Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
አማካሪ ዶክተር ገረመው ለሙ ፊርማ ቀን ለ በአጥሂው የቀረበ ማረጋገጫ ይህ የመምህርተማሪ ምክክር ወይምእና የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ሂደት ናሙና ከመቅረጸ ድምጽ ወደ ጽሁፍ የተሸጋገረ ከሕከአዘ ማስታወሻ የክፍል ውስጥ ውይይታዊ ሒደቱ የተከናወነው የተማሪዎቹን ትክክለኛ መጠሪያ ስያሜ በመጠቀም ነው በዚህ ጥናታዊ ዘገባ ላይ ግን የምርምር ስነምግባራዊ መርህዎን ከመጠበቅ አንጻር የተማሪዎቹ የየግል መጠሪ ስያሜ የተጸውኦ ስም በወል ስም ተማሪ ተቀይሮ መቅረቡን ልብ ይሏል ከኛ ፉሠማሪ ለጋድ መዎማ ፉጳሳ ፀኛሪ መምህር አሺ ተማሪ የመጀመሪያው አንቀጽ ነው ከዚያ አሁን ቀጣዩ ደግሞ የሀተታው ክፍል ነው የሚቀጥለው ተማሪ አሺ በአጠቃላይ በአጠቃላይ ተማሪ በአጠቃላይ መምህር በአጠቃላይ ብለህ ደግሞ መጨረሻው አንቀጽ ላይ ከላይ ያስቀመጥከውን ሀሳብ ታስቀምጣለህ ማለት ነው ግልጽ ነው።
ባካሄዱት ጥናት ላይ እንደገለጹት በተማሪዎች ጽሁፋዊ ስራዎች ላይ የሚቀርቡ ምጋቤ ምላሾች በሁሉም የተለያዩ እርከኖችደረጃዎች ላይ የሚገኙ የሁለተኛ ቋንቋ ተማሪዎችን የመጻፍ ክሂል ማዳበር ስለመቻሉ ወይም አለመቻሉ አሁን ካለው ተጨባጭ መረጃ አንፃር ጊዜው ገና መሆኑን አመልክተዋል ርከ እንዳስረዱት በመምህራን የሚቀርብ ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ ተማሪዎች ስህተቶቻቸውን በመረዳት እንዲያስተካክሉ የሚረዳ ብቻ ሳይሆን የተማሪዎቹን ተነሳሽነት ለማዳበርና ምቹ የሆነ የመማር ማስተማሪያ አካባቢን ለመፍጠር ይረዳል የመጻፍ ክሂል ከአፍላቂ የክሂል ዘርፍ ይመደባል ከዚህ አኳያ ተማሪዎቹ በተረጋጋና በደስተኛነት ስሜት ሐሳብ ለማመንጨትም ሆነ ከመምህራን የሚቀርቡላቸውን የጽሁፋዊ ስራዎቻቸው ማሻሻያ ግብዓቶችን በተግባር ላይ እንዲያውሉ ለማስቻል የተነሳሽነት ስሜታቸውን ከፍ ማድረግ ያስፈልጋል በዚህም ምክንያት የመምህራን ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ የተማሪዎቹን ፍላጎት ለማነሳሳት ታላቅ ሚና ይኖረዋል በሌላ በኩል ልበ ባቀረቡት ጥናት ላይ የ ህ ን ሐሳብ በመደገፍ አንዳስረዱትየመምህራን ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ ጠቀሜታ የተማሪዎችን ስህተቶች ለማቃናትና ተማሪዎቹ ያሉበትን ደረጃ እንዲገነዘቡ ማድረግ ብቻ ሳይሆን የሌሎች ሰዎችን ጸሀፍያንን አተያይ ዘብፀለ በመውሰድ የግላቸው ሐብት እንዲያደርጉት ይረዳል ክርከ በተመሳሳይ እንደገለጹት በተማሪዎች ጽህፈት ላይ የሚቀርብ ምጋቤ ምላሽ ተማሪዎቹ በልምምድ ወቅት የሚፈጽሟቸውን ስህተቶች በመቀነስ የተማሪዎቹን የመጻፍ ክሂል ለማጎልበት ይረዳል በዚህም ምክንያት እንደ ልባ ጥናታዊ ስራ ዘገባ ተማሪዎች ምጋቤ ምላሽ የማያገኙ ከሆኑ በግል ጥረታቸው ብቻ የሚያከናውኑት ተግባር የተሳሳተ ግንዘቤ ሊፈጥርባቸው ይችላል በተጨማሪም እንደ ጠበበ ገለዓዛ ተማሪዎች ምጋቤ ምላሽ የማያገኙ ከሆኑ ጽሁፋዊ ስራቸውን ፍጹም እንደሆነ በማሰብ የመከለስ አዝማሚያቸው ሊቀንስ ይችላል ከዚህ አኳያ በቅርብ ጊዜ የተከናወነ ጥናቶች ቹከ ቪርከፅበ ጠ ርከ እና ዞዐዘ እንደሚያስረዱትም የመምህር ምጋቤ ምላሽ የተሰጣቸው ተማሪዎች ምጋቤ ምላሽ ካልተሰጣቸው ተማሪዎች በተሻለ ደረጃ ትክክለኛ ጽሁፋዊ ክለሳ ማድረጋቸውን ያረጋግጣሉ ዛዝ በበኩላቸው የምጋቤ ምላሽ አስፈላጊነት ሲያስረዱ ተማሪዎች ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ ካልተቀበሉ ጽሁፋቸውን እንዴት መከለስ እንዳለባቸውና በየትኞቹ ጉዳዮች ላይ ልዩ ትኩረት ማድረግ አንዳለባቸው አስተማማኝ ግብዓት ስለማይኖራቸው ጽሁፋቸውን ለመከለስ አይነሳሱም በመሆኑም በ ማብራሪያ መሰረት ምጋቤ ምላሽ በተለይ የሁለተኛ ቋንቋ ተማሪዎች የመጻፍ ክሂል ትምህርታቸውን አንዴት ማጎልበት እንደሚችሉና በተመሳሳይ መምህራንም የተማሪዎቹ ጽሁፋዊ ችግሮች ምን ምን እንደሆኑ በመመርመር የመፍትሔ ሐሳቦችን ለማቅረብ መሳሪያ ይሆናቸዋል በሌላ በኩል የምጋቤ ምላሽ ጠቀሜታ ለጀማሪ ፀሀፍት ወይም ተማሪዎች ብቻ አለመሆኑን በበጠፀ ገልጸው በአንፃሩ በሳል ጸሀፍትም መልዕክቶቻቸውን ለአንባብያን በተገቢ መንገድ ማቀበል መቻል አለመቻላቸውን ለመፈተሽ ይረዳቸው ዘንድ ከቢጤዎቻቸው ወይም ልምድ ካላቸው አርታኢያን ሸ አገዛን እንደሚጠይቁ አስረድተዋል በአጠቃላይ ከላይ የተለያዩ ተመራማሪዎች አጥፒዎች እና ፀሀፍት ካቀረቡት ማብራሪያ መረዳት የሚቻለው የመምህራን ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ ተማሪዎች ያሉበትን ደረጃ ለመገንዘብ አእንዲችሉ ጠንካራና ደካማ ጎናቸውን እንዲረዱ በምን በምን ጉዳዮች ላይ ልዩ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው እንዲገነዘቡና ጽሁፋቸውን ደጋግመው በመከለስና ድክመቶቻቸውን በማረም የመጻፍ ክሂላቸውን ለማጎልበት የሚያስችላቸው መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን ነው የምጋቤ ምላሽ አይነቶች በመጻፍ ክሂል የምግበረጃን አይነቶች በተመለከተ ምሁራን ከተለያዩ አንግሎች አኳያ በተለያዩ የአመዳደብ ስልቶች በመከፋፈል ለማስረዳት ሞክረዋል ይህን በተመለከተ ኋከዘ እና ሌሎች ከየመጻፍ ክሂል አንጻር የምጋቤ ምላሽ ን አይነቶች የተለያዩ ፈርጆች ያሏቸው መሆኑን በመጠቆም ይሁንና በባህሪ ተመሳስሎነታቸው መሰረት በእየወገናቸው መመደብ እንደሚቻል ለማሳየት ሞክረዋል በዚህም መሰረት ከምጋቤ ምላሽ ከዋኙ ወይም አቅራቢው አንጻር የመምህር የጓደኛ የግል እና ኮምፒዩተር አገዝ ቋንቋ መማር የምጋቤ ምላሽ አይነቶች ከምጋቤ ምላሹ የአቅርቦት ጊዜ አንጻር የዘገየ እና ፈጣን የምጋቤ ምላሽ አይነቶች ከምጋቤ ምላሹ ቅርጽ አንጻር ቀጥተኛ አና ኢቀጥተኛ ምጋቤ ምላሽ ከምጋቤ ምላሹ የአቀራረብ ወይም ያከዋወን መንገድ አንጻር የመምህርተማሪ ምክክር አና የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ ከምጋቤ ምላሹ የቅድሚያ ትኩረት አኳያ የሰዋስው የሆሄያትፊደላት ወዘተ ምጋቤ ምላሽ ምጋቤ ምላሹ ከሚቀርብበት የጽሁፋዊ ስራው አርከን ወይም ደረጃ አንጻር ከሒደታዊ ጽህፈት መማር ማስተማር ጋር በተገናኽ በክለሳ ደረጃ ላይ የሚቀርብ ምጋቤ ምላሽ በአርትኦትዐቨበ ደረጃ የሚቀርብ ምጋቤ ምላሽ ወዘተ በማለት በሚዛመዱባቸው ባህርያታቸው አማካይነት መመደብ አንደሚቻል ከዉከባ እና ሌሎች አስረድተዋል ከእነዚህ ጸሐፍያን የአመዳደብ ስርዓት አንጻር ይህ ጥናት ቀዳሚ ትኩረት ያደደርገው ከምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ወይም አከዋወን አኳያ በተፈረጁት በመምህር ተማሪ ምክክርና በመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ ላይ ሲሆን የምጋቤ ምላሹን የአቀራረብ ስልትቅርጽ በተመለከተም ሁለቱም ቀጥተኛና ኢቀጥተኛ የምጋቤ ምላሽ አይነቶች ተግባራዊ ተደርገዋል ይህ ከላይ የተገለጸው የምጋቤ ምላሽ አይነቶች የአመዳደብ ስርዓት እንደተጠበቀ ሆኖ አብዛኞቹ ምሁራን አጥፒዎች ቪርከፀከበፀየ አና ሌሎች ፎጸበ ርዕከፀከ የምጋቤ ምላሽ አይነቶች በማለት በተደጋጋሚ የሚጠቅሷቸው ከምጋቤ ምላሽ ከዋኙ ወይም አቅራቢው አኳያ ማለትም የግል የራስ ግምገማ የጓደኛ ምጋቤ ምላሽ የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ እአና የመምህርተማሪ ምክክራዊ ምጋቤ ምላሾች አንጻር በመሆኑ አነዚህን አበይት ሊባሉ የሚችሉ የምጋቤ ምላሽ አይነቶች ምንነት በተመለከተ ቀደም ሲል የተገለጹት ምሁራንና ሌሎችም ያቀረቧቸውን ሐሳቦች በማከተት እንደሚከተለው ለማቅረብ ተሞክሯል ያፖሠሰ ፇምጋማ የግል ግምገማ የሚከናወነው በተማሪው ጸሀፊው አማካይነት ነው የግል ግምገማ መሰረታዊ ዓላማው ተማሪዎች በጽሁፎቻቸው ላይ ተደጋጋሚ ሂሳዊ ንባብ በማከናወን የሀሳባቸውን ትክክለኛነት ተጠያቃዊነት ተያያዥነት ወዘተ በመመርመርና ክለሳ በማድረግ የመጻፍ ክሂላቸውን እንዲያጎለብቱ ማስቻል ነው ይሁን እንጅ አንዳንድ አጥፒዎች የግል ግምገማ በመጻፍ ክሂል ላይ መሻሻል እንደማያመጣ ይገልጻሉ ለምሳሌ ከ ተማሪዎችን በሶስት ምድብ ከፍለው ባካፄዱት ጥናት የደረሱበትን ውጤት ሲገልጹ የራስ ግምገማ ባላከናወኑ ወይም ምንም አይነት ምጋቤ ምላሽ ባልተቀበሉ ተማሪዎችና የራስ ግምገማ ባካሄዱ ተማሪዎች መካከል የቸሎታ ልዩነት ያላስተዋሉ ሲሆን በአንፃሩ የመምህር ምጋቤ ምላሽ በተቀበሉ ተማሪዎች ላይ ግን መሻሻል ማስተዋላቸውን አስረድተዋል በአንፃሩ በ የጓደኛ ምጋቤ ምላሽንና የግል ግምገማን ውጤታማነት በንጽጽር በማጥናት የደረሱበት ውጤት እንደሚያሳየው የግል ግምገማ ያከናወኑ ተማሪዎች የጓደኛ ምጋቤ ምላሽ ከተቀበሉሱ ተማሪዎች በተሻለ ሁኔታ የመጻፍ ክሂል መሻሻል ማሳየታቸውን አስረድተዋል ይቃጋ ያደያኛ ምጋን ምጎ ይህ የምጋቤ ምላሽ ምንጭ በተለያዩ ጸሀፍያን ዘንድ ልዩ ልዩ ስያሜዎች ሲሰጠው ይታያል ከእነዚህም መካከል የጓደኛ ምላሽ የጓደኛ ምዘና የጓደኛ ሂስ የጓደኛ ክለሳ የጓደኛ አርትኦት ወዘተ የሚሉት ይገኙበታል እነዚህ ስያሜዎች የሚወክሉትም አንድ ተማሪ ከሌላ ተማሪ ዳጓደኛ የሚቀበለውን ምጋቤ ምላሽ ለማመልከት ነው የጓደኛ ምጋቤ ምላሽ አንዱ መሰረታዊ የመማርማስተማር ተግባር አካል ሲሆን ተማሪዎች የየራሳቸው የሆኑ አድማጮች እንዳሏቸው እንዲያስቡና የተነሳሽነት ስሜታቸው እንዲጨምር እገዛ ያደርጋል እከ ሀ በበ በ በተጨማሪም የጓደኛ ምጋቤ ምላሽ ፈጣን ምላሽ በማስገኘቱና የመምህሩን እና የተማሪዎችን ጊዜ ቆጣቢ ከመሆኑ አንፃር ተመራጭነት እንዳለው ዞከ ጠቁመዋል በተመሳሳይም አእዘሕበ ያቀረቡትን ሐሳብ ዋቢ በማድረግ እርበቨ እንዳስረዱት የጓደኛ ምጋቤ ምላሽ ተማሪዎቹ አድማጭ በማግኘት በራስ የመተማመን ስሜታቸው እንዲጎለብት የተለያዩ አተያዮችን እንዲቀበሉና ለመጻፍ ያላቸው ፍላጎት እንዲጨምር ሊያደርግ ስለሚችል ጠቃሚነቱ የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል ይሁን እንጅ አዐበአ እና እክህዌከሃ እንደሚሉት የጓደኛ ምጋቤ ምላሽ አተገባበር በሁለተኛ ቋንቋና በመጀመሪያ ቋንቋ ተማሪዎች መቼት ውስጥ በሁለት አበይት ምክንያቶች የተለያየ ያደርገዋል እነዚህም የመጀመሪያው የሁለተኛ ቋንቋ ተማሪዎች ገና ቋንቋውን በመማር ሒደት ውስጥ የሚገኙ በመሆናቸው ምክንያት የጓደኛ አርማትን መቀበል አይፈልጉም ቢቀበሉም አስተያየቱን በጽሁፋቸው ውስጥ አይተገብሩትም በሁለተኛ ደረጃም ተማሪዎች በሚኖርባቸው ባህላዊ ተጽዕኖና የክፍል ውስጥ የመማርማስተማር ዘዴን ካለመገንዘብ በመነጨ ስሜት በክፍሉ ውስጥ ሙሉ ስልጣን ያለው መምህሩ ብቻ ናቸው ብለው ያስባሉ በመሆኑም ተማሪ ጓደኛ በእነሱ ጽሁፍ ላይ ገንቢ ምጋቤ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል በቂ እውቀትና ስልጣን የለውም ብለው ያምናሉ በዚህም ምክንያት ተማሪዎች ጽሁፋቸውን በሚከልሱበት ወቅት የጓደኛቸውን አስተያየት ወደጎን በመተው በመናቅ ስሜት ላይተገብሩት እንደሚችሉ ያስረዳሉ ቦያመምረ ምጋዕን ምጎ የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ በተማሪዎች የጽህፈት ስራ ላይ የሚቀርብን ማንኛውንም ግብዓት ያካትታል ይህ ምጋቤ ምላሽ ተዘውታሪና ተማሪዎች የጽሁፍ ስራዎቻቸውን ለመከለስ የሚያስችላቸው የምጋቤ ምላሽ ምንጭ ነው ይሁን እንጅ እንደ ገለባ የመምህር ምጋቤ ምላሽ ዓላማ በተማሪዎቹ ጽሁፍ ላይ የሚገኙትን ችግሮች ሁሉ በማረም ፍጹም ትክክለኛ ስራ ማድረግ ሳይሆን ተማሪዎቹ ማስተላላፍ የፈለጉትን ሐሳብ ወይም አራሳቸውን በብቃት የሚልፁበትን ስልት እንዲማሩ መርዳት ነው ያመምሀሠረሮ ምጋጌ ምጎጃ ውጨፖታማዕታ ከሌሎቹ የምጋቤ ምላሽ ምንጮች በተለይም ከመምህርተማሪ ምክክር አንፃር ሲቃኝ በመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ ውጤታማነት ላይ የተካሄዱ የተወሰኑ አገርኛና የውጭ አገራት ጥናቶችን ማግኘት በመቻሉ አጥኝው እስካሁን ባገኘው መረጃ መሰረት በዚህ መስክ ከተለያዩ ተላውጦዎች አኳያ የሚመረምሩ በቂ ጥናቶች ተከናውነዋል ለማለት ባያስደፍርም የተሻለ ነው ለማለት ግን ይቻላል ለምሳሌ በአማርኛ ቋንቋ ላይ በአገር ውስጥ በሁለተኛ ዲግሪ ደረጃ ምጋቤ ምላሽን በተመለከተ ከተካሄዱት ሶስት ጥናቶች መካከል ሁለቱ እንዳለ እና ትዕግስት በመምህራን ምጋቤ ምላሽ አሰጣጥ ውጤታማነት ላይ ያተኮሩ ናቸው የጥንታዊ ስራዎቹን ውጤት በተመለከተ በንኡስ ክፍል ስር ይቀርባል የመምህር ምጋቤ ምላሽ ጠቃሚ ነገር ግን ውስብስብ ርጠሀፀ በመሆኑ በርካታ አጥፒዎች ከተለያዩ አቅጣጫዎች ጥናት አከናውነዋል ከእነዚህ ጥናቶች መካከል ክከከ አና ሌሎች በሄ መምህራን በሚያቀርቡት የምጋቤ ምላሽ አሰጣጥ ስልት ማለትም በቀጥተኛ አርማት በመለያ ኮድ እአርማት ስህተቶችን በመክበብ ወዘተ ላይ ያተኮሩ ሲሆኑ ሌሎቹም ለምሳሌ ዘፀሀዐከፀ ዞሾጩከጠዉበ እና ነሃከሃ ከምጋቤ ምላሹ የትኩረት አቅጣጫ ወይም ከቅርጽ በርዘብ እና ከይዘት ርከፀበእ አንፃር በተናጠል ወይም በንጽጽር የመረመሩ ናቸው የመምህራንን ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ ውጤታማነት በጥናት ካረጋገጡት ምሁራን መካከል ለምሳሌ የከጠጸዉበ እና ነሃሃከሃ ተማሪዎችን በአራት ምድብ በመክፈል ሙከራቸውን አከናውነዋል በዚህም መሰረት ለመጀመሪያው የተማሪዎች ምድብ ምንም አይነት የመምህር ምጋቤ ምላሽ ያልተሰጠ ሲሆን ለሁለተኛው ምድብ ሰዋስዋዊ ምጋቤ ምላሽ ለሶስተኛው ምድብ ይዘት ርበዌበከእ ተኮር ምጋቤ ምላሽ እንዲሁም ለአራተኛው ምድብ ይዘትንና ሰዋስውን ያቀናጀ ምጋቤ ምላሽ እንዲወስዱ ተደርጓል በመጨረሻ በተገኘው ውጤት መሰረትም ሶስቱ ምድቦች ከተሰጣቸው የምጋቤ ምላሽ አይነት አኳያ በጽህፈት ስራዎቻቸው ላይ መሻሻል ሲያሳዩ በአንዛሩ ምንም አይነት ምጋቤ ምላሽ ያልወሰዱ ተማሪዎች በቀጣይ ስራዎቻቸው ላይ መሻሻል አላሳዩም ከዚህም በመነሳት የዮነጠጂ እና ነሃሃከሃ በማጠቃለያቸው ላይ አንደጠቆሙት በተለይ ይዘትንና ሰዋስውን ያካተተ የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ መስጠት ለተማሪዎቹ የመጻፍ ክሂል መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሊኖረው እንደሚችል አረጋግጠዋል ሌላው የመምህር ምጋቤ ምላሽን ውጤታማነት በተግባር የፈተሸው የቅርብ ጊዜ ጥናት ሀከ ያከናወኑት ጥናት ሲሆን ይህ ጥናት የመምህርን ቃላዊና ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ በ ህሃዘቪፀበ ዮፀከ ውጤታማነት በተመለከተ በካንቦዲያ በሚገኙ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ አካፄደዋል ጥናቱ የተከናወነው በአንድ ክፍል ውስጥ በሚገኙ ተማሪዎች ላይ ሲሆን ተማሪዎቹ በሁለት ምድብ ተከፍለው ቃላዊ ምጋቤ ምላሽ ለ ተማሪዎች አንዲሁም ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽም ለ ተማሪዎች እንዲቀርብ ተደርጓል መረጃዎቹም የተሰበሰቡት በጽሁፋዊ መጠይቅ በከፊል በተዋቀረ ቃለመጠይቅ እና ለሁለት ወራት ያህል በቀረበው የልምምድ ሒደት መጀመሪያና ማጠቃለያ ላይ ተማሪዎቹ ባቀረቡት የአንቀጽ ጽሁፍ አማካይነት ነው የመረጀዎቹ ትንታኔ ተከናውኖ በተገኘው ውጤት መሰረትም ቃላዊ ምጋቤ ምላሽ የተሰጣቸው ተማሪዎች ከንኡሳን ጉዳዮች ማለትም ከሰዋስው ከቃላት ከስርአተ ጽህፈትና ከሆፄያት በተጨማሪም ከአበይት ጉዳዮች ማለትም ከይዘትና የሐሳብ አደረጃጀት አኳያ መሻሻል ሲያሳዩ በአንጻሩ ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ የተቀበሉት ተማሪዎች ግን በጽሁፋዊ ስራዎቻቸው ላይ ከፍተኛ ጥራት መሻሻል ያሳዩት በቋንቋ አጠቃቀምና በሐሳብ አደረጃጀት ላይ ብቻ መሆኑን አጥፒው ገልጸዋል ይሁን እንጅ ዘዐር« እንደጠቆሙት የምጋቤ ምላሽን ልዩ ልዩ ተላውጦዎች ጸዘከ በተመለከተ በማንኛውም ቋንቋ ውስጥ የተሟላ ጥናት ተከናውኗል ለማለት አያስደፍርም ያመምሠረ ጽዶያፉፎ ምጋጌ ምሳ ፇራረ ዴሥፖመጋረጋደቻና መረኘረሥቻ በተማሪዎች ጽሁፋዊ ስራዎች ላይ የሚቀርቡ የመምህራን ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሾች በተለያዩ መንገዶች ሊቀርቡ ይችላሉ ዘዘገ ከእነዚህ የተለያዩ ዘዴዎች መካከል የተማሪቹን የመጻፍ ክሂል ከማጎልበት አኳያ የትኞቹ የተሻሉ ተመራጮች እንደሆኑ ለማረጋገጥ በውጭ አገር ተመራማሪዎች ጥናቶች ተከናውነዋል ከእነዚህ ዘዴዎች ውስጥ ዋና ዋናዎቹ ምልክቶች ሃበ እና መለያዎች ርዐ ቀጥተኛ አርማት አዎንታዊ እና አሉታዊ እርማቶች ጥያቄዎች እና አስተያቶች መሆናቸውን የተለያዩ ጸሀፍያን የ እና ክከቨ ሃጠፀ እና ሌሎች ጠቁመዋል በሌላ በኩል ዘርከጪጠ እነ ዛዝልጠባ እና ጠ ያቀረቡትን ሐሳብ ዋቢ በማድረግ እንደገለጹት መምህራን ለተማሪዎች የሚያቀርቡት ምጋቤ ምላሽ በየትኛው ዘዴ ወይም እንዴት መሆን አለበት የሚለው ጉዳይ በቋንቋ ማስተማር ተግባር ላይ ሰፊ ትኩረት አግኝቶ በርካታ ውይይቶችና ጥናቶች ተካሄደዋል በመሆኑም በዚህ ጥናት ላይ የእነዚህን የምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ዘዴዎች ምንነትና ውጤታማነትን በተመለከተም የተለየዩ ምሁራን ዮፀጠ እና ክከዘ ልዘቨ ክጪጠ ርዐቦ ያቀረቡት ሐሳብ እንደሚከተለው ባጫጭሩ ይቀርባል ኛ ቀጥተኛ እርማት ቀጥተኛ አርማት የተማሪዎቹን ድክመቶች በመጠቆም ትክክለኛውን የቋንቋ አጠቃቀም ወይም ስርዓት የማቅረቢያ መንገድ ሲሆን ይህ ዘዴ የተማሪዎቹን ድክመቶች ምንነትና ትክክለኛ ቅርፅ በመጠቀም ለተማሪዎቹ የሚያስቀረው ተግባር ባለመኖሩ ምክንያት ከከፍተኛ ይልቅ በዝቅተኛ የክፍል ደረጃዎች ላይ ለሚገኙ ተማሪዎች ተመራጭነት እንዳለው ፀ በ እና ከቨ ያስረዳሉ ኛ ኢቀጥተኛ እርማት ይህ የምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ዘዴ የተማሪዎችን ልዩ ልዩ ድክመቶች ምንነት በግልጽ ከመጠቆም ይልቅ ወኪል በሆኑ ምልክቶች እና መለያዎች ኢርቱዕ በሆነ መንገድ የማመልከቻ ስልት ነው ለምሳሌ ማመልከት የተፈለገው ድክመት የስርዓተነጥብ አጠቃቀም ችግር ከሆነ ችግሩ በታየበት ቦታ ላይ በቀስት በማመልከት ወይም ከስሩ በማስመርና ስነ በማለት መጠቆም ይቻላል እንደ ዕርዐዘፎ ገለፃም ስህተት መሆኑን በማሳወቅ ተማሪዎች ትክክለኛውን የቋንቋ አጠቃቀም ስልት በራሳቸው ጥረት አንዲፈልጉ ማመልከት ለተማሪዎቹም ሆነ ለመምህራን እጅግ ጠቃሚ ዘዴ ነው ይሁን እንጅ መምህራን የሚጠቀሙባቸው መለያዎችና ምልክቶች ተማሪዎቹን የማያደናግሩና በየጊዜው የማይለዋወጡ መሆን ይኖርባቸዋል ኛ አዎንታዊ እና አሉታዊ ምጋቤ ምላሾችፁ አዎንታዊ ምጋቤ ምላሾች የተማሪዎቹን ስህተቶች በቀጥታ የማይተቹ ነገር ግን ኢቀጥተኛ በሆነ መልኩ መሻሻል አንዳለባቸው የሚያመለክቱ በመሆናቸው ተማሪዎቹ ለምጋቤ ምላሽ ያላቸው አመለካከት አዎንታዊ እንዲሆን ያደርጋል በመሆኑም ተማሪዎቹ የተሰጣቸውን ምጋቤ ምላሽ በመቀበል በጽሁፎቻቸው ክለሳ ወቅት ለመተግበር ይበረታታሉ በአንፃሩ ትክክለኛ አይደለም ስህተት ነው አንደዚህ አይባልም ወዘተ በማለት የሚቀርቡ አሉታዊ ምጋቤ ምላሾች የተማሪዎቹን ስነልቦና ሊጎዱ ስለሚችሉ ተማሪዎች ለምጋቤ ምላሽ የሚኖራቸው አመለካከት አሉታዊ አንዲሆን መንስኤ ሊሆኑ ይችላሉ ቨበ በዚህም ምክንያት በመጻፍ ክሂል ላይ የተከናወኑ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት አዎንታዊ ምጋቤ ምላሽ ማቅረብ የተሻለ ተመራጭነት ይኖረዋል ኛ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ይህ ዘዴ የተማሪዎቹን ጽሁፋዊ ችግሮች ከማረም ባሻገር ተማሪዎቹ ጽሁፋዊ ስራዎቻቸውን በጥልቀት በመመርመር የሐሳብ ግልጽነት እና የአገላለጽ ስልት ተገቢነትን እንዲፈትሹ ያስችላል በመሆኑም ይህ ዘዴ መምህራን የተማሪዎቹን ስህተቶች በመጠቆምና ጥያቄያዊ አስተያየቶችን በማቅረብ ተማሪዎቹ ለጥያቄዎቹ መልስ በመስጠት ሒደት በራሳቸው ድክመቶቻቸውን የሚያቃኑበትን መንገድ እንዲፈልጉ ለማነሳሳት ይረዳል ከላይ በተጠቀሱትና ሌሎችም መንገዶች የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ በሚቀርብበት ወቅት መምህራን ትኩረት ሊያደርጉባቸው የሚገቡ መሰረታዊ መርሆዎች ፀዘበርሯ ምን ምን እንደሆኑ ኛቨ እና ዘፀዐዐርዐርዩ በሰባት ነጥቦች በመከፋፈል እንደሚከተለው ለማስታወስ ሞክረዋል መምህሩ ብቸኛ መልስ ሰጪ መሆን የለባቸውም ጽሁፋዊ አስተያየት ብቸኛ አማራጭ ሆኖ መታየት የለበትም መምህራን በእያንዳንዱ የተማሪ ጽሁፋዊ ስራ ላይ ለሚታዩት ለእያንዳንዱ ችግሮች ምላሽ እንዲሰጡ አይጠበቅባቸውም የመምህር ምጋቤ ምላሽ በተናጠላዊ አንድ ተማሪ ላይ እና ባቀረበው ጽሁፋዊ ስራ ላይ ብቻ ሊያተኩር ይገባል እንጂ ጥቅል በሆኑ አጠቃላይ የመምህሩ ግንዛቤ ላይ ሊያተኩር አይገባም መምህራን በአንድ ተማሪ ጽሁፋዊ ስራ ላይ ብቻ በማተኮር ከተገቢው በላይ ሐሳባቸውን በጽሁፍ ሊያቀርቡ ሊናገሩ አይገባም መምህራን ማበርታቻን እና ገንቢ የሆኑ ሂሶችን በማዋሀድ ሁለቱንም በምጋቤ ምላሹ ውስጥ ሊያካትቱ ይገባል እንዲሁም መምህራን ተማሪዎቻቸውን በተናጠል አንደ አንድ ግለሰብ ሊያስተናግዲቸው እና ያቀረቡትንም ጽሁፋዊ ስራ በእነሱና በመምህራን በተማሪዎች እንዲሁም በተማሪዎቹ መካከል የሚከናወነው የሐሳብ ልውውጥ አንዱ አካል አድርገው ሊያስቡት ይገባል የሚሉት መሰረታዊ መርኅዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል በአጠቃላይም እነዚህንና ሌሎች ዝርዝር የአተገባበር መርሆዎችንና የአቀራረብ መንገዶችን በጠበቀ መልኩ መምህራን የሚያቀርቧቸውን ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሾች ምሁራን የ ከሀ በተለያዩ ፈርጆች በመከፋፍል እንደሚከተለው ለመግለጽ ሞክረዋል ያመምሀረ ጽሥፉፎ ምጋዕን ምጎ ለመዳድሮሀ የተለያዩ ምሁራን የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሾችን ከርዝማኔዎቻቸው ከሚይዙት የቃላት መጠን አኳያ ወይም ከሚያስተላልፉት መልእክት አኳያ በተለያዩ መንገዶች ለመፈረጅ ለመመደብ ሞክረዋል አነዚህ ምሁራን የጠቆሟቸው የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ ምደባዎች በአቀራረባቸው ቢለያዩም በውስጣቸው ከሚያካትቷቸው መሰረታዊ ነጥቦች አኳያ ግን ተመሳሳይነት አላቸው በዚህም ምክንያት ሁሉንም ማቅረብ ተገቢ ባለመሆነ የሚከተሉት የ ፀጠ እና ከህከ ምደባዎች በሌሎቸ ጸፃፍያን የተነሱትን መሰረታዊ ነጥቦቸ አካተው የያዙ በመሆናቸው ምክንያት ለአብነት ቀርበዋል በዚህ መሰረት ዘ በአቀረቡት ሞዴል የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ አቀራረብ አይነቶችን በርዝማኔዎቻቸው እና አስተያየቶቹ በሚያስተላልፏቸው መልእክቶች በሁለት በመመደብ አንደሚከተለው በምሳሌዎች አጠናክረው ለማስረዳት ሞክረዋል ሀ የአስተያየት ርዝማኔ በሚይዙት የቃላት ቁጥር ልኬት መሰረት አጭር አስተያየት ከ ቃላት አማካይ አስተያየት ከ ቃላት ረዥም አስተያየት ከ ቃላት በጣም ረዥም አስተያየት እና ከዚያ በላይ ቃላት ለ የአስተያየት አይነቶች ፈርጆች ጥያቄ ወይም መረጃ መጠየቅ ለምሳሌ ለመግለጽ የፈለከው ነገር በትክክል ምንድን ነው ። ከስ ሀለጓት ችሙፈቡሁ አከናውነዋል የመጽምም ፀየቦሀ ቁጥጥር ቡድን ቅሙፈቡሶ አከናውነዋል ድሙፈቡሶ ርበቪክር የሀ ቅሙቡአ ቅድመ ሙከራ ፈተና ቡድን አንድ የመጽምም የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ ቅሙቡሁ ቅድመ ሙከራ ፈተና ቡድን ሁለት ድሙቋቡአ ድህረ ሙከራ ፈተና ቡድን አንድ ቅሙቡሶ ቅድመ ሙከራ ፈተና ቡድን ሶስት ድሙመቡሁ ድህረ ሙከራ ፈተና ቡድን ሁለት የመተም የመምህርተማሪ ምክክር ድሙቡሶ ድህረ ሙከራ ፈተና ቡድን ሶስት በሰንጠረዥ ላይ የተጠቆሙት የእነዚህ ሁለት ጽሁፋዊ ፈተናዎች ርፅስ ተመሳሳይ ወይም አንድ አይነት ነው የርዕሱ አመራረጥ ሒደትም አጥፒው በመጀመሪያ ሶስት የረዥም ጊዜ ልምድ ያላቸው መምህራንን የተማሪዎቹን መማሪያ መጽሐፍ በመጠቀም ከተማሪዎቹ አጠቃላይ ዳራ አንጻር ጽሁፍ ለመጻፍ አመቺ የሆኑ ከ ርዕሶችን እንዲያቀርቡ በማድረግ እነዚህን ርዕሶች በመጀመሪያ ለጥናቱ ተሳታፊ ተማሪዎች ቀርበው ተማሪዎቹ ለፅህፈት የሚመርጧቸውን ርዕሶች እንዲጠቁሙ ተደርጓል በመቀጠልም በአብዛኞቹ ተማሪዎች የተመረጠውን ርዕስ በመለየት ለጥናቱ የቅድመ ሙከራና የድህረሙከራ ፈተናዎች ርዕስ በመሆን ቀርቧልቅድመ ሙከራ ጥናቱም በዚሁ መንገድ ተከናውኗል የፈተናው አቀራረብም ጥያቄ መመሪያ ወይም ቅርጽ ዐዘበከ አቀራረብ በ ሃቨ የጽሁፋዊ ስራ ፈተና አቀራረብ ስልት የተዘጋጀ ነው በአባሪ ኘ ላይ የቀረበውን መመልከት ይቻላል የጽህፈት መልመጃዎች በዘከ በቅድመ ሙከራ ጥናቱ ላይ ቅድመ እና ድህረ ፈተናውን ጨምሮ በአራት የተለያዩ ርዕሶች ላይ እንዲሁም በዋነው ጥናት ላይ ተማሪዎቹ በተመረጡ ሰባት የተለያዩ ርዕሶች ላይ የቅድመና ድህረ ፈተናዎቹን ርፅሶች ጨምር ከ ቃላት ባላነሰ ጽሁፎችን በክፍል እና በቤት ስራ ዐበጠፀበ መልክ እንዲጽፉ ተደርጓል በዋነው ጥናት ላይ የርእሶቹ ብዛት ሰባት የተደረገበት ምክንያት ተማሪዎቹ በአንድ ወሰነትምህርት ውስጥ የሚኖራቸውን ክፍለጊዜያት በአግባቡ በመጠቀም በዚህ የጊዜ ቀመር ውስጥ የሚያሳዩትን የመጻፍ ክሂል ለውጥ ደረጃ ለመለካት ያስችላል ተብሎ ስለታመነ ነው ከእነዚህ ሰባት ርዕሶች ውስጥ ስድስቱ ለጽህፈት ልምምዳዊ ሒደቱ ሲውሉ አንዱ ርዕስ ደግሞ ለቅድመና ለድህረ ፈተና ተግባራት ሊውል ችሏል በመሆኑም በእያንዳንዱ ስድስት ርዕሶች ላይ የመጀመሪያውን ረቂቅና የመጨረሻውን ጽሁፍ ጨምሮ ሶሰት ሶስት ረቂቆችን ጪቪ በአጠቃላይ ጽሁፎችን እና ሁለት የቅድመና ድህረ ፈተናዎችን በድምሩ ጽሁፋዊ ስራዎችን በዋናው ጥናት ላይ አከናውነዋል ጽሁፎቹን የሚጽፉት በአራት የተለያዩ የአፃፃፍ ስልቶች ማለትም በትረካ ከበከህ በገለፃ ቨዐ በአስረጂ »ዐዐቪካ እና በአነፃፃሪ ርክዐበ የአፃፃፍ ስልቶች ነው በተለያዩ የአጻጻፍ የአደራረስ ስልቶች እንዲጽፉ የሚደረግበት ምክንያትም ቀደም ሲል በምእራፍ ሁለት ንኡስ ክፍል ስር በተገለጸው ለዚህ ጥናት በቀረበው ጽንሰፃሳባዊ ሞዴል መሰረት ተማሪዎቹ ከቀላል የአፃፃፍ ስልት ወደከባድ እንዲሸጋገሩ በማድረግ በእነዚህ በተለያዩ የአፃፃፍ ስልቶች ላይ የሚያጋጥሟቸው ችግሮች የይዘት ወይም የቅርጽ ልዩነቶች ያሏቸው ከሆኑ ነጥረው አንዲወጡ ለማድረግ ስለሚስችሉና ይህንንም ሐሳብ ሊያጠናክሩ የሚችሉ የተለያዩ ጽሁፋዊ መልመጃዎች በተማሪዎች የመማሪያ መጽሐፍ ውስጥ የሚገኙ በመሆናቸው ምክንያት ነው የርዕሶቹ መረጣ ሒደትም የተከናወነውነፁ በአጥሂው በተጠፒ ተማሪዎቹና በአማርኛ መምህራን ተሳትፎ ነው የአተገባበር ሒደቱን በተመለከተም በመጀመሪያ የተጠፒ ተማሪዎቹን ባህላዊ ዳራና የብስለት ደረጃ በቅርበት ሊረዱ የሚችሉና የረዥም ጊዜ ልምድ ያላቸው ሶስት መምህራን ከአስር እስከ አስራ አምስት የሚደርሱ የተለያዩ ርዕሶች እንዲያቀርቡ ከተደረገ በቷላ ከዚህም በመቀጠል እነዚህን ርዕሶች ለተጠፒ ተማሪዎቹ በማቅረብ ከአንድ ጀምረው እስከ መጨረሻው ድርስ ለጽሁፍ ርፅስነት የቅድሚያ ትኩረት የሚሰጧቸውን በደረጃ እንዲጠቁሙ ተደርጓል በተከታይም በአብዛኞቹ ተማሪዎች የቅድሚያ ትኩረት የተሰጣቸው አስር ርዕሶች ተለይተው በአብዛኞቹ ተማሪዎች የተመረጠውና የመምህራንን ይሁነታም ያገኘው ርዕስ ለቅድመና ድህረ ፈተና እንዲሆን በማድረግ ቀሪዎቹ ስድስት በተከታታይ የተማሪውን ትኩረት ያገኙ ርዕሶችም ለክፍል ውስጥና ለቤት ስራ ጽሁፋዊ ልምምዶች በርዕስ ነት እንዲቀርቡ ተደርጓል ይህን ማድረጉ ያስፈለገበት ምክንያትም ምንም እንኳ ስቀድሞ እነዚህ ርዕሶች በመማሪያ መጽሐፍ ላይ ሲቀርቡ ለክፍል ደረጃው እንደሚመጥኑ በባለሞያዎች ታምኖባቸው ቢሆንም ከዚህም ባሻገር ምናልባት ተማሪዎቹ በርእሶቹ ላይ ባለቸው ፍላጎቶች ግንዛቤዎች እና የተለያዩ ዳራዎች ምክንያት በጽሁፋዊ ስራዎቻቸው ላይ ሊፈጠሩ የሚቸሉ አሉታዊ ተጽአኖዎች ወይም የውጤት ልዩነት አምጪ ተላውጦዎችን አስቀድሞ ለመቀነስ ያስችላል የሚል ግንዛቤ በመኖሩ ምክንያት ነው የጽህፈት መልመጃዎቹ አቀራረብ ሒደትም የመማሪያ መጻህፉን በመጠቀም በመጻህፉ ላይ በቀረቡት መመሪያዎች ወይም ትአዛዛት መሰረት የተለያዩ የአቀራረብ ስልቶችን በመከተል ለምሳሌም ማብራሪያዎችን ገለጻዎችን ወይም ትእዛዞችን በማስቀደም መነሻ የሚሆኑ ሐሳቦችን በማቅረብ አስፋፍተው አንዲጽፉ በማድረግ ምሳሌዎችን በማቅረብ ቢጋሮችን በመጠቀም ጅምር ሐሳቦችን ወይም ታሪኮችን አስፋፍተው እንዲጽፉ በማድረግ ወዘተ ተግባራዊ ተደርገዋል ቃለመጠይቅ ከከህ ቃለመጠይቅ የቀረበው ለተማሪዎች ሲሆን ዓላማውም በሙከራ ጥናቱ ወቅት ተግባራዊ በተደረጉት በመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽና በመምህርተማሪ ምክክር ላይ ያላቸውን አጠቃላይ አስተያየቶች ለማሰባሰብ ነው የጥያቄዎቹ ብዛት አስራ አንድ ሲሆኑ አቀራረባቸውም በከፊል የተዋቀሩ ጠሀህርኪፀ ናቸው ጥያቄዎቹም በክፍል ውስጥ የጽህፈት ልምምድ ሂደት ላይ ያተኮሩ እንዲሆኑ በማድረግ በመጀመሪያ በአጥፒው ከተዘጋጁ በጊላ በተከታይነትም ሁለተኛ ዲግሪ ያላቸው ሶስት የአማርኛ መምህራንና ሁለት የስነልቦና ዞኔሃርከነ ባለሞያዎች ተገምግመው አስተያየት እንዲሰጡባቸው ተደርጓል በመጨረሻም ለጥናቱ አማካሪ ቀርበው ተጨማሪ ማሻሻያ ተደርጎባቸዋል ከዚህም ባሻገር በመጀመሪያ ለዋናው ጥናት ከመቅረቡ በፊት በቅድመ ሙከራ ጥናቱ ላይ ተፈትሾና መጠነኛ ማሻሻያ ተደርጎ ለምሳሌ የሞያዊ ቃላት ለተማሪዎቹ በቀላሉ ግልጽ አለመሆን ችግር በመስተዋሉ በምሳሌዎች እንዲብራሩ ተደርጓል በዋናው ጥናት ላይ ለሙከራ ቡድን አንድና ቡድን ሁለት ቀርቧል ከእያንዳንዱ ተማሪ ጋር የተከናወነው ቃለመጠይቃዊ ሒደትም በአማካይ ከአስር አስከ አስራምስት ደቂቃዎች የወሰደ ነበር መረጃዎቹም በመጀመሪያ በመቅረጸ ድምጽ ተሰብስበው ከዚያም ቃል በቃል ወደ ጽሁፍ እንዲሸጋገሩ ሀጨበበ ተደርጓል አነዚህ ቃለመጠይቃዊ ጥያቄዎችም የቅድመ ጥናቱ በአባሪ ሀ እንዲሁም የዋነው ጥናት በአባሪ ኀ ላይ ቀርበዋል ከዚህም በተጨማሪ ከቃለመጠይቃዊ ሂደቶቹ የተሰበሰቡት ናሙና መረጃዎችም የቅድመ ሙከራ ጥናቱ በአባሪ ለ ኛ እና ኛ እንዲሁም የዋናው ጥናት በአባሪ ኛ እና ኛ ላይ ቀርበዋል ከዚህም በተጨማሪ እነዚህን መረጃዎች በይዘቶቻቸው ተመሳሳይነት በንኡሳን ርዕሶች ስር በመመደብ በዋናው ጥናት በምእራፍ አራት ንኡስ ክፍል ውስጥ ማብራሪያዎችን ወይም ገለጻዎችን ለማቅረብ ጥረት ተደርጓል የመረጃ አሰባሰብ ሒደት ርከከ ኮርርሀህጤ ከላይ ለመግለጽ እንደተሞከረው ከመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎች መካከል ቅድመ ሙከራ ፈተና እና ድህፈ ሙከራ ፈተና እንዲሁም የተማሪዎች ጽሁፋዊ ስራዎች በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ የተማሪዎቹ ልዩ ልዩ የክፍል ውስጥ ጽሁፋዊ ስራዎች እንደመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያነት ሊካተቱ የቻሉት ለሙከራ ቡድኖቹ የቀረበው የድህረ ሙከራ ፈተና ውጤት እና ለተማሪዎቹ የቀረበው ቃለመጠይቅ መነሻ በመሆን ያገለገሉት እነዚህ የመምህር ተማሪ ምክክርና የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ የተከናወነባቸው የተማሪዎች ጽሁፋዊ ስራዎች ስለሆኑ ነው በእነዚህ የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎች አማካይነት የሚከናወነው የመረጃ አሰባሰብ ሒደትም እንደሚከተለው ይሆናል የቅድመ እና ድህረ ሙከራ ፈተናዎች ቅድመና ድህረ ሙከራ ፈተናዎች በቅድመ ሙከራ ጥናቱና በዋና ጥናቱ መጀመሪያ እና ማጠናቀቂያ ላይ የቀረቡ ናቸው የፈተናዎቹ ዓላማም በጥቅሉ ሲታይ የጥናቱን ተሳታፊ ተማሪዎችን ወቅታዊ ነባራዊ የመጻፍ ክሂል ችሉታ ለመረዳት እና በሙከራ ሒደቱ መጨረሻ ላይ ተማሪዎቹ ያሳዩትን ለውጥና የለውጡን ደረጃ በቡድኖቹ ውስጥ በተናጠል እንዲሁም በቡድኖቹ መካከል በንጽጽር ለመመርመር ነው የፈተናዎቹም አቀራረብ አንድ አይነት ነበር ይህ ማለት በሌላ አገላለጽ በቅድመ ሙከራ እና በድህረ ሙከራ ፈተናዎቹ ላይ ለተማሪዎቹ የቀረበው የጽሁፍ ርዕስ የጊዜ መጠንና የአጻጻፍ ትዕዛዛትመመሪያዎች በሁለቱም ጊዜያት አንድ አይነት ነበሩ ፈተናዎቹ የቀረቡት ለሶስቱም ቡድኖች ሲሆን ሶስቱም ቡድኖች በተመሳሳይ ጊዜያት ውስጥ በአጥሂውና በሁለት ተጨማሪ መምህራን እገዛ አማካይነት ጽሁፋዊ ተግባራቱን እንዲያከናውኑ ተደርጎ ወረቀቶቹ ተሰብስበዋል አነዚህ የተማሪዎች ቅድመና ድህረ ሙከራ ፈተናዎችም በተመረጡ ሁለት የተለያዩ አራሚዎች መምህራን ውጤት እንዲሰጣቸው ተደርጓል አራሚዎቹም ከአስራ አምስት እስከ ሰላሳ አመታት ያህል ጥናቱ በተከናወነበት አካባቢ የማስተማር ልምድ ያላቸው በመሆናቸው ምክንያት የተማሪዎቹን አጠቃላይ ዳራ ማለትም ባህላዊ ሐይማኖታዊ ስነልቦናዊወዘተ አንዲሁም የአማርኛ ቋንቋ የጽሁፋዊ ስራዎቻቸው ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በተመለከተ አስቀድሞ በቂ ግንዛቤ ያላቸው ናቸው ተብሎ ይታመናል የአራሚዎቹ ተናጥላዊ ግላዊ የአስተራረም ሒደት አንድ ወጥ አካሄድን የተከተለና ከጊዜ ወደ ጊዜ የማይለዋወጥ ለማድረግ ይቻል ዘንድም የመጀመሪው ቅድመ ሙከራ ጥናት ከመከናወኑ በፊት በቅድሚያ በጥናቱ ላይ በተግባር በሚውለው የ ህከ እአና ሌሎች የተማሪዎች ጽሁፋዊ ስራዎች መመዘኛ መስፈርት ይህ መስፈርት በአባሪ መ ላይ ቀርቧል ላይ አጥፒው በተገኘበት ሰፊ ምክክር በማከናወን በአራሚዎቹ ዘንድ በቂ ግንዛቤና የጋራ መግባባቶች እንዲኖሩ ተደርጓል በተመሳሳይ በአራሚዎቹ መካከል ያለውን አስተማማኝነት ለማረጋገጥና በሁለቱ አራሚዎች የተገኘውን ውጤት በመተንተን ለማነጻጸር ይቻል ዘንድ ለማህበራዊ ሳይንስ መስክ የመረጃ ትንተና ሒደት ሊውል የሚችለውን የ ኮ ፕሮግራምን በተግባር ላይ በማዋል የፒርሰን ኮርሌሽን ኮፊሽንት ዐበ ርበዌልቨበ ርፀቨርጪበከ ተሰልቶ በሁለቱ አራሚዎች መካከል ጉልህ የሆነ የአስተራረም ልዩነት አለመኖሩን ለማረጋገጥ ተችሏል በሁለቱ አራሚዎች መካከል ጉልህ የሆነ የአስተራረም ልዩነት ባለመታየቱ ምክንያትም ቀደም ሲል በዚህ ጥናት ትልም ዐፀዐ ላይ ተጨማሪ ሶስተኛ አራሚ ወይም አጥፒው ተሳታፊ የሚሆኑት በሁለቱ አራሚዎች መካከል ጉልህ ልዩነቶች ሲታይ እንደሆነ በመገለጹ ምክንያት በቅድመ ሙከራ ጥናቱም ላይ ሆነ በዋናው ጥናት ላይ ሶስተኛ አራሚ ማካተቱ አስፈላጊ ሆኖ አልተገኘም የህ የአራሚዎችን አስተማማኝነት ለማረጋገጥ የተከናወነው የመረጃ ትንተና ሂደት የዋናው ጥናት በንኡስ ክፍል እንዲሁም የቅድመ ሙከራ ጥናቱ በንኡስ ክፍል ስር እና ስር ባጭሩ ቀርቧል ከዚህም በተጨማሪ ሰንጠረዣዊ መረጃዎች በ አባሪ ዘ ላይ ቀርበዋል የተማሪዎች ጽሁፋዊ ስራዎች የጥናቱ ዓላማ የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ እና የመምህር ተማሪ ምክክር በተማሪዎች ጽሁፋዊ ስራዎች ላይ ከቀረቡ ከተካሄዱ በኋላ የተማሪዎቹ የመጻፍ ክሂልእድገት ላይ ያላቸውን የተጽዕኖ አይነት አዎንታዊ ወይም አሉታዊ እና የተጽእኖ ደረጃ መመርመር ነው በዚህ ሒደት ውስጥ የመምህር ምጋቤ ምላሽ በሁለት አበይት ጉዳዮች ይዘታዊ ርበፎበክ እና ቅርጻዊ በርጠ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ በተለያዩ ስልቶች ቀርቧል እነዚህም ይዘታዊው ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ በህዳግ ጠከ ወይም በጽሁፍ መጨረሻ ላይ በአረፍተነገር ወይም በአንቀጽ መልክ ሲቀርብ በተጨማሪም ቅርጻዊው ምጋቤ ምላሽ በቀጥተኛ እና በኢቀጥተኛ አቀራረብ ስልት ቀርቧል ኢቀጥተኛው አቀራረብም በኮዳዊ ወይም በመለያ ዐ እና በኢኮዳዊ ሀበር የምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ስልቶች ተግባራዊ ተደርጓል በዚህም ጊዜ በምእራፍ ሁለት በተገለጸው መሰረት ተማሪዎቹ ተግባራዊ የሚሆኑትን ምልክቶችና ትርጓሜዎቻቸውን ወይም ውክልናዎቻቸውን በተመለከተ ገለጻ ተደርጎላቸዋል በተመሳሳይ በተማሪዎች ጽሁፋዊ ስራዎች ይዘት ላይ የተካሄዱት ምጋቤ ምላሾች ያተኮሩት በምዕራፍ ሁለት ስር በቀረበው ንድፈሐሳባዊ መረጃዎች መሰረት በጽሁፍ አደረጃጀት በአንቀጽ አገነባብ እና በሐሳብ ተያያዥነት ርከበ ላይ ሲሆን የተማሪዎችን የፀሀፊዎችን የተነሳሽነት ስሜት የሚቀንሱ አሉታዊ አስተያየቶችን በመቀነስ አዎንታዊ አስተያየቶች ምክሮችና የማሻሻያ ሐሳቦችን ለማቅረብ ጥረት ተደርጓል በተመሳሳይ በመምህርተማሪ ምክክር ላይ ፀሀፊውን በስም በመጥቀስ ተናጠላዊ ቡድናዊ ወይም ትብብራዊ ምክክር በማከናወን በጽሁፋዊ ስራዎቻቸው ላይ የተመሰረተ ውይይቶች እና አስተያየቶች ተካናውነዋል ከዚሁ ጋር በተያያዘ ለተማሪዎቹ የሚቀርበው ጽሁፋዊ አስተያየትና በመምህር ተማሪ ምክክር ላይ የሚቀርቡትን የመወያያ አጀንዳዎችና ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ተገቢነት ያላቸው መሆን ወይም አለመሆናቸውን ለማረጋገጥ ይቻል ዘንድ በመጀመሪያው የተማሪዎች ጽሁፋዊ ረቂቅ ላይ የቀረቡትን በተግባር የዋሉትን አስተያየቶችና የመወያያ ርአሰጉዳዮችን የያዙ ናሙናዎችና መረጃ መመዝገቢያ ቅጽ በፎቶኮፒ በማባዛት ልምድ ላላቸው ሁለት የተለያዩ መምህራን ለግምገማ በማቅረብ ከመምህራነ ጋር ምክክር ተደርጓል በመምህራኑ የተሰጡ መጠነኛ አስተያየቶችና የማሻሻያ ሐሳቦችን ለምሳሌ ቀለል ያለ ቋንቋ መጠቀምና ረዘም ያሉ አስተያየቶች አሰልቺነት እንዳይኖራቸው አጠር አድርጎ ማቅረብን በተመለከተ በመቀበል በተከታዮቹ የተማሪዎች ረቂቆች ላይ ተግባራዊ እንዲሆኑ ተደርገዋል የትግበራ ሒደቱን በተመለከተም ተማሪዎቹ በአያንዳንዱ ርዕሶች ላይ በአቀረቧቸው የመጀመሪያ ረቂቃዊ ጽሁፎች ላይ ለቡድን አንድ በምክክር እንዲሁም ለቡድን ሁለት በጽሁፍ መልክ በይዘት ላይ ያተኮሩ ምጋቤ ምላሾችን ካከናወኑ በኋላ ያገጂቸውን ምጋቤ ምላሾች አስተያቶች የማሻሻያ ሐሳቦች ማበረታቻ ወዘተ በግብአትነት ተጠቅመው ሁለተኛውን ረቂቅ ጽፈው እንዲያቀርቡ ተደርጓል በሁለተኛው ረቂቃዊ ጽሁፍ ላይም በቅርጽ ላይ ያተኮረ ምጋቤ ምላሽ እንዲቀርብላቸው ተደርጓል ይህ ቅርጽ ወይም መዋቅርተኮር ምጋቤ ምላሽ በቀዳሚነት የቀረበውም በተለያዩ ምሁራን በተደጋጋሚ በተጠቆሙትና ዋና ዋና በሚባሉት አምስት የሁለተኛ ቋንቋ ተማሪዎች መዋቅራዊ የጽህፈት ድክመቶች ላይ ማለትም በቃላት አጠቃቀም በቁጥር መስማማት ባለቤትና ማሰሪያ አንቀጽ ስምምነት በድርጊት ጊዜ እንዲሁም በስርዓተነጥብ አጠቃቀም ላይ በሚስተዋሉ መሰረታዊ ችግሮች ላይ የቅድሚያ ትኩረት በማድረግ ነበር በእነዚህ ቅርጻዊመዋቅራዊ ድክመቶች እናወይም ጠንካራ ጎኖች ላይ ለሁለቱም የሙከራ ቡድኖች የቀረቡት ምጋቤ ምላሾችም ሁለቱንም ስልቶች ማለትም ቀጥተኛ እርማትን እና ኢቀጥተኛ እርማትን ያካተቱ እንዲሆኑ ተደርጓል ምክንያቱም አንደ ሀበዐ አና ከበየ ገለዛ በተማሪዎቹ የመጀመሪያ ልምምዳዊ ጽሁፋዊ ስራዎቻቸው ላይ ቀጥተኛ ምጋቤ ምላሽ መቅረቡ ተማሪዎቹ ትክክለኛውን ቅርጽ ይሁነኝ ብለው እንዲዋሀዱት ወይም የራሳቸው የአጻጻፍ መንገድ እንዲያደርጉት ሲረዳቸው በተመሳሳይ በተከታዮቹ የልምምድ ጊዜያትም ኢቀጥተኛው ምጋቤ ምላሽ መቅረቡም ተማሪዎቹ በመምህራቸው ለተጠቆሙት ድክመቶች ወይም ስህተቶች አማራጭ ምላሾች አዲፈልጉ ይረዳቸዋል በመሆኑም ሁለቱም የየራሳቸው የሆነ ጠቀሜታ ስለሚኖራቸው በቅድመ ሙከራ ጥናቱም ሆነ በዋናው ጥናት ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት ተደርጓል ይህ የክፍል ውስጥ የምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ሒደቱ የተከናወነውም በአጥሂው ቢሆንም በአንጻሩ የቅድመና ድህረ ፈተናዎች እርማት የተካሄደው በሌሎች መምህራን አገዛ ነው ሙከራው ከክፍል መምህሩ ይልቅ በአጥፒው እንዲከናወን ከተመረጡባቸው ምክንያቶች ውስጥ ቀዳሚዎቹ የመጀመሪያው ተማሪዎቹ የሚያከናውኗቸው ጽሁፋዊ እና ምክክራዊ የመምህር ምጋቤ ምላሸ አሰጣጥ ሒደቶች ንድፈሐሳባዊ መረጃዎቹ በሚጠቁሙት መሰረት በትክክል መከናወናቸውን በቅርብ ለመከታተል ወይም ለመቆጣጠር አንዲሁም ተማሪዎቹም በተለያዩ ጊዜያት በተደጋጋሚ የሚቀርቡላቸውን ምጋቤ ምላሾች ተጠቅመው ጽሁፋቸውን መከለስ ወይም አለመከለሳቸውን ትኩረት ሰጥቶ በቅርበት ለመከታተል አመቺ ይሆናል ተብሎ በመታቀዱ ሲሆን ሁለተኛው ምክንያትም የጽሁፋዊም ሆነ የመምህርተማሪ ምክክራዊ የምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ሒደቶችን በተመለከተ ቀደም ሲል በምእራፍ ሁለት ስር ከቀረቡት የተለያዩ ምሁራን ንድፈሐሳባዊ ዳራዎች አንጻር አጥሂው የተሻለ ግንዛቤ ይኖረዋል ተብሎ በመታሰቡ ነው በአጠቃላይም እነዚህ ከላይ በዝርዝር ለመግለጽ የተሞከሩትን የመምህርተማሪ ምክክራዊ የምጋቤ ምላሽና የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ የትኩረት አቅጣጫዎች ቅደምተከተላዊ ሒደታዊ የአቀራረብና አተገባበር ሒደቶች እና እርስበርሳዊ ዝምድናዎቻቸውን ወይም ትስስራቸውን በተመለከተ ከሁለቱ የሙከራ ቡድኖች ቡድን አንድ እና ቡድን ሁለት አኳያ ምን እንደሚመስል ለማመልከት ይረዳ ዘንድ ተከታዩ ስእላዊ መግለጫ ቀርቧል ቅድመ ሙከራ ፈተና የተመረጡ ርዕሶች የተማሪ ጽሁፋዊ ረቂቅ ተማሪ ምጋቤምላሽ ምክክራዊ ይዘት ተኮር ምጋቤ ምላሽ የመምህር ምጋቤ ምላሽ የተማሪ ክለሳ የተማሪ ሆወዐበ ጽሁፋዊ ረቂቅ ቀጥተኛ የመምህር የመወያያ ምጋቤ ምላሽ ጥያቄዎች የመከታተያ ። ፅከ ፎጪበበ ዘዉ ፀጠ ነሃር ጩጨጪ ላይ እንደተረጋገጠው የመምህር ተማሪ ምስክራዊ ምጋቤምላሽ በተገቢውና በትክክለኛው አካፄድ ከቀረበ በሁለተኛ ቋንቋ ተማሪዎች የመጻፍ ክሂል አድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል ሥልት ነው ለማለት ይቻላል ከዚህ አኳያ ዘዘበ ባከናወኑት ጥናት የጠቆሟቸው የመምህር ተማሪ ምክክራዊ ምግበመረጃ አምስት መሰረታዊ ፋይዳዎች ማለትም የመምህር ተማሪ ምክክራዊ ምጋቤ ምላሽ ግላዊ ትምህርትና ማብራሪያ በማቅረብ የመጻፍ ክህሎትን የማዳበር ላቅ ያለ አቅም ያለው መሆኑ እጅግ ሰፊና ጥልቅ የሆኑ ምጋቤ ምላሻዊ አስተያየቶችን በአጭር ጊዜ በማቅረብ የመምህራን ጊዜ ለመቆጠብ መቻሉ ከጽሁፋዊ አስተያየት አንጻር የፊት ለፊት ገለጻና ክንዋኔ ከመሆኑ ጋር በተዛመደም የተሻለ ግልጽና የተመጠነ ሊሆን መቻሉ መምህሩና ተማሪውን በማቀራረብ መልካም ተግባቦታዊ ሂደት እንዲፈጠር ማስቻሉ እንዲሁም ከምክክራዊ ሂደቱ የሚመነጭ የሂሳዊና የተጠያቃዊ አስተሳሰብን በተማሪዎች ህሊና እንዲቀረጽ የማስቻል አቅሙ ጉልህ መሆኑን በዚህ በተከናወነው ጥናትም ላይ በተግባር ለማረጋገጥ ተችሏል ከዚህ አንጻር የዚህ ጥናት ውጤት ከላይ ለአብነት የተጠቆሙት አጥፒዎች የደረሱበትን የመደምደሚያ ሀሳብ የሚያጠናክር ሆኖ ተገኝቷል ማለት ይቻላል በሌላም በኩል ተማሪዎቹ በሚያከናውኑት የምክክራዊ ሂደት ተሳትፎ ላይ ከመምህሩ ባለሙያ የሚቀስሙትን የሐሳብ አገላለጽ እና አነሱ ከሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች ገለጻዎች ማብራሪያዎች አኳያ ከመጻፍ ክዛላቸው በተጓዳኝነት የንግግር ክሂላቸውንም ማዳበር መቻላቸውንና የፍራሀት ስሜታቸውንም ማስወገድ መቻላቸውን ለመረዳት ተችሏል ከዚህም ባሻገር ጽሁፋዊ ተግባራትን ማከናወን ያለባቸው ለምዘና ወይም ውጤት ለማግኘት ወይም ለማጣት ሳይሆን በሚቀርቡላቸው አበረታች አስተያየቶች በመታገዝ ጠንካራ ጎኖቻቸውን በተሻለ ደረጃ ለማሳደግ እንዲሁም ከሚቀርቡላቸው ሂሳዊ አስተያየቶችና ውሱን አሉታዊ ሀሳቦች በመነሳት ድክመቶቻቸውን ለማረም የሚስችላቸው የመማርማስተማሩ ሂደት አንዱ ክፍል አንደሆነ እንዲገነዘቡት አድርጓቸዋል በመሆኑም ተማሪዎች ከዚህ ቀደም ይማሩበት አንደነበረው ውጤት ተኮር የጽህፈት ትምህርት ከመምህራቸው በቀዳሚነት የሚፈልጉት ወይም የሚጠብቁት ማርክ ወይም ውጤት እንዲጻፍላቸው እና ጽሁፋዊ ስራውን ሳይሆን የተጻፈውን ውጤት በማየት ብቻ ወረቀቱን ከእነሱ የሚያርቁት አልያም ቀደው የሚጥሉት እንዳልሆነ ግንዛቤ አግኝተዋል ማለት ይቻላል ስለዚህም በዚህ ጥናት ላይ ተግባራዊ በሆነው የጽህፈት ልምምዳዊ ሂደት መማራቸው የጽሁፋዊ ስራዎቻቸውን ድክመት ጥንካሬ በተመለከተ ከመምህራቸው ጋር በጥልቀት በመወያየትና ስራዎቻቸውንም ደግመው ደጋግመውም በማንበብ በመጨረሻም ተከታታይ ክለሳዎችን ማከናወን አንደሚጠበቅባቸው አስቀድመው አንዲረዱ የሚያደርጋቸው መንገድ አንደሆነ ለመገንዘብ ተችሏል ከዚህም ባሻገር በራስ የመተማመን ስሜታቸውን ከጊዜ ወደግዜ በማሻሻልና ለጽሁፋዊ ስራ ያላቸውን ተነሳሶት አንዲያዳብሩ እንዳገዛቸው ለማወቅ ተችሏል አጥፒው በክፍል ውስጥ የልምምድ ሂደት ላይ በተግባር እንዳስተዋለው ተማሪዎች ጽሁፋዊ ስራዎቻቸውን እንዲያሳዩ ከመጠየቃቸው በፊት በራሳቸው ተነሳሽነት አስተያየት በጽሁፍም ሆነ በውይይት መልክ እንዲሰጣቸው ጥያቄ ያቀርቡ ነበር ይህ የሚያስገነዝበው ተማሪዎች ልምምዳዊ ተግባራቱን መሰረታዊ አላማ በሚገባ መረዳታቸውን እና የሂደቱንም ቅደምተከተላዊ የአተግባበር ስርአት አስቀድመው የሚያውቁት መሆኑን ነው በመሆኑም ከዚህ መረዳት የሚቻለው መምህራን በተለይ ተማሪዎችን የመጻፍ ክሂል ልምምዳዊ ሂደት ከማሰራታቸው በፊት አንደ የመምህር ተማሪ ምክክራዊ ምጋቤ ምላሽና የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ የመሳሰሉ በጥናት የተፈተሹ መሰል ውጤታማ ተግባራትን ወጥነት ባለው መልኩ ሳይሰለቹ በተከታታይ እንዲተገብሩ ማድረግና የትግበራውን መሰረታዊ አላማም ለተማሪዎች ማስገንዘብ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ነው ሌላው የዚህ ጥናት ውጤት እንደምታዊ ትርጓሜ የሚያረጋግጠው የመምህር ምጋቤ ምላሽ ያከናወኑ ተማሪዎች ከቁጥጥር ቡድን ተማሪዎች አንጻር ሲታዩ በድህረ ፈተና ላይ የተሻለ ውጤት ማስመዝገባቸው የሚያሳው ተማሪዎቹ ከሚፈጽሟቸው ግድፈቶች እርማት ወይም ማስተካከያ ባሻገር ማስተላለፍ የፈለጉትን ሐሳብ ወይም አካባቢቸው የመግለጽ አቅማቸው ከቁጥጥር ቡድኑ ተማሪዎች አንጻር ሲመዘኑ የላቀ መሆኑን ነው ይህም ጅዐዐ የመምህር ምጋቤ ምላሽ መሰረታዊ ግቡ ምን እንደሆነ ካቀረቡት ሐሳብ ጋር የሚዛመድ ነው አንደምሁሩ ማብራሪያም የመምህር ምጋቤ ምላሽ አብይ አላመው አንድን ጽሁፋዊ ስራ በማረም የተማሪዎችን ስራ ፍጹም ትክክለኛ ማድረግ ሳይሆን በማንኛውም ርአሰጉዳይ ላይ ሐሳብን በብቃት የመግለጽ ስልትን ማስተማር መሆኑን ከጠቆሙት ሐሳብ ጋር ይዛመዳል ስለዚህም የመምህር ምጋቤ ምላሽ ፈርጀብዙ ፋይዳዎች እንዳሉት የጥናቱ ውጤት አንደምታዊ ትርጓሜ አመላካች ነው የመጻፍ ክሂል ከአፍላቁቂ የክሄል ፀዐህርቨህሄ ፈርጆች ውስጥ አንዱ መሆኑ ይታወቃል በመሆኑም የተማሪዎች የመጻፍ ክሂል መሻሻል በትይዩነት ሃሳብ የመፍጠር የመፈንጠቅ የማደራጀትና በገዘሃድ አውጥቶ የማሳየትየመጻፍ አቅማቸውን ማሻሻል መቻላቸውን ያሳያል በመሆኑም የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽና የመምህር ተማሪ ምክክራዊ ምጋቤ ምላሾች ማጠንጠኛቸው መነሻቸው የተማሪዎች ጽሁፋዊ ስራዎች ቢሆኑም በተጨማሪም መሰረታዊ ግባቸውም ተማሪዎች ጽሁፋዊ ተግባራት በብቃት ለመወጣት የሚያስችል ክህሎት እንዲናጎላብቱ ማስቻል ቢሆንም ከተማሪዎቹ ምላሽም ሆነ አጥፒሂው በተግባር እንደተረዳው ከመጻፍ ክሄል እና ከቋንቋ ትምህርቱም ባሻገር የአስተሳሰብ አድማሳቸውን ለማስፋትና አካባቢያቸውን ለመግለጽ አስችሏቸዋል ለማለት ይቻላል ከትግበራ ሂደቱ እና በጥናቱ ውጤት ማረጋገጥ የተቻለው ሌላው ጉዳይ የመምህር ተማሪ ምክራዊ ሂደቱን ቡድናዊ እና ተናጥላዊ በማድረግ እያፈራረቁ መተባበሩ ለመምህራንም ሆነ ለተማሪዎቹ ከፍተኛ ፋይዳ ያለው መሆኑን ነው ለምሳሌም ከተማሪዎች አንጻር ተማሪዎች አንዱ የሌላው ጠንካራ ጎኖችን በልምድነት እንዲቀስሙ ሲረዳ በአነጻሩ ብልህ ከሌሎች ስህተቶች ይማራል እንዲሉ ተማሪዎች የሌሎች ተማሪዎችን ስህተቶች እንዳይደግሙ ይረዳቸዋል በአንጻሩ ከመምህራን አኳያም ተመሳሳይ እና ተደጋጋሚ የሆኑ በተለይ በአፍ መፍቻ ቋንቋ ተጽዕኖ ምክንያት የሚከሰቱ ወይም የአፍ መፍቻን ቋንቋን ሰዋሰዋዊ ስርአት ወደ ሚሜማሩት ቋንቋ በማሸጋገር የሚፈጽሟቸውን የወል ግድፈቶች በአጭር ጊዜ ለይቶ ምጋቤ ምላሾችን በምክክራዊ ሂደቶች ወይም በጽሁፍ በማቅረብ ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ያስችላል በተጨማሪም መምህራን እነዚህን ስልቶች በትግባር ላይ በማዋል ቢጠቀሙባቸው የመጻፍ ክሂሉን የመማር ማስተማር ፃዛደት በማፈራረቅ አሰልቺነትንም ለማስወገድ አንደሚረዳ በጥናቱ የትግበራ ሂደት ለመገንዘብ ችሏል ከትግበራ አኳያም በመምህር ምጋቤ ምላሽ ሂደት ወቅት በመምህሩም ሆነ በተማሪዎች ዘንድ በቅድመ በጊዜ አና በድህረ ምክክር ሂደት ወቅት መተግበር ያለባቸው ጉዳዮችን ሳያዛቡ ተግባራዊ ማድረግ መዘንጋት የለበትም በመሆኑም ከተማሪዎች የግንዛቤና የክፍል ደረጃ አንጻር ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች መለየቱና መመዝገቡ በውይይት ጊዜም ተማሪዎች ሐሳባቸውን እንዲገልጹ በቂ ጊዜ በመስጠትና በማበረታት ሁለትዮሻዊ ተግባቦታዊ ግንኙነቱን ማጠናከርና በሁለቱም ወገን ማስታወሻ መመዝገቡ አስፈላጊነቱ የጎላ ነው ለተገኘው አፇንታዊ ውጤትም እገዛ ማድረጉን መረዳት ተችሏል በድህረ ምስክራዊ ሂደቱም ላይ የዕለቱን የውይይት አበይት ነጥቦች እንዲሁም በተማሪው ትኩረት ማግኘት ያላቸው ቀጣይ ጉዳዮች በማስታወሻ መያዝይ ኖርባቸዋል ይህተግባር አንድም ተማሪ ወደፊት ማሻሻል የለበትን ድክመቶችና ማጠናከር ያለበትን ጥንካሬ በውል እንደገነዘብ ሲረዳው ከመምህራን አንጻር ምየ ቀጣይ ንጊዜ የውይይት አጀንዳ ለመቅረጽና ተማሪው ለውጥ ያሳየባቸውን ወይም ያላሳየባቸውን ጉዳዮች በመለየት ፍሬ ወይም ትርጉም ያለው ምስክራዊ ተግባራትን ለማከናወን እንደሚቻል በዚህ ጥናት ላይ በተግባር ለማረጋገጥ መቻሉን የተገኘው የጥናት ውጤት ያለክታል ይህ ክዋኒም በተናጥል መከናወኑ ተማሪዎች ወደራሳቸው ወደውስጣቸው በማት ለለውጥ እንዲነሱ የሚያነሳሳቸው መሆኑን በጥናቱ ሂደት ማረጋገጥ ተችሏል በአንጻሩም ስክራዊ ሂደቱ በጥቅሉ ለተማሪዎቹ በሙሉ የሚከናወን ቢሆን በተማሪዎች መካከል ከሚኖረው የችሉታ ተበልጦ ጋር የተገናዘበ ተገቢ የሆነ ምስክር ለማከናወን ካለመሳቻሉም በላይ ተማሪዎችም ወደውስጣቸው በመመልከት ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ ና መሻሻሎችን እንደየመጡ የሚያስችላቸው መሆኑ ተናጠላዊ የመምህተ ተማሪ ውይይት ካላከናወኑት ቁጥጥራዊ ቡድን ተማሪዎች ካስመዘገቡት ውጤት መረዳት ይቻላል በሌላ በኩል በቁጥጥር ቡድን ተማሪዎች የተመዘገበው ውጤት የሚጠቀመው እውነታ በውጤት ተኮር አቀራረብ ተማሪዎችን ለመመዘንለመፈተን አላማ ብቻ ታቅዶ ጽሁፋዊ ተግባራትን ማከናወኑ ተማሪዎች የጽህፈትን ስራ እንዲማሩበት ሳይሆን እንዲፈሩት ከማድረጉም ባሻገር የጽህፈት ክሂል ላይ ፈጣንና ከፍ ያለ ውጤት ማስመዝገብ ሂደቱን አዳጋች እንደሚያደርገው የቁጥጥር ቡድኑ ተማሪዎች ከሙከራ ቡድኖቹ ተማሪዎች አንጻር ሲታዩ በልምምዳዊ ሂደቱ ትግበራ ላይ የነበራቸው ተነሳሶት እና ያስመዘገቡት ውጤት ያሳያል ይሁንና ምንም አይነት ጽሁፋዊ ተግባራትን ከማያከናውኑ ተማሪዎች አንጻር ሲታይ ተማሪዎች ሰፊ ልምምድ ከማከናወንና ከግላዊ እርማት አንጻር ለውጥ ሊያሳዩ እንደሚችሉ ይህ በቁጥጥር ቡድኑ የተመዘገበው ውጤት አመላካች ነበር በመሆኑም በተለያዩ ምክንያቶች መምህራን መምህር ምጋቤ ምላሽ ማቅረብ በማችሉበት ሁኔታ ውስጥ ቢሆኑ እንኳን ተማሪዎች ተከታታይነት ያለው ጽሁፋዊ የልምምድ ተግባራትን እንዲተገብሩ አድሉን መስጠቱ በአማራጭነት ሊታይ እንደሚቸል የጥናቱ ግኝት ያሳያል ከዚህ አኳያ ተገቢ የሆነ የመምህራን ምጋቤ ምላሽ ያልቀረበበት የተማሪዎች ጽሁፋዊ ስራ ልምምድ ሄደት ምንም ካለመጻፍ ይቆጠራል የሚል ሐሳብ ያላቸውን ምሁራን አስተያየት ከዚህ ጥናት ግኝት ጋር የሚቃረን ፃሳብ ነበር ለማለት ይቻላል ምክንያቱም በዚህ ጥናት የሙከራ ጥናትም ሆነ ዋናው ጥናት ላይ በተግባር እንደተረጋገጠው ተገቢ የሆነ የመምህር ምጋቤ ምላሽ ያላከናወነ የቁጥጥር ቡድን ተማሪዎች በድህረ ፈተና ውጤቶቻቸው ላይ መሻሻል መሻሻል ማሳየታቸውን ለማየት ተችሏል ባጠቃላይ ከላይ የቀረበው የጥናቱ ውጤት ማብራሪያ ከጥናቱ አብይ አላማ አንጻር ሲሆን ከዚህ በመቀጠልም ከጥናቱ ዝርዝር ዓላማዎች አኳያ የጥናቱን ግኝት ማብራሪያ ይሆናል የመጀመሪያው የጥናቱ ንኡስ ዓላማ የመምህርተማሪ ምክክር በተማሪዎቹ የመጻፍና ክሂል ፅድገት ላይ ምን አይነት ተጽእኖ አዎንታዊ ወይም አሉታዊ ተጽእና እንዳለው እና የተጽእኖው ደረጃም ምን ያህል እንደሆነ መመርመር የሚለው ሲሆን በዚህም መሰረት የመምህርተማሪ ምክክር ያከናወኑ የቡድን አንድ ተማሪዎች በአጠቃላይ በመጻፍ ክሄላቸው ላይ ጉልህ የሆነ አዎንታዊ የውጤት መሻሻል ማስመዝገባቸውን የድህረ ሙከራ ፈተና ውጤቶቻቸው ከቁጥጥር ቡድኑ ጋር በንጽጽር ሲታይ ከተመዘገበው ውጤት ለማረጋገጥ ተችሏል በመሆኑም ከዚህ የመረጃ ትንታፄ ሒደት መገንዘብ የሚቻለው በተማሪዎች ጽሁፋዊ ስራዎች ላይ የሚከናወነው የመምህርተማሪ ምክክር በተማሪዎች አጠቃላይ የመጻፍ ክሂል አድገት ላይ ያለው የተጽእኖ አይነት አዎንታዊ መሆኑን እንዲሁም የተጽአኖው ደረጃም ጉልህ መሆኑን ነው ስለዚህም ከጥናቱ መላምቶች መካከል የመምህርተማሪ ምክክር ባከናወኑ ተማሪዎችና በቁጥጥር ቡድን ተማሪዎች መካከል አጠቃላይ የመጻፍ ክሂል እድገትን በተመለከተ በድህረ ሙከራ ፈተና አማካይ ውጤቶቻቸው ላይ ጉልህ ልየነት አለ የሚለው አማራጭ መላምት ተቀባይነት ማግኘቱን ለማረጋገጥ ተችሏል ሁለተኛው የጥናቱ ንኡስ ዓላማ የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ በተማሪዎቹ የመጻፍ ክሂል ዕድገት ላይ ምን አይነት ተጽእኖ አዎንታዊ ወይም አሉታዊ ተጽእኖና አንዳለው እና የተጽአኖው ደረጃም ምን ያህል እንደሆነ መመርመር የሚለው ሲሆን ለዚህ የጥናቱ ንኡስ ዓላማ በቀዳሚነት መልስ ሊሰጥ የሚችለው መረጃና ትንታኔ የሚገኘው በንኡስ ክፍል ስር ነው በአጠቃላይ በዚህ ንኡስ ክፍል ቡድን ሁለት ከቡድን ሶስት ጋር በንጽጽር የታዩ ሲሆን ከተከናወነው የመረጃ ትንተና ሂደት መረዳት እንደተቻለው የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ ያከናወኑ ተማሪዎች ከቁጥጥር ቡድኑ አንጻር ሲታዩ ጉልህ የሆነ አዎንታዊ መሻሻል ማስመዝገባቸውን ለመረዳት ተችሏል በመሆኑም ይህ ውጤት ከጥናቱ መላምቶች መካከል የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ ባከናወነኑ ተማሪዎችና በቁጥጥር ቡድን ተማሪዎች መካከል አጠቃላይ የመጻፍ ክሂል እድገትን በተመለከተ በድህረ ሙከራ ፈተና አማካይ ውጤቶቻቸው ላይ ጉልህ ልዩነት አለ የሚለው አማራጭ መላምት ተቀባይነት ያገኘ መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል ሶስተኛው የጥናቱ ንኡስ ዓላማ የመምህርተማሪ ምክክር እና የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ የተማሪዎቹን የመጻፍ ክሂል እድገት ከማጎልበት አኳያ ያላቸውን ተመሳሳይነት ወይም ልዩነት በሙከራዊ ጥናት መመርመርየሚለው ሲሆን በዚህ መሰረት በተናጠል የተገኙትን ውጤቶች ትንታፄ ሲቃኝ የመምህርተማሪ ምክክር አና የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ የወሰዱ የሁለቱም ቡድን ተማሪዎች በአጠቃላይ የመጻፍ ክሂሎቻቸው ላይ ጉልህ የሆነ መሻሻል ማሳየታቸውን ለማረጋገጥ መቻሉ ቀዳሚው የዚህ ጥናት ግኝት ነው ለማለት ይቻላል በሌላ በኩል ይህ ሁለቱም የምጋቤ ምላሽ አይነቶች በተማሪዎች ጽሁፋዊ ስራዎች ላይ ያለቸው አዎንታዊ አስተዋጽኦ አነደተጠበቀ ሆኖ የተገኙት ውጤቶች ተጨማሪ አውነታንም አመላካች ነበሩ ለማለት ይቻላል። ከዚህም በተጨማሪ ልዩ ልዩ ልምምዳዊ ሒደቶችን ወይም መልመጃዎችን እንዲሁም የክፍል ውስጥ ስራ የቤት ስራና ልዩ ልዩ ሙከራዎችና ፈተናዎችን የሚያከናውኑት አውቀትና ግንዛቤ ለማግኘት እንጂ ማርክ ወይም ውጤት ተጽፎ አንዲሰጣቸው ብቻ አለመሆኑን መገንዘባቸውን አመልክተዋል በሌላም በኩል መምህራን በጽሁፋዊ ስራዎቻቸው ላይ አስተያየቶች ጥያቄዎች ማሻሻያዎች እና ልዩ ልዩ ማስተካከያዎችን የሚያቀርቡላቸው ጽሁፋዊ ስራዎች ድክመት ስላለባቸው ወይም የተማሪዎች ችሎታ ዝቅተኛ ስለሆነ ሳይሆን ከጊዜ ወደ ጊዜ ችሎታቸው እየተሻሻለ እንዲሄድ ለማስቻል መሆኑን መረዳታቸውን ጠቁመዋል በተለይም ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ የቀረበላቸው ተማሪዎች አስተያየቶቹ ከመጀመሪያ ጀምሮ እስከመጨረሻ ድረስ ከቀይ ብእር ይልቅ በአረንጓዴ ብእር በመጠቀም መቅረብ መቻሉ ቀደም ሲል በቀይ ብእር መቅረቡ ልምምዳዊ ተግባራቱን ከማከናወናቸው በፊት በ አይሳካልኝም እና በ አልችልም ባይነት ስሜት በውስጣቸው ይፈጠርባቸው የነበረው የፍርፃትና የድንጋጤ ስሜት ሊቀንስ መቻሉን በቃለመጠይቃዊ ሒደቱ ላይ በሰጧቸው ምላሾችና በጽሁፋዊ ስራዎቻቸው ላይ በተግባር ለማረጋገጥ ችለዋል ይህ የጥናቱ ውጤት የሚያመለክተው በአገራችን በተለምዶ ምክንያቱ አሳማኝ ሆኖ በውል ባይታወቅም በአንደኛ በሁለተኛም ሆነ በኮሌጆችና በዩኒቨርስቲ ደረጃዎች ላይ መምህራን እርማትም ሆነ አስተያየት በቀይ ብእርአስክርቢቶ መጠቀማቸውን መለስ ብለው እንዲያስቡበት የሚሻ ጉዳይ መሆኑን ነው ምዕራፍ ስድስት ማጠቃለያ መደምደሚያ እና የወደፊት የጥናት አቅጣጫዎች መግቢያ በዚህ ምፅራፍ ውስጥ አራት አበይት ጉዳዮች ይቀርባሉ እነዚህም በቀዳሚነት የዚህ ጥናት ውጥን ከሆነው ከጥናቱ ዓላማ በመነሳት እስከ ጥናቱ ግኝት ማብራሪያ ድረስ በዝርዝር የቀረቡ አበይት ነጥቦች ባጭጭሩ በጭምቅሐሳብ መልክ ይቀርባሉ ከዚሁ ጋር በተያያዘም የጥናቱ መደምደሚያ ይቀርባል በመቀጠልም የጥናቱን ግኝት እንዲሁም የጥናቱን ማጠቃለያና መደምደሚያ መሰረት በማድረግ ባለድርሻ አካላትና የትምህርት ባለሞያዎች ወደፊት ትኩረት ሊሰጧቸው የሚገቡ ተግባራትን በተመለከተ የመፍትፄ ሐሳቦች በሚል ርእስ ምክረሐሳቦችን ለመጠቆም ጥረት ተደርጓል በመጨረሻም ይህን ጥናት እውን ለማድረግ ከተከናወነው ጥልቅ ንባብና ከጥናቱ ሙከራዊ የትግበራ ሒደት በመነሳት ለቀጣይ ተመራማሪዎች የጥናት አቅጣጫዎች ሐሳብ ፈንጣቂ ሊሆኑ ይችላሉ ተብለው የሜታሰቡ ርእሰጉዳዮች የወደፊት የጥናት አቅጣጫዎች በሚል ንዑስ ርዕስ ስር ለመጠቆም ተሞክሯል ማጠቃለያ የዚህ ጥናት ዓብይ ዓላማ የነበረው የመምህርተማሪ ምክክር ርበአዌጩከርበ እና የመምህር የጽሑፍ ምጋቤ ምላሽ በለበቪበ ሾፀከ በተማሪዎች የመጻፍ ክሂል ዕድገት ላይ ያላቸው ተጽዕኖ በጥቅሉ ሲታይ ምን አይነት አዎንታዊ ወይስ አሉታዊ እንደሆነና የተጽእኖው ደረጃም ምን ያህል እነደሆነ በሙከራዊ ጥናት መመርመር ነበር በዚህ አቢይ ዓላማ ስር በጥናቱ መቋጫ ላይ ምላሽ ያገኛሉ ተብለው የታሰቡ አምስት የጥናቱ ንኡሳን ዓላማዎችም ነበሩ እነዚህም ኛ የመምህርተማሪ ምክክር በተማሪዎቹ የመጻፍ ክዛል ዕድገት ላይ ምን አይነት ተጽእኖ አዎንታዊ ወይም አሉታዊ ተጽአኖ አንዳለው እና የተጽእኖው ደረጃም ምን ያህል እንደሆነ መመርመርኛ የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ በተማሪዎቹ የመጻፍ ክሄል ፅድገት ላይ ምን አይነት ተጽአኖ አመንታዊ ወይም አሉታዊ ተጽእአና እንዳለው እና የተጽእኖው ደረጃም ምን ያህል እንደሆነ መመርመርኛ የመምህርተማሪ ምክክር እና የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ የተማሪዎቹን የመጻፍ ክሂል እድገት ከማጎልበት አኳያ ያላቸውን ተመሳሳይነት ወይም ልዩነት በሙከራዊ ጥናት መመርመር ኛ የመምህር ተማሪ ምክክርና የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ የተለያዩ የተማሪዎች ንዑሳን የጽሁፍ ክሂሎችን ጽሁፋዊ ስራ ይዘት አደረጃጀት ቃላት አመራረጥ የቋንቋ አጠቃቀም እና ስርአተ ጽህፈት ድክመቶች ከመቀነስ አንጻር ሁለቱ የምጋቤ ምላሽ አይነቶች በእነዚህ የተለያዩ የተማሪዎች ንዑሳን የመጻፍና ክሂሎች ላይ የሚኖራቸውን ተጽእኖዎች ተመሳሳይነት ወይም ልዩነት ያላቸው መሆናቸውን መመርመር በመጨረሻም ኛ የመምህር ተማሪ ምክክርና የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ የክፍል ውስጥ አተገባበር ሂደት በተመለከተ በተማሪዎች የመጻፍ ክሂል እድገት ላይ ከሚኖራቸው አዎንታዊ ወይም አሉታዊ ተጽእኖዎች አንጻር ተማሪዎች ያላቸውን አስተያየት መመርመር የሚሉት ንኡሳን የጥናቱ ጥያቄዎቸ ነበሩ ጥናቱ የተከናወነው በዶዶላ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ሲሆን ጥናቱ የተከናወነበት የጊዜ ገደብም ከ ዓም እስከ ዓም ድረስ አጥሂው በአካል በመገኘት ለትልመ ጥናቱ ለሙከራ ጥናቱና ለዋናው ጥናት የሚረዱ የተለያዩ መረጃዎችን ከትምህርት ቢሮዎች ከመምህራን እንዲሁም በዋነኛነት የጥናቱ ተሳታፊዎችከነበሩት ተማሪዎች ተግባራዊ የክፍል ውስጥ ልምምዳዊ ሒደቶችን በማከናወን ልዩ ልዩ መረጃዎችን በማሰባሰብ ነበር የእነዚህ መረጃዎች የመሰብሰቢያ መሳሪያዎችም በቀዳሚነት ተማሪዎች በክፍል ውስጥ ያከናወኑዋቸው ልዩ ልዩ መልመጃዎች በ ዓም እና በ ዓም ሁለት ተከታታይ የትምህርት ዘመናት ውስጥ ለሁለት ወሰነ ትምህርት የተከናወነ ለጥናቱ ተተኳሪዎች የቀረበ የቅድመ ሙከራና የድህረ ሙከራ ፈተናዎቹ እንዲሁም ለጥናቱ ተሳታፊ ተማሪዎች ለአማርኛ መምህራን ለርዕሳነ መምህራን አና ለትምህርት ቢሮ ሐላፊዎች በ ዓም በትልመጥናቱ ዝግጅት ወቅት በአጠቃላይ በምእራብ አርሲ ዞን የሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ሁኔታ በተመለከተ በቀረቡላቸው ቃለመጠይቆች አማካይነት ነበር ይህን የጥናቱን ዓላማ ከዳር ማድረስ ይቻል ዘንድም ሙከራዊ ጥናት ተግባራዊ ተደርጓል ይህ የጥናት ስልት የተመረጠበት ምክንያትም ከጥናቱ አቢይ ዓላማ አንጻር ጥገኛ ያልሆኑ ተላውጦዎች ጥገኛ በሆኑ ተላውጦዎቸ ላይ ያላቸውን ተጽእኖ መመርምር ተመራጭ በመሆኑ ምክንያት ነበር በዚህም መሰረት ከተከናወኑት ልዩ ልዩ ንኡሳንና ዓበይት ተግባራት መካከል ቀዳሚው ዓብይ የመረጃ ትንተና ተግባር የነበረው ሶስቱም የጥናቱ ተሳታፊቡድኖች በተናጠል ሲታዩ ከልምምዳዊ ተግባራቱ በኋላ በድህረ ፈተና ውጤቶቻቸው ላይ ያሳዩትን አሉታዊ ወይም አዎንታዊ ለውጦች መመርመር ነበር በዚህ ሒደት የተገኘው ምላሽ እነደሚጠቁመውም ሁለቱም የሙከራ ቡድኖች በተናጠል ከቁጥጥር ቡድኑ አንጻር ሲታዩ በጽሁፋዊ ክሂላቸው አድገት ላይ ጉልህ የሆነ አዎንታዊ መሻሻል ማሳየታቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል ይህም መሻሻል በአሐዝ ሲገለጽ የቡድን አንድ ተማሪዎቹ አማካይ የመጻፍ ክሂል ውጤታቸው በ ነጥብ ሲጨምር በተመሳሳይ ቡድን ሁለት በ ነጥብ አንዲሁም ቡድን ሶስት ተማሪዎቹ አማካይ የመጻፍ ክሂል ውጤታቸው በ አማካይ ነጥብ መሻሻል ማሳየታቸውን ለመረዳት ተችሏል ይህም ውጤት ከጥናቱ ዓብይ ዓላማ አኳያ በጥቅሉ ሲታይ የመምህርተማሪ ምክክር እና የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ በተማሪዎች የመጻፍ ክሂል እድገት ላይ ያላቸው የተጽእኖ አይነት አዎንታዊ ሲሆን የተጽአኖው ደረጃም ጉልህ እንሆነ ያስረዳል ከዚህም በተጨማሪ ቀደም ሲል የቀረበውን አሐዛዊ መረጃ ትንታኔ በንጽጽር ሲታይ አንደምታዊ ትርጓሜው የሚጠቁመው የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ ከመምህርተማሪ ምክክር አንጻር ሲታይ የ አማካይ ነጥብ ብልጫ ቢያመለከትም ይህ ውጤት በመካከላቸው ጉልህ ልዩነት እንደማያመለክት ከተከናወነው የልዩነት ትንተና የተገኘው ውጤት ያስረዳል ከዚህ የጥናቱ ግኝት በመነሳትም የመምህር ተማሪ ምክክርና የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ መካከል ተባልጦን በመፍጠር አንዱን ከሌላው ተመራጭ ማድረግ እንደማይቻል ለማረጋገጥ ተችሏል በሌላ በኩል ሁለቱም የመምህር ምጋቤ ምላሽ አይነቶች የየራሳቸው የሆኑ ጠንካራ ጎኖች አንዳሏቸው ግንዛቤ ተገኝቷል ይኸውም ከንኡሳን የተማሪዎች የመጻፍ ክሂሎች አንጻር የሙከራ ቡድኖቹ በተናጥል ከቁጥጥር ቡድኑ ጋር ሲነጻጻሩ ሁለቱም ከጽሁፋዊ ስራ ይዘትና አደረጃጀት ላይ ጉልህ የሆነ መሻሻል ሲያሳዩ ከዘህ በተጨማሪ ግን የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሽ ያከናወኑ የቡድን ሁለት ተማሪዎች ከቃላት አጠቃቀምና ዝርዝር ከሆነ ከስርአተ ጽህፈት አማካይ ውጤቶቻቸው አንጻር ጉልህ የሆነ መሻሻል አስመዝግበዋል ይሁን እንጅ በቃለመጠይቅ የተገኘው መረጃ አንደሚያመለክተውና በተጨማሪም በክፍል ውስጥ በተካፄደው ጽሁፋዊ የልምምድ ሒደት ላይም አጥፒው በተጨባጭ ለማረጋገጥ አእንደቻለው የመምህርተማሪ ምክክር ያከናወኑ ተማሪዎች በጽሁፋዊ ስራዎቻቸው ላይ ከመምራቸው ጋር ቀርቦ በግልጽ የመወያየት የመጠየቅና ምላሽ የመስጠት ልምድን እንዲያጎለብቱ እንዳስቻላቸው እንዲሁም በቋንቋ ትምህርቱ ላይ የተሻለ አዎንታዊ አመለካከቶችን እንዲያዳብሩ ከማስቻሉ አንጻር ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ ነው ለማለት ያስችላል በዚህም ምክንያት ተማሪዎችን ወደፊት በዚህ አይነት መንገድ የማስተማሩ ሒደት ቢቀጥል በመጻፍ ክሂላቸው ላይ ብሎም በሌሎቹ ተጓዓዳኝ የቋንቋ ክሂሎቻቸው ላይ በተለይ በመናገርና በማዳመጥ የሚኖራቸውን ችሎታ ለማዳበር እንደሚረዳቸው በጥናቱ የትግበራ ሒደት ላይ የተገኙ መረጃዎች አንደምታዊ ትርጓሜዎች ያስረዳሉ በአጠቃላይም ቀደም ሲል ከተገጸው የጥናቱ አንደምታዊ ትንተና እና በሁለቱ ሙከራዊ ቡድኖች መካከል ከተመዘገበው ተቀራራቢ አጠቃላይ የድህረ ሙከራ ፈተና አማካይ ውጤት አኳያ ሁለቱም ተቀራራቢ የሆነ ፋይዳ አስመዝግበዋል ለማለት ይቻላል መደምደሚያ በአጠቃላይ ከላይ በአጫጭሩ የቀረቡትን አበይት የጥናቱ ውጤቶች መሰረት በማድረግ የሚከተለው ድምዳሜ ላይ መድረስ ተችሏል ኛ በተማሪዎች ጽሁፋዊ ስራዎች ላይ የሚደረጉ የመምህርተማሪ ምክክራዊ ምጋቤ ምላሽም ሆነ የመምህር ጽሁፋዊ ምጋቤ ምላሾች በተማሪዎች የመጻፍ ክሂል አድገት ላይ ያላቸው ተጽእኖ አዎንታዊ መሆኑንና የተጽአኖው ደረጃም ጉልህ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል ይህም አውነታ ቀደም ሲል በምእራፍ ሁለት ውስጥ ይህን ጉዳይ በተመለከተ በተለያዩ ምሁራን የቀረቡትን ሁለት ተቃራኒ ሐሳቦች ከአገራችን መቼትና ተጨባጭ እውነታዎች አኳያ አንዱን በመደገፍና ሌላውን በመቃወም ሐሳብ ለማቅረብ አስችሏል ለማለት ይቻላል በዚህም መሰረት በተለይ ከገራችን ሁለተኛ ቋንቋ ተማሪዎች ስነልሳናዊና አጠቃላይ ዳራ አንጻር የመምህር ምጋቤ ምላሽ ጉልህ ጠቀሜታን በተመለከተ ጠንካራ የድጋፍ አቋም ያላቸውን የ ዘዐዩ ጠ እና ዘነሃበ ሂ እና ዘዛሃበ የ ምሁራን ሐሳቦች ከማጠናከር አኳያ የሚዛመድ ሲሆን በአንጻሩ በእነ ዘሀ ፐፌጢርዐቪ እና ርከቪሸ የቀረበውን ሐሳብ ማለትም በሁለተኛ ቋንቋ ተማሪዎች ጽሁፋዊ ስራዎች ላይ የሚከናወን የመምህር ምጋቤ ምላሽ አቅርቦት ሒደት አላስፈላጊ ብቻ ሳይሆን እጅግ ጎጂ ተግባር በመሆኑ ሊወገድ ይገባል በማለት ያቀረቡትን ማብራሪያ ትክክለኛ አለመሆን በተጨባጭ ማስረጃ ያረጋገጠ ውጤት ተገኝቷል ማለት ይቻላል በመሆኑም በዚህ ጥናት የተገኘው ውጤት የመምህር ምጋቤ ምላሽ ለተማሪዎች የመጻፍ ክሂል መዳበር የሚያበረክተው አስተዋጽኦ አዎንታዊ ከመሆኑም ባሻገር ጉልህ የሆነ መሻሻል ሊያስመዘግብ መቻሉን የዚህ ጥናት ውጤት አመላካች መሆኑን ለመረዳት ተችሏል ኛ ሌላው ጉዳይ የመምህርተማሪ ምክክር በተናጥል ሲታይ ከተመዘገቡት ጉልህ መሻሻሎች መካከል በተለይ የትኛውን ንኡስ ክሂል ላቅ ባለ ደረጃ ለማዳበር ረድቷል። መልስ አዎ ጥያቄ በአጠቃላይ አስካሁን መምህሩ በጽሁፋዊ ስራህ ስራሽ ላይ ስላከናወኑት የምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ሒደት ምን አስተያየት አለህ አለሽ። መልስ አዎ አረዳዋለሁ ጥያቄ መምህር ምጋቤ ምላሽ አተገባበር ሒደት ላይ የወደድከው ነገር ምንድን ነበር። መልስ አዎ አረዳዋለሁ ጥያቄ በመምህር ምጋቤ ምላሽ አተገባበር ሒደት ላይ የወደድከው ነገር ምንድን ነበር። መልስ አዎ ለኛ ተማሪ አምስት ክፍል የምማረው ዶዶላ ሁለተኛ ደረጃ ጥያቄ በጽሁፋዊ ስራህ ስራሽ ላይ የመምህር ምጋቤ ምላሽ አንዲቀርብልህ አእንዲቀርብልሽ ትፈልጋለህ ትፈልጊያለሽ። መልስ አዎ ጥያቄ በመምህር ምጋቤ ምላሽ አተገባበር ሒደት ላይ የወደድከው ነገር ምንድን ነበር። ካልተረዳህውካልተረዳሽው ምን ታደርጋለህታደርጊያለሽ መልስ አዎ ጥያቄ በአጠቃላይ አስካሁን መምህሩ በጽሁፋዊ ስራህ ስራሽ ላይ ስላከናወኑት የምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ሒደት ምን አስተያየት አለህ አለሽ። መልስ አም ግልፅ ነው ጥያቄ በአጠቃላይ እስካሁን መምህሩ በጽሁፋዊ ስራህ ስራሽ ላይ ስላከናወኑት የምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ሒደት ምን አስተያየት አለህ አለሽ። መልስ አንድ ፅሁፍ ከፃፍኩኝ በላ ጥያቄ የመምህር ምጋቤ ምላሽ ጽሁፋዊ ስራዬን እንዳሻሽል ረድቶኛል ብለህ ብለሽ ታስባለህ ታስቢያለሽ። መልስ አዎ ግልፅ ነው ጥያቄ በመምህር ምጋቤ ምላሽ አተገባበር ሒደት ላይ የወደድከው ነገር ምንድን ነበር። መልስ አዎ ጥያቄ መምህሩ ካቀረቡት ቀጥተኛ አርማት ጽሁፋዊ ስህተቶችን በቀጥታ ከማስተካከል እና ቀጥተኛ ካልሆነ እርማት ስህተቶች መኖራቸውን ከመጠቆም ከማመልከት የትኛው ስልት ጽሁፋዊ ስራዬን ለማሻሻል አረድቶኛል ብለህ ብለሽ ታስባለህ ታስቢያለሽ። መልስ መጀመሪያ ርዕስ ከፃፍኩኝ በኋላ ለማሻሻል ጥያቄ የመምህር ምጋቤ ምላሽ ጽሁፋዊ ስራዬን አንዳሻሽል ረድቶኛል ብለህ ብለሽ ታስባለህ ታስቢያለሽ። መልስ የለም ጥያቄ በመምህር ምጋቤ ምላሽ አተገባበር ሒደት ላይ የወደድከው ነገር ምንድን ነበር። መልስ አዎ አረደዋለሁ ጥያቄ በመምህር ምጋቤ ምላሽ አተገባበር ሒደት ላይ የወደድከው ነገር ምንድን ነበር። ስለዚህ በዚህ ቢቀጥል ጥሩ ነው በጣም ጥሩ ነው ጥያቄ በአጠቃላይ አስካሁን መምህሩ በጽሁፋዊ ስራህ ስራሽ ላይ ስላከናወኑት የምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ሒደት ምን አስተያየት አለህ አለሽ። መልስ አዎ ጥሩ ነው ጥያቄ በመምህር ምጋቤ ምላሽ አተገባበር ሒደት ላይ የወደድከው ነገር ምንድን ነበር። ምጋቤ ምላሹ እንዲቀርብልህ እንዲቀርብልሽ የምትፈልገው የምትፈልጊው ጽሁፋዊ ስራው ምን ደረጃ ላይ እያለ ወይም ሲደርስ ነው የመምህር ምጋቤ ምላሽ ጽሁፋዊ ስራዬን እንዳሻሽል ረድቶኛል ብለህብለሽ ታስባለህ ታስቢያለሽ። መልስ አዎ ጥያቄ በመምህር ምጋቤ ምላሽ አተገባበር ሂደት ላይ የወደድከው ነገር ምንድን ነበር። መልስ ያው የሚያርምልኝን ጥያቄ ወደፊት በመምህራን ምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ሂደት ላይ ምን ምን ጉዳዮች ቢሻሻሉ ቢቀነሱ ወይም ቢካተቱ የተሻለ ይሆናል ብለህ ብለሽ ታስባለህ ታስቢያለሽ። አረፍተ ነገር መልስ አዎ ጥያቄ በመምህር ምጋቤ ምላሽ አተገባበር ሂደት ላይ የወደድከው ነገር ምንድን ነበር። መልስ አዎ ጥያቄ በአጠቃላይ እስካሁን መምህሩ በጽሁፋዊ ስራህ ስራሽ ላይ ስላከናወኑት የምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ሂደት ምን አስተያየት አለህ አለሽ። መልስ አይ በቃ እንዲሁ ምንም አስተያየት ሳይሆን ዝም ብዬ በጣም ጥሩ ነው ነኛ ተማሪ ሶስት ክፍል ጥያቄ በጽሁፋዊ ስራህ ስራሽ ለይ የመምህር ምጋቤ ምላሽ አንዲቀርብልህ እንዲቀርብልሽ ትፈልጋለህ ትፈልጊያለሽ። መልስ አዎ እረዳዋለሁ ጥያቄ በመምህር ምጋቤ ምላሽ አተገባበር ሂደት ላይ የወደድከው ነገር ምንድን ነበር። መልስ ሁለተኛውን ጥያቄ ወደፊት በመምህራን ምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ሂደት ላይ ምን ምን ጉዳዮች ቢሻሻሉ ቢቀነሱ ወይም ቢካተቱ የተሻለ ይሆናል ብለህ ብለሽ ታስባለህ ታስቢያለሽ። መልስ አሥ አሻሽላለሁ ጥያቄ በአጠቃላይ እስካሁን መምህሩ በጽሁፋዊ ስራህ ስራሽ ላይ ስላከናወኑት የምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ሂደት ምን አስተያየት አለህ አለሽ። መልስ ጥሩ ነው ነኛ ተማሪ አስራ ሶስት ክፍል ጥያቄ በጽሁፋዊ ስራህ ስራሽ ለይ የመምህር ምጋቤ ምላሽ አንዲቀርብልህ አንዲቀርብልሽ ትፈልጋለህ ትፈልጊያለሽ። መልስ የመጀመሪያው መምህሩ እያረመ ቢሰጠኝ ጥያቄ ወደፊት በመምህራን ምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ሂደት ላይ ምን ምን ጉዳዮች ቢሻሻሉ ቢቀነሱ ወይም ቢካተቱ የተሻለ ይሆናል ብለህ ብለሽ ታስባለህ ታስቢያለሽ። መልስ በጣም ጥሩ ነው ነኛ ተማሪ አስራ ዘጠኝ ክፍል ጥያቄ በጽሁፋዊ ስራህ ስራሽ ለይ የመምህር ምጋቤ ምላሽ አንዲቀርብልህ እንዲቀርብልሽ ትፈልጋለህ ትፈልጊያለሽ። መልስ አዎ እረደዋለሁ በጣም አዎ ጥያቄ በመምህር ምጋቤ ምላሽ አተገባበር ሂደት ላይ የወደድከው ነገር ምንድን ነበር። መልስ ቀጥተኛው እርማት ጥያቄ ወደፊት በመምህራን ምጋቤ ምላሽ አቀራረብ ሂደት ላይ ምን ምን ጉዳዮች ቢሻሻሉ ቢቀነሱ ወይም ቢካተቱ የተሻለ ይሆናል ብለህ ብለሽ ታስባለህ ታስቢያለሽ።