Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ምነው አስቻለው ምን ሆነሃል። አለችው ቆም ብላ እየተመለከተቻት። ሓመሙ መሥ ፕትገ አለች ድንገት ጥቂት አሰብ ስታደርግ ይህን ጥያቄ መጠየቅ አያስፈለጋትም ፍሬሕይወት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የብዙዎች የፖለቲካ ሰዎች ከአዲስአበባ መሄድ እየተለመደ ነው። አለቻት ኮስተር ብላ። እሱ ልክ ነው። ምን ልታደርግ ነው። እባክሸን ትዝታዬን እፈልገዋለሁ አላት። ሌላ ትዝታ እፈልጋለሁ አላት አንተነህ። የማደርገውን ሁሉ የማደርገው ለዓላማና ለድርጅት ስል እንደሆነ እንድትረጅልኝ ብቻ። ታዲያ ምን ላድርግ። ሰፈርሽ የት ነው። ኡራኤል ነው አለች እንዳቀረቀረች። የበለጠ የሚያመኝ ሀሳቡ ነው። አንች ግን መሣሪያ ለመደበቅ እንዴት ተባበርሽ። ደግሞም መልካም ሰዎች ናቸው ለሰው ያላቸው ይገዛኛል እነርሱ ዘንድ የበላይና የበታች የለም ሁሉም በየፍራሹ ላይ ኩርትም ብሎ የሚያወራው ስለሚስጥረ ነው። ሰው ሲቆርጥ የቱን ያህል መከራና ስቃይ እንደሚችል ያየችው ከሚስጥረ ነው። ፍሬ እንዳሰበችው ሆነ ድንቅነሽ ስቃይ ሳይበዛባት በነካ ነካ ግርፋት ብቻ ታለፈች። ይሆንልኛል ብለሸ ነው። እኔ እዚህ ቤት መጥቷል እርሱ አየኝ ማለት ደግሞ አለቀልኝ ማለት ነው ከዚህ በፊት እንደምንም ራሴን ለመደበቅ የሞከርኳቸው ሙከራዎች ተሳክተውልኝ የመጡት ሁሉ ሳያዩኝ አምልጫለሁ አሁን ግን እየከበደ ይመስለኛል ስለዚህ ሽፋን እፈልጋለሁ አለች። ማረፊያ ያሳጣሽ ምዕራፍ አለ። ቁቱ ቁ ሮቤል ሳሎን ቤት ጠረጴዛ ላይ ትልቅ ወረቀት ዘርግቶ የስዕል እርሳሶችና ላሏስ ደርድሮ በርከክ አለ። ወረቀቱ ላይ የሠራውን ስዕል ለመመልከት ከተንበረከከበት ብድግ አለና ራቅ አለ። ሚሚን በብዙ ነገር ያስታውሳታል። በትዝታው ፈገግ አለ። ለምን እንደዛ እንዳደረገች የገባው የስንብት እንደነበረ የተረዳው ግን ቆይቶ ነው።
ከጠዋቱ በአራት ሰዓት ስብሰባ አላት መቅረት አይኖርባትም ድንገት ቅዱስን አሰበችው እርሱስ የት ይሆን ያደረው። አለችው። ስትገባ ቅዱስን አገኘችው እንደሁልጊዜው በደንብ ለብሷል ስታየው ልቧ በደስታ ፈነደቀች እቅፍ አድርጋ ሳመችውጡ ዘርዓይና ጋዲኅ ግን አልመጡም ቅዱስ ለዕለቱ የተዘጋጀ ውይይት ባለመኖሩ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧቸው መሄድ እንዳለበት ነገራቸውና ወዲያውኑ ወጣ ሲወጣ ስሜቱ ጥሩ አልነበረም በሚቀጥለው ቀን እንዲገናኙ ፍሬሕይወትን ቀጠራት ከነአስቻለው ቤት ስትወጣ እኩለ ቀን እየሆነ ነበር ጋዲሳና ዘርዓይ ግን አሁንም ብቅ አላሉም ከአንተነህ ጋር ያሳት ቀጠሮ ገና ከሰዓት በኋሳ ነው ሌላም ቀጠሮ የላትም ምናልባትም አንተነህም ጎረቤት ሊደውል ይችል ይሆናል ስለስልኩ ሰታስብ ርምጃዋን ፈጠን አደረገችው ፍሬሕይወት ከቤት አልወጣችም የጠበቀችው ኣልደረሳትም ሀሳቧን መሰብሰብ አቅቷት እንደተጨነቀች ዋለችና እሰራ አንድ ሰዓት ሲሆን ከቤት ወጣች ፈጠን ያለ እርምጃ የሰዎችን ዐይን እንዲስብባት አልፈለገችም ሰውነቷን ዘና አድርጋ በቀስታ ርምጃ ለመሄድ ሞከረች አለባበሷን ተመለከተችው የሚያሳጣ አይደለም ሁል ጊዜም የሰው ዐይን የሚጠራባት ጫማዋም ዛሬ አጠር ያለ ተረከዝ ያለው ቆንጆ ጫማ በማድረጓ ተስተካክሏል የስልክ መልፅክትም ወደ መድረሻዋ አስጠላ ስትቃረብ ደርሶ መጸለይም አማራት ጭንቅ አላት ግን እንዴት ነው የምትጸልየው። ሌላ ምን ምርጫ አላት። አንተነህ አለችው ሄዋን በቀስታ። ፍሬ የት ነች። ሣዊ አላት ዐይኖቹን እንደገና ገልጦ አቤት አንተነህ አለችው በፍጥነት ፍሬን እንዴት ነው የማገኛት። በስተግራ በኩል ባሌት መንደሮች መሀል በኮረኮንች መንገድ ወደውስጥ ገቡ ጥቂት እንደሄዱ አንድ ትልቅ አረንጓዴ የብረት በር አጠገብ ሲደረሱ ቆሙና በሩን ሦስት ጊዜ መታ መታ አደረገው ልጁ በሩ ወዲያውኑ ተከፈተ ግርማ ሞገሱ ያማረ ትልቅ ቤት ጉብ ብሏል ግቢው ሙሉ በሙሉ በአስፋልት የተነጠፈ ሲሆን የአጥሩ ጥጋጥግ ባማሩ አበባዎች ተውቧል ግድግዳው የተሠራበት ውድ ጠጠር ያብለጨልጫል አድናቆቷን ሳትችጨርስ ወደቤቱ በስተጀርባ አለፉ መደዳውን ተያይዘው ከተሠሩት ቤቶች የአንደኛው በር ተከፈተና ገቡ ከፊት ለፊቷ አንተነህ አልጋ ላይ ጋደም ብሎ አየችውጦ ከቶውንም ምንም ለማለት አቅም አልነበራትም ቃላት ከአንደበቷ መውጣት ተስኗቸው በጉሮሮዋ ውስጥ እየተተረማመሱ ሳግ ፈጠሩ ልታደርግ የቻለችው አንድ ነገር ብቻ ነው ሮጣ አልጋው አጠገብ መንበርከክ መታዘዝ የማያስፈልገው እንባዋ እንደፈለገው እየወረደ በጉንጮቿ ላይ ፈሰሰ ልትከለክለው አልፈለገችም ያሻውን ያህል ወርዶ ውስጧን እንዲያጥብላት ፈቀደችለት በቃ። በሩ በቀስታ ሲከፈት ቀና አለች ዐይኖቿን ማመን አቃታት የገባችው ሄዋን ነች ዐይኖቿን አንዴ ወደ አንተነህ ደግሞ ወደ ሄዋን እያደረገች አንከራተተቻቸው ሄዋንን በዚህ ዓይነት አጋጣሚ አገኛታለሁ ብላ በፍጹም አላሰበችም ለሰላምታ ተቃቀፉ ሰላምታዋ ለፍሬ ያላትን ስሜት የንጸባረቀላት መሰላትና ከልቧ ደስ አላት ስለሄዋን የነበራት ግምት ትክክል ሆኖ አገኘችው የተንደላቀቀ ሕይወቷን ለትግል የሰጠች ወጣት መሆኗን ክፍል ስደትና እስራት የተደረገውን የቤት ለቤት አሰሳ በመቃወም የፕሮፓጋንዳ ሥራ ለመሥራት በሁሌም አካባቢዎች ዝግጅቱ ተጠናከረ ለሥራው የሚያስፈልጉ ዕቃዎች በሙሌ ተሟልተዋል ወጣት ሁሉ በሥራ ተወጠረ ለአፍታ እንኳ አረፍ ሳይሉ ሲባክኑ ውለው ማደር ከጀመሩ ሰንብተዋል እዚህ ቀጠሮ እዛ ቀጠሮ ማታ ደግሞ የተግባር ሥራ ቅድመ ዝግጅቱ በተጠናቀቀበት ዕለት ከቀኑ አሰር ሰዓት ላይ ፍሬሕይወት ከድካሟ የተነሳ የማቅለሽለሽ ስሜት ተሰማት ኪሷን ስትፈትሽ አራት ብር አገኘች በአቅራቢያው ወዳለች ኪዮስክ ተጠጋችና ለስላሳ ጠየቀች ለስላሳውን ከፍቶ ሲሰጣት በአንድ ትንፋሽ ጨለጠችው የለስላሳውን ጠርሙስ ለባለሱቁ መስጠቷንም እርግጠኛ አይደለችም ብቻ ምድር ሰማዩ ዞረባት ሆዷ ግልብጥብጥ ልቧም እንደ መክዳት አደረጋት በፍጥነት ተቀመጠች የጠጣችው ሚሪንዳ እንደፈነዳ የቧንቧ ውሃ ተረጨ ምንም ነገር በሆዷ ውስጥ ሳይቀር አስመለሳት በመጨረሻ መራራ ሀሞት ወጣ ቀና ብላ አካባቢዋን ተመለከተች ባለሱቁ ግራ ገብቶት ይመለከታታል ውሀ አለችው በደከመ ድምፅ ውሀውን ጠጣች ሲተረማመስ የነበረው ሆዷ የተረጋጋ መሰላት በግንባሯ ላይ ችፍፍ ብሎ የነበረ ላብ ቀዝቀዝ ሲል ተሰማት ጠራረገችው እፎይ። አለች በረጅሙ ተንፍሳ ግቢና ትንሽ አረፍ በይ አላት ባለሱቁ በሀዘኔታ አይ አይለኝም እግዜር ይስጥልኝ አለች የለስላሳውን ዋጋ እየከፈለች ምንም ከ በቀጥታ ወደቤቷ ተመልሳ ገብታ አልጋዋ ላይ ከተዘረረች በኋላ ነው ሰዓቷን ያየችው ለአስራ አንድ ሰዓት ሰዓት ያህል ጊዜ አላት ትንሽ ማረፍ ትችላለች ዓይኖቿን ጨፍና ሩብ ጉዳይ ሆኗል አንድ ሰውነቷን ዘና ለማድረግ ሞከረች ሃሳቧ ግን ሊያርፍ አልቻለም የሚጠብቃትም ሥራ የሚያሳርፍ አይደለም ቢሆንም አል ያሳር ቢ ኣጋዋ ላ ጥቂት መቆየት አለባት። ተሸወድኩ የምትለው ነገር አይገባኝም አለችው ዳንኤል ያልጠበቀው ነገር ሆኖበት ግራ ግብት ሲለው አየች በዚሁ መቀጠል ነበረባት እናም ዳንኤልን እቅፍ አደረገችና ሳም አድርጋው ስመለስ እንገናኝ ብላ ለመልስ ጊዜ ሳትሰጠው ትታው ሄደች ከአሁን አሁን ተከተለኝ በማለት ልቧ ድው ድው ማለት ጀመረች ግን ዞር አላለችም ሰዓቷን ተመለከተች ግዜ አላት ታክሲ ካገኘች በሚገባ ትደርሳለች ታክሲውን ወዲያውኑ አገኘችና እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን አጠገብ ስትወርድ አምስት ደቂቃዎች ነበሯት ቀጠሮዋ ፍላሚንጎ ነው ደቂቃዎቹ ይበቋታል ራመድ ራመድ እያለች አስፋልቱን አቋረጠችና ወደ ቦሌ የሚወስደውን መንገድ ያዘች ቀና ብላ አካባቢዋን ቃኘት ስታደርግ ክው ብላ ደነገጠች ፍላሚንጎ አካባቢ መንገዱ ተዘግቶ አላፊ አግዳሚው ይፈተሻል ይገጣበራል ይገፋል የቀጠሮ ሰዓት ማሳለፍ ከመቼውም ጊዜ ይልቅ አስጊ በመሆኑ በሰዓቱ መድረስ ነበረባት ወይኔ ቅዱስ ተበላህ። አፍታም ሳይቆይ የኡራኤል ቤተክርስቲያን በተደናገጡና መሄጃ በጠፋቸው ሰዎች ተሞላ ተከታትለው አብዮት ጥበቃዎቹ ሰዉን እየገፈታተሩ ገቡ ቦርሳዋን ደበቀችና ነጠላዋን እንደተከናነበች መሬቱ ላይ በግንባሯ ተደፋች ካሁን አሁን አንጠልጥለው አነሱኝ የሚለው ስጋት ቢያስጨንቃትም ባለችበት ሁኔታ ከመቆየት የተሻለ አማራጭ የላትም ቀስ ብላ አካባቢውን ለማየት ትሞክራለች ጥበቃዎቹ የመሰላቸውን ሰው ሁሉ እያዳፉ ይነዱታል ከተወሰነ መተረማመስ በኋላ አካባቢው ሰላም አገኘ ከጥቂት ሰዎች በስተቀር ሰው ሙልጭ ብሎ ወዐጣ ከተንበረከከችበት ተነስታ አግዳሚው ወንበር ላይ ተቀመጠችና እንደገና ማሰብ ጀመረች ምናልባት ሰፈር አካባቢም እንዲሁ ዓይነት አሰሳ ካለ እናቷ የቱን ያህል እንደሚጨነቁ ስታስበው ደግሞ የበለጠ ተረበሸች እንደምንም ብላ መደወልና ደህንነቷን መንገር ይኖርባታል የሕዝብ ስልክ ያለበትን ቦታ ለማስታወስ ሞከረች ልታስታውስ ግን አልቻለችም ሰዓቷን አየች ጊዜው እየመሸ ነው። ሰፈራችን ግን ትንሽ መረጋጋት ይታይበታል አለችው የገጠማትን አስታውሳ አንድ አማራጭ አለን ቆሻሻውን እንደማትጠየፊ እርግጠኛ ነኝ አላት አስቻለው። በአጥርና አጥር መሀል ባለ ቀጭን መንገድ ውስጥ ገቡ አስቻለው ጎንበስ አለና በአጥሩ ስር ባለው የቆሻሻ ፍሳሽ መውረጃ ላይ ለውሻ መከላከያ የተወነጋገረውን እንጨት እያነሳ ወደጎን አደረገው በይ ነይ አላት አስቻለው በዐይኖቹም እያመላከታት ምንም አላመነታችም እግሯን በቀስታ ወደቦዩ ሰደደችው እግሯን ሲቀዘቅዛት ቆሻሻውን ውሀ አስባ ዝግንን አላት ምርጫ የለም ለመሹለክ ጎንበስ ስትል ትንፋገኑ በአፍና በአፍንጫዋ ገባ እንደምንም ሾልካ ገባች እንደገባች አስቻለውን መጠባቅ ነበረባት እነጋዲሳስ። ይፈሳል የሕዝቡ ታማኝ አገልጋይ ነኝ የሠርቶ አደሩ ወታደር ብረት አነሳሁ ከጓዶቿ ጋር እኩል በመድረሳቸው ፍሬሕይወት በጣም ተደሰተች ለትግል ተነሳሁ ሥራቸውን ጨርሰው እጆቻቸው ነፃ ሲሆኑና የተኩሱ ድምጽ ጠላት ይፍራ ይሸበር የሌሊቱን ፀጥ ያለ ኣየር ሲያደፈርሰው እኩል ሆነ ከመቅጽበት የፍር ባይ ልቡ ይሰበር አቅራቢያቸው ወደአለው የእነእሸቱ ግቢ ገቡ ድንገተኛ አደጋ ቢሰበር አጥንቴ ቢንቆረቆር ደሜ ቢያጋጥም ተብሎ የተዘጋጀው የአገባብ መንገድ ተግባራዊ ሆነ እሸቱ ላዲስ ስርዓት ልምላሜ ኒ አስቀድሞ ደብቆት የነበረውን መሰላል አመቻቸና ሁሉም በፍጥነት ፍጹም ነው እምነቴ ወደግቢው ገቡ ሁሉም ከገቡ በኋላ እሸቱ ግንቡ ላይ ወጥቶ የትግሉ ነው ሕይወቱ መሰላሉን ወደውስጥ አስገባ ት ታ ሁሉም አሉ ሶስቱም ቀና ብለው ግቢው ሰፊ ነው በገቡበት በኩል የከብቶች ቤት አለ ከከብቶቹ መ ተዋል የ አለመላው እናት ድምፃቸውን ሰምተው ቤት አጠገብ ያለችው የከብቶች መኖ ማከማቻ ቤት ምቹ ነበረች ተያ እ እዚያ እየሰጡ መሆኑን ለመረዳት ጊዜ የሚወስድባቸ እሸቱ ጓደኞቹን አስገብቶ የመኖ ማከማቻዋን ከውጭ ዘጋና ወደቤቱ በረም ገባ እሸቱ የሰጣቸውን ጋቢና ፍሬሕይወት የያዘችውን ነጠላ ለብሰው አልነ ጥግት ናት ብለው ተቀመጡ ጋብ ብሎ የነበረው ተኩስ ባሰበት ሠራች መለሱ ዓይ ስቴንስ ሺ ቀርፆ ሲጨር የውሾቾ ጩ ከተኩሱ ድምጽ ጋር ተደርቦ የአካባቢውን ሰላም እንደገና ወደሥራ ቸ ው ተ መ ር ደስጣ ወረቀቱን ወደአጠገቡ ጠበው በእያንዳንዱ ሌሊት የተኩስ ድምጽ መስማት የተለመደ እተ ው የማባዣ ቀለሙን አዘጋጀ አዴፍርሰ ሥራውን ጀመረ ኒ ስለሆነ ማንም ከመኝታው አይነሳም አደፍርሉ በራሳቸው የተሠራ የማባዣማሽን ነው ኒ ሥ ፍሬሕይወት እነጋዲሳን አሰበቻቸው ያሉበትን ቦታና የተኩሱን አቅጣጫ ግን ማገናዘብ አልቻለችም ስታስበው ዝግንን አላት ጆሮዎቿን ወደ ተኩሱ አቅጣጫ አቀናች ድንገት ተኩሱ ረጭ አለ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ ቀጠለ አቅጣጫውን ለመረዳት በሞከረች ቁጥር ግን ትደነግጣለች አስቻለው አሁንም አሁንም በፊቷ ድቅን እያለ አስቸገራት በማንኛውም ጊዜ ጭንቀት ሲበዛባት እንደሚሰማት ሁሉ መንፈሷ የሆነ መጠጊያ ፈለገ መጸለይ አማራት የተከተለው ኃይለኛ ተኩስ ሀሳቧን በታተነባት። ከዚያ ግቢ መውጣት ግዴታ ነው በማንኛውም ሠዓት ለከብቶች ምግብ ለመስጠት ሰው መምጣቱ የማይቀር ስለሆነ ሳይታዩ መውጣት ይኖርባቸዋል ኩርምት ብለው ያደሩ እግሮቻቸውን ጥቂት አፍታቱና በቀስታና አንድ በአንድ በዋናው በር ወጡ የንጋቱ ተኩስ ከአእምሮዋ አልጠፋ ብሏት ፍሬሕይወት ግሬ አለክርቄከክ ኳኤኤር አስቸገራት ማጣራት ያስፈልጋታል ከጃኬቷ ስር ወገቧ ላይ አስራው የነበረውን ነጠላ ፈታችና ለበሰችው የጠዋቱን ተከ አቅጣጫ ተከትላ እነአስቻለው ተመድበውበት ወደነበረው ቦታ ዛፎች ሰዎች ይንጫጫሌሉሌ እግሮቿ አልታዘዝ አሏት ግን መሄድ አለባት አንዲት አሮጊት ሴት ከወደግርግሩ አቅጣጫ ሲመጡ ተመለከተች እማማ ምንድነው ግርግሩ። ሴትዮዋ ትግሉን በከፍተኛ ስሜት ከሚደግፉት የሴቶች ማሀበራት አመራሮች አንዴ ነች ለፍሬሕይወት በፍጹም ጊዜ አልሰጠቻትም በፍጥነት ከዚያ አካባቢ እንድትጠፋ ጎተጎተቻት በደመነፍስ የኡራኤልን መንገድ ተከትላ ሄደች እንባዋ ዐይኖቿን አቃጠላቸው ልትገታው አልቻለችም ገነፈለባት ለስንቱ ተለቅሶ ይዘለቃል ብለሽ ነው ልጄ አሏት አንዲት ሴት በአጠገባቸው ስታልፍ ቀደም ሲል የጠየቀቻቸው ሴት ናቸው እርምጃዋን ቀነስ አደረገችና አብራቸው መሄድ ጀመረች እማማ የሞተውን ልጅ ያውቁታል። ስብሰባ ቦታ ሲደርስ ሄዋንና ሌላ አንድ ሰው ቀድመውታል። ቢከባትም ሁሉን ነገር መጥላት ብትጀምርም ፍሬሕይወት ከቅዱስ ጋር ወደ አላት ተለዋጭ ቀጠሮ መሄድ አለባት በተሰበረ ልብ ብትሆንም በሰዓቱ ደረሰች ቅዱስ ግን የለም ልቧ የበለጠ ፈራባት የቅዱስን ደህንነት ተጠራጠረች ኣስር ደቂቃዎች አለፉ ከዚያ በላይ ግን መቆየት አደገኛ ነው መንገድ ለውጣ ወደሰፈር ተመለሰች ገጽታዋ ተስፋ መቁረጧን የማለፍፍ መሰላት ቅዱስ የት እንደደረሰና ምን እንደገጠመው አላወህቀችም በላይ እንደወጣ አልተመለሰም አስቻለው ሞቶ አስከሬኑ እንኳ እንዳይነሳ ተከልክሉ ባሳደጉት ሰዎች ደጅ ለብዙ ሠዓታት መቆየቱን ስታስበው ይዘገንናታል የአስቻለው እናት ድቅን ተስፋ መቁረጥ ጣውዬ መኗ እባ አሉባት እንባዋን መቆጣጠር አቃታት በዚህ መሪር ሀዘን ወቅት አጠገባቸው ሆና ልታጽናናቸው ብትችል ምን ነበረበት ገኖ የግቢውን በር ስትገባ የበላይሁን እናት ጠሯት። እባክሽን ተጠንቀቂ ፍሬ አላት በላይሁን እንደተገናኙ። አላት ኮስተር ብሎ። ራስ ምታት ሲፈልጣት አድሮ ዓለም ዝብርቅርቅ ብሎባታል ሁኔታዋን ማንም ተመልክቶ ጥሩ ስሜት እንደሌላት ለማወቅ አይቸገርም እናቷም ጠየቋት የምትወዳት የትምህርት ቤት ጓደኛዋ መሞቷን እንደሰማች ነገረቻቸውና አብረዋት አዘኑ ከቤት ሳትወጣ ዋለችና ወደማታ ሄዳ ለቅሶ እንድትደርስ አስፈቀደች ከራሷ ጋር ስትሟገት ሀያ አራት ሰዓት ሊሞላት ቢሆንም ጥርት ያለ አቋም ልትይዝ አልቻለችም ከአንተነህ ጋር መገናኘት እንዳለባቸው ብታምንም ስለሰማችው ነገር ከእርሱ ጋር በመነጋገርና ባለመነጋገር መሀል ተወጥራ ነው አድራ የዋለችው በመጨረሻውም ሰዓት ቢሆን አንተነህን ልትዘጋው እንደማይገባት ነፍሷ ነገረቻት በአስራ ሁለት ሰዓት ከአንተነህ ጋር የተገናኙት መርካቶ ልደት ኬክ ቤት ነው አንተነህ ትናንት ከነበረበት ሁኔታ ብሶበት እንደሆነ እንጂ አልተሻለውም በማንኛም ደቂቃ የከፋ ነገር ሊደርስ እንደሚችል ነው ስሜቷ የሚያንሾካሹክላት ከሁሉም በላይ ሰላሟን ያሳጣት በፓርቲው ውስጥ የተፈጠረው መከፋፈል ነው መተማመን በሌለበት ጥርጣሬ ጉልበት ያበጃል መጠራጠር ደግሞ ኃይልን ይሸረሽራል እርምጃቸው ሁሉ ወደሞት የሚጣደፍ ሆኖ ተሰማት ከአንተነህ ጋር ሲጫወቱ ወትሮ የነበረው ጣዕም አልነበረም ጥቂት ደቂቃዎች ቆይተው ወጡ ወዴት እንደሚሄዱ ባታውቅም አንተነህን ተከተለችው ወደራጉኤል መንገድ ሄዱ ወደፒያሳ የሚሄደው ኖናው አስፋልት ላይ ሲደርሱ ቆሙና ታክሲ ያዙ አራት ኪሎ ከታክሲ ሲወርዱ ለዓይን ያዝ አድርጓልየኸአራት ኪሎ መንደሮች መሀል ባሉ ጨለማ መንገዶች ውስጥ ለውስጥ ሄዱ ከተያያዙትና ጭንቅንቅ ካሉት ትናንሽ ሱቆች በስተጀርባ በጠባብ መንገድ አልፈው አንድ ግቢ በር ላይ ቆም አሌ። እንደገና ሌላ ግቢ መሰል ነገር አለፉና ወደውስጥ ገቡ ጭርንቁስ ቤት ነው አንተነህ መክፈቻ አወጣና በሩን ከፈተ ሁሉ ነገር የሚከናወነው በጸጥታ ነው ተከትላው እንደገባች በሩን ዘጋና ቆለፈው ጨለማው ዐይን ቢወጉ አይታይም ግትር እንዳለች ቀረች አንተነህ በዳበሳ መብራቱን አበራው ውስጡ ከውጭው የባሰ አስቀያሚ ክፍል ነው አስጠላት ግድግዳና ጣሪያውን ተዚዙራ ተመለከተችው አንድ እንኳን ፈካ ያለ ነገር አይታይበትም ጎንበስ ብላ የረገጠችውን መሬት አየችው አፈር ነው ሁሉም ነገር ቀፈፋት ከፊታቸው ሲታዩ የሚብለጨለጩትን ሱቆች ታዘበቻቸው አንተነህ ከግድግዳው ምንም የማትለይ አጭር በር ገፋ አደረጎ ከፈተና የተሻለ እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ አላት ሁኔታዋን የታዘበ በሚመስል አነጋገር በሀሳቧ አንተነህን ባለፈው ያገኘችበትን ሁኔታኖ የአሁኑን እያነጻጸረች ነበርና ለዓላማ ሲባል ሁሉሌንም መሆን እንደሚቻል ለራሷ አረጋገጠች ወደክፍሉ ውስጥ ለመግባት ጎንበስ ማለት ነበረባት። በመጠኑ ሻል ያለ ክፍል ነው በክፍሉ አንድ ጥግ ፍራሽ ተዘርግቷል ብርድልብስም ተነጥፎበታል ከፍራሹ አጠገብ አንድ ወንበር አለ በሌላው ግድግዳ ጥግ ደግሞ አነስ ያለች ጠረሌዛ አለች ጠረጴዛው ላይ የምግብ ማብሰያ ቁሳቁሶች ተደርድረዋል እስከአሁን ቆመሻል እንዴየ አላት አንተነህ የወዲያኛውን ክፍል መብራት አጥፍቶ ሲመለስ ከፍራሹ ዳር ላይ ተቀመጠች በጣም ይቀዘቅዛል እግሯን ሰብስባ ኩርትም አለች አንተነህ ከትንሸ ሻንጣ ውስጥ ጋቢ አውጥቶ አለበሳት ጋቢውን ሲደርብላት ቅዱስን አስታወሰችው የት ደርሶ ይሆን። አላት አንተነህ ጃኬቱን አውልቆ ፍራሹ ላይ እየወረወረው አልኮበለልኩም አለችው። ሌላ ትዝታ እፈልጋለሁ አላት አንተነህ። ተስፋ አንቆርጥም አላት አንተነህ። አንድ ፅድል አለን አላት ዳኙ ከብዙ ማሰብ በኋላ። አላት ታሪኩ ጥቂት እንደሄዱ። ቤት ሲደርሱ ማንም የለም። ያን ጊዜ ሥራ ነበራታ አለችው እናቱ ቀበል አድርጋ። ሁሉም የማሆነው ከቆየን ነው በየትኛዋ ደቂቃ ምን ሊሆን እንደሚችል ምንም መገመት አይቻልም አላት ተስፋ መቁረጡን በሚያሳይ ሁኔታ። አላት አንድ ሰው መኪና ተራው ውስጥ ገብታ ጥቂት እንደቆመች። አጠገቧ ያለውን ሰው ቀና ብላ ተመለከተች። አይዞሽ አላት። አላት ከተማ። አላት ለሁለተኛ ጊዜ። አንተነህ አንድ ሀሳብ በአእምሮው ውስጥ ብልጭ አለበት። ፍሬሕይወት ምን ሆና ይሆን። አዲስ አበባ መመለስሽ ግድ ሆኗል አላት ከተማ ገና ቤት እንደገባ ወደመኝታ ቤት ጠርቷት። ስትገባ አንድ ትልቅ ሰው ተቀምጠዋል ሰውየው በምን ወደዚያ እስር ቤት እንደመጡ ገረማት።