Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ብለዋል ዮሐ ጌታ ሥጋውን እውነተኛ ምግብ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይማናትና ክርስቲያናዊ ሕደዉት ያጸ ያንራታ የክርስቶስ ጸጋ ከመሰጠቱ በፊት ሰው ሁሉ በራሱ ጥረት ሕግን ለመፈጸም ግዴታው ነበር በዚህም የተነሣ የሕግን ትእዛዛት ሁሉ ለመፈጸም አዳጋች ሰለሆነ ማለት አንዲቱን ትእዛዝ እንኳ የሻረ ሕግን ሁሉ በፈጸመው በክርስቶስ ያመኑ በመንፈሱ የሚመሩ ሁሉ በእርሱ ጸጋ እንደ ሕግ ፈጻሚዎች ተቆጥረዋል ሮሜ እንግዲህ ክርስቲያኖች በእምነትም በሥራም በክርስቶስ ጸጋ ሥር ናቸው እንጂ ጸጋውን እንደ ተቃወሙት አይሁድ በሙሴ ሕግ ሥር አይደሉም በጸጋው ሥር ሆነው ትእዛዛትን ሁሉ በሕገ ተፋቅሮ ፈጽመውታልና ስለዚህም በበደላቸው የተነሣ በሕግ ከሳሺነት ከሚመጣው የሞት ፍርድ ነፃ ናቸው ምክን ያቱም በክርስቶስ እምነትና ጥምቀት በተገኘው ጸጋ አማካኝነት ከበደላቸውና ከኃጢአታቸው የሚነጹበት ምሕረት የሚያገኙበት የመዳን ጸጋ ስላላቸው ነው ስለሆነም እውነተኛ አማኞች በመንፈሳዊ ሕይወታቸው እንቅፋት ቢያጋጥማቸው ተስፋ አይቆርጡም እንዲያውም ንሥሐ በመግባታቸው ጸጋ ይጨመርላቸዋል መንፈሳዊ ተጋድሏቸውም ይጸናላቸዋል ከበፊቱ ይልቅ የሕግ ትእዛዛትን ለመፈጸም የሚያስችልና የሚያበረታታ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋና ረድኤት ይበዛላቸዋል በክርስቶስ በእውነት ላመኑትና ለተከተሉት ሁሉ የጸጋው አጋዢነትና የጸጋው አዳኝነት አይለያቸውም የጸጋ አዳኝነት ስንል የሰው ልጆችን መዳን ያመለክታል ታዳያ ሰው መዳኑ ከምን ነገር ነው። ታሪኩና ምሳሌውስ እንዴት ነው።
ትምህርተ ዛይማናትና ክርስቲያናዊ ሕይወት ክፍል ሁለት የክርስቶስ የማዳን ሥራና ጸጋው በቃሉና በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን መግቢያ የክፍል ሁለት ርእስ እንደዚህ በረጅሙ የተቀረጸበት ምክንያት የጽሑፉን ዐቢይ መልእክት በቅድሚያ ለማስገንዘብ ያህል ነው ባጭሩ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን በሚል ርእስ ተነሥቶ ስለ እያንዳንዱ ምሥጢራት ታሪክና የአፈጻጸም ሥርዓት ከሌላውም አብያተ ክርስቲያናት ጋር ያለውን ግን ኙነትና ልዩነት በማነፃፀር መግለጡ በበቃ ነበር ነገር ግን ስለዚህ ጉዳይ በየጊዜው በአገራችን ምሁራን የተዘጋጁ ብዙ ጠቃሜ መጻሕፍት ስላሉ እነዚህኑ ማጥናት እንጂ እነርሱን አሰመስሎ እንደገና መጻፉ እምብዛም ተፈላጊነት አይ ኖረውም በተለይም በሊቃውንት ጉባኤ ተዘጋጅቶ በ ዓም ለሁለተኛ ጊዜ የታተመው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ሥርዓተ አምልኮትና የውጭ ግንኙነት እንደዚሁም በማኅበረ ቅዱሳን አዘጋጅነት በ ዓም የታተመው ትምህርተ ሃይማኖት ርትዕት የተባሉ መጻሕፍት ከላይ ለተጠቀሱት ጉዳዮች ጠቃሚነታቸው ስለታወቀ ለመማሪያም ሆነ ለማስተማሪያ ያስፈልጉናል በነዚህና በመሳሰሉት መጻሕፍት ላይ አዲስ የሚጨመር ነገር ኖሮ ሳይ ሆን ይኸንኑ ትምህርትና እምነት ለአዲሱ ትውልድ ጥያቄ እንደሚስማማ አድ ርጎና ያንኑ በበለጠ አጠናክሮ ለማቅረብ ታስቦ የተጻፈ ነው ይልቁንም ስለ ምሥጢራት አሰፈላጊነት በአዲሱ ትውልድ ዘንድ እየተረሳ እንዳይሄድ ለማድረግና በጊዜያችንም እየጐላና እየገፋ ለመጣው ለተቃዋሚዎች ጥያቄ ምላሽ መስጠት ግዴታ ሆኖብናል ስለዚህም በጽሑፋችን ትኩረት የምንሰጠውና በአ ጽንኦት የምናጠናው ዐቢይ ጉዳይ በክርስቶስ የመዳናችን ምሥጢርና በቤተ ክርስቲያናችንም የምሥጢሩ አፈጻጸም በምን ሁኔታና ሥርዓት እንደሆ ነ በመመልከት ነው አንዳንድ ወገኖች የመዳናችን ምሥጢር በእምነት ብቻ ስለሚፈጸም ሌሳ ነገር አያስፈልግም ይላሉ ቃለ እግዚአብሔርን ሰምቶ በማመን ብቻ መጽደቅ ስለሚቻል የምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን አስፈላጊነት አይታየንም በማለት አጥ ብቀው ይከራከራሉ ነገር ግን እነርሱ እንደሚሉት ሳይሆን መዳናችን ቃለ እግዚአብሔርን ሰምቶ በማመን ቃሉን ሰምቶ በማድረግና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን በመፈጸም እንደሆነ ቅዱሳት መጻሕፍትን ምስክር በማድረግ በአ ጭሩ ለማሰረዳት ሞክረናል ከትእዛዛት አንዱን የሻረ ሁሉን እንደ ሻረ ስለሚቆጠር ሁሉንም መፈጸም ይገባናል እንጂ አንዱን ብቻ መርጦ መያዝ ሌላውን ማጣጣል ሁሉን ም እንዳፈረሰ ይቆጠራል ያዕ እርሱ የደኅንነታችንና የጽድቃችን ሁሉ ባለቤት ክርስቶስ ሁሉንም እንድንፈጽም አዞናል ጌታ የመነ የተጠመቀ ይድናል ነው ያለው እንጂ ያመነ ብቻ አላለም ማር ከውኃና ከመንፈስ ያልተወለደ መንግሥተ ሰማያት እንደማይገባ ጌታ አረጋግጣል ዮሐ ጥምቀት የምሥጢራት ሁሉ መጀመሪያ ነው ጌታም የጥምቀትን ምሥጢር ለማጠናከር እርሱ ራሱ አርአያ ሊሆነን ከሁሉ በፊት ሥራውን የጀመረው ራሱን ዝቅ አድርጎ በእደ ዮሐንስ በመጠመቅ ነበር እርሱ እንደ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛዩማናትና ክርስቲያናዊ ሕይወት ተጠመቀ እኛም እንድንጠመቅ አዘዘን እንግዲህ ጌታ ያዘዘውን የጥምቀትን ሥርዓት በጌታ ቃል ተመርኩዘን እንፈጽመዋለን ጌታ በቃሉ ያዘዘውን በተግባር የፈጸመውን መሠረት በማድረግ ስለ ሌሎቹ ምሥጢራትም በየቦታቸው ገልጸናል የእግዚአብሔር የማዳን ሥራው በዕለተ ዓርብ አንድ ጊዜ የተፈጸመ ሲሆን የመዳኑ ጸጋ በየጊዜው ለሚነት ትውልድ ሁሉ የማደርሰው በቃሉ አ ገልግሎት ማለት በስብከተ ወንጌልና ምሥጢራትን በመፈጸም ነው ስለዚህ ነው ሐዋርያት ለጸሎትና ቃሉን ለማገልገል እንተጋለን የሚሉት የሐዋ ቃሉን ማገልገል ማለት የጌታን ቃል ማስተማር በስሙም ን ስሐና የኃጢአት ሥርየት መስበክን ያመለክታል ሉቃ በጸሎት መትጋትም ማለት በክርሰቶስ ሰም አምነው ንስሐ ለሚገቡትና የኃጢአት ሥርየት ለሚያስፈልጋቸው ተገቢውን ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን በልዩ ልዩ ሥርዓተ ጸሉት አማካይነት መፈጸም እንደሆነ ከሐዋርያት የዕለት በዕለት ተግባር ለማወቅ ይቻላል የመጀመሪያዎቹ አማኞች ቃሉን በማመንና በመቀበል ብቻ አልቀሩም በሐዋርያት ሥራ እንደ ተጻፈው ቃሉንም የተቀበሉት ተጠመቁ በዚያም ቀን ሦስት ሺህ የሚያህል ነፍስ ተጨመሩ ካለ በኋላ በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቁረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር ይላል የሐዋሥራ እንግዲህ የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች የሐዋርያትን ትምህርት በመስማት ቃሉንም በማመን ምሥጢራትንም በመፈጸም በየጸሎቱም በመትጋት በመንፈሳዊ ፍቅርና አንድነት መኖራቸውን እያስታወስን የእነርሱን አርአያ መከተል ክርስቲያናዊ ግዴታችን መሆኑን አ መልክተናል በዚህ ጽሑፍ ላይ በተለይም በክፍል ሁለት በምዕራፍ አንድ ለማስረዳት የሞከርነው ከላይ የጠቀስነውን የመጀመሪያዋን ቤተ ክርስቲያን ፈለግ በመከተል የመዳናችን ጸጋ ለሁላችን የሚደርሰን በቃሉ በማመንና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን በመፈጸም እንደሆነ ነው ምክንያቱም ቃለ እግዚአብሔርና ምሥ ጢራተ ቤተ ክርስቲያን ለመዳናችንና ለመቀደሳችን ሲባል ከአንድ ጌታ የተሰጡ ናቸውና ስለዚህ ነው ገና ከመጀመሪያው በርእሱ ላይ ሳይቀር የመዳናችን ሥራና ጸጋ በቃሉና በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን እንደሆነ የገለጽነው ሰለ ሰባቱ ምሥጢራት እያንዳንዱን ከመግለጻችን በፊት የጸጋን ትርጉምና ዓይነት እንዲሁም ጸጋ ከኃጢአትና ከሕግ በተለይም ከቤተ ክርስቲያን ምሥጢራት ጋር ያለውን ግንኙነት በአጭሩ ለማስረዳት ሞክረናል ይህም የሆ ነበት ምክንያት ከእያንዳንዱ ምሥጢራት ስለምናገኘው የጸጋ ዓይነት በቅድሚያ እንድናውቅና አስፈላጊው ግንዛቤ እንዲኖረን ለማድረግ ነው በክፍል አንድ ምዕራፍ ሦስት የመዳናችንና የመቀደሳችን ምሥጢር የጸጋው አሰጣጥና የሥራው አፈጻጸም በመንፈስ ቅዱስና በቤተ ክርስቲያን አማካይነት እንዴት እንደሚከናወን በአጭሩ ገልጸናል በተለይም በጸሎተ ሃይማኖት አንቀጽ ፊደል ተራ ሐ ጋር የዚህ ክፍል ሁለት አርእ ስተ ትምህርት ቀጥታ የተያያዘ ነው እንደዚሁም በአንቀጽ ኃጢአት በሚሠረይባት በአንዲት ጥምቀት እናምናለን ከሚለው ኃይለ ቃል በከፊል በመውሰድ ስለ ሥርየተ ኃጢአት ብቻ አስረድተን የቀረውን ማለት ጥምቀትን በተመለከተ ግን ከምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ጋር እንደምንገልጽ በዚያው በቦታው ላይ አመልክተናል ይህም የሆነበት ምክንያት ጥምቀት የምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን አንዱና የመጀመሪያው ሰለሆነ ነው እንግዲህ በዚህ ክፍል በመጀመሪያ የጌታችንን የማዳን ሥራውንና ጸጋውን በእግዚአብሔር የተጠሩት ሁሉ በቃሉ አገልግሎት በቤተ ክርስቲያን ጸሎትና በተቀደሱት ምሥጢራት አማካይነት እንዴት እንደሚያገኙት በአጠቃላይ መልኩ እንመለከታለን ቀጥሎም ከቃለ እግዚአብሔር ጋር ከሰባቱ ምሥጢራት ሁሉ በአንድነትና በተናጠል ከእያንዳንዳቸው በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ለምእመናን ስለሚታደለው ልዩ ልዩ የጸጋ ስጦታዎች ለማስረዳት እንሞክራለን ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛፀማናትና ክርስቲያናዊ ሕሀወት ምዕራፍ አንድ ስለመዳናችን ምሥጢር ስለ ጸጋና ስለቤተ ክርስቲያን ምሥጢራት ሀ መዳናችን ቃሉን በማመንና ምሥጢራትን በመፈጸም ነው ቃለ እግዚአብሔር ጸሎትና ምሥጢራት አይሊያዩም በክፍል አንድ ጸሎተ ሃይማኖትን መሠረት በማድረግ ስለ ክርስትና እም ነት በመጠኑ ተምረናል ይህ የእምነት ትምህርትና እውቀት ጸጋና በረከት ሁሉ ቃለ እግዚአብሔርን በመስማት ብቻ ስለሚገኝ ለመዳናችን የቃሉ አገ ልግሎት ማለት ስብከተ ወንጌል ብቻ እንጂ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ለምን ያስፈልጋሉ። በማለት የሚጠይቁ ወገኖች ይኖራሉ እርግጥ ነው ከሁሉ በፊት ለመዳናችን እምነት ያስፈልጋል እምነት ደግሞ ከመስማት ይመጣል መስማት ደግሞ ከእግዚአብሔር ቃል ነው ማለት በስብከተ ወንጌል ነው ሮሜ ነገር ግን መዳኖችን የወንጌልን ቃል በመስማት ይጀምራል እንጂ በዚህ አያከትምም ይህ በመጀመሪያ ደረጃ የሚሰጥ ሳላመኑት ሁሉ ለፍጥረት ሁሉ የሚሰበክ የወንጌለ መንግሥት ጥሪ የንስሐ ጥሪ ወደ ክርስቶስና ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ማቅረቢያ ነው በዚህም የመጀመሪያ ሥራ እግዚአብሔር የመረጣቸውን ሁሉ በሀብት ስቦ በረድኤት አቅርቦ ወደራሱ ይጠራቸዋል ያቀርባቸዋል የተጠሩት ደግሞ በንዑሰ ክርስቲያንነት ደረጃ ቃለ እግዚአ ብሔርን እየሰሙ ከቆዩ በኋላ አዲስ ሕይወትን እንዲቀዳጁና ጸጋ መንፈስ ቅዱስን እንዲያገኙ የሚያበቃቸው ሌላ መንገድና ሥርዓት አሰፈላጊ ስለሆነ ጌታ ራሱ አዘጋጅቶላቸዋል ሁላችንንም በዚህ መንገድ እንድንሄድ አዞናል መን ገድ የተባለውም ቃሉን ሰምቶ መፈጸምና ያዘዘንን የቤተ ክርስቲያን ምሥጢራት ሁሉ መፈጸም ነው መዳናችን በአንድ ወቅት ተፈጽሞ የሚያልቅ ነገር አይደለም የራሳ ችንና የሌሎች ክርስቲያኖችን የሕይወት ታሪክ ብንመረምር የመዳናችን ጉዳይ እስከ ሞት ድረስ በሂደት ላይ የሚገኝ መንፈሳዊ ትግል ያለበት ክርስቲያናዊ የሕይወት ጉዞ ስለሆነ በመንገዳችን ላይ መውደቅና መነሣት የማይቀር ነው ምክንያቱም ጌታ እንዳለው መሰናክል ግድ ሳይመጣ አይቀ ርም ሉቃ ስለዚህ ለመዳናችን በርትተን መሥራት አለብን ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ የራሳችሁን መዳን ፈጽሙ ፊልጵ እንግዲህ ቃሉን ሰምተን በማመንና ቃሉን በመፈጸም እንጽና ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ ያፅ ስለ ምሥጢራት በቃሉ የታዘዘውን እንፈጽም ምሥጢራት ሁሉ ያለ ጸሎት እንደማይፈጸሙ እንደዚሁም ምሥጢራት በምንም ሁኔታ ያለ ቃለ እግዚአብሔር ብቻቸውን አይፈጸሙም ስለዚህ ቃለ እግዚአ ብሔር ጸሎትና ምሥጢራት የማይለያዩ የአንድ አካል ክፍሎች ስለሆኑ ሦስቱንም መፈጸም ክርስቲያናዊ ግዴታችን ነው እንግዲህ ከሦስቱ አንዱ ብቻ ማለት ቃለ እግዚአብሔርን መስማት ብቻ ይበቃኛል የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ብቻ ያስፈልገኛል ሌላው ምንም አ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛፀመናትና ክርስቲፀናዊ ሕይፎዉት ያደርግልኝም ብሉ በግል ውሳኔ በቤተ ክርስቲያን ከሚፈጸመው ጸሎትና ምሥጢራት ራስን ማግለል አደገኛ ሁኔታ ነው በመጀመሪያ የክርስቶሰን ትእዛዝ ማቃለል ይሆናል ሁለተኛ ከክርስቶስ አካል ከሆነችው ከቤተ ክርስቲያን ውጭ በመሆን ከአንዱ ቸር ጠባቂያችን ከክርስቶስና ከመንጋው ተለይቶ መቅረትን ወይም መባዘንን ያስከትልብናል ከክርስቶስ መጋቢነትና ጥበቃ ውጭ በመሆን በዚህ ሆነ በኋለኛው ዓለም ለሚመጣው አኣደጋ ሁሉ እን ጋለጣለን ለምሳሌ አንድ ሰው የአንድ ሀገር ዜጋ ሆኖ ሳለ በብቸኝነት የሀገሩን ሕግ ትቶ ኅብረተሰቡን ረስቶ ራሱ በራሱ በግለኝነት ላወጣው ሕግ እንጂ ለሌላ አልገዛም ብሎ በሀገር ውስጥ መኖር እንደማይቻል እንዲሁም አንድ ክርስቲያን የሀገረ እግዚአብሔር ዜጋ ሆኖ ከቤተ ክርስቲያን ሕግ ውጭ መኖር አይቻለውም ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያን የሰማያዊውን የእግዚአብሔር መንግሥት ወክላ የምትሠራ እርሷ ናትና በየጊዜው የምታውጀው ሕጓም የመን ግሥተ ሰማያት ሕግ ነውና ከቤተ ክርስቲያን የጸሎት ሕይወት መለየት ሦስተኛ ችግርን ያስከትላል ይኸውም በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን በኩል ከሚገኘው ጸጋ በመራቆት ክርስቲያናዊ ሕይወታችን እየጐደፈ ይሄደል በመጨረሻም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋና ረድኤት እየተለየን ከቀቢጸ ተስፋ እንደርሳለን ስለዚህ ከዚህ ሁሉ ለመዳን ሦስቱንም ሳንነጣጥላቸው ሁሉንም በአግባቡና በሥርዓቱ ብንፈጽማቸው እንጠቀማለን እንጂ አንጐዳም ቃለ እግዚአብሔርን በመሰማት ጸሎትን በማድረግና ምሥጢራትን በመፈጸም ሕይወታችንን ከቤተ ክርስቲያን ሕይወት ጋር አንድ በማድረግ ብንኖር የክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔር ፍቅር የመንፈስ ቅዱስ ኅብረት ከእኛ ጋር ይሆናል ለመዳናችን ጥምቀትን እንድንፈጽም ወንጌልን ለዓለም ሁሉ እንዲያስተምሩ ያዘዘ ክርስቶስ የተቀደሱ ምሥጢራትንም እንዲፈጽመ ሐዋርያትን አኳቸዋል እንግዲህ ሂዱና አ ሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችሁ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አ ድርጓቸው እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ ማቴ በማለት ጌታችን ያዘዘው ማስቲማርን ብቻ ሳይሆ ማጥመቅንም ጭምር እንደሆነ ግልጽ ነው ስለዚህ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ክርስቶስ ከእኛ ጋር ማለት ከቤተ ክርስቲያን ጋር ሁልጊዜ እንዳለ በማመን ወን ጌልን በማስተማርና ምሥጢረ ጥምቀትን በመፈጸም ትእዛዙን እንጠብቃለን ያመነ የተጠመቀም ይድናል ማር በማለቱ ደግሞ በምሥጢረ ጥምቀት ከክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ተካፋይ መሆናቸውን በማመን ለተጠመቁ ሁሉ የክርስቶስ የማዳን ጸጋው እንደሚሰጣቸው ያመለክታል ጌታም ራሱ መጠመቁ እኛ እንድንጠመቅ ለማድረግና የእርሱንም የጸጋ ምሥጢራት ለመቀበል እንድንበቃ የሚያስችል ሥርዓት መሥራቱን መዘንጋት የለብንም ጌታ ሥራውን የጀመረው በጥምቀቱ ነው ጥምቀቱም እኛን ከኃጢአትና ከሞት ያዳነበት የሞቱና የትንሣኤው ምሳሌ ነው ሉቃ ስለዚህ ይህን አምነን በምንጠመቅበት ጊዜ በሕማሙና በሞቱ የተገኘው የማዳን ሥራ ፍሬ ጸጋው ይደርሰናል ይህም ማለት በኃጢአት ከመጣብን ከመርገመ ሥጋና ከመርገመ ነፍስ ፈጽሞ እንድናለን ሰው ሁሉ ሕፃናትም ጭምር በጥንተ አብሶ ከመጣው መርገምና ፍዳ ነፃ አይደሉም በጥንተ ተፈጥሮ የነበረው ጸጋ ስለ ተገፈፈ በሐዲስ ተፈጥ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛፀማኖትና ክርስቲያናዊ ሕይደዉት ሮ የመዳን ጸጋ ያስፈልጋቸዋል የመጀመሪያዎቹ ወሳጆቻችን በተሳሳቱ ገዜ የ ነበራቸውን ጸጋ አጡ ከቀደመው ክብራቸው ወረዱ በልዩ ልዩ መከራ ውስጥ ወደቁ በክርስቶስ ሞት በተደረገው እርቅ ደግሞ አዳምና ሔዋን ወደ ጥንት ቦታቸው እንዲመለሱ ተፈቅዶላቸው የአዳምና የሔዋን ልጆችም እንደየ ጸታቸው በአርባ በሰማንያ ቀናቸው ሲጠመቁ በዘር ከወረደው መርገም ይገላገላሉ የቀደሙ ወሳጆቻችን ያስወሰዱት የጸጋ ልጅነት በጥምቀት ይመለስላቸዋል ከቀ ኑ አቆጣጠር በቀር ይህ በሁሉ የታወቀ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ነው በማለት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ሰለ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የጻፉትን ተመልከት ርተ ሃይማኖት ርትዕት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕ ዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትቤቶች መምሪያ በማኅበረ ቅዱሳን ትምህርት ክፍል በየሰንበት ትቤቶች ለሚማሩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማስተማሪያ የተዘጋጀ ዓም ገጽ በኃጢአታችን ምክንያት ከመጣብን የፍርድ ቅጣት በውኃ በመጠመቅ መዳናችንን ለማስረዳት ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ከብሉይ ኪዳን ታሪክ በመጥቀስ ታሪክና ምሳሌውን ከአማናዊው ጋር በማገናዘብ እንደሚከተለው ተርጉሞ ያስረዳናል ጥቂቶች ማለት ስምንት ነፍስ በውኃ የዳነበት መርከብ ሲዘጋጅ የእግዚአ ብሔር ትዕግሥት በኖኅ ዘመን በቆየ ጊዜ ቀድሞ አልታዘዙም ይህም ውኃ ደግሞ ማለት ጥምቀት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል ካለ በኋላ በውኃ ተጠምቆ መዳን ምን ማለት እንደሆነ ሲገለጽ የሰውነትን እድፍ ማስወገድ አ ይደለም ለእግዚአብሔር የበጎ ኅሊና ልመና ነው እንጂ ይህም በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ነው ብሏል ኛ ጴጥ የክርስትና ጥምቀት እንደ መጥምቁ ዮሐንስ ጥምቀት አይደለም የክርስትና ጥምቀት በውኃ ብቻ አይደለም በውኃ መጠመቅ ማለት በመንፈስ ቅዱስ መጠመቅ ማለትም ነው በውኃና በመንፈስ በምንጠመቅበት ጊዜ ከኃጢአታችን ድነን አዲስ ልደትን እናገኛለን የክርስቶስ ትንሣኤ ተካፋይ እን ሆኖለን ዮሐ ሮሜ የተጠቀሰው ሐዋርያ እንዳለው ጥምቀት የ ሰውነትን እድፍ ለመታጠቢያ አይደለም በውኃና በመንፈስ ማለት በክርስቶስ መንፈስ በመጠመቃችን ከሙታን ከተነሣው ክርስቶስ ጋር አንድ መሆናችን ትንሣኤ ልቡና በጎ ኅሊና አዲስ ሕይወትን ከእርሱ እንደምናገኝ ያስረዳናል በጥምቀት መዳን ማለት በዚህና በመሳሰሉት ይተረጐማል እንግዲህ ጥምቀት የክርስትና እምነት ምሥጢር ነው የመዳናችንም ጸጋ ነው የመዳናችን ምሥጢር በክርስቶስ ነው ጥምቀት ደግሞ ከአዳኛችን ጋር አንድ ያደርገናል ሮሜ ከአዳኞችን ከመድኃኒታችን ጋር አንድ ከሆንን ከእርሱ የመዳንን ጸጋ ከኃጢአት ቁስል የመፈወስ ሀብትን እናገኛለን ስለዚህ ጥምቀት እኛን ከክርስቶስ ጋር አንድ በማድረግ የደኅንነትን ጸጋ የሚያ ሰጠን በግብረ መንፈስ ቅዱስ የሚከናወን ታላቅ ምሥጢር ነው ተ ዓርቡ የማዳን ሥራ በሥጋውና በ በዕለተ ዓርብ ባደረገው ተልእኮ ጌታችን ለዓለም ሁሉ ለአንዴና ለዘላለም የፈጸመውን የማዳን ሥራውንና አምላካዊ ጸጋውን እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ በየዘመኑ የሚነሙት ትውልድ ሁሉ በቀላሉ አግኝተው የሚድኑበትን መንገድ አ ዘጋጅቷል ይህንንም የማዳን ሥራ የሚያከናውኑለትን ሐዋርያቱንና ተተኪዎቻቸውን ቤተ ክርስቲያኑንና ምሥጢራቱን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል መሥርቷል አደራጅቷል ዛሬም የማዳን ሥራውን የሚሠራ እርሱ ራሱ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛደማናትና ክርስቲያናዊ ሕይወዉት ባለቤቱ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረሰ ከቤተ ክርሰቲያኑ ጋር በመሆን ነው ማቴ በአርአያውና በአምሳሉ በክብር የፈጠረው ሰው የፈጣሪውን ቃል ኪዳን አፍርሶ በኃጢአትና በጨለማ ወድቆ በነበረ ጊዜ ጌታ የወደቀውን ሰው ወደ ቀደመ ክብሩ ለመመለስ ሰው በመሆን በሥጋ መጥቶ በሥጋው የበደለኛውን የሰውን ሕማምና ሞት ተቀብሎ በሞቱ ሞትን ደምስሶ በትንሣኤ ው አዲስ ሕይወትን በመስጠት አዳነው ስለዘህ ጉዳይ ነገረ መስቀሉንና ትን ሣኤውን በገለጽንበት አንቀጸ ሃይማኖት በክፍል አንድ ተመልክተናል ከዚህ ደግሞ የዕለተ ዓርቡ የማዳን ሥራው እስከ ዕለተ ምጽአት ለሚነሙት ሁሉ የመዳናቸው ምሥጢር እንዴት በሚታይና በሚጨበጥ መንገድና ሁኔታ በቃሉ አገልግሎትና በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚፈጸም ለማስረዳት እንሞክራለን ቀድሞውንም በማይታየው ባሕርዩ ቃለ እግዚአብሔር ወልድ እኛን ለማዳን ወደዚህ ዓለም ሲመጣ በሚታይና በሚጨበጥ መንገድ በሥጋው ተገልጾ ነው አሁንም እንደ ቀድሞው ለእኛ እንደሚስማማ በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን አማካይነት በተለይም በምሥጢረ ቁርባን በሚታይና በሚጨበጥ መን ገድ የሕይወት ምግብ ሆኖ እኛን ለማዳን ቀርቧል የምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንም ትርጉም ይኸው ነው በሜታየው ነገር የማይታየውን ጸጋ የምናገኝ በት መንገድ ነው ለአንዴና ለዘላለም የተፈጸመው ታላቁ የዕለተ ዓርብ የማዳን ሥራው ለዓለም ሁሉ እንዲዳረስ የምሥራቹን ቃል ወንጌልን እንዲያስተምሩ በስሙ ንስ ሐና የኃጢአት ሥርየትን እንዲሰብኩ ምሥጢራትንም እንዲፈጽሙ ጌታ ሐዋርያትን አዚቸዋል ማቴ ኛ ቆሮ ሉቃ ስለዚህ ነው ሐዋርያት ቃሉን ካስተማሩና ካሳመኑ በኋላ በማጥመቅ እጃቸውን በመጫን በማቁረብ የጸሎትና የቃሉን አገልግሎታቸውን በትጋት ይፈጽሙ እንደ ነበር የተጻፈው የሐዋ ይኸን ሁሉ ከጌታ ተምረውታል በተለይም ስለ ምሥጢረ ቁርባን ሰፋ ያለ ትምህርት ተሰጥቷቸዋል ያያጋሟጭሪ ዕቋ ወረደው ይይይወጋም ዳራ ምሥጢረ ረዶሒፈሪ ሥርዓተ ቁርባንን ካቋቋሪሠሀበት ከስቅለት ዓርብ ዋዜማ ከምሴተ ኀሙስ በፊት ሁለት ዓመት ያህል ቀደም ብሎ ከሰማይ ስለ ወረደው የሕይወት እንጀራ ምሥጢር ስለ ሥጋውና ደሙ ምሥጢር ጌታ በሰፊው ለሕዝቡ አስተምሯል ይህም በወንጌለ ዮሐንስ ምዕራፍ ስድስት ተመዝግቦ ይገኛል በምዕራፉ መጀመሪያ ላይ እንደ ተጻፈው ጌታ አምስቱን የገብስ እንጀራና ሁለት ዓሣ በተአምራት አበርክቶ አምስት ሺህ ሕዝብ ያህል እንደ መገበ ይገልጻል ይህም ተአምራዊ ድርጊት ለምሥጢረ ቁርባን ትምህርት በር ከፋች ማለት መግቢያ ሆኗል በዚህ መነሻነት የተበረከተውን እንጀራ የበሉት ሰዎች በማግሥቱ ጌታን ፈልገው አገኙት ሕዝቡም ጌታን የፈለጉበት ምክንያት ስለበሉና ስለጠገቡ እንጂ ተአምራቱን ምልክቱን በማየት እንዳልነበረ ማእምረ ኅቡዐት ጌታ ገልጸ ነግሯቸዋል ዮሐ ቁም ነገሩ ይህን ተአምር የፈጸመው እርሱ ማን እን ደሆነ መመርመርና በእርሱም ማመን ነበር የእነርሱ ፍላጉት ግን ማንም ይሁን ማን የሚያበላቸውና የሚያጠግባቸው መሪ ንጉሥ መፈለግ እንጂ የተአ ምራቱን የምልክቱን ትርጉም ከማወቁና ከማመኑ አልነበረም ዮሐ ስለዚህ ጌታ ለሚጠፋ መብል አትሥሩ ነገር ግን ለዘላለም ሕይወት ለሚኖር መብል የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ ሥሩ የእግዚአብሔር ሥራ እርሱ በላከው እንድታምኑ ነው አላቸው ዮሐ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይማናትና ክርስቲፀይናዊ ሕፎወት እነርሱ ግን ያዩትን ምልክት ትተው ሌላ ምልክት ፈለጉ ሥራህን አይ ተን እናምንብህ ዘንድ ምን ምልክት ታሳየናለህ። ትምህርተ ዛሀሀዛናትና ከርስቲያናዊ ሕሯወዉት ስላልገባቸውና ስላስጨነቃቸው ተሰናክለውበታል ጌታ በሥጋው ወደ ሰማይ ያረገው የዕለተ ዓርቡን ተልአኮ ከፈጸመ በኋላ ነው ከሰማይ የወረደውና ሥጋ የለበሰው ኃጢአትንና ሞትን አስወግዶ የዘላለም ሕይወትን ሊሰጠን ስለሆነ በመስቀል ላይ ሥጋውን ቆርሶ ደመን አፍ ስሶ የመስቀልን መሥዋዕትነት ተቀብሏሷል ሥርየተ ኃጢአት አግኝተን መዳናችንና የዘላለም ሕይወት መውረሳችን በመስቀል ላይ ለቤዛ ዓለም በተሠዋው ሥጋና ደም ስለሆነ ሥጋው እውነተኛ የሕይወት እንጀራ ደሙም እውነተኛ የሕይወት መጠጥ መሆኑን አምነን እንድንቀበለው ጌታችን ያስተማረው ገና ከጥምቀቱ በኋሳ በነበረው በሁለተኛው የአይሁድ ፋሲካ ነበር ዮሐ ስለ ሕማሙና ሞቱ ስለ ትንሣኤውና ዕርገቱ ደቀ መዛሙርቱ ገና የማያውቁ ሰለሆነ ስለ ሕይወት እንጀራ ጌታ ያስተማረው ሁሉ እጅግ አስ ጨንቋቸው ነበር ከዚህም የተነሣ ከደቀ መዛሙርቱ ብዙዎቹ ወደ ኋላ ተመለሱ ወደፊትም ከእርሱ ጋር አልሄዱም ዮሐ አሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ግን በእምነት ጸንተው የሕይወት ቃል ከእርሱ ጋር ብቻ መሆኑን መሰክረው ከእርሱ አልተለዩም ነበር ዮሐ ይእሪሮወሦ ዳራ ምሥለ ጸታሥሦ ንሙ ስለ ሥጋውና ደሙ ጌታ የተናገረውን ቃል ሁሉ ሐዋርያት ቢያም ኑም ሥጋው እውነተኛ መብል ደሙም እውነተኛ መጠጥ ሆኖ እንዴትና መቼ እንደሚያገኙት ገና አያውቁም ነበር ጌታ ግን መዋዕለ ትምህርቱን ማለት የሦስት ዓመት ከሦስት ወር ሥራውን ጨርሶ የዕለተ ዓርቡን ተልእኮ የሚፈጽምበት ሰዓትና ጊዜው ሲደርስ ምሥጢሩን ገለጸላቸው በቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት አቆጣጠር አራተኛው የአይሁድ ፋሲካ ሲደርስ ጌታ ከዚህ ዓለም ወደ አብ የሚሄድበት ሰዓት እንደ ደረሰ አውቆ በዚህ ዓለም ያሉትን ወገኖቹን የወደዳቸውን እስከ መጨረሻ ወደዳቸው ዮሐ ለውጮቹ ሳይሆን ለእነዚህ ማለት ለሐዋርያቱ በመጀመሪያ የመንግሥተ ሰማያትን ምሥጢር በኋላም የሥጋውንናኖ የደሙን ምሥጢር ገልጸላቸዋል ማቴ ማር ስለ ኃጢአታችን ሥርየት በስቅለት ዓርብ ለዓለም ሁሉ መድኃኒት እንዲሆን በመስቀል ላይ ለአንዴና ለዘላለም መሥዋዕ ት አድርጎ ያቀረበውን ሥጋውና ደሙን ሁልጊዜ እንዲያገኙትና በእውነተኛ የሕይወት ምግብነት እንዲቀበሉት ሕግና ሥርዓትን ሠርቶላቸዋል ይህንንም እንደ አይሁድ ቀን አቆጣጠር በዕለተ ዓርብ የመጀመሪያው ክፍለ ጊዜ ማለት በእኛ አቆጣጠር በስቅለት ዋዜማ በጸሎሉተ ኀሙስ ማታ ሥጋውን እውነተኛ ምግብ ደሙንም እውነተኛ መጠጥ አድርጎ ሰጥቷቸዋል በዚያች ምሽት የኦሪትን የእንስሳት መሥዋዕት የአይሁድን የፋሲካ እራት ለመጨረሻ ጊዜ ፈጽሞ አማናዊውንመዳንንና የዘላለም ሕይወትን ያገኘንበትን መሥዋዕት የራ ሱን ሥጋና ደም አቅርቦላቸዋል ይህንንም ታላቅ ሥራ ያከናወነው ኅብስ ቱን አንሥቶ ባርኮ ቆርሶ ይህ ሥጋዬ ነው ብሉ ጽዋውንም እንደዚሁ አንሥቶ ባርኮ ይህ በመሰቀል ሳይ ለኃጢአት ሥርየት የሚፈሰው ደሜ ነው ሁላችሁም ከዚህ ጠጡ ባላቸው ጊዜ ነበር ማቴ ጌት በሥጋው መሥዋዕት ነት በሞቱ ያዳነን መሆኑን አያሰብን ይህን የሠራልንን ሕግና ሥርዓት እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እንድናደርገው አዞናል ሉቃ ኛቆሮ ስለዚህ ዛሬ ከቤተ ክርስቲያን በአርአያ ኅብስት የምንቀበለው የክርስቶስ ሥጋ በአርአያ ወይን የምንቀበለው የክርስቶስ ደም መሆኑን አምነን የመዳናችን ምሥጢር የሚሜፈጸምበትን አምላካዊ ጸጋ እናገኛለን እንግዲህ መዳናችን በጌታ ሥጋ ነው ምክንያቱም ይህ አካላዊ ዝነገነገርህኽ ትምህርተ ዛደማናትና ክርስቲያናዊ ሕጾዉት ቃልን የተዋሐደ ሥጋ ነው የኃጠአታችንን የሞት ቅጣት የወሰደው ይህ የጌታ ሥጋ ነው ሞትን ሽሮ ከመቃብር የተነሣው ታዲያ ከዚህ ከመለኮታዊ ሥጋ ጋር አንድነት ከሌለን አንድንም ስለዚህ በጥምቀት ከጌታ ጋር አንድ ሆነናል በመንፈስ ቅዱስ ኃይልም የሞቱና የትንሣኤው ተካፋይ ለመሆን ችሎታውን ሰጥቶናል እንደዚሁም በቅዱስ ቁርባን ከእርሱ ጋር አንድነታችንን በማጽናት ሕይወትንና ትንሣኤ ዘለክብርን በማግኘት ከእርሱ ጋር እንኖራለን ምክን ያቱም ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ ብሏልና ዮሐ አለበለዚያ ሥጋውና ደሙን ካልተቀበልን ሞት እንጂ ሕይወት የለንም ምክንያቱም የወልደ እጓለ እመሕያው ክርስቶስን ሥጋ ካልበላችሁ ደሙንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም ተብሎ ተጽፏልና ዮሐ እንግዲህ ብዙዎቹን የጌታን ደቀ መዛሙርት ያስጨን ቅ የነበረው ከሰማይ የወረደው የሕይወት እንጀራ ምሥጢር በጸሎተ ኀሙስ ማታ በተፈጸመው በቅዱስ ቁርባን ሥርዓት በእምነት ለጸኑት ለአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ብቻ እንዲታወቅ ሆነ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የዕለተ ዓርቡ የማዳን ሥራ በሥጋውና በደሙ ምሥጢር በሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን አማካይነት እን ዲቀጥል ተደረገ የሐዋሥራ ቀራያዕ ዌረያ ያሥሥጢራፖ ይዶታ መያሇባናፖሦው የምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ሁሉ የበላያቸው መክብባቸውና መፈጸሚያቸው የሆነው ቅዱስ ቁርባን በጌታ ትእዛዝ ጸሎተ ኀሙስ ማታ መመሥረቱ ከሳይ ተገልጧል ሉቃ ምሥጢረ ቁርባን ከሁሉ በላይ የሆነበት ምክንያት ጌታ የሰውን ልጆች ለማዳን በዕለተ ዓርብ በመሰቀል ላይ ሥጋውን በመቁረስ ደሙን በማፍሰስ ካሣ የከፈለበትን የማዳን ሥራውን የፈጸመበትን ሁኔታ የሚያረጋግጥና የሚመሰክር ከመሆኑ ጋር አማኞች ከሥጋውና ከደሙ ተካፋይ እንዲሆኑ በማብቃት የሕይወትን ጸጋ እንዲቀበሉ ስለሚያደርግ ነው ስለዚህም የሌሎቹ ምሥጢራት ሁሉ በቅዱስ ቁርባን አማ ካኝነት የምሥጢራቸውን ትርጉምና ፍጻሜ ያገኛሉ ምሥጢረ ቁርባን የሚከናወንበት ጸሉተ ቅዳሴ እጅግ የከበረና ለክርስቲያኖች ሁሉ ጸጋና በረከትን የሚያሰጥ ነው የዝግጅቱ ክፍል ሳይቆጠር ጸሎተ ቅዳሴ ሁለት ዐበይት ክፍሎች አሉት የመጀመሪያው ቃለ እግዚአ ብሔር የሚሰማበትና ትምህርተ ወንጌል የሚሰጥበት ጊዜ ነው ሁለተኛው መሥዋዕተ ቁርባን የሚፈጸምበት ነው ሰለዚህ ጸሎተ ቅዳሴ ሥርዓተ አም ልኮት ብቻ ሳይሆን ስብከተ ወንጌል የሚካሄድበት ክርስቲያናዊ ፍቅርና ሰላም የሚመነጭበት መልካም ሥራ የሜወጠንበትና የሚፈጸምበት በመሆኑ ቤተ ክርስቲያን ከምታከናውናቸው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶች ሁሉ ከፍተ ኛውን ቦታ ይዞ ይገኛል በኦሪቱ ሥርዓት በቤተ መቅደስ ይፈጸም የነበረው የብሉይ ኪዳን መሥዋዕት በቅዱስ ቁርባን በመተካቱ ለሐዲስ ኪዳኑ የአምልኮት ሥርዓትና ምሥጢር ሁሉ መሠረት ከመሆኑም ጋር ጌታ ዳግመኛ እስኪመጣ ድረስ የክርስቶስ የሞቱና የትንሣኤው ምሰክር ሆኖ ይቆያል መሥዋዕት ከሆ ነልን ከሐዲስ ኪዳኑ የፋሲካ በግ ከክርስቶስ ጉን በዕለተ ዓርብ የፈሰሰው ደምና ውኃ የመዳንና የጽድቅ ጸጋ ምሥጢራት ሁሉ ምንጭ በመሆኑ ይህን የመሥዋዕ ት ምሥጢር በምትፈጽም ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ ጸጋ በብዛት ይሞላባታል የወንጌልን ቃል አምነው ምሥጢረ ቁርባንን የሚቀበሉ አማኞች ሁሉ የክርስቶስ የጸጋው ምሥጢር ተካፋይ ይሆናሉ እነርሱ ጌታ ኅብስቱን አንሥቶ ባርኮና ቆርሶ ለደቀ መዛሙርቱ ሲሰጣቸው እንካችሁ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛፎማናትና ክርስቲያናዊ ሕይዉት ብሎ የተናገረውን እንዲሁም ጽዋውን አንሥቶና አመስግኖ ሲሰጣቸው ሁላችሁም ከእርሱ ጠጡ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የሐዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው ያለውን ቃለ ወንጌል ማቴ አምነው ክርስቶስ በመካከላቸው ተገኝቶ ዛሬውኑ እንደ ፈጸመው አድርገው በመቀበላቸው በእውነት የመዳኑ ጸጋ ለእነርሱ ደርሷቸዋል ሥጋዬን የበላ ደሜን የጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው የተባለውም በእነርሱ ላይ ይፈጸማል ዮሐ ነገር ግን ሳያምኑ የሚቀበሉትና በመጠራጠር የሚተውት ሁለቱም ክመዳን ጸጋ ውጭ ናቸው ምክንያቱም እነርሱ ገና በምሥጢረ ሥጋዌ አላመኑም ማለት ነው ጸጋ እግዚአብሔር ለሰዎች ልጆች የተሰጠው ቃለ እግዚአብሔር ወልድ በሚታይና በሜዳሰስ በሥጋ ሰውነት በመምጣቱ ነው በሰውነቱ ሕማማትን በመቀበል እኛን በማጽደቅ በቅዱስ ደሙ ፈሳሽነት ከኃጢአታችን በማንጻትና ከእግዚአብሔርም ጋር በማሰታረቅ ጸጋ በጸጋ ላይ እንድንቀበል አ ብቅቶናል እንግዲህ በሚታይና በሚዳሰሰ ሰውነቱ የማይታየውን መለኮታዊ ጸጋውን እንዳጐናጸፈን እናስተውል እንዲዚሁም ዛሬ አካሉ በሆነችው ቤተ ክርስቲያን አማካይነት በሚታዩና በሚዳሰሱ ምሥጢራቱ የማይታየውን ረቂቁን ጸጋ መንፈስ ቅዱስን እንቀበላለን እንግዲህ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ሥጋ ከመልበሱ የተነሣ ጸጋ እግዚአ ብሔር በሥጋውና በደሙ እንደመጣልን እንረዳለን ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው ሥጋዩ እውነተኛ መብል ደሜም እው ነተኛ መጠጥ ነውና ዮሐ የተባለውን የጌታን ቃል እንዴት በተግባር እንደምናውለው እስኪ በጽሞና እናስብ። መልስ በጸሎተ ኀሙስ ማታ ጌታ ምሥጢረ ቁርባንን በመሠረተ ጊዜ የትና እንዴት እንደሚገኝ ለሐዋርያት አስተምሯቸዋል ሉቃ ይኸውም ዛሬ በቤተ ክርስቲያናችን የሚገኘው ለሐዋርያት የተሰጠው የቅዱስ ቁርባን ምሥጢር ስለሆነ ምእመናን ንስሐ እየገቡ የጌታን ሥጋ እየበሉ ደሙንም እየጠጡ እንደ ወንጌሉ ቃል የዘላለም ሕይወትን ጸጋ ያገኛሉ ይህ ምሥጢር የጸጋ ሁሉ ምንጭ ስለሆነ ሌሎቹ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ሁሉ በሥጋው በደሙ ምሥጢር አማካኝነት ይፈጸማሉ ስለዚህም እያንዳንዱ ምሥጢረ ቤተ ክርስቲያን ከጌታ ሥጋና ደም ጋር በመንፈሰ ቅዱስ ኃይል የተያያዘና ከጌታ ሕማምሞትና ትንሣኤ ጋር የተዛመደ ስለሆነ የራሱ የሆነ ልዩ ልዩ ጸጋን የመሰጠት ችሉታ አለው ስለ ተቀደሱት ምሥጢራት እንደ ዓይነታቸውና እንደ ሁኔታቸው በየስማቸው የተገለጹ ስለሆነ በቦታቸው ላይ እንመለከታቸዋለን ፖዕፉም መፊዕ ቀዱዴዕ ይጠናሃራልጳ በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የሚገኘው ጸጋ ለተስፋችን ሕይወት ይሰጠዋል ያሳድገዋል በኃጢአት የተነሣ በልዩ ልዩ ፈተናም ብንወድቅ እንኳ በምሥጢረ ንስሐ አማካይነት ተሰፋችን ይታደሳል ጌታ ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይዐት አለው ካለ በኋላ ይቀጥልና እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ ዮሐ በማለቱ ተሰፋ ትንሣኤ በምሥጢረ ቁርባን እንደሚሰጥ ያመለክታል በጸሎተ ሃይማኖት የሙታንን መነሣት ተስፋ እናደርጋለን የሚመጣውንም ሕይወት ለዘላለሙ አሜን በማለት የገለጽነው እምነትና ተስፋችን ከላይ በጠቀስነው የወንጌል ቃልና ለቅዱስ ቁርባን ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይማናትና ክርስቲያናዊ ሕዩዉት በተሰጠው ቃል ኪዳን አማካኝነት ይጸናል ይታተማል ተስፋ መንግሥተ ሰማያትን ጸጋ መንፈስ ቅዱስን የምናገኘው በእምነታችን ጸንተን በቤተ ክርስቲያን የሚፈጸሙትን ልዩ ልዩ ምሥጢራት በመቀበል እንደሆነ እን ረዳለን ጸጋ መንፈስ ቅዱስም በክርስቶስ ለተሰጠን ተስፋችንና ለዘላለም ርስታችን መያዣ ዐረቦን ነው ኛ ቆሮ ኤፌ እንግዲህ በመንፈሰ ቅዱስ ኃይል በምሥጢራት ባገኘነው ጸጋ ተነሣስተን ለጸሎት እንተጋለን ይልቁንም ዘወትር የአቡነ ዘበሰማያትን ጸሎት በማድረስ ከእምነታችን ከተስፋችንና ከፍቅራችን ባለቤት ከሆነው ከእግዚአ ብሔር ጋር በመንፈስና በእውነት በመገናኘት የተስፋችንን ቃል ኪዳን እናጠናክራለን በተስፋውም እየተደሰትን ፈተናና መከራን እየታገሥን የሚገባንን ለመሥራት በፍቅሩም ሆነን መልካሙን ሥራ ለማከናወንና ዘወትር ለመታገል የሚያበቃንን የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ እርሱ ባለቤቱ እን ዲጨምርልን እንደፈቃዱ እየኖርን በተአምኖ ብንለምነው አይነሣንም ዖሄፖ ያይያሪሪኖ ያማያሃ ሥራው ያምሥጪዉጪራፖ ይፖ ይረታ ጄ ያጋ ሪፇምጳሷ ለጸሎትና ወንጌልን ለማስተማር ከመትጋታቸው ጋር ሐዋርያት ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን ይፈጽሙ እንደ ነበር ተገልዷል ይህም ማለት በየጊዜው ያጠምቁና ያቆርቡ ነበር ማለት ነው የሐዋሥራ ጌታ የማዳን ሥራውን የፈጸመው እንደ መሥዋዕትና እንደ ሊቀ ካህናት በመሆኑ ስለ ነበር ሐዋርያትም የርሱን መሥዋዕት በማቅረብ የእርሱን የክህነት ሥልጣን ወክሎ በመሥራት የማዳን ጸጋውን ለብዙዎች አዳርሰዋል ዛሬም ይህንን ሥራ በመቀጠል ቤተ ክርስቲያን ወንጌልን ከመስበክ ጋር ሲወርድ ሲዋረድ በመጣላት የክርስቶስ የክህነት ሥልጣን መሠረት የምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን ጸጋ በክርስቶስ ስም ላመኑት ሁሉ ለማዳረስ ትጥራለች ኃጢአትን እንድታስተሠርይ ጌታ በሰጣት ሥልጣን በስሙም ንስ ሐና የኃጢአት ሥርየትን በመስበክና ልዩ ልዩ ምሥጢራትን በመፈጸም ተነሳ ሕያንን ከኃጢአት እሥራት በመፍታት ቤተ ክርስቲያን ሰውን ከእግዚአብሔር ታስታርቃለች ሰውና ሰውንም በፍቅር ታስተባብራለች ዮሐ ሉቃ የማስታረቅም አገልግሉት ለቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ካህ ናት ተሰጥቷል በሐዲስ ተፈጥሮ የሆነው ሁሉ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስ ታረቀን የማስታረቅም አገልግሉት ከሰጠን ከእግዚአብሔር ነው እግዚአ ብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከእርሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ እን ግዲህ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማለድ ስለ ክርስቶስ መልዕክተኞች ነን ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን ስለ ክርስቶስ እንለምናለን ይህንን ቃል ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለራሱና ለቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች በተ ሰጠው ሥልጣን መሠረት ተናግሮታል ኛ ቆሮ የማስታረቁና የማዳን ሥራው እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እንዲቀጥል ጌታ ለሐዋርያቱና ለተተ ኪዎቻቸው በጸጋ መንፈስ ቅዱስ የክህነትን ሥልጣን ሰጥቷቸዋል ምክንያቱም በእነርሱ በሚፈጸመው ምሥጢራት በጸሎትና በቃሉ አብል ግሎት ኣማካይነት የመዳን ጸጋ ለዓለም ሁሉ እንዲዳረስ ነው ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛፀማናትና ከርስቲያናዊ ሕፀወት ለ ስለ ጸጋና ስለ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የጸጋ ትርጉም ምንነቱና ዓይነቱ ጸጋ ምን ማለት እንደሆነ ከማየታችን በፊት ጸጋ ከየት መጣ። ጸጋን ከመሠረቱ ልንረዳው የምን ችለው እኛን ለማዳን ሲል ክርስቶስ ሰው በመሆኑ በሕማሙና በሞቱ ምክን ያት ኃጢአትን ደምስሶ ሰውን ከእግዚአብሔር በማስታረቁ ነው ይህም ማለት የጸጋ የመጀመሪያ ዓላማና የሥራ ውጤት የአዳምንና የልጆቹን በደል መደም ሰሰና ከፈጣሪም ይቅርታን ማስገኘት ነው እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ በማለት ዮሐንስ መጥምቁ ስለ ክርስቶስ መስክሯል ዮሐ ወደሙ ለኢየሱስ ክርስቶስ ያነጽሐነ እምኩሉ ኃጣውኢነ የኢየሱስ ክርስቶስም ደም ከኃጢአታችን ሁሉ ያ ነጻናል ኛዮሕ ስለሰዎች ኃጢአት የተሠዋው በጉ የፈሰሰው ደሙ ለኃጢአተኞች ሁሉ ፈውስመድኃኒት ሆናል ጸጋ ማለትም ይህ ነው ስለዚህ ነው የክርስቶስ ሥጋና ደም በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከፍተኛ ክብር የሚሰጠው ስለዚህም ምሥጢረ ቁርባን የምሥጢራት ሁሉ መሠረትና የጸጋ ሁሉ መገኛ ሆኗል ምክንያቱም የደኅነታችን ጸጋ በመስቀል ላይ ከተሠዋው ከክርሰቶስ ሥጋና እንዲሁም ከፈሰሰው ደምና ውኃ የተገኘ ነውና እንግዲህ ጸጋ ማለት በመጀመሪያ ደረጃ በክርስቶስ ቤዛነት ከእግዚአ ብሔር የሚገኝ የኃጢአት ሥርየትና እርቅ ነው ፍጡር ከፈጣሪ መታረቅ የመጀመሪያ የጸጋ ውጤት ነው የጠፋው ልጅ ከአባቱ ጋር የመታረቁን ታሪክ እዚህ ላይ እናስታውስ ሉቃ ክርስቶስ በጸጋው እንዳጸደቀን እርቅና ሰላምን እንደሰጠን ኃጢአት ባለበትም እንዴት ጸጋውን እንዳበዛልን እንመልከት ሮሜ ጸጋ የኃጢአት መደምሰሻ ነው ሰንል በዚህ ብቻ የሚቆም አይደ ለም ጸጋ ኃጢአትን ከደመሰሰ በኋላ በኃጢአት ምክንያት የመጣውንም ሞት ያስወግደዋል በክርስቶስ ሕማምና ሞት የተገኘው ጸጋ የዘላለም ሕይወትን ያስገኛል ገነት መንግሥተ ሰማያትን ያሰጣል ስለዚህ ጸጋ ከሁሉ ነገር በላይ ነው ምክንያቱም ጸጋ የእግዚአብሔር ፍቅር የሚገለጽበት የቸርነቱና የምሕረቱ ውጤት ነውና እንግዲህ በሁለተኛ ደረጃ በጥንተ አብሶ በአዳም ኃጢአት ሕግ በማፍረሱ ምክንያት የመጣብንን መርገም ሽሮ ሞትን ደምስሶ በክርስቶስ የተገኘው ጸጋ የዘላለም ሕይወትን አሰጥቶናል ያጣነውን ገነት አስመ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛደማናትና ክርስቲያናዌ ሕዩፎዉት ልሶልናል ስለዚህ ጸጋ ማለት ጽድቅንና መዳንን ለማግኘት የሚረዳን ከአእግዚአ ብሔር የሚገኝ ስጦታ ነው በጸጋው ኣዲስ ሕይወትን አግኝተን አዲስ ፍጥረት ሆነናል ጸጋ የእግዚአብሔር ልጅነትን አስሰጥቶ የመንግሥቱ ወራሽ አድርጐ የመጨረሻውን ተስፋና ደስታ ለመካፈል ያበቃናል ኛቆሮ ኤፌ ገላ ሮሜጸ በዚህና በመሳሰሉት ልዩ ልዩ የጸጋ ትርጓሜ ለመገንዘብና ለማስገንዘብ የምንፈልገው ነገር ቢኖር ጌታ አምላክ ከሰው ልጅ የሚያገኘው ጥቅም ሳይኖር እንዲያውም የፈጣሪውን ቃል ኪዳን ተላልፎ በመበደሉ የእግዚአብሔር ጠላቱ ሆኖ ሳለ ሮሜ እርሱ ግን በዓይነ ምሕረት ተመልክቶ ታላቅ የቸር ነትና የርኀራቴ ሥራ ማድረጉ ለሰው ልጅ ያለው ፍቅር ምን ያህል ታላቅ እን ደሆነ በአድናቆት እንድንመለከተው ነው በልዎ ለእግዚአብሔር ግሩም ግብርከ እግዚአብሔርን ሥራህ ግሩም ነው በሉት መዝ እያልን ታላቁን የፍቅር ሥራውን በአንክሮና በተዘክሮ ሆነን እንማረዋለን እንግዲህ ይህ እጅግ የሚያስደንቀው አምሳካዊ የፍቅር ሥራው ሁሉ ጸጋ ይባላል እግዚአ ብሔር ለሰው ልጅ እንዲሁ በነፃ ያደረገለት የረድኤት ሥራ ነውና ጸጋንም ጸጋ ያሰኘው ከቸሩ እግዚአብሔር ያለምንም ዋጋ ለሰዎች ደኅንነት በነፃ የሚሰጥ ስለሆነ ነው። ለሚለው ጥያቀ መልሱ በክፍል አንድ እንደተመለከትነው በእርግጥ ሰው በራሱ ጥፋት መከ ረኛታማሚና ሟች መሆኑ ከአዳም ጀምሮ የነበረ ታሪክ ነው ይህም የሆነበት ምክንያት የሰው ዘር ከጥንተ አብሶ ጀምሮ ለፈጣሪው ሕግ ባለመታዘዙ በነፍስም በሥጋም ጉስቋላ ፍጡርሕመምተኛና ሟች ሆኗል ስለሆነም ለዚህ ችግራችን መፍትሔና መድኃኒት አስፈልጉታል ሕግ ለዚህ ችግር መፍትሔ አይሰጥም ምክንያቱም ሕግ መፍረድና መቅጣት እንጂ ማዳን አይሆንለትምና ሰው ከወደቀበት አዘቅት በራሱ ጥረትና ትግል ብቻ ለመውጣት ቢያስብና ቢሞክርም አልተከናወነለትም ሰው ራሱን ለማጥፋት ሲችል ራሱን ለማዳን ግን አልቻለም በጥንተ አብሶ ለፈጣሪው ባለመታዘዙ ከእግዚአብሔርም በመራቁ የ ነበረው ኃይልና ችሎታ ተቀንሷል እንግዲህ ሰው ከወደቀበት አዘቅት ሊወጣ የሚችለው በእግዚአብሔር እጅና ክንድ ብቻ ነው ይህም የክርስቶስ ጸጋ ነው የተጐሳቆለችው ነፍሱ የወደቀችው ሰውነቱ የጠፋችው ሕይወቱ በክርስቶስ ጸጋ ልትነሣና ልትድን ችላለች በጸጋም ከፈጣሪዋ ጋር በመታረቋ ሕይወትን አግኝታ እንደገና ተወልዳ አዲስ ፍጥረት ሆናለችቡ የሞት ሞት ከተፈረደባት ከሲኦልና ከዘላለም ሥቃይ ነፃ ወጥታለች እንግዲህ በክርስቶስ አምነው ከዚህ ዓለም በሞት ለሚሜለዩት ሁሉ በገ ነት በደስታ የመኖር ተስፋ አላቸው ነገር ግን ለማያምኑትና የክርስቶስ ጸጋ ለሌላቸው የሲኦል ሥቃይ ይጠብቃቸዋል የጸጋ አዳኝነት ለሚያምኑት ብቻ የተሰጠ ነው አማኞች ነፍሳቸው ብቻ ሳይሆን ሥጋቸውም ይድናል በትን ሣኤ ዘለክብር ከነፍሳቸው ጋር በመዋሐድ መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳልና የጸጋ ማዳን ለነፍስም ለሥጋም ነውና በክርስቶስ አምነን በጸጋው ለዳንን ሁሉ ደግሞ ታላቁን የእግዚአ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይማናትና ክርስቲያናዊ ሕይወት ብሔርን ጸጋ ለመዳናችን ማስረጃ ለተስፋችንና ለርስታችን መያዣ የሆነውን መንፈስ ቅዱስን ለመቀበል እንድንችል እርሱ ባለቤቱ አብቅቶናል ኤፌ በተለይም የሰማዩ አባታችንን በእውነት ለሚለምኑት ሁሉ መንፈስ ቅዱስን እንደሚሰጣቸው በወንጌል ተጽፏል ሉቃ በተሰጠንም በመን ፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን እንደ ፈሰሰ ማለት እንደ አደረ ከሐዋርያው ጳውሎስ እንማራለን ሮሜ ይሀም መንፈስ ቅዱስ የሚያጸናንና የሚያጽናናን የሚያነጻንም የቅድስናንም ጸጋ የሚሰጠን እርሱ ነው ክርስቲያኖች ሁሉ ያለ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እስከ መጨረሻው ድረስ በትዕግሥት መንፈሳዊ ሕይወታቸውን ሊመሩና የመዳን ጸጋቸውን ሊያገኙ የሕይወት አክሊላቸውንም ሊቀዳጁ አይችሉም በክርስቶስ ሕማምና ሞት የምሕረት ጸጋን የኃጢአት ሥርየትን በእምነትና በጥምቀት አግኝተናል ይህንንም ከክርስቶስ ያገኘነውን ጸጋ በልዩ ልዩ ፈተና ምክንያት እንዳንተወውና እንደገናም ከከፍተኛ የኃጢአት አዘቅት ውስጥ እንዳንወድቅ የሚረዳን መንፈስ ቅዱስ ነው በቅድስና ጐዳና የሚመራንና ከክፋትና ከነውር ሥራ ሁሉ እንድን ርቅ በመልካም አኗኗር ራሳችንን እንድንቆጣጠርና በፍቅረ እግዚአብሔር እን ድንያዝ ሊያደርገን የሚችል እርሱ ብቻ ነው መንፈስ ቅዱስ ከቅድስና ጸጋው ጋር ለመዳናችን የሚያዘጋጁንንና የሚያስፈልጉትን ልዩ ልዩ ጸጋዎች ማለት ስጦታዎች በክርስቶስ ላመኑት ለቤተ ክርስቲያን አባላት ያድላል ቆሮ ለአንዳንዶች የማሰተማር ስጦ ታ ለሌሎች ተአምራት የማድረግ በልሳን የመናገር ሰውን የመርዳትና የማስተዳደር አገልግሎት ይሰጣል በነዚህና በሌሎችም ልዩ ልዩ ሰጦታዎች ምክንያት ሕዝበ ክርስቲያኑ መንፈሳዊ ኑሯቸው እንዳይደክምና በሃይማኖትና በምግባር በትሩፋትም ጸንተው ለተስፋው ሀገር ለገነት ለመንግሥተ ሰማያት እን ዲበቁ ይሆናሉ ምእመናን መሪያቸውን ክርስቶስን በእግር ሳይሆን በግብር እን ዲከተሉትና እርሱንም እንዲመስሉት የሚያበቃቸው የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ነው እንግዲህ መልካሙን ሥራ ለመሥራት ሐሳቡን የሚሰጠን ፈቃዳችንንም የሚያ ነሣሣው የእግዚአብሔር ጸጋ መሆኑን አምነን ለመንፈስ ቅዱስ መታዘዝ ይኖርብናል ስለዚህ ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔር መንፈስ አታሳዝኑ ኤፌ የጸጋና የምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ግንኙነት ስለ ጸጋ ከላይ ተመልክተናል ከእንግዲህ ወዲህ ጸጋ ከምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ጋር ያለውን ግንኙነትና የምሥጢራትን ምንነት በታሪክና በምሳ ሌ ጭምር እንደሚከተለው በአጭሩ እንመለከታለን በእግዚአብሔር ጸጋ ማለት በመሰቀል ላይ በፈሰሰው በክርስቶስ ደም የሰው ልጆች ኃጢአት ተደምስሶ ዓለም ሁሉ እንደዳነ እናምናለን ይህ አንድ ጊዜ የተፈጸመው የማዳን ሥራና ጸጋው ለሁሉም ሰው የተሰጠ ቢሆንም ተቀባይ ከሌለ ደግሞ መሰጠቱ ብቻ በቂ አይሆን ም ስለዚህ ጸጋን ለማግኘት አምኖ ወደ ቤተ ክርስቲያን መምጣት ያስፈልጋል ጸጋ ላመኑትና ለተዘጋጁት ሁሉ በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን አ ማካኝነት ይሰጣል ይታደላል እንግዲህ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የተባሉት የክርስቶስን ጸጋ በእምነት የምንቀበልባቸው የተቀደሱ የጸጋ ምልክቶችና መሣሪያዎች ሲሆኑ በማይታየው ውስጠ ምሥጢራቸው ደግሞ በቃለ እግዚአብሔርና በጸሎት አማካይነት ጸጋን የሚያስገኙና በግብረ መንፈስ ቅዱስ ለአማኞች የሚከፋፈሉ የጸጋ ስጦታዎችን የያዙ ናቸው በዚህም የተነሣ ቤት ክርስቲያን የጸጋው ግምጃ ቤት ተብላለች ምክንያቱም በሚታየው ምሥጢራቷ ኣማካይነት የማይታየውን ጸጋ እግዚአብሔር በቃል ኪዳኑ መሠረት ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛደማናትና ክርስቲያናዊ ሕይጠት በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ጠብቃና ይዛ የምትገኝና በየጊዜውም ጸጋውን የምታሰጥ በመሆኗ ነው ሰለ ምሥጢረ ቤተ ክርስቲያን ምንነት ሲጽፉ የግብፁ ቄስ ማርቆስ ዳውድ እንደሚከተለው በአንድ ዓረፍተ ነገር ገልጸውታል ምሥጢረ ቤተ ክርስቲያን የተቀደሰ ሕግና ሥርዓት ነው በእርሱም በኩል አማኝ ሁሉ በሚታይ ወይም በሚሰማ አኳኋን በአፍአዊ በውጭ ምልክት አማካይነት የማይታየውን ጸጋ ይቀበላል ክርስቶስን ማመናችንና መቀበላችን የሚረጋገጠው በጸጋው መዳናችንም የሚታወቀው ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን በመፈጸም ብቻ መሆኑን ማመን ይኖርብናል አለበለዚያ ግን ከቤተ ክርስቲያን ውጭ ሆኖ በግለኝነትና በራስ አ ስተያየት ብቻ ተመርቶ እግዚአብሔር ያውቃል እርሱ ያድነኛል ሌላው ነገር አያስፈልገኝም እያሉ የቤተ ክርስቲያንን ምሥጢራት በመናቅ በክርስቶስ ወንጌል የታዘዙትን የጸጋ ምሥጢራት ሳይፈጽሙ መቅረት የክርስቶስ ደም የተከፈለበትን ጸጋ ማክፋፋት ስለሆነ አዲሱን ኪዳን እንደአፈረሱ ተቆጥ ሮ በእግዚአብሔር ዘንድ ቅጣትን ያስከትልባቸዋል ወደ ዕብራውያን በተጻፈው መልእክት እንደተገለጸው የጸጋውን መንፈስ የተቃወሙት አይሁዶች ከሁሉ የባሰ ቅጣት እንደሚገባቸው ያመለክታል ሽ የሙሴን ሕግ የናቀ ሰው ሁለት ወይም ሦስት ቢመሰክሩበት ያለ ርኅራጌ ይሞታል የእግዚአብሔርን ልጅ የረገጠ ያንንም የተቀደሰበትን የኪዳኑን ደም እን ደርኩስ ነገር የቆጠረ የጸጋውንም መንፈስ ያክፋፋ እንዴት ይልቅ የሚብስ ቅጣት የሚገባው ይመሰላችኋል። ኪር እር ህፒከፎ ከርከህየርከ ርከህዮርከ ርተበርበ ለ ለኮኮ በ ፖር ኮበበቨበፀ ፎ ኮ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይማናትና ክርስቲያናዊ ሕይወት ለዘላለም ያስቀጣል ምክንያቱም እነርሱን አለመቀበል ምሥጢረ ሥጋዌን እን ደ አለመቀበል ማለት ጌታ ሰው መሆኑን ጥምቀቱን ሕማማቱንሞቱንና ትንሣኤውን እንደ መካድ ስለሚቆጠር ነው ንስሐ ገብቶ በወንጌል ያመነና የተጠመቀ ግን ይድናል ማር በክርስቶስ ያገኘነው ነፃነትና አዲስ ሕይወት በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን አማካይነት ለአማኞች ሁሉ ይሰጣል የዚህንም ታሪክና ምሳሌ በኦሪት መጻሕፍት ውስጥ እናገኘዋለን እያነፃፀርንም እንማረዋለን እሥራኤ ላውያን ደሙ በበሩ መቃን ላይ በተረጨው በፋሲካ በግ ከመከራና ከሞት እን ደዳኑና ከግብፅ ባርነት ነፃ እንደወጡ ክርስቲያኖችም በመስቀሉ ላይ በፈሰሰው የክርስቶስ ደም ከኃጢአትና ከሞት ድነዋል ከዲያብሎስ ግዞትም ነፃ ወጥተዋል ዘፀሪ ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዲልና ኛቆሮ ዛሬም ይህንን የደኅንነትና የነፃነትን ጸጋ መቀበላችንና ማግኘታችንን የምናረጋግጠው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚሠዋው በክርስቶስ ሥጋና ደም በቅዱስ ቁርባን መሥዋዕት ነው እሥራኤላውያን በቀይ ባሕር ውስጥ በተአምራት ተሻግረው ነፃ ሕዝብ በመሆን አዲሱን የነፃነት ኑሮ እንደ ጀመሩ ሁሉ እንዲሁም ክርስቲያኖች በምሥጢረ ጥምቀት እንደገና ተወልደው አዲስ ፍጥረት ለመሆናቸው የሚያስረዳን ታሪክና ምሳሌ ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሁሉም ሙሴን ይተባበሩት ዘንድ በደመናና በባሕር ተጠመቁ ሁሉም ያን መንፈሳዊ መብል በሉ ሁሉም ያን መንፈሳዊ መጠጥ ጠጡ ይከተላቸው ከነበረው ከመንፈሳዊ ድንጋይ ጠጥተዋልና ያም ድንጋይ ክርስቶስ ነበረ ያለውን ተመልከት ኛቆ ሮ እንግዲህ ሕዝበ እሥራኤል ሙሴን የተባበሩት በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ከሆነ ሕዝበ ክርስቲያንም ከክርስቶስ ጋር ሊተባበሩ የሚችሉት በባሕሩ በተመሰለው በጥምቀት በደመና በተመሰለው በምሥጢረ ሜሮን በመንፈሳዊ ምግብና መጠጥ በተመሰለው በሥጋውና በደሙ ምሥጢር በመሳተፍ እንደሆ ነ እናምናለን እነዚህ ሦስቱን ካልፈጸምን ከክርስቶስ ጋር ኅብረት አንድነት የለንም በደብረ ሲና በእሳትና በመለከት ድምፅ ታጅቦ የታወጀው ሕገ ኦሪት ለቤተ እሥራኤል ሁሉ የሕይወታቸው መመሪያና መተዳዳሪያ እንደሆነ ሁሉ እንዲሁም በኢየሩሳሌም በጽርሐ ጽዮን በልሳነ እሳት በበዓለ ኀምሳ የወረደው መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያንን በጸጋውና በሕገ ተፋቅሮ የሚመራና የሚያስተዳድር ሆኗል ወደሚያስፈራው የሲና ተራራ ሳይሆን አእላፍ መሳእክትና የበኩራት ማኅበር በደስታ ወደ ተሰበሰቡበት የጽዮን ተራራ የእግዚአብሔር ከተማ ወደ ሆነችው ሰማያዊት ኢየሩሳሌም በመንፈስ ቅዱስ አማ ካኝነት እንደርሳለን ለዚህ የሚያበቃንን ጸጋ ከእርሱ እናገኛለን ይህም የመን ፈስ ቅዱስ ጸጋ ዛሬ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለጥሙቃን በምሥጢረ ሜሮን የሚ ሰጠው የክርስቲያንን ሕይወት የሚያድሰውና የሚቀድሰው እንደሆነ እናምናለን ዘጸአ የሐዋ ዕብራ እሥራኤላውያን ከተስፋው ሀገር እስኪገቡ ድረስ በድንኳን ውስጥ ከበረሓ ወደ በረሓ አርባ ዓመት ሙሉ ሲንከራተቱ ከሰማይ የወረደ መና እየተመገቡ እንደኖሩ ሁሉ እንዲሁም ክርስቲያኖች በድንኳንና በበረሓ በተመሰሉት በሥጋ ድንኳናቸው በሰውነታቸው እና በዚህ ዓለም ኑሯቸው እስካሉ ድረስ ምግበ ነፍስ የሚሆናቸውን ከሰማይ የወረደውን እውነተኛ የሕይወት ምግብ የክርስቶስን ሥጋና ደም በመመገብ ይኖራሉ ኛ ቆሮ ዮሐ ስለዚህ ነው ዛሬ ምሥጢረ ቁርባንንና ቃለ እግዚአብሔርን በየጊዜው ማግኘት ያለብን ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይደማናትና ከርስቲተያናዊ ሕይወት ክርስቲያኖች በዚህ ዓለም መጻተኞች እንግዶች ማለት ሀዢ እን ደሌላቸው ተንከራታቾች ሆነው የሚኖሩበት ምክንያት እውነተኛ ሀገራቸው ገነት መንግሥተ ሰማያት ሰለሆነች ነው በእንደዚህ ያለ የችግር ኑሮ ውስጥ ሲኖሩ ሳለ በትዕግሥት እንዲዳወጡትና መከራውንም በመቻል በሰላም እን ዲያልፉት ለተስፋውም ሀገር እንዲበቁ የሚያደርጋቸው በክርስቶስ የተገኘው የጸጋ እግዚአብሔር ረድኤት ነው ጸጋ እግዚአብሔርም የሚገኘው በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ሰለሆነ ከሥጋ ልደቱ ጀምሮ እስከ ሞቱ ድረስ ለመንፈሳዊ ልደቱና ለክርሰቲያናዊ ሕይወቱ የሚያስፈልጉትን ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ማናቸውም ክርስቲያን መቀበል ግዴታው ነው የእግዚአብሔር ልጅ ነቱን የቤተ ክርስቲያን አባልነቱን ሳያከብር የቀረ ግን ዕለት በዕለት የሚያስፈልገውንና ለክርስቲያናዊ ሕይወቱ የሚጠቅመውን መንፈሳዊ ምግብና ኃይል ስለማያገኝ በድካም ምክንያት ከመንገድ ላይ ወድቆ በመቅረት ከተስፋው ሀገር አይደርሰም ሦ ርዕራያፖ ሪምኋ ጸጋ እግዚአብሔር የት ይገኛል።