Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
እኛ ዛሬ የምንድነው እንዴት ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክና እምነት አጭር ዳሰሳ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ትክክለኛውን ሐዋርያዊ ትምህርት የያዘች ጥንታዊትና ታሪካዊት ቤተ ክርስቲያን ናት ጥንቅር ዲን ዘላለም ቻላቸው ነሐሴ ዓም «አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነስቷአል ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ በክርስቶስ ደግሞ ህያዋን ይሆናሉና ኛ ቆሮ «እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል ብርቱ የሆነ በእርሱ ለእኔ ታላቅ ሥራን አድርጓልና ሉቃ ማውጫ የቃላት ትርጉም ኢትዮጵያኔ ከ ከ ከ ከ ከ ከ ከ እ እ እ እ እ ን ዘ ዘ ሄ ን ዘ ኦርቶዶክስ ከ ከ ከ ከ ከ ከ ተ ተ ከ ን እ ዘ ዘ ዘ ዘ ዘ ዘ ዘ ቴቴ ቴቴ ተዋህዶ ከ ከ ከ ከ ከ ከ ከ ከ ከ ከ እ ተ ከ አ አ ዘ ከ ሄን አሩ ቤተ ክርስቲያን«ኢ ህእ ን ዘ ዘ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ አምልኮተ እግዚአብሔር«« አምልኮተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ በህገ ልቡና በህገ ኦሪት በህገ ወንጌል እ ን ን ዘ ዘ ን ዘ ቴ«« ወቅታዊ መረጃዎችሥሻሣፖ ክክ እ ከ እእ እ እ ን ን ዘ ዘን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መሠረተ እምነት የአስተምህሮዎቻችን ምንጮች ነገረ ድኅነት«ኢ አዳምና ልጆቿ እንዴት ዳኑ። ገ አምስቱ አዕማደ ምስጢር «ኢ« ምሥጢረ ሖ ምሥጢረ ምሥጢረ ምሥጢረ ምሥጢረ ሄ የቃላት ትርጉም ኢትዮጵያ «ኢትዮጵያ» የሚለው ቃል «የተቃጠለ ፊት» የሚል ትርጉም ያለው የግሪክ ጥምር ቃል ነው ቃሉን ከግብጽ በስተ ደቡብ እስከ ህንድ ውቅያኖስ ድረስ ያለውን ቦታ ለማመልከት ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀሙበት ሆሜርና ሄሮዱተስ የተባሉት ግሪካውያን የታሪክ ጸሐፊዎች ናቸው ምክንያታቸውም በቦታው ይኖሩ የነበሩ ሰዎች የቆዳ ቀለም ነው የጥንት ግብጻውያን ከአገራቸው በስተደቡብ ያለውን ቦታ የኩሽ ምድር እያሉ ይጠሩት ነበር ሊቀ ነቢያት ሙሴም ግብጽ ተወልዶ ያደረና የግብጻውያኑን ባህልና ቋንቋ የሚያውቅ ስለነበር ኦሪትን ሲጽፍ ቃሉን ተጠ ቅሟል ከጌታችን ልደት በፊት በሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጽሐፍ ቅዱስን ከዕብራይስጥ ወደ ግሪክ ፅርፅዕ ቋንቋ የተረጎሙት ሰብአ ሊቃናት ሊቀ ነቢያት ሙሴ «ኩሽ» እያለ የጻፈውን «ኢትዮጵያ» በሚለው ሆሜርና ኔሮዱተስ በተጠ ቀሙበት ግሪክኛ ስም ተክተውታል ይህ ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ከ ጊዜ በላይ ተጠቅሷል በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ የሚለው ቃል በምሥራቅ አፍሪካ የምትገኘው ስኩዌር ሜትር ያህል ስፋት ያላት ሀገር መጠሪያ ነው ኦርቶዶክስ «ኦርቶዶክስ» የሚለው ቃል ቀጥተኛ ትክክለኛ የሚል ትርጉም ያለው የግሪክ ጥምር ቃል ነው ይህንን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ ለቤተ ክርስቲያን ቅጽልነት ገላጭነት የተጠቀሙት በ ዓም በኒቅያ የዛሬይቱ ኢስታንቡል አጠገብ የምትገኝ ከተማ የተሰበሰቡት ጳጳሳትና የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ናቸው የጉባዔው መጠራት ምክንያት የነበረው የጌታችን የመድኅኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የባህርይ አምላክነት የካደው የአርዮስ የምንፍቅና ትምህርት ነበር የጉባኤው ታዳሚዎች አርዮስን ተከራክረው ከረቱ በኋላ የክህደት ትምህርቱን አውግዘው የቀደመች እምነታቸውን አጽንተው ሲለያዩ ሃይማኖታቸውን ኦርቶዶክስ ብለዋታል ዛሬ ይህንን ስያሜ ኦሬንታል አብያተ ክርስቲያናት የኢትዮጵያ የግብጽ የሶርያ የህንድ ማላንካራ የአርመን እና የኤርትራ አብያተ ክርስቲያናት እና ግሪክና ራሽያን የመሳሰሉ የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ይጠቀሙበታል ተዋህዶ ይህቃል «አንድ መሆን» የሚል ትርጉም ያለው የግእዝ ቃል ነው ቃሉ ቤተ ክርስቲያናችን የእግዚአብሔር ልጅ ቃል ሰው መሆንን ምስጢረ ሥጋዌን በተመለከተ ያላትን እምነት የሚገልጽ ነው ቤተ ክርስቲያናችን ቅድመ ዓለም የነበረው የእግዚአብሔር ልጅ ቃል አምላካዊ አካልና ባህርይ እና ከእመቤታችን ከቅድስት ደንግል ማርያም የነሳው ሰዋዊ አካሉና ባህርይ ከሁለት አካል አንድ አካልነት ከሁለት ባህርይ አንድ ባህርይ እንደሆነና ከድንግል ማርያም የተወለደው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው ነው ብላ ቤተ ክርስቲያናችን ታምናለች ቤተ ክርስቲያን ይህ ቃል በዋነኝነት በግሪኩ መጽሐፍ ቅዱስ «አክሌስያ» የሚለውን ቃል የሚተካ የሚወክል የግዕዝ ጥምር ቃል ነው ትርጉሙም የክርስቲያኖች የምዕመናን አንድነት ማለት ነው ከዚህ በተጨማሪ ለአምልትና ለጸሎት የተለየን ሥፍራ የቤተ ክርስቲያንን አስተዳደርና እያንዳንዱን ክርስቲያን ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውሳል። ገሳ ሰላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር በዚህ ምድር በእግረ ሥጋ ተመላለሰ በእነዚህ ዓመታት «ለቀደሙት እንዲህ እንደተባለ ሰምታችኋል እኔ ግን አንዲህ አላችኋለሁ» እያለ የበለጠችውንና ፍጹም የሆነችውን ህገ ወንጌልን ሠራ እነሆ ከዚያ በኋላ ለ ዓመታት ያህል በህገ ወንጌል እየተመራን እግዚአብሔርን አምልከናል አምልኮተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከላይ በተጠቀሱት ሦስቱም ሕግጋት እግዚአብሔርን አምልካለች አሁንም እያመለከች ነው በህገ ልቡና ኢትዮጵያ በሕገ ልቡና ዘመን ሀገረ እግዚአብሔር ነበረች ሌላው ዓለም ከእስራኤላውያን በቀር በአምልኮተ ጣኦት ውስጥ በነበረበት ዘመን የኖኅ ልጆችና የልጅ ልጆች የአባታቸውን እምነት ይዘው በመግባታቸው አገራችን በአምልኮተ እግዚአብሔር ልትታወቅ ችላለች በጥፋት ውኃ ዘመን ከስምንት ቤተ ሰቦቹ ጋር ከሞት ከተረፊው ከጻድቁ ከኖኅ ልጆች ካም የተባለው ወደ አፍሪካ ምድር እንዲመጣና በልጆቹ ጋር አማካኝነት ኢትዮጵያን እንዳቀና ትውፊታዊ መረጃዎች ይጠቁማሉ ይህንን አባባል ከሚያረጋግጡልን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል ላ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ያገባት ሴት ሲፓራ ኢትዮጵያዊት ነች ዘፀ በእስራኤላውያን ሕግ ከአረማውያን ጋር መጋባት ክልክል ነበር ስለዚህ ሙሴ ኢትዮጵያዊቷን ያገባው በሕገ ልቡና አምልኮተ እግዚአብሔር ስለምትመስለው ነው ንግስተ ሳባ የሰሎሞንን ጥበብ ለማየት ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዛ ነበር አየሩሳሌም ደርሳ ንጉሥ ሰሎሞንን ስታገኝ «አንተን የወደደ ከእስራኤልም ዙፋን ያስቀመጠህ አምላክህ እግዚአብሔር የተባረከ ይሁን ኛ ነገ ማለቷ በሀገራችን የነበረውን አምልኮተ እግዚአብሔር የሚያሳይ ነው በህገ ኦሪት ኢትዮጵያ በህገ ልቡና እግዚአብሔርን ስታመልክ ከቆየች በኋላ በ ዓመት ቅል ክ ገደማ ንግስተ ሳባ የንጉስ ሰሎሞንን ጥበብ ለማየት በሄደችበት ጊዜ ህገ ኦሪትን ይዛ በመምጣቷና በጉዞዋ ወቅት ከንጉስ ሰሉሞን የጸነሰችው ልጂ ምኒልክ ሲያድግ አባቱን ለመጎብኘት ወደ ኢየሩሳሌም ሄዶ ሳለ ታቦተ ዮንን ይዞ በመምጣቱ ኢትዮጵያ ወደ ህገ ኦሪት ተሸጋግራለችፎ ይህም ህገ ኦሪትን ለመቀበል ሁለተኛዋ ሀገር ያደርጋታል እስከ ጌታችን ልደት ድረስም በዚሁ ህግ ኖራለች በህገ ወንጌል ክርስትና ክርስትና እንዴት በ ዓም ወደ ኢትዮጵያ እንደገባ የሚያስረዳው የሚከተለው አስደናቁ ታሪክ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ላይ ተመዝግቧል «የጌታም መልአክ ፊልልስን ተነስተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ ወደሚያወርደው ምድረ በዳ ወደ ሆነ መንገድ ሂድ አለው ተነስቶም ሄደ እነሆም ሕንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግስት አዛዥና ጃንደርባ የነበረ በገንዘቧ ሁሉ የሰለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሳለም ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር ሲመለስም በሠረገላ ተቀምጦ የነቢዩን የኢሳያይስን መጽሐፍ ያነብ ነበር መንፈስም ፊልጸስን ወደዚህ ሠረገላ ቅረብና ተገናኝ አለው» ሐዋ ከዚህ በኋላ ፊልስ ጃንደረባውን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት እንደስተማረው ውሃ ወዳለበት ሲደርሱም ጃንደረባው «ኢየሱስ ክርስቶስ የአግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ አምናለሁ» ብሎ እምነቱን መስክሮ እንደተጠ መቀና ወደ ሃገሩ እንደሄደም ተጽፎአል የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊዎቹ አውሳብዮስ ዘቂሳርያና ሄሬኔዎስ እንዲሁም ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ይህ ጃንደረባ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ክርስትናን እንደሰበከ ጽፈዋል እንግዲህ የክርስትና እምነት ወደ ኢትዮጵያ የገባው በዚህ መልኩ በ ዓም ነበር ይሁን እንጂ እስከ ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ ግን ክህነት አልመጣም ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያንንም ጥምቀት ቁርባን መፈጸም አልተጀመረም ነበር በ ዓም በአክሱም ቤተ መንግስት ያደገውና በትውልድ ግሪካዊ የሆነው ፍሬምናጦስ በኛው የእስክንድርያ ፓትርያርክ ቅዱስ አትናቴዎስ አማካኝነት ጵጵስናን ተሹሞ ከመጣ በኋላ ግን ምስጢራት መፈጸም ጀምረዋል ከዚህ በኋላ በነበሩት ዘመናት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ወርቃማና የስኬት ዘመናትን እንዲሁም አሳዛኝና የውድቀትና የጥፋት ዘናትን በማፈራረቅ አሳልፋለች ከአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያለውን የቤተ ክርስቲያኒቱን ታሪክ በአጭሩ ቀጥለን እንመለከታለን ዓም አባ ሰላማ ከኢትዮጵያን ሊቃውንትና መምህራን ጋር በመሆን ስብከተ ወንጌልን በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች ወደ ምዕራብ እስከ ዛሬዋ ሱዳን ድረስ ወደ ደቡብ እስከ ዛሬዋ ሶማልያ ድረስ ወደ ምስራቅ እስከ ደቡብ አረብያ የዛሬዋ የመን ድረስ አስፋፍተዋል በርካታ ቅዱሳት መጻሕፍትም በዚህ ዘመን ወደ ግዕዝ ተተርጉመዋል ዓም ከ ዓም የተደረገውን የኬልቄዶንን ጉባዔ ባልተቀበሉ ኦርቶዶክሳውያን ላይ ካቶሊካውያን መከራ ባፀኑባቸው ጊዜ ሀቱ ቅዱሳን በስደት ወደ ሃገራችን ገቡ እነርሱም በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ወንጌልን ሰበኩ ገዳማዊ ህይወትን አስፋፉ መጻሕፍትንም ከተለያዩ ቋንቋዎች ወደ ግእዝ ተረጓሙ በዚሁ ዘመንም ቅዱስ ያሬድ ተነስቶ ቤተ ክርስቲያናችን እስከ ዛሬ ድረስ የምትጠቀምበትን ዜማ እና የዜማ መጻሕፍት ደርሷል ከ ዓም ይህ ዘመን ከአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ እያበበ መጥቶ የነበረው ክርስትና በከፍተኛ ሁኔታ በሚከተሉት ሁለት ምክንያቶች ተዳክሟል በዐረቢያ ምድር የእስልምና መነሳትና በእስልምና ኀይሎች ምክንያት የኢትዮጵያ የባሕር በሮች መዘንት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ከሌሎች የክርስትና ዓለም ጋር የነበራት ግንኙነት መዳከም ዮዲት በተባለች ሴት መሪነት በኢትዮጵያ ውስጥ የነበሩ አይሁዳውያን ተነስተው ክርስቲያኖችን ማሳደዳቸውና መግደላቸው አብያተ ክርስቲያናትንና መጻሕፍትንም ማውደማቸው ከ ዓም ይህ ዘመን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ተልዕኮ እንዲሁም መንፈሳዊ አገልግሎት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ያደረሰበት ዘወን ነው አባ ኢየሱስ ሞአ የሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳምን መስርተው በገዳሙ ውስጥ በርካታ ደቀመዛሙርትን አስተማሩ ከዚህ ገዳም የወጡ በርካታ አባቶች ወደ ተለያዩ አቅጣጫዎች በመሠማራት ወንጌልን ሰበኩ ለምሳሌ ያህልም አቡነ ተሃይማኖት ደቡብ ኢትዮጵያን አባ ጊዮርጊስ ቤተ አዎሃራን አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ዳውንትንና አካባቢውን አቡነ ዜና ማርቆስ መካከለኛው ኢትዮጵያን አስተምረዋል እነዚህ አባቶች ደግሞ የተለያዩ ገዳማትን መስርተው ደቀ መዛሙርትን በማፍራታቸው የእነርሱ ደቀመዛሙርትም ወደ ተለያዩ ቦታዎች እየሄዱ ወንጌልን ሰብከዋል ክርስትናንን አስፋፍተዋል በሰሜን ክፍል አቡነ መድኃኒነ እግዚእ እና ሰባቱ ክዋክብት በመባል የሚታወቁት ደቀመዛሙርቶቻቸው በትግራይና በጎንደር አካባቢ ክርስትናን አስፋፍተዋል ገዳማትን መስርተዋል በዚህም ምክንያት ዘመኑ የቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ህይወት ከፍተኛ ደረጃ የደረሰበት ነገስታት ሳይቀሩ ለክህነትና ለቅድስና የበቁበት ዘመን ሊሆን ችሏል ከ ዓም ይህ ዘመን በተከታታይ በተፈጠሩ በደረሱ ሁኔታዎች ምክንያት ቤተ ክርስቲያን መከራ የተቀበለችበትና የተዳከመችበት ዘመን ነው የአክራሪ እስልምና ወረራ በ ዓም አካባቢ በዘመኑ ኀያል በነበረው በቱርክ መንግስት አስታጣቂነት የዘመተው አህመድ ግራኝ በርካታ ክርስቲያኖች ገደለ ብዙዎችን በግዳጅ አሰለመ ካህናትን ጨፈጨፈ እጅግ በጣም ብዙ ገዳማትን አብያተ ክርስቲያናትንና መጻሕፍትን አቃጠለ የካቶሊኮች መምጣት የአህመድ ግራኝ ወረራ ሌላ ችግርን ወለደ በአህመድ ግራኝ ወረራ ጊዜ የኢትዮጵያ መሪ የነበሩት አጹ ልብነ ድንግል ወራሪውን ለመቋቋም የሜሆን ድጋፍ ከፖርቹጋል መንግስት ጠይቀው ነበር እርዳታው በተለያዩ ምክንያቶች ሲጓተት ከቆየ በኋላ የፖርቱጋል መንግስት ወታደሮች መጥተው በእነርሱ እርዳታ ግራኝ ድል ሆነ ይሁን እንጂ ከዚህ በኋላ ከፖርቹጋል መንግስት ወታደሮች ጋር የመጡት የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን መልዕክተኞች «ካቶሊክ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሃይማኖት ይሁን» የሚል ጥያቄ አቀረቡ ጥያቄው በጊዜው ተቀባይነት ቢያገኝም ከዚያ ቀጥሎ ባሉት ዘመናት ብዙ የካቶሊክ ሚሲዮናውያን ወደ ሃገራችን ለመምጣት አጋጣሚ ተፈጥሮላቸዋል። የአንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት ቀጥተኛ መግበያ በር እየተዘጋ የስርጥ በር እንዲጠቀሙ ተገደዱ በአጠቃላይ በቤተ ክርስቲያን ላይ የነበረው የስነ ልቦናና የሞራል ተጽእኖ ከባድ የነበረበት ዘመን ነበር የደርግ ሥርዓት መለወጥን ተከትሉ ከሸ ስከ አሁን ድረስ ያለውንም በዚሁ መንገድ በአዎንታዊና በአሉታዊ ማየት እንችላለን በአዎንታዊ ጎኑ የእምነት ነጻነት መታወጁ የተወረሱ የቤተ ክርስቲያን ንብረቶችና ይዞታዎች መመለስ መንፈሳዊ የኅትመት ሥራዎች መፈቀዳቸው የሰንበት ትምህርት ቤቶች በየአብያተ ክርስቲያናቱ መቋቋምና መጠናከር በአንዳንድ የከተማና ከተማ ነክ አድባራት ለልማት ሥራዎች የሚውሉ ሕንፃዎች መሠራታቸው «ተማረ» የሚባለው ክፍል በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተሳትፎ መጀመሩ ሐዋርያዊ አገልግሎት በመጠኑም ቢሆን ማንሰራራት መጀመሩ የሚጠቀሱ መልካም ጅምሮች ናቸው ይሁን እንጂ በርካታ ችግሮችም ይታያሉ የሐዋርያው ተልዕኮው አድማስና አፈጻጸም የተቀናጀና ስልታዊ አለመሆን የሚዳርጉትን ሐዋርያዊ ተልዕኮዎች ከችግሩ ስፋትና መጠን አንጻር የማይወጣጠኑ መሆናቸው ቤተ ክርስቲያን ለህልውናዋ ሳይቀር አደጋ በነበሩ በብዙ ችግሮችና ውጣ ውረዶች ያሳለፈችና ሁል ጊዜ ደልቷትና ተመችቷት የኖረች ይመስላል ባለፉት ዘመናት ለተፈጠሩ ችግሮች ሁሉ ቤተ ክርስቲያን ተጠያቂ ማድረግ ዘረኝነት በውስጥም በውጭም የአክራሪ እስልምና እንቅስቃሴዎች እና አስተዳደራዊ ችግሮች ጥቂቶቹ ናቸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አሁን ያሉትን መልካም ጅምሮች አጠናክራ የተሻለ ሐዋርያዊ አገልግሎት እንድትፈጽምና ወንጌልን ለሁሉም ማድረስ እንድትችል የሚታዩትም ችግሮች እንደቀረፉ ሁላችንም ልንነሳና የየበኩላችንን አስተዋጽኦ ልናበረክት ይገባናል ወቅታዊ መረጃዎች በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኢትዮጵያ ውስጥና ከኢትዮጵያ ውጭ የሚኖሩ ሚሊዮን ያህል ተከታዮች አሏት ከእነዚህ ውስጥ ያህሉ ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌላቸውና በተለያዩ የዓለም ክፍሉች የሚኖሩ ናቸው የኢኦተቤተ ክርስቲያን በሃገር ውስጥ በውጭ ሀገር ደግሞ ሃገረ ስብከቶች አቋቁማ የእግዚአብሔርን መንግስት እየሰበከች ትገኛለች ሐገረ ስብከት ማለት በአንድ ሊቀ ጳጳስ የሚመራ የአገልግሉት ክልል መዋቅር ማለት ነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መሠረተ እምነት የአስተምህሮዎቻችን ምንጮች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ምንጮች ሦስት ናቸው እነዚህም ሀ ቅዱሳት መጻሕፍት አምላካችን እግዚአብሔር በየዘመናቱ የተለያዩ ሰዎችን እያስነሳ ለሰው ልጅ መማሪያ የሚሆኑ መጻሕፍትን አስጽፏል ከእነዚህ መጻሕፍት መካከል የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከሕገ ወንጌል መሠራት በፊት የተጻፉ እና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ከጌታችን መወለድ በኋላ የተጻፉ ተለይተው አሥራው መጻሕፍት ይባላሉ እነዚህም በአንድ በላይ ሲጠረዙ «መጽሐፍ ቅዱስ» ተብለው ይጠራሉ ከእነዚህ ከአሥራው መጻሕፍት ውጪ የሆኑት ሌሎቹ ደግሞ አዋልድ መጻሕፍት ይባላሉ እነዚህ መጻሕፍት የአሥራው መጻሕፍትን ለማብራራት በተለያዩ ዘመናት ለነበሩ ችግሮች መፍትሄ ለመስጠትና አሥራው መጻሕፍት ከተጻፈበት ዘመን በኋላ የተደረጉ ነገሮችን ለመመዝገብ ለጸሎትና ለምሥጋና እና ለመሳሰሉት አገልግሎቶች በተለያዩ ጊዜያት ዘመናት የተጻፉ ናቸው ለ የጉባኤያት ውሳኔዎች በቅዱሳን ሐዋርያት እግር የተተኩ የቤተ ክርስቲያን አባቶችና መሪዎች ጳጳሳት በቤተ ክርስቲያን የተፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት የምንፍቅና አስተምህሮዎችንና ከክህደታቸው አልመለስ ያሉ መናፍቃንን ለማውገዝና ትክክለኛውን የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ለማጽናት በተለያዩ ጊዜያት ጉባኤያትን አድርገዋል የኢኦተ ቤተ ክርስቲያን ሦስት ዓለም አቀፍ የቤተ ክርስቲያን ጉባኤያትንና ውሳኔዎቻቸውን ትቀበላለች እነዚህም በ ዓም እኤአ የተደረገው የኒቅያ ጉባኤ በ ዓም እኤአ የተደረገው የቁስጥንጥንያ ጉባኤ እና በ ዓም እኤአ የተደረገው የአፌሶን ጉባኤ ናቸው ሐ ሐዋርያዊ ትውፊት ትውፊት የሚለው ቃል «አወፈየ ሰጠ» ከሜለው የግእዝ ቃል ግስ የተገኘ ቃል ሲሆን የተሰጠ የተቀበሉት የሚል ትርጉም አለው ስለዚህ ሐዋርያዊ ትውፊት ማለት ከሐዋርያት ጀምሮ በቃል በጽሑፍና በተግባር ሲፈጸም በመመልከት ሲወርድ ሲዋረድ ከእኛ ዘንድ የደረሰ የቤተ ክርሰቲያን ትምህርት እና ሥርዓት ማለት ነው ሐዋርያትና ሌሎቹ የጌታችን ደቀመዛሙርት ወንጌልን መጀመሪያ ያስተምሩ የነበሩት በቃል ነበር። በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበሩ ሰዎች በዘር የሚወርሱት የአዳም በደል ስለነበር ምንም አይነት መልካም ሥራ ቢሠሩ ወደ ገነት የመግባት እድል አልነበራቸውም ነቢያቱም ይህንን «ጽድቃችን እንደ መርገም ጨርቅ ሆነ በማለት ገልጸውታል በጌታችን በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የአዳምን በደል ዋና በሞቱ ከከፈለና ዓለም ከእግዚአብሔር ጋር ከታረቀ በኋላ የምንኖር ሰዎች ግን በዚህ በአዳም በደል አንጠየቅም የእያንዳንዱ ሰው ድኅነት በራሱ እምነትና ምግባር ላይ የተመሰረተ ነው ዛሬ አንድ ሰው ለመዳን መንግስተ ሰማያትን ለመውረስና የዘለዓለም ሕይወት ባለቤት ለመሆን ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን አሟልቶ መገኘት ጥኖርበታል እነዚህም እምነት የእግዚአብሔርን አምላክነትና ፈጣሪነት የጌታችንን የመድኀኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የእግዚአብሔር ልጅነትና ተሰቅሎና ሞቶ ይህንን ዓለም ማዳንና በሚቀጥለው ክፍል የምንመለከታቸውን የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መሠረተ እምነቶች ማመን አለበት ያለ እምነት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም» ዕብ « ያመነ የተጠመቀ ይድናል ያላመነ ግን ይፈረድበታል» ማር ምስጢራትን መፈጸም ካመነ በኋላ ለመዳን የግድ መጠመቅ የጌታችንን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን መቀበል ሲበድል ኀጢአት ሲሠራ ንስሐ መግባትና ሌሎች ምስጢራተ ቤተ ክርሰቲያን መፈጸም አለበት «ሰው ከውሃና ከመንፈስ ካልተወለደ ወደ እግዚአብሔር መንግስት አይገባም» ዮሐ «ሥጋዬን ያልበላ ደሜን ያልጠጣ የዘላለም ህይወት የለውም» ዮሐ ምግባር ያመነ እና ምስጢራትን የፈጸመ ሰው ለመዳን እምነቱን እና በምሥጢራቱ አማካኝነት ያገኘውን ጸጋ በመልካም ሥራ ምግባር መግለጥ መተርጎም አለበት መልካም ምግባር ማለትም ከኀጢአት መራቅ እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጣቸውን አሠርቱን ሕግጋት ትዕዛዛትና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እነዚህን ሕግጋት ያጸናባቸውን ቱን ቃላተ ወንጌልና ማቴ ቨሸ አሥሩን ብጹአን ማቴ መፈጸም ጌታችን ዳግም ለፍርድ ሲመጣ ለምንጠይቃቸው የምግባር ጥያቄዎች ማቴ ተግባራዊ መልስ ማዘጋጀት ቅዱስ ጳውሎስ ለገላትያ ክርስቲያኖች በጻፈው መልዕክቱ የዘረዘራቸውን የመንፈስ ፍሬዎች ገላ አፍርቶ መገኘትና እነዚህን የመሳሰሉ ነገሮች ናቸው እነዚህ ሦስት ለድኅነት አስፈላጊ የሆኑ ነገሮች ማሟላት ለመቻል ማለትም በእምነት ለመጠንከር ወደ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን ለመቅረብ እና የመልካም ምግባር ባለቤት ለመሆን አንድ የቤተ ክርስቲያን አባል የሆነ ክርስቲያንም ሆነ አባል ለመሆን በዝግጅት ላይ ያለ ሰው የሚከተሉትን መፈጸም እንዳለበት ቤተ ክርስቲያናችን ታስተምራለች የእግዚአብሔርን ቃል መማርና ማወቅ የእግዚአብሔር ፈቃድ ምን እንደሆነና ምን ማድረግ እንዳለብን ለማወቅ ያንንም እንዴት ማድረግ እንደምንችል ለመረዳት ቅዱሳት መጻሕፍትን በማንበብና ወደ መምህራን በመቅረብ ቃሉን መማር አለብን « መጸለይ መጸለይ ማለት ከእግዚአብሔር ጋር በተመስጦ መነጋገር ላደረገልን ነገር ማመስገንና የምንፈልገውን ነገር መለመን እምነታችንን መግለጥ ማለት ነው ጸሎት በህብረትም በግልም ይፈጸማል ላ መጾም መጾም ማለት ለሥጋ የሚመቹ ምግቦችን የእንስሳት ውጠ »ኔቶችን መጠጦችንና ሌሎች ነገሮችን በፈቃድ መተው ማለት ነው ዓላማውም የሥጋን ኀይል አድክሞ ከኀጢአት ሥራዎች ማራቅና ሥጋን ለነፍስ ማስዝት ነው « መስገድ ከወገብ እያጎነበሱ ወይም መሬት እየወደቁ የሚፈጽሙት ተግባርና እንቅስቃሴ ነው ዓላማውም ለእግዚአብሔር ፍጹም መገዛትን ፍጹም አምልኮትን መግለጥና ሥጋን ማድከም ነው ምፅዋት ለራስ የሆነን ነገር ገንዘብ ምግብ ልብስ ለሌሎች ማካፈል ማለት ነው « ማገልገል ያወቁትን ለሌሎች ማሳወቅ ሌሎችን ወደ ቤተ ክርስቲያንና መንፈሳዊነት ማምጣት ማለት ነው እነዚህን ነገሮች መፈጸማቸው የድኅነትን አክሊል ለመቀዳጀት ብቁ እና የተገባን ያደርገናል ማለት ግን አይደለም ምክንያቱም ምንም ያህል እምነት ቢኖረን ምንም ዓይነት ድቅ ምግባር ብንሠራ የእምነታችንና የጽድቃችን ዋጋ ከመንግስተ ሰማያት ዋጋ ጋር ሊተካከል አይችልም ስለዚህ ድኅነት እግዚአብሔር በቸርነቱና ለሰው ልጆች ባለው ፍቅር የሚሰጠን ስጦታ ጸጋ ነው አምስቱ አዕማደ ምስጢር «አምድ» ማለት «ምሰሶ» ማለት ሲሆን «አዕማድ» ማለት ደግሞ ምሰሶዎች ማለት ነው አዕማደ ምስጢር ማለት ደግሞ «የምስጢር ምሰሶዎች» ማለት ነው አምስቱ አዕማደ ምስጢር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መሠረታዊ የሆኑ የሃይማኖት አስተምህሮዎች የሚገለጡባቸው አምስት ርዕሶች ናቸው እነዚህም ምስጢረ ሥላሴ ምስጢረ ሥጋዌ ምስጢረ ጥምቀት ምስጠ ረ ቁርባንና ምስጢረ ትንሣኤ ሙታን ናቸው አዕማድምሰሶዎች የተባሉት ምሰሶዎች ለአንድ ቤት መቆም ወሳኝ እንደሆኑት ሁሉ እነዚህም ወሳኝ የቅድስት ቤተክርስቲያን አስተምህሮዎች በመሆናቸው ነው ምስጢር የተባሉት ደግሞ በጣም ረቂቅና በሰው ልጆች ሕሊና መርምሮ ሙሉ ለሙሉ ለመረዳት ከባድ ስለሆኑ ነው ቀጥለን እያንዳንዳቸውን በአጭር በአጭሩ አንመለከታለን ምሥጢረ ሥላሴ «ሥላሴ» የሚለው ቃል ሦስትነት የሚል ትርጉም ያለው የግእዝ ቃል ነው ምስጢረ ሥላሴ የእግዚአብሔርን አንድነትና ሦስትነት የምንማርበት የትምህርት ክፍል ነው የምናመልከው አንድ አምላክ በሦስት አካላት እንዳለ ለአበውለነቢያትና ለሐዋርያት ተገልጧል ስለዚህ አምላካችንን ቅድስት ሥላሴ እንለዋለን ትርጉሙም «ልዩ ሦስትነት» ማለት ነው «ልዩ» መባሉም ቀጥለን እንደምንመለከተው ሦስት ሲሆን አንድ አንድ ሲሆን ሦስት ስለሆነ ነው ያሥዛፅ ሥዕተንፉ የሥላሴ ሦስትነት በአካል በስምና በግብር ነው እያንዳንዳቸውን በዝርዝር እንመለከታለን ይጎነም ፖታያታፓንፉ እነዚህ ሦስት አካላት የየራሳቸው ልዩ ስም አላቸው አብወልድመንፈስ ቅዱስ ይባላሉ አንዳቸው በሌላው ስም አይጠሩበትም ይህ ስማቸው ቀጥሎ እንደምንመለከተው ግብራቸውን የሚገልጥ ነው ዖፇዖዝሮረ ፖጋያታ በግብር አብ ወላዲ አሥራጺአስገፒ ወይም መገኛ ነው ወልድ ደግሞ ተወላዲ ከአብ የተገኘ መንፈስ ቅዱስም ሠራጺ ከአብ የወጣ የተገኘ ነው «ወልድና መንፈስ ቅዱስ ከአብ ተገኙ ወጡ ሲባል መገኘታቸው መውጣታቸው የፀሐይ ብርሃንና ሙቀት ሁለቱም ከክበቡ ባለመቀዳደም አንድ ጊዜ ተገኙ እንደማለት ያለ እንጂ እንደ ሥጋ ልደት ሕገ ሰብን አይከተልም አይደለም ስለዚህ በሥጋ ልደት አባት ልጁን እንደሚቀድመውና እንደሚበልጠው አብ ከወልድና ከመንፈስ ቅዱስ አይበልጥም እነርሱም ከአብ አያንሱም በሥላሴ ዘንድ መቀዳደምም መበላለጥም የለም ይላጳል ሥታታንፉ የአካል ሦስትነት ማለት ሦስቱ አካላት እያንዳንዳቸው ፍጹም አካል አላቸው ማለት ነው ይህ አካል ተጨባጭ ወይም ቁሳዊ አካል አይደለም መንፈሳዊ አካል ነው ለምሳሌ ነፋስ አካላዊ ነው ልንጨብጠውና ልንዳስሰው ልናየውም ግን አንችልም ባለመታየቱ ግን የለም ልንለው አንችልም ባሕር ሲያናውጽ ዛፍ ሲያወዛውዝ ግን በሥራው መኖሩን እናያለን ከነፋስ ደግሞ የሰው ነፍስ ትረቃለች ከሰው ነፍስም መላእክት ይረቃሉ እነዚህ ሁሉ የምናውቃቸው ረቁቃን አካላት ናቸው የዚህ ሁሉ ፈጣሪ እግዚአብሔር ደግሞ ፍጹም መንፈስ ስለሆነ በማይነገር መጠን ረቂቅ ነው ይህ ረቂቅ አካል የሌለበት ቦታ የለም በምድርምበሰማይምበአየርምበማንኛውም ቁስ አካል ሁሉ ይገኛል በሁሉ የመላ ነው ዖያሥፅ ሪሮድንፖ ሦስቱ አካላት አብ ወልድና መንፈስ ቅዱስ በባሕርይ በህልውና እና በመለኮት አንድ ናቸው በባሕርይ አንድ ናቸው ስንል ሦስቱ አካላት በዘለዓለማዊነት ሁሉን ቻይነትምሉዕነትረቂቅነትና በመሳሰሉት ነገሮች አንድ ናቸው እነዚህ የሦስቱም አካላት ባሕርይ ናቸው ማለት ነው ሕልውና ማለት አኗኗር ማለት ነው በህልውና አንድ ናቸው ስንል አንዳቸው በአንዳቸው ውስጥ ይኖራሉ ማለታችን ነው አብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ውስጥ ህልው ነው ይኖራል ወልድም በአብና በመንፈስ ቅዱስ ውስጥ ህልው ነው መንፈስ ቅዱስም በአብና በወልድ ውስጥ ህልው ነው መለኮት ማለት ገዢነትመግዛት ማለት ነው በመለኮት አንድ ናቸው ስንል በመፍጠር በመስጠት በመንሳት በማዳን በመግደል በማጽደቅ በመኮነን ይህንን በመሳለው ሁሉ አንድ ናቸው ማለት ነው ምሥጢረ ሥጋዌ «ሥጋዌ» የሚለው ቃል «ሥጋ መሆን» «ሥጋነት» የሚል ትርጉም ያለው የግእዝ ቃል ነው ምስጢረ ሥጋዌ ደግሞ ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል እግዚአብሔር ወልድ አዳምን ለማዳን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ሰው መሆኑን የምንማርበት ትምህርት ነው «ነገሥ ድኅነት» በሚለው ክፍል ላይ እንደተመለከትነው አምላካችን እግዚአብሔር ከልጅ ልጁ ተወልዶ እንደሚያድነው በድሉ ለወደቀው ለአዳም ተስፋ ሰጥቶት ነበር የዘመኑ ፍጻሜ ሲደርስ እግዚአብሔር ወልድ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ በእመቤታችን ማህጸን አድሮ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ሰው ሁኖ ተወልጻል።