሠረት ምክንያት ሆኖአልነ ሁሉም ቅማንት ከአንደኛው የዘር ክፋይ ላይ ብቻ ስለሚደርስ በጋብቻ ሕጋቸው መሠረት አንዱ ከሌላው የዘር ሐረግ ጋር ሊጋባ ይችላል የቅማንት ሃይማኖት ጥንታዊና ልዩ ልዩ ፅምነቶችን ያካተተ ሃይማኖት በመሆኑ የተለየና ትኩረትን የሚስብ ነው በሰሜን ማዕከላዊ ኢትዮጵያ የእስልምና ሃይማኖት ከመምጣቱ በፊት በቅደም ተከተል የተከሰቱ ሦሰት ዓይነት ሃይማኖቶች ነበሩ ከሁሉም በጣም ጥንታዋ የሆነው የጥንት አገዎች በተለያየ መልክ ያመልኩት የነበረውና አስከቅርብ ጊዜም የአሁኖቹ የአገው ሕዝቦች ያምኑበት የነበረው አረማዊኦገው እየተባለ የሚታወቀው ነው ሁለተኛው ደግሞ ከሁለት ሺ ዓመት በፊት በሰሜን ኢትዮጵያ የተሠራጨው የአብራውያን ሃይማኖት ኦሪት ሲሆን ሦስተኛው ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ጀምር ማለትም ከአንድ ቪህ ስድስት መቶ ዓመት በፊት የተሰፋፋው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ሃይማኖት ነው የክርስትናን ሃይማኖት ከኢትዮጵያ ሕዝቦች አንድ ሦስተኛው ያመልከዋል የቅማንት ሃይማኖት በአብዛኛው አረማዊአገው ሲሆን በተጨማሪም የአብራዊ ኦሪት ሃይማኖት እምነትን በውስጡ ያቀፈና በመጠኑም ቢሆን ኦንዳንድ የክርስቲያን እምነቶችን ያካተተ ነው በመሆኑም የቅማንት ሃይማኖት አረማዊኦሪታዊ ነው እንላለን በቅሣንት ሃይማኖት ያለው የኦሪት አምነት ይዘት ባለፋት ሁለት ቪ ዓመታት የአብራውያን ሃይማኖት እየተለዋወጠ ና አየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም አስካሁን ሳይለወጥ ጥንታዊነቱን አንደያዘ ይገኛል የቅማንት ጉሬቤት የሆነው በአገውነቱ የሚታወቀው የኢትዮጵያ ጥቁር እስራኤላዊ» እየተባለ የሚታወቀው ፈላሻ ሲሆን ከፍ ብሎ የተገለፀውን ዓይነት የኦሪት ሃይማኖት አምላኪ ነው ምንም አንኳን ፈላሻዎች በአንድ አምላክ ብቻ ነው የሚያምኑት ቢባልም በሂደት ከሌሎች እምነቶች ወስደው ወደ ራሳቸው ሃይማኖት ያዋሃዷቸው እንዳሉ ስለምንረዳ የፈላሻን ሃይማኖት ሙሉ በሙሉ ኦሪታዊ ነው ለማለት ስለማያስደፍር አረማዋኦሪት ነው የምንለው የቅርብ ግንኙነት አራት መቶ ሃምሣ ሺ እስኩዌር ማይል ስፋት ያላት ኢትዮጵያ በዉስጧ ከሰባ በላይ የቋንቋ ዓይነት የሚናገሩ በግምት ከሃያ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ በላይ የሚኖርባት አገር ስትሆን የቅማንት ሕዝብ ከሌሉቹ ጉረቤት ከሆኑት ሕዝቦች ጋር ያለን ግንኙነት መመልከት አስፈላጊ ይሆናል ጥናቱ የተካሄደው ጥንት የሀበሾች ሀገር አቢሲኒያ እየተባለ ይጠራ በነበረው በሰሜን እና በማዕከላዊ ሰሜን ደጋማው የኢትዮጵያ ከል ነው ይህ አካባቢ ሀበሾች እየተባሉ የሚታወቁ የሃስት ዋና ብሔረሰቦች መኖሪያ ነው ለመግለጽም ያህል የፖለቲካውን የበላይነት የያዘው ቁጥሩ አስከ የሚደርሰው አማራ ከአማራው ጋር የሚዛመደው የፖለቲካውን መድረክ የሚጋራው ቱጥሩ የሚሆነው ትግሬ እና ጥንታዊና የመጀመሪያው የአብዛኛዉ የአገር ክፍል ሠፋሪዎች የነበሩት በአሁኑ ጊዜ ቁጥራቸው ተመናምኖ የሚደርሰው የአገው ሕዝብ ሲሆን ቅማንት የአገው አንዱ ቅርንጫፍ ነው እነዚህ ሃስት ሕዝቦች ምንም አንኳን የመጀመሪያዎቹ ሁለቱ ሴማዊ ቋንቋ ተናጋሪ ሦስተኛው ደግሞ በመሠረቱ የኩሽ ቋንቋ ተናጋሪ ቢሆኑም ሁሉም ዝርያቸው አንድ ሆኖ የጋራ የሆነ የባህል ሥረመሠረት ያሳቸው ናቸው በነገራችን ላይ ከአፍሮ እስያ አምስት የቋንቋ ንዑስ ዘርፎች ሁለቱ የሴምና የኩሽ ቋንቋዎች መሆናቸው መታወጦት አለበት ዝርያን በተመለከተ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ኮኬዣዥያን ሆኖ ሴማዊም ሆኑ የኩሽ ቋንቋ ተናጋሪዎች አንድ ዓይነት የሰውነት ይዘትና ቅርጽ አሳቸው በርግጥ ከጥቁር ዝርያዎች ቡሽማኖይድስ ጋር በመጠኑ የመዳቀተል ሁኑታ ቢኖርም የኢትዮጵያ ውያኑን መሠረታዊ የሆነውን መልክና አቋም አለወጠ ውም የኮኬዥያን ዝርያ ያሳቸው ኢትዮጵያውያን ቀጥ ያለ መካከለኛ ቁመናና ደልደል ያለ ሰውነት አላቸው መልካቸውን በተመለከተ አንዳንዶቹ ጠየም ያሉ ሌሉቹ ደግሞ የቀይ ዳማና ቀዮች ናቸቐው የራስ ቅላቸው በአብዛኛው ቦጠጥ ያለ ሆኖ አፍንጫቸው በከፊል ሠፋፊና አንዳንዱም ቀጥ ያለ ነው ፀጉራቸው አንዳንዱ ዞማ ሌሉች ደግሞ ከርዳዱ ፀጉር ያላቸው ይገኛሉ አገው አማራና ትግሬ ከደጋው ምዕራባዊ ቆላማ አገር ከሚኖሩት ጥቁሮች ዘር የበላይ ነን ብለው የሚያምኑ በመሆኑ ከእነሱ ጋር ባይጋቡም በአገልጋይነት ከያዙአቸው ጥቁሮች ልጅ ማስወለድ ግን የተለመደ ነበር አማራና አገው ከአነሱ አፈጣጠ ርና መልክ ለየት ያሉትን ሰዎች በሚከተለው አፈታሪክ ለይተው ያስቀምጣሉ «ዳግ እላዝርሌር ፅውሃ ያሟፈፊጥረያምት ወቀፉሦ ያሰው ምሃነዕጳሷ ሪፈሮ ሠራ ኃጓቀ ጸጎም ለቃፕፓሖም ጣም ረሪያፇና ጥሮና ዕፅው ያፈጠረሪ ሉለደሃና ዳግ ደዳ ጨዕሌጴሮ ሐጎ ሥፖዕዕል ሠፉ በጳጎም ሐታፇሃ ሂሄ ሐዝሳቦ ሲያወማው ሷጥፐ ያመፅ ሙ ሰው ሆንታ መጨረ። ይህ ፀሐፊ ፈጽሞ ተጨባጭነት የሌላቸውና ሊታመኑ የማይችሉ አፈ ታሪኮችን በመጠኑም ቢሆን በከፊል ወደ ማመኑ ደረጃ ተቃርቦ ነበር ከነዚህም ተረቶች መካከል በቅርብ ዘመዳሞች የግብረሥጋ ግንኙነት እንደሚደረግ አንድ ሰው ወደ ሞት አፋፍ ሲደርስ የተፈጥሮ ሞት ከሚሞት ይልቅ ቴቄስ ተጠርቶ አንገቱን እንዲቆርጥ ወዘተ የመሳሰሉት ተቀባይነት የሌላቸው አሉባልታዎች ይገኘብታል ነገር ግን ሚስዮናዊው ፍላድ ቅማንት ማንኛውንም የሃይማኖት ሥነሥርዓት ሚስጥራዊ በሆነ መንገድ ከነሱ በስተቀር ማንም ሌላ ሰው ሳያውቀውና ሳይሰማው የሚከናወን በመሆኑ ለዚህ መሰረተቢስ ለሆነ ሠይጣናዊ አስተያየት ምክንያት ሳይሆን እንዳልቀራ በኋላ መገንዘቡን ያስረዳል የአሱንም እግር ተከትሎ የመጣው ሃሄንሪ እስተርን የተባለው ሚሲዮናዊ ቅማንቶች ስለሃይማኖታቸው ምንም ዓይነት መረጃ እነደማይሰጡ ነው የሚያጠናክረው በተወሰነ ጊዜ ግን ወደ ቋጥኝ ሄደው ሚስጢራዊ አምልኮት አንደሚያካሃሄዱ ገልጺል ሌላው ኢትዮጵያን የጐጉበኘ ማርቲን ሾን ሐውግሊን የተባለ ጀርመናዊ ነው አንደ ሐውግሊን አገላለ በቅማንትና በአማራው የገዢ መደብ መካከል የማኀበራዊና የፖለቲካ ትስስር እንደነበርና ከቅማንት ልማዳዊ አፈታሪኮች አንደተገነዘበም ጽፏል በማከልም «ቅማንቶች በታማኝነታቸውና በጀግንነታቸው ምክንያት ንጉሠ ነገሥቱ እጅግ በጣም ብርቅዬ ባለሟሎሉቻቸውና የቤተሰቦቻቸው ጠባቂ ያደር ጓቸዋል» ይሳል በቅማንቱና በአማራው የአመራር መደብ ጋር የነበረው የፖለቲካና የወታደራዊ ትብብር የተጠናከረ የቅርብ ግንኙነት በመፍጠሩ የንጉሠ ነገሥቱ ቋሚ ዋና ከተማ የሆነችው ጐንደር በቅማንት መሬት መሐል ላይ በዎቹ ዓም እንድትመ ሠረት ማስቻሉን ሐውግሊን ገልጾታል አንዲያውም አብዛኛው ክርስቲያን አማራ ከሚያስበው በላይ የቅማንት ባለሟሎች በፖለቲካው ውስጥ ምን ደረጃ እንዳላቸው በግልጽ ስለሚያውቁና እንደ አማራውና ትግሬው ባላባቶች የክልል ሥልጣን ፈላጊዎችና የሥልጣን ተቀናቃኝ ባለመሆናቸው የአማራው ነገሥታት በቅማንቱ ላይ የበለጠ እምነት ጥለውባቸው እንደነበረ ነቦዞ የአማራውና የቅማንቱ መተባበር ቅማንት ጥንታዊውን አረማዊ ኦሪታዊ ሃይማኖቱን እንደያዘ እንዲቆይ ረድቶታል ሌሉች ኦሪታዊ የአገው ሕዝቦች ለብዙ መቶ ዓመታት በተካሄዱ ደም አፋሳሽ በሆኑ ጦርነቶች ቀስ በተስ በአማራው ሲደመሰሱ ቅማንቶችን ግን ለጊዜው ሃይማኖታ ቸውንና ባህላቸውን እንደያዙ በሰላማዊ መንገድ በፍላጐታቸው ክርስትናን እንዲተበሉ ተዋቸው በዎቹ ዓም ወደ አፄ ቴዎድሮስ የተላከው የእንግሊዝ ቡድን አባል የነበረው ሆርሙዝድ ራሳም ደግሞ ሲገልጽ «ከአፄ ቴዎድሮስ በስተቀር በማንኛውም ጊዜ ቢሆን አንድ የሃበሻ ንጉሥ እንደ ቅማንቶች ያለ ታማኝ ባለሟሎች አግኝቶ አያውቅም» ይላል ቅዱስ ቦታዎች ናቸው ብለው በሚያምኑባቸው ድግናዎች ደኖች ስለሚደረገው ሥርዓተቅዳሴ ሲያብራራ «ሃይማኖታቸው ልክ በሶሪያ እንደሚገኙት አንሳሪስ ሕዝብ እጅግ በጣም ሚስጥራዊ ነው በክርስቲያኑም ሆነ በእስልምናው ዓለም ያልታወቀ ሥርዓተቅዳሴና ሥነሥርዓት ያካሄዳሉ» በማለት ዘግቧል ለሁለት መቶ ዓመታት ያህል ስለቅማንት በአውሮጳውያን የተሰጡትን ተባራሪ የሆኑ አስተያየቶችን በማሰባሰብና የራሱን የመስክ ጥናት በማካሄድ ፍሬድሪክ ሲሙንስ የተባለ አሜሪካዊ የጂኦግራፊ ምሁር ነበር ሠፋ ያለ ጥናት ያካሄደው እኤአ ከ ባለው ጊዜ በቤጌምድርና ሰሜን ጠቅላይ ግዛት ሰለሚገኙት ቅማንቶች ያደረገው ጥናት ያለንን እውቀት አዳብሯል ወደፊት እንደሚገለፀው «ሰሜናዊ ምዕራብ ኢትዮጵያ በ» የሚለው አስደሳች ጥናታዊ መጽሐፍ ነበር ስለቅማንት የመስክ ጥናቴ መሠረታዊ መመሪያ የሆነን ብዙውን ጊዜ አንድ የሥነሕዝብ ተመራማሪ የመስከ ጥናት ለምን እንደሚ ያካሂድ ዓላማውን ጥናቱ ለሚካሄድበት ኀብረተሰብ አስረድቶ ተቀባይነት ለማግኘት አንደሚቸገር ግልጽ ነው በተለይም ለምዕራ ባዊው ዓለም ባህል ተጋልጠው ለማያውቁት ለቅማንት ገበሬዎች እውነትነቱ የማይታበል ነው ማንበብና መጻፍ ስለማይችሉ ፀጉረልውጦች የሚያደርጉትንና በተለይ አጥው በጽሑፍ ለማስፈር የሚያደርገውን ጥረት ሁሉ በጥርጣሬ ይመለከቱታል በተማረው ክፍል በእጅ የተጻፉ ታሪካዊ ሥነጽሑፎች በቤተክርስቲያን ውስጥ ይቀመጡ ስለነበር እኔም ስለቅማንትና ጉረቤት ስለሆኑዋቸው አማራና ፈላሻ ታሪክና ባህል መጽሐፍ እንደምጽፍ አስረዳሁ በጉዳዩ ላይ ላለመተባበር ሲያቅማሙ ሲሙንስ የጻፈውን መጽሐፍ አውጥቼ ሌሉች አውሮጳውያን ከጻፉት አንዱ መሆኑን ሳሳያቸውና የቅማንት የፈላሻና የአማራ ሰዎች ፎቶግራፎች መኖራቸውን እንዲያውም አንዳንዶቹ በአጋጣሚ የራሳቸውንና የሚያውቋቸውን ሰዎች ፎቶግራፎች በተመለከቱ ጊዜ በተመሳሳይ ሁኒታ አስቀድሞም ይኸው ዓይነት ጥናት መካሄዱን በመገንዘባቸውና በሰዎችም ላይ ምንም ዓይነት እንከን አለማጋጠሙን በማመዛዘን ሊረጋጉና ሊተባበሩኝ ቻሉ በሲሙንስ አገላለጽ «እምነታቸውና ሥነሥርዓታቸው ምስጢራዊ ስለሆነው» ስለቅማንት ማንነት ከማወቃ ችንና የዕለት ተዕለት ተግባራቸውን እያከናወኑ ኑሮአቸውን እንዴት እንደሚመሩ ከማየታችን በፊት ስለቅማንትና ጥንታዊ ቅድመቅድመአያት ስለሆነው የአገው ሕዝብ ታሪካዊ አመጣጥ እንመለከታለን ምዕራፍ ሁለት የአገው ባህል ታሪክ ፈጣን እድገት የአገው ቅርንጫፍ ስለሆነው የቅማንት ሕዝብ ታሪክ ለማወቅ እንዲረዳን የአገው ሕዝቦች የባህል ታሪክ አድገት እንደመን ደርደሪያ እንደሚከተለው በአጭሩ ቀርቦአል በመሠረቱ ስላለፈው ጥንታዊ የኢትዮጵያ ታሪክ ብዙም አልተጻፈም ስለሀገሪቱ ቅድመታሪክና ታሪክ አንዳንድ በጣት ሊቆጠሩ የሚችሉ አጠቃላይ ሥራዎች ቢኖሩም አገው በማዕከላዊነት ስለነበረው ታሪካዊ ድርሻ አንዳቸውም ከሞላ ጐደል እንኳን አይገልጹም ቅድመታሪክ በ ዓመተ ዓለም እና ምናልባትም ከዚያ በፊት ቡሸማኖይድና ኮኬዥያን የተባሉት የሰው ዘሮች በደጋማው ኢትዮጵያና በአካባቢው በአዳኝነትና በፍራፍሬ ለቃሚሜነት ይኖሩ ነበር የኮኪዥያን አዳኞችና ፍራፍሬ ለቃሚዎች የነበሩት ያለጥርጥር ቅማንትን ጨምሮ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ያሉት የኩሽ ቋንቋ ተናጋሪ ሕዝቦች ጥንታዊ ዘረማንዘራቸው እንደነበሩ እንረዳለን የዕፅዋት ጥናቶች እንደሚያመለክቱት ምንም እንኳን ፅፅዋትን በማለማመድ ጥንታዊት ኢትዮጵያ ሙሉ በሙሉ ብቸኛዋ አገር ባትሆንም ሰብሎችን በማለማመድና በማሠራጨት ከፍተኛ ድርሻ ነበራት በሰሜንና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ አሁን ያለውን የአገው ሕዝብ አሠፋፈር ስናጠና ሰብልን የማለማመድንና ማሠራጨትን ሥራ ሲያከ ናውኑ የነበሩት ቡሽማኖይድ ሳይሆኑ የጥንት የኩሽ ቋንቋ ተናጋሪ ሕዝቦች መሆናቸውን እንገነዘባለን ጥንታዊ አገው ከሌላ አገር በስርጭት የደረሰውን ስንዴና ገብስ የመሳሰሉትን የተለያዩ ሰብሎችን ያመርት እንደነበረና እነሱም በአካባቢያቸው የሚገኙትን መበላት የሚችሉ ሌሎች ሰብሎችን በማለማመድና አገልግሎት ላይ በማዋል የታወቁ ነበሩ ለመጥቀስ ያህል ጤፍና ዳጉሣ እንዲሁም የቅባት እህል የሆኑትን ኑግና ተልባን አለማምደው ያሰራጩት አገዎች ናቸው የአዝእርትና የአትክልት ማልማት ዘዴ ከክርስቶስ ልደት ከ ዓመት በፊት በጥንታዊ አገዎች ዘንድ የታጦቀ ሲሆን እንስሳትን ማለማመድ ደግሞ ከክርስቶስ ልደት ከ ዓመት በፊት ከኑቢያኖች እንደተማሩ ታውቋል ዕፅዋትን የማለማመዱ ዘዴ ለኢትዮጵያ ከኬዥያኖች በቡሸማኖይዶች ላይ የባህል የበላይነትን ሳያቀዳጃቸው አልቀረም በመሆ ኑም ሕዝባቸውም እየበዛ በመሄዱ አካባቢያ ቸውን በመቆጣጠር ጥቅም ላይ በማዋል ሕዝቡን አደራጅተው ለጦርነት ለማዘጋጀት ምቹ ሁኔታ ስለተፈጠረላቸው የቡሽማ ኖይድ ዝርያዎችን በአብዛኛው ከአካባቢያቸው እንዲሰደዱ ሲያደርጉ አንዳንዶቹ ደግሞ በተለያየ መልክ በባሕል ለውጥና በመዳቀል ተውጠው እንዲቀሩ ሆኖአል ከዐዐዐ ዓመተ ዓለም ቀደም ብሎ የደቡብ አረቢያ ሕዝቦች ባሕላቸውን ይዘው ወደ ሰሜናዊ የአገው አገር አካባቢ ከመምጣታቸው በፊት የኩሽ ቋንቋ ተናጋሪዎች መላ ኢትዮጵያን ተቆጣጥረው እንደ ነበርና እንዲያውም ወደ ደቡብ በመስ ፋፋት ድንበርተኛ ወደሆኑት አሁን ኬንያ ኡጋንዳና ታንዛኒያ እየተባሉ ወደሚሜጠሩት አገሮች ሳይቀር መሠራጨ ታቸው የታወቀ ነው ኢትዮጵያዊ ሥልጣኔ ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ ዓመተ ዓለም መጨረሻ ላይ አነስተኛ ዝናብ በነበረባት የመን በመስኖ የእርሻ ኤኮኖሚ ላይ የተመሠረተ ሥልጣኔ ነበር ከ ዓመተ ዓለም በኋላ በደቡብ አረቢያ ከሚገኙ አገሮች እየተነሱ አንዳንድ ጐሣዎች ከተከዜ ወንዝ በስተሰሜን የሚገኘውን ደጋማውን የኢትዮጵያ ክፍል ቅኝ ግዛት ማድረግ ጀመሩ ይህም ሂደት ለ ዓመት ያህል ሳይቀጥል አልቀረም በዚያን ጊዜ ከደቡብ አረቢያ የመጠ ት ሕዝቦች የተገናኙት አስቀድሞ ሠፋሪና ነዋሪ ከሆኑት የአገው ጥንታዊ ቅድመቅድመአያቶች ጋር ነበር የደቡብ አረቢያ ባህልና የጥንታዊው አገው ባሕል በመቀላቀላቸው ሦስተኛ ባህል ሊፈጠር ችሏል ነገር ግን ጠቅላላ ውሕደት ስላልተከሰተ ነባሩ ባህልም ሆነ ከደቡብ አረቢያ የመጣው አንዱ ሌላውን ጨርሶ ሳይደመስስ የየራሳቸውን የባህል ትውፊት በመያዝ ቆዩ የማኀበራዊና የባህል እድገት በዚህ ዓይነት መዳቀል ምክንያት አንድ ደረጃ ከፍ በማለቱ «ኢትዮጵያዊ ሥልጣኑ» እያልን የምንጠራው አቆጥቁጦ ወደ ደቡብ በመዛመቱ ኢትዮጵያ የጥንታዊ ሥልጣኔ በር ከፋችና ማዕከል ሆነች የደቡብ አረቢያ ሕዝቦች ለኢትዮ ጵያዊው ሥልጣኔ ሇብዙ አስተዋፅኦ አድርገዋል ለመጥቀስ ያህል የጥሬ ካብ ሥራ የሐውልት ሥራ ከእርከን ጋር የተያያዘ የመስኖ ሥራና ምናልባትም ማረሻና ቀንበርን ማስተዋወቅ የመሳሰሉት ከብዙዎቹ ጥቂቶቹ ናቸው በተጨማሪም ውስብስብ የሆኑ የማኀበራዊ አደረጃጀት ስልት በተለይም በመጀመሪያው ምዕራፍ ሳይ የተገለጸው ባለሁለት መደብ ማኀበራዊ ተቋም ማለትም በአንድ በኩል የነቃውን ክፍል ያቀፈው ባለ ታላቅ ባህል» እና በሌሳ በኩል ደግሞ አርሶ አደሩንና ሌሎች ዝቅተኛ የሕብረተሰብ ክፍሉችን ያጠቃለለው «ባለ ትንሸ ባህል» እየተባለ የሚታወቀውን አደረጃጀት የደቡብ አረቢያ ሕዝቦች ይዘውት የመጡት ሥርዓት ነው ከሁሉም በላይ ልቆ የሚታየው አስተዋፅኦ ደግሞ የሑፍ ፊደላትን ማስተዋወቃቸው ነው ምንም እንኳን የደቡብ አረቢያ ሕዝቦች ቁጥራቸው አነስተኛ ቢሆንም ቋንቋቸው ወይም ደግሞ የእነሱን ቋንቋ የተካው ግዕዝ ባለሥነጽሑፍ ቋንቋ ስለነበሩ ከሌሉች ቋንቋዎች ሁሉ የበላይነትን ሊቀዳጅ ትሷል ጥንታዊ የአገው አባቶችም ቢሆኑ ለኢትዮጵያ ሥልጣኑ ብዙ አስተዋፅኦ አድርገዋል አብዛኛው የሕዝብ ክፍል ስለነበሩ አሁን የምናየው ኢትዮጵያዊ የእነሱን ልዩ የሰውነት መልክና ቅርጽ እንዲይዝ ሆኖአል በተጨማሪም በግብርናው ሥልጣኔ በኩል ጥንታዊ አገዎች የአደረጉት አስተዋፅኦ በቀላሉ የሚገመት አይደለም በደቡብ አረቢያ ቀደም ብሎ የሚታወቁትን ስንዴና ገብስ አንዲስፋፉ ከማድረጋቸውም በላይ ሌሎች ለምግብነት የሚያገለግሉ መሠረታዊ የሆኑ አገር በቀል ሰብሎችን በማለማመድ እንዲሠራጩ ያደረጉት አገዎች ናቸው ቀጥሎ በነበሩት መቶ ዓመታት ብዙ የሥልጣኔ ማዕከሎች ተመሥርተው ነበር ከክርስቶስ ልደት ወዲህ በጣም ሥልጣኔ ተስፋፍቶ የነበረው ግን የሃይማኖት ሐውልቶች በብዛት ተሠርተው በነበሩበት በአክሱም ከተማ ነበር የኦሪት ሃይማኖት እምነት ከደቡብ አረቢያ አስቀድሞ ወደ ኢትዮጵያ ተሠራጭቶ የነበረ ቢሆንም የኢትዮጵያ አክሱማዋ መንግሥት ገዥ በነበረው በንጉሥ ኤዛና ዘመነ መንግሥት በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ በመግባቱ የክርስትና ሃይማኖት በአክሱም ከተማ ነዋሪዎች ከተጠናከረ በኋላ በስፋት በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ገበሬዎች ስር ሊሰድ ትላል ከጊዜ በኋላ ግን ኢትዮጵያ በደቡብ አረቢያ ይዛው የነበረችውን ግዛቷን በፋርስ መንግሥት በመነጠቋ ሥልየእዋ እየተዳከመ መጣ የእስልምና ሃይማኖት እየተስፋፋ በመምጣቱ ወደ ሜድተራኒያን አረቢያና ምሥራቅ አፍሪካ ወደአሉ የንግድ ማዕከሎች የሚደረገውን የኢትዮጵያውያን የንግድ አንቅስቃሴ ተገታ ከሌላው ዓለም ጋር የሚያገናኛት የቀራት አንድ በር ደግሞ በኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኩሽ ቋንቋ ተናጋሪ የሆኑት የቤጃ ጐሣዎች ተነሥተው አክሱምን በመውረር ከሌሎች የኑቢያ ክርስቲያን መንግሥታት ጋር የነበረውን መንገድ በመስበር በመዝጋታቸው ግንኙነት ተቋረጠ የመጨረሻው ወድቀት ደግሞ አዲሱን ኢትዮጵያዊ ባህል ያልወደዱት አንዳንድ የአገው ሕዝቦች በአመፅ መነሣሣት ነበር ይህንን በሚቀጥለው ንዑስ ክፍል እናየዋለን ኤድዋርድ ጊቦን በኢትዮጵያ ስለተከሰተው ጠቅላላ ሁኔታ ሲገልጽ «በሃይማኖት ጠሳቶቻቸው ዙሪያውን ተከበው ዓለምን እረስተው ዓለምም ራሷ እነሱን አረስታቸው ኢትዮጵያ ውያን ለአንድ ሺ ዓመት ያህል አንቀላፉ» በማለት ይደመድመዋል ኢትዮጵያዊ ሥልጣኔ ወደ ደቡብ ስለመስፋፋቱ ኢትዮጵያዊው ሥልጣኔ ተመናምኖ ተዳከመ እንጂ ጨርሶ አልወደመም ነበር በቤጃዎችና በአስልምና ኃይሎች የተከበበው ተራፊው የኢትዮጵያ ሥልጣኔ ኃይሉን በመካከለኛው የኢትዮጵያ ደጋማ ደልዳላ አካባቢ እንደገና ማጠናከር ጀመረ እኤአ በ ዓም አካባቢ የሰሜኑ ሕዝብ በከፊል ተከዜን ተሻግሮ አገዎችን እየገፋ መስፈር ቀጠለ ቀጥሎም ለረዥም ዘመናት የአገውና የሴም ቋንቋ ተናጋሪዎች በአንድ ላይ በመኖራቸው ምክንያት በመካከላቸው መዳቀል ተከተለ ከሁለቱ ሕዝቦች የኢትዮጵያዊ ሥልጣኔ መሥራች ስደተኞች በወታደር ኃይል በይበልጥ የተጠ ናከሩ ስለነበሩ ተፅዕኖና ማድረግ በመቻላቸው የሁለቱ ሕዝቦት መቀላተል በመፋጠኑ ውሕደት በሂደት በመከሰቱ «የመጀመሪያው አማራ» ኘሮቶአማራ ብቅ አለ ተከዜን ሳይሻገሩ አዚያው የቀሩት ኢትዮጵያውያን ደግሞ የአሁናዝ የትግሬ ሕዝብ ቅድመቅድመአያቶች ነበሩ የመጀመሪያው አማራ «ባለትልቅ ባህል»ና «ባለትንሻ ባህል» ተብለው በሚታወቁት ሁለት መደቦች የተከፈለ ሃበ ኃይሉን በከፍተኛ ፍጥነት እያጠናከረ ኋላቀር የሆኑትን ኦ ዎች በቁጥጥሩ ማድረጉን ተጠለ ከተከዜ በስተደቡብ የነበሩት አገዎት ከጥንታዊው አማራ ሕብረተሰብ ጋር በመተሳ ቀላቸው የማኀበራዊና ባህላዊ ለውጥ በማስከተሉ ቀጣዩ ክሰተት የሁለት ሕዝቦች ውሕደት ሆነ ውሕደቴም የአማራው አካል የሆነው ሦስተኛው ዓይነት ባህል እንዲፈጠር ረዳ ምንም እንኳን ብዛት ባለው የአማራ ሕዝብ ቢከበቡም ይህ የባህል ውሕደት ሲካሄድ ቅማንቶችና አንዳንድ ሌሎች አገዎች ማንነታቸውንና ባህላቸውን ጠብቀው የኖሩ አልጠፉም የባህል ልውውጡ በእንካበእንካ ቢሆንም የጥንታዊ አማራ ባህል የበላይነቱን መያዝ ቻለ በዚህም ምክንያት ቋንቋው የአገው ቅሪት ሳይለየው ሴማዊ ሆኖ ሃይማኖቱ ደግሞ በጊዜው የአረማዊ ኦሪታዊ እምነቶችን ያካተተ የክርስትና ሃይማኖት ነበር በግብርናው ረገድ አማራው በአብዛኛው የሚያመርታቸው ሰብሎች በአገዎች የተላመ ዱትን የእህልና የአታክልት ዓይነት ሆነ የመጀመሪያው የአማራ ባህል ከጥንታዊው አገውና ከደቡብ አረቢያ ከመጡት ተስፋፊዎች ባህል ጋር አስቀድሞ የተዳቀለ ሲሆን ዘግየት ብሉም በዘመናት ሂደት በተጠናከረ ሁኔታ ከአገዎች ጋር በሁለተኛ ደረጃ የባህል ውሕደቶች እንደተካሄዱ እንገነዘባለን አገዎች ከጥንታዊው አማራ የተማሩት የቴክኖሎጂና የአደረጃጀት ስልት አካባቢውን መቆጣጠር ስላስቻላቸው ቀደም ብሎ ቅድመአያቶቻቸው ሳይጠቀሙበት የቀረውን የመሬት ሀብት መጠቀም አስቻላቸው ባለማረሻ ሞፈርና ቀንበር ሌሎች የብረት መሣሪያዎ ችንና የአርሻ ዘዴዎችን ተግባራዊ በማድረግ ሠፋፊ መሬቶችን ማረስ ጀመሩ የተሻለ ጥልቅ እርሻ በማረስ ረግረጋማ ቦታዎችን በማድረቅና የመስኖ ሥራንም በመጠቀም ክረምት ከበጋ ማምረት በመቻላቸው ምርት ተትረፈረፈ የቴክኖሎጂ ለውጥና የተፋፋመ የኢኮኖሚ ዕድገት የሕዝብ ብዛትን አስከተለ ይህም በተቃራኒው ብዙ ደኖች እየተጨ ፈጨፉ ወደ አርሻ መሬት በመለወጣቸው የደጋማይቱ ኢትዮጵያ የደን ሃብት ተመና መነ ደኖች በመጨፍጨፋቸውና ረግረጋማ ቦታዎች ስለደረቁ በመጠኑም ቢሆን ኑሮአቸውን ለመደጉም ይታደኑ የነበሩት የዱር አንስሳት አብረው ጠፉ የአማራው ቴክኖሎጂ ባስከተለው የአካባቢው ለውጥ ምክንያት ወደ ድሮው ዓይነት ኑሮአቸው አገዎች መመለስ ስላልቻሉ ቀስ በቀስ ባህላቸው እየተለወጠና እየተዋጠ ከአዳኝነትና ከኋላቀር የጓሮ አታክልት አልሚነት ወደ ገጠሬ ገበሬነት ተሸጋገሩ የባህል ግንኙነት በአገው ሕዝብ ላይ ያስከተለው ስሜት የአንድ አገር ተወላጅ ነባር ሕዝብ አንድ ሌሳ ቡድን በኃይል ተፅዕኖ ሲያደርግበት የሚሰጠው ምላሸ ይኖራል አንዳንድ ጊዜ በዝምታ ሁኒታዎችን ተቀብሎ ወደ አንድ አካባቢ ራሱን ያገላል ሌላው ደግሞ የመጣውን ላለመቀበል ራሱን አደራጅቶ እንደገና ተጠናክሮ በመታገል ከተፅዕኖው ነፃ ሆኖ ሥልጣን ለመያዝ ይፍጨረጨራል አማራው ተከዜን ተሻግሮ ወደ አገው አገር ጣልቃ በመግባቱ ባህላቸው የተለወጠውም ሆነ ያልተለወጠው አገዎች የተቃውሞ አንቅስቃ ሴዎች ማድረጋቸው አልቀረም ይህ ዓይነቱ እንቅስቃሴ ነበር ከተከዜ በስተሰሜን የነበረውን ኢትዮጵያዊ ሥልጣኔ ለመጨረሻ ውድቀት የዳረገው በአፈታሪክ የታወቀችው ንግሥት ዮዲት ጉዲት የተባለችው ፈላሻ አገው የጦር መሣሪያ በማንሳት ከአማራውና ከትግሬው ኃይል ጋር ከዘጠነኛው እስከ አስራ አንደኛው ምዕተ ዓመት በተደረጉት የትጥቅ ትግሎች ከተካፈሉት የአገው የጦር መሪዎች አንዷ ሆና በምሳሌነት ትጠቀሳለች አብዛኛውን የኢትዮጵያ ክፍል በመቆጣጠር አገዎች መቼ ሥልጣን እንደያዙ የታሪክ ማስረጃዎች በግልጽ ባያስረዱም የላስታ አገዎች የዛጉዌን ስርዎመንግሥት አብዛኛውን ጥንታዊት ኢትዮጵያን እኤአ ከ እስከ ዓም ድረስ መግዛታቸው የተረጋገጠ ነው በዚያ ዘመን ኢትዮጵያ በደንብ የተደራጀ መንግሥት ያላትና ግዛቷ ሰሜንንና ማዕከላዊ ደጋማውን የኢትዮጵያ ክፍል ያካተተ ነበር አንዳንድ ጽሑፎችና ኣፈ ታሪኮች አገዎች ከዚህ ቀደም ብሉ ሥልጣን ይዘው እንደነበር ያስረዳሉ ይህም በአገው እንቅስቃሴ ጊዜ የአማራውና የትግሬው ኃይል ቀስ በቀስ አየተሸረሽፈ መጥቶ በመጨረሻ መገርሰሱን የሚያስገነዝብ ነው አገው ሥልጣኑን በጨበጠበት ወቅት የትግሬውና የአማራው ሥልጣኔ ወደ «ጨለማ ዘመን» ገባ ብዙም ባይታወቅ የኤኮኖሚው ተቋም ተንኮታኩተ በከተሞች ተቋቁመው የነበሩ ታላላቅ ገበያዎች ፈራርሰው ግብይት በየመንደሩና በየሜዳው ሆነ ከተሞችም የአውሬ መፈንጫ ሆነ የአማራውና የትግሬው «ታላቁ ባሕል» ተብሎ የሚታወ ቀውም ሆነ ማቆጥቆጥ የጀመሬራው ቴክኖሎጂ ተሽመድምዶ ወደ ገጠሬነት ተለወጠ በመሆኑም የውስጥና የውጭ ግንኙነቶች ተቋርጠው ጉሰኝነት ተስፋፋ በዚያን ዘመን ነበር ኢትዮጵያዊው ሥልጣኔ በአብዛኛው ጭራሾ የጠፋው ወይም የፈራረሰው ባላባታዊ መንግሥት በኢትዮጵያ ስለማቆጥቆጡ እኤአ በ ዓም አካባቢ አማራው አመፅ አስነስቶ የመጨረሻውን የዛጉዌ ስርዎ። አስቀድሞ እንደተጠቀሰው ቅማንቶች የሚኖሩት በተበታተኑ ሠፈራዎቸ ሲሆን የከርከርና የጭልጋ ሁኑታም ከዚህ የተለየ አይደለም በእርሻ ላይ ያሉት ሠፈራዎች ከአንድ እሰከ አራት የሚደርሱ ቤቶች በአንድ ላይ ያሉበትና በተመሳሳይ ሁኔታ ሌሎች ቤቶችም ከ ሜትር እስከ ሜትር በሚደርስ አንዱ ከሌላው ተራርቀው ይገኛሉ በመሠረቱ መንደር የምንለው ከ እስከ የሚደርሱ ቤቶች ጠፍ በሆነ ቦታ ሳይ ተሰብስበው የተገኙ እንደሆነ ነው በቅማንት ኀብረተሰብ ግን ይህ አይታወቅም ጆርጅ ፒ መርዶክ እንዳለው የቅማንት ሕብረተሰብ ቤተሰቦች አንዱ ከአንዱ ተራርቆ በከፊል በመገለል በጉርብትና የሚኖሩ እንጂ በመንደር የተሰባሰቡ አይደሉም በከርከርና በጭልጋ እንዲሁም በሌሉች ቦታዎች እንደሚታየው ሁሉ የታረሱ መሬቶች ያደሩ መሬቶች የግጦሸ መሬቶችና ቁጥቋጦዎች በረድፍ ሥነሥርዓት ይዘው ይገኛሉ በእነዚህ ቦታዎች ደግሞ አልፎ አልፎ ጣልቃ ገብ ሆነው አሠራራቸው በተለይ የቅማንቶች ስልት ነው ተብለው የታወፋት የአንቁሳል ቅርጽ ወይም ክብ የሆነ ግድግዳቸው ጨፈቃና የጭቃ ምርጊት ሆኖ የሣር ክዳን ቤቶች ይታያሉ በአጭሩ በኀብረተሰቡ መካከል ያልተያዘ ሰፊ ቦታ አይገንም አንዱ ኀብረተሰብ ከሌላው ኀብረተሰብ ሰው ሠራሸ በሆኑ ወይም የተፈጥሮ ድንበሮች ተከልለው ይገኛሉ ቅማንቶች በጥንታዊ ባህላቸው መሠረት ርስታቸውን ተካፍለው ይኖራሉ ይህም ሁኔታ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከተቋቋሙት የቤተክርስቲያን ሥነሥርዓትና ከመንግሥት የአስተዳደር ተወካዮቸ ጋር የሚያጋጭ አይደለም ሁሉንም ቅማንት ደግሞ አስተሳስሮ የቆየው በአንድነት ላይ ሆነው የሚያከብሩት የአረማዊኦሪታዊ ሃይማኖት ክብረበዓል ነው ዝርዝር ጥናቱ የተካሄደው በሰንሰለታማ ተራራዎችና ገደላገደል ተከፋፍለው በከርከር በሚገኙ ሦስት ንዑሰ ኀብረተሰቦቸ ላይ ነው ዋናው ጥናት የተካሄደበት በተለይ ከርከር አንቸው ሚካኤል ይባላል ይህ ቦታ የጥቁር አባይና የተከዜ ወንዞት ተፋሰሶች መለያና መቨጋገራያ በር መሆኑ ይታወቃል ወደ ጐንደር የሚወስደውና የሁለቱንም ወንዞች ተፋሰስ የሚያሸጋግሪው የእግር አውራ ጉዳና አሁንም ከዘመናት አገልግሉት ከኋላ በዚህ አልፎ ይሄዳል የከርከር ሕዝብ ብዛት እኤአ በ ዓም ሲሆን በተለይ የአንቸው ሚካኤል ሕዝብ ደግሞ ነበር የደቡብ ምሥራቅ የከርከር ጫፍ ከጉንደር ከተማ በእግርም ሆነ በተሸከርካሪ ጣሊያኖች በሠሩት መንገድ ስድስት ማይል ወጣ ብሎ ይገኛል በመጽሐፉ የመጀመሪያው ሽፋን ያለውን ርታ ይመልከቱ የእዋ ትንጂ ዞልስዋገን መኪና ከአሁን በፊት ሌሳ መኪና አይቶት ስለማያውቅ አንዳንዴ እየተነዳች ሌላ ጊዜ ደግሞ በግፊና በሸክም ነበር መንገዱን ያገባደደችው መንገዱ ሁለት ማይል ተኩል ያህል ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ከሄደ በኋላ ወዶ አንቸው ሚካኤል እሩቡን ያህል እንደዘለቀ ይቋረጣል ከዚህ መንገድ ተገንጥሎ ማይል ያህል ሰሜናዊ ምዕራብ አቅጣጫን ተከትሎ የሚሄድና ከከርከር ሰሜናዊ ትሪያንግል ጫፍ የሚገናኝ መንገድ ይገኛል ሌላው በጣሊያኖች ተሰርቶ ለብዙ ዘመን ከተተወ በኋላ እኤአ በ ዓም ተጠግኖ በበጋው ወራት አገልግሎቱ እንዲቀጥል የተደረገ መንገድ አለ ምንም እንኳን እነዚህ የመገናኛ መስመሮች ቢኖሩም ከከርከርና ከሌሎች ቦታዎች ወደ ጉንደር የሚደረጉ ግንኙነቶች በአእግር በአህያና በበቅሎ ነው ዝቅተኛው የመንግሥት አስተዳደር እርከን የከርከርና ዋሳጅ ምክትል ወረዳ ሲሆን በአማራና በቅማንት ሹማምነት ይመራል ነገር ግን በከፍተኛ ደረጃ ያሉት የወረዳውና የአውራጃው ጽሕፈት ቤቶች ጉንደር ከተማ ነው የሚገኙት ሁለተኛው ጥናት የተካሄደበት ቦታ ደግሞ ከከርከር በሕዝብ ብዛት ይበልጣል ከጐንደር ወደ ደቡብ አቅጣጫ ለ ማይል ያህል በአውራ ጉዳና ከተጓዙ በኋላ እንደገና ወደ ሰሜን አቅጣጫ አነስተኛ መኪና በሚያስኬድ መንገድ ጉዞ በመቀጠል የጓዋንግ ወንዝን ተሻግሮ የጭልጋ ማዕከል ይገኛል ወንዙ በሚቀንስበት ወራት የመንግሥት ሳንድሮቨር መኪናዎችና የአንድ ነጋዴ የጭነት መኪና ስለሚመሳለሱበት በመጠኑም ቢሆን መንገዱ ደህና ነው የጭልጋ ኀብረተሰብና የጭልጋ ወረዳ ድንበሮች እዚህ ላይ ይገጣጠማሉ ለጭልጋ ወረዳ አውራጃና ለአካባቢው የአስተዳደርና የገቢያ ማዕከል ሆነው የሚያገለግሉ ሁለት ከተሞች ቅርብ ለቅርብ ይገኛሉ እነዚህ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተቆረቆሩት ከተሞች በአብዛኛው በቅርብ ጊዜ የመጡ ነዋሪዎቻቸው ቅማንት ያልሆኑ ቢሆንም ከዚህ ላይ ሊነሠ የቻሉት ስለጭልጋ ኀብረተሰብ የተሟላ ግንዛቤ እንድናገነ ስለሚረዳ ነው «ጭልጋ» የሚለው ስያሜ ከመሠረታዊው የቅማንት ሕብረተሰብ ይዞታ አሁን ሰፋ ያለ በአማራው መንግሥት የተፈጠረ የአስተዳደር ዘርፍ ነው ከሁለቱ ትናንሽ ከተሞች ላቅ ያለው አይከል የአውራጃው አስተዳደር ማዕከል ናት ከተቆረቆረች ዓመት የሚሆናት ይህች ከተማ ያሀል ሕዝብ ይኖርባታል በመንግሥቱ ጽሕፈት ቤት ግቢ ውስጥ ጥንታዊ የአማራ ዓይነት የድንጋይ ቤቶች አሉ የአካባቢው የጥንት ዓይነት ቤቶች ቅርጻቸው ኣራት ማዕዘን ግድግዳቸው እንጨትና ጭቃ የሆኑ የቆርቆሮ ክዳን ባላቸው ዘመናዊ ቤቶች እየተተኩ ነው በአዲስ መልክ ከተሠሩት ቤቶች መካከል በርካታ መሸታ ቤቶች አንድ ምግብ ቤት ሱቆች አንድ አነስተኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤትና ከጉንደር ከተማ ጋር የሚያገናኘው የስልክ ቤት የመሳሰሉት ይገኙበታል የጭልጋ ወረዳ የአስተዳደር ማዕከል የሆነችው ሠራባ ደግሞ አንድ መቶ ያህል ሕዝብ የሚኖርባት መንደር ናት ከተመሠረተች ሃያ ዓመት የሚሆናት ይህች መንደር ቁጥራቸው አነስተኛ ከሆነው ዘመናዊ ቤቶችና በኮንክሪት ከተሠራው አንድ አንደኛ ደረጃ በረር ቤት በስተቀር ሌሎቹ የጥንት ዓይነት የሣር ቤቶች ና ው ከከርከር በስተሰሜን በቅርቡ የአስተዳደርና የገቢያ ማዕከል ሆና የተመሠረ ተችው ትክል ድንጋይም በአዲሱ ስልት የተሠሩ ሕንፃዎች አሏት አይከል ሰራባና ትክል ድንጋይ ብቻ ናቸው በቅማንት አካባቢ የሚገኙት አነስተኛ ከተሞችነ የቤት አሠራራቸው ከጥንቱ የአካባቢው የቤት አሠራር ዓይነት የተለየ ነው ከነዚህ ከተሞች በስተቀር በሌሎች የቅማንት አካባቢዎች አዲሱ የቤት አሠራር አይታወቅም በአይከልና በሠራባ መካክል የብሔራዊው ሕዝባዊ ኑሮ እድገት ሚንስቴር ጣቢያ ይገኛል በሠራባ የሚገኘው አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዘመናዊ የምዕራባዊ አርኪቴክቸርና ዲዛይን እና በውጭ ሀገር ፋብሪካ በተመረቱ ቁሳቁሶች ኮቆርቀሮ ክዳን በስተቀር የተሠራው በቅማንት አካባቢ የሚገኘው ብችኖ ሕንፃ ነው መኖሪያ ሠፈርና ቤታቸው እንደ ብረት የጠነከሩት የስልሳ ዓመት አዛውንቱ የአቶ ረዳ ቤት ዓይነተኛውን የቅማንት ቤት ይወክላል አንድ ሺ ጫማ አለፍ ብሎ ደግሞ የታናሽ ወንድማቸው የአዮ ቤት ይገኛል የአቶ ረዳ ቤተሰብ ሁልጊዜ ደስተኛና ወፈር ያሉትን ሃምሣ ዓመት ዕድሜ ያላቸውን ባለቤታቸውን ወይዘሮ አዳነችን የሃያ ዓመት ዕድሜ ያለውን ሉሎጋና ያላገባውን ልጃቸውን መልኬንና የአልጋ ቁራኛ የሆኑትን የሰማንያ ዓመት ሽማግሌ አባታቸውን አቶ አየነውን ያካትታል ዕድሜያቸው እንደቅደም ተከተላቸው ሠላሣ አምስትና ሠላሣ ዓመት የሆነው ደንዳና ልጆቻቸው ነጋሽና ቢተው ሚስት አግብተው ጉጆ በመውጣት ከአባታቸው ቤት ኦጦ ገብ ቤት ሠርተው ኖሪራሉ ይህ በእርሻ መካከል የተመሠረተው ሠፈራ ሶስት ተቀራርበው የተሠሩ ቤቶችንና ለልዩ ልዩ አገልግሎት የተሠሩትን ትናንሽ ጉጆዎችን ያጠቃልላል እንደሌሎች የአገሬው ቅማንት ቤቶች የአቶ ረዳ ቤት ግድግዳው ጨፈቃና በጭቃ የተመረገ ሆኖ ጣራው የሣር ክዳን ነው ሁለት ዓይነት የጣሪያ ቅርጽ በቅማንት ሀገር የተለመደ ሲሆን በብዛት የሚገኘው የእንቁላል ሽሙልሙል ቅርፅ ያለው ነው ሌላው ደግሞ እምብዛም በብዛት ባይታይም ክብ የሆነው የጣራ ዓይነት ነው የአቶ ረዳና የቢተው ቤቶች የእንቁሳል ቅርፅ ያላቸው ሲሆን አስራ አምስት በሃያ አራት ጫማ በሆነ ቦታ ላይ አርፈዋል የነጋሸ ቤት ግን ክብ ሆኖ መሀል ለመሀል ዙሪያውን ጫማ ነው ጣሪያውም የእንቁላል ቅርጽ የሚመስለው ቤት ሁለት ምሰሶዎቸ ብቻ ሲኖረው ክብ የሆነው ግን መሀል ላይ የተተከለ አንድ ወጋግራ ምሰሶ ወይም ቤቱ ትልቅ ከሆነ አራትና ከዚያም በላይ የሆኑ ወጋግራዎች ምሰሶዎች መሀል ለመሀል ዙሪያውን ይቆማሉ ክብ የሆነው ቤት ሾጣጣ ጣሪያና አንድ ጉልላት ሲኖረው ሸሙልሙል ቅርጽ ያለው ቤት ደግሞ በዚያው ልክ ቅርፁን ይዞ ወደላይ ከፍ ይልና በመጨረሻ ላይ ሶስት ጫማ ስፋት ያለው ድምድማት ይኖረዋል ሁለቱም ዓይነት ቤቶች ለአየርና ለብርሃን ማስገቢያ ጭምር እንዲያገለግለ ከቋሚ አንጨት ጋር በማጠፊያ የተያያዘ አንድ የአንጨት በር ብቻ አላቸው አቶ ረዳም ሆኑ ሌሎች ግለሰቦች ባለ ሁለት ምሰሶው ቤት የበለጠ ተወደዳጅነት እንዳለው ይናገራለ ምክንያቱም ቤቱ ሰፋ ያለ ቦታ እንዲኖረው ከማስቻሉም በላይ እነዚህ ሁለት ምሰሶዎቸ ቤቱን በሶስት እኩል ቦታዎች በመክፈል ለአገልግሉት ምቹ ስለሚያደርጉ ነው የመጀመሪያው ሲሶ አቶ ረዳና ወይዘር አዳነች አንግዳ ያስተናግ ዱበታል ምግብ ይበላበታል የእጅ ሥራ ይሠራበታል ለመኝታም ያገለግላል ዋናው ምድጃም የሚገኝበት በዚህ ክፍል ውስጥ ነሀ ባለሶስት ጉልቻ ከሆነው ምድጃ የሚነሳው ጭስ ጥቀርሻ የጠገበውን የሣር ክዳን ጣራ እየሰረገ ወደ ውጭ ይወጣል የሚቀጥለው የቤቱ ሲሶ ደግሞ ለክምችት የሚያገለግሉ ከጭቃና ከእበት የተሠሩ ቁመታቸው አስከ አምስት ጫማ የሚደርስ ጐጉታዎች አሉ ወደ በሩ ያሉት እነዚህ ሁለቱ ሲሶዎቸ በአጠቃላይ ወለል ተብለው የሚታወቀው ክፍል ነውወ ሶስተኛው ሲሶ ደግሞ ጨለም ያለውና «ማጀት ተብሎ የሚጠ ራው ነው ወይዘሮ አዳነች በዚህ ክፍል ነው ምግብና ጠላ የሚያዘጋጁት ለእንግዶች ከሚዘጋጀው ቡናና ምግብ በስተቀር ቤተሰብቡ የሚበላው ምግብ ብዛቱንም ሆነ ጥራቱን ጎረቤት አንዳያየው ማጀት ውስጥ ነው የሚዘጋጀው የቤት እቃዎችንና ቁሳቁሶችን በተመለከተ አልጋ ወንበሮችና በጥልፍልፍ ጠፍር የተሠሩ ሶፋመሰል አግዳሚ ወንበሮች የመሳሰሉት ይገኛሉ እነዚህ እቃዎች በአቶ ረዳና በልጆቻቸው የተሠሩ ናቸው አንዳንድ ቤቶች ደግሞ ለመኝታና ለመቀመጫ የሚያገለግሉ መደቦች አሏቸው የእንጨት ሙቀጫ ከነዘነዘናው በያንዳንዱ ቤት የሚገኝ ዕቃ ነው ወይዘሮ አዳነችና የልጆቻቸው ሚስቶች ጥራጥሬ ለምግብ የሚሆኑ ቅባትና እህል የሚወቅጡበት ሙቀጫና በተጨማሪም የድንጋይ ወፍጮ ተተክሎ ከነመጁ ይገኛል ዳቦና እንጀራ የሚቀመጥበትና የሚበላበት ሞሶብ እንደክብር የወግ አቃ ይቆጠራል ሞሰቡ በሾጣጣ ክዳን ተገጥሞ ምግቡ በውስጡ ይቀመጣል እንዲሁም በጥንቃቄ የተሠራ ምግብ በሞሶብ ሆኖ ይቀርብና እንግዶች ዙሪያውን ከበው ይመገባሉ አንድም ሆነ ሁለት ከእንጨት የተሠሩ ገበቴዎች በወይዘሮ አዳነችና በልጆቻቸው ሚስቶች የተሰፉ የተለያዩ የስፊት እቃዎች በፈላሻዎች የተሠሩ እንስራዎችና ማሰሮዎች የቅል ሸክናዎች የልብስ ቁሳቁሶች የእርሻ መሣሪያዎችና የጦር መሣሪያዎች ከሚጠቀሱት የቤት እቃዎችና ቁሳቁሶች መካከል ናቸው ከአቶ ረዳ መኖሪያ ቤት አጠገብ ክብ የሆነ ያልተመረገ ቤት የፍየሎች ያህያዎችና በተለይ ደግሞ ገና ያላደጉ እንስሳት የሚጠለሉበት ጋጣ አለ ትላልቅ እንስሳት በተለይ ከብቶት ፈረሶችና በቅሎዎች ግን እዚያው አጠገብ በግንዲሳና በእሾሃማ አጥር በተሠራው በረት ውስጥ ማታ ማታ ይታጎራሉ ዶሮዎች በዋናው ቤት ውስጥ የሚራቡ ሲሆኑ አንዳንድ ቤተሰቦች ደግሞ አህዮቻቸውንና ሌሎች እንስሳትን ሌሊት ሌሊት በቤት ውስጥ እንዲያድሩ ያደርጋሉ እያንዳንዱ ቤተሰብ በጭቃና በጨፈቃ የተሠሩ ክብ የሆኑ የእህል ጎተራዎች ከቤቱ ጋር በማያያዝ ይሠራል እንዲሁም ከቤት ውጭ የእህል ማከማቻ ክብ ጉድጓድ ይኖራል ሚስት ላላገቡ ጎረምሳ ልጆች ለአንድ ሰው መኝታ ብፓፖ የምትሆን አራት ማዕዘን የሆነች በጭቃና በጨፈቃ የተሰራች ጎጆ ስቅሎ ማየት የተለመደ ነው የአቶ ረዳ ልጅ መልኬ ድሮ ታላቅ ወንድሞቹ ይኖሩባቸው ከነበሩት ጎጆዎች ቀጥሎ ትንሽ ጎጆ አለችው በአቶ ረዳ ቤት ዙሪያ ልዩ ልዩ የጓሮ ተክሎችና ቅመማቅመሞች የሚተከልበት የታጠረ ግቢ ጓሮ አለ ከዚህም በስተቀር የተለያዩ ሰብሎችና የቅባት እህሎች በሰፊው ታርሰው የሚዘራባቸው የእርሻ ቦታዎች በተለያየ ቦታ ተራርቀው በተቆራረጠ ሁኔታ ይገኛሉ በዚህም ምክንያት የአንድ ቤተሰብ እርሻ ይዞታ ኩታገጠም አይደለም ሰባ በመቶ የሚሆኑ ያገቡ ወንዶች መኖሪያቸውን ከወላጆቻቸው አጠገብ መመሥረት የተለመደ መሆኑ ቢታወቅም ማንኛውም ትዳር ያለው ጎልማሳ ቢፈልግ ከአማቶቹ አካባቢ ፍላጎትና ምርጫው ከሆነም ከወላጆቹ አጠገብ መኖሪያ ቤቱን ሠርቶ የመኖር ሰፊ ምርጫዎች አሉት አንድ ቤት ሠሪ አንዳንድ ጊዜ ቤት ለመሥራት ካቀዳቸው አማራጭ ቦታዎቸ ላይ ጭብጥ አፈር በመዝገን ወደ ጠንቋይ አዋቂ ወስዶ በማሳየት የትኛው ቦታ የተሟላ ጤንነትና ሃብት ሊያስከትል አንደሚችል በማስጠንቆል ቤቱ የሚሠራበትን ቦታ ያስመርጣል እስከ ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ማብቂያ ድረስ ያገቡ ሰዎች «የጢስ ግብር» ለአማራ ሹም ላለመክፈል ሲሉ ቤታቸውን ከወላጆቻቸው አጠገብ መሥራት የተለመደ ነበር የጋራ ቤተሰብ የምንለው አባወራውንና ባለቤቱን ያላገቡ ልጆቻቸውንና እንዲሁም ያገቡ ልጆቻቸውን ከነቤተሰቦቻቸው ያጠ ቃልላል እንደዚህ ያለው ቤተሰብ ሳቢጠራ በአንድ ትልቅ ቤት ውስጥ የሚኖሩ ሲሆን ቤቱ ለእያንዳንዱ ቤተሰብ ለመኝታ ቤት ለምግብ ቤት ለማብሰያና ለማከማቻ እንዲያገለግል የተከፋፈለ ነው በአሁኑ ጊዜ ግን አዲስ ያገቡ ባልና ሚስት ለትንሽ ዓመታት ከባልየው ቤተሰብ ጋር ከኖሩ በኋላ የራሳቸውን ቤት ሠርተው ጉጆ ይወጣሉ በዚህ ዓይነት ሂደት ነጋሽና የሃያ ሰባት ዓመቷ ሚስቱ አልማዝ እንዲሁም አስራ ስምንት ዕድሜ ያላት ፀሐይ ከባለቤቷ ከቢተው ጋር አልፈውበታል የቤት ግንብታ ሥራ ሰብል ከተሰበሰበ በኋላ በበጋው ወቅት ተጀምሮ ክረምቱ እስኪገባ ይቀጥላልጸ ሥራው በቅርብ የቤተሰብ አባሎች የሚከናወን ሲሆን እቅድ ማውጣትና የጉልበት ሥራው በአቶ ረዳና በልጆቻቸው ይሠራል በቅድሚያ የቤት መሥሪያ እቃዎች ይዘጋጁና ቤት ሊሠራ ወደ ተመረጠበት ቦታ ይወሰዳሉ ከዚያም ልጆቻቸው ከቆረሟቸው የተለያዩ ዛፎች ለወራጅ ለቋሚና ለምሰሶ ወይም ለወጋግራ የተመረጡት እንጨቶች ተጠ ርበው ይዘጋጃሉ የቤት ሥራው እንደተጀመረ ጐን ለጐን ለማገርና ለግድግዳው የሚያገለግለው ጨፈቃ በየዓይነቱ ተቆርጦ ይቀርባል ቀጥሎም ሴቶች ለጭቃና ለእበት ማቡኪያ የሚሆነውን ውሃ እንዳቀረቡ ወንዶች አቡክተው ሴቶች የቤቱን ምርጊት ሥራ እንዲቀጥሉ ያስረክቧቸዋል የቤቱ ሥራ ከቤተሰብ አቅም በላይ ሆኖ ባዕድ በሆኑ ሰዎች እንዲሠራ ከተፈለገ አሠሪው መጠጥና ምግብ በቀን አንድ ጊዜም ሆነ ሁለት ጊዜ ማቅረብ ይኖርበታል ሁሉም አሁን የማይከተለው ቢሆንም በጥንቱ ልማድ መሠረት አቶ ረዳ ዶሮ አርደው መጠነኛ ግብዣ በማድረግ አዲሱ ቤት ይመረቃል በተጨማሪም ከግብዣው ጋር ተያይዞ «መስቂ» የተባለው ልዩ የተባረከ ጠሳ ከቤቱ ፊት ለፊት ይረጫል ቅዱስ ቦታዎች ቅዱስ ቦታዎች ድግናዎች ለእያን ዳንዱ የቅማንት ኅብረተሰብ በጣም አስፈላጊና በሕይወታቸው ወሳኝ ጉዳይ ናቸው እነዚህ ብዛት ያሳቸው ቅዱስ ቦታዎች በአማካይ ደረጃ በሚገኙት ቅማንት ዘንድ ከፍተኛ ግምት የሚሰጣቸው በመሆኑ የቅማንትን ሕብረተሰብ ከሌሎች ጉረቤት ከሆኑ ማኀበረሰቦች ልዩ አዛውንቱ አባወራ ጠብመንጃ አንግበው ከሚስታቸውና ከልጃቸው ጋር ከቤታቸው አጠገብ የተነሱት ቤቱ ከድንጋይና ከጭቃ የተሠራ ነው ብዙ የዚህ ዓይነት ቤቶች በቅማንት አገር አይታዩም ያደርጋቸዋል ቅማንቶች መጸለይ የሚፈልጉት ገላጣ በሆነ ቦታ ላይ ስለሆነ አብዛኛውን ጊዜ የጸሎት ሥነሥርዓታቸውን የማያካሄዱት ሠፊ በሆኑ ድግናዎች ነው እነዚህ ቅዱስ ቦታዎች ለሁለት ፈጽሞ ለተለያዩ ዓይነት አገልግሎት ይውሳሉ አንደኛው ለክብረበዓል ሌላው ደግሞ ለመቃብር ቦታ በተለይ የተወሰነ ነው ድግናዎች ጥንታዊ የባሕል ጀግኖችን ለዘለዓለም ለማስታወስ ታስቦ በእነሱ ስም የተሰየሙ ናቸው የክብረ በዓል ሥነሥርዓት የሚካሄደው በዓመት አንድ ጊዜ ለተወሰኑ ዓመት በዓላት ቢሆንም ትማንቶች ዘወትር ስለየዕለቱ ኑሮአቸው መሳካት አክብሮታቸውን ለአምላ ካቸው በድግናዎች ይገልጻሉ ለምሳሌ አንድ ግለሰብ ሥራ ጀምሮ እንደሆነ ፍፃሜውን እንዲሠምርለት ይሳላል ወይም እንደሚፈ መው ቃል ኪዳን ይገባል እያንዳንዱ ኀብረተሰብ የየራሱ ድግና ሲኖረው ከርከር ሰባት ድግኖች ስሳሏት የመሪነቱን ሥፍራ ይዛለች ገላጣ ቦታ ላይ መጸለዩ ባህላቸው ቢሆንም የጭልጋ ወምበር እየተባለ የሚታወቀው ከፍተኛው የቅማንት የሃይማ ኖትና የፖለቲካ መሪ «ሸዋንግ የሚባል ለተለያየ የጸሎት አገልግሉት የሚውል ቤት አለው ይህም የሆነበት ምክንያት ቅማንቶች ዙሪያውን ብዛት ባሳቸው ክርስቲያኖች በመከበባቸው የሃይማኖት ሥነሥርዓቱን በክፍት ቦታ ማድረግ ባለመፈለጋቸው ነው ሌላው በሁለተኛ ደረጃ መንፈሳዊ አምልኮት የሚካሄድበት ቦታ «ቆሌ» ወይም መንፈስ አለበት ተብሉ በሚታወት ቦታ ነው ይህ ቦታ ድግና ተብሎ ከሚታወቀው የክብረበዓል ቦታ በደረጃ ዝቅ ያለ ከአካባቢው መንፈስ ቆሌ ጋር ግንኙነት የሚደረግበት ነው ተብሎ ይነገራል ቦታው ከትልቅ ተራራ ጫፍ ሳይ ወይም የአንድ ገደል አፋፍ ሊሆን ይችላል ብዙውን ጊዜ በእንደዚህ ባሉ ቦታዎች ሳይ የሚገኝ አንድ ትልቅ ዛፍ ወይም ቋጥን ይሆናል እነዚህ ቆሌ አለባቸው ተብሎ የሚታመንባቸው አንዳንድ ቦታዎች «ምዝግና» ወይም «አደራ» እግዚአብሔር እና ሌሎች አማልእክት የሚታሰቡበት ቦታዎች ናቸው አምልኮት ከሚካሄድባቸው ቦታዎች በጣም የታወቀው ጭልጋ ውስጥ ጀልሸቭ ከተባለ ቦታ አጠገብ የሚገኘው «አዳሪ ፈርዳዳ» የእግዚአብሔር ፈረስ የሚባለው ነው በዚህ ኮረብታማ ቦታ ሳይ አንዲት ብቸኛ ዛፍ ምልክት ስትሆን አፈታሪካቸው እንደሚያ ስረዳው በጥንት ዘመን እግዚአብሔር ሕዝቡን ለመጉብኘት በፈረስ ወርዶ በነበረ ጊዜ የፈረሱ ኮቴ ያረፈበት ድንጋይ ላይ ምልክቱን ትቶ እንደተመለሰ ነው የሚነገረው ሌሎች ቅዱስ የሆኑ ቦታዎች ደግሞ ምንም ዓይነት የክብረበዓል ሥነሥርዓት የማይደሪሣሃባፐው ነገር ግን ያለፉት ወንበሮች አስከሬን ያረፉባቸው የመታብር ቦታዎች ናቸው የመጨረሻዎቹ ሦስቱ የከርከር ምበርሮት የተቀበሩት አበራክርና በተባለ ቅዱስ ቦታ ላይ ይገኛል ከአይምባ ቆሌ ከናተኛ ቦታ ላይ ሆኖ የሚታየው ከርከር አንቸው ሚካኤል በከፊል ሲታይ በሁለቱ ቁንጮ ተራራዎች መካከል ከአድማስ ባሻገር ጣና ሐይቅ አለ አካባቢው ወይና ደጋ ነው ከርከር ትማይታይና የቅማንት መሰብሰቢያ በተባለ ቦታ አንድ ደልዳላ ተራራ ላይ በወምበር ጃርጊ ሥቃብር ላይ በሣም ዝዙኅዓ የሆነ የወርካ ዛፍ የሚገነ ሲሆን ዛፉ የዛሬ ። ግደ ፍቅ መመመ ምዕራፍ ስድስት የፖለቲካ አደረጃጀት በጥንት ዘመን በተለይ በጦርነት ጦትት ወይም በኀብረተሰቡ ዘንድ ጠቅላላ ተውስ ሲፈጠር የመጩረሻው የፖለቲካ ሥልጣን ለእያንዳንዱ የጉሣ አባት ለምሳሌም እን ንደ ዘጠኙ ሳሉት የ«ክብር» የባህል ጀግኖች ይሰጥ ነበር ቻርት ቁ ይመልከቴ በሠላም ጊዜ ግን ሥልጣን ዲሞክራ ሲያዊ በሆነ መንገድ ይከፋፈል ነበር እኤአ ከ ዓም ትንሽ ቀደም ብሉ ትቅማንቶኝ በፖለቲካው ረገድ በባላባታዊው አገዛዘ ሥር ቢወድቁቱም ምንም ብዙ የሚያስፈራ የጦር ኃይል ስሳልነበራቸው ተፅፅኖ ሳይደረግባቸው የውስጥ የራስ ገዝ ሥልጣን ይዘው አንዲቆዩ ተፈቀደላቸው የኢትዮጵያ ነገሥታት ዜና መዋፅዕሉች እንደሚያስረዱት ቅማንት ምንጊዜም በአማራው ላይ እንዳልተነሣና የእራሳቸው አፈታሪክም ቢሆን የጦር ጀግኖቻቸው በአማራው መንግሥት ውስጥ ይሠሩ እንደነበር ነው የሚዘክሩት ይህ ለረዥም ዘመን የቆየው ከፊል ነፃ የፖለቲካ አስተዳደር ተቋም ብዙ የፍትሕ አመራር ሥልጣንን ስላጉናፀፋቸው ከባህላዊ ሕጋቸው ያፈነገጠውን እንዲታረም በማድረግ እንዲጓዙ ረድቷቸቐዋል በዚህም ምክንያት የጉሣው ማንነትና የኀብረተሰቡ አንድነት ለዘመናት ተጠብቆ ቆይቶአል በዎቹ ቅማንት የአማራን ባህል እንዲቀበል ሲገደድ የቅማንት ሃይማኖት እየተዳከመ በመምጣቱና ባህላቸውና ፖለቲካውም በአንድ ላይ የተሳሰሩ ስለነበር ጥንታዊው የፖለቲካ መዋቅር ጭምር እንዳልነበረ ሆነ የአንድነት መለያ የነበረው ተገልሎ የመኖር ስሜት እየተዳከመ መጣ ምንም እንኳን የነገሥታቱ የማስገደጃ ትዕዛዝ ባይኖርም የአማራን ባህል የመቀበሉ ሂደት በፍጥነት ቀጥሎ ብዙዎች በባህል ለውጥ አማራ አምሃራይዝድ ሆኑ ሂደቱም ቀጠለ አማራው በቅማንቱ ላይ የበላይነት ከያዘ ወዲህ የአስተዳደር ሥልጣን ደረጃው በየዘመናቱ የተለያየ ቢሆንም በአንፃሩ የባላባታዊ ሥርዓት ከመተከሉ በፊት የነበረውን ተመጣጣኝ የሆነ ሥልጣን እንደያዙ ቆይተዋል አማራው የፖለቲካውን ሥልጣን ቢይዝም ፍትሕ አሰጣጥን በተመለከተ ቅማንቶች ከፍተኛ የውስጥ ነፃነት ነበራቸው ይህ ነፃነት በአማራው ላይ ምንም ሥጋት ባለማስከተሉ ቅማንቶች የአራሳቸውን ሕጋዊ ችግሮች በራሳቸው የፖለቲካና ሃይማኖታዊ አደረጃጀት ስልትና ሥርዓት መሠረት መፍትሔዎችን ያስገኙ ነበር ሆኖም ከፍትሕ አሰጣጥ በስተቀር ሌላው ዓይነት ሥልጣን እስከ ተወሰነ ደረጃ ድረስ ነበር እንደጥንታዊው ዘመን ባህላቸው ቅማንት ዲሞክራሲያዊ ፈለግን በተከተለ መልክ ሥልጣንን ወደታች በተወረድ ያከፋፍሉ ነበር በዚህም መሠረት አብዛኛው የአስተዳደርና የዳኝነት ሥራ የሚሠራው በመጨረሻው ዝቅተኛ አርከን ላይ በሚገኘው የአዛውንቶች ሸንጐ ሲሆን በዚህ ደረጃ ሊፈቱ ያልቻሉ የአስተዳደርና የዳኝነት ችግሮች በመካከለኛ ደረጃ ከዚህ በላይ ለሚገኙ ቀሳውስትና የታወቁ ግለሰቦች ላሉበት የፖለቲካ ሥልጣን ለያዘ ቡድን ይተላለፋል በዚህ ደረጃ ችግሩ ካልተፈታ ደግሞ የመጨረሻውን የፖለቲካና የሃይማኖት ሥልጣን ለያዙት ለሁለቱ የጭልጋና የከርከር ወምበሮች ይተው ነበር የአዛውንቶች ሸንጐጉ የአዛውንቶች ሸንጉ መሠረታዊ የሆነ የቅማንት የሥልጣን ንዑስ ዘርፍ ነው የአዛውንቶች ሸንጐ አባላት የሸማግሌዎችና በኀብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነትና አክብሮት ያላቸው ሰዎች ስብስብ ነው ከፍተኛውን የመናገር የመከራከርና የመወሰን የኃይል ሚዛን ያላቸው በ«ካሣ ሥነሥርዓት ያለፉ ማለትም ከጉልማሳነት ወደ አዛውንትነት በሥርዓት ለማለፍ መስፈርቱን አሟልተው አክብሮት የተሰጣቸው ብጐ ሽማግሌዎች ናቸው ዋናው የደረጃቸው መለኪያ ወደ እሣግሣዚአብሔር ምዝግና የቀረቡ ናቸው ተብሉ ሲታመን ነው ሁሉም አዛውንቶች በካሣ ማለፍ ባይኖርባቸውም የአዛውንቶች ሸንጐ ከሃይማኖት ጋር የተሳሰረ ነው ማኀበራዊ ኑርን የሚመለከቱ የአስተዳደርና የፍትህ የዕለት ተዕለት ጉዳዮች ለአማራው ባለሥልጣን ሳይተሳለፉ ለቅማንቶች የአዛውንቶች ሸንጐ ቀርበው ይሠስናሉ በዚህም ምክንያት የቅማንት ኀብረተሰብ በፍቅር ተሳስሮ አንዲኖር አጋዥ ሆኗል ጥንት የክብር ዘር ያላቸው የሸንጐ አባላት አስተያየት ነበር ተሰሚነት የነበረው ይህ ዓይነት ዝንባሌ በመስፈኑና የቀሳውስትና የጦምበሮች ምርጫ ከቄስ ቤተሰብ ብቻ በመሆኑ ከሞላ ጐደል ዴሞክራሲያዊ የነበረው ሥርዓት ወደ ኣንድ ቡድን አመራር ተለውጦ እንደነበር እንገነዘባለን ሆኖም ባለፋት አርባ ዓመታት የ«ክብር» ዘር አባላት የበላይነት እየጠሩ በመምጣቱ የቡድናዊ አመራር ሥርዓትም ጉልቶ መታየቱን አቆመ መደበኛና መደበኛ ያልሆኑ ሸንጉዎች ሁለት ዓይነት ሸንጐዎች አሉ መደበኛና መደበኛ ያልሆኑ ሸንጉዎች መደበኛ ቨሸንጐዎች ወርሃዊ ስብሰባቸውን የሚያካሂዱት የቅማንት ኀብረተሰብ በሚካፈሉበት ማሕበር ነው ስለ ማኅበራዊ አባልነት አመራረጥና ዓላማ በሚቀጥለው ሰባተኛው ምዕራፍ ላይ ተገልዷል በመደበኛው ሸንጐ አዛውንቶች የፍትህንና የአስተዳደር ጉዳዮችን ለውይይትና ለውሳኔ ያቀርባሉ በየዓመቱ የሚመረጥ መሪ አለቃ ሰብሰባውን የሚመራ ሲሆን ለሚሰጠው አገልግሉት የሚከፈለው ነገር ባይኖርም በኀብረተሰቡ ዘንድ የተለየ ክብር ይኖረዋል እንዳአስፈላጊነቱ አቤቱታዎችንና ክሶችን እያየ ከሸማግሌዎች መካከል መርጦ ላቋቋማቸው ንዑስ ኮሚቴዎች ሥራውን ያከፋፍላል አንድ ንዑስ ኮሚቴ አንድ መሪና ሌሎች አምስት አባላት ያሉት ሲሆን ይህም እያንዳንዱ ወንድ ቅማንት በኀብረተሰቡ ውስጥ ባለው መንግሥት በሕይወቱ አንድ ጊዜ ሚና ኖሮት እንዲያገለግል እድል ያገኛል ማለት ነው ንዑስ ኮሚቴው ጉዳዮቹን በማጣራት የመደበኛው ሸንጐ ውሳኔ እንዲሰጥበት ያቀርባል መደበኛ ያልሆኑት የአዛውንቶች ሸንጉዎች ከዚያም ከዚህም የተውጣጡና በከሳሸና በተከሳሸ የተመረጡ አንድ የቡድን መሪና ከአምስት እስከ ሰባት የሚደርሱ አባላት ያሉት ሆኖ ዋናው ሥራው የፍትሕን ሥራ ማከናወን ነው በመደበኛውና በንዑስ ሸንጐው እንዲሁም መደበኛ ባልሆነው ሸንጐ የሚደረጉት ምርመራዎችና በጉዳዩ ላይ የሚደረጉት ውይይቶች ብዙ ወራትንና ከዚያም አልፎ ዓመታትን ሊጨርሱ ይችላሉ ይህም የጊዜ መራዘም በማኅበረሰቡ መረጋጋትን ያስከ ትላል ምክንያቱም አንድ ቀን ተከራካሪዎቹ ሸንጐው በነፃ ይለቀናል የሚል ግምት ስለሚኖራቸው አንዱ በአንዱ ላይ ግጭት ለማስነሣት አይደፍርም ክስ አድሜያቸው የገፋና በካሣ ሥርዓት ያለፉ በመሆናቸው አቶ ረዳ የአንድ መደበኛ ሸንጐ አባል ሆነው አብዛኛውን ጊዜ መደበኛ ያልሆነ ሸንጉ ይመራሉ የመስክ ሥራዬን በማከናውንበት ጊዜ አቶ ረዳና ሌሎች የአንድ አዛውንት ሸንጐ አባላት ሆነው ሲሠሩ ታዝቤቧያለሁ በተለይ ሲያስችሉ ያየሁት አንድ ወጣት ሰው ከአንድ ሸምገል ካለ ግለሰብ ላይ ፈረስ ገዝቶ በክፍያና በርክክብ ሳይ የተነሣውን ክርክር ነበር በቀጠሮው ቀን ዒቂማምና ሸበቶ የሆኑ አዛውንቶች ጋቢያቸውን ደርበው ሜዳዎችን አቋርጠው በመምጣት ገላጣ በሆነ ሥፍራ ላይ በሁለት ዛፎች ሥር ተኩለኩሉ በቀረበላቸው አንድ ማንቆርቆሪያ ጠላ ጊዜያዊ መስተንግዶ እየተደረገላቸው እንዳለ ማንኛውም የሚወስነው ቅጣት በዋስ አማካይነት ተፈጻሚ እንደሚሆን በመገንዘብ የስብሰባው መሪ በቅድሚያ ሁለቱ ተከራካሪዎች ዘመድ አዝማዳቸው ባሉበት ዋስ እንዲጠሩ አደረጉ ከዚያም አቶ ረዳና ሽማግሌዎቹ ሁለት ወገኖች የሚሉትን ለመስማት በተናጠል አነጋገሯቸው ይህም የተደረገው በአንድ ላይ ቢያነጋግሯቸው በባለጉዳዮችና በምስክሮች መካከል ጭቅጨቅ እንዳይነሣና የፍርዱ ሂደት እንዳይደናቀፍ በማሰብ ነበር ሸማግሌዎቹ ጉዳዩን እንዳጠኑት ወጣቱ ከሸማግሌሊሌው አንድ ፈረስ በብር ገዝቶ ቀብድ ብር ሰጥቶ ቀሪውን ብር ገንዘብ እንዳገኘ ከፍሎ ፈረሱን ለመረከብ ተስማምተው አንደነበርና ወጣቱ ቀሪውን ከፍሎ ፈረሱን ለመውሰድ ቢጠየቅ የመጀመሪያውን የቀብድ ክፍያ ሽማግሌው በመካዱ ነበር ክርክሩ የተነሣው ሽማግሌዎቹ ለብዙ ሳምንታትና ሰዓታት እየተቀመጡ ጉዳዩን መርምረው ካጣሩ በኋላ አንድ ውሳኔ ላይ ደረሱ ውሳኔውም «ሸማግሌው ገንዘቡን ይመልስ ወይም ፈረሱን ያስረክብ» የሚል ነበር ብዙ ጊዜ እንደሚያጋጥመው ሸማግሌው ውሳኔውን ስለተቃወመ መብቱም የተጠበቀ ስለሆነ ሸማግሌዎች ጉዳዩን በጥሞና መመርመር ቀጠሉ ሸማግሌው መንቻካ ብጤ በመሆኑ ትዕዛዙንም ሳይፈጽም እንዲያውም ወደስብሰባው መምጣቱን አቋረጠ ለብዙ ወራት ወደስብሰባው እንዲመጣ ቢለመንም አሻፈረኝ በማለቱ የአዛውንቶች ሸንጐ ባህላዊ ውግዘታቸውን ለማድረግ በማሰባቸው በላኩት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ «በሸንጐጉጐው እንድትገኝ ካልተገኘህ እንረግምሃለን በማለት ትዕዛዝ አስተላለፉ አርግማኑ የሚፈፀመው የተባረከው «መስኪ» ተብሉ የሚታወተውን ጠላ በሚረገመው ሰው ስም መድፋት ነበር የማይቀረው ውሳኒ ከሚሰጥብኝ ብሎ በመፍራት በመጨረሻ ሽማግሌው ሸንጉው ፊት ቀርቦ ውሉን ለመፈጸም ተስማማ ሆኖም ለውሉ ሃስፈጸሚያ ከውል ውጭ በተጨማሪ ብር እንዲሰጠው ተደረገ አንድ ውሳኔ ተቀባይነት ሲያገኝ ሁለቱን ተከራዛሪዎች ድንጋይ አሸክሞ ማስታረቅ የተለመደ ሰለነበር በመጀመሪያ ሸማግሌው ቀጥሎ ደግሞ ወጣቱ ድንጋይ ተሸክመው ተራ በተራ «ይቅር በለኝ ከተባባሉ በኋላ ተሳስመው የመጨረሻው እርቅ ሆኖ በአዛውንቶች ሸንጐ ተመርቀው ተሰናበቱ ሁሉም የሸንጎ አባላት በ«ካሣ» ሥነሥርዓት ያለፉ በመሆኑ ምርቃታቸው ከፍተኛ ግምት የሚሰጠው መሆኑን መረዳት ተገቢ ነው በአቶ ረዳና በሌሎች የሸንጎ አባላት የታዩት ሌሎች ክርክሮች ስለመሬት ይዞታ መብት ሌሊት ሌሊት ድንበሮች ተገፍተው ስለሚገኙ የሚከሰቱትን ችግሮችና የመሳሰሉትን ያካትታል ልዩ ልዩ ጉዳዮች ደግሞ አንድ ግለሰብ ውሻው በመግደሉ ከአንድ አባወራ ራቅ ባለ የአርሻ ይዞታው ላይ ስልሣ ዛፎች ባልታወቀ ሰው ስለተወሰደበትና አንዳንድ ሰዎች ደግሞ ስለተሰደቡ ያቀረቡትን የካሣ ጥያቄ ይመለከት ነበር አንድ ጉዳይ በአዛውንት ሸንጎ ሳያልቅ ለብዙ ጊዜ ከተዘና ሊያልቅ ካልቻለ ከፍ ወደአለ የቅማንት የፖለቲካና ሃይማኖት ድርጅት ይተሳላለፋል ምን ጊዜም ቢሆን ቅማንቶች አንድ ጉዳይ በሸንጐዎቻቸው እንዲያልቅ ነው ፍላጐጉታቸው ይህንኑ ለማጠናከር አቶ ረዳ «አንድ አይነድ አንድ አይፈርድ» የሚለውን ጥቅስ በየጊዜው ያነሳሉ ክርስቲያን ቅማንቶችና ሸንጉዎቻቸው በክርስቲያን ቅማንቶች ዘንድ ሁለቱም ዓይነት ባሕላዊ ሸንጐጉዎች አሉ መደበኛው ሸንጐ በየወሩ አንድ ወይም ሁለት እሁዶች የሰንበቴ ስብሰባ ተብሎ በሚታወቀው የማኅበሩ አባላት በሚገኙበት ቀን ይደረጋል ሸማግሌዎች በየዓመቱ በሚመረጡና እኩል ሥልጣን ባላቸው ሁለት መሪዎች ሰብሳቢነት ሥራቸውን ያከናውናሉ በክርስቲያን ቅማንቶች ዘንድ ሽማግሌዎች በ«ካሣ ሥነሥርዓት ማለፍ ተፈላጊነት የሌለውና አንዲሁም እንደ አረማዊኦሪታዊ ቅማንቶች የሃይማኖት ተፅዕኖ በሸንጐዎች ላይ አይኖርም ነገር ግን በአንዳንድ የክርስቲያን ቅማንቶች ዘንድ በአረማዊኦሪታዊ ሥርዓት የነበረው ኃላፊነት ወደ አማራው መዋቅር ሙሉ በሙሉ አልተሸጋገረም ስለሆነም ያዛውንቶች ሸንጐዎች ውሳኔአ ቸውን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ የባህላዊ አሠራሩን ትንሸ ለማሻሻል ጥረት እያደረጉ ቢሆንም አሁንም ከጥንቱ የቅማንት አሠራር ሥነሥርዓት ለመላቀቅ አልቻሉም ለምሳሌ የሸንጐውን ውሳኔ ለማስፈፀም ከአስር ዓመት በፊት ክርስቲያን የሆኑት አንካን ወደ ድግናው አሁንም መሄድ አለባቸው እዚያ ሄደው ለአግዚአብሔር ምዝግና ፀሎት በማድረግ ውሳሄአቸውን አልቀበልም ወይም ካሣ አልከፍልም ባለው ሰው ላይ ተገቢው ቅጣት እንዲወስንበት ያደርጋሉ ጥፋተኛ ነው የተባለው ሰው በምዝግና ተቀጥቶ መጥፎ ዕድል ቢያጋጥመው ወይም ጥፋቱን አምኖ ካሣውን ለተበዳዩ ቢከፍል ተበዳዩ ወደ ድግናው ሄዶ የእንስሳ መስዋዕት በማቅረብ በኀብረተሰቡ ላሉ አዛውንቶች ግብዣ ያደርጋል በሁሉም ክርሰቲያን ቅማንቶች ዘንድ በአዛውንቶች ሸንጐ የሚሰጠው የመጨረሻ ውሳሄ አጥፊውን በማውገዝ ጠሳ መሬት ላይ በመድፋት ሲሆን ሰንበቴው ደግሞ ወንጀለኛ የተባለውን ሰው በመርገም ነው ይህ «መስኪ» የተባለውን የተደገመበትን ጠሳ በመድፋት የሚደረገው የአርግማን ባህል በአረማዊኦሪታዊ ቅማንቶች ሲደረግ ከነበረው ሥነሥርዓት የተወሰደ ሆኖ እናገኘዋለን የቅማንት የአዛውንቶች ሸንጐዎች በኀብረተሰቡ ውስጥ በፍትሕ አሰጣጥ ረገድ የሚጫወቱት ሚና የክርስቲያን ቅማንቶች የሰንበቴ ማኀበራትም ሆኑ የክርስቲያን የአዛውንቶች ሸንጐዎች ካላቸው የፍትሕ አሰጣጥ ኃላፊነት በጣም የላቀ ነው በነገራችን ላይ የሰንበቴ ማኅበራት በክርስቲያን አማራዎችም ያለ ሥርዓት ነው ክርስቲያን ቅማንቶች አሁንም ቢሆን ወደ አማራው ባለሥልጣን ሳይሄዱ ጉዳያቸውን እርስ በእርሳቸው ለመጨረስ ነው ፍላጐታቸው አሠራሩ ሁልጊዜ አንድነታቸውን ከማስጠበቁም በላይ ከሞላ ጐደል በአማራውና በቅማንቱ መካከል ያለው ግንኙነት ድንበር ተዘግቶ አንዲቆይ አድርጓል የ ዥ ጋ አ ሩ መደበኛ የአዛውንቶች ሸንጐ ሁለት ዓመት የፈጀውን የመሬት ክርክር ሲመለከቱ የያዙት ረጃጅም በትር ውሻ ለመከላከል ይጠቀሙበታል ቢሆንም በሚቀጥሉት አስርና ሃያ አመታት ክርስቲያን ቅማንቶች ሙሉ በሙሉ የአማራን ባህል ተተብለው በባህላዊ ውህደት አማራ አምሃራይዝድ እንደሚሆኑ በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል ቨንጎዎችና የውጭው ዓለም የአዛውንቶች ሸንጎ ከቅማንት ኅብረተሰብ ውጭ ከሌላው ዓለም ጋር ግንኙነት በማድረግ የሚጫወቱት ሚና አለ ከማኅበረሰባቸው ውጭ ከሚነጋገሩባቸውና ውሳኒ ከሚሰጡባቸው ጉዳዮች በጥቂቱ ለመጥቀስ ያህል ከአማራው ኀብረተሰብ ጋር ግንኙነት በማድረግ በትብብር የሰው ጉልበት አዋጥቶ መንገድ ለመጠገንና እንዲሁም በአካባቢው ሚሲዮናውያን እንዲገቡም ሆነ አንዳይገቡ ተነጋግሮ ውሳክ መስጠትን የመሳሰሉትን ያካትታል ሌላው ደግሞ በአካባቢው ተጨማሪ አዲስ የመሰብሰቢያ አዳራሾችን ወይም አዲስ መንገዶችን በጋራ ለመሥራት የሚደረጉ የጋራ ግንኙነቶች ይኖራሉ መካከለኛው የፖለቲካ ሥልጣን በድሮው ዘመን ዝቅተኛ ቀሳውስት አባጋሪየስ እና ክብር የሆኑ ከፍተኛ ቀሳውስት ከመዘና አሁን ካሳቸው የፖለቲካ ሥልጣን የበለጠ በፖለቲካው ሰፊ ሚና ነበራቸው በአሁኑ ወቅት ለስሙ ያህል አንዳንድ ክርክሮችን አዳምጦ መፍትሔ ከመፈለግና በኀብረተሰቡ ዘንድ ሰላም ሰፍኖ መልካም ግንኙነት እንዲኖር ምክር ከመስጠት በስተቀር ብዙም ኃላፊነት የላቸውም ሆኖም ፍትህን በተመለከተ ወምበሩን ይረዳሉ ዛሬ አብዛኛው የፍትሕ ሥራ የሚከናወነው አፈሊቅ ተብሎ በሚታወቀው የወምበሩ ቃል አቀባይ ነው አፈሊቁ ከክብር ዘር በወምበሩ የሚመረጥ ሲሆን በትርፍ ጊዜው ለሚሠራው ሥራ ተገቢውን ክፍያ ወምበሩ ይሰጠዋል በኅብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነትና አክብሮት ያለው ብቻ ነው ለዚህ ሥራ ብቁ የሚሆነው ባለፉት ዘመናት አፈሊቁ ከቦታ ቦታ እየተዘዋወረ ለከርከሮች ውሳኔ ይሰጥ ነበር እንዲሁም ኀብረተሰቡና ቀሳውስቱ የቅማንትን ሕግ እያከበሩ መሆኑን ይቆጣጠር ነበር አፈሊቁ ቅጣት የመወሰንና ቅጣት የመሰብሰብ ሥልጣን ቢኖረውም በቀሳውስቱ ላይ ይህንኑ ሥልጣን የተጠቀመበት ጊዜ በኅብረተሰቦች ዘንድ ብዙም አይታወስሰም እያንዳንዱ ወምበር ብዙ አፈሊቆች የነበሩት ቢሆንም የአረማዊኦሪታዊ ቅማንት ቁጥር በፍጥነት እየቀነሰ በመምጣቱ ክፍት በሆኑት የአፈሊት ቦታዎች ሌላ ሰው መተካት አስፈላጊ ሆኖ አልተገነም አፈሊቁቴ ሊወስናቸው ያልቻላቸው ችግሮችና ጉዳዮች ለወምበሩ እየቀረቡ ተገቢውን ውሳኔ ያገኛሉ ወምበር የመጨረሻው ዳኛ ወምበሩ የቅማንት ቀሳውስት የበላይ ብቻ ሳይሆን የፍትህና የአመራር ሥልጣን ያለው ሰው ነው በመካከለኛ ደረጃ በሚገኘው የፖለቲካ ሥልጣን አካላት ሊፈቱ ያልቻሉ ክርክሮች ወይም ጥሎሉች ወደ እሱ ይመራሉ ቅማንቶች በአስገዳጅ ሁኔታዎች የአማራን ባህል እንዲቀበሉ ከመደረጉ በፊት በከርከር አንድ የበላይ ወምበር በጭልጋ ደግሞ አንድ ሌላ የበሳይ ወምበር በአጠቃላይ ሁለት ወምበሮች ነበሩ ከወምበሮች ተጥሎ አስር የሚያህሉ ንዑስ ወምበሮች የነበሩ ሲሆን ከጓንግ ወንዝ በስተምስራቅ ያሉት በከርከር ወምበር ሥር ከጓንግ ጦንዝ በስተምዕራብ የነበሩ ደግሞ በጭልጋ ወምበር ሥር ይታዘዙ ነበር በጣም አስቸጋሪ ጉዳይ ካላጋጠማቸው በስተቀር ንዑስ ወምበሮቹ ማንኛውም ለሚቀርብላቸው ክርክሮች ሁሉ ውሳኔ ይሰጡ ነበር እኤአ በ ዓም መጀመሪያ አካባቢ ሁለቱ የበላይ ወምበሮች ብቻ ቀሩ ከሁለቱ ወምበሮች የከርከሩ ወምበር ሳቅ ብሉ ስለሚታይ «ታላቁ ወምበር» አየተባለ ይጠራል እኤአ በ ዓም የከርከሩ ወምበር ከሞቱ ወዲህ በምትክ ሌሳ ወምበር ሳይሾም በመቅረቱ በአሁኑ ጊዜ የጭልጋው ወምበር ብቻ ነው በመላው የቅማንት አገር የሚገኘው ከወንበሩ ፊት መቅረብ ወምበሩ አብዛኛውን ጊዜ ከከመዘናውና ከፍተኛው ቄስ በኀብረተሰቡ ከሚገኙ ቀሳውስት ጋር ሆኖ ነው አቤቱታዎችን የሚቀበለው ሦስቱም አካላት ከሳሸንና ተከሳሽን በማነጋገርና አስፈላጊ የሆኑትን ጥያቄዎች በመጠየቅ ከመጨረሻ የውሳኔ ሃሳብ ላይ ይደርሳሉ ነገር ግን የመጨረሻውን ውሳኔ የሚሰጠው ወምበሩ ነው ጉዳዩ የሚመለከታቸው ደጋፊዎችና ምስክሮች ዋሽተው ከተገኙ ምዝግና እንደሚቀጣቸው አስቀድሞ ማስጠንቀቂያ ይሰጣቸዋል ከሳሽና ተከሳሸ ለክሱ ተመጣጣኝ ነው የተባለ ለዳኝነት ከብት ወይም ሰብል ወይም አህል ብዛቱን ወይም ስፍሩን ገልጸው ዋስትና ቦንድ ማቅረብ አለባቸው በመፅሬቤረሻ ከሁለቱ አንዱ የተረታው ለዋስትና ያስያዘው ንብረት በመተጫሓ ሰም ገቢ ይሆንና ወምበሩ ከዚሁ ድርሻውን ያገኛል ከርክሮች በመረጃዎች አለመሟላት ምክንያት ዳር ሊደርሱ ካልቻሉ ወይም በሁለቱ ሠወገኖት በኩል የተነገረው ታሪክ እኩል ሚዛን ከደፋ ወምበሩ ከሳሸና ተከሳሸን በአቅራቢያው ወደሚገኘው ቅዱስ ድግና ደን ይወስዳቸዋል ከዚያም በወምበሩ ትእዛዝ መሠረት ቀሳውስቱ ለተከሳሹ መጥረቢያና ማጭድ ይሰጡታል ተከሳሹ በያዘው መሣሪያ በድግናው ከሚገኙ አንዱን ዛፍ ቆርጦ መጣል ስላለበት በሚቆርጥበት ጊዜ ጮክ ብሉ «ወንጀለኛ ሆኙ ከተገኘሁኝ ይህን ዛፍ እንደቆረጥኩት ምዝግና እኔንም ይቆራርጠኝ» ማለት አለበት ተከሳሽ በአርግጥ ወንጀለኛ ከሆነ የሚመጣበትን መቅሰፍት በመፍራት ገና መሣሪየውን ሳይነካ ጥፋቱን በመናዘዝ ንስሀ ይገባል ንፁህ መሆኑን ካመነ ግን ዛፉን ለመቁረጥ ወደኋላ ስለማይል አርግማኑ ውሸታም ወደሆነው ከሳሽ እንዲተላለፍ ይደረጋል ከሳሹ የሐሰት ማስረጃ ማቅረቡን ወይም ተከሳሹ የመቁረጫ መሣሪያውን ከመቀበሉ በፊት ስለጥፋቱ በማመን ንስሀ ከገባ ማንኛውንም ቅጣት በቀጥታ ሁለቱም ወገኖች ግማሽ ግማሹን ይከፍሳሉ በመጨረሻ ውሳኔ ላይ ሲደረስ ወምበሩ የገንዘብ መቀጫ ይጥሳል ከዚህም በስተቀር ንብረቶችን ወደ ትክክለኛው ባለ ሀብት ይመልሳል መሬትን የሚመለከት ክርክር ከሆነ ሕጋዊ ባለመሬቱ ማን እንደሆነ ያረጋግጣል ተራ ለሆኑ የሃይማኖት ሕጐች መጣስ አጥፊው ለሰባት ሌሊት ባዶ መሬት ላይ እንዲተኛ ወይም ለሰባት ቀን ኮሶ እንዲጠጣ ወይም በየተኑ ውሃ በማመላለስ ሰውነቱን እንዲታጠብ ሊወሰን ይችላል እንዲሁም ቅዱስ ቦታዎችን ማርከስ ለሃይማኖት አባቶች ተገቢውን አክብሮት አለመስጠትና በዓላትን በተገቢው ሥነሥርዓት አለማክበር ሎት እስከ ሁለት አሞሌ ጨው ሊያስከፍሉ የሚችሉ ጥፋቶች ናቸው ወምበሩ የቅማንት የጥንት ባህሎችና ልምዶች ተጠብቀው አንዲቆዩ በጣም የሚያስፈሩ ማለትም የቀብር ሥነሥርዓት ከመከልከል ጀምሮ እስከ ገነት መግቢያ በሮችን መዝጋት ድረስ የሚደርስ ቅጣት ይወስናል እርግማንና ከኀብረተሰብ ማግለል በወምበሩ የሚሰነዘሩ ቅጣቶች ሲሆኑ አብዛኛውን ጊዘ ተሣባራዊ የሚሆኑት የእሱን ሥልጣን በሚቀናቀኑት ሳይ ነው ለምሳሊ አንድ ግለሰብ የወምበሩን ውሳኒ ሳይቀበል ቢተር መሠረታዊ ከሆነው ከቅማንት ሃይማኖታዊ ሥርዓት ው ጋብቻ ቢፈጽጵም ከነብረተሰቡ ይገለላል ከኀብረተሰቡ መገለል ማለት የማይሻርና የማይለወጥ እንዲያውም ሰውዬው ከሞተም በኋላም ተግባራዊ የሚሆን ውሳኔ ነው የተወገዘ ወጦይም የተገለለ ሰው ቀብሩ በሥነሥርዓት አይፈጸምም ወደገነት ያስገባል ተብሎ የፒደረገው ሥርዓተቅዳሴ ስለማይደረግለት ወደገነት መግቢያ በር ሁሉ እንደተዘጋበት ይቀራል ነፍስ ግድያና ወምበሩ ለወምበሩ የሟቀርብ በጣም የከፋ ወንጀል ቢኖር ነፍስ ግድያ ነው ለቅማንቶች ድንገተኛም ይሁን ወይም በመከሳከል ጦቅት የሚደርስ ግድያ በአጠቃላይ የሰውን ነፍስ ማጥፋት ማለት ስለሆነ በነፍሰገዳይነት ነው የሚያስጠ ይቀው የቅማንት ሕግ «ዓይን ያጠፋ ዓይኑ ይጥፋ ስለሚል የአንድ ሰው ሕይወት ያጠፋ ግለሰብ የሚሰጠው ፍርድ ሕይወቱ በሟች ዘመድ እንድታልፍ ማድረግ ነው ምርጫ ባይኖርም አንድ አርዳታ ግን ሊደረግለት ይችላል ይኸውም ዘመዶቹ የደም ካሣ ከፍለው እንዲታረቁ ማድረግ ነው ከሃምሣ ዓመት በፊት የደም ካሣ ዐ ማርያ ቴሬዛ ብር ነበር አሁን ግን ዝቅተኛው አራት መቶ ብር ሆኖ አንዳንድ ጊዜ ከ እስከ ብር ይደርሳል የገዳይ ቤተሰቦች ከሟች ቤተሰብ ጋር በሸንጉዎችና በሌሎች አስታራቂዎች አማካይነት ስምምነት ላይ መድረስ ካልቻሉ ወምበሩ በጉዳዩ ጣልቃ ይገባል ከሁለቱ ወገኖች ስምምነት ከተደረሰ መከፈል የሚገባው ካሣ በወጦምበሩ ወይም በአዛውንቶች ሸንጐ አማካይነት የቃል ስምምነት ይገባሉ ይህም ስምምነት በሁለቱ በኩል ለመንግሥት ሹማምንት ይሰጥና እነሱም በተጨማሪ ለወንጀሉ መከፈል የሚገባውን የገንዘብ ቅጣት ከጥፋተኛው ተቀብለው ለግድያ የተጠቀመበትን ማሣሪያ በመግፈፍ በውርስ ለመንግሥት ገቢ ያደርጋሉ በዚህም መሠረት መንግሥት ስለነፍስ ገዳዩ ወንጀል በቅማንቶች የተሰጠውን ውሳኔ አፀደቀ ማለት ነው በስምምነቱ መሠረት አስፈላጊው ሁሉ ከተሟላና የመንግሥት ቅጣት ገቢ ከሆነ በኋላ ገዳዩ ላይ በተጨማሪ ሌላ ቅጣት እንዳይደርስበትም ፋይሉ ይዘጋል እስከትርብ ጊዜ ተነንቶትን የሚመለከት ክስ የአማራው መንግሥት ለጭልጋ ወይም ለከርከር ወምበር ያስተላልፍ ነበር ጦምበሩም ሦን እርምጃ አንደሰነ። የ«ክብር»ና የ«የታንቲ» የዘር ክፍያዎች በአባት የዘር ሐረጋቸው የሚለዩ ሲሆን የቅስና ደረጃን ለማግኘት የአባት የዘር ግንድ ወሳኝ ነው በአንድ የዘር ግንድ ያሉ ሰዎች ጋብቻቸው ከውጭ እንጂ እርስ በእርሳቸው አይጋቡም የመጨረሻው የከርከር ወምበር ልጅ እንደነገሩኝ አንድ «ክብር» ሌሳ «ክብር» ሴት ወይም አንድ «የታንቲ» ሌላዋን «የታንቲ» ቢያገባ ልክ እህቱን እንዳገባ ነው የሚቆጠረው ሆኖም የጋብቻው ሕግ ተራ የዝምድና ክፋይ ሐረጐችን አይመለከትም ስለዝርዝሩ መግለጫ ቁጥር ሁለትን ይመልከቱ ጥብቅ የሆነው የጋብቻ ሕግ በኀብረተሰቡ ዘንድ የተከለከ ለውን የዘመዳሞች የእርስ በእርስ ጋብቻን ሲቆጣጠረው ቆይቷል ከዚህም በስተቀር ቀደም ብሎ እንደተጠቀሰው ቀሳውስቱ ከቀብር ሥነሥርዓት ማገድ ጀምሮ እስከ ገነት በር መዝጋት ውግዘት የሚደርስ የሚያስፈራ ቅጣት ስለሚወስኑ የሕጉ ተግባራዊ መሆን አጠያያቂ አልነበረም በመሆኑም ማንም ይህን ሕግ ለመጣስ ስለማይፈልግ ቅማንት ያልሆነ ሌሳ ሰው ውስጣቸው አይገባም እስከቅርብ ጊዜ ድረስም ከእነሱ መካከል በጋብቻ ምክንያት ይህን በቅርብ የተሳሰረ ኅብረተሰብ ጥሎ የሄደ የለም ስለዚህ ይህ ጭምር አደረጃጀት በወምበሩና በቀሳውስቱ ጥበቃ እየታገዘ ሕብረተሰቡ ከሌላው ሕዝብ ጋር እንዳይገናኝ አጥር ሆናኖ ኖሯል ምንም እንኳን የቅማንት አፈታሪኮች የኢትዮጵያ ዚና መዋዕሎችና አገር ጎብኝ አውሮጳውያን ብዙ ሚስቶት ማግባት የተፈቀደ እንደነበረ ቢገልጹም በቅማንት ኀብረተሰብ ጋብቻ አንድ ለአንድ ነው የሚፈቀደው እቁባት መያዝ ኣለ ቢሆንም በሕጋቸው መሠረት ከአንድ ሚስት በላይ ማግባት የተከለከለ ነው ማንኘውም ቅማንት ወንድም ሆነ ሴት በአጠቃላይ «ክብር» ወይም የታንቲ» ተብሎ ይታወቃል የግለሰቡን ያታና ትክክለኛ ደረጃቸውን ለመረጋገጥ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ሁሉም ክብር ወንዶች ክብር ተብለው ይጠራሉ እንዲሁም የየታንቲ ወንዶች የታንቲ ይባላሉ ይህ ሊሆን የሚችለው ግን የየታንቲ ወንድ ልጅ ልጅ ከሆኑ ነው መገለጫ ሁለትን በድጋሜ ይመልከቱ አንድ ወንድ ወይም ሴት የየታንቲ ዘር ሆናሆና የአንድ ወንድ የክብር የልጅ ልጅ ወንድ ወይም ሴት ይሁን ሰንከራይሁራ» ተብለው ይጠራሉ «ሁራ» ማለት ልጅ ማለት ነው የክብር ዘር የሆነች ሴት አባቷ ክብር ከሆነ «ሰንክራ»ትባላለች የየታንቲ የዘር ክፍይ ያላት ነገር ግን «ሰንክራይሁራ» ካልሆነች «አናዝቴ» ትባላለች የታንቲ የሆነ ወንድ የልጅ ልጅ ናት የትውልድ ሐረግ የአባት የዘር ግንድን ተከትሎ ስለሚታይ ልጆች የአባታቸውን የዘር ሐረግ ተከትለው ነው የሚቆጠሩት ነገር ግን የጋብቻ አፈጻጸምን በተመለከተ ጥንድ የሆነው አደረጃጀት በንዑስ ዘርፎች በቀላሉ አይለይም የታንቲ የሆነ አባት ያሳቸው እና «ሰንክራ» የሆነች እናት ያላቸው ልጆች ከጋብቻ በስተቀር በማንኛውም ረገድ የ«የታንቲ» ደረጃ ተሰጥቶአቸው «የታንቲ» ወይም «አናዝቲ» ተብለው የሚጠሩ ሳይሆን «የሴንክራ ልጅ» ተብለው ነው የሚታወቁት «ሴንክራሁራ» ደረጃው ክብር ለመሆን የተቃረበ ስለሆነ ከክብር ጋር አይጋባም ይህ የሚያመለክተው የክብር ከፍተኛ ደረጃን ለመጠበቅ ያህል የክብር የልጅ ልጆችን እንኳን ይህን መብት ይነፍጓቸዋል ከቅርብ ዘመድ ጋር የግብረሥጋ ግንኙነት ማድረግና ጋብቻ መፈፀም በማንኛውም የቅማንት የዘር ክፋዮች የተወገዘ ሲሆን በደም የተገናኙ ከሆነም ሰባት ትውልድ ቆጥረው መጋባት እንዳለባቸው ነው ባለፉት አርባ ዓመታት ቅማንቶች ይህን የጋብቻ ባህል ወደ አራት ትውልድ ዝት ያደረጉት ቢሆንም የጥንቱ ሕግ የተሻለ መሆኑን የማሚናገሩ አሉ በክብርና በየታንቲ ያለው ልዩየነት ቀደም ብሎ አንደተ ገለፀው ወምበሮች ከፍተኛ ቀሳውስትና ከፍተኛ የሃይማኖትና የፖለቲካ መሪዎች እንዲሁም የወምበሩ አፈሊቅ ቃል አቀባይ እና ዋናው የአልፍኝ ኃላፊ ከክብር የዘር ሀረግ ካላቸው ነው የሚመረጡት ዝቅተኛ ቄሶች «መስኪ» የተባለውን የተቀደሰ ጠሳ ጠበል የሚጠብቁት ደግሞ ከየታንቲ ዘር ነው የሚመረጡት እስከቅርብ ጊዜ ድረስ አንድ የክብር ሸማግሌ መደበኛ ያልሆነ የአስታራቂነትና የአማካሪነት ሥራ ስለሚሠራ በፍትሕ በኩል ያለው የሥራ ድርሻ ቀላል አይደለም አንድ የታንቲ ወይም ሴንክሬይሁራ በደል ከደረሰበት የክብሩን ጉልበት በመሳም ችግሩን ይገልጻል የክብር ሽማግሌው በቀሳውስት በኩል ከፍተኛ ውግዘትም ሆነ እርግማን አንደሚደርስ በማግባባት ያስታርቃል ለክብር ሸማግሌው የተሰጠው ሥልጣን በክብርና በየታንቲ ላለው የመደብ ልዩነት አንዱ ምልክት ነው ሆኖም በአሁኑ ዘመን በማስታረቁ ሥራ የሚጫወቱት ሚና በክብር ወይም በየታንቲ ወይም በሴክራይሁራ ሸማግሌዎች መካከል ልዩነት አይታይም ዛሬ ባለባበስ በቤትና በመሣሪያ እንዲሁም በመሬት ይዞታ በክብርና በየታንቲዎች ልዩነት ባለመኖሩ በሀብት በኩልም አንዱ ከሌላው አይበልጥም አንዳንድ ሰዎች ክብሮች ከየታንቲዎች የበለጠ በርካታ መሬት የነበራቸውና ያሳቸው ናቸው ቢሉም ይህንኑ በተጨባጭ የሚያረጋግጥ ማስረጃ አልተገኘም ከሠላሣ ዓመት በፊት ግን በተለያዩ ሥነሥርዓቶች ክብሮች ከየታንቲዎች ተለይተው በተሻለ መቀመጫ ይቀመጡ አንደነበር ይነገራል ክብሮች ምግብና መጠጥ አንዲሁም የእጅ ውሃ በመታጠብ ቀሳውስት ከተስተናገዱ በኋላ ከየታንቲዎች ቀድመው ቀሳውስቱን ሳይጨምር ይሰጣቸው ነበር ከአንድ መቶ ዓመት በፊት ወጣት ክብር ለአንድ ሽማግሌ የታንቲ መጠጥ እንኳን አይቀዳለትም ነገር ግን የየታንቲ ሽማግሌ ለወጣቱ ክብር መጠጥ መቅዳት ሃ ሃ ቴህ ሹትዷዞፅፅ ቱዛ ሬፇፀዐ ጉዬዐ ቕዞኔፃሣ ዛኛ ጃሃ ዛሩርህፅ ቀዛ ጋዘ ትዬሇ ሦቦፇዛቲዝሄ ቦ «ሟፃፃ ቴህ ጋሁዛፅ» ሬፇቦ ጋሁዛፅ ቴዢፅ ዬህ ህ ጃሟዋ ሣ ቭወ ችሄፅፅ ቭቀቫ ጋዘ ቕትዬዞዕፅ ቹወ ችዬዞዕ ፅ ቫ ጋዞ ጋሁሪ ወፅ ጋሁዛፅ ቫ ቱሠዛሀ ዛ ጋዘ ቕትዬሮዕፅ ችዬቤተፅ ፅ ሇቱሠዛሀ ዛ ጋዞ ጋሁ ሁቫ ዛ ያሠመመ ቋሁር ቴሬቴዌሠቲፅ ቕ ሎሞዌ ማሳለፍ ባሕሉ ይፈቅድ ነበር አንድ የታንቲ አንድ ክብርን በመንገድ ላይ ሲያገኝ እድ ይነሳል አሁን የማይደረግ ቢሆንም ጉልበት መሳምም ይጠበቅበት ነበር በአጠቃላይ በቅማንት ኅብረተሰብ የየታንቲ ዘር ከክብር በዝቅተኛ ደረጃ ይታይ ስለነበር ሁለት የኅብረተሰብ መደቦች እንደነበሩ የሚጠቁም ነውጡ ሊላው በግልጽ የሚታወቀው ሦስተኛው ዝቅተኛ ደረጃ መደብ ደግሞ በውርስ የተገኙትን ባሪያዎችን አገልጋይ የሚያጠቃልል ነው እነዚህ እንደባሪያ የሚያገለግሉት ጥቁሮች የተገኙት ከቆላማው ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል ነው ድሮ በቅማንቱ ክልል በባሪያነት ሲያገለግሉ የነበሩት በአሁኑ ወቅት ነፃ ቢሆኑም መሬት ስለሌላቸው በእኩል አራሽነት» ወይም በግርድናም ሆነ በሎሌነት ተቀጥረው ይሠራሉ አንዳንድ ሰዎች ከባሪያቸው ልጅ ሲያስወልዱ ልጁን «ውላጅ» ማለት የተለመደ ነበር በባሪያው አሳዳሪ ዘመን አንዳንዶቹ ሴት አገልጋያቸውን በመወሸም ሌሎች ደግሞ እንዳጋጠማቸው የግብረ ሥጋ ግንኙነት በማድረግ ሴትዮዋ አርግዛ ልጅ ከወለደች ጌታዋ ልጁን የግል አገልጋይ ያደርገው ነበር የአባት ጉሣ የክብር የቃል ዘር ቆጣሪዎች የአባትን የዘር ሐረግ በመከተል እስከ አሥራ አራት ትውልድ በመቁጠር ጥንታዊ ከሆኑት በግልጽ ከተከፋፈሉት ዘጠኙ የባሕል ጀግኖችና የጐሣ መሥራቾች ጋር ያገናኙታል መግለጫ ቁጥር አንድን ይመልከቱ የታንቲዎች በዚሁ መልክ ትውልዳቸውን የሚቆጥሩ ቢሆንም የተለየ የባሕል ጀግና ስለሌላቸው የጉላ መለያ የላቸውም ብዙዎቹ የየታንቲ ዘር ቆጣሪዎች መጨረሻ ላይ እንደምንም ብለው ከክብር የባሕል ጀግና ጋር ያገናኙታል እንደ ቅማንቶች አባባል ክብር «ንፁሕ ቅማንት» ሲሆን የታንቲዎች ግን ካልታወቁ ሌሎች ሕዝቦች ጋር ተጋብተው የተዳቀሉ ናቸው ይሏቸዋል ዛሬ የክብርና የየታንቲ የኅብረት ማኅበራት ለምሳሌ የጋራ ንብረት ወይም የተለየ የግዛት ይዞታን የመሰለ ነገር ባይኖራቸውም የሠፈራ መሬትን በተመለከተ በአካባቢዎች ተወስነዋል ይኸውም ናዚ የንጋሲ እና የዛና የተባሉት የክብር ክፋይ ጐሣዎች የቅማንት ምሥራቃዊ ክፍል በሆነው በከርከር አካባቢ ተሠራጭተው ይገኛሉ መግለጫ ቁጥር አንድን ዞሙሥ ሥ ጨመ መመ ዲም ና ንፍ ይመልከቱ ይህም ከብዙ መቶ ዓመታት በፊት ምናልባት ግዛታቸው በደንብ የተለየና ጠንካራ የሆነ ማኅበራዊ ድርጅት እንደነበራቸው ያስገነዝበናል ቁንሥው ላይ የነበረውን እያንዳንዱን የባህል ጀግና ለማስታወስ በራሱ ስም የተሰየመ አንድ ወይም ከዚያ በላይ ድግና ቅዱስ ደን አለ በቅማንት እየተረሱ ከመጡት ቁንጮው ላይ ከነበሩት አባቶች ጋር ያለው በጣም የሳሳ የግንኙነት ሰንሰለት ቢኖር በድግናዎች ለባህል ጀግናች መታሰቢያ የሚደረገው መስዋዕት ብቻ ነው የአባትን የዘር ሐረግ ተከትሉ የሚደረገው የጐሣ ቆጠራ ለመሬት ይዞታ ባለቤትነት አይጠቀሙበትም ነገር ግን ለአንድ የፖለቲካና የሃይማኖት መሪነት ምርጫ አስሰፈሳጊ ነው በዚህ ሁኔታ የትውልድ ሐረጉን በመምዘዝ እነማን በፖለቲካና በሃይማኖት መሪነት ተመርጠው አንዳገለገሉ እንደማስረጃ አድርጉ ማቅረብ የተለመደ ነው ማንኛቸውም ሦስቱ የክብር ዘር የሆኑት የከርከር ጐሣዎች ወይም በጭልጋ የሚገኙት የጐሣ ቅርንጫፎች ለከርከርና ጭልጋ ወምበር ለመሾም በቅደም ተከተል ለየአካባቢያቸው እጩዎችን ማቅረብ ይችላሉ በተመሳሳይ ሁኔታም ለቅስና እና ለአንዳንድ አነስተኛ የፖለቲካና የሃይማኖት መሪነት እጩዎችን ያቀርባሉ ዝቅ እያለ ሲወርድ ብዙ የአባት የዘር ሐረግ ክፍልፋዮች ስለሚኖሩ ቀሳውስት ከነዚህ ውስጥ ሊመረጡ ይችሳላሉ ሆኖም በአሁኑ ጊዜ የዘር ሐረጐች ፋይዳ ስለሌላቸው እንደ ጥንቱ የተለዬ ስያሜም አይሰጣቸውም አንድ ወጥ የሆነው የአባት የዘር ሐረግ ቆጠራ በአሁኑ ጊዜ የሚነሣበት ምክንያት ቢኖር የጋብቻ ሕግንና ሃይማኖትን በተመለከተ ብቻ ነው ከአንድ ወጥ የዘር ሐረግ ቆጠራ ጋር የተያያዙ ሌሎች ልማዶችም አሉ አንድ ልጅ የአባቱን አንደኛ ወይም ዋና ስም ለራሱ የመጨረሻ ስም አድርጐ መውሰድ እንዲሁም ቆሌና ዛሮችም ወደ ቤተሰብ የሚሸጋገሩ ስለሆነ የአባት የሆነው ለወንዶች የእናት የሆነው ደግሞ መስመሩን ተከትሎ ወደ ሴት ልጅ ይተሳለፋል ከጋብቻ በኋላ ባልና ሚስት የራሳቸውን ቤት ሠርተው ጐጆ እስከሚወጡ ድረስ ሁለት መኖሪያ ይኖራቸዋል ይኸውም ሙሸራዋ ከዘመዶቿ ቤት ትኖራለች ባል ደግሞ ከገዛ ዘመዶቹ ጋር ይኖራል ይህን በተመለከተ በምዕራፍ በዝርዝር እንመለከተዋለን ከሦስትና አምስት ዓመት በኋላ ሙሸራው ብዙውን ጊዜ ከእናት አባቱ ቢት አጠገብ ቤት ሠርቶ መኖሪያውን እዚያው ያደርጋል በጣም የቅርብ ቤተሰብ የሆኑ በአንድ ሳላይ መኖር በአብዛኛው የተለመደ ነው ሆኖም በጣም ሰፋ ባለመልኩ የአክስትና የአጐት ልጆች ከነልጆቻቸው ተሰባሰበው በአንድ ላይ የመኖር ሁኔታም አለ አንድ ግለሰብ በቤተሰብ ውስጥ በሚፈጠር ግጭት ወይም በኑሮ መዛባት ምክንያት በሁለት ቦታዎች መኖር የሚገደድበት ጊዜም ይኖራል አዲስ ትዳር መሥራቾች አንደፍላጐታቸው በሚስትዮዋ ወላጆች ወይም ሌሳ ዘመድ አጠ ገብ ወይም ከአባቱ ሌላ ከሌላ ዘመድ አጠገብ ኑሮአቸውን ሊመሠርቱ ይችሳላሉ በመሠረቱ የቅማንት ወንድ ልጆች የአባታቸውን መኖሪያ አካባቢ ሳይለቁ ይኖራሉ ቢባልም በተግባር ሲታይ ግን ብዙ ጊዜ ከዚህ ውጭ በተለያዩ ቦታዎች መኖሪያ መመሥረታቸውን በግልጽ መረዳት ይቻሳል ባለፉት መቶ ዓመታት ቅማንቶች የአባት መኖሪያን እንደሚያከብሩና የአባትን የዘር ግንድ ተከትለውም ትውልዳቸውን ይቆጥሩ አንደነበር ቢታወቅም አሁን ቀስ በቀስ አንድ ግለሰብ በሌሎች ቦታዎች ኑሮውን መመሥረት እንደሚችልና የዘር ሐረግንም በተመለከተ የአፕትንና የአባቱን ሐረግ መምዘዝ ከተጀመረ ሰነባብቷል ቀደም ብሎ እንደተገነዘብነዉ የአባት የዘር ግንድን መሠረት ኣድርጐ ሐረግ መምዘዙ ጉዳይ አሁንም በከፍተኛ ደረጃ በጐሣዎችና በዋና ክፋዮች ዘንድ ከሃይማኖት ጋር የተሳሰረው ማኅበራዊ አደረጃጀት እንደተጠበቀ ነው የግራና ቀኝ የትውልድ አደረጃጀትና መሬት ይዞታ አንዳንድ ማኀበራዊ ኃላፊነትን ለመወሰን እንዲረዳ የአባት የዘር ሐረግን ተከትሎ ትውልድን መቁጠር የነበረ ቢሆንም ባህላዊ ትብብርን ለማግኘትና የንብረት አወራረስን በተመለከተ የግራና ቀኝ የትውልድ ሐረግን መምዘዝ የተለመደ ነው የመሬት ተካፋይ ለመሆን የእናትንና የአባትን ዘር መቁጠር ለምን እንደሚያስፈልግ ከዚህ ቀጥሎ እንረዳለን የመሬት ተካፋይ ነኝ ለማለት የእናት ወይም የአባት የዘር ሐረግን እስከ አሥራ ስድስት ትውልድ ቅድመቅድመአያት ወይም ከዚያ በላይ ቆጥሮ መጀመሪያ መሬቱን ካረሰው ሰው ጋር ትውልዱን ካገናኘ በፋ ይሆናል ብዙ የቅማንት ወንዶች የሚኖሩት በአባታቸው የትውልድ ቦታ ነው ዘር አቆጣጠራቸውም ይበልጥ የሚያዘነብለው የአባት የዘር ሐረግን ተከትሎ በመሆኑ አንድ ግለሰብ እርዳታና የሥራ ትብብር ሲያስፈልገው በመጀመሪያ በአካባቢው የሚገኙትን የአባቱን ዘመዶች ነው የሚጠይቀው አቶ ረዳ የእርሻ ወበራ ደቦ ሲያስፈልጋቸው መጀመሪያ ልጆቻቸውን ቀጥሉ ወንድሞቻቸውን ከነልጆቻቸው በመጨረሻም የአጐጉቶቻቸውን ልጆች ያስተባብራሉ ሥራው ብዙና ከባድ ከሆነ ደግሞ ያሳቸውን ዘመድ አዝማድ ማኅበርተኞቻቸውን በጡት ልድነትና በአበልጅነት የሚታወቁትንና ጉረቤቶቻቸውን እንዲተባበሩዋቸው ይጠይቃሉ አንድ ግለሰብ ባለው የሥራ ጫና መጠን እንዳስፈላጊነቱ ከሁለቱ የዝምድና ሐረጐች ጋር ያለውን ግንኙነት ያጠብቃል ወይም ያላላል ከሁለቱም ወገኖች የጉልበት እርዳታና አንዳንዴም ጠብ ሲያጋጥመው እንዲያግዙት ያደርጋል ከሩቅ አካባቢ የሚገኙ የእናትና የአባት ወገኖች በሠርግ በተዝካርና በቀብር ሥነሥርዓቶች ከመገኘት በስተቀር በጉልበት ሥራ እንዲረዱ አይጠበቅም ነገር ግን የእናትም ሆነ የአባት ወገኖች አንድ ዘመዳቸው በሰው እጅ ቢጠፋ ደሙን መበቀል የራሳቸው ወገን ነፍስ ሲያጠፋ ደግሞ የደም ካሣ መዋጮ መክፈል ይኖርባቸዋል አንድ ቅማንት ዘመዱ የሆነ ሰው ደም ካለበት የሟች ወገኖች ዘር ቆጥረው ሊገድሉት ወይም ጉዳት ሊያደርሱበት ስለሚችሉ በዚህ ረገድ መተባበር ይኖርበታል በመሬት አጠቃቀም ብዙ ጊዜ ግጭትና ክስ ሊነሣ ይችላል ይህ ሁኔታ የሚከሰተው አንድ ተወላጅ ነኝ የሚል ሰው ለብዙ ዘመን ተዳፍኖ የቆየውን የርስት ጥያቄ የዘር ሐረግ በመምዘዝ ማረስ አለብኝ ብሎ ሲነሣ ነው በመሠረቱ አንድ ግለሰብ መሬት የግል ንብረቱ ሳይሆን ከዘመዶቹ ጋር ተወላጅ የሆነበትን መሬት እየተካፈለ ወይም ከሌላ መሰሉ ከሆነ ሰው መሬት እየተከራየ በማረስ አለባገለባውን ብቻ ያገኛል አባወራው ሲሞት ሚስቱ በጋራ ያፈሩትን ተንቀሳቃሽ ንብረት ግማሹን አንስታ ሌላውን ግማሸ ለልጆቿ ትተዋለች የመሬት ባለመብትነት የሚወሰነው በደም ትስስር ስለሆነ ሚስት ባሏ ይዞት የነበረውን የመሬት ባለመብትነት መጠየቅ አትችልም ለስሙ ያህል ቢሆንም ወንድና ሲት ልጆች አባታቸው በሁለቱም የዘር ሐረግ ይዞት የነበረውንም ሆኖ ገና ወደፊት በተወላጅነቱ ሊጠይቅ የሚችለውን መሬት የመጠየቅ ሁሉም እኩል መብት አላቸው አንድ አባወራ ሚስቱ ያላትን የመሬት ተጠቃሚነት መብት ጥያቄ ከዘመዶቿ ጋር ቅራኔ ሊያስነሣበት ስለሚችል ብዙ ጊዜ ጥያቄውን ከማንሳት ይቆጠባል ይህን መብት ብዙውን ጊዜ ለወንድሞቿ ይተወዋል ነገር ግን መሬቱ ከሚያርሰው እርሻ አጠ ገብ ወይም ኩታገጠም ከሆነ የተዳፈነውን የመሬት ጥያቄ ሊቀሰቅሰው ይችላል ለምሳሌ ያህል አቶ ረዳ የወይዘሮ አዳነች ወላጆች ከሚቆጣጠሩት ትናንሸ ቁራሽ መሬቶችን በዚህ ዓይነት መብት ተጠቅመው ያርሳሉ ቅማንቶት በተወላጅነት ያገኙትንና ወደፊት የይገባኛል ጥያቄ ሊያነሱበት የሚችሉትን መሬት «ርስት» ይሉታል «ርስት ነፃ ይዞታ ማለት ሲሆን ተቃራኒው «ጉልት» ጭሰኝነት የሚለው ነው ሌላው አለባገለባውን ብቻ ለመጠቀም የሚያስችል ርስት ደግሞ በሌሎች ማኅበረሰብ የሚገኝ ለስሙ ያህል «ርስት የሚባል ነገር ግን ጥያቄውን ለማስፈፀም ፈጽሞ ከማይቻልበት ደረጃ ላይ የደረሰ መሬት ነው አንድ ቅማንት ገበሬ በአንደዚህ ባለ መሬት ለመጠቀምና እርሻውንም በቤቱ አካባቢ ለማሰባሰብና ለማጠናከር ሲፈልግ ይህን መሰል መሬት በጭሰኝነትም ቢሆን ይይዛል በዚህ ሁኔታ በኩታገጠም የሚያገኘውን መሬት ለሌሳ ሰው ማከራየት የሚችል ቢሆንም ይዞታውን ግን በውርስ ሊያስተላልፍ አይችልም በከርከርና በጭልጋ በአንዳንድ ቦታዎች ገበሬዎች ለሚጠ ቀሙበት ርስት «አሥራት» እየተባለ የሚታወቀውን ግብር ይከፍላሉ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የገዥው መደብ ሹማምንት ግብሩን ይሰበስቡ ነበር አሁን ግን «ፈረሰኛ» እየተባሉ በሚጠሩ ዝቅተኛ ሹማምንት ተቆጣጣሪነት ግብሩ ገቢ የሚሆነው በቀጥታ ለብሔራዊው መንግሥት የገንዘብ ሜኒስቴር ነው ፈረሰኞች ደግሞ የጨው ግብር የሚባለውን ለራሳቸው ይሰበሰባሉ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ አሥራትና የጨው ግብር በእህል በማር በአሞሌ ጨውና በሌሎች ውጤቶች ይከፈል እንደነበር ቢታወቅም በአሁኑ ወቅት ክፍያው በኢትዮጵያ ብር ተተክቷል ዛሬ እያንዳንዱ ገበሬ የትምህርትና የጤና ታክስም መክፈል ግዴታው ነው እኤአ በ ዓም ከመላው ከርከር ከልዩ ልዩ ዓይነት ግብሮች የተሰበሰበው የኢትዮጵያ ብር ነ በሌላ አካባቢ የሚኖሩ የቅማንት ኅብረተሰቦች አሥራት አይከፍሉም ነገር ግን «አምሾ» እየተባለ የሚታወቀውን ከፍተኛ ግብር ለባላባታዊ የጉልት አስተዳዳሪ ይከፍላሉ በጦርነት ጊዚ ላሳዩት ጀብዱና በታማኝነታቸው የተሾሙት የባላባታዊው የገዥ መደብ አባላት በአንድም ሆነ ከዚያም በሳይ በሆኑ ማኅበረሰቦች ላይ የተለያየ ሥልጣን ይኖራቸዋልሱ ግብር ይሰበስባሉ የዳኝነት ሥራ ይሠራሉ እንዲሁም እርሻቸውን በሕዝቡ በኩዳድ ያሳርሳሉ በአውሮጳ የባላባታዊ አገዛዝ ሥርዓት ተንሠራፍቶ በነበረበት ወቅት አንደነበረው የሥልጣን ተዋረድ ዓይነት በኢትዮጵያም የሚሰጡ ማዕረጐች አሉ እነዚህም እንደ ሥልጣን ቅደም ተከተል ከላይ ወደ ታች ንጉሠ ነገሥት ንጉሥ ራስ ደጃዝማች ፊታውራሪ ቀኛዝማች ግራዝማች ይባላሉ ሌሎች በሥልጣን ደረጃ መሠረት ያልተቀመጡ የሹመት መጠ ሪያዎች ልዑል ገዥ ባላምባራስ ፈረሰኛ ሻለቃ መቶ አለቃ ባሻ አምሣ አለቃ በጅሮንድ አሥር አለቃ አዛዥ ጭቃ ሹም ሻምበል የተባሉ ናቸው እንደነዚህ ዓይነት የሹመት መጠሪያዎች ሊወረሱም ላይወረሱም ይችላሉ እንዲያውም አንድ ባለማዕረግ ታማኝነቱን ሲያጓድል ወይም የገዥው ጠንካራ ደጋፊ ካልሆነ የሹመት መጠ ሪያውን ሊገፈፍ ይችሳል አንዳንድ ጊዜም ከፍተኛው የባላባት ገዥ በሥሩ ሌሎች ንዑስ የባላባት ገዥዎችን ሊመድብ ይችሳላል። በሃይማኖት ምክንያት ለድግስ የሚሰበሰበው መዋጮ ተመልሶ ለመላው ኅብረተሰብ ስለሚውል የቅማንቶችን የአንድነት ቃልኪዳን የሚያድስና የሚያጠናክር ከመሆኑም በላይ የባህል ድንበራቸው ተጥሶ በውስጣቸው ሊሉች ሠርገው እንዳይገቡ የሚያግድ ነው በእንካበእንካ መተጋገዝ ቅማንቶች ቀላል ግምት የማይሰጠው የዕቃና የአገልግሎት ልውውጥ በእንካበእንካ ያደርጋሉ ይህም በጡት አባትና በጡት ልጅ መካከል በተደረገ ቃልኪዳን መሠረት የሚደረግ አፀፋዊ ምላሽ ወይም በአንድ ግለሰብና በሚዜዎቹ መካከል በደቦ መረዳዳት ወይም በአንድ ማኅበር አባላት መካከል በደቦ ቤት በመሥራት ረገድ መተጋገዝ ሊሆን ይችሳላል በእንካበአንካ የሚደረጉት የአገልግሎት ልውውጦች ዋጋቸውን ተምኖ ለማመዛዘን አስቸጋሪ ነው ለምሳሌ አንድ ቄስ ዘወትር የሚመግበውንና ጥሩ አገልግሎት የሚሰጠውን አንድ ገበሬ ሕዝቡ ከፍተኛ ምስጋናና ምርቃት እንዲሰጠው ተፅዕኖ ሊያደርግ ይችላል በሌላ መልክ ደግሞ ሁለት ቤተሰቦች እርስ በእርሳቸው ተራ በተራ ተጠራርተው በማያቋርጥ ሁኔታ ስጦታ መለዋወጥና መገባበዝ ይኖራል እንዲሁም አንድ ሀብታም ሰው ስሙን ለማስጠራት አስቦ በየጊዜው ሕዝቡን በመጋበዝ ሊያስደስት መሬቱን ለሚያርሱለት ደግሞ የተለዬ ከፍተኛ ስጦታ ሊያደርግ ይችላል በአጠቃላይ ስናየው አንዱ ለአንዱ በአፀፋው ወይም በእንካ በእንካ የሚያደርግለትን በሚዛን ላይ አስቀምጦ ማመዛዘን ያስቸግራል የሥራና የዕረፍት ቀናት ዕለታዊ ጥረትግረትና ዕለታዊ ደቦ ከሰንበት ከምዝገና እና ከገባርሁ በዓላት በስተቀር በቅማንቶች ዘንድ ሁሉም ቀናት የሥራ ቀን ናቸው አቶ ረዳና ቤተሰቦቻቸው ሥራ የሚደምሩት ከንጋት በፊት ቀደም ብሎ ነው ወይዘሮ አዳነች እንደተነሱ እንጨቱን አስተካክለወ በምድጃው ላይ እሳቱን ያያይዛሉ አሳቱ ከጠፋ ትንሽ ቀዳዳ ባለው እንጨት ላይ ሌሳ እንጨት በማፋጨት የሚወጣውን ትንሽ እሳት በደቃቅ ፍግ ማያያዝ ይትሳሉ ነገር ግን ብዙ ጊዜ እሳት እንዳይጠፋ ጥንቃቄ ይደረጋል እሳቱ እንዳይጠፋ ወይዘሮ አዳነች ፍም ከአመዱ ውስጥ አዳፍነው ያስቀምጣሉ ከጠፋም የልጅ ልጃቸውን ወደ ጉረቤት በመላክ የከሰል ፍም እንዲያመጡላቸው ያደርጋሉ ከዚያም ወይዘሮ አዳነችና ምራቶቻቸው ፀሐይና አልማዝ በቀን ሁለት ጊዜ የሚበሉትን ምግብ አዘጋጅተው ከባለቤቶቻቸው ጋር እና ሊላም ሰው ካለ በአንድ ላይ ሆነው ይመገባሉ ሴቶች ወደ አረሻ ቦታ ለሥራ መሄድ ያለባቸው ከሆነ ከመሄዳቸው በፊት አስፈላጊ የሆነውን የቤት ሥራ መሥራት ስላለባቸው ከሌሊቱ በ ሰዓት መነሣት ይኖርባቸዋል ወደ እርሻ ለሥራ የማይሄዱ ከሆነ ግን የማገዶ እንጨት በመልቀምና ትልቅ እንስራ ወይም ቅምጫና ትልቅ ቅል በመያዝ አጠገባቸው ወደአለ ምንጭ ወይም ወንዝ በመውረድ ውሃ በማመላለስ ጊዜአቸውን ያሳልፋሉ ውሃ ብዙ ጊዜ የማይጠጣ ሲሆን ዕቃ ለማጠብ ምግብ ለማዘጋጀትና ጠሳ ሰላብ ለመጥመቅ ይጠቀሙበታል ቤት መጽዳት ሕፃናትን መያዝ የጓሮ አታክልት መኮትኮት የእጅ ሥራ መሥራትና እህል በወፍጮ መፍጨት የመሳሰሉት ለሴቶች የተተው ሌሎች ተግባሮች ናቸው በሬዎች በተለይ በክረምት ወራት ተለቀው ሣር መልቀም ስለማይችሉ አቶ ረዳ ከእንቅልፋቸው እንደተነ የመጀመሪያ ሥራቸው በሬዎቻቸው መኖ እንዲያገኙ ማድረግ ነው ከቤታቸው ሲወጡ ከምድጃው ከሜወጣው የባሕር ዛፍ ቅጠል ጭስ ከተሞላው የማለዳው ብርዳም አየር ጋር ይጋፈጣሉ በዚያን ጊዜ ላሞች መጮህና መንቀሳቀስ ይጀምራሉ አውራ ዶሮውም ጩኽኸቱን ያስተጋባል አቶ ረዳና ሶስት ልጆቻቸው ቁርሳቸውን በልተው ወደየሥራቸው ይሠማራሉ የዕለቱ ተግባር በእርሻ ላይ ውሎ ወይም ቤት መሥራት ወይም ወደገበያ መሄድ ሊሆን ይችላል አልፎ አልፎም አንደ አቶ ረዳ ያለ አዛውንት በሸንጐ ላይ በመገኘት የዳኝነት ሥራ መሥራትም ያጋጥመዋል ትንሽ አደግ ያሉ ወጣት ልጆች ቁርሳቸውን ትላላቅ ሰዎች ከበሉ በኋላ በተራቸው በልተው ጦንዶች ከብቶችን ለማሠማራትና ለመጠበቅ ይወጣሉ ልጃገረዶች ግን በጣም ትናንሽ ከሆኑት ልጆች ጋር በቤት ቀርተው እናቶቻቸውን በቤት ሥራ ይረዳሉ የወይዘሮ አዳነችን አብዛኛውን ጊዜ የሚፈጀው በጣም አስፈላጊ የሆነውን በየዕለቱ የሚበላውን ምግብ የማዘጋጀቱ ሥራ ነው ምግቡ የሚቀቀለውና የሚጋገረው ሦስት ጉልቻ ባሉት የአሳት ምድጃ ላይ ነው ሥጋ የሚበሳው በሁለት ወይም ከዚያም በላይ በሆኑ ሣምንታት አንድ ጊዜ ብቻ ነው ብዙ ጊዜ በዋና ምግቦች መካከል ቆሉና ንፍሮ ለመክሰስ ይቀርባል አንዳንድ ጊዜም በቅመም የጣፈጠ ዳቦ መብላትም የተለመደ ነው ዳቦው በምጐጐ የሸክላ ምጣድ ወይም በገበር ምጣድ ላይ ቃ ብሎ እንዲበስል ተደርጐ ይጋገራል አቶ ረዳና ቤተሰቦቻቸው ዳቦ ብቻ በቂ አለመሆኑን በመገንዘብ በርካታ አህል በተለይም ገብስን ጠላ ለመጥመቅ አገልግሎት ያውሉታል ለጠላው ማጣፈጫም የጌሾ ቅጠል ይጨመርበታል ቡና ድሮ በቅማንት ኅብረተሰብ እንዳይጠ ጣ የተከለከለ የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ጊዜ ግን ዋጋውም በመወደዱ ለአንዳንድ ክብር ለሚሰጣቸው የተለያዩ ቀናት ብቻ ይፈላል ቡናን በጨው ወይም በማር ይጠጡታል ወተት ደግሞ በተለይ ለሕፃናት ነው የሚሰጠው በቀን ሁለት ጊዜ ለሚቀርቡት ዋና ምግቦች ምሣና እራት በሚገባ ጣፍጦ በድስት የተሠራ ወጥ ሳዌብ እና እንጀራ አራህ ይቀርባል ወጡ በርበሬ የበዛበትና ብዙ ዓይነት ቅመማ ቅመም ቅቤ ዘይት ሽንኩርት አንዳንድ ጊዜም ሥጋ ታክሎበት በሸክላ ድስት ተጥዶ ተንተክትኮ ሲበስል ይወጣልነ እንጀራው ደግሞ ብዙ ጊዜ የጤፍ አልፎ አልፎም የገብስ ወይም የማሽሳ ወይም የስንዴ የበቆሎ ዱቄት ከተቦካ በኋላ ክብ በሆነ የሸክሳ ምጣድ ምጐጉጐ ተጋግሮ ዓይናማ ሆኖ ይወጣልነፁ በርካታ እንጀራ እንደ ጠረጴዛ በሚያገለግለው ሞሰብ ላይ ተደርድሮ ከቀረበ በኋላ እጅ የሚያስቆረጥመው ወጥ በላዩ ላይ ቀስ በቀስ እየተደረገ ይበላል የዞን ሕኾገተ መወ ህህ ከ«ሃ አልፎ አልፍ ሲያጋጥም ለስላሳ ዓይብ ከጦጡ ሳይ እየተደረገ የሚበላበትም ጊዜ አለ አይቡ በዳቦም ሲበላ ጥሩ ነቦ ምሸት ላይ አቶ ረዳና ልጆቻቸው ከዕለታዊ ተግባራቸው ሲመለሱ የልጅ ልጆቻቸው ደግሞ ከብቶቻቸውን እየነዱ ወደ በረት ያስገባሉ ከዚያም ላሞች ከታለቡ በኋላ እራት ተበልቶ ጐልማሶቹ በእሳቱ መድጃ ዙሪያ እንደንብ በመስፈር ጠላ እየጠጡ ስለውሉሎአቸው ያወካሉ በአጋጣሚ የመጣ እንግዳ ዘመድም ካለ አብርሮ ይስተናገዳል በመጨረሻም የመኝታ ሰዓት ሲደርስ አቶ ረዳ ይተኛሉ ሚስት ያገቡት ልጆቻቸውም ስለመሸ ወደየቤታቸው ስለሚሄዱ ሁሉም ነገር ፀጥ ረጭ ይሳል ባልና ስት በአንድ ላይ የሚተኙ ሲሆን ትናንሽ ልጆቻቸውም አንዳንድ ጊዜ አብረዋቸው ይተኛሉ ሰንበት የምዝገግና እና የገባርሁ በዓላት «ሰንበት» ተብሉ የሚታወቀው ከአርብ ምሽት ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ምሸት ያለው ጊዜ ነው የሃይማኖት ሥነሥርዓት በዚሁ ዕለት የሟካሄድ ባይሆንም በእርሻ ቦታዎችና በቤት ውስጥ ከሚሠሩ ሥራዎች በመታቀብ ሙሉ ቀኑን በዕረፍት ያሳልፉታል ለዚሁም አረማዊ ኦሪት ሃይማኖት ተከታይ ቅማንቶች ብቻ ናቸው በከፊል የሰንበትን ሥነሥርዓት የሚጠብቁት ከባድ ሥራ አይሠሩም ቀለል ያሉ ሥራዎችን ግን ያከናውናሉ በአብዛኛው ሰሜንና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ የሚገኙ ሕዝቦች ሰንበትን እንደ ዕረፍት ቀን አድርገው የሚመለከቱት ባይሆንም የበዓል ቀን ነው ብለው የሚያከብሩት ቅማንቶች ከሌሎች ጐረቤቶቻቸው ጋር ያላቸው ልዩነት ቢኖር ሰንበትን አንደ ዕረፍት እንጅ እንደ በዓል ቀን አድርገው አለመውሰዳቸው ብቻ ሳይሆን ሌሎች በየወሩ የሚመጡትን የሃይማኖት ቀናትንም ዘወትር በዕረፍት ብቻ ስለሚያከብሩ ነው በወር አንድ ጊዜ ሐሙስ ቀን የምዝግና የእግዚአብሔር በዓል ሌላው ሐሙስ ደግሞ ጥንት ምናልባት እንደ አንድ ዝቅተኛ አምላክነት ይታይ ስለነበረው አሁን ደግሞ እንደ አንድ መልአክ በታወቀው ገባርሁ ስም ይከበራል ሁለቱም ቀኖች እንደሰንበት በዕረፍት ታስበው ይውላሉ በእነዚህ ቀናት በቅዱስ ድግናዎች የሚደረግ ሥነሥርዓት ባይኖርም ቅማንቶች ጸሎት ያደርጋሉ የማኅበራት ስብሰባ ያካሂዳሉ እንዲሁም በምዝግና እና በገባርሁ ስም ለጐረቤቶች የጠላ ግብዣ ማድረግ የተለመደ ነው የኦሪታውያን ሰንበት ከሃይማኖታቸው ጋር ከመጨመሩ በፊት ሥፖናልባት በወር ሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሚሆኑ ሐሙስ ቀኖች የቅማንት የሃይማኖት የዕረፍት ቀኖች አንደነበሩ መገንዘብ ይቻላል ቅማንቶች ቅዱስ ናቸው ለሚሏቸው ከአካባቢያቸው ከሚገኙ ድግናዎች ጋር የሚታወቁትን ጥንታዊ ባህላዊ ጀግኖቻቸውን በየወሩ አንድ ወይም ከዚያ በላይ በሆነ የዕረፍት ቀን ያከብሯቸዋል ለእያንዳንዱ ባህላዊ ጀግና የአንድ ቀን በዓል የሚታሰብ ሲሆን የዕረፍት ተኖች ብዛትም በኅብረተሰቡ አካባቢ ባሉት ቅዱስ ድግናዎች ብዛት መሠረት ይወሰናል እያንዳንዱ ኅብረተሰብ ቢያንስ አንድ ድግና ብቻ ሲኖረው ሌሎች ከዚያ በላይ ሊኖራቸው ይችሳል በዓመት ውስጥ በየወሩ ከሚከሰቱት ዓመት በዓል አንደኛው ከሁሉም የላቀ ነው ተብሎ ስለሚወሰድ ለባህላዊ ጀግናው ክብር በስሙ በተሰየመው ድግና ልዩ ሥነሥርዓት ይካሄድለታል ለሌሎች የባህል ጀግኖች የዓመት በዓላት ቀን ግን ልዩ የክብረ በዓል ሥነሥርዓት ሳይካሄድ እንዲሁ በዕረፍት ቀን ብቻ ታስቦ ይውላል ዓመታዊ የሥራና ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴ ዑደት የቅማንቶችን ዓመት በዓላት አከባበር ስንመረምር የኢኮኖሚና የሃይማኖታዊ እንቅስቃሴዎች አንዱ በሌላው ላይ ተደጋጋፊና የተሳሰሩ መሆናቸውን እንረዳለን ማንኛቸውም ኢትዮጵያዊ ገጠሬና የጉሣ አባላት አካባቢያቸውን በቴክኖሎጂ ለመቆጣጠር እንዲያግዛቸው በመለኮታዊ ኃይሎች የሚተማመኑ ቢሆንም ቅማንቶችን ልዩ የሆነው የሃይማኖታቸው ባሕርይ በውጭ ከጐጉረቤቶቻቸው ተገልለው እንዲኖሩ በውስጥ ደግሞ አርስ በርሳቸው በአንድ ላይ ተሳስረው አንዲኖሩ አድርጐአቸዋል የጸሎት ሥነሥርዓታቸውን በምስጢር በድግና ውስጥ የሚያካሂዱ በመሆናቸው በሌሉች በሰሜናዊና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዘንድ ልዩ ስለሚያደርጋቸው አንዳንድ የተሳሳተና ተቀባይነት የሌለው ጭፍን ትርጉም በመስጠት «ከእንጨት የመጡ ምስጤ ራዊ ዕምነት በጫካ የሚያካሂዱ» እያሉ ሃሜት የሚሰነዝሩ አይጠ ፉም ተን መቁጠሪያ ቅማንቶች ወርንና ጨረቃን በአንድ ዓይነት ስያሜ «አረፋ እያሉ ሰለሚጠሩ ምናልባተ ጥንት ጨረቃን ተከትሎ የሚደረግ የቀን አቁጣጠር ሥርዓተ እንደነበራቸው የሚጠቁም ነው ከዚህም በስተቀር የክዋክብትን ዓመታዊ እንቅስቃሴና ስለጨረቃ ገታ አንዳንድ ግንዛቢ ቢኖራቸውም ሰለኮከብ ቆጠራ ያሳቸው ዕውቀት ውሱን በመሆኑ ለዘመናዊ የቀን መቁጠሪያነት አይጠተሙበትም ስለሆነም ክርስቲያን ኢትዮጵያውያን የሚጠቀሙበትን አእያንዳንዳ ባለ ቀን ወራትና ጳጉሜ ተብሎ ባለ አምስት ወይም በ ዓመት አንድ ጊዜ ስድስት ቀናት ያሉትን ተጨማሪ ወር የተን አቆጣጠር ሥርዓት ይከተላሉ መግለጫ ቁጥር አራትን ይመልከቱ ይህ አቆጣጠር ከጎርጎሪዎስ አቆጣጠር ሰባት ዓመት ሠደጋላሳ የተረ በመሆኑ እኤአ መስከረም ቀን ዓም በኢተዮጵያ አቆጣጠር መስከረም ቀን ዓም ነበር ቅማንቶች ይህን አቆጣጠር ከአማራው በመውሰዳቸው የሚጠቀሙበት የወር ስያሜ አማርኛ ነው ሆኖም ለወቅቶች ስያሜ የቅማንትኛ ቃላትን ይጠ ቀማሉ እንደ አማራውና በመካከለኛው ምሥራት አካባቢ የሚኖሩት ሕዝቦች የመጀመሪያው የቀኑ ሰዓት ከንጋቱ ሳይ ጆምሮ እስከ ፀሕይ ግባት ይደርሳል ሌላው የሌሊቱ ተጣይ ጊዜም አስከ ንጋቱ አስራ ሁለት ሰዓት ይደርሳል የቅማንት አገር መሬት ለምድር ወገብ ቅርብት ስላለው የፀሐይ መውጫና መግቢያ ሰዓት በዓመት ውስጥ ብዙ ለውጥ አያሳይም ይህም በመሆኑ ከጥዋቱ አንድ ሰዓት ሁልጊዜ በሃያ አራት ሰዓት ዞሮ የሚደርሰው በተመሳሳይ ጊዜ ነው የቀኑን ግምታዊ ሰዓት የፀሐይን አቀማመጥ ተመልክተው ማወቅ ይችላሉ ይህን ሁኔታ በተመለከተ አቶ ረዳ በዚህ መልክ ዘወትር የቀኑን ሰዓት እቅጩን ሲነግሩኝ አደነቅ ነበር የክብረ በዓላት መጀመር የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ክርስቲያን ዘመን አቆጣጠር የሚጀምረው በመስከረም ወር ቢሆንም የቅማንት ዓመታዊ ኃይማኖታዊ ሥነሥርዓት ዙር በሁለተኛው ወር ጥቅምት ላይ ይጀመራል በዚህም ምክንያት ዓመታዊ የክብረ በዓላቸው የመጀመሪያው ዙር የመኸር ወቅት ከሚጀምርበት ከጥቅምት ወር ጀምሮ ነው በጥቅምት ወር መግቢያ የመጀመሪያ ማክሰኞ ፅለት ቅማንቶች የዓመት በዓል መክፈቻ ቀን «በዓለቤዛ» የተባለውን የቅዱስ ድግና የበዓላት ሥነሥርዓት ማክበር ይጀምራሉ ይህ በዓል ከርከር በሚገኘው ለምዝግና ድግና ላይ የሚከበር ሲሆን ስያሜው የምዝግና የእግዚአብሔር መታሰቢያ መሆኑን ያመለክታልተመሳሳይ በዓል ሐምሌ ላይ ማክሰኛ ዕለት ከባዱ የክረምት ጦቅት እስኪያልፍ ድረሰ የድግናዎች ዓመታዊ ክብርበዓላት መዝጊያ ሥነሥርዓት የሆነው በዓልዓለሜ የተባለው ክብረበዓል ይከበራል አዚህ ላይ ሊታወት የሚገባው በዓመት ሁለት ጊዜ የቅማንት ክብረበዓል የሚካሄድበት ድግና ከርከር የሚገኘው ጋለምዝግና የአግዚአብሔር መታሰቢያ ብቻ መሆኑ ነው በበዓላት መክፈቻና መዝጊዖ ሥነሥርዓት ብዙ በጐች ለመሰዋዕትነት እየታረዳ የሚከበሩ በዓላት ነበሩ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የከርከር ቀሳውስት መደበኛውን የመክፈቻ ክብረበዓል ሳያከብሩ በማንኛውም ድግና ሥነሥርዓት መካሄድ አይቻልም ነበር ይህም ሁኒታ በየትኛውም አካባቢ የሚገኝ የቅማንት ኅብረተሰብ የከርከሩ ወምበር የበላይ መሆኑን የሚያስገነዝብ ነው የመጨረ ሻዎቹ ቀን በአረማዊኦሪታዊ ሃይማኖት ያምኑ የነበሩ ቅማንቶች ባለፉት ጥቲት ዓመታት ክርስትናን የተቀበሉ ቢሆንም ዛሬም በዓመት በዓል መክፈቻና መዝጊያ በዓላትን ስለሚያከብሩ በሌሳ አካባቢ ያሉት ቅማንቶች የበዓሉ አከባበር በራሳቸው ቀሳውስት አእንደተጀመረላቸው በመቁጠር የተለመደውን የበዓላት አከባበር ዙር ይቀጥሉበታል አዚህ ላይ መገንዘብ ያለብን በድግና ሳይከበሩ የቀሩ አንዳንድ ሥነሥርዓቶች በማንኛውም ጊዜ ሊካሄዱ የሚችሉ መሆኑን ነው አረማዊኦሪታዊ ቅማንቶች ለተራ ጸሎት ሥነሥርዓት ካልሆነ በስተቀር በድግና ለሚካሄዱ ክብረበዓላት የሚከተሉትን ነገሮች መፈፀም አለባቸው ቀሳውስት ለበዓሉ ዝግጅት በመጀመሪያ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ኮሶ ማኘክ ይኖርባቸዋል በክብረበዓሉ ዋዜማ ቀሳውስቱም ሆኑ ማንኛውም ወደ ድግና የሚገባ ሰው ግብረሥጋ ከመፈፀም መታቀብ አለበት በመጨረሻም ቀሳውስቱ ሙሉ ንፅሕናቸውን ለማግኘት ሰውነታቸውን ታጥበው የፀዳ ልብስ መልበስ አለባቸው ቀሳውስቱና ማንኛውም ተራ ሰው ከበዓሉ ዋዜማ ጀምሮ መስዋዕት የማድረጉ ሥነሥርዓት አእሰከሚጠናቀቅበት ማግሥት ድረስ ይዖማሉ አንድ ቀን አየሩ ቀዝቃዛ ውርጫማም በሆነበት በዓሉ በሚከበርበት ጥዋት አንድ ዝቅተኛ ቄስ በገና ይዞ ወደ ድግናው ገብቶ በገናውን ሲደረድር አየሩ በሙሉ በሙዚቃ ተሞሳ ሌላው ቄስ ደግሞ በአንድ ላይ የተደባለቀ ማርና ወተት በተባረከው ቅዱስ መሬትና ዛፎች ላይ ያርከፈክፍ ጀመር ወምበሩ የተሰበሰበውን ቀሳውስትና ሕዝቡን እየመራ ድግናው መሐል ሲደርስ ተቀመጠ ሌሎች ግን ዙሪያውን አጅበውት ቆሙ ከዚያም በአዕዋፍት የተሞላው አልፎ አልፎም በዝንጀሮዎች የሚዘወተረው ድግና ከየአቅጣጫው በሚመጡ አረማዊኦሪታዊ ቅማንቶች ተጥለቀለቀ ድግናው ለተሰየመለት የሕል ጀግና ሁለት ቄሶች ለአንድ ሰዓት ያህል ከጸለዩና ከተደሱ በኋላ የቅማንት ኅብረተሰብ ከአንዱ የጥንት ቅድመኦያታቸው የባህል ጀግና ጋር ያላቸውን ቃል ኪዳን እንደገና ያድሳሉ በእሱም አማካይነት በእርስ በርሳቸው መካከል ያለውን አንድነታቸውን ያጠናክራሉ ቀሳውስቱና ወምበሩ ከለምለሙ ድግና የሚመጣውን የሚያውድ ጥሩ ሽታ ያለውን የግራር ሙጫ ዕጣን እያሸተቱ ወደ ዳር ሲወጡ በድጋሚ ዝቅተኛው ቄስ በገናውን ያሰማ ጀመር ከፍተኛው ቄስ ደግሞ ማር በመሬቱ ላይ አርከፈከፈ በመጨረሻም ተሰብሳቢዎቹ ምርቃት ተቀብለው እንዲቀመጡ ተፈቀደላቸው ነገር ግን ክርስቲያን ቅማንቶች ከአሮጌው ሃይማኖት» ተገልለው ለብቻቸው ሲቀመጡ ቀሳውስት ከሁሉም ተራ ሰው ተነጥለው ለብቻቸው ቦታቸውን ያዙ አልፎ አልፎ የግዕዝ ቃላት የሚጨመሩ ቢሆንም ጸሎት ቅዳሴና ምረቃው የሚደረገው በቅማንትኛ ነው ቅማንቶች እንደሚሉት ለሥነሥርዓቱ የሚጠቀሙባቸው አንዳንድ ቃላት በጣም ጥንታዊ በመሆናቸውና በአሁኑ ጊዜ ለዕለታዊ ንግግር ስለማይጠቀሙባቸው ትርጉማቸውን ለማወቅ አዳጋች መሆኑን ይገልፃሉ የሚቀጥለው የበዓሉ አከባበር ክፍል ለመስዋዕት ደም የማፍሰሱና ድግስ የመብላቱ ጉዳይ ነበር ለመስዋዕት የተዘጋጁት አንስሳት ለሥነሥርዓቱ የበኩላቸውን አስተዋፅዖ ለማድረግ በደመ ነፍስ በመጠባበቅ ሳይ ናቸው በድግናው አካባቢ ከሚኖሩ የኀብረተሰቡ አባላት በመዋጮ የቀረቡ ሲሆን ትልቁ ክብረበዓል በሚኖርበት ጊዜ በርካታ ጥንድ ቀሳውስትና ለመስዋዕት የተዘጋጁ በርካታ አንስሳት ይኖራሉ እንዲሁም ብዙ ሕዝብ ይሰበሰባል መግለጫ ቁጥር የቅማግት ቀግ መፋጣዕኔዩና ቋመታዊ ሥራ ዑውደቾ እንደ ክብርዋና ካዳስቲ የመሳሰሉ ቅዱስ ድሣናዎት አንድ ተልት ድንጋይ ወይም ትናንሽ የድንጋይ ክምር የመስዋዕት መንበር ሊኖራቸው ይችላል ነገር ግን በአብዛኛዎቹ ድግናዎች የመሰዋዕት እንስሳት የሚታረዱት መሬት ላይ ነው አንስሳቱ በሚታረዱበት ጊዜ በዝቅተኛ ደረጃ የሚገኙ ቀሳውስት ዋናው ቴሰ በባርክበት ጊዜ የአንስሳውን አግሮች ወጥረው ይይዛለ ከብቱ ታርዶ ደሙ ወደ መሬት ፈስሶ ካለቀ በኋላ ከፍተኛው ዌስ የኋላና የፊት አግሮቹን በሠላ ቢላዋ ይሠነዝራል ቀሳውስቱ ደሙን በጠሳ ይታጠቡታል ግማሹን ጠላ ጠጥተው ከፊሉን ደሃሞ በደም በተጨማለቀተው መሬት ላይ ያፈሱታል በአካባቢው ሕዝብ መዋጮ የተዘጋጀውን ምሃብና መጠጥ በታረደው እንስሳ አጠገብ ሰዎቹ ሲያስተምጡ በሰሜናዊ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ በተለመደው ዓይነት «ዕልልታ» በማሰማት ነው ከዚያም አንስሳውን ገፈው ሥጋውን በመቆራረጥ ጠና ያሉት ያረጡ ሴቶች ወጥ አንዲሠሩ ይደረግና ሕዝቡ ሠጡን በአንጀራ ይመገባል በተጨማሪም ጠላና ጠጅ በጋን ይወርድና እየተቀዳ ይጠጣል ቀሳውስቱ ምርጥ ምርጥ የሆነውን ምሣግብ ተሰጥቷቸው ፆማቸውን አንዲፈቱ ይደረጋልኑ በመጨረሻም የተረፈ ምግብና ጠላ ካለ ሕዝቡ ተከፋፍሎ ወደየቤቱ ይዞ ይሃዳል የመስክ ጥናቱን በማካሂድበት በጥቅምት ወር ውስጥ በየቀኑ የተዘራውን ሰብል አስተዳደግ አከታተል ሃነበር አት ረዳና ልጆቻቸው በአርሻ ቦታቸውና በጓሮአቸው የተዘራውን ባለስድስት ረድፍ ገብስ ጉመን ተልባ አተር ባቄላና ሽንኩርት የመሳሰሉትን በጥሩ ሁኑታ እየደረሱላቸው ስለሆነ በኩራት እየተመለከቷቸው ነው ሰብሎች አሽተው የመታጨጃ ጊዜያቸው እየተቃረበ ነው በዚህ ወር እንደተለመደው አልፎ አልፎ ከሚንጠባጠበው ዝናብ በስተቀር ሰማዩ አየጠራ የክረምቱ ወቅት እያከተመ ይመስላል ነገር ግን አቶ ረዳን ጨምሮ ኅብረተሰቡ ከባድ ዝናብ ከዘነበ የደረሰውን እህል ሊያወድምባቸው ስለሚችል ከቀትር በኋላ የሚያንዣብበውን ደመና በሥጋት ይመለከቱታል ይህ መጥፎ አጋጣሚ አንዳይከሰት አዛውንቶች የተስተካከለ ዝናብ እንዲሰጣቸው የአካባቢው ቀሳውስት የጸሎት ሥነሥርዓት አንዲያካሂዱላቸው ይማፀኗቸዋልበአሁኑ ወቅት በአንዳንድ አካባቢ የቄስ አጥረት ስላለ ይህንኑ ሥነሥርዓት የጥንቱን አፈ ታሪክ የሚያውቁ ክርስቲያን ቅማንቶች ያካሂዱላቸዋል ዘንድሮ ከባድ ዝናብ ዘንቦ ሰብላቸውን ባለማበላሸቱ አቶ ረዳ ያሉበት ኀብረተሰብ የተደረገዞፀ በዓላዋ ሥነሥርዓት የተሳካ ሆኖላቸዋል ቀሳውስትና አዛውንቶች ከብት አርደው ሲያጠናቅቁ አረማዊኦሪታዊና ክርስቲያን ቅማንቶች የተስተካከለ ዘናብ እንዲዘንብላቸው በሚያደርጉት በዓላዊ ሥነሥርዓት በየፊናቸው ለሥነሥርዓቱ የአካባቢው ቆሌ በሚኖርበት ቦታ ላይ በቀሊው ስም ወይም ቅዱስ በሆኑት ባህላዊ ጀግኖች ሰሥ በሚጠሩ ድግናዎች ሊሆን ይችላል ዝናቡ በጥቅምት ወር በጣም እየጠነከረ ከመጣ ሥርዓተጸሎቶች በተደጋጋሚ ይደረጋሉ በተለይም የሚሳተፉት የክርስቲያን ቅማንቶችም ቁጥር ከፍ ይሳል የአካባቢ ቅዱስ ድግናዎች ክብረበዓል በገዳር ወር እንደተለመደው ጋራዎች ደማቅ አረንጓዴ ምን የተጐናፀፉ ይመስላሉ ወንዞችም ጠርተው ፀሐይ ወርቃማ ነፀብራቋን በላያቸው ላይ ትፈነጥቃለች መሬቱ እየደረቀ ሲሃድ በላዩ ያለው ሰብል መጐምራት ጀምሯል ይህ ጊዜ የክረምቱ ወቅት ማለፉን የሚያበስር ነው ከዚህ ወር ጀምሮ አች ረዳና ልዶቻቸው መኸር ስብሰባውን የተያያዙት ሲሆን ባቄላ ዳጉሣ ኑግና ተልባ በመድረሳቸው ሥራው እየከበደና እየተጠናከረ መጥቷል በሕዳር ወር አጠቃላይ የሆነ የሃይማኖት ክብረበዓል ባይናርም አንዳንድ ኅብረተሰቦች ባህላዊ ጀግኖቻቸውን ለማስታወስ አነስተኛ ክብረ በዓል ይኖራቸዋል ተከታዩ የታህሳስ ወር ፀሐያማና ደረቅ ነው አት ረዳና ቤተሰቦቻቸው የደረሰውን እህል በመሰብሰብ ከፍተኛ ርብርቦሽ የሚያደርጉበት ወቅት ነው ለአጨዳ ከደረሱት ሰብሎች መካከል ጤፍ ስንዴና በዚህ ዓመት ሁለተኛ ሰብል ሆና የደረሰው ባለሁለት ረድፉ ገብስ በልጋ የመሳሰሉት ናቸው አቶ ረዳ አስቀድመው የመጀመሪያውን የ«በልጋ» ምርት በመስከረም ወር ወቅተው ወደቤታቸው ያስገቡ ቢሆንም መሬቱ በቂ እርጥበት በማግኘቱ ሁለተኛውን የገብስ ምርት ለማግኘት ችለዋል አንዳንድ ዘመን የዝናቡ ወቅት በመኸር ወራት ከቀጠለ ለሦስተኛው ጊዜ ይህንኑ ሰብል ማምረት እንደሚችሉ ነው የሚታወቀው በዚህ ወር አቶ ረዳና ቤተሰቦቻቸው አዝመራቸውን እየሰበሰቡ ወደ ቤታቸው ወስደው ጐተራዎቻቸውን ስለሞሉ የመንፈስ እርካታና ደስታ እንደሚያገኙ አይጠሬጠርም ጥረትግረታቸው ከተገቢው ሥርዓተጸሎት ጋር ተጋግዘው እንደገና የተትረፈረፈ ምርት እንዲያገኙ ረድቷቸዋል በዚህ ወትት በተለያዩ ማኅበረሰቦች በክብርዋ ሰም በሚ ጠፍ ድግናዎች የክብረበዓል ሥነሥርዓቶች ይካሄዳሉ በተመሳሳይ ጊዜያት ዋላጅ በሚገነው የክብርዋ ወንድም በካዲስቲ ስም በሚጠ ራው ድግና እና ኮሰጌ በሚገኘው የክብርዋና የካዲስቲ አባት የአይደርኪ ጓደኛ በሆነው በጀገሪሆ ስም የተሰየመው ድግና የክብረበዓል ሥነሥርዓቶች ይደረጋሉ በምዝግና ለጋስነት በተገኘው ስጦታ የመደሰቻ ወቅት በአምስተኛው ወር ጥር ላይ የአየሩ ጠባይ ፀሐያማ መሆኑን በመቀጠል መሬቱ በጣም እየደረተ ሲሄድ ወንዞችም በጣም ይጐድላሉ የበጋው ውቅት እንደቀጠለም ጋራዎች ወደ ወርቃማ ብጫማነት መለወጥ ይጀምራሉ እነ አቶ ረዳ ጤፍ አጨዳውን ተያይዘውታል ሽምብራውም ስለደረሰ ከደረቀው መሬት ላይ እየነቀሉ በመሰብሰብ ላይ ናቸው እህል እየወቁ ማስገባቱም ከፍተኛውን የሥራ ድርሻ በመያዝ ቀጥሏል በዚህ ወቅት ጥጋብ ነው የመዝናኛ ጊዜ ስላለ ከአካባቢው ኀብረተሰብ ውጭ ያሉትን ዘመድ አዝማድ ለመጠየቅ አጋጣሚው አሁን ነው። በማለት ስለጐመን ያላቸውን ዝቅተኛ ግመት የገለጹልኝን አልረሳውም «የክብረበዓል መዝጊያ» በዓል ዓለሜ የጥንቱ የባህል ትውፊት ሲሆን ብዙ ጊዜ በከርከር በአንዳንድ የተለያዩ ቡድኖች ታስቦ ይውላል ይህን የተረሳ ሥነሥርዓት አሥርም ሆኑ ቁጥራቸው ከዚያ በላይ የሆነ ወንዶችና ሴቶች በአንድ ላይ ተሰብስበው በግ አርደው በመብላትና ቡና አፍልተው በመጠጣት ያከብሩታል ጸሎት ከማድረስ በስተቀር የሥጋታቸው የሚያረጋጋ የተለየ የቅዳሴ ሥነሥርዓት አይደረግም በአሁኑ ጊዜ የጥንቱ ሥርዓት አባል የሆኑ ቄሶች በከርከር ስለሌሉ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ሲደረግ እንደነበረው የክብረበዓል መዝጊያው በትልቅ ስብሰባ አይከበርም በዚሁ ወቅት እንዲሁ በጣም ዝናብ ስለሚበዛ መንቀሳቀስ ከማይቻልበት ጊዜ ጋርም ይገጣጠማል አሥራ ሁለተኛው ወር ነሐሴ ከፍተኛው ዝናብ የሚዘንብበት ጊዜ ቢሆንም ባለፈው ዓመት በነበርኩበት ጊዜ ይጥል ከነበረው ዝናብ በጣም ያነሰ ነበር ዝናቡ በሚበዛበትና ደመናማ በሆነበት ጊዜ እንኳን በከርከርም ሆነ በጭልጋ የሙቀቱ ልክ ከ ዲግሪ ፋረንሐይት ወርዶ አያውቅም ብዙ ውሃ የበዛበት መሬት የሚፈልገው ጤፍ የሚዘራው በዚህ ወር ነው ጥራጥሬና የቅባት እህሎች በማደግ ላይ ሲሆኑ ደብዛዛ አረንጓዴ መልክ ያለው ገብስ ከሁለት እስከ ሦስት ጫማ ቁመት አድጐ ነፋስ ሲያወዛውዘው ልክ እንደማዕበል የሚተም ይመስላል ተልባና ዳጉሣ ትንሸ ከፍ ብለዋል እንዲሁም የቅባት እህል የሆነው ኑግ አረንጓዴ አገዳው አንድ ጫማ ያህል አድጓል ድንች ደርሶ በመሰብሰብ ሳላይ ሲሆን ጉመኑም ደርሶ እየከረደደ ነው በዚህ ወቅት የቅማንት ቴሶችና አዛውንቶች ሙሉውን የነሐሴን ጦር ይዖማሉ በዓመት አምስት ቀንና በአራተኛው ዓመት ደግሞ ስድስት ቀን ያለው የኢትዮጵያ ኛ ወር የሆነው ጳጉሜን ከነሐሴ ወር ይቀጥላል በዚህ ዘመን ዓመቱ በተለየ መልክ ድርቅ ሰለነበር ጳጉሜን ውስጥ አንድ ቀን ብቻ ነበር የዘነበው እስካሁን ያልተዘራ እህል ቢኖር ሸምብራ ብቻ ነው ሌሎች ሰብሎች በማደግ ላይ ሲገኙ በልጋ የሚባለው ገብስ ግን ወደ ደብዛዛ ቢጫነት ተለውጦ ለአጨዳ ደርሷል በቅድመመዝኸር በድሃ ገበሬዎች ከሚከሰተው ረሃብ ከድንችና ከጐጉመን ተጥሉ ከችጋር የሚያተርፋቸው ባለ ሁለት ረድፉ ገብስ በልጋ ነው ይህ የገብስ ዓይነት ሌላው ቀርቶ እሸቱ እንኳን ሊበላ የሚችል ነው አንዳንድ ዘመናት የመጨረሻዎቹ አንድ ወይም ሁለት ወራት የዘመኑ ምርት ዝቅ ያለ ከሆነ አንድ ሰው ለችግሩ መሸጋገሪያ እንዲሆንለት አንድ ከብት ሽጦ እህል መሸመት ይገደዳል ሌላው አማራጭ ደግሞ ትርፍ ካለው ዘመድ ወይም ጓደኛ መበደር ይሆናል ሆኖም አቶ ረዳ ለምግብና ለዘር የሚሆን በቂ እህል ስለነበራቸው አልተቸገሩም በዚህ ወቅት ብዙ ገበሬዎች በየጊዜው ጐተራቸው እየተራቆተ ጐመን ብቻ እየበሉ ያሳለፉትን ጊዜያት ያነሣሉ የአቶ ረዳ አባት አቶ አየነው ልጅ በነበሩበት ጊዜ ተከስቶ ብዙ ሕዝብ የጨረሰውን የረሃብ ዘመን ሲያስታውሱ ግን በጣም ይሰቀጥጣቸዋል ቢሆንም በአስቸጋሪ ሁኔታ ከመሞት መሰንበት የሚመርጥ መሆኑን ቅማንቶት በተረት ሲገልፁት «ከሞተ ንጉስ ይሻላል በቁም ያለ ድሃ ገበሬ» ይሳላሳሉ አዲሱ ዓመትና አዝመራ መስከረም ለክርስቲያኖች የዓመቱ የመጀመሪያ ወር ሲሆን ለቅማንቶች ደግሞ የሃይማኖት እንቅስቃሴዎቻቸውን ዑደት የሚዘጉበት የመጨረሻው ወር ነው የዚህ ወር የመጀመሪያው ቀን በሰሜናዊ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ የከባዱ የክፈምት ወቅት ማክተሙን የሚያበስር ነው ነገር ግን በቅማንት አካባቢ የዝናብ ወራት የሚፈፀመው በሚቀጥለው የጥቅምት ወር ላይ በመሆኑ የቅማንት ክብረበዓሎች ዑደት ምናልባትም የተፈሣው የመጀመሪያው የወራት መነሻ የሆነው ቀን የመሬቱ እርጥበት ምጥጥ በሚልበት በጥቅምት ሠር ሳይሆን አይተርም አዲሱ የዘመን መለወጫ መስከረም አንድ ዓመት በዓል ለቅማንቱ ለአማራውና ለፈላሻው የዕረፍትና ልዩ ምግብ የሚበላበት ቀን ነው አቶ ረዳና ቤተሰቦቻቸው ጥሩ ምግብ በመብላትና በመጠጣት ያለፈውን ዘመን የገመግሙበትና ወደፊቱ ደግሞ ምን ሊከተል ይችል ይሆን በማለት ሲያሰላስሉ የሚውሉበት ቀን ነው በተጨማሪም አዲሱ ዘመን ዛሮች የሚሾሙበት ቀን ስለሆነ ለቃልቻው አዮ ሥሪ የሚበዛበት ተን ይሆናል በዚሁ ቀን አዮ ሌሎች የዛር ትግሮችን ከመፍታቱ ሌላ አዲሱ ዓመት ምን ይዞ እንደሚመጣ የሚተነብይበት ዕለት ነው በጥቅምት ወር ዱባው ደርሶ አየተቆረጠ ነው በልጋው ደርቆ እየታጨደ ሲሆን ከስር ከስር ደግሞ በቲ ዝናብ በመገኘቱ ሁለተኛውን የበልጋ ምርት ለማግኘት ቃርሚያው እየታረሰ ዘር እየተዘራ ነው በጥሩ ሁኔታ እርሻው ከተሳካ የተትረፈረፈ ምርት ስለሚኖርና ጐተራዎቻቸው ስለሚሞሉ በሚቀጥለው በቅድመ መኸር ወቅት ሊከሰት ከሚችል ርሃብ ዋስትና ይኖራቸዋል ውሃው እየጠነፈፈ መሬቱ እየደረቀ ሲሄድ የሰብሎችን የተለያየ ሕብረቀለማት ማየት ዓይንን የሚማርኩ ከመሆኑም በላይ ጋራዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ አሸብርቀው ሜዳዎችና ሸንተረሮች በአደይ አበባ እንቁጣጣሸ አበባ ተንቆጥቆጠው ማሳዎች አልፎ አልፎ በሰማያዊ የተልባ አበባ ተሸፍነውና እዚያና እዚህ በአበቡት የኩሸሸሌ ክፍት ቀይ አበባዎች ታጅበው አገሩ ደምቆ ሲታይ መላው የቅማንት አካባቢ ለፖስት ካርድ የተዘጋጀ ስዕል ይመስላል ማለት ማጋነን አይሆንም የጭልጋ ወምበር በቤታቸው ከሚያደርጉት የአንድ ቀን ጸሎትና ግብዣ በስተቀር በዚህ ወር በድግናዎች የሚደረጉ ክብረ በዓላት የሉም በሚቀጥለው የጥቅምት ወር በአቶ ረዳና ጐረቤቶቻቸው ዘንድ ሰብል ሰብሰባው በጣም ይፋፋማል እንዲሁም ዓመታዊው የክብረበዓላት ዑደት እንደገና በአዲሱ ዘመን ይከፈታል ወቅቱ እንደልብ መንቀሳቀስ የሚቻልበትና ጐተራዎችም ሞልተው ምግብ የሚትረፈረፍበት ጊዜ ነው በዚህ ወቅት አቶ ረዳ ልጆቻቸውና የልጅ ልጆቻቸው ልክ አባታቸው አቶ አየነው በዘመናቸው ያደርጉት እንደነበረው ሁሉ ለመጪው ዓመታዊ የኢኮኖሚያዊና መንፈሳዊ ዑደት ለሚያደርጉት ተሳትፎና ጥረትግረት አርቀው ማቀድ ይጀምራሉ ምዕራፍ ዘጠን የምዝግና ሰዎች የሕይወት ዑደት ቅማንቶች ከአንዳ የሰውነት ደረጃ ወደሌላው ሲሸጋገሩ የሚያደርጓቸው ሥነሥርዓቶች በሕይወታቸው ሂደት የሚያልፉባቸውን ልዩ ልዩ አርከናኙ በግልጽ ያንፀባርቃሉ አንድ ግለሰብ ከአንዱ ወደሌላው ሄደት ሲሸጋገር በመንፈሳዊ ሥነሥርዓቶች ይከበራለሉ አንድ ልጅ ተወልዶ የቅማንት ኅብረተሰብ አባል ሲሆን ጉርምሶ ሲያገባ ሲሸመግል ሞቶ ወደሌላው ዓለም ሲቨጋገር በየደረጃው የሚያካሂዷቸው ከሃይማኖት ጋር የተያያዙ ሥነሥርዓቶች አሏቸው እንደነዚህ ዓይነት በምዝግና በእግዚአብሔር በጉ ፈቃድ የሚካሄድ ክብረበዓላት የቅማንት ኀብረተሰብን የሚያስተሳስሩና ቅማንቱ ከሌላው ኀብረተሰብ ጋር ሳይቀላቀል ልዩ የሆነውን ማኀበራዊ ሥርዓቱን ጠብቆ እንዲቆይ አድርጉታል ከዚህ ቀጥሎ እያንዳንዱ ቅማንት በኀብረተሰቡ ውስጥ ባለው መዋትርና በባህሉ ሥነምግባር መሠረት ሕይወቱን እንዴት እንደሚመራ እናያለን በሴት የወር አበባና በመጫትነት ወቅት የተከለከሉ ነገሮች የሰውን የሕይወት ዑደት ለመዘርዘር ልጅ ከሚወለድበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ዕለተ ሞቱ ድረስ ማየት የተለመደ ነው ነገር ግን የቅማንቶችን የሕይወት ሂደትና ከዚህም ጋር ተያይዘው ያሉት ከአንዱ ወደ ሌላው ደረጃ የመሸጋገሩ ጉዳይ በዕለተ ሞት ብቻ ሳይገታ ከመቃብር በኋላም ሌሎች ሥነሥርዓቶች እንዳሉ ነው የምንረዳው እንዲሁም በተመሳሳይ ሁኔታ ስለቅማንት የሕይወት ዑደት ስናጠና ልጅ ከሚወለድበት ጊዜ ጀምሮ ሳይሆን ከልደት በፊት ወደኋላ ሄደን አንዲት ለአቅመ ሄይዋን የደረሰች ሴትን ቅማንቶች በምን ዓይነት መልክ እንደሚመለከቷት መገንዘብ ይኖርብናል የቅማንት ሴቶች የወር አበባቸው በሚመጣበት ጊዜና በሚወልዱበት ወቅት እንዳልፀዱ እንደረከሱ ስለሚታዩ ለአንድ ሳምንት ከኀብረተሰቡ ተገልለው ይሰነብታሉ ይህ እምነትና ባህል በሌሎችም የአገው ሕዝቦችም ዘንድ ያለ ሲሆን ከሴቶች የሚፈሰው ደም መርገም የሚያረክስና ጉጅ ነው ተብሎ ይታሰባል አንዲት ሴት በሥረዓተቅዳሴ ቦታ ላይ መገኘት የምትችለውና ሙሉ በሙሉ ንፁሕ ናት የምትባለው ስታርጥ ብቻ ነው ይህ የሰውነት ፍጥረታዊ ለውጥ እንደተከሰተ ወደ ማንኛውም ቅዱስ ቦታ መሄድና እንዲሁም ለሥርዓተቅዳሴ የተዘጋጀውን ምግብና መጠጥ መጋበዝ ትችላለች የቅማንት ሴት የወር አበባዋ በሚመጣበት ወቅት በተለይ ለዚህ አገልግሎት ተብሉ በማንኛውም ቤተሰብ ቤት አጠገብ በተሠራ ጐጆ ውስጥ ትገለላለች በምንም ምክንያት ጉጆዋን ለቃ መውጣት ስለማትችል ምግቧ በቬተሰቧ አማካይነት ይቀርብላታል በምትነፃበት በሰባተኛው ተቀን ጉጆውን ታፀዳለች ሰውነቷን ታጥባና ልብሶቿን አጣጥባ ለብሳ ወደ ዕለታዊ ተግባሯ ትመለሳለች በወር አበባ ጊዜ ይህ ለብቻ የመገለል ሁኔታ ትኩረቴን በጣም ሊሰብ የቻለው አንድ ነገር ቢኖር በዚህ በተከለከለ ባህል ታቡ ምክንያት አንዲት ሴት ከአድሜዋ አንድ አራተኛ የሆነውን ወርቃማ የምርታማነት ጊዜ በእረፍት ላይ ማሳለፏ ነው ስለዚህ ጉዳይ ከአንዳንድ የቅማንት ወንዶች ጋር ለውይይት አንስቼ ሳነጋግራቸው ያላቸው አቋም «ሴቶች ሥራ አይበዛባቸውም አንዲት ሴት በወር አበባ ምክንያት ስትገለል የእሷ የሥራ ድርሻ በቤተሰቡ ባሉ ሌሉች ሴቶች ይሸፈናል» የሚል ነው በአጠቃላይ በወንዶች እይታ የሴት ሥራ ሳይሠራ እንደማይቀርና ሴት ቁጭ ብሳ ጠሳ እየስጣች ወሬ በማውራት እንደምትውል ነው ግምታቸው ከዚህ ጋር በተያያዘ መልኩ ሌላ የተከለከለ ባህል ቢኖር ሴቶች በሚወልዱበት ጊዜ የሚደረገው ማግለል ነው አንዲት ሴት አርግዛ የመውለጃ ጊዜዋ ሲቃረብ ጊዜያዊ የሆነ የማግለያ ጐጆ ከዋናው ቤት አጠገብ ይሠራሳታል ሕፃኑ አንደተወለደ ልጂን ይዛ ወደ ጐጆው በመግባት ለሰባት ቀን ትቀመጣለች የልድ ልደት አንዲት ሴት የመጀመሪያዋን ልጅ በአናቷ ወይም በአማቷ ቤት ትወልዳለች ከዚያ በኋላ የሚመጡትን ልጆቿን ግን በራሷ ቤት ነው የምትወልደው በቅማንት ቤተሰብ ልጅ በሚወለድበት ወቅት ከሚወሰዱት እርምጃዎች ጋር ለመተዋወቅ ይረዳን ዘንድ ፀሐይ ከአማቶቿ በአቶ ረዳና በወይዘሮ አዳነች ቤት የመጀመሪያዋን ልጅ በወለደችበት ወቅት የተወሰደውን እርምጃ አንመልከት አንድ ተን ፀሀጥ ባለና አየሩ በመኸር ወቅት ሽታ በተሞላበት ሌሊት ፀሐይ ምጥ ተያዘች ምጡ እየጠነከረ ስለመጣ ወይዘሮ አዳነች አብረው ከሚኖሩት ከጎረቤቶቻቸው በአዋላጅነት የታወቁትን እንዲረዱና ፀሐይን በምጡ ጊዜ እንዲያበረታቱ አስጠ ሯቸው ምጡ ለፀሐይ በጣም አስቸጋሪ ቢሆን ኖሮ የአይደርኪ ሚስት የነበረችውን እንተላ የተባለችውን የባህል ጀግና ምልኪ ለመለማመን ሴቶች ልዩ ጸሉት ማድረግ ይገደዱ ነበር ሆኖም ፀሐይ የአሥራ ስድስት ዓመት ወጣትና ጠንካራ ሴት ስለነበረች ችግሩን በቀላሉ ተቋቁማ ወንድ ልጅ በደህና ተገላገለች ልጁ እንደተወለደ ወይዘር አዳነች እትብቱን ቆርጠው ከቋጠሩ በኋላ ቀሪውን እትብትና የአንግዴውን ልጅ አቶ ረዳ ከጓሮአቸው ቀበሩት አንዳንድ የግል ቆሌና ዛር አዲስ ሕፃን ሲያለቅስ በመስማት በአካባቢው ሊያንዣብቡ ይችሉ ይሆናል ብለው ቅማንቶች ይገምታሉ በተለይ ፀሐይ መጥፎ የሆነ ቆሌ ወደ ሕፃኑ አጠገብ ሊመጣ ይችላል ብላ ስለሠጋች ቆሌው እንዲርቅ ለማባበል አንድ ዶሮ በማረድ መስዋዕት ተደረገለት የታረደውን ዶሮፎ ወጥ ሠርተው ሕፃኑ ሲወለድ ለነበሩት ሰዎች ግብዣ አደረጉላቸው በተጨማሪም በማዋለድ ረገድ የረዱ ሰዎች ሁሉ እንደውለታ ተቆጥሮላቸው ሌላ ቀን አንድ ጥሩ የምግብ ግብዣ ይኖራቸዋል ፀሐይ ወንድ ልጂን ይዛ ወደምትገለልበት ጐጆ ከሳ ገባች ልጁ የተወለደበት ዋናው ቤት አእንዲነፃ ወምበሩ በደገሙበት ቀኖና ፀበል በቤቱ ዙሪያና በማዋለዱ ተግባር በተካፈሉት ሴቶች ላይ ተረጨ። የሚሉ አባባሎች ይገኘበታል በሌላ ጊዜም ቁንጥጫ ጥፊ ወይም በምግብ መቅጣት በወላጆች የሚወሰዱ እርምጃዎች ናቸው ሦስቱ ወንደማማቾች ጠባያቸውን እንዲያሳምሩ የቁልምጫ ምግብና መጠጥ መስጠትም የተለመደ ነው ወጣት ወንዶችና ልጃገረዶች አንድ ላይ ሆነው መጫወት ስለማይከለከሉ ታደሰ ከልጃገረዶች ጋር ይጫወታል ይደባደባል ነገር ግን ከፈቃደሥጋ ጋር የተያያዘ ጨዋታ አይፈቀድም ጉረምሳ ወንዶችና የደረሱ ልጃገረዶች በአንድ ላይ መተኛትም ክልክል ነው ስለ ግብረሥጋ ግንኙነት ብዙ ጊዜ በቤት ውስጥና ሰው በተሰበሰበበት ቦታ ላይ መነጋገር እንደ ነውር ስለሚቆጠር ወጣቶች ስለዚህ ጉዳይ ብዙ ጊዜ ቀስ በቀስ ግንዛቤ ለማግኘት የሚችሉት ትላልትቅት ወንዶች የሚያደርጉትን የእርስ በእርስ ውይይት በማዳመጥ ነው የንጽሕና አጠባበት ትምህርት በቅማንቶች ዘንድ መስጠት ከሚገቡት ትምህርቶች ዋነኛው ነው ታደሰ ምግብ ከመብላቱ በፊትም ሆነ ምግብ በማዘጋጀት በሚረዳበት ጊዜ እጁን መታጠብ እንዳለበት እንዲያውት ይደረጋል ታላቅ ወንድሙ ወርቄም እንጀራ መብላትና ከሞሰቡም እንጀራ መቁረስ ያለበት በቀኝ እጅ መሆኑን ግራ እጁን በጥፊ እየተመታ እንዲማር ይደረጋል እንዲሁም በወር ወይም በሁለት ወር አንድ ጊዜ ልብሳቸውን እንዲያጥቡ ምክር ይሰጣል ታደሰና ወልዱ መቼና የት ሽንትና ዓይነምድር መፀዳዳት እንዳለባቸው በመሠረቱ ትምህርት አይሰጣቸውም ወልዱ ዕድሜው ከሁለት ዓመት በታች በመሆኑ ሁለቱንም ከቤት ውስጥ ቢያደርግ ቁጣ አይደርስበትም እያደገ በሄደ ቁጥር ግን የሚፀዳዳው ከቤቱ እየራቀ እየሄደ ነው ጐረምሶችና ትላልቅ ሰዎች ሽንታቸውን ከቤት አጠገብ ለመሽናት ቢችሉም ለዓይነ ምድር ግን ወደ ጫካና ሜዳ መሄድ ይኖርባቸዋል በወጣትነት ሙያዊ ሥልጠና አንድ ልጅ ወደፊት ሊሠማራበት ባሰበው የሙያ መስክ እንዲለማመድ ዝግጁ ማድረግ ተገቢ ነው ይህ ዓይነት ዝግጅት በልጅነት በጨዋታ መልክ ነው የሚጀመረው ታደሰና ጓሉ በእንጨትና በጭቃ የጨዋታ ቤት ይሠራሉ በትራቸው ላይ በመንፈራጠጥ ፈረስ መጋለብ ይለማመዳሉ እንዲሁም በሹል እንጨት እርሻ ማረስ ይሞክራሉ ጓሉ በበትሩ እርፍና ሞፈር እያዘጋጀ ታደሰ እንደበሬ ሆኖ እንዲጉትት ያደርገዋል ታደሰ ወልዱን አንድ ቀን «እንደበሬ እጠምድሃለው» ይለዋል ይህንን የሰሙት ወይዘሮ አቦነሽ «እንደዚህ ብታደርግ ጉንጮችህን በቁንጥጫ አነሳልሃለሁ» እንዳሉት አስታውሳለሁ የመጫወቻ የበሬ ጅራፍ ከእንጨትና ከልጥ መሥራት የተለመደ ነው እንደወርቄ ያሉ የአምስት ዓመት ልጆች ከእሱ ከፍ ካሉ ልጆች ጋር ጥጃ ጥበቃ በመውጣት በሥራው ላይ ሆነው የእአረኝነቱን ሥራ ይለማመዳሉ አንድ ሃያ ኪሎ ግራም የሚመዝን ልጅ አንድ ሺህ ኪሉ ግራም የሚመዝነውን በሬ ምንም ፍንክች ባይልለትም በዱላ ሲመታው ማየት አዲስ ነገር አይደለም ወጣት አረኞች የሚበላ እሸት ካገኙ የማንም ይሁን የማን ባለቤቱ ሳያያቸው ቀጥፈው ይበላሉ ይህ አጋጣሚ ነው ትናንሽ ልጆችን ከእናታቸውና ከምድጃቸው እርቀው ወደ እረኛነቱ የሚጐትታቸው ወርቄ ዕድሜው አሥራ ሁለት ዓመት ሲሆን ከጐረቤት የእርሻ ቦታ እሸት እየሰረቀ በማስቸገሩ አንድ የተናደደ ገበሬ «ከብቶች እህሌን እንዳይበሉ በአጥር እየተከሳከልኩ ቢሆንም ወርቄ የተባለ ልጅ እንደ ዝንጀሮ አጥር እየዘለለ እየገባ ነው ግድየለም አንድ ቀን ከወርቅ የበለጠ ካሣ ይከፍላታል» ብሎ በማማረር መፎከሩን አስታውሳለሁ ወጣት ልጃገረጆች አፈር እየፈጩ በማቡካት የውሸት እንጀራ በመጋገር ይለማመዳሉ ከሦስት ዓመታቸው ጀምሮ ዶሮ ከመጠበቅ አልፈው እሰከ ዕቃና እንጨት ማቅረብ ሥራ ላይ ይደርሳሉ ከዓመትና ከሁለት ዓመት በኋላም የመላሳኩን ሥራ ይያያዙታል ልጆች ስምንት ዓመት ሲሞላቸው በማንኛውም ዓይነት ሥራ በመሳተፍ ወላጆቻቸውን ይረዳሉ ልጃገረዶች ወፍጮ የምንታሖላሦትላዳጣኖድዓዓ እ አ ትት ትትቢኑእ እቤ ይፈጫሉ ቤት ያፀዳሉ ከዶሮና ከሥጋ ወጥ በስተቀር ሌላውን ምግብ ሁሉ ማብሰል ይትላሉ ወሀንዶች ልጆች ደግሞ ከአባታቸው ጋር ወደገበያ በመሄ ቤት በመሥራትና በአርሻውም ቦታ አንዳንድ ሥራዎችን በመሥራት ይረዳለ አንዳንድ ጊዜ ነሽ ማንኛውም አባት እንደሚያደርገው ሁሉ ልጁ ሠርቄ በሬዎችን ጦ ምዶ ትንሽ ሾሮችን እንዲያርስ ይፈቅድለታል በመጀመሪያው የጉርምስና እና የኮረዳነት ጊዜያቸው ወንዶችና ሴቶች ልጆች ለሕይወት አሰፈላጊ የሆኑትን ነገሮች ለመሥራት የሚያስችላቸውን ፅውቀት ይሬጩጨጨብዛጣለ ለጦላጆቹጀም ሆነ ለልጆቻቸው ደህንነት ሲባል ልጆቹን ገና በወጣትነታቸው ኑሮ ምን አንደሚመስልና እንዴት መቋቋም እንዳለባቸው ማስተማር ጠቃሚ መሆኑን ያውቃ ሉ ይህ ከሆነ አንድ ሰው እርጅና ሲመጣ ጠንካራና በቂ ችሎታ ያላቸው ወንዶች ልጆችና ያገቡ ጠንካራ ሴቶች አጋር ይሆኑለታል ማለት ነው በዚህ ረገድ አቶ ረዳ የታደሉ ናቸው ጥሩ አቋም ባላቸው ሦስት ጉልበታም ልጆቻቸው እየተረዱ በራሳቸውና በባለቤታቸው የዘር አረግ ያገኙዋቸውን መሬቶት አገላብጠው ለማረስ አስችሏቸዋል ብዙ የምርት ውጤት ለአቶ ረዳ ብዙ ሀብትና ኃይል ማለት ሲሆን አንድ ልጅ ብቻ ቢኖራቸው ኖሮ ይህን ያህል አያምርቱም ምንም ልጅ ባይኖራቸው ደግሞ ጠቅላላ ውድቀት ይሆንባቸው ነበር አልባሳትና ጌጣጌጥ እንደ ታደሰ ያሉ የአምስትና የስድስት ዓመት የቅማንት ሕፃናት ከፊል ሰውነታቸውን ራቁታቸውን እንዲሄዱ ቢፈቀድላቸውም ከዚህ ዕድሜ በኋላ ግን ሁልጊዜ ልብስ መልበስ ይኖርባቸዋል ትናንሽ ወንዶች ልጆች ጥብቆ ብቻ ልጃገረዶች አንድ ወጥ ቀሚስ ከፍ ያሉ ልጆች ደግሞ ረዥም ቁምጣ ይለብሳሉ ወርቄና ታላቁ የሆኑት ዘመዶቹ ከአጀ ጠባብ ጋር ቁምጣ ሱሪ ወይም ባትተሁለት ወይም ረዥም ሱሪ በቀበቶ ወይም በሸምቀቆ ይታጠቃሉ ባርኔጣ ወይም ቆብ ብዙም አልተለመደም ከዚሁ ላይ ነጭ ጋቢ ወይም ኩታ ደርቦ መሄድ የተለመደ ነው አንዳንድ ጐረምሶች ጋቢውን በሸሚዝ ምትክ ይለብሱታል የበግ አጐዛና ብርድ ልብስ በሰውነት ላይ ጣል አድርጐ መሄድም አለ ወይዘሮ አዳነችና ምራቶቻቸው አንድ ወጥ ቀሚስ ከመቀነት ጋር ያደርጋሉ እንዳስፈላጊነቱም ኩታ በላዩ ላይ ይደርባሉ አንዳንድ ጊዜ ቀሚሱ ይጠለፋል ኩታውም ቆንጆ ጥለት ሊኖረው ይችላል ከቆዳ ወይም ከጉንደር ከተማ የሚገኝ ከመኪና ጉማ የተሠራ ነጠላ ጫማ ማድረግ ከትርብ ጊዜ ወዲህ በአንዳንድ ሰዎች እየተለመደ መጥቷል ልጆች በሰማያዊ ዶቃና ዛጉል ያጌጠ ማተብ በአንገታቸው ላይ ያደርጋሉ ልጃገፈዶች ደግሞ ከመዳብ ወይም ከብር የተሠሩ የእጅ አምባርና ባለዶቃ የእግር አልቦ ያጠልቃሉ ከዚህም በስተቀር ሴቶችም ሆኑ ወንዶች የብር ወይም የመዳብ ተለበት በጣታቸው ያደርጋሉ ከአሸን ክታቡ ጋር የኢትዮጵያን ወይም የእንግሊዝ ወይም የጣልያን ሳንቲሞች በገመድ ተንጠልጥለው በአንገት ላይ በማጥለቅ ለጌጥነት ያገለግሳሉ ክብ የብር ጉትቻ ለማድረግ ሴቶች ጆሮአቸውን የስበሳሉ ከአምሣ ዓመት በፊት ወንዶችም የጆሮ ሉቲ ያደርጉ ነበር ንቅሳት አንዱ የመጋጌጫ ስልት ሲሆን ንትሳቱ በአንገት በድድ በደረት በግንባርበእጅና በቁርጭምጭሚት ላይ ሊሆን ይችላል ቅብዓኑግ ከጥቀርሻ ጋር ተቀላቅሎ እንዲሞቅ በማድረግ ማቅለሚያ ከተዘጋጀ በኋላ በግራር ወይም በአጋም እሾህ ማቅለሚያውን በማጣቀስ በተፈለገው የሰውነት ክፍል ላይ በመጨቅጨት ንቅሳቱ ዝግጁ ይሆናል ንቅሳት ከጌጥነቱ በተጨማሪ ለበሸታ ፈውስና መከላከያም ሆኖ ያገለግላል በአንገት ላይ ንቅሳት ሲደረግ እንቅርትን እንደሚያድንና ድድን መነቀስ ደግሞ የጥርስ መድማትንና ቁርጥማትን ያስቀራል ይባሳል እንደ ፀሐይና አልማዝ ለመሳሰሉት ቆነጃጅት ደግሞ ቡዳ እንዳይበላቸው ንቅሳት ጥሩ መከላከያ መሆኑ ይነገራል ወልዱን የመሳሰሉ ትናንሽ ልጆች የተለየ የፀጉር አያያዝ ስልት የላቸውም አራትና አምስት ዕድሜ ያሳቸው እንደ ታደሰ ያሉት ልጆች ፀጉራቸውን ተላጭተው ትንሸ ቁንጮ ብቻ ከአናታቸው ላይ ይተዋል አሥር ዓመት ሲሞላቸው እንደ ወርቄ ሙሉ በሙሉ ፀጉራቸውን ይላጫሉ ዕድሜያቸው አሥራ ስምንት ዓመትና ከዚያም በላይ የሆነ አንደ ነጋሸ ያሉ ጉረምሶች በመሰሎቻቸው ዘንድ እንደተለመደው ሁሉ ፀጉራቸው አጠር ያለ ሲሆን እንደ አቶ ረዳ ጠና ያሉ ሰዎች ግን በጣሊያን ወረራ ዘመን እኤአ ከ ዓም አርበኞች ያደርጉት እንደነበረው ፀጉራቸውን ያጉፍራሉ አንዲት ልጃገረድ አራት ዓመት ሲሞላት ፀጉሯ እንዲያድግ ይደረግና ከራስ ቅሏ በስተጀርባ ትንሸ ቦታ ተላጭቶ ዙሪያውን ሹሩባ ጋሜ ትሠራለች ስምንት ዓመት ሲሞላት ደግሞ መሐል ሳይ የተላጨው ይተውና እንዲያድግ ተደርጉ ሳዱሳ ይሆናል አንዲት ሴት አግብታ ለብዙ ጊዜ ከቆየች በኋላ ፀጉሯ ሙሉ በሙሉ እንዲያድግ ይደረግና ሹሩባ ቁንዳላ ትሠራለች ጠ ና ያለች ስትሆን ደግሞ እንደ ወንዶች ፀጉሯን ታሳጥራለች ይህን ዓይነት የፀጉር አያያዝ ሀዘንተኛ ሴቶችም ይጠቀሙበታል የቅማንቶች ልብስ አለባበስ የፀጉር አያያዝና ጌጣጌጥ አደራረግ በቤጌምድርና ሰሜን ከሚኖሩት አማራና ፈላሻዎች ጋር አንድ ዓይነት መሆኑን መገንዘብ አያስቸግርም ጋብቻና የጉርምስና ጊዜ በተለይ የቅማንትን የጋብቻ ሁኔታ ለመረዳት እንዲያስችለን የነጋሸና የቢተው ታናሽ ወንድም የሆነው የአቶ ረዳ ልጅ መልኬ ቆንጆዋን ከበቡሽን ሲያገባ የተደረገውን የጋብቻ ሥነሥርዓት በኋላ እንመለስበታለን አስቀድሞ ግን የቅማንት ጋብቻ በአጠቃላይ እንዴት እንደሆነ አናያለን ልጃገረዶች ገና በወጣትነታቸው አንዳንድ ጊዜ ሰባት ዓመት ሲሞላቸው በአብዛኛው ግን ከስምንት ዓመት እስከ አሥራ አምስት ዓመታቸው ባለው ጊዜ ውስጥ ይዳራሉ ከጋብቻ በፊት የግብረ ሥጋ ግንኙነት ስለማይፈቀድ የሴቶች ክብረንጽሕና አለመደፈር ለጋብቻ ወሳኝ ነገር ነው ይህም በመሆኑ አንዲት ሴት ፈት ካልሆነች በስተቀር ድንግልነቋ ካልተጠበቀ ባል በቀላሉ አታገኝም በሴቶች ዘንድ ከጋብቻ ውጭ የሚደረግ የግብረሥጋ ግንኙነት የተከለከለ ስለሆነ በጋብቻ ጊዜ ነገሩ ከተደረሰበት ለፍች ያደርሳል ከጋብቻ በፊትም እርግዝና የተወገዘ በመሆኑ ብዙ ጊዜ አይከሰትም ጋብቻ የሚፈጸመው በልጅነት በመሆኑ ልጅ የሚፀነሰው ጋብቻው ከተፈፀመ ከጥቂት ዓመታት በኋላ ነው ዕቁባት ማስቀመጥ ቢፈቀድም ብዙ የተለመደ አይደለም ሊፈቀድ የሚችለውም አንድ ያገባ ሰው ሚስቱ ለአካለ መጠን ያልደረሰች ከሆነ ነው አንዲት ድሀ ልጃገረድ በሀብት ማነስ ምክንያት ዘመዶቿ ሳይድሯት ሲቀሩና ከዝቅተኛ ቤተሰብ በመምጣቷ ባል የማግኘት ዕድሏ የተመናመነ ከሆነ ምርጫዋ ከአንድ ሀብታም ቤት ገብታ በግርድና መተጠር ይሆናል በዚህ ጊዜ የአሳዳሪዋ ወንድ ልጅ ያገባም ሆነ ያላገባ ወጦወሸሟት ልጅ ልትወልድ ትትላለች ያለችበትን ቤተሰብ ከለቀቀች ልጁን ከአባቱ ዘንድ ጥላው ትሄዳለች ጥንት የባሪያ አሳዳሪ ሥርዓት በሰፈነበት ዘመን አንድ ሰው ከባሪያው ጋር የግብረሥጋ ለመፈጸም ይችል እንደነበረ ቢታወቅም ሴተኛ አዳሪነት ግን በቅማንት ዘንድ ፈጽሞ አይታወቅም ወንዶች ከአሥራ ስምንት እስከ ሃያ ዓመት ድረስ ባለው ዕድሜያቸው በአብዛኛው ጋብቻ የሚፈጽሙ ቢሆንም የጋብቻው ጊዜ አስከ ሠላሣ ዓመት ዕድሜ ድረስ ሊራዘም ይችሳል ከጋብቻ በፊት የግብረሥጋ ግንኙነት ለማድረግ የወንዶች እድል የጠበበ ነው ነገር ግን አልፎ አልፎ ጠና ካሉና ባሉቻቸው ከሞቱባቸው ሴቶች ጋር ድርጊቱን ይፈጽማሉ አስገድዶ መድፈር በቅማንትች ዘንድ አይዘወተርም ግብረ ሰዶምም ቢሆን አንዳንድ ጊዜ በአረኞች መካከል ሊከሰት ይችል ይሆናል እንጂ ብዙ አይታወቅም የቅማንት ጋብቻ በዘልማድ በሙሽሸራውና በሙሽሪት ወላጆች መካከል በሚደረግ የቃል ውል መሠረት የሚፈጸም ነሶዐ የመሬት አለኝታና ሌላም ሀብት በጋብቻ ጊዜ ወሳኝነት ስላለው በሙሽራውና በሙሽሪት ቤተሰቦች መካከል በሚደረገው የስምምነት ውል የሚገለጽ ጉዳይ ነው ጋብቻው ፋሁ የዊናት አና ሠርጉ ስናው ለአንድ ወንድ ቅማንት ከጉረምሳነት ወደ ጉልማሳነት የሚያሸጋግረው ድልድይ ነው ሴቶች ግን ገና ወጣት ስለሆኑ ሁልጊዜ ወደዚህ ደረጃ ተሸጋገሩ ማለት አያስደፍርም ለወንዶችም ሆነ ለሴቶቹ ለዚህ ደረጃ በመብቃታቸው ሌላ የተለዬ ሥነሥርዓት አይካሄድላቸውም በጋብቻ ወቅት የሚደረግ የሀብት ዝውውር ሙሽራውና ሙሽሪት ለኑሮአቸው ማጫመቋቋሚያ አንዲሆንላቸው ወላጆቻቸው በየበኩላቸው የገንዘብና የእንስሳት መዋጮ በማድረግ ይሰጧሟቸዋል መጠኑም አስተድሞ በተስማሙበት የቃል ውል መሠረት ይሆናል አንዱ ወገን ከፍ ያለ ማጫ ሌላው ደግሞ ዝቅ ያለ ማጫ ካቀረበ ፍት በሚያጋጥምበት ወቅት እሱ ወይም እሷ ልዩነቱን የመውሰድ መብት በቃል ውላቸው ላይ የተጠበቀ ይሆናል የጥንቱ የጋብቻ የባህል ትውፊት ደግሞ ጋብቻ ከመፈጸሙ በፊት ለሙሽራይቱ እጅ መንሻ መታያ የሚሆን የኢትዮጵያ ብር ከ እስከ ዐ ማሪዖ ቴሬዛ ብር መክፈል አሰፈላጊ ነበር የሙሸራው ቤተሰቦች አቅማቸው ከፍተኛ ከሆነ በዚያው መጠን ክፍያውን ከፍ ማድረግ ይችላሉ እጩው ሙሽራና አባቱ ለሙሽራይቱ ወላጆች ለአጅ መንሻ የሰጡት ገንዘብ እንደገና ተመልሶ ለባለትዳሮቹ በሁለት ዓይንት መልክ ለመቋቋሚያ የሚሰጥበት መንገድ አለ የመጀመሪያው በሠርጉ ድግሰ ማብቂያ ላይ ሙሸራው የጀግና ፉከራ አሰምቶ አማቶቹ በመደሰት በሸልማት መልክ ገንዘቡን የሚመልሱበት ሁኔታ ያለ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የሙሽራዋ አባት ለምንጣፍ የሚሆን ጀንዲ ሌማት የተለያዩ እቃዎችና እንዲሁም ሙሽራዋ በግል የምትጠቀምበት በአረብ ቆዳ የተለበደ አገልግል በልዩ ልዩ ዕቃዎች ተሞልቶ መስጠት የተለመደ ነው አንዲያውም የመታያው ገንዘብ ለዚህ ጉዳይ በቂ ሆኖ ካልተገኘ የሙሽራይቱ አባት ከራሱ ገንዘብ የሚጨምርበት ጊዜም አለ ጥንት ቅማንቶች ጋብቻው የጠነከረና የሰመረ እንዲሆን ሀብታቸውን ወደልጆቻቸው ማስተሳለፍ አስፈላጊነቱን ስለሚያም ኑበት የአጅ መንሻው ከፍተኛ እንደነበረ ታውቋል በአሁኑ ጊዜ ግን መታያው ለስሙ ያህል የሁለቱን ቤተሰቦች ትስስር በሚያጠናክር መልክ ከበጉ ፈቃድ መግለጫነት የሚያልፍ አይደለም አንድ ሰው ከጓደኞቹ ጋር በመሆን አንዷን ልጃገረድ አስገድዶ በመጥለፍ ጋብቻ መፈጸም ብዙም የተለመደ አይደለም ሆኖም ግለሰቡ አንዲት ልጃገረድ ለማግባት ፈልጐ ድሃ በመሆኑ ምክንያት የልጅቷ ወላጆች ጋብቻውን ቢከለክሉት ጠለፋ ሊካሄድ ይችላል በጠለፋ ምክንያት በቤተሰቦች መካከል ግጭት አንዳይፈጠር የቅማንት ቄሶችና ሸማግሌዎች በጠላፊው ላይ የገንዘብና የከብት ቅጣት በመጣል የልጅቷ አባት እንዲካስና በኀብረተሰቡ ዘንድ ክብሩ ተጠብቆ አንዲቆይ ለማድረግና ሁኔታው እንዳይባባስ ይከላከላሉ ይህ የሀብት ዝውውር ወይም ቅጣት ሳይሆን በመሠረቱ አባትዬው ለተጋቢዎች የሚመልሰው ነው ዋናው ቁምነገር ግን የልጆቷ አባት መልካም ዝና እንዳይጐጉድፍ ለደረሰበት በደል ሥርዓት በያዘ መልክ እንዲካስ ማድረጉ ነው የባሕል ሲቪል ጋብቻና ሃይማኖታዊ ጋብቻ አብዛኛውን ጊዜ ቅማንቶች በባህል ሲቪል እና ሃይማኖታዊ የጋብቻ ሥነሥርዓቶች የተሳሰራሉ ሦስተኛው ዓይነት ትስስር ደግሞ ሴትና ወንድ በሁለቱም ፈቃደኝነት በአንድ ላይ መኖር ሲጀምሩ የሚያጋጥም ነው ይህ ዓይነት ትስስር ለአጭር ጊዜ ሆኖ ከሁለቱም ወገኖች አንዱ በማንኛውም ጊዜ ሊያፈርሰው ይችላል በባህል ጋብቻው የሃይማኖት ሥርዓተቅዳሴ ሳያስፈልግ ሠርግ በመደገስ ብቻ የሚፈጸም ነው ይህ ዓይነት ጋብቻ በሁለቱ ወገኖች የጋራ ስምምነት መሠረት ንብረታቸውን እኩል በመካፈል ሊያፈርሱት ይችላሉ ነገር ግን ባልና ሚስቱ ጠና ያሉ ሆነው በካሣ ሥነሥርዓት አልፈው በአዛውንትነት የሚታወቁ ከሆነ መፋታት አይችሉም በዚህ ሁኔታ የሚገኙ ባለትዳሮች አንደኛው እንኳን ቢሞት እንደገና ለማግባት የወምበሩን ፈቃድ ማግኘት አስፈላጊ ይሆናል እንዲሁም እሷም ሆነች እሱ ካሁን በፊት በካሣ ሥነሥርዓት ያላለፉ ከሆነ ይህንኑ መፈጸም ግዴታ አለባቸው በቅማንት ኅብረተሰብ ሃይማኖታዊ የጋብቻ ሥነሥርዓት የሚካሄደው በቀሳውስቱ ዘንድ በመሆኑ አልፎ አልፎ የሚያጋጥም ነው አንድ ቄስ ለማግባት ሲፈልግ ከወምበሩ ፈቃድ ማግኘት ይኖርበታል ከዚያም ከቄስ እድምተኞቹ ጋር በመሆን ወደ እጮኛው ቤት ይሄድና በሌሎች ቄሶች አማካይነት የቅዳሴ ሥነሥርዓት ከተካሄደ በኋላ ሙሽራዋን የሚያከብራትና የማይፈታት መሆኑን ቃለ መሐሳ ይፈጽማል ለሴቲቱ የካሣ ሥነሥርዓት ማካሄድ አስፈሳጊ ቢሆንም አግቢው ቄስ ግን ቀደም ብሎ ክህነት ሲቀበል ሥነሥርዓቱ የተካሄደለት ስለሆነ በድጋሚ የካሣ ሥነሥርዓት አያስፈልገውም በመሠረቱ አንድ ቄስ ሚስቱ ከሞተችበት ወምበሩን አስፈቅዶ ሌላ ማግባት አይከለከልም የመልኬና የከበቡሽ ጋብቻ የሃያ ዓመት ዕድሜ ያለው ወጣትና መልከ መልካሙ መልኬ ዛሬ የአሥር ዓመት ዕድሜ ያላትን ቆንጆና ዓይነ አፋር የሆነችውን ከበቡሽን የሚያገባበት ቀን ነው ከንጋት በኋላ ገና በማለዳው መልኬና ዕድምተኞቹ በነጫጭ ልብስ አሸብርቀው ወደ ከበቡሸ ወላጆች ቤት የሚያመራውን ጠመዝማዛ የእግር መንገድ ተያያዙት መልኬ ዘመድ አዝማድ በሆኑትና በሌሎች ከጋብቻው በፊት በተመረጡ ስምንት ሚዜዎች ታጅቦ ነበር ከዚያም መልኬና አድምተኞቹ ሸር ጉድ ከበዛበት የሙሸራይቱ መኖሪያ ቤት ደረሱ ከሦስት ቀን በፊት ትልቅ ዳስ ተጥሎ የድርቆሽ ሣርና የባሕር ዛፍ ቅጠል ጉዝጓዝ ለሠርገኞች ተነጥፏል በከበቡሽ ዘመዶች የሚጋገረው የትኩስ አንጀራ ሸታ ቅመማ ቅመም ከበዛበት ምራቅ ከሚያስውጠው የወጥ ሽታ ጋር በአንድ ላይ ተቀላቅሉ ኑ ብሉኝኑ ብሉኝ። » እያሉ ይጮሁ ነበር ለክርስቲያኖች ዕሑድ የተጀመረው ግብዣ ሰኞ ዕለት እንዳበቃ ረቡዕ ምሽት ላይ ደግሞ አረማዊኦሪታዊ ቅማንቶች ብቻ የሚካፈሉበት ድግስ ተጀመረ ስምንት ያህል ቄሶችና ሰማንያ ሌሎች ሰዎች ነበር የተገኙት አንዳንዶቹ በዚሀ በዓል ለመገኘት ለአንድ ቀን በእግራቸው ተጉዘዋል ወምበሩ ቀሳውስቱና በካሣ ሥነሥርዓት ያለፉ አዛውንቶች በተለይ ለዚህ በዓል ተብሎ በጨፈቃ በተሠራው ጉጆ ውስጥ በአንድ ላይ ሲሰበሰቡ ሌሎቹ ተራ ሰዎች ውጭ ሆነው ይጠባበቁ ነበር ከቀሳውስቱ ጸሎትና ቅዳሴ በኋላ ግብዣው ቀጠለ በጐጉጆው ውስጥ ላሉት ምግባቸው በተለይ የሚዘጋጀው ከደጃፍ ላይ ነበር ከጐጆው መሐል ላይ የተባረከው ጠላ የተሞላባቸው ሽክናዎች ተራ ሰዎች እንዳያዩዋቸው በትንሽ መጋረጃ ቢጤ ተከልለለው ተደርድረዋል የተባረከውን ጠላ በተለይ በጠባቂነት የተመደበው ሰው በጐጆው ለታደሙት እንግዶች ያድል ነበር በማግሥቱ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ጀምሮ ሁለተኛው የቃሥነ ሥርዓቱ ክፍል ተጠለ ከአራት ማኅበረሰቦች ደብር የተውጣጡ ስምንት ቴሶቸ በወምበሩ እየተመሩ ሥርዓተ በጭልጋው ወምበር አባት ተዝካር ሕዝቡ በግብዣ ላይ እንዳለ ጸሎትና መዝሙር አሰሙ በጸሎቱ ላይ ስለቅማንት ኀብረተሰቦች ደኅንነት ስለማሚች ነፍስ የምዝግናን የክብርዋንና የጽሳተሙሴን ስም በማንሣት ጸሉት ያደርጉ ነበር ጸሉቱ እንዳበቃ ፊታቸውን ወደ ምሥራት በማዞርና አጃቸውን በማንሳት ወደታት ዝተ ብለው በመውረድ መሬቱን ሳሙ ከዚያም በዚያው አጠገብ በሚገነ አንድ የመስዋዕት ማቅረቢያ ቦታ ለከፍተኛው ቴስ አንድ የሚያገሣ በሬና ሦስት በጉች ቀርበውለት አነስተኛ ቄሶች የእንስሶችን እግሮች ጠፍረው እየያዙለት አረዳቸው ድግሱ ቀኑን ሙሉ ውሉ እስከ ማግስቱ አኩለ ተቀን በቆየበት ጊዜ ጋሉን ጠላና ጋሎን ጠጅ ተጠጣ በብዙ መትዎች የሚቆጠሩ እንጀራዎች በሥጋ ወጥ ተበልተው አለቁ ምሸት ላይ አነስተኛ የወረባ ሥነሥርዓት ነበር ወሠረባው አንድ ቄስ አየተመራ ቄሶቹ ልዩ የሆነውን ዝማሬያቸውን ያሰሙ ነበር ሁለት ቄሶች በሦስት ሜትር ተራርቀው በቀስታ እንቅስቃሴ ዙሪያውን በመሽከርከር መዘመር ተጠሉ ቄሶቹ አየደጋገሙ የአንዷን የተከበረች አሮጊት ስም በዜማ ሲያነሥሠ ሴትዮዋ ተነስታ በዘፈኑ ተቀላቀለቻቸው ከዚያም ሌሉች አሮጊት ሴቶች ተራ በተራ አየዘፈኑ ሲጨርሱ ፊታቸውን በመጋረጃ ወደተጋረደው የተባረከ ጠበል አዙረው እጅ በመንሳት ይቀመጡ ነበር ሥነሥርዓቱ ሲያልቅ የተባረከው ጠጅ ታደለ ሌላው ሕዝብና ቀሳውስቱ ሌሊቱን በሙሉ እያወጉ ሲበሉና ሲጠጡ አድረው ተጨማሪ ሌሳ ሥነሥርዓት ባይኖርም በማግሥቱ የመዝናናቱ ጉዳይ ቀጠለ በመጨረሻም የመሰነባበቻ ምልክት መስጫ የሆነው በጋኖች ውስጥ የነበረው አተላ ሲደፋ ሕዝቡ ጃልሻቭን በመልቀቅ ከሰዓት በኋላና በምሸት ወደየቀየው ተመለሰ ቄሶች የግለሰቦችን ሁለተኛውን የሙት ዓመት ለማስታወስ በተጨማሪ «ዓመታት» ተብሉ የሚታወቀውን የቅዳሴ ሥነሥርዓትም ያካሂዳሉ ይህ ሁኔታ በየዓመቱ የሟች አስከሬን ባረፈበት ድግና ለብዙ አሥርተ ዓመታት የሚቀጥል ይሆናል የእግዚአብሔርን ትዕዛዛትና የቅማንትን ሥነምግባር ሕግጋት ጠ ብቀው ሕይወታቸውን ያለፋትን ትውልዶች ለማስታወስ የሚደረግ ሥነሥርዓት መሆኑን እንገነዘባለን ምዕራፍ አሥር ባህላዋ ለውጥና ቅማንት የመጨረሻ በሆነው በዚህ ርዕስ የቅማንት ሃይማኖትና ከዚሁ ጋር የተሳሰረውና ተነጥሎ ሊታይ የማይችለው የባህል ድንበር መቆጣጠሪያ ስልታቸው በአማራው ባህል ውሕደት አምሃራይዜሽን ሂደት የተጫወቱትን ሚና እንዳሰሳለን የቅማንት ኀብረተሰብ የድንበር መቆጣጠሪያ ስልት የአካባቢው ማኀኅበራዊ ባህላዊ ነፀብራቅና ውርስ ባሕርይ ነው ሊባል ይችላል በመሆኑም ምንም እንኳን ቅማንቶች የበላይነት በነበረው በአማራው ሕዝብ ተከበው የኖሩ ቢሆንም ቴክኖሎጂና መለኮታዊ እምነቶች ለሕይወት አስፈላጊ የሆኑትን ነገሮች ከማጣትና ተለዋዋጭና አስተማማኝ ካልሆነው መልክአምድራዊ ተዕዕኖዎች ከሚመነጩ ሥጋቶች ጠብቀዋቸው አንዳቆዩአቸው ሁሉ ይህ ባህሳዊ ውርስም ሁሉን ዓይነት ችግሮች ተቋቁሞ ባህላቸው ሳይበረዝ ማንነታቸው ተጠበቆ እንዲቆይ ረድቷቸው ነበር ሆኖም በመጨረሻ የአማራን ባህል መቀበል ግዴታ እየሆነ በመምጣቱ የቅማንት ማኅበረሰብና ባህሉ እየቀረ መጥቷል ለውጥን ሲከላከል የነበረው የባሕል ድንበር አጥር እያላቸው ለምን የቅማንትነት መለያቸውና የኑሮ ዘይቤአቸው በከፍተኛ ፍጥነት አየተለወጠ እንደመጣ እንመረምራለን እዚህ ላይ በተጨማሪ መነሣት የሚገባው ነገር ቢኖር የቅማንት ባህላዊ ለውጥ ለምን የምዕራባዊያንን የፈረንጆችን ፈለግ እንዳልተከተለና በመጨረሻም የአማራው ባህል በቅማንቱ ሳይ ብቻ ሳይሆን በአጠ ቃላይ በሌሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦችም ላይ የአስከተለውን ተፅዕኖ እናያለን የቅማንት የአማራን ባህል በመቀበል በባህል ለውጥ ወደ አማራነት የመለወጡ አምሃራይዜሽን ሂደት በሦስት ደረጃዎች ተከፍሎ ሊታይ ይችላል የመጀመሪያው ከፍተኛውና የመጨረሻው በማለት ተለይተዋል የአማራን ባህል የመቀበል ሂደት በዝርዝር ከመታየቱ በፊት ስለሂደቱ አጭር የሆነ አጠቃላይ መግለጫ መስጠት አስፈላጊ ይሆናል የመጀመሪያው የአማራ ባህል በሌሎች ሕዝቦች ላይ ለዘብ ባለ መልኩ ተቀባይነት ማግኘት የጀመረው አማራው የኢትዮጵያን የመንግሥት ሥልሣን እኤአ ከ ዓም ጀምሮ ሲረከብ ነበር ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ቅማንቶች ከአማራው ጋር ቀጥታ ግንኙነት የነበራቸው ቢሆንም የራሳቸው የሆነውን ማኀበራዊ መታወቂያቸውን ይዘው በመጓዛቸው የአማራን ባህል የመቀበሉ ሁኔታ ዘገምተኛ ነበር የአማራን ባህል የመቀበሉ ሂደት በዝቅተኛና በአዝጋሚ ደረጃ ላይ የነበረ ቢሆንም አፄ ዮሐንስ አራተኛ የተለያዩ ብሔረሰቦችን በአንድ ላይ አሰባስቦ አንድ ጠንካራ የኢትዮጵያ መንግሥት ለማቋቋምና ከውጭ የሚመጣን ጠላት በጦር ሃይል ለመመከት እንዲረዳቸው አስበው በማስገደድ ክርስቲያን እንዲሆኑ የማድረጉን ኘሮግራም ሲያወጡ አዝጋሚነቱ ቀርቶ ሂደቱ ተፋጠ ነ ስለሆነም ቅማንት የክርስትናን ሃይማኖትን ተቀብሎ አማራ የማድረጉ ሂደት ከፍተኛው እመርታ ላይ ደረሰ ንጉሠ ነገሥቱ ለዘመናት የቆየውን አረማዊኦሪታዊ ሃይማኖት ተጠብቆ እንዲቆይ ያደረገውን የማኅበራዊ ድንበር አጥር በማያዳግም ሁኔታ አንዳልነበረ በማድረጋቸው በቅማንት ላይ የደረሰው ባህሳዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ካሉት ብሄረሰቦች ላይ ከተደረገው ተፅዕኖ ሁሉ የከበደ ነበር ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላም በግዴታ አማራ የማድረጉ ሁኔታ አንደገና አገርሽቶ በቅማንት ማኀበራዊና ባህላዊ ሥርዓት ላይ የተፅዕኖ እርምጃ በመውሰዱ የአማራን ባህል እንዲቀበሉና በባሕል ለውጥ አማራ እንዲሆኑ የመጨረሻው የእንቅስቃሴ ክፍል ነው እንላለን የመጀመሪያው ወደአማራነት የመለወጥ ሂደትና ሕብረብሔራዊ መቻቻል በአማራው ሕዝብ የተከበቡት የቅማንትና የሌሎች አገው አካባቢዎች ከአማራው ባሕል ጋር መተዋወቅ የጀመሩት ገና «የመጀመሪያው አማራ» ኘሮቶአምሃራ እኤአ በ ዓም አካባቢ የተከዜን ወንዘ ተሻግሮ በስተደቡብ ካለው የአገው ሕዝቦች ጋር ግንኙነት ሲፈጥር ነበር ቀደም ብሎ በምዕራፍ ሁለት እንደተገነዘብነው የአማራው ሕዝብ ባህል እየተጠናከረና የአገው ሕዝብ ብዛት እየቀነሰ በመምጣቱ ሁኑታው አስቀድሞ እንደነበረው የባህል መቀላቀል መዳቀል መሆኑ ቀርቶ ቀስ በቀስ የአማራው ናክ የሎን ባህል እየዋጠ ጠቅላላ የባህል ውሕደት እየሆነ መጣ «አማራ የመሆን ሂደት አምሃራይዜሽን እያልን የምንጠ ር የባሕል ውሕደት በሌሉች በርካታ አገዎች ዘንድ በኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ ነበር የተጠናቀቀው በተወሰኑ አንዳንድ አካባቢዎች በባህል ለውጥ አማራ የማድረጉ እንቅስቃሴ ዘገምተኛ ስለነበር አንዳንድ የአገው ጐሣዎች አማራ በሆነው ሕዝብ ተከበው ልዩ የሆነውን ባህላቸውን በአካባቢያቸው ጠብቀው ለመኖር ችለዋል በዚህ ሁኔታ አገዎችና ጐረቤቶቻቸው የሆነው አማራው በአካባቢያቸው የተረጋጋና መቻቻል የሰፈነበት ሕብረማኀበረሰብ ፈጥረው መኖር ቀጠሉ የባህል ውሕደቱ ሂደት ፍጥነት አንዱ ከሌላው የተለየበት ልዩ ልዩ ምክንያቶች ነበሩ የስሜንና የላስታን ሁኔታ የተመለከትን እንደሆነ አካባቢዎቹ ተራራማና ጉራንጉር ስለሚበዛባቸው የአማራን ባህል በማሰራጨቱ ረገድ ከፍተኛ ተፅዕኖ ነበረው በቋራ አካባቢ የሚገኙት አገዎች ደግሞ ከአማራው የሥልጣን ማዕከል እርቀው ይኖሩ ስለነበር ባህላቸውን እንደያዙ ለረዥም ጊዜ ለመቆየት ችለዋል በሌላ በኩል ለምሳሌ በስሜን በላስታ በአገው ምድር የሚገኙ አገዎች በመልክአምድሩ በመጠቀም አብዛኛውን ጊዜ በጦር ሃይል በመቋቋም ለዘመናት ባህላቸው በአማራው ባህል የመለወጡን ሂዳት ገትተውት ቆይተዋል የአገው ሕዝብ በሰፊው በውሕደት አማራ የመሆኑን ሂደት ከመያያዙ በፊት የቅማንቶች አረማዊኦሪታዊ የሆነው ሃይማኖታቸው በአነሰ መልኩ አረማዊ በበለጠ መልኩ ደግሞ ኦሪታዊ ከሆኑት በጠሳትነት ከሚተያዩት ሌሎች አገዎች ልዩ ያደርጋቸው ስለነበር ቅማንቶት የራሳቸው የሆነውን የመቆጣጠሪያ ስልት በመቀየሰ ይበልጥ ኦሪታዊ በሆነው ባህል ሳይዋጡ ቆይተዋል ይህ ባይሆን ኖሮ ተመሳሳይ ሕዝብ እንደመሆናቸው አካባቢያቸውም ኩታገጠም እንደመሆኑና ሌሎች አገዎችም በሕዝብ ብዛት ስለሚበልጡ የባህሉ ውሕደት ቀላል በሆነ ነበር ከዚህም በስተቀር በተመሳሳይ ሁኔታ የባህል መዳቀል መቀላቀል መቆጣጠሪያ ስልታቸው እያደገና እየዳበረ በመምጣቱ ዙሪያውን ከቦአቸው የነበረውን የአማራውን የባሕል ተፅዕኖ ፈጣን አንቅስቅሴ ለመግታት አስችሏቸዋል በመሆኑም የአማራውና የቅማንቱ ባህሎች በመቻቻል የተረጋጋ ኅብረማኀበረሰብ መቻቻል ሠፍኖ እንዲቆይ በመርዳቱ ቅማንቶች ባህላዊ ሕልውናቸውን ከሊሌሉች የአገው ጉሣዎች በተለየ መልክ ጠብተው ለመኖር በቅተዋል ምንም እንኳን አገዎች በየጊዜው ከፍተኛ ተቃውሞ ቢያሳዩም እንዲሁም ወደኋላ የሚጉትቱ የተለያየ ምክንያቶች ቢያጋጥሙም ፈረንጆች አውሮጳውያን ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣታቸው እኢአ ከ ዓም በፊት በነበሩት ምዕተ ዓመታት በባህል ለውጥ ወደ አማራነት የመለወጣቸው ሂደት በጣም በሰፊው ቀጥሎ ነበር የቅማንት ሕዝብ በአማራው የፖለቲካ አገዛዝ ሥር መቼ እንደወደቀ በትክክል ባይታወቅም ምናልባት በቅማንቶች መሬት አገር ላይ የተቆረቁረትውና እራሳቸውም በማንኛውም ረገድ ይደግፏት የነበረችው የአማራው መንግሥት ቋሚ መናገሻ ከተማ የነበረችው ጉንደር በዎቹ ዓም ስትመሠረት በመጀመሪያዎቹ ዓመታት ሳይሆን አይተርም ቅማንቶች ነበሩ በሰው ኃይል በእርሻ ውጤቶችና በማገዶ ረገድ የጐንደር ከተማን ቀጥ አድርገው ይዘዋት የነበረው በተለይ ማገዶ አትራቢ በጉንደር ከተማ አካባቢ ባይኖር ኖሮ ሌሉች የኢትዮጵያ ከተሞች እየተመሠረቱ እንደጠፉት ሁሉ የጉንደርም ዕጣ ፋንታ ይኸው ነበር የሚሆነው እንደ አብዛኛዎቹ የአገው ጉሣዎች ቅማንቶች ብዙም አማራውን በኃይል ለመቋቋም ባለመሞከራቸው በሠላም እንዲኖሩ ተትተወ ነበር የቅማንቶችን አፈታሪኮችና የአማራውን መዋዕለ ዜናዎች ስንመረምር በሁለቱ ሕዝቦች መካከል ምንም ዓይነት ግጭት አንዳልነበረ ነገር ግን በአማራውና በሌሎች አገዎች መካከል ጦርነቶች እንደተካሄዱ ይገልጻሉ ቅማንቶች በሠላም መኖርን መርጠው ግብር ብቻ እየገበሩ አርፈው በመቀመጣቸው አማራው የአገዛዙን ሥርዓት በመዘርጋት የቅማንቱን ፖለቲካዋና ሃይማኖታዊ ሥርዓት መደምሰስ አስፈላጊ ሆኖ አላገኘውም ቅማንቶች በአማራው ሥር በሠላም መኖርን የመረጡበትን ምክንያት ስንመረምረው በአካባቢያቸው የቅማንት ጠላት ናቸው ብለው የፈረጁአቸው በአብዛኛው ኦሪታዊ የሆኑ አገዎች እንዳይተናኮሉአቸው አማራውን አጋር ለማድረግ ታስቦ እንደሆነ ከአፈታሪካቸው እንገነዘባለን ከዚህም በስተቀር ቅማንቶች እንደ ሌሎች አገዎች አክራሪ ኦሪታውያን ባለመሆናቸውና ሠላማዊ ሆነው በመገኘታቸው በአማራው ከመደምሰስ ተርፈዋል በአጭሩ ወታደራዊ ኃይል ማኀበራዊ አደረጃጀትና ቴክኖሎጂ እንደ ፈላሻ የመሳሰሉትን የአገው ቅርንጫፎችን ሕልውና አስከብሮ ሊያቆያቸው ባለመቻሉ በአማራው ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በጦርነት ተደምስሰው በአሁኑ ጊዜ በሰሜን ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ተበታትነው እንዲኖሩ ሲገደዱ ቅማንቶች ሠላምን የመምረጡ ሁኑታ ካላቸው ከፍተኛ ሃይማኖታዊ ሥነምግባር ጋር ተዳምሮ የጐሣው ሕልውና በሚገባ ተጠብቆ እነዲቆይ ረድቷል። በማኀበራዊና በፓለቲካ አደረጃጀት ረገድ በአማራው ባላባታዊ አገዛዝ ሥርዓት ሥር ሆነው ከፊል የራስገዝነት መብት የነበራቸው ከመሆኑም በላይ በባህላዊ ሥነሥርዓት በኩል ሙሉ በሙሉ ነፃ በመሆናቸው አስፈላጊ ያልሆነ የተለየ ባህል ወደራሳቸው ማኀበራዊና ባህላዊ ሥርዓት ሠርጐ እንዳይገባ ለመከላከል አስችሏቸው ነበር እዚህ ላይ መገንዘብ የሚያስፈልገን የቅማንቱ ኀብረተሰብ ከአማራው ጋር በበጐ ፈቃደኛነት የፖለቲካና የኤኮኖሚ ግንኙነት ባይመሠረት ኖሮ ቀደም ብሎ የአማራን ባህል በግድ የመቀበሉ ሁኔታ የማይቀር እንደነበር ነው በፍላጐት ተቀባይነት ካገኙት የአማራ ባህል መካከል ቴክኖሎጂ ነክ ነበሩ እንደሚታወቀው ሁሉ ቢያዝነው ሁለተኛው ሺ ዘመን ቀደም ብሎ በነበሩት ክፍለ ዘመናት ጥንታዊ የሆነውን የራሳቸው የነበረውን የጓሮ አታክልት እርሻ አስተራረስ ዘዴ በመተው የአማራውን የተሻለ የአርሻ ዘዴ መውረሳቸው ይታወቃል የሕብረ ማኀበረሰቦች ተረጋግቶ መኖር ውሕደትን ለጊዜው የሚገታ እንጂ ጨርሶ በርን መዝጋት ስላልሆነ የቅማንት የባህል ድንበር የመቆጣጠሪያ ስልቶችን እያለፉ ቴክኖሎጂነክ ያልሆኑ አንዳንድ የአማራ ባህሎችም በቅማንቶች ዘንድ ተቀባይነት ሳያገኙ አልቀሩም ይህም በመሆኑ አንዳንድ በክርስትና ሃይማኖት ውስጥ ያሉ መሠረታዊ ዕምነቶችን ወይም ባህሎችን ወደራሳቸው ወስደው ሲጠቀሙባቸው ቆይተዋል ለምሳሌ በኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ የቅማንት የግል መጠሪያ ስሞችን በመተው የአማራ መጠሪያ ስሞችን መጠተም ጀምረዋል ለረዥም ጊዜ በቆየው የመጀመሪያው የአማራ ባህል የመቀበሉ ሂደት በፈጣን የባህል ውሕደት እንዲተካ ለማድረግ ያስችል የነበረው ብቸኛ አማራጭ የቅማንቱን ሃይማኖትና አብረው የተሳሰሩትን የባህል ድንበር መቆጣጠሪያ ስልቶችን በማስወገድ ይሆን ነበር እንዲሁም በአማራውና በቅማንቱ የአካባቢ ማኀበራዊና ባህላዊ የመቻቻል ግንኙነት ምክንያት በማዝገም ይካሄድ የነበረው ውሕደትም በዚሁ መልክ ለብዙ ዘመናት ሊቀጥል በቻለ ነበር ሆኖም አዲስ የሆኑ ለውጥ ሃስከተል የሚችሉ የውጭ ሁኔታዎች በመካከሉ ስለተከሰቱ ሊሆን አልቻለም ከፍተኛው የባህል ለውጥ ሂደትና የማኀበራዊ ድንበር የመቆጣጠሪያ ስልቶች መፈረካከስ የመጀመሪያው የቅማንት የአማራን ባህል ተቀብሎ በውሕደት አማራ የማድረጉ አንትስቃሴ ከቅማንቶትች መካከል ቅርብና ታማኝ የሆኑ ባለሟል በነበሯቸው በአፄ ቴዎድሮስ ኛ ዘመነ መንግሥት እኤአ ከ እስከ ቀጥሎ ነበር አሁንም ቢሆን ቅማንቶች አፄ ቴዎድሮስን ብዙ ጊዜ እንደረዷቸውና በአፀፋውም አፄው ብዙ ደግና በጐ ነገሮችን እንዳደረጉላቸው የሚናገሩት በርካታ ታሪኮች አሏቸው ከአሳቸው ቀጥሎ ግን የክርስቲያን አክራሪ መሪ የነበሩት አፄ ዮሐንስ አራተኛ የቅማንትን ሃይማኖታዊ ሥርዓት በከፊል በማፈራረስ ቅማንቱ ሙሉ በሙሉ የአማራን ባህል እንዲቀበል የማኀበራዊና የባህላዊ በሩን ከፈቱት በአፄ ዮሐንስ አራተኛ ዘመነ መንግሥት የኢትዮጵያ ነፃነት በግብፆች በሱዳን ማኅዲስቶችና ድርቡሾች በአውሮጳ ቅኝ ገዥዎች በተለይም በጣሊያን ወረራ ምክንያት አደጋ ላይ ሊወድቅ ተቃርቦ ነበር ከበባ ሲያደርጉ የነበሩት ኃይሎች ሕዝቡን በመከፋፈል የእስልምና ሃይማኖት ያላቸውን ኢትዮጵያውያን ድጋፍ ለማግኘት የሚያደርጉትን ጥረት ለማክሸፍ አፄ ዮሐንስ በተለያዩ ሃይማኖት የተከፋፈሉትን ኢትዮጵያውያን አንድ አድርጉ ለመግዛት ተነሣሥ ሠራዊታቸውን ዘመናዊ የጦር መሣሪያ በማስታጠቅ እስላሞች አረማዊኦሪታዊ ቅማንቶች ኦሪታዊ ፈላሻዎችንና የሙስሊምአረማዊ ወይጦዎችን በአዋጅና በኃይል የክርስትናን ሃይማኖት እንዲከተሉ ማስገደዱን ተያያዙት አስገድዶ የማጥመቁ ተግባር በቅማንቶች ላይ ውጤታማ በመሆኑ የአማራውን ባህል የመቀበሉ ሂደት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ ነበር እስላሞችና ፈላሻዎች በዚያን ጊዜ በጣም ብዛት የነበራቸውና በተለያዩ አካባቢዎች ይናሩ ስለነበር ተፅዕኖው ይህን ያህል ከባድ አልነበረም ቅማንትች ግን ቁጥራቸው አነስተኛና በአንድ አካባቢ ተሰብስበው ይናሩ ስለነበር የአማራው ማዕከል ከሆነትውም የጐንደር ከተማ አጠገብ በመሆናቸውና የመሬት ባለመብትም ስለነበሩ በአማራው በኩል በቀላሉ ጥቃት ሊሰነዘርባቸው አንደሚችል ለመገመት አያዳግትም የፈሩት አልቀረም አንዳንዶቹ ቅማንቶች በመሣሪያ በመገደዳቸው ከፊሉቹ ደግሞ መሬታቸውን ሊነጠቁ በመሆኑ በክርስትያንነት ተጠምቆ የአማራን ባህል ከመቀበል በስተቀር ሌሳ አማራጭ አልነበራቸውም አፄ ዮሐንስም የክርስትና ሃይማኖትን የተቀበሉትን ከግብር ነፃ በማድረግ ያበረታቷቸው ነበር በሌላ በኩል ደግሞ የሃይማኖት ለውጡን ለማመቻቸት በከርከር የሚገኘውን የቅማንቶች ሃይማኖታዊ መሪ ማዕከል በማስነሣትና ድሮ ጦምበሩ የነበረውን ግብር የመሰብሰብ ሥልጣን በመግፈፍ ግብር ስብሰባው በባላባታዊው እገዛዝ የመሬት ሥሪት እንዲወድቅ አደረጉት ይህ በመሬት ሳቢያ እያስፈራሩ ክርስትናን የማስፋፋቱ ጉዳይ በቅማንቶች ላይ ተግባራዊ ቢሆንም ሥረመሠረት በሌላቸው ፈላሻዎች አዳኝ ወይጦዎችና እስላሞች ሁሉም መሬት አልባ ስለነበሩ በሚገባ ተግባራዊ አልሆነም ከዚያም ደርቭሾች አፄ ዮሐንስን በ ዓም ገድለው በቅማንት አካባቢና በጐንደር የሟገኙትን አብያተክርስቲያናት በማቃጠላቸውና በማፈራረሳቸው ቅማንትን ወደ ክርስትና ሃይማኖት የመለወጡ ሂደት እየቀዘቀዘ መጣ በዚየን ጊዜ ብዙ ቅማንቶች ወደነበሩበት እምነት ቢመለሱም በርካታ በከርከር የሚገኙ ቅማንቶች መሬታቸው በጉልበት ተይዞ የጭሰኛ ግብር እንዳይጣልባቸው ክርስቲያን ሆነው መቆየትን መረጡ ወደክርስቲያንነት በመለወጣቸው ምክንያት የቀድሞው ሥርዓት በመፈራረሱ በምሥራቅ ይገኙ የነበሩ ቅማንቶች ለከርከር ወምበር ይገብሩ የነበረው ግብር ተቋረጠ በጭልጋ የነበሩ ቅማንቶች ግን የክርስትና ሃይማኖትን እንዲቀበሉ ብዙም የኃይል አስገዳጅ ሁኔታ ስላላጋጠማቸው እኤአ እስከ ዓም ድረስ ለወምበሩ ሲገብሩ ቆይተዋል የተጠመቁቅማንቶች ወደ ገነት እንዳይገቡ ወምበሩ ለምን አላወገዘም ተብሎ መጠየቁ አይቀርም ሁለት ምክንያቶች ነበሩ አንደኛው ምክንያት ጥንታዊ ወምበሮች እንደጠቆሙት የተጠመቁ ሰዎች ከባድ መቅስፍት እንደሚደርስባቸው በአፈታሪካቸው አስቀድሞ የተነገረ በመሆኑ ሲሆን በሁኔታው የተደናገጡ ገጠ ሬዎችም ይህን ሁኔታ ለአማራው የክርስቲያን ሹም ሲገልፁ ደግሞ ሹሙ በአረማዊኦሪታዊ ሃይማኖት ተከታዮችና ይህን እርግማን በተናገሩት ላይ እርግጠኛ የሆነ መቅሰፍት እንደሚደርስ በመስበኩ ግራ በመጋባታቸው ሲሆን ሁለተኛው ምክንያት ደግምሞ የእነሱ ምዝግና እና የክርስቲያን እግዚአብሔር አንድ መሆናቸውን ቀስ በቀስ በማመናቸው ነበር ሌሎች የቅማንት መላአክት ከሊሉች የክርስቲያን ቅዱሳን ጋር ተመሳሳይነታቸውን መቀበሉም ለዕምነት ለውጡ አስተዋፅኦ አድርጓልከሁሉም በላይ ደግሞ የቅማንትንም ሆነ የክርስቲያን ሃይማኖትን ቢከተሉ ሁለቱም መንገዶች ጥሩ ወደሆነችው ሰማያዊ ገነት መንገድ የሚያመራ መሆኑን በመቀበላቸው ነበር አስገድዶ የባህል ለውጥን እንዲቀበሉ የማድረጉ ጉዳይ የቅማንትን ሃይማኖታዊ ድርጅት ጨርሶ ባያጠፋውም እንደ መሠረት ድንጋይ የጠነከረውን የባህል የድንበር አጥር ግን በሚገባ በማነቃነቅ አንገዳግዶት ነበር ምንም እንኳን ከአረማዊ ኦሪታዊው ሃይማኖት አስኳል ውጭ ቢሆኑም ክርስቲያን የሆኑት ቅማንቶች ቁጥር በርካታ ስለነበር በሥጋ ዝምድና እና በማኅበር ቃልኪዳን እንደተሳሰሩ ነበር አረማዊ ኦሪታዊ የሆኑ ቅማንቶችም ክርስቲያን ከሆኑ የሥጋ ዘመዶቻቸው ጋር የቅርብ ዕለታዊ ግንኙነት ስለነበራቸው ይህም ሁኔታ ከውጭው የክርስቲያን ዓለም ጋር ባለው ግንኙነት እንደ ድልድይ ሆኖ ያገለግል ጀመር ወደ ክርስቲያን የመለወጡ ሂደት የአረማዊ ኦሪታዊውን የቅማንት ኅብረተሰብ ማኀበራዊና ኤኦኖሚያዊ ተቋምን በማዳከሙ የደጋፊዎቻቸውንና የተከታዮቻቸውንም ቁጥር አመናመነው በሌላ በኩል ደግሞ መሪዎቻቸው የነበራቸው ሥልጣንና ክብር እየተሸረሸረ በመምጣቱ አንዳንድ የሃይማኖት የኃላፊነት ቦታዎችን የሚፈልጋቸው በመጥፋቱ ክፍት ሆነው መቅረት ጀመሩእነዚህ እርስ በርሳቸው የተያያዙ ሁኔታዎች ቅማንቶች የአማራን ባህል የመቀበሉን እንቅስቃሴ በጣም አፋጠነው ይህም በመሆኑ ለዘመናት የነበራቸው የባህል ነፃነትና የውስጥ የራስገዝ ሥልጣን በዎቹ ዓም ጀምሮ በአማራው አመራር እየተሸረሸረ መጣ የቅማንት ሃይማኖት በተግባር ላይ ሲታይ ከማኅበራዊና ከባህላዊ ዘርፎች ሥርዓት ጋር የተሳሰረ ስለነበር አረማዊ ኦሪታዊው የሆነው የቅማንት ዕምነት ሲተው በባህሉ ውስጥ የነበሩትን መሠረታዊ ነገሮችንና ትውፊቶችን መርሳት ግድ ሆነ መጠነኛ የሆነውን ክፍል ብቻ ወደ ልጁ በመተላለፉ ወደ ልጅ የልድ ልጅ ሲወርድ ሲዋረድ ደግሞ ጭራሹኑ እየጠሩ ሄደ። ባለ አንድ ዘርፍ የዘር ሐረግ አቆጣጠር እና አክራሪ ባሕርይ ከነበረው የጋብቻ ሥነሥርዓታቸው ጋር የተያያዘው ጥንድ ማኀበራዊ አደረጃጀት ተረሳ እንዲሁም ለቅማንት የፖለቲካና ሃይማኖታዊ አባቶች የነበረው ታማኝነት ተመናመነ ሴቶችን በወር አበባ ወቅታቸውና ልጅ በሚወልዱበት ጊዜ የማግለሉ ባህል ቀረ ሌሎች የጎረቤት ኀብረተሰብቦች የረከሱ ናቸው በማለት እንዳይቀላቀሏቸው የሚደረገው ክልከላም ተቋረጠ ከዚህም በስተቀር በአረማዊኦሪታዊ ሃይማኖት ሥነሥርዓት መሠረት ከአንዱ የሰውነት ደረጃ ወደ ሌላው ደረጃ ለመሸጋገር የሚደረገው ሥርዓተጸሉት የአንድነታቸው ጥንካሬ መሠረት የነበረ ሲሆን ይህም ወደ እያንዳንዱ ኀብረተሰብ ውስጥ ሊሠርፅ አልቻለም ከዚህ ቀጥሎ ለምን በርካታ ቅማንቶች በፍጥነት የአማራን ባህል በመቀበል አማራ እንደሆኑ እናያለን ለዚህ ጥያቄ መልሱን ለማግኘት አስቀድሞ ተመሳሳይ የሆኑ ባህላዊ መለያ ባሕርያት ለለውጥ ያላቸውን ዝግጁነትና ዝንባሌ መረዳት ያስፈልጋል የባህል ውህደት ሊከሰት የሚችለው ተመሳሳይ የሆኑ መሠረታዊ የባህል መለያ ባሕርይ ሲኖሩ መለያ የሆኑት ባሕርይ ከነባሩ ባህል ጋር ተሳስረውና ተዋህደው በአንድ ዓይነት የባህል ዘርፍ ሊፈረጁ ሲችሉ እና ከነባሩ የባህል መለያ ባሕርይ ጋር የማይጋጩ ወይም ሁኔታውን ጨርሶ የማያኮላሹ ሆነው ሲገኙ ነው በቅማንት ባህል ውስጥ የነበሩ ብዙ ጥንታዊ የአገው ባህሳዊ ትውፊት ከአማራው ባህል ጋር ሥረመሠረታቸው አንድ የነበረ በመሆኑና የሚጣጣሙ ሆነው በመገኘታቸው በአማራው አቻ ባህላዊ መለያ ባሕርይ በቀላሉ ሊተኩ ችለዋል ዝርዝሩ በምዕራፍ ሁለት ይገኛል የመጀመሪያው የኃይል ተፅዕኖ አንድ ጊዜ ከተደረገ ወዲህ መሠረታዊ የሆነው የማኀበራዊ ድንበር የመቆጣጠሪያ ስልቶች ስለተሰበሩ አቻ የሆኑ በተመሳሳይ ባህል የሚፈረጁ የሁለቱም ሕዝቦች የባህል ትውፊቶች ስለነበሩ የቅማንቱ ባህል በአማራው ተውጦ ውህደት ሊፈጠር ችሏል በአገውና በአማራው በነበረው ግንኙነት ምክንያት በአንድ በኩል አንዱ የበላይ የሆነ ባህል ቦለነበረው በሌላ በኩል ደግሞ የሁለቱም ባህ ሉች ተመሳሳይነት ስለነበራቸው ውህደቱ እንደተከሰተ ዓይነተኛ ምሳሌ ነው ይህም ዓይነት የማመዛዘን ጉዳይ አረማዊኦሪታዊ ቅዱሳንን ከክርስቲያን ቅዱሳን ጋር ከሚያመሳስለብት ሁኔታ ጋር የተለየ አይደለም አፄ ዮሐንስ ያወጡትን ትዕዛዝአዘል የባህል ለውጥ ኘሮግራም ከእሳቸው ወዲህ የመጡት ነገሥታት ትኩረት ባይሰ ጡትም ቅማንቶች የአማራውን ባህል የመተበሉን ሁኔታ ቀጥለውበታል የባህል ለውጡ ሂደት ቀደም ብሉ በባህል ድንበር የመቆጣጠሪያ ስልት ተገትቶ ከነበረበት ከመጀመሪያው አማራ የመሆን ሂደት በተፋጠነ መልክ በአሁኑ ጊዜ በጣም እየተጣደፈ ነው እኤአ በዎቹ አብዛኛው ቅማንት ባህሉንና የማኅበረሰቡን ሥርዓት እንደያዘ ቢቆይም ወደ ክርስቲያንነት የመለወጡ ሂደት በተጠናከረ መልክ ቀጠለ በዚያን ጊዜ በምሥራቅ ቅማንት በከርከር የሚገኙት ቅማንቶች በግምት ግማሹ ክርስትናን ተቀብለው ነበር ማለት ይቻላል ከቅማንቱ ሃይማኖትና ባህል ሙሉ በሙሉ ባልተላቀቁት በአዲሶቹ የክርስቲያን ሃይማኖት ተከታዮች እየተረዳ አሮጌው ሥርዓት እየተንገዳገደ ቆይቶ ነበር ምንም እንኳን ያልተጠመቁት ቅማንቶች ከክርስቲያኖች ጋር በአንድ ሳይ ተቀላቅለው የቅዳሴ ሥነሥርዓቶችን ባያካሂዱም ክርስቲያኖቹ ገንዘብ ማዋጣቱንና በክብረበዓሎች መገኘቱን አልተውም ዛሬም ቢሆን ይህ ዓይነቱ ሁኔታ በጭልጋ ባሉት ኅብረተሰቦች ዘንድ እንደ ቀጠለ ነው በተለይ የተለያዩ ጭንቀቶችን ለማስወገድ ወይም አካባቢያዊ ችግሮችን ለመቆጣጠር ሲፈልጉ ቅማንቶች እንደገና ወደ አሮጌው ሃይማኖታቸው ተመልሰው ልዩ ሥነሥርዓታቸውን ቢያካሂዱ ከአማራው ጋር በአንዳንድ ሁኔታዎች ተመሳሳይነት ስለነበረው በአማራው በኩል የጠነከረ ተቃውሞ አይደርስባቸውም ነበር ይህም ሊሆን የቻለው የአማራው የክርስትና ሃይማኖት አንዳንድ ጠንካራና መሠረታዊ የሆኑ አረማዊኦሪታዊ እምነቶችን በውስጡ በማስታረቅ ያካተተ በመሆኑ ሳይሆን አልቀረም ከጣልያን ወረራ ወዲህ እኤአ ከ ዓም ጀምሮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሁለተኛውን የሃይማኖት ማስፋፋት ዕቅድ ዘረጋች የዚህ ዘመቻ ዋና ዓላማ በጉሣ የተከፋፈለችውን ኢትዮጵያን አንድ ለማድረግና በየጊዜው ሠርገው የሚገቡትን የውጭ ይሉችን ለመቋቋም እንዲያስችል ታስቦ ነበር በዚህም መሠረት ያልተጠመቁ ቅማንቶች ርስታቸውን እንደሚነጠቁ ማስጠንቀቂያ ይደርሳቸው ጀመር ይህ ኘሮግራም ቅማንቶችን ብቻ ሳይሆን ሌሉች በማዕከላዊ ምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኙትን አናሳ ጉሣዎችንም ጭምር ይመለከት ነበር በዚያን ጊዜ እነዚህ ጐሣዎች አብዛኛዎቹ የክርስትናን ሃይማኖት ከሞላ ጐደል የተቀበሉ ቢሆንም የአማራው ባህል ግን ሙሉ በሙሉ በውስጣቸው አልሠረፀም ነበር በዚያን ዘመን ነበር አንድ አክራሪ ሰባኪና አጥማቂ ተነሳስቶ ሁሉም ቅማንት መጠመቅ እንዳለበት በመስበኩና የተፅዕኖ እርምጃም በመውሰዱ የቅማንት በባህል ለውጥ አማራ የመሆን ሂደት ከከፍተኛው የዕድገት ደረጃ ላይ ደርሶ ወደ ፍጻሜው ደረጃ የተሸጋገረው የፍጻሜው አማራ የመሆን አምሃራይዜሽን ሂደት የቅማንት የአማራን ባህል የመቀበሉ ሂደት የመጨረሻው ደረጃ አሁንም ቀጥሎ እኤአ በዎቹ ዓም እርምጃው ተፋጠነ በእነዚህ ዘመናት ሳይጠመቁ የቀሩት ቅማንቶች ከአንድ ሺህ በላይ አይሆኑም ነበር በኃይልም ሆነ መሬታቸውን በመንጠ ቅና ጭሰኛ በማድረግ ክርስትናን እንዲቀበሉ አስገዳጅ ሁኔታዎች ቢፈጠሩም በግትርነትና በአክራሪነት እምቢተኛ የሆኑት የቅማንት የሃይማኖት መሪዎች የሚመረጡባቸው የክብርና የየታንቲ የዘር ሕረግ አባላት በእምነታቸው ፀንተው ቆዩ በመጨረሻም እነዚህ ኅብረተሰቦች ለኢትዮጵያ መንግሥት ችግራቸውን አመልክተው ጥያቄአቸው በመንግሥት በኩል ተቀባይነት ስላገኘ ያለአንዳች እንቅፋት የሃይማኖት ነፃነታቸው እንዲጠበቅ ትዕዛዝ ተሰጥቶላቸው ነበር ነገር ግን የቅማንቱ ማኀበራዊና ባህላዊ ተቋም ወደፊት ምንም እንደማያዋጣ በመገንዘብ በጥቂት የሃይማኖቱ አክራሪዎች የሚደገፈው የጥንቱ የቅማንት አኗኗር ዘዴ ዘለቄታነቱ አጠራጣሪ እየሆነ መጣ በመሆኑም የሕዝብ ብዛት ሁኔታ ከሌሎች ምክንያቶች ጋር ታክሎ የድሮው ዓይነት የቅማንት አኗኗር ዘይቤ ወደፊት እንዳይራመዱ ከማድረጉም በላይ አሮጌውን ሃይማኖት አስካሁን አጥብቀው የያዙት የዕምነቱ ተከታዮችም በኀብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነትና ቦታ አግኝተው ለመንቀሳቀስ ባለመቻላቸው የቅማንቱን ባህል ለመጭው ተተኪ ትውልድ ማስተላለፍ ተሳናቸው አንድ ሃይማኖታዊ ክብረ በዓልን ለማክበር በርካታ ሰዎች ተገኝተው ለተለያዩ ሥርዓተቅዳሴዎች ለምሳሌ ተዝዛካር የበልግ ወቅት የልምላሜ ክብረበዓላት ለመሳሰሉት መዋጮ ማድረግ አስፈላጊ ከመሆኑም በላይ ለተሳውስቱም ኑኙር አስፈላጊ የሆነውን ድጉማ መስጠት ይገባ ስለነበር ለእነዚህ መሠረታዊ ጉዳዮች መፍትሔ ባለመገኘቱ ችግሩ ተባባሰ ከሁሉም በላይ ደግሞ ሊወጡት ያልቻሉት ውስብስብና ጥብቅ በሆነጡ የጋብቻ ደንባቸው መሥረት ቁጥራቸው ከተመናመነው አረማዊኦሪታውያን መካከል ለልጆቻቸው የትዳር ጓደኛ ማግኘት አለመቻላቸው ነበር በዚህ ምክንያት አንድ ዝቅተኛ ቄስ ሁለት ልጃገረድ ልጆቹ ባል እንዲያገቡ ክርስትና አንዲነሱ ማድረግ ግዴታ የሆነበት ጊዜም አጋጥሟል የወምበሩ ሚስት ሳትቀር ሴት ልጆቿ አረማዊኦሪታዊ ሃይማኖት ተከታይ የሆኑ የትዳር ጓደኞች የማግኘት ችግር እንደሚያጋጥማቸው አሳስቧታል ከዘመድ ጋር ተጋብትችት ግብረሥጋ መፈሀም መቅሰፍት የሚያስከትል መሆኑን ስለሚያምኑ ከዚህ ለመዳን ቅማንቶች ክርስቲያን ከሆኑ ጐረቤቶቻቸው ጋር ለመጋባት በመገደዳቸው የቅማንት ኀብረተሰብ ከሃይማኖት ጋር የተያያዘው ባህል የመኖር ሕልውናው ለረዥም ጊዜ እንደማይቆይ በግልጽ እየታዬ መጣ እኤአ በ ዓም አምስት መቶ ያህል አረማዋዊ ኦሪታዌ ቅማንቶች በዕምነታቸው ፀንተው የቆዩ ቢሆንም በሚቀጥሉት ሠላሣ ዓመታት ጊዜ ውስጥ ሁሉም የክርስትናን ሃይማኖት ይቀበላሉ ወይም ከዚህ ዓለም በሞት የሚለዩ ይሆናል እንዲሁም ክርስቲያን የሆኑት ቅማንቶች ጥንታዊ የሆነውን አረማዊኦሪታዊ የባህል ትውፊቶች በሚቀጥሉት አሥርተ ዓመታት ጊዜ ውስጥ በመርሳት በብዙ ሚሊዮን በሚቆጠረው የአማራው ብሔረሰብ ባህሳቸው ተውጦ ጠቅላሳ ውህደት እንደሚፈጠር አያጠራጥርም በአሁኑ ጊዜ በክርስትና ሃይማኖት የተጠመቁት «ቅማንት» አየተባሉ ቢጠሩም ይህ የመታወቂያ ስም ሙሉ በሙሉ ከአማራው ጋር ሲወሃዱ የሚቀተር ይሆናል ክርስቲያን ቅማንቶች አሁንም ቢሆን የቅማንት ጐሣ አካልና የአንድ ዓይነት ስሜት ተካፋይ መሆናቸውን ያንጸባርቃሉ በአረማዊኦሪታዊ ቅማንቶችንና በአማራው መካከል ይታይ የነበረው ማኅበራዊ ልዩነት በግልጽ ጐልች ባይታይም በአሁኑ ወቅት ክርስቲያን ቅማንቶች በመጠኑም ቢሆን ከአማራው ጋር በማኅበራዊ ኑሮ ረገድ መጠነኛ የሆነ ልዩነት አላቸው በባህል ግን ይህን ያህል የጐላ ልዩነት የላቸውም በክርስቲያን ቅማንቶችና በአማራው መካከል ዖለው አነስተኛ ማኅበሪዊ ልዩነት ባዕድ ያሆኑትን ሕዝቦች ከማግለል የባህል ባሕርይ የመነጨ ሳይሆን በጋብቻ ረገድ በሚያጋጥሙ ችግሮች ምክንያት ነው።