Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ትምህርተ ዛህዩማናትና ክርስቲያናዊ ሕፀዉት ምዕራፍ ሦስት ክርስቲያናዊ ሕይወት ከእግዚአብሔር የተሰጠው ሕጉ ነበር ሁለቱ የቃል ኪዳን ወገኖች ማለት እግዚአብሔርና ሕዝቡ የሚገናኙበት በሕጉ ላይ በተሰጡት ቃሎች ነበር ሕዝቡ ሕጉን ከጠበቁ እግዚአብሔር ደግሞ ሕዝቡን ይጠብቅ ነበር። ሐዋርያትም ለጸሎትና ለቃሉ አገልግሉት ይተጉ ነበር የሐዋ ሥራ። እኛም የእነርሱን አርአያ በመከተል በእግዚአብሔር ጸጋ ታግዘን ለእንደዚህ ዓይነቱ ኃጢአት ጸም ጠቃሚ መሆኑን የማያምን ቢኖር በራሱ መንፈሳዊ ሕይወት ይሞክርና ይዐወቅ በጸም በጸሎትም የሚኖር ካለ በጳጁ ያለው ነገር ወርቅ እንጂ መዳብ እንዳልሆ ግ ትገነንኽኮ እንጻይጠትፍከት ክጥብቅ ጅያኽ ጾም እሎጭት የሚናጭ ነገር ሕጮ ደለም ራሱን የቻለ ታላቅ መንፈሳዊ ገድል ነው በጾም በጸሎት እግዚአብሔርን ማገልገል እንችላለን በጸምና በጸሎ ትም ሌሊትና ቀን እያገለገለች ከመቅደስ አትለይም ነበር ተብሎ የተጻፈላት ነቢይቱ ሐና ሕፃኑ ኢየሱስን በቤተ መቅደስ አገኘችው በዚያችም ሰዓት ቀርባ እግዚአብሔርን አመሰገነች የኢየሩሳሌምንም ቤዛ ለሚጠባበቁ ሁሉ ስለ እርሱ ትናገር ነበር ሉቃ ንጽሕን ስለ መጠበቅ ከዝሙት ስለ መሸሸ በክፍል ሦስት ምዕራፍ ሁለት አታመንዝር የሚለውን ትእዛዝ ተመልከት ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛደመሟኖትቫ ክርስቲያናዊ ሕይደዉት በሥጋ ድክመትና በዚያም በኩል የሚመጣውን ፈተና የምንከላከልበትን መንገድና ስልት ከቅዱሳት መጻሕፍትና ከቅዱሳን ገድል መማር አለብን መን ፈሳዊ ተጋድሉን ከሐዋርያው ጳውሎስ እንማር እርሱ በውጭም በውስጥም ብዙ ዓይነት ፈተናና መከራ ደርሶበታልና በሐዋርያዊው ኃላፊነትና ሥራው ከደረሰበት መከራና ፈተና ሌላ በሥጋው በኩል የሚያጋጥመውን ፈተና እንዴት እንደተቋቋመውና ሥጋንም መግዛት እንዴት እንደሚቻል ሲገልጽ እኔ ያለ አሳብ እንደሚሮጥ ሁሉ እንዲሁ አልሮጥም ነፋስ እንደሚጐስም ሁሉ እን ዲሁ አልጋደልም ነገር ግን ለሌሎች ከሰበክሁበኋላ ራሴ የተጣልሁ እንዳልሆን ሥጋዬን እየጉሰምሁ አስገዛዋለሁ ብሏል ኛቆሮ ሥጋን መጉጐሰም ማለት ምንድን ነው።
ትምህርተ ዛህዩማናትና ክርስቲያናዊ ሕፀዉት ምዕራፍ ሦስት ክርስቲያናዊ ሕይወት በመንፈሳዊ ተጋድሉሎ መልካሙን ገድል ተጋድዩአለሁ ሩጫውን ጨርሼአለሁ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ ወደፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል ይህንም ጻድቅ ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ ያስረክባል ደግሞም መገለጡን ለሚወዱት ሁሉ እንጂ ለእኔ ብቻ አይ ደለም ኛጢሞ ይህ ቃል ቅዱስ ጳውሉስ በሐዋርያዊ አገልግሎቱ መጨረሻ ላይ ውድ ልጁ ለሆነው ለጢሞቴዎስ በጻፈው በሁለተኛ መልእክቱ ላይ ይገኛል ሐዋርያው የክርስቶስን መስቀል በመሸከም መከራ በመቀበል መላ ሕይወቱን በመንፈሳዊ ተጋድሎ ፈጽሞታል ረጂሙንም ሐዋርያዊ ጉዞ በማድረግ በታናጂ እስያና በምድረ አውሮፓ በባሕርና በየብስ በተፋጥኖ ከሥራ ጓደኞቹ ጋር በመዘ ዋወር የክርስቶስን የምሥራች ዜና ለብዙዎች እንዲዳረሰና በጨለማም ለሚኖ ሩት አሕዛብ የክርስቶስ ብርሃን እንዲበራላቸው አድርጓል በዚህም አገር አቋ ራጭ ጉዞው የተልዕኮውን ሩጫ ሐዋርያዊ አገልግሎቱን በመፈጸሙ የጽድቅ አክ ሊል እንደሚቀዳጅ ገልጸልናል የእርሱን ፈለግ ለሚከተሉት የክርስቶስን መገለጥ ለሚወዱት ሁሉ ይህን የጽድቅ ዋጋ እንደሚያገኙ አስረድቷል ሰለዚህ እያንዳንዳችን በተሰጠን ጸጋ መሠረት የሐዋርያውን ትምህርትና አርአያ ተከትለን እንደ ስጦታችንና እንደ ችሎታችን መንፈሳዊ ሩጫችንን መጀመር ይገባናል መልካሙን ገድል መንፈሳዊ ተጋድሏችንን መቀጠል ይኖርብናል በክርስቶስ ጸጋ ሆነን የምናደርገው መንፈሳዊ ተጋድሎ ክርስቲያናዊ ሕይወታችንን ለመልካም ውጤት ያበቃዋል መልካም ፍሬን እንዲያፈራ ያደርገዋል እንግዲህ በዚህ በያዝነው ምዕራፍ በመጀመሪያው ርእሰ ትምህርት ውስጥ መንፈሳዊ ተጋድሎ ለክርስቲያናዊ ሕይወት አስፈላጊነቱንና ምንነቱን እን ዲሁም አፈጻጸሙ ችግርና መከራ ያለበት ስለ መሆኑ በአጭሩ ተገልጣል መንፈሳዊ ተጋድሎ በትዕግሥት መከራ መቀበልን የሚጠይቅ ቢሆንም ተስፋው በሰማይም በምድርም ዋጋ ያለው ስለሆነ ተጋዳዩን ያረካዋል የልብ ደስታና ሰላም ይሰጠዋል በመሠረቱ ያለ ጸጋ አጋዥነት መንፈሳዊ ተጋድሎ ግቡን ስለማይመታ ጸጋን ለማግኘት እግዚአብሔርን በጸሎት መለመን ያስፈልጋል ስለዚህ ቀጥሎ በሁለተኛው ርእሰ ትምህርት ስለ ጸሎት ከሙሉ በከፊሉ ለማ ቅረብ ጥረት ተደርጓል በመጨረሻም ስለ መንፈሳዊ ተጋድሎ መርሐ ግብር በመጠኑ ለማየት ሞክረናል ክርስቲያናዊ ሕይወት በክርስቶስ ጸጋና በመንፈሳዊ ተጋድሎ ፍሬን ያፈራል ከወገናችንም ያሉት ደግሞ ፍሬ ቢሶች ሆነው እንዳይቀሩ የግድ ስለሚያስፈልገው ነገር በመልካም ሥራ እንዲጸኑ ይማሩ ቲቶ ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ከጥንተ ተፈጥሮ በተለየ ሁኔታ በሐዲስ ተፈ ጥሮ በክርስቶስ ጸጋ ያገኘነው አዲስ ሕይወት ነው በዳግም ልደት የተገኘው ይህ መንፈሳዊ ሕይወታችን በክርስቶስ ጸጋ እንደተገኘ እንዲሁም በጸጋው አጋ ዢነት በቃለ እግዚአብሔር እያደገ መጥቶ ለፍሬ ይበቃል ያለ ክርስቶስና ያለ ጸጋው ክርስቲያናዊ ሕይወታችን አያፈራም ይህንንም በወይን ግንድና በቅርን ጫፎቹ መሰሎ አሰተምሮናል ዮሐፁ መዳናችን በጸጋው እንደሆነ እን ዲሁም ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና ሥራችንም ለፍሬ የሚበቃው በጸጋው ነው አንድ ነገር ለፍሬ መብቃቱ የሚታወቀው ለቆመበት ዓላማና ግብ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይመሻትና ክርስቲፀናዌ ሕዩጠት ለመጨረሻው ቁም ነገር ሲደርስ ነው ለምሳሌ አንድ የወይን ግንድ ተተክሎ ካደገ በኋላ ፍሬ ማፍራት ይገባዋል እንደዚሁም ኣንድ አማኝ ለቆመበት ዓላ ማ ላመነበት ተስፋ ብቁ ሆኖ የሚገኘው ለመንግሥተ ሰማያት የሚያበቃ የእምነትና የሥራ ፍሬ ሲኖረው ነው እንግዲህ አንድ አማኝ በክርስቲያናዊ ሕይወቱ ፍሬ የሚያፈራው እምነቱን እስከ መጨረሻው በመጠበቅ መልካሙን ም ገድል በመጋደል ነው ከዚያ በኋላ ነው ሩጫዬን ጨረስሁ በማለት የጽድቅ አክሊልን ሊቀዳጅ የሚችለው ኛጢሞ ያለ እምነትና ያለ መልካሙ ገድል የሕይወት አክሊል እንደማይገኝ አውቀን በየፅለቱ ለክርስቲ ያናዊ ሕይወታችን ፍሬያማነት መንፈሳዊ ተጋድሉሎአችንን መፈጸም ይኖርብ ናል ክርስቲያናዊ ሕይወት በጸጋው ሰለ መጠናከሩ ክፍል ሦስት ምዕ ራፍ አንድ በፊደል ተራ ረ ቁጥር ተመልከት ዖመፊያዊፎ ፌጋድሥ ረታም ተጋድሎ ማለት ምን ማለት ነው። የክርሰቲያን ተጋድሎ መንፈሳዊ የተባለበት ስለ ሦስት ምክንያት ነው መጀመሪያ ተጋድሎው መንፈሳዊ እንጂ ሥጋዊ አይደለም ምክንያቱም መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለ ምና ኤፌ ይህም ማለት ሰው ከሰው ጋር በመጣላት የሚያደርገው ትግል ወይም ጦርነት አለመሆኑን ይገልጽልናል ሁለተኛ መንፈሳዊ መባሉ በመንፈስ ቅዱስ አነሣሽነትና ረድኤት በክርስቶስ ስም የሚካሄድ መሆኑን ያስገነዝበናል በክርስቶስ ላለው አዲስ መንፈስ የሚለው ቃል በቅጽል ካልተገለጠ በቀር የተለያየ ትርጉም ይኖረዋል በግልጽ ከታወቁት ምንባቦች በቀር መጽሐፍ ቅዱሰን በምናነብበት ጊዜ በአንዳንድ ቦታ ያለ ቅጽል መንፈስ የሚለውን ስናገኝ የእግዚአብሔር መንፈስ ወይም የሰጡ መንፈስ ወይም ሌላ ዓይነት መንፈስ እንደ ሆነ የምናውቀው በዓረፍተ ነገሩ አገባብ ወይም በአንተጹ ይዘትና ሁኔታ ነው በአጠቃላይ በዚህ መጽሐፍም መንፈስ የሚለውን ቃል በተገለጸው መንገድ ለመረዳት ይቻላል ነገር ግን መንፈሳዊ ተጋድሎ የሚለውን ቃል በተመለከተ አንድ ወጥ ትርጉም ብቻ ይኖረዋል ይኸውም የእግዚአብሔር መንፈስ ያደረበት ሰው ወይም መንፈሱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ጓብረትና አንድነት ያለው ሰው የማያካ ሂደው መንፈሳዊ ተጋድሉ የሚያደርገው መንፈሳዊ እንቅስቃሴና ተግባር ማለት እንደሆነ በማያሻማ ሁኔታ በሚቀጥሉት አንቀጾች ተገልዲል ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይማናትና ክርስቲዖናዊ ሕይወት ሕይወታችን መንፈስ ቅዱስ መሪና አስተማሪ በመሆን የሚያነቃቃና የሚያጽ ናና የሚያርምና የሚገሥጽ የሚረዳና የሚያጸና እንደ ሁኔታችን ልዩ ልዩ ስጦታን እየሰጠ የሚያሠራ ነው ስለዚህ የክርስቲያን ተጋድሉ የመንፈስ ቅዱስ ተጋድሎ ወይም መንፈሳዊ ተጋድሎ ይባላል ሦስተኛው በመንፈስ ቅዱስ የነቃውና የተዘጋጀው የእኛው የተፈጥሮ መን ፈሳችን ነው የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንንመንፈስ ቅዱስ ራሱ ከመን ፈሳችን ጋር ይመሰክራል የተባለውን ቃል ስናጠና የፈጣሪና የፍጡር መንፈስ በአንድነት ሆነው እንደሚሠሩ እናያለን ሮሜ ሐዋርያትም እኛና መንፈስ ቅዱስ ፈቅደናል ሲሉ ከአሕዛብ ወደ ክርስትና ለተመለሱት ክርስ ቲያኖች በተላለፈው ውሳኔያቸው ውስጥ ገልጠውታል የሐዋሥራ መንፈስ ቅዱስ በአማኞች ልቡናና መንፈስ ውስጥ እያደረ እንደሚወስሰንና እን ደሚያስወስን እንደሚመሰክርና እንደሚያስመሰክር እንደሚፈቅድና እን ዲፈቀድ የሚያደርግ መሆኑን ከጥቅሶቹ ለመማር እንችላለን ስለዚህ በክርስቶስ መንፈስ መሪነትና አጋዢነት የአማኞችም የተፈጥሮ መንፈስ ጸጋን በመቀበል ብቃትን በማግኘት ለክርስቲያናዊ ተጋድሏቸው ሁሱ ተንቀሳቃሽና አንቀሳቃሽ ኃይል ሆኖላቸዋል እንግዲህ መንፈሳዊ ተጋድሎ ሰንል የእግዚአብሔር መን ፈስ ከሰው መንፈስ ጋር እንደ አባትና ልጅ እንደ መምህርና ደቀ መዝሙር እንደ አሠሪና ሠሪ አብሮ ተባብሮ የሜከናወን መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ነው የመንፈስ ቅዱስ ሱታፌ የአለበት የሰው መንፈስ ያለ ፍሬ አይቀርም የመንፈስ ፍሬን ያፈራል እንጂ ገላ ክርስቲያናዊ ተጋድሎ ብቻ ለብቻ አይካሂድም የእግዚአብሔር መን ፈስ ስለ ሰዎች ደኅንነትና ጽድቅ በሰዎች አድሮ እንጂ ከሰዎች ውጭ ሆኖ አይ ሠራም የእግዚአብሔር ቃል ሰው በመሆኑ እርሱ የእኛን ሥጋ ነሥቶ ለእኛ ደግሞ ቅዱስ መንፈሱን ሰጠንች። ስለዚህ የጌታ የእግዚአብሔር መንፈስ በሰው አድሮ የሰውን መንፈስ በማነቃቃትና በማነሣሣት ለመንፈሳዊ ተጋድሎ ብቁ ያደርገዋል ይህም ማለት ሰው ያለውን የተፈጥሮ ኃይል ሁሉ እንዲጠቀም በሙሉ ልቡ ተነሣሥቶ በተቻለው መጠን አስፈላጊውን ሁሉ እንዲያከናውን ይገፋፋዋል ያደፋፍረዋል ማለት ነው እንጂ የሰውን መንፈስ ወደ ጉን ትቶ መንፈስ ቅዱስ ብቻውን የሚያደርገው ነገር አይደለም ምክንያቱም መንፈሳዊ ተጋድሎ የሚካሄደው ለሰው በሰው እስከሆነ ድረስ መንፈስ ቅዱስም ስለ እኛ ደኅንነትና ሰላም የሚያደርገው ሁሉ በሰው ልቡናና መንፈስ ውስጥ ኣድሮ ስለ ሆነ ነው እንግዲህ ከተጋድሏችን በፊት የሰው ልቡናና መንፈስ በእግዚአብሔር መንፈስ በክርስቶስ መንፈስ መታደስ ይገባዋል ሰለሆነም ሁልጊዜ መጸለይ ያስፈልገናል አቤቱ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ ኣድስ ከፊ ትህ አትጣለኝ ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ መዝ ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ለፍሬ እንዲበቃ አስፈላጊውን ክብካቤ ጥረትና መንፈሳዊ ተጋድሎ ማድረግ ይጠበቅብናል ክርስቲያናዊ ሕይወታችን በዛፍ ተክል ይመሰላል ከችግኝ ማፍላት ጀምሮ ፍሬ እስከሚያፈራበት ጊዜ ድረስ ያለው ድካም ቀላል አይደለም ችግኙ የሚተከልበት ቦታ የአየር ንብ ረት የአፈሩ ለምነት የውኃው መገኘት ሌሎችም ሁኔታዎች ሁሉ እንዲመ ቻቹ ማድረግ ያስፈልጋል እነዚህ ሁሉ ተሟልተው እንዲገኙ አትክልተኛው መውጣት መውረድ አለበት የዛፉ ችግኝ እንዲያበቅል እንዲለመልም እን ዲያብብና እንዲያፈራ ያልተቆጠበ ጥረት ያደርጋል በየጊዜው ውኃ ማጠጣት ሥጋነ ነሥአ ወመንፈሶ ቅዱሰ ወሀበነ የዓርብ ውዳሴ ማርያም ተመልከት ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይመማናትና ክርስቲያናዊ ሕሯዉት ማረምና መኮትኮት ፀረ ዕጽዋት ፀረ ሕይወት የሆኑ በሽታዎችን በመድኃኒት መከላከልና ሌሎችም አስፈላጊ ነገሮችን ሁሉ ያከናውናል አትክልተኛው ከብዙ የሥራ ድካም በኋላ በትዕግሥት ጠብቆ ነው የዛፉን ፍሬ ሊያገኝ የሚችለው እንደዚሁም እንደ አዲስ ተክል የሚቆጠረው አዲሱ ሕይወታችን ማለት ክርስ ቲያናዊ ሕይወታችን አድጐ ለፍሬ እስኪበቃ ድረስ ዕለት በዕለት ጠንክረን በትዕ ግሥት መሥራት በመንፈሳዊ ተጋድሎ መጽናት ይገባናል የክርስቲያን ሕይወት በውኃ ዳር እንደ ተተከለች ዛፍ ነው በእን ደዚህ ያለ ቦታ የተተከለች ዛፍ አትደርቅም ሁልጊዜ እንደ ለመለመች ነው ፍሬዋንም በየጊዜው ትሰጣለች መዝ ምክንያቱም ውኃ በሚገኝበት በለምለም አካባቢ ስለምትገኝ ነው የክርስቲያንም መንፈሳዊ ሕይወት እን ዲለመልምና እንዲያፈራ የሕይወት ውኃ በአለበት አካባቢ መገኘት ይኖርበ ታል ይህም የሕይወት ውኃ ከቤተ ክርስቲያን ከቤተ እግዚአብሔር ይፈልቃል ሕዝ የሕይወት ውኃም ከቃለ እግዚአብሔርና ከምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ይገኛል ክርስቲያናዊ ሕይወት ማደግና ማፍራት በነፍስ እንጂ በሥጋ እን ዳልሆነ የታወቀ ነው ሰለዚህ ክርስቲያን ከሥጋው ይበልጥ ነፍሱን በመውደድ ነፍሱን እየመገበ ማሳደግ ያስፈልገዋል የነፍስ ምግቧም ቃለ እግዚአብሔር ነው ሰው ከእግዚአብሔር ኣፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይ ኖርም የተባለውን እያንዳንዱ ክርስቲያን እያሰበ በቃሉ ለመኖር ለቃሉ በመታዘዝ እግዚአብሔርንና ሰውን በሙሉ ልብ ማገልገል ይኖርበታል ማቴ መልካሙንም ሥራ ለማከናወን ክርስቲያን ሁሉ በቆራጥነት ተነሣ ሥቶ መልካሙን ገድል መጋደል ይጠበቅበታል ኛጢሞ ዳረ ኃዉጳልታቻና ፈፊተናም ዝሇሃታፖ ገ ያው ልያ ። እንግዲህ ተጋድሏአችን በአንድ በኩል ኃጢኣትን ከእኛ ላይ ማስወገድ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የመንፈስ ፍሬ የተባሉት ከእኛ ጋር እንዲሆኑ አጥብቀን መያዝ ነው ስለዚህ መጋደላችን በሁለት አቅጣጫ ትምህርተ ዛይማናትና ክርስቲወናዊ ሕሄዉጠት ይሆናል አንዱን ይዞ ሌላውን መተው ክርስቲያናዊ ሕይወታችንን ጉደሎ አድ ርጐ ፍሬ እንዳያፈራ ያደርገዋል እኛ ማድረግ የሚገባን የኃጢአትን ሥራ ቀስ በቀስ እያስወገድን የጽድቅን ሥራ ደግሞ እያሳደግን መሥራች ነው ጽድቅን የምናፈራው እግዚአብሔርን ከሁሉ በላይ በመውደድ እም ነታችንንና ተስፋችንን አስከ መጨረሻው በመጠበቅ ሰውን እንደ ራሳችን በመውደድ በጎሥራን ለማከናወን ያልተቆጠበ ጥረትና ትግል እንዲያውም ራስን መሥዋዕት እስከማድረግ ድረስ ለባልንጀራችን የሚያሰፈልገውን ሁሉ በመፈጸም ነው እንዲህ ዓይነቱ መንፈሳዊ ተጋድሎ ክርስቲያናዊ ሕይወ ታችንን ወደ ፍጹምነት ደረጃ እንዲደርስ ያደርገዋል በክርስቶስ ጸጋ ውስጥ ሆኖ እምነት ተስፋና ፍቅር በምልዐት ያለው ክርስቲያን መንፈሳዊ ሕይወቱ ጉድለት አይኖርበትም ምክንያቱም በእግዚአብሔር ያለው እምነቱ በክርስቶስ መገለጥ ላይ የተመሠረተ በመሆኑ የሃይማኖቱ እውነተኛነት የተረጋገጠ ይሆን ለታል እንደዚሁም በክርስቶስ ያለውን የተስፋ ቃል ወደፊትም ስለሚያገኘው የመንግሥተ ሰማያት የርስቱ መያዣ የሆነው መንፈስ ቅዱስ በልቡናው ሆኖ ስለሚመሰክርለት በምድራዊ ኑሮው ምንም መከራና ፈተና ቢያጋጥመው እው ነተኛ መንፈሳዊ ደስታ አይለየውም ፍቅሩም ግብዝነት የሌለበት መንፈሳዊ ፍቅር ከመሆኑ የተነሣ ከኃጢአት ርቆ ትእዛዛትን ሁሉ ስለሚፈጽም ክርስቲያናዊ ሕይወቱ የተሟላ ነው ያልነው ይህን በመሰለ ምክንያት ነው ከእምነት ከተስፋና ከፍቅር የሚበልጠው ፍቅር ቢሆንም ከሦስቱ የሚቀድመው ደግሞ እምነት ነው እንግዲህ በቅድሚያ የሃይማኖት ተጋድሎ ያስፈልገናል ስለዚህ ነው ቅዱስ ጳውሎስ ለልጁ ለጢሞቴዎስ ሲጽፍ መልካም ጦርነት ትዋጋ ዘንድ ይህችን ትእዛዝ አደራ እሰጥሃለሁ እምነትና በጉ ኅሊና ይኑርህ መልካ ሙን የእምነት ገድል ተጋደል በማለት ያዘዘው በእምነት እውነተኛ ልጄ ብሎ ለሚጠራው ለጢሞቴዎስ የሰጠው ይህ ትእዛዝ በእምነት ልጆቹ ለሆነው ሁሉ ስለሆነ ትእዛዙን ተግባራዊ ማድረግ ይገባናል ኛጢሞ እና ይን እንዲህ ዓይነቱን የሃይማኖት ተጋድሎ ለልጁ ለጢሞቴዎስ ብቻ ሳይ ሆን በጠቅላላ ለፊልጵስዮስ ክርስቲያኖችና በእነርሱም አማካይነት ለአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ትእዛዙን ሲያስተላልፍ በአንድ ልብ ስለወንጌል ሃይማ ኖት አብራችሁ እየተጋደላችሁ በአንድ መንፈስ እንድትቆሙ ስለ ኑሯችሁ እሰማ ዘንድ ለክርስቶስ ወንጌል እንደሚገባ ኑሩ ብሎናል ፊልጵ እን ግዲህ መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያኖት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ ራእይ ተብሏልና ላለፈው ንስሐ ገብተን ተስፋ ላለበትና ዋጋ ለሚያሰጠው ለእው ነተኛው ሃይማኖት በርትተን እንሥራ ግብዝነት የሌለበትን ሐሰት ያልተቀላቀለበትን እውነተኛ ስብከተ ወንጌል እናካሂድ ከሃይማኖት ተጋድሎ ጋር ሌሎች የጽድቅ ሥራዎችን በትጋትና በሙሉ ኃይላችን ማከናወን የሚገባን በጎ አድራጐቶች መልካም ገድሎች አሉ ልዩ ልዩ ዓይነት የኃጢአት ሥራዎችን ለመከላከል በዓይነትና ንዑሳን ኃጣውእን ለመዋጋት እንደሁኔታው በተለያዩ መንገዶች ተቀናብረው የተዘጋጁ ደንቦችና መመሪያዎች እንዳሉ እንደዚሁም ለጽድቅ ሥራዎችም አሉት በዚህ ምዕራፍ የሚገኙትን ቁጥር ተመልከት እንግዲህ እነዚህ ሁሉ በግራና በቀኝ እን ዳሉ አውቀን ሁላችንም ራሳችንን በመመርመር ለንስሐ የሚገባ ፍሬ በማድረግ በቃለ አግዚአብሔር እየተመራን ከመንፈስ ቅዱስ በተሰጠን ኔኣጋ መሠረት በአንድ በኩል ክፉውን ሁሉ እየተዋጋን በሌላ በኩል በጐውን ሁሉ እየሠራን ለዘላለም ሕይወት የሚያበቃ ፍሬን እናፍራ ለዚህም ምሳሌ የምናደርገው በነህምያ መሪ ነት የተሠራው የኢየሩሳሌም የግምብ አጥር ነበር ይህ ግምብ እንዳይሠራ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛፀማኖትና ክርስቲያናዊ ሕይወት ጠሳቶች በተነሙባቸው ጊዜ ሥራው እንዳይቋረጥ በአንድ በኩል በጦር መሣሪያ እየተከላከሉ በሌላ በኩል ደግሞ ቅጥሩን አጥሩን እየገነቡ ሥራቸውን በእግዚአ ብሔር ረድኤት ፈጽመዋል እኩሌቶቹ ብላቴኖቼ ሥራ ይሠሩ ነበር እኩሌቶቹም ጋሻና ጦር ቀስትና ጥሩርም ይዘው ነበር ቅጥሩንም የሚሠሩትና ተሸካሚዎቹ በአንድ እጃቸው ይሠሩ ነበር በአንድ እጃቸውም የጦር መሣሪያቸውን ይይዙ ነበር አናጢዎቹም ሁሉ እያንዳንዱ ሰይፉን በወገቡ ታጥቆ ይሠራ ነበር ነህ ሎራጋሮታ ዝሎ ሃያፇ ሄሪ ዶፈሠሮታው ጹጋ ይዕጋጠፖ ለበጎነው ሥራ ሁሉ ለመልካሙ ገድል ሁሉ መሪና አርአያ የሆ ነውን የክርስቶስን ትእዛዝ እንከተል በጠባቡ መንገድ እንድንሄድና ወደ መን ግሥተ ሰማያት በምታገባው ደጃፍም እንድንገባ ተጋደሉ ብሎ ያዘዘን ራሱ ክርስቶስ ነው የጌታን ትምህርት ከሰማው አንዱ ሰለሚድኑ ሰዎች ብዛት ማነስ እንዲህ ሲል ጠይቆት ነበር ጌታ ሆይ የሚድኑ ጥቂቶች ናቸውን። እኛም የእነርሱን አርአያ በመከተል መንፈሳዊ ሕይወታችንን ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛማኖትና ክርስቲያናዊ ሕደጠት እናጠናክራለን ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ሳናቋርጥ ዘወትር እንድንጸልይ ያስተምረናል ኤፌ ኛተሰ እንደ ሐዋርያው ትምህርት ሳናቋርጥ ለመጸለይ እንዲቻል ቤተ ክርስቲያን የዘወትር ጸሉት በየ ሰዓቱና በየዕለቱ እንዲሁም በተለየ ሁኔታ በየሰንበቱ በየወሩና በየዓመቱ እን ደየ ዘመኑ ለሚፈጸሙ ኣጽዋማትና በዓላት ሁሉ ልዩ ልዩ ጸሎትን አዘጋጅታ ሁሉም ምእመናን እንዲሳተፉ ታደርጋለች ቤተ ክርስቲያኖችን በሰጠችን መመሪያ በግልና በማኅበር ጸሎት በእውነትና ባመንፈስ ከልባችን ከተሳተፍን ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ከበጎ ሥራ ጋር የጽድቅ ፍሬን ያፈራል ጸሎታችን በተጠናከረ ቁጥር ክርሰቲያናዊ ሕይወታችንም በዚያው መጠን ይጠናከራል አሮጌው ሰውነታችን በጸሉት ጸጋ ይታደሳል የደከ መው ይበረታል የተዳደፈው በንስሐ ጾምና ጸሎት ይነጓል የጠመመው ይቃናል የጐደለው ይሟሳል በአጠቃላይ ደካማ ጐናችን የሚታረመውና ጠንካራ ጐናችንም የሚጸናው መከራና ፈተናንም ለመቋቋም የሚያስችለን በክርስቶስ ጸጋ የጸሎት ኃይል እንደሆነ የታመነ ነው ምክንያቱም በሙሉ እምነት ለእግዚአብሔር የምናቀርበው ጸሎት ለክርሰቲያናዊ ሕይወታችን ኃይልና ጽንዕ የሚሆነንን የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ስለሚያሰጠን ነው አም ናችሁም በጸሎት የምትለምኑትን ሁሉ ትቀበሳላችሁ በማለት የጸጋ ሁሉ አም ላክ አረጋግጦልናል ማቴ ሰለዚህ እላችኋለሁ የጸለያችሁትን የለመናችሁትንም ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ ይሆንላች ሁማል ማር የጸሎት ሕይወታችንን በተጠናከረ ሁኔታ የምንገልጽባቸው ልዩ ልዩ የጸሎት ክፍሎች ወይም መግለጫዎች ይኖራሉ ከነዚህ ዋና ዋናዎቹ ሦስት ናቸው ዖራሥሥሪመድው ያቃጳሳ ታፖ የመጀመሪያው የጸሎት መግለጫ የተለመደው የቃል ጸሎት ነው ይህም በታወቀው የዘወትር ጸሎት ድምፅን በማሰማትም ሆነ በለሆሳስ ይገለጓል በማኅበርም ሆነ በግል ይህ ዓይነቱ ጸሎት በቤተ ክርስቲያንም በቤትም ወይም አመች በሆነ ቦታ ሁሉ ይፈጸማል የጸሎቱም ይዘት እንደየ ጊዜውና እንደየ ሁሄታው በተለያየ መንገድ ሊቀርብ ይችሳል በምን ጸልይበት ጊዜ ኣሳባችንን ሰብስበን በአንድ ልብ ሆነን መጸለይ ይገባናል ከንፈርን በማንቀሳቀስና በመናገር የምናካሂደው የቃል ጸሎት እንዳለ ሆኖ ቀስ በቀስ የጸሎቱን ኃይለ ቃል በአጽንኦት በምናስብበት ጊዜ ረቂቅና ጥልቅ ወደ ሆነው ኅሊናችን እንዘልቃለን በዚህ ሁኔታ በመቀጠል የጸሎቱን ትርጉምኖ የቃሉን መልእክት በአእምሯችን በማጤን የጸሎታችንንም ሰሚ ባለቤት በማሰብ ወደ ውስጠኛው ክፍል ወደ ኅሊና ጸሎት ከዚያም እጅግ ጥልቅ ወደ ሆነው ወደ ልቡና ጸሎት እንደርሳለን ህጠፎ ላዘርከበበ ፔከ ምዐህዮ ዐ ከይ ጮቫጸዘበይ ፕከፁ ዮብሃርዙ ሂከ ህዘከሃ ሸጸርፎኗ ፎ በገጽ እንዶ ተጻፈው ሦስቱ የጸሎት ክፍሎች የተባሉት የቃል ጸሎት የኅሊና ጸሎትና የልቡና ጸሎት እንደሆኑ እንደሚከተለው ይገልጻልገበ ርአዘከሄ ዘከፀበነ ክሮ ከ ርክበርሃ «ኬህከፎ ክየፎፀ ነሃ ከርከ የ ኩዩ የፎይ ከበበር ሃ ከ ሂከኋክ ህክ የዉሃፍ ከፎ የ ፀጺሃ ሃ ር ሂከር ከኬ ከክርከ »ሃር ዩኮሃፍ ከ ከ ዐየከ በዝ ከ ከ በሌላ አገላለጽ እነዚህ ሦስቱ በብዙዎች ዘንድ ጩኮነጨነርር እፎቨበቢ ክመበዘ በመባል ይታወቃሉ በተቀራረቡ ቃላት ለመተርጐም የመጀመሪያው የቃል የድምፅ ጸሎት የሁለተኛው የማሰላሰል ጸሎት ሦስተኛው የተመሰጦ ጸሎት በማለት ልንገልጻቸው እንችላለን ዝነገነገርህኽ ትምህርተ ዛፀማናኛትና ክርስቲፀዞናዊ ሕይፎጠት ፌሬ ድ ት ል ወ መ መ ቹቹችሽ ሪ ያዳቾሟግሠሌረሮ ሥልሷ ጋረ ያንገፈና ታፖፓ የምንጸልየውን የጸሉት ኃይለ ቃል በመተርጐም በኅሊናችን በአ እምሯችን መከታተልና ማወቅ ብቻ ሳይሆን የራሳችንንም መንፈሳዊ አቋም የምንጠይቅበት የተለየ የጸሎት ክፍለ ጊዜ እንዲኖረን ያስፈልጋል ከተለመደው የቃል ጸሎት በተለየ አኳኋን ራሳችንን ከእግዚአብሔር ቃል ጋር እያገናኘን በማ ነፃፀር የምናደርገው ጸሎት አለን ይህም የኀሊኖ ጸሎት ወይም የአእም ሮ ጸሎት ሊባል ይቻላል ምክንያቱም ሰለ ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ምን ነት ዓላማና ተግባር በቃለ እግዚአብሔር ኣኳያ እየመረመርን በማገናዘብ ለተግባራዊነቱም በኅሊናችን ውስጥ በማውጣትና በማውረድ እያሰላሰልን በጸሉት እየታገዝን የምናደርገው ውስጣዊ የመንፈስና የአእምሮ እንቅስቃሴ ስለሆነ ነው ይህ ዓይነቱ ጸሎት አብዛኛውን ጊዜ ቅዱሳት መጻሕፍትን ከማንበብ ጋር ይከናወናል በየዕለቱ ቅዱሳት መጻሕፍትን የማንበብ ልምድ ከጸሎት ሕይወታ ችን አንዱ ክፍል ስለሆነ ይህን አዘወትሮ ማድረግ ይጠቅመናል ምክንያቱም የመዳን እውቀት ከቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚገኝ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሉስ ለጢሞቴዎስ ሲጽፍ ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መዳሕፍትን አውቀሃል ብሏል የመዳን ጥበብ ለማግኘት ብቻ ሳይሆን ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና ምግባራችን የተቃናና ፍጹም እንዲሆን የሚያዘጋጀን ቅዱሳት መጻሕፍትን በማን በብ እንደሆነ ይኸው ሐዋርያ ያስረዳናል የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጐ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል ኛጢሞ እንግዲህ ከቃለ እግዚአብሔር ጥናት ጋር በጽሞና ለማደረገው የኅሊና ጸሎት በየዕለቱ ጊዜ ወስነን ብናዘወትር ክርስቲያናዊ ሕይወታችን እያደገና እየተጠናከረ ይሄዳል በተለይም እግዚአ ብሔር ለእኛ ስለ አለው ታላቅ ፍቅሩ በበለጠ ለማወቅ ያስችለናልና ይህንን ዓይ ነት የጸሎት ሥነ ሥርዓት አጥብቀን መከታተል ይኖርብናል ይዳ ሂዳ ጩጨረ ፍቅረ ጋሮ ያይሳያና ታሑታ የልቡና ጸሎት ምሥጢራዊ ቅርጽና ይዘት ያለው ለብቻ በጽሞና የሚፈጸም ጸሎት ነው የጸሎኮ አጀማመርና ሁናቴ ቀላል ቢመሰልም በጸጋ እግዚአብሔር ወደ ፍጹምሃት ደረጃ ያመራል የዚህ ጸሎት ምሥጢራዊነት ከእግዚአብሔር ጋር ብቻ ለብቻ የሚደረግ ከምሥጢራዊ ወዳጅ ጋር የሚካሄድ ግንኙነትና ንግ ግር ይመስላል በከፍተኛ ደረጃ የሚገኙ ቅዱሳን በተመስጦ ከእግዚአብሔር የሚገናኙበት በንጽሐ ልቡና ሆነው ክብሩን የሚያዩበት ገናናነቱን የሚያደን ቁበት የጸሎት ዓይነት ነው በፍጹም ፍቅር የሚወዳቸውንና የሚወዱትን ፈጣሪያቸውን በይነ ልቡናቸው እያዩ ያመሰግኑታል በመጨረሻው ማዕረግ ያሉ እዚህ ላይ ልብ ሲባል እንደ ሴማውያን ዕብራውያን እና እንደ መጽሐፍ ቅዱሳዊው ትርጉም እንጂ እንደ ዘመናዊው አስተሳሰብ ሰሜታዊነትንና ውዴታን ብቻ የሚያመለክት ሳይሆን መላውን የሰውን ሰብእና ሁሉ ነው ልብ ለሰው ሕልውና ለውሳጣዊው ሰው ቀዳማዊና መሠረታዊ ነገር ነው » በዚህ መንገድ ሲተረጐም ልብ በሰውነት ውስጥ ከሚገኘው ከአንድ ቁስ አካላዊ ክፍል እጅግ የራቀና የላቀ ነገር ነው በእግዚአብሔር አርአያና አምሳል ለተፈጠረውና ያልተወሰነ መንፈሳዊ ችሎታ ሰአለው ለሰው ተፈጥሮ ባሕርይ አካላዊ ልብ አፍአዊ ውጫዊ ምልክት እንደሆነ ከላይ ከተጠቀሰው መጽሐፍ በገጽ እንደሚከተለው ተገልዷል ዝ« ዘ ዘ ርዐበኣ ከፎ ህበ በ ከር ክር የከ ሂከክ ከር በከ ፎበ ክነከ ክህ ከፎ በነክ ክ አቨፍርክከ ህቪ ከፎ ከ ዐ ከር ከህክክ ፐከ ከጸቪ ከ ክመቨክየነ ዐክ ዐ ከክ በ ክሮ ዘበበፍበ ዘበ በቤርፎብ ከ ነዛ ክር ከርቢ ከ ከበ ከቋክ በር ዐልክ ክ ከፀ ከ ሂከ ዐከነሃርል ከ ህነ ፍነቨከ ከፎ ከሀበ ሀህ ሀሀ ከ ከሀከነቋከ ርየፎጳቪዘፎ ከዝ ከ ከፎ ዘጠቧወሮ ከዐ ዘኡፎበርኔኔ ዐ ርሀ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛደመናትና ክርስቲያናዊ ሕፎወት ቅዱሳን በጸሎታቸው እስከ ነጽሮተ ሥሉስ ቅዱስ ይደርሳሉ እንዲህ ዓይነቱ ጸሎት ለቅዱሳን ብቻ እንጂ በወጣንያንነትና በማዕከላዊ ነት ለሚገኙ ክርስቲያኖች አያስፈልግም ተብሎ የሚተው ሳይሆን ይልቅስ የእነር ሱን አማላጅነት እየጠየቅን የእነርሱን አርአያ በመከተል በእግዚአብሔር ጸጋ ታግዘን ለእንደዚህ ዓይነቱ ጸሎት ለመድረስ መትጋት አኣለብን በጽሞና ለብቻችን ሆነን ምሥጢራዊውን የልቡና ጸሎታችንን የምናደርስበት ጊዜ አ ዘጋጅቶ በየዕለቱ መፈጸም የተደቀሰውን የመንፈሳዊነት ኑሮ ያቀዳጀናል ስሙን ለመቀደስ ክብሩን ለመውረስ ያበቃናል እንግዲህ የልቡና ጸሎት በክርስቶስ በእግዚአብሔር ፍቅር ላይ ስለሚያተኩር ሰሙን በምንጠራበት ጊዜ በመንፈስ እርሱ ከአኛ ጋር እኛም ከእርሱ ጋር እንደሆንን እንገነዘባለን በዚህ ወቅት ስሜታችን ከአሳባችን ልቡናችን ከአእምሯችን ሳይሊያይ ከውጭው ዓለም ጫጫታ ራሳችንን ለይተን በውስጣዊ የኅሊና ጸጥታ በአንድ አሳብና ልብ ሆነን በፍጹም ኃይላችንና በፍጹም ነፍሳችን ከሚወደንና ከምንወደው እግዚአብሔር ጋር የመንፈስ አንድ ነትን እንድናገኝ ይሆናል በአምላካችን በእግዚአብሔር ፊት እንደሆንን አው ቀን የፈጣሪያችንን ገናናነት እያደነቅን ለእርሱ በመንፈስና በእውነት እን ሰግዳለን በፍጹም ትኅትናና ፍቅር ሆነን እናመሰግናለን እንግዲህ ንጹሕ ጸሎት ወይም የልቡና ጸሎት የተባለው በዚህና ይህን በመሰለ ሁኔታ እን ደሚገለጽ ተረድተን ገንዘብ ልናደርገው ይገባናል ጭረ ወቅፖጀጃ ጸታሎት ከዚህ በላይ ከተጠቀሱት ሌላ በየጊዜውና በየወቅቱ በሥራ ላይም ሆነን ከሥራም ውጭ በሆንን ጊዜ በጥድፊያም ሆነ በእረፍት ወቅት ሁሉ እግዚአ ብሔርን የምናስብበትና የምናመሰግንበት አጭር ጸሎት ይኖረናል ይኸውም ቅዱስ ጳውሎስ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ ያለውን በመከተል በማንኛቸውም ቦታና ጊዜ የሚፈጸም ልዩ ጸሎት ነው ኤፌ ። በመንገድም ወይም በሥራ ገበታ ወይም በሌላ ሁኔታ ውስጥ ሆነን ለሚያጋጥመን ክፉም ሆነ ደግ ነገር ሁሉ ከላይ በተሰጠን የጸሎት መመሪያ እግዚአብሔርን ስለሁሉም ነገር በልባችን ማመሰገን ይገባናል ይህ አጭር የልቡናና የኅሊና ጸሎት ካልተጠበቀ ክፉ ነገር ሁሉ ያድነናል በዚህም ላይ ክርስቲያናዊ ሕይወታችን የተቀደሰ ይሆናል ስለሁሉም ነገር በሁሉም ጊዜ እግዚአብሔርን በአመሰገነው ቁጥር ሕይወታችንም ሥራችንም ይባረካል ለክርስቲያናዊ ሕይወታችንና ለዕየለቱ ሥራችን የሚረዳን ይኸው ሐዋርያ ሌላ ተግባራዊ የጸሎት መመሪያ ይኸው ሐዋርያ ሰጥቶናል ይኸውም ከላይ ከጠቀስነው ጋር ይመሳሰላል በመጀመሪያ እግዚአብሔርን ማመሰገን ይቀድማል ከምስጋና ጋር ደግሞ ሥራችንን ወይም የምናደርገውን ነገር ሁሉ ዝም ብለን እንዲሁ የምንፈጽመው ሳይሆን በጌታ በእግዚአብሔር ስም እንድናደ ርገው ያስተምረናል የጸሎቱም መመሪያ ቃል በመዝሙርና በዝማሬ በመን ፈሳዊም ቅኔ በጸጋው በልባችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ እግዚአብሔር አብን በአርሱ በክርስቶስ እያመሰገናችሁ በቃል ቢሆን ወይም በሥራ የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም አድርጉት ይሳል ቆላ እንግዲህ ይህንን የተቀደሰ መመራየ በመከተል በሥራችንም በማኅበራዊ ጠቪጊ ጅርልሃርዮ ጸክ ክ ር ኾህር ኮ ዐ ኮሎ ከፍ የሚለውን ክፍል ከገጽ ተመልከት ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛደማናትና ክርስቲያናዊ ሕጾጠት ኑሯችንም ውስጥ ተግባራዊ ማድረግ ይገባናል ይህንና ሌሎችንም የሐዋርያውን መመሪያ አጥብቀን በመያዝ ለተግባራዊነቱም ብንጥር ጸሎት ዕለት በዕለት ኑሯችን ውስጥ ወሳኝ ማሚና እንዲኖረው እናደርጋለን ይህ አድራጐት ደግሞ ከቀጠለ ክርስቲያናዋ ሕይወታችን በመልካም ምግባር እንዲያሸበርቅ በሃይማኖት እንዲጸና ያደርገዋል መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ የተባለው ተፈጻሚነት ያገኛል ማቴ የሚያጋጥመንን ክፉ ነገር ለመቋቋም ወቅታዊ የኅሊና ጸሎት ማድረግ እጅግ ይጠቅመናል በሰው ሰውኛ ስሜት ተነሣሥተን ክፉን በክፉ በእልህና በቁጣ በመጣላት ከሚፈጠረው የሥጋና የነፍስ አደጋ የሚጠብቀን የክርስቶስን ስም ጠርተን በስሙ ስንጸልይ ነው ምክንያቱም የተቀደሰውን የእግዚአብሔርን ስም በመጥራት የክርስቶስን አርአያ እንድንከተል ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ይረዳናል የክርስቶስን ትኅትና ትዕግሥትና ፍቅር በማሰብ ለክፉ ነገር የተ ነሣሣው የቁጣ ስሜታችን ይበርዳል ስለ ክርስቶስ ፍቅር ብለን ክፉውን በክፉ ሳይሆን በደግ ለማሸነፍ እንችላለን የምናሸንፈውም በጸሎትና በቃለ እግዚአብሔር መመሪያ በመኖር ነው ሮሜ በዚህም መንፈሳዊ ተጋድሏችንን እናጠናክራለን መፈቿፎ ፌድሑሥ ያጸሑምፖ ሥጋድታሥ ው ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው ዮሐ በጥምቀት ከውኃና ከመንፈስ በመወለድ ክርስቲያኖች በመንፈሳዊ ሕይወት ይኖራሉ ሆኖም ሰው የሥጋም የመንፈስም ልደት ስላለው ሁለቱም ማለት የሥጋና የመንፈስ ሕይወት አለው በሥጋና በመንፈስ ባሕርይ ውስጥ ስለሚኖር ሕይወቱ ትግል የበዛበት ሆኖ እናገኘዋለን ምክን ያቱም ፈቃደ ሥጋና ፈቃደ ነፍስ ሁልጊዜ ስለሚቀዋወሙ ነው ገላ የሥጋ ኃይል ሲያይል የክርስቲያን መንፈሳዊ ኑሮ እየደከመ ይሄዳል ይህእን ዳይሆን የመንፈስ ቅዱስ ጸጋና ረድኤት ያስፈልገዋል በዚህ ጊዜ ነው መን ፈሳዊ ተጋድሏችን ተጠናክሮ ለመጨረሻው ድል የሚበቃው ታዲያ ይህ የመን ፈስ ቅዱስ ኃይል የእግዚአብሔር ረድኤት የሚገኘው ራሳችንን በጸሎት በመወ ሰን ነው በጸሎት የምንለምነውን ለክርስቲያናዊ ሕይወታችን የሚያ ስፈልገውን ጸጋ መንፈስ ቅዱስን እንደሚሰጠን ክርስቶስ አስተምሮናል ሉቃ መንፈስ ዝግጁ ሲሆን ሥጋ ግን ደካማ እንደሆነ የገለጸልን ጌታችን ወደ ፈተና እንዳንገባ በትጋት እንድንጸልይ የተግባር መመሪያን ሰጥቶናል ማቴ መንፈሳዊ ሕይወታችንና ተጋድሎአችን በትጋት ከም ናደርገው የዘወትር ጸሎታችን ጋር የተገናኘ መሆኑን እናስተውሳላለን ስለ ዚህ ነው መንፈሳዊ ተጋድሏችን የጸሎት ተጋድሎ ነው የተባለው ጸሎትን የሚያስተምረን እን ድንጸልይም የሚያደርገንና የመንፈስንም ብርታት የሚሰጠን መንፈስ ቅዱስ ስለሆነ እርሱን ከማሳዘን እንቆጠብ ሮሜ ኤፌ እንግዲህ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ ተብሏልና ለመንፈሳዊ ተጋድሎአችን ብርታት እንድናገኝ ዘወትር በመንፈስ ቅዱስ ተመርተን ለመጸለይ እንትጋ ኤፌ ይሁዳ ዓለም በተለያዩ መንገዶች ወጥመዱን ዘርግቶ ክርስቲያናዊ ሕይወታችንንና የጸሎት ሥርዓታችንን እየተፈታተነው ይገ ኛል ዓለም ከሚያመጣብን ፈተና ሌላ ከራሳችን ድካም የመነጨው የእምነት ጉድለትና ስንፍናም አለ እንግዲህ እነሂህን ፈተናዎች ልንቋቋም የምንችለው ለጸሎት ቁርጠኛ ሐሳብ ኖሮን ዘወትር የጸሎት ተጋድሎ ለማድረግ ስንወስን ነው ይህንንም ለመፈጸም በመጀመሪያ በእምነታችን ላይ በስሕተት በማወ ቅም ሆነ ባለማወቅ የመጣብንን ጥርጥርና ጉድለት አስወግደን በሙሉ ልብ አም ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይጣናትና ክርስቲፀናዊ ሕፀዉት ነን ወደ አምላካችንና አባታችን መጸለይ መንፈሳዊ ግዴታችን መሆኑን መረዳት ብቻ ሳይሆን በተግባር መጀመር ይኖርብናል የጀጩረም መልካም ሥራ መሆኑን አውቆ ለዘላቂነቱ እንዲታገል ትዕግሥትንና መጽናናትን ከእግዚአ ብሔር እንዲያገኝ ለራሱም ለሌላውም ይጸልይ ከላይ እንደ ጠቀስነው በመጀመሪያ እምነታችንን ፍጹም ለማድረግ ያልተቆጠበ ጥረት ማድረግ አለብን በእግዚአብሔር የተገለጸው የእምነት እውቀት መሠረቱና ምንጩ ቅዱሳት መጻሕፍትና ቤተ ክርስቲያን ሲሆኑ ምስክ ሮቹም እነርሱ ናቸው የያዝነው እምነት ተስፋና ፍቅር ሁሉ የተገኘው በሁለቱ ምስክሮች አማካይነት በሚገኘው ጸጋ እግዚአብሔር ስለሆነ ይህ ጸጋ በአ ማኙ ልቡና በማደር እምነቱን ወደ ፍጹምነት ደረጃ ያደርሰዋል ሰለዚህ በቅዱሳት ጩጻሕፍት በተጻፈው በቃለ እግዚአብሔር ተመርተን ከቤተ ክርስቲያን በሚሰጠው ጸሎትና ትምህርት እንዲሁም ከተቀደሱች ምሥጢራት በመሳተፍ በምናገኘው እምነት ተስፋና ፍቅር ላይ ተመሥርተን የዘወትር ጸሎታችንን ለመፈጸም ያልተቆጠበ ጥረት እናድርግ ከእግዚአብሔር ያገኘነው የእምነት የተስፋና የፍቅር ጸጋ እንዲሁም ሌሎቹም የጽድቅ ሥራዎች ሁሉ በጸሎት ኃይል ካልተደገፉ እየቀዘቀዙ ሰለሚሄዱ ከዚህ በታች የተመለከቱትን የጸሉትና ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ተጋድሉን ማከናወን ይኖርብናል በእግዚአብሔር ፍቅርና በክርስቶስ ጸጋ የሚካሄድ የመንፈሳዊ ተጋድሎ መርሐ ግብር መግቢያ የመርሐ ግብሩ ዓላማ ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ብጸሉትና በቃለ እግዚአብሔር እንዲጠናከርና የመንፈስ ፍሬን እንዲያፈራ እኛም ለመንግሥተ ሰማያት የበቃን እንድንሆን የሚያዘጋጀን ነው ይህንን በምናደርግበት ጊዜ የእግዚአብሔርን ፈቃድ መፈጸማችን ሰለሆነ ራሳችንንና ሌሉችንም ለመጥቀም እንችላለን ስለዚህም ዕለት ዕለት የምናካሄደው ይህ መርሐ ግብር አሰፈላጊ ነቱ ስለታመነበት በማከተለው አኳኋን ቀርቧል ዶራሪድቋ ዳመመራረምፖኖ ያያ ያፇ ሬር ፍቀርሮቨ ዴኖ ንፇሪምሦ መርሐ ግብራችን የተሳካና ፍሬያማ እንዲሆን ዘላቂና ዋስትኖ ያለው ለማድረግ በቅድሚያ መርሐ ግብሩን የሚያካሄደው ሰው አቋሙንና አመለካከቱን መመርመርና ግስተካከል አለበት የመንፈሳዊ ተጋድሉ ተካፋዮችና የመርሐ ግብሩ ፈጻሚዎች የሆንን ሁላችን አቋማችንና አመለካከታችን ተአምኖአችንና ተስፋችን እንዲሰተካከልና ዓላማችንንም ከግቡ ለማድረስ እንድንችል በሦስት አር እስተ ሃይማኖት ላይ መመሥረት ይኖርብናል እነዚህም ከላይ በርእሱ ላይ የተጠቀሱት ሲሆኑ የመጀመሪያው በእግዚአብሔር ፍቅር ስለመሆን በፍቅሩ ሰለ መታመን በፍቅሩም ሰለ መኖር ነው ይኸውም የተአምኖአችንና የተሰፋችን መጩሠረትና አቋም በማንና በምን ላይ እንደሆነ በቅድሚ የሚጎል ጽልን ቃለ ሃይማኖት ነው ሁለተኛው በክርስቶሰ ጸጋ የሚለው ቃለ አሚን ነው ይህም መርሐ ግብራችን በጸጋው አጋዢነት የሚካሄድ መሆኑን የሚያስገ ነዝበን ሲሆን ይህንንም ጸጋ የምናገኘው በክርስቶስ ስለሆነ በእርሱ አምነን በጸጋው ተጠናክረን የምናደርገውን ሁሉ በስሙ ማድረግ እንዳለብን ያስታው ቀናል በክርሰቶስ ሰም የተደረገው ሁሉ በጸጋውና በፍቅሩ እንደተደረገ ይቆጠራል ሰለሆነም እግዚአብሔርን በእርሱ ከማመስገን ጋር መንፈሳዌ ተጋድሉአችንን ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሰም ማድረግ እን ዝነገነገርህኽ ትምህርተ ዛደማኖትና ክርስቲያናዊ ሕደወት በፍቅሩ በመተማመን ከጸናን በፍቅሩም ከኖርን በችሣራችንና በፈተናችንጊዜ ጸጋውና ረድኤቱ አይለየንም በፍቅሩ መኖር ማለት አኛ አሱን በምንወድበት ፍቅር መኖር ማለት ሳይሆን እርሱ እኛን በወደደበት ፍቅሩ ማለት በቸርነቱና በበጎነቱ ተማምኖ በጸጋው መኖር ነው ከሳይ በርእሱ ላይ የተመለከተው የፍቅር ዓይነት የመጀመሪያውና ታላቁ የፍቅር ዓይነት መሆኑ ግልጽ ነው እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ያለው ፍቅር እንጂ ሰዎች ለእግዚአብሔር ያላቸው ፍቅር አይደለም እግዚአብሔር ልጁን ክርስቶስን የወደደበት ፍቅሩ ለሰዎችም በመሆኑ የፍቅሩን ታላቅነትና መለኮታዊነት ያስገነዝበናል ዮሐ ልጁን በወደደበት ፍቅሩ ስለ ወደደን ነው የእግዚአብሔር ልጆች የተባልነው ሰለዚህም ነው ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ የእግዚኣብሔር ልጆች ተብለን ልንጠራ አብ እንዴት ያለውን ፍቅር እንደ ሰጠን እዩ በማለት በአንክሮ የገለጸው ኛዮሒ ይህ መለኮታዊ ፍቅር እንደ ሰው ሰውኛ ፍቅር ተለዋዋጭና የማያሰተማምን ሳይሆን እውነተኛና ዘላቂ ስለሆነ በእግዚአብሔርና በፍቅሩ በመተማመን የምናካሂደው መንፈሳዊ ነገር ሁሉ ለክርስቲያናዊ ሕይወታችን የተሰፋና የመጽናናት የረድኤትና የሞራል ኃይል ሰጭ ምንጭ ይሆነናል ፍቅሩ ካለንና በፍቅሩም ከተማመንበት ከጥርጥርና ከፍርሃት ነፃ እንወጣለን የኅሊና ሰላም እናገኛለ። » የመጀመሪያው ስለ ጸሎት ነው » ሁለተኛው ከጸም ጸሉት ጋር ልዩ ልዩ ኃጢአትን ስለ መከላከል ይሆናል ሦስተኛው ለክርስቲያናዊ ሕይወታችን እድገት በቃለ እግዚአብሔር መሠረት እየተመራን በእምነት በተሰፋ በፍቅር ሆነን በቤተ ክርስቲያን ውሰጥ መኖርንና ማገልገልን ይመለከታል እንግዲህ ከላይ እንደጠቀስነው በመጀመሪያ ስለ ጸሎት ተጋድሎ እንመለከታለን ለእግዚአብሔር ለአምላካችንና ለአባታችን በመንፈሰና በእውነት ዘወትር ተግቶ መጸለይ በአውነት የሚሰግዱ ለአብ በመንፈስና በእውነት የሚሰግዱበት ጊዜ ይመጣል አሁንም ሆኗል አብ ሊሰግዱለት እንደ እነዚህ ያሉትን ይሻልና አእግዚአ ብሔር መንፈስ ነው የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ያስፈልጋቸዋል ዮሐ ጸሎት የእምነትና የአምልኮት መግለጫ ስለሆነ በመጀመሪያ አምልኮትና ስግደት ለሚገባው ለአንድ አምላክ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ጸሎታችንንና መሥዋዕታችንን በእውነትና በመንፈስ ሆነን ለእርሱ ማቅረብ ይገባናል ስለዚህ ነው ጸሎታችንን በቅድሚያ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዳ አምላክ ብለን በመጀመር የዘወትር በትምህርተ ጥቅስ ውሰጥ ያለው ቃል በክርሰቲያናዊ ሕይወታችን ውስጥ የሚያጋጥመንን መንፈሳዊ ሂደት ደረጃ በደረጃ ያሳየናል መከራን ከመቀበል ጀምሮ ተስፋውን እስከ ማግኘት ድረስ ያለውን መን ገድ ያጠቃልላል በመጀመሪያ መከራ መቀበል ትዕግሥትን ያስገኝልናል ትዕግሥት ደግሞ በልዩ ልዩ ፈተና ስንፈተን በፈተና መጽናትን በተግባር ተፈትኖ ማለፍን ወይም በፈተና የማይበገር ወይም በፈተና የጸና አቋምና ጠባይን ያስገኝልናል በፈተና የጸኖ አቋም ደግሞ ተስፋውን እንደሚያስገኝልን ከላይ የተመለከተው ጥቅስ ያስረዳናል ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛፀማናትና ክርስቲዞናዊ ሕሄወት ደሚያስፈልግ በዚሁ ምዕራፍ ማጠቃለያ ተገልጂል ሦስተኛው መንፈሳዊ የተባለውን ኃይለ ቃል ይመሰከታል እርሱም የተጋድሎውን ዓይነትና ሂደት የሚገልጽ ነው ይህም ማለት የነፍስ ደኅንነትና ሰላም እንጂ የሥጋ አሳብና ጥቅም ሳይኖርበት በመንፈስ የሚመራ ማለት ነው በተለይም የመንፈስ ቅዱስ ኅብረትና ረድኤት ያለበት መሆኑን ያስገነዝበናል ስለዚህ ጉዳይ በዚህ ምዕራፍ ከላይ በቁጥር ውስጥ በአጭሩ የተጻፈውን ተመልከት እንግዳህ በእነዚህ በሦስቱ ላይ ሳይመሠረት የሚካፄኒድ የተጋድሎ መርሐ ግብር ምንም መንፈሳዊ ቢመስል የክርስቲያናዊነት ባሕርይ ስለ ሌለው ዋጋ አይኖረውም ሩጫችንና ተጋድሏችንን ሁሉ እንዲያው በከንቱ ነፋስን እንደ መከተል ይሆንብናል ዓላማም አይኖረውም ለድክመታችንም መጽናናትን ለመከራችንም ተስፋን አናገኝበትም እነዚህ ሦስቱ ማለት የእግዚአብሔር ፍቅር የክርስቶስ ጸጋና የመንፈስ ቅዱሰ ኅብረት ከእኛ ጋር ከሆኑ እኛም በሦስቱ ከጸናን በተጋድሏችን የሚያጋጥሙን የመከራና የፈተና የእንቅፋትና የሽንፈት አጋጣሚዎችን ሁሉ እንድናልፍና በትንሣኤ ልቡናም ተነሣሥተን ክፉውን እንድንተወው መልካሙን እንድናከናውነው የሚያደርገን የተስፋና የመጽናናት ኃይልና ረድኤት አይለየንም ፖታሪ ያፉፍረ ፍዔይይም ዖሟያሳጂወው የበጎነገር ሁሉ የጸጋ ሁሉ ሥርና መሠረት ኃይልና ረድኤት የእግዚአብሔር ፍቅር መሆኑን በሩቁ የምናውቅ ቢሆንም ፍቅሩን በትክክል አው ቀንና ተማምነን በፍቅሩ ለመኖር ምን ያህል ልምምድ አድርገናል። የእግዚአብሔር ፍቅር ግን ከሁሉም የተለየ ነው ፍቅሩን አለማፀቅ እግዚአብሔርን አለማወቅ ነው ምክንያቱም እግዚአብሔር ፍቅር ነውና ኛዮሐ እና የዚህ ዓለም ፍቅር ያለው የእግዚአብሔር ፍቅር የለውም ኛዮሐ እንግዲህ የዓለምን ፍቅር ሁሉ ትተን በክርስትና ሃይማኖት የታወቁትን ሦስቱን የፍቅር ዓይነቶች አጥብቀን እንከታተል የመጀመሪያውና ታላቁ ፍቅር እግዚአብሔር ለሰዎች ያለው ፍቅር ነው ይህም መለኮታዊ ፍቅር ሰለሆነ በዓይነቱም በይዘቱም ከሁሉም የበለጠና የተለየ ባሕርይ አለው ሁለተኛው ሰው ለእግዚአብሔር ያለው ፍቅር ሲሆን ሦስተ ኛው ደግሞ ሰው ለሰው ያለው ፍቅር ነው ስለ ሁለተኛውና ስለ ሦስተኛው ፍቅር በክፍል ሦስት ምዕራፍ ሁለትን ተመልከት ዳዳ ዌፊረ ሰቋዳኛ ያቋው ፍቕሩ ዳሳ ሣመፇ እግዚአብሔር ለሰዎች ያለውን ፍቅር የሚገለጸው እኛ በደለኞች ሳለን እንዲሁ እኛን በመውደዱ የተነሣ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለውን ኣንድ ልጁን ወደዚህ ዓለም ልኮ ቤዛ አዳኝ እንዲሆነን በማድረጉ ነው ዮሐ ሮሜ ኛዮሐ የእግዚአብሔርን ፍቅር የምናውቀው ስፋቱንና ጥልቀቱን የምናስተውለው ክርስቶስ ለእኛ ሲል ለመዳናችን ያሳየውና ያደረገው የፍቅር ሥራ መሆኑን እናውቃለን እናምናለንም ስለዚህ የእናንተ ሥርና መሠረት በፍቅር ይጸና ዘንድ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ ከፍታውም ጥልቅነቱም ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል ከመታወቅም የሚያ ልፈውን የክርስቶስን ፍቅር ለማወቅ ትበረቱ ዘንድ ተብሎ የተጻፈውን ተገን ዝበን በሥራ እንተርጉመው ኤፌ በሥራ መተርጐም ማለት የእግዚአብሔርን ፍቅር ይኽውም የክርስቶስን ፍቅር ከጥቅሱ ሳይ እንደ ተገለጸው ለማወቅና ለማመን በርትተን የሃይማኖታችን የክርሰትና ሕይወታ ችን የመንፈሳዊ ተጋድሏአችን ሁሉ ሥር መሠረት እንዲሆን ማድረግ ነው ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛደመናትና ክርስቲፀናዌ ሕፀወት ጸሉታችንን እንድናደርስ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን የተደነገገው ከላይ ጥቅሱ እንደሚመራን እውነተኛ ጸሎት በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይ ነት ያለው ጸሎት በእውነትና በመንፈስ የሚቀርበው ነው እግዚአ ብሔር መንፈስ ስለሆነ በመንፈስና በእውነት የሚጸልዩትን የሚያመል ኩትንና የሚሰግዱለትን ይፈልጋል ጸሎት ለሃይማኖታችንና ለክርስቲያናዊ ሕይወታችን አስፈላጊ ስለ ሆነ በሕገ ቤተ ክርስቲያን በተወሰኑ ጊዜያት ሰዓታት ውስጥ ሁላችን ክርስቲያኖች በየዕለቱ አዘውትረን ልንጸልያቸው የሚገባንን ልዩ ልዩ ጸሎት ለምሳሌ ያህል በተከታታይ አቅርበናል እንግዲህ ለእምነታችን ታዛዥ በመሆን በመንፈሰና በእውነት ለእግዚአብሔር ጸሎት ማድረግን እናዘውትር ወደ ፈተና እንዳንገባ ተግተን እንጸልይ ግብዝነት የሌለበትን እውነተኛ ጸሎት ገንዘብ እናድርግ እንደ ራሳችን ፈቃድ ሳይሆን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ አም ልኮታችንን በትክክል እንፈጽም ለማን። ይህን መኝታ ከጠላት የተንኮል ሥራ ሁሉ አድነህ ትባርከው ዘንድ ጠባቂ መልአክም ታደርግልኝ ዘንድ ወደ አንተ እጸልያለሁ በሌሊትም ተነሥተው አንተን ከሚያመሰግኑት ከትጉ ሃን አገልጋዮችህ ጋር እኔም በበኩሌ አንተን ለማመስገን ችሎታውንና ኃይሉን ትሰጠኝ ዘንድ እለምንሃለሁ ስብሐት ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ይእዜ ኒ ወዘልፈኒ ወለዓለመ ዓለም አሜን እግዚኦ ረሰየነ ድልዋነ ከመ ንበል በአ ኩቴት አቡነ ዘበሰማያት የሚለውን በጸሎትህ መጀመሪያና መጨረሻ ድገም ያያ ያያወምሯ ኃሐሟድረሃው ያደራሥ ያራሯ መመሬዖፖ ከጠዋትና ከማታው ጸሉት ሌላ በግልም ሆነ በኅብረት በማናቸውም ጊዜ ጸሎት ማድረግ ይቻላል በማናቸውም ሰዓትና ወቅት ሁልጊዜ መጸለይ ለክርስ ቲያን ደስታው እንጂ ችግሩ መሆን የለበትም ሁልጊዜ እንድንጸልይ ሐዋርያዊ መመሪያ አለን በጸሎትና በልመና ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ ሳታ ቋርጡ ጸልዩ ተብሏል ኤፌ ተሰ ስለዚህ በማኖቸውም ጊዜና ቦታ በእውነትና በመንፈስ ሆነን አጭር የኅሊና ጸሎት ማድረስ ይገባናል ሰለ ጽድቅህ ፍርድ ሰባት ጊዜ በቀን አመሰግንሃለሁ የሚለውን ቃል ይዘው የቤተ ክርስቲያናችን አባቶች ሥርዓት ሠርተዋል መዝ ምእመናን ሁል ቀን በሄቱ ጊዜያት እንዲጸልዩ የቀድሞ አባቶች ሥርዓት ሠርተዋል ቱ ጊዜያት የሚባሉትም ነግህ መለስት ቀትር ተሲያት ሠርክ ንዋም መንፈቀ ሌሊት ናቸው ከነዚህም ተለይቶ በነግህና በሠርክ በጠ ዋትና በማታ የሟጸለየው ጸ በቤተ ክርስቲያን እንዲሆን ታዚኳል በቀሩት ጊዜያት ግን ምእመናን በቤታቸው ወይም ተግባር ቢያዙበት ሥፍራ ሆነው ጸሎቱን አቁጻሮውን እንዲያደርሱ ተፈቅዳል ለካህኖትም ከዚህ በቀር ሌላ በተለይ የታዘዘ የጸሎት ሥርዓት አላቸው እንግዲህ በልዩ ልዩ ቦታ ያለን አማኞች እንደየ ሁኔታችን እንደ ሥራችን ጠባይ እንደ ቀኑ ውሎአችን እያየን እግዚአብሔርን በጸሎት የምናስ ብበት መንገድ እናዘጋጅ እንጂ ለጸሎት ጊዜ የለንም አንበል እግዚአብሔርን የቤተ ክርስቲያን ጸሉት መጀመሪያ በዓ ም ታትሞ የነበረውን እንደገና በ ዓም በኢት ዮጽያ ሊቃውንት ታርሞና ጅቶ በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት አዳስ አበባ ታተመ ገጽ መቅድሙን ተመልከ እስከ ኛው ክፍለ ዘመን የነበረችው የጥንቷ የሕንድ ቤተ ክርሰቲያን ጳጳሳት መነኮሳትና ገዳማውያን በየዕለቱ ጊዜ ሲጸልዩ ተራው ቀሳውስትና ምእመናኑ በየሰለቲ ጊዜ ጠዋትና ማታ በየአ ጥቢያቸው ቤጥ ክርስቲያን በመገኘት ይጸልዩ ነበር ከላይ በተጠኞኛሰው ርከፀከክ በርቪተብሎ በተሠየ መው የሕንድ መጽሔት ውስጥ ገከሪ ፐከዕጠጩ ርከበሀፀ ሀህ በሚል ርእስ የተጻፈውን አንብብ በተለይም ገጽ ተመልከት ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛደማናትና ክርስቲያናዊ ሕፀዉት የምንገናኝበት ቦታና ጊዜ እንፈልግ መቼም ቢሆን በልባችን ውስጥ ገብቶ የሚያዝዘን ሥጋዊ ባለሥልጣን የለም ምክንያቱም ከእግዚአብሔር በቀር በኅሊናችን ውስጥ ያለውን የሚያውቅ አይኖርምና ስለዚህ በዕለቱ ሥራችንም ሆነ በእረፍታችን መካከል እግዚአብሔርን የምናሰታውስበት ጊዜና ቦታ በልባችን ውስጥ እናዘጋጅለት በሥራም ሆነ በመንገድ ሳለን በአጫጭር የኅሊና ጸሎት እግዚአብሔርን እያሰብንና እያመሰገንን ሌላውን ነገር ሁሉ ለማከናወን የሚከለክለን ነገር የለም ከሁሉም በላይ የምትወደውን እግዚአብሔር አምላክህ ያደረገልህን ቸር ነት ሁሉ እያሰብክ በቤትህ ሰትቀመጥ በመንገድም ስትሄድ ስትተኛም ስት ነሣም አመስግነው ሰላንተ ያለውን ፍቅር አትዘንጋ ዘዳ እንዳትረሳ ውም በየሰዓቱ የምታደርገው ጸሎት ለአምላክህ የፍቅር መታሰቢያ የምስጋና መሥዋዕት ይሁንልህ ሁልጊዜ ስለ ሁሉ ነገር እግዚአብሔር አምላካችንንና አ ባታችንን በክርስቶስ ሰም ከማመስገን አትቆጠብ ኤፌ በድንገት ስለሚያጋጥምህ ክፉም ነገር ሁሉ ሳትደናገጥ ኅሊናህን በእምነት ለእግዚአብሔር ጥለህ ለርሱ በጸሎት ንገረው ክፉውን በደግ ለማሸነፍ የምትችልበትን ጸጋና ረድኤት ይሰጥሃል ሮሜ ስለ ክርስቲያናዊ ሕይወትህና ምግባርህ በጠዋት ጸሉትህ ቃል በገባኸው መሠረት በየሰዓቱና በየወቅቱ በሥራ መተርጉሙን እንድትከታተለው የሚያስችልህ አጫጭር የኅሊና ጸሎት ማድረሰ ለዕለቱ መንፈሳዊ ተጋድሎህ መከናወንንና ሥምረትን ያስገኝልሃል ዋዛ ፈዛዛን ሳቅ ስላቅን ትቶ ሳይ ሰለቹና ሳይዘናጉ ባልተከፋፈለ ኅሊና በአንድ ልቡና ሆኖ በየጊዜው በእውነትና በመንፈስ ተግቶ በመጸለይ የክርስቶስንና የቅዱሳኑን አርአያ በመከተል የግብዞች እርሾ ያለበትን ጠባይንና ምግባርን ማሻሻል ይቻላል እንግዲህ ይህ ዓይነቱ ተግባራዊ ጸሎት ነው ከሌሎቹ ተለይቶ ከዕለት በዕለት ማኅበራዊ ኑሮአችንና ሥራችን ጋር ተገናዝቦና ተዛምዶ የሚገኘው ከእንደዚህ ዓይነቱ ጸሎት ነው ከመንፈስ ቅዱስ ኃይልና ረድኤትን አግኝተን እምነትና ምግባራችንን ለማዋሐድ የምንችለው ከቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት ጋር የሚካሄደው የጸሎት ዓይነት ለክርስቲያናዊ ሕይወታችንና እምነታችን ጥራትንና ብቃትን ይሰጠዋል ተስፋ ችንንና ፍቅራችንን ያጠናክረዋል የተረሳውንና የጉደለውን መንፈሳዊ እውቀታ ችንን ያሟላዋል ስለዚህ አመች ቦታና ጊዜ በመመደብ በግልም ሆነ በኅብረት ከቃለ እግዚአብሔር ጋር የሚካሄደውን ጸሎት ማድረግ አስፈላጊ ነው በቤተ ክርስቲያናችን ከዓመት እስከ ዓመት ከመዝሙረ ዳዊት የሚሰበከውና ከሐዲስ ኪዳንም የሚነበበው በመጽሐፈ ግጻዌ ተዘጋጅቶ ስለሚገኝ የየዕለቱን ማለት የዘወትሩንና የየሰንበቱን ምንባቦች ማወቅና ማጥናት ይገባናል ከዚህ ሌላ ወደ ከፍተኛው የቅዱሳን ጸሎት ለመድረስ የሚያበቃንን የመንፈስ ቅዱስ ጸጋና ረድኤት ከእግዚአብሔር እንዲሰጠን መለመን ይኖርብናል ለዚህም የቅዱሳን የጸሎታቸው በረከት አይለየን የቅዱስ ጳውሎስ ቡራኬ ይድረሰን የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፉቀሮ ያመያ ቀፉፅዕም ንረጐ ዕያያጎቻራ ጋሪ ይያቻ። ጳሷ ጾም ጸሎት ብቻውን አይበቃንም ዋናው የመንፈስ ትግል ነው ክፉውን አምርሮ እምቢ ማለት ያስፈልጋል ያዕ ዕብ ጸም ጸሎት ይበቃናል ብለን ዝም ብለን ብንዘናጋ ኃጢአት በልቡናችን ገብቶ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛፀማናትና ክርስቲዖናዊ ሕደወት ስለሚያስቸግረን ክፉውን የምንቋቋምበት ጠንካራ የመንፈስ ትግል ያስፈልገባናል ክፉውን እምቢ አሻፈረኝ የምንልበት የሞራልና የመንፈስ ኃይል ከሌለን ወይም እንዲኖረን ካላደረግን በፈተና መውደቃችን አይቀሬ ነው ጾም ጸሎት እሱን መንፈሳዊ ትግልን ይረዱታል ኃይልና ደጀን ይሆኑለታል እንጂ እሱን አይ ተኩትም ይህ የፈቃድና የመንፈስ ኃይል በውስጣችን ካለ ወደ ልቡፍችን መቅደስ ሊገባ የመጣውን ክፉ አሳብ ለመከላከል ወይም የገባውን ለማስወጣት የሚያስችለን ስለሆነ እርሱን አጥብቀን ልንይዘውና በጸም በጸሎት ከእግዚአ ብሔር በምናገኘው ጸጋና ረድኤት ዘወትር ልንገለገልበት የሚገባን የመንፈስ ቅዱሰ መሣሪያ ነው እንግዲህ ይህ በውስጣችን ቀስበቀስ እያደገ የመጣውን የተጋድሎ መንፈስ ክፉውን እያሰወገደ በጐውን የሚተካ መሆኑን አውቀንና አም ነን ሁልጊዜ እንድንጠቀምበት ያስፈልጋል ስለዚህ ነው የመርሐ ግብራችንም ስያሜ የመንፈሳዊ ተጋድሎ መርሐ ግብር የተባለው ያኃዉጳቻ ሪዉድቅ ማ ርድረኖሷ ፉኃፉፍዕ ኃሮጥ ማ ያሮጽናናናጳ እንግዲህ እነዚህ ሦስቱ ጸሎት ጾምና የመንፈስ ትግል ለክርስቲ ያናዊ ሕይወት መጠናከር ያስፈልጉናል እነዚህ ሦስቱን በሚገባ በተግባር ካዋልናቸው በእግዚአብሔር አጋዢነት የኃጢአትን ጦር ድል ለመንሣት ችሎታው ይሰጠናል ነገር ግን ይህን ሁሉ ፈጽመን ምናልባት በኃጢአት ብን ወድቅ ተስፋ መቁረጥ የለብንም ተስፋማ እንዳንቆርጥ የዓለም መድኃኒት ክርስቶስ አለልን ኃጢአታችንን ብንናዘዝ እርሱ ይቅር ይለናል የእርሱ ደም ከኃጢአታችን ሁሉ ያነጻናልና ትልቁ ኃጢአት ኃጢአት የለብኝም ማለት ነው ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን እውነትም በእኛ ውስጥ የለም ኛዮሐ ኃጢአት እንዳለብን ብናምንና ብንናዘዝ ለእኛ ኃጢአት ቤዛ ሆኖ በሞተልንና በተነሣልን በክርስቶስ ጸጋ እንድናለን ከክርስቶስ ጋር በታማኝነት ከጸናን ጸጋ ይበዛልናል በጸጋው ኃጢአታችን ይደመሰሳል በሕግ ምክንያት ምንም ኃጢአት ቢበዛ በክርስቶስ በኩል የመጣልን ጸጋ ደግሞ የበለጠ ይበዛልናል ሮሜ ታዲያ ጸጋ ይበዛልን ዘንድ ኃጢአት እናድርግ ማለት ደግሞ የዘባቾች አባባል ነው እንደዚህም ብሎ ማሰብና መናገር በአግዚአብሔር ቸር ነትና የማዳን ሥራው ላይ ማፌዝና መቀለድ ይሆናል ጸጋ ይበዛልን ዘንድ ኃጢአት እናድርግ ማለት ትልቅ ስሕተት መሆኑን መረዳት አለብን ጸጋውን ከሰጠን ከክርስቶስ ጋር በሞትም በሕይወትም አንድ ከሆንን ኃጢአትን አና ደርግም ምክንያቱም ከክርስቶስ ጋር በመስቀል ለኃጢአት ሞተናል ማለት ከኃጠአት ተለይተናል አሁን የምንኖረው ኑሮ በክርስቶስ ትንሣኤ ያገኘ ነው አዲስ ሕይወት ነው በመጀመሪያው ትንሣኤ ማለት በትንሣኤ ልቡና የሚኖሩ ሁሉ በሥጋ ፈቃድ ሳይሆን በመንፈስ ስለሚመላለሱ በምድራዊ ኑሮአ ቸው ውስጥ ከሚያጋጥማቸው ኃጢአት ጋር እየተዋጉ ይኖራሉ ኃጢአትን እን ዳናደርግ ታዘናልና ለኃጢአት እጅ ላለመስጠት ያላሠለሰ ጥረት ማድረግ ይኖርብናል ነገር ግን ከላይ እንደ ጠቀስነው ኃጢአትን ባጋጣሚ ብናደርግ የኃጢአታችን ማስተሥርያ የሆነው መድኀኔዓለም ክርስቶስ እንደአለልን ተጽፎአል ኛዮሐ ዳግመኛም ለእኛ የሚራራ የአብ ሊቀ ካህናት ክርስቶስ እን ደሆነ ስለምናውቅ በጸጋውም ሰለምንተማመን ምንጊዜም ቢሆን ተስፋ መቁረጥ የለብንም ተስፋ መቁረጥ ሞትን ያመጣብናል ምክንያቱም ተስፋ መቁረጥ ማለት ራስን ከጸጋው መለየት ማለት ነው ራሱን ከጸጋው የለየ ደግሞ ሞት ዝነገነገርህኽ ትምህርተ ዛዩማናትና ክርስቲያናዊ ሕጠት እንጂ ሕይወት የለውም ዕብ ስለዚህ እነዚህንና እነዚህን የመሳሰሉ የእግዚአብሔር ቃል የጸጋና የተስፋ ቃል ሰላሉን በእነርሱ እየተጽናናን ከወደቅንበት ተነሥተን መንፈሳዌ ተጋድሉአችንን መቀጠል ነው እንጂ ተጋድሉአችንን ማቋረጥ በክርስቲያናዊ ሕይወታችን ላይ መፍረድ ይሆንብናል ምክንያቱም ተጋድሎን ማቋረጥ እጅን ለኃጢአት መስጠት ሰለሆነ ሌሉች ያልተጠበቁ ፈተናዎችን በሕይወታችን ላይ ያመጣብናል ጻድቅ ሰባት ጊዜ ሲወድቅ ሰባት ጊዜ ይነሣል የተባለው እኮ ሦስት ጊዜ ሲወድቅ አንድ ጊዜ ወይም ስድስት ጊዜ ሲወድቅ ሁለት ገዜ ይ ነሣል አልተባለም አንድ ጊዜ ሲወድቅ አንድ ጊዜ ይነሣል ሁለት ጊዜ ሲወ ድቅ ሁለት ጊዜ ይነሣል ይህም ማለት በወደቀ ቁጥር ይነሣል እንጂ አያ ሠልስም አያቋርጥም አይዘገይም እንግዲህ እኛም በወደቅን ቁጥር ወዲያው እየተነሣን በመድኃኔዓለም አለኝታነት ታምነን በእርሱ ጸጋና ምሕረት ተስፋ አድርገን በእርሱ አጋዢነት ሃይማኖታችንን ጠብቀን በጆጾም በጸሎት ጸንተን ተጋድሎአችንን አጠናክረን አስከ መጨረሻው ብንጋደል ጽድቅን እናፈራለን እሰከ መጨረሻው የታገሠና የጸና ይድናልና ማር እርሱም ደግሞ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ተን ያለ ነቀፋ እንድትሆኑ አስከ ፍጻሜ ድረስ ያጸናችኋል ወደ ልጁ ወደ ጌታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችሁ እግዚአብሔር የታመነ ነው ቆሮ በቃሉ መሠረት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በእምነት በተስፋ በፍቅር መኖርና ማገልገል ከላይ በቁጥር ኃጢአትን ሰለ መከላከል በጥቂቱ አውስተናል ከዚህ ደግሞ ጽድቅን እንድናፈራ ቃለ እግዚአብሔርን በመከተል በቤተ ክርስ ቲያን ውስጥ እየኖርን የሚፈለግብንንና የሚገባንን መልካም ሥራ የትኛው እን ደሆነ አውቀን አገልግሎታችንን በትጋት እንድንፈጽም የሚያሳስብ መርሐ ግብር ነው ተገሐሥ እምእኩይ ወግበር ሠናየ ከክፉ ሽሽ መልካምንም አድ ርግ እንደተባለው ክፉውን ነገር በመከላከል ብቻ ተጋድሏችንን አናቆምም ቀጥለን መልካሙን ነገር ደግሞ ማድረግ ይገባናል መዝ ሪፅቋ ሯማምታሦሦናኖ ምቨያራቻፇቻ ሐማጋወ ቃታ ያፇፉቆሦ መዱእይፉፍፖ ጳኖዖዎኖ መልካም ለማድረግ መልካሙን ነገር በትክክል ማወቅ ይኖርብናል እንዲያው በልማድ የሚመራ ሰው በጨለማ የሚሄድን ሰው ይመሰላል የጨለማ ተጓዥ ትክክለኛውን መንገድ መያዝ አለመያዙን አያውቀውም ባጋጣሚ ትክክለኛውን መንገድ እንኳ ቢይዝ በመንገዱ ላይ በጨለማው ምክን ያት ብዙ አደጋ ስለሚያጋጥመው ክከአሰበበት መድረስ አለመድረሱ አይታ ወቅም እንደዚሁም ክፉ ወይ በጎ እንደሆነ ሳናውቅ በልማድ የያዝነው ነገር ካለ ውጤት አይኖረውም በተለይም በአሁኑ ዘመን የምንገኝ ክርስቲያኖች ጥበብና እውቀት በተስፋፋበት ዓለም ውስጥ ይልቁንም ተቃዋሚዎች በበዙበት ኅብረተ ሰብ መካከል ስለምንኖር ሰለሃይማኖታችንና ስለ ተስፋችን የበለጠ አውቀን ለሚጠይቁንም መልስ ለመስጠት መቻል አለብን መንፈሳዊ አኗጽኗራችንንም ለሚያሙትና ለሚሳደቡት በበጎ ኅሊና ሆነን በጎ ምግባራችንን እንዲያውቁት እናድርግ ስለዚሁ ጉዳይ ቅዱስ ጴጥሮስ ሐዋርያዊ መመሪያውን እን ደሚከተለው ሰጥቶናል ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛዩመማናትና ክርስቲዖናዊ ሕሯዉት በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁአችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን በክርስቶስ ያለውን መል ካሙን ኑሯችሁን የሚሳደቡ ሰዎች ክፉን እንደምታደርጉ በሚያሙበት ነገር እን ዲያፍሩ በጎ ኅሊና ይኑራችሁ ኛጴጥ እንግዲህ ከላይ እንደ ተጠቀሰው ስለ ተሰፋችን ስለ ሃይማኖታችን ስለ መንፈሳዊ ኑሯችንና ስለ መሳሰሉት ቢጠይቁን መልስ ለመስጠት እንድንችል መጀመሪያ የክርስትና ትምህርትና እውቀት እንዲኖረን ያስፈልጋል ይህ አውቀት ደግሞ እንዲኖረን ከፈለግን ከቃለ እግዚአብሔር እናገኘዋለን ቃሉን ደግሞ ከቅዱሳት መጻሕፍት ማለት ከብሉያትና ከሐዲሳት እናገኘዋለን ስለዚህ ክርስቲያናዊ ሕይወታችን እንዲያድግና ጽድቅን እንዲያፈራ የመጀመሪያው ነገር ቃለ እግዚአብሔርን መማርና ማጥናት ነው ይህንን ከልጅነታችን ጀምሮ ያደረግ ነው ብንሆን በኋላም ጊዜ የጀመርን ብንኖር ምንም የማናውቅም ብንገኝ ሁላችንም ቃሉን በትክክል አውቀን ለሌሎችም እያሳወቅን በቃሉ መሠረት ክርስቲያናዊ ሕይወታችንን መምራት ቅድሚያ የሚሰጠው የመጀመሪ ያው ሥራችን መሆን ይገባዋል እንግዲህ ለቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት ጊዜ ሰጥተን የመርሐ ግብራችን አንዱ ክፍል አድርገን እንያዘው በበን ሥራ ሁሉ ፍሬ እያፈራችሁ በእግዚአብሔር እውቀት እያደ ጋችሁ ለጌታ እንደሚገባ ትመሳለሱ ዘንድ እንለምናለን ቆላስ ያጳሂጸወጨሮ ይት አሰቋመቋፆ የቃለ እግዚአብሔር ጥናታችንን ከቤተ ክርስቲያን ውጭ ሳይሆን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በመኖርና በማገልገል መካሄድ አለበት ምክንያቱም የክርስትና ሕይወታችንን የጸጋ ልጅነታችንን ከእግዚአብሔር ያገኘነው በቤተ ክርስቲያን አማካይነት ስለሆነ ትክክለኛውን የቃለ እግዚአብሔር ትምህርትና ትርጉም ከዚያው እናገኘዋለንና ነው በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ በጸጋው እን ደተወለድን ከዚያው ሆነን በቃሉ እየታነፅን ማደግ ይኖርብናል ቃሉና ቤቱ አይለያዩም ሁለቱም የእርሱ ናቸውና ቃሉን የሰጠን እርሱ ነው ቤተ ክርስቲያንንም ያቋቋመ እርሱ ነው ስለዚህ ከቤተ ክርስቲያን ውጭ ሆኖ ቃሉ ብቻ ይበቃኛል ማለት ታላቅ ስሕተት ነው ይልቅስ እንደ ነቢይቱ ሐና በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ እየኖርን አምላካችንን እናገልግለው በጸምና በጸሎትም ሌሊትና ቀን እያገለገለች ከመቅደስ አትለይም ነበር ተብሎ ስለ እርሷ የተጻፈውን እያሰብን እኛም በተሰጠን ጸጋ መሠረት የእግዚአብሔርን ቤት እናገልግል ሌቃ እንግዲህ በቃለ እግዚአብሔር ተመሥርተን ክርስቲያናዊ መርሐ ግብራችን መንፈሳዊ ተጋድሎአችን እናታችንና አስተ ማሪያችን በሆነችው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በመኖርና በማገልገል ይሁን ክፍል ሦስት ምዕራፍ አንድ በፊደል ተራ ረ ቁጥር ተመልከት እንዴት ነው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለመኖርና ለማገልገል የምን ችለው። በሁለት ዐበይት መንገድ ነው የመጀመሪያው ሃይማኖታችንና ተስፋችንን አስመልክቶ የሚደረግ ሲሆን ሁለተኛው ደገሞ የምግባርንና የፍቅርን ሥራ ሁሉ ይመለከታል ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይማናትና ክርስቲያናዊ ሕጾወት ራቻም ዕኃጋዕታ ወሄሷ ዳሃሰሎት ዳፖጋ ዕርዕዶዕም ሰሐመታሃ ዳዳምሮ ይታ ማረሮጳ የመጀመሪያው እንደ ቅዱሰ ጳውሎስ መመሪያ መልካሙን የእምነት ገድል እንድንጋደል የሚያሳስብ ነው ኛጢሞ ሰሐ ሆጭና ሃይማኖት አብራችሁ እየተጋደላችሁ በአንድ መንፈስ እንድትቆመ በማለት ሐዋርያው የሰጠንን ትእዛዝ በቤተ ክርስቲያን ውሰጥ ሆነን ተፈጻሚ ለማድረግና የቃሉንም አገልግሎት ለምእመናን ሁሉ ለማዳረስ ነው ፊልጵ ዛሬ ቤተ ክርስቲያናችን በአንድ በኩል ሃይማኖቷን በሃይማኖት ስም በሚቃወሙ ወገኖች በሚሠራጨው እንግዳ እምነትና ሥርዓት በሌሳ በኩል አሳባቸው ምድራዊ በሆኑ የዓለም ሀብታም ሕዝቦች የኑሮ ይትባሀልና እንደዚሁም በዘመናዊ ትምህርትና ፍልሰፍና ተጽእኖ መካከል ሆና ተወጥራ ሰለምትገኝ እው ነተኛና ትክክለኛ ሃይማኖቷን ለመጠበቅና ለትውልድም ለማሰተላለፍ ከመቼውም ይበልጥ የካህናትና የምእመናን የኅብረት ጥረትና ትግል አስፈልጓል ይህን ተግባራዊ ለማድረግ አሁንም ቃለ እግዚአብሔርን እያጠናንና እያስጠናን በሰብከተ ወንጌል ሥራ በመሳተፍ የቤተ ክርስቲያናችንን ሐዋርያዊ ተልእኮ ማሟላትና ምእመናንን ከኑፋቄና ከክህደት መጠበቅ የካህናት ኃላፊነት ብቻ ሳይ ሆን ስጦታና ችሎታ ትምህርትና ዕውቀት ያላቸው ምእመናንም ጭምር ነው እያንዳንዱ ክርስቲያን ቃሉን ተምሮ እውነትን ይዞ ለሃይማኖቱ ተከራካሪና ጠበቃ ይሁን ሁሉም ለሃይማኖቱ ዘብ ይቁም ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ ይሁን ይሁዳ በሰው ልማድ ምንም እንኳ የምንመላለስ ብንሆን እንደ ሰው ልማድ አንዋጋም የጦር ዕቃችን ሥጋዊ አይደለምና ምሽግን ለመስበር ግን በእግዚአብሔር ፊት ብርቱ ነው የሰውንም አሳብ በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሳውን ከፍ ያለ ውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን ለክርስቶስም ለመታዘዝ አእምሮን ሁሉ እንማርካለን መታዘዛችሁም በተፈጸመች ጊዜ አለመታዘዝን ሁሉ ልንበቀል ተዘጋጅተናል ኛቆ ሮ ሃይማኖተ ወንጌልን በትክክል ተረድተን ለማስረዳት ጠብቀን ለማ ስጠበቅ የምንችለው በቤተ ክርስቲያን አማካይነት በምናገኘው ሀብትና ረድኤት ነው ሃይማኖታችንና ተስፋችንን አውቀን ለመኖርና ከእግዚአብሔርም ዋጋ የምናገኘው የቤተ ክርስቲያንን ጸሎሉቷን ትምህርቷን ምሥጢራቷን በመካፈል ስለሆነ ኑሯችንና አገልግሎታችን ከእርሷ ጋር በጥብቅ የተያያዘ መሆን እን ደሚገባው ሁላችንም ማመን ይኖርብናል ክርስቶስ በደሙ በዋጃት በአንዲት ቤተ ክርስቲያን ማመን ራሱ ሃይማኖት ነው ክፍል አንድ ጸሎተ ሃይማ ኖት አንቀጽ ተመልከት ስለዚህ በቃለ እግዚአብሔር መሠረት ሃይማኖታ ችንና ተስፋችንን እየጠበቅን በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን እየተሳተፍን በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ ለመኖርና ለማገልገል ብንወስንና ብናደርገው ራሳ ችንንም እንጠቅማለን ሌሎችንም አንረዳለን ይህን በመርሐ ግብራችን ይዘን በየጊዜውና በየወቅቱ በትጋት እንድንፈጽመው እናታችን ቤተ ክርስቲያን አደራ ትላለች ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛይማኖትና ክርስቲያናዊ ሕፀዉት ባጀራቻ ዳ ራቆሃ መውደያምያ ራም ለሃልኋግሎተታቻ ይራፇልጳ ከዚህ ሌላ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሆነን የምንሠራው ዐቢይ ጉዳይ አለ ይኸውም ከመንፈሳዊ ሥራችን ጋር ጉን ለጐን የሚሄደው የማኅበራዊ አገልግሎታችን ነው በተለይም እንደኛው በአርአያ ሥላሴ የተፈጠሩ ወገኖቻችን በየመንገዱ ያለ ምግብናና ያለ መጠለያ በየቦታው ወድቀውና ተጥለው መገኘታቸው እጅግ አሳሳቢ ሆኖብናል ባልንጀራህን እን ደራስህ ውደድ የተባለውን አምላካዊ ትእዛዝ አሜን ብለን የተቀበልን ሁላችን ክርስቲያኖች የነዳያንን መራብና መራቆት እያየን የሕሙማንን ሰቆቃ እየሰማን ዝም ብሎ ማለፉ እጅግ ማሳዘኑ አልቀረም እስካሁንም ለጋስ ምእመናን በሚያደርጉት ምጽዋት ነዳያን እየተረዱ መቆየታቸው ይታዐወሳል ሆኖም የርዳታው አሰጣጥ በተናጠል ስለሆነና ድርጅታዊ አሠራር ስለሌለው የችግረኞች ችግር እምብዛም አልተቃለለም ለዚህ መፍትሔው እያንዳንዱ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በሰበካ ጉባኤ ኃላፊነት በቃለ ዓዋዲው ድንጋጌ መሠረት የበጐ አድ ራጐት ክፍል ተቋቁሞ ርዳታ ሁሉ በአንድነት ተሰብስቦ በእቅድ በተዘጋጀ መን ገድ በሥራ ላይ ቢውል ከፍተኛ ውጤት ያስገኛል የምእመናን ርዳታ በዚህ ሁኔታ በተደራጀ መንገድ ቢቀናጅ ጤና ያላቸው ችግረኞች እየሠሩ ራሳቸውን እንዲረዱ ማድረግ ይቻላል በአግባቡ ከሆ ነ የውጭ ርዳታንም ለማግኘት ጥረት ማድረጉ ይጠቅማል እንግዲህ ይህንና ይህን የመሳሰለውን ሥራ ለማከናወን የምእመናን ሁሉ መልካም ፈቃደኝነትና ጥረት ያስፈልጋል እንግዲህ ሁላችንም በየሰበካችን በየአጥቢያችን የበጎ አድ ራጐት ሥራ እንዲቋቋምና ችግረኞችም በአግባቡ እንዲረዱ በየበኩላችን ሰውን ወዳጅና ቸር በሆነው በእግዚአብሔር ፊት በልቡናችን ቃል ብንገባና በሥራ ብናውለው በሰማይም ዋጋ አግኝተን በምድርም ተወዳጅነትን ኣትርፈን በደስታ እንኖራለን ለዚህ ለተቀደሰ ሥራ በመርሐ ግብራችን ውስጥ ቦታ ሰጥተነው በጊዜው ጊዜ ብንፈጽመው ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ጽድቅን ያፈራል እንግዲህ በቸርነቱ ለዘላለም ሕይወት እንድንበቃ በተቀደሰው ሃይማኖትና በእግዚአብሔር ተስፋና ፍቅር ራሳችንን እየጠበቅን ሌሎችንም ከሞትና ከዘላለም ኩነኔ እንዲድኑ ያልተቆጠበ ጥረት ማድረግ ልንፈጽመው የሚገባን መንፈሳዊ ተጋድሎ ነው በፍቅር ሆነን በጉውን ሥራ እየፈጸምን የክርስቶስን ምሕረት በመጠባበቅ በእርሱ ስም ተግተንና ተዘጋጅተን እንድንኖር እናታችን ቤተ ክርስቲያን አደራ ትላለች ወዳጆች ሆይ ከሁሉ ይልቅ በተቀደሰ ሃይማኖታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ እየተጋችሁ በመንፈስ ቅዱስም እየጸለያችሁ ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ አንዳንዶች ተከራካሪዎችንም ውቀሱ አንዳንዶችንም ከእሳት ነጥቃችሁ አ ድኑ አንዳንዶችንም በሥጋ የረከሰውን ልብስ እንኳ እየጠላችሁ በፍርሃት ማሩ ይሁዳ ባለዛር ወዐርዐ ትምህርተ ዛፀማናትናቫ ክርስቲዖናዊ ሕይወት ስ መ በዚሁ ጽሑፋችንን እናጠቃልላለን በመጨረሻም ስሙን ያልገለጸው የመዝገበ ሃይማኖት ደራሲ በመጽሐፉ ፍጻሜ የጻፈውን በመጥቀስ የሚከተለውን ስብሐተ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር በጮሆን እናቀርባለን ስብሐት ለእግዚአብሔር ወጣኒ ወፈጻሚ ከሃሊ ወገባሬ ኩሉ ሎቱ ይደሉ አኩቴት እስከ ዘመነ ዘመናት በምድር ወበ ሰማያት በባሕር ወበቀላያት ለዓለመ ዓለም አሜን ለሚችል ለሚጀምር ለሚፈጽም ቻይ ሁሉን ለፈጠረ እግዚአ ብሔር ምስጋና ይድረሰው ለእሱ ከዘመን እስከ ዘመናት በምድርም በሰማይም በባሕርም በጥልቆችም ለዘለዓለሙ ምስጋና ይገባዋል አሜን እመሂ ስሕትኩ አንትመ እለ በመንፈስ አርትዕዎ የተሳሳትኩትም ቢኖር እናንተ በመንፈስ ያላችሁ አቃኑት አነሣሥቶ ላስጀመረን አስጀምሮ ላስፈጸመን ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን ስብሐት ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለመ ዓለም አሜን መ ህዝገበ ሃይማኖት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የድርሰት ክፍል ተዘጋጀ ዓ ም ገጽ «እግዚኦ ረስየነ ድልዋነ ከመ ንበል በአኩቴት አቡነ ዘበሰማያት ዝነገነገርህኽ።