Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
አያቴ ሲተርቱ «ሰው ኑሮውን ይመስላል» ያሉት ልክ ነው ሆሆ። ይህ ቆጥራ ሁለት ዓይነት ብቻ ነው የምታስቢው። ለቤተሰቧ ስለመንገር እነርሱው ተባበሩን ሁላችንም ጥቁር ለብሰን ሀበን ተቀመጥን መሄዳችንን ጉዳዩን ጁ ጁቋ ያልጠበቅናት ሀብታሟ ጓደኛችን ጀሚላ ብርቱካን መስላ ሀዘን ልትደርስ መጣች የአበባ የዘወትር ምሳሌ ነበረች ላለመዋሸትም እኒም አንዳንዴ እሷን መሆን ተመኝቻለሁ ነፍሷን ይማረውና አበባ ከመሞቷ በፊት «እንደ ጀሚላ ጥሩ ሰው ቢያጋጥመኝ እኮ አንደርሷ ሰማይ እነካ ነበር በአንዴ። ልብሱን ሲያወልቅ ገላው ክሌላ ሰው ሙቀት ይፈልጋል በጣም ውዬው ደክሞታል ና ማስመስሌን አውቆታል ሽማግሌው ካንድ ጓደኛው ጋር ሲያወራ «አነ አንድ ከዛባ ውሸታሟ ጋ ነኝ» ብሎ ሲለው ሰማሁ «ሁሌ ስትዋሸኝ ውሸቷ ይጥመኛል ደግሞ ውሸቷ ያልበሰለ ነው ሸምግዬ አያለሁ ገና ነህ ትለኛለች ውሸቷ አስኤሰለቸኝ ልያትና ውሸታም ብዬ አባርራታለሁ» የገረመኝ ግን ታወቀብኝ ብዬ አለማፈሬ ነው አንዳንዴ ሙልጭ እድርጉ ሰድቦኝ ገፍቶ ከቤቱ እስካላወጣኝ አልፄድም ብዬ እቀመጣለሁ ክብር የለ ስሜት የለ ሌላው ቢቀር ንዴት የለ አጥንት የሚሰብር ስድብ ሰምቼም ውርደት የለም ምንም አይመስለኝም የሰውነት ስሜቶች ድብን ብለው ሞተዋል ክሌላው ጋር ስዳክር እነርሱም ምጥጥ እያረጉ ሲያባርሩኝ ለዚህ ሕይወቴ የክለር ዝርዝር ቢሰጠው ከለሩ ያለመወላወል ጥቁር ነው ህይወቴ ከለሩ ጠቁሯል ለዚያውም ሙሉ አዕምሮዬን ካበሳሸ ጥላሸት ጋር። ስናገር ስፄድ ስራመድ ስቀመጥ በስልት ሆኖናአል ስስቅም በስልት ስለምስቅ አስካካለሁ በሲጋራ እየጠቆረ ያለውን ከንፈሬን ለመሸፈን ደማቅ ሊፕስቲክ እጠቀማለሁ የሲጋራ ጭስ መንስኤው የአረቦቹ ግፊት ነበር።
ከዚህ በፊት ከሌሎች ወይም እራሷ የጥፊውን ጉዳይ ሳታውቀው አትቀርም አይኗን ወደ መሬት ተክላ «አንዳንዶቹ እኛን እንደዛ ነው የሚያስቡን ግን ሁሉም አይደሉም ጥሩዎችም አሉ እኔ ለምሳሌ ካንቺ የከፋ ሥራ ነበረኝ አሁን ደግሞ በጣም ጥሩ ሰዎች ጋ እየሠራሁ ነው እኛ በአገራችን ብቻ ነው ክብር ሊኖረን የሚችለው በሌሎች አገሮች የተሰደዱ ጓደኞቼ እንደዚህ እንደኛ በጣም አይገዙ አንጂ ሁሌ ያነሰ ቦታ ነው ያላቸው አሁን አንቺ ስለመብትሽ እርሺ ማሰብ ያለብሽ እንዴት ቶሎ አገርሽ የምትገቢበትን ሁኔታ ነው አዚህ የመጣሺው ገንዘብ ለማግኘት ነው መሥራት አለብሽ ጠንካራ ሁፒ ተሽቀዳድመሽ ባዶ እጅሽን አገሬ ልግባ ብለሽ አትወስፒ የተሻለ ነገር ይዘሽ ሂጂ ትንሽ ከሠራሽ ቤተሰብሽን ልትረጅበት የምትችይበትን ገንዘብ ልታገሺፒ ትችያለሽ እኛ ሁላችንም ጓደኞቼን ጨምሮ የመኖሪያ ፈቃድ የለንም ፖሊስ እስኪይዘን ተደብቀን እንሠራለን ያች የምታሠራሸ ሴትም ልታገኝሽ አትችልም ሥራ ለማግኘቱ ሁላችንም እንረዳሻለን ለጊዜው ከኔ ጋር እቤቴ ልውሰድሽ የቡና እቃዎች አሉኝ ቡና እያፈላሁልሽ ስለነገሩ ትወስኛለሽ እመፒኝ ሀሳቤ ደስ ካላለሽ መልሼ እኔው እራሴ አመጣሻለሁ » አመንካ ት ምዕራፍ ሁለት የረዳችኝ ልጅ ቅድስት ከሌ ሎች እኩዮቼ ሴቶች ጋር አስተዋወቀችኝ ገና ሳያቸው ኦዲስ አበባ የእስልምና ስማቸውንና እውነተኛውን አስተዋወቴቱኝ ሳባ አበባ ሳልዋ ዘመናይ አይሻ ጽጌረዳ ጆሚላነ ጀሚላና ስባህ አቅርብ ቦታ እንጀራ ለኔ ሲሉ ሊገዙ ሳልዋ ሽሮ ልታበስል ኩሽና ልታቀራርብ ተበታተነ ኩሽና አይሻ ደግሞ ቡና ብዙ ፍራት በሶስት እርምጃ የምትገመተዋ ጠባብ ክፍል ቅር ያለባት ትመስላለት ተመኘኽረሏት ጐኔን ማሳርፍበት ትንሸ ቦታ ቢሰጡኝ ብዬ ፀለይኩ ትልቁን ቤት በአጋማው የመኖሪያ ፍቃዱ ከተከራየው ሰውዬ መደበቅ ነበረብን ሰውዬውና ሚስቱ ካንድ ልጃቸው ጋር ሲመጡ የሚመጡበት ጊዜ የታወቀ ስለሆነ ሲመጡ ጠባቧ ክፍላችን ትዘጋለች ጮክ ብሎ ለመሳቅም ሆነ ለማውራት የሚችሉት ቅድስት ሰባህ እና ጀሚላ ብቻ ነበሩ ሌሎቻችን እንታፈናለን ጀሚላ አይሻና ሳልዋ የሆነ የሚያመሳስላቸው የሚያጣምራቸው ነገር አላቸው ሰባህ ወደ ቅድስትም ወደነአይሻም ታወላውላለች ይህች ቅድስት ግን የተለየች ናት እድለኛ ሆንኩና ገና ሳምንት ሳይሞላኝ የቅድስት ዘመድ የሆነች ሴት ትወልድና በሥራ እንድረዳት በፊት የሚከፈለኝን ደሞዝ እንደምትክፍለኝ ተዋውላኝ ሥራ ጀመርኩ ለዚያውም ሀሙስ ለእረፍት ወጥቼ አርብ አገባለሁ። ወንድ ለመሳብ መላ አካሏን ስታቁነጠንጥ አኡዝቢላ አይኑን ጨፈን ገለጥ እያደረገ ቀጠለልኝ በአገሩ ሴቶች በጣም እንደሚመካ የአረብ ሴት ቆሽሻ አታውቅም በሕጋችን ከሚያቆሽሻት ነገር እንከላከልላታለን እያሰ ችሩ ለው ነው አራሱን እየተቆጣጠረ ምንም ሳይነካኝ እቅፍ አድርጐ እንደ አገሩ ሴቶች ውስጡ ከሚያሰቃየው ሙቀት ሲከላክልልኝ አደረ ጠዋት ላይ «ይህን የመሰለ ውብ ሌሊት አሳልፌ አላውቅም እንዲህ እራሴን መግታት የዎችል ጆግና ነኝ ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር ሴት በጣም ስለምወድ እንኳን አጠገቤ ተኝታ ይቅርና ገጽ ሳስባት ውስጤ ያተኩሳል ዛሬ ወንድ ሆፔ ከወንድነቴ ፊት በቆራጥነት ተጋተርኩ ይታይሸ ለዚያውም ክምታምር ምንም ከማታውቅ ንፁህ ልጅ ጋር አድሬ ቡናማ ገላዋ ልቤን እያቀለጠው በነጋታው ሳልዋ ትንሽ እንኳን አፈር ሳትለ ክፍያዋን ልትወስድ መጣች ገና ሲያያት እነዚያ ርህሩህ አይኖች ተቀይረው በንዴት ቀሉ። » «ኦ ታሪኩ ረጅም ነው» «ረጅም ታሪክ እወዳለሁ ብዙ ጊዜ መጨረሻው አስደሳች ነው» ፊቷን በፈገግታ አበራችልኝ ቆንጆ ናት ፈገግ ስትል አይኗ እንደመከደን ይልና ቅልብስ ረጃጅም ሽፋሸፍቶቿ ይበልጥ የሚስቡ ይሆናሉ «ደግሞ እንደልብ ወለድ ታሪክ አይነት ነው የሮሚዮና የጁሌት ታሪክን አንብበሻል ሙች ሙች የኔ ታሪክ ከነርሱ አይተናነስም ደህና ደራሲ ቢያቀናብረው ከየት ልጀምርልሽ አዎ ታውቂያለሽ አብረውኝ ይማሩ የነበሩ አምስት ጓደኞቼ እንደኔ ሁሉም ትምህርታቸውን አንደጨረሱ ሰአጐታቸው ልጅ እንደሚዳሩ ያውቁት ነበር ነገሩ የተለመደ ስለሆነ ወንዱም የአጉጐቱን ልጅ አላህ ሰአዳም ሀዋን እንደፈጠረለት ሁሉ እርሷን ለእርሱ የፈጠረለት መሆኗን ስለሚያምን እርሷን ሌላ ሰው ካገባ እራሱን እንደ ደካማ ሰነፍ የራሱ የሆነ ነገር ሲነጠቅ ዝም ብሎ የሚያይ ፈዛዛ ተደርጐ የተቆጠረ ስሰሚመስለው የአጐት ልጁን ቢወዳት ባይወዳት አይለቅም ታዲያ ከእነዚያ ጓደኞቼ ጋር ስለወደፊት ባሌ ሳላወራ የሚታየኝ እነቪያ በትንሽነቴ ያየቷቸው ሞኛሞኝ አይኖቹ ስለሆኑ እበሽቅና ንግግሬን አቆማለሁ ጓደኞቼ ግን ልቤን እንድከፍትለት ይመክሩኝ ነበር ምክንያቱም ሁኔታዬ እየገፋ ልጁን እንዳልጠላና ኑሮዬን እንዳላማርር ያስቡ ስለነበር ነው ከኔ በቀር ሁሉም ስለአጐታቸው ልጅ ቀናነት መልክ ሁሌ እያወሩ ራሳቸውን በፍቅር ለማሰር ይሞክራሉ እኔ ግን አላህ ሲያማክረኝ እንደማላገባው የነገረኝ ይመስል እንደነሱ አልሞከርኩም በተለይ አንዲ ከአጐቷ ልጅ ፍቅር ስለያዛት እራሷን እድለኛ ታደርግ ነበር ይህች ልጅ አባቷና አጐቷ ሲጨቃጨቁ ካሁን አሁን ቃላቸውን ያጥፉና የወደፊት ባሌን አጣለሁ እያለች ጭንቀቷን ስትነግረን በሳቅ እንፈነዳ ነበር ቪር ባህሏ ከባህሌ ህብረተሰቧ ከእኔ ህብረተሰብ በጣም የተራራቀ ስለሆነ ወሬዋ አዲስና የሚስብ ሆነብኝ ሳላስበው የእመቤቴ አልጋ ጫፍ ሳይ ተቀመጥኩ በጣም ስህተት ነበር ብቻ በወቅቱ የአልጋ ጫፍ መሆኑ እንጂ የማን አልጋ ለሚለው ቁብ ስላልነበረኝ ተደሳደልኩ «ባሌ ሙስጠፋን ስተዋወቅ ሊያገባኝ ከነበረው የአጐቴ ልጅ ጋር አባቴ የጋብቻችን ቀን ከአንድ ዓመት በኋላ እንደሚሆን ተስማምተው ለትምህርት ውጪ አገር ፄዶ ነበር እኔ ከታናሽ ወንድሜ ትንጂ እህቴ እና ከዳዳ ሞግዚታቸውን የሚጠሩበት የተለምዶ ስም ጋር ሆፔ የገበያ አዳራሽ ውስጥ የሚገኝ የመጫወቻ ቦታ ነበርኩ ድንገት ሁለት ጐረምሶች ሲሯሯጡ ሙስጠፋን ገፉትና የአይን መነፅሩ ሲፈናጠር እንዴት እንደሆነ ሳላውቀው ራመድ ብዬ ቅልብ አደረግኩት በፈገግታ አየኝ አስተያየቱንና አይኖቹን አረሳቸውም ያለመነፅር በጣም የተዋቡ ናቸው ስታወራልኝ የበፊት ባሏን ፊት ለፊት የምታይ ይመስል አይኗን እያባበለች ፈገግ ትላለች አይኗን መልሳ ቡዝዝ ታደርግና ፈካ እዝን እዝን እኔን አታየኝም «ከዛ የትም ሳይፄድ አዛው የጫወታ ቦታ ቆም በዓይኑ ሲክተለኝ አየሁ እኔን ከሌሎች ሴቶች ለመለየት አስቸጋሪ ሲሆንበት በዓይኖቼ እዚህ ጋ ነኝ እለዋለሁ ብዙ ተያየን መጨረሻ ላይ ጥቅልል ወረቀት ሲወረውር ጠም። ከከተማ ከተማ ይጠራሩ ይመስል እናትና ልጅ ባንድ ቤት ሆነው ካንዱ ክፍል ወደሌላኛው በስልክ ያወሩና አንዱ ክፍል ላይ እንዲገናኙ ይቃጠራሉ እኔም የተሰጠኝን ጊዜ ጠብቄ ሥራዬን የምጀምረው ባሎቻቸው ሥራ ከሄዱ በኋላ አበቦችን ከነጤዛቸው ቆርጦ አስተካክሎ ለእመቤቴና እናቷ ከእንቅልፍ የመንቂያቸው ስዓት ሲደርስ አበባ ይቬ በመግባት በደመቀ ፈገግታ ሰብሀ አልኬር እንደምን አደሩ ብዬ መስኮት በመክፈት ንፁህ አየር አስገብቼ እመቤቶቼን አቀሰቅስና «ጣዛጅ አሲር» ትኩስ ጭማቂ በማቅረብ ነው እመቤቴ ለፆሙ ዝግጅት ገና አስራ አምስት ቀን ሲቀረው እናት አባቷ ቤት ገባች እኔም አብሬአት ይህ የፆም ወቅት ቤተሰብ ለመሰባሰቢያ የመረጠው ወቅት በመሆት ብዙዎቹ ይህን ጊዜ ከቤተስቦቻቸው ለመቀራረቢያ ከያሉበት ለመስባሰቢያ ይጠቀሙበታል ፆሙ እስኪያበቃ ብቻ የምንቆይ መሆኑ በጀኝ እንጂ የዚህ ቤት ሥራ ሙትት ያደርጋል ታዲያ ከጠዋት እስከማታ በቪህ ባህር በሚያክል ቤት ስዋከብ እውልና ወደ ማታ እግሮቼ ይዝላሉ ለመኝታ ወደተሰጠኝ ክፍል ማምራት እራሱ ትልቅ ሥራ ነው ብዙ ደረጃዎችን አልፎየቤቱ አናት ላይ ከተወጣ በኋላ እንደ ቀልድ የተገነቡት ክፍሉች ከወጥ ቤት ሠራተኛ አንስቶ እስከ የፅዳት ሠራተኞች መኝታዎች ናቸው ሁሉም ሲለፋ ስለሚውል ድንገት ሊገጣጠም ብቻ የቸልታ ሰላምታ ተለዋውጦ ክፍሉ ገብቶ ቶሎ አልጋ ላይ ለመውደቅ ይቸኩላል አንደዛ ደክሟቸው ቶሎ የማይተኙ ሲያስካኩ የሚያመሹት አዲሶቹ የሥራ ጓደኞቼ ሜሪና ክሬስ ከኔ ቀጥሎ ባለው ክፍል እስክለምዳቸው ድረስ መኝታ ነስተውኝ ነበር ሜሪ በጣም ወጣት መስላኝ ነበር ዕድሜዋን እስከነገረችኝ ጊዜ ድረስ አጠር ያለች ልጅ እግር ናት መጀመሪያ ሜሪንና ክሬስን ሳያቸው ክሬስ አሮጊት ከመምሰሏ በቀር ሌላ ምንም የመልክ መለያ የሌላቸው እህትማማቾች መስለውኝ ነበር በቷላ ግን ክሬስ በሁለታቸው መካከል ስላለው የመልክ ልዩነት አስረዳችኝ ለኔ ግን ሁለቱም ፊሊፒኖች ትናንሽ ቅድ አይኖችና ድፍጥጥ አፍንጫ ያላቸው ተመሳሳይ ፍጡሮች ናቸው በሥራ በጣም ይተጋገዛሉ ቋንቋቸውን መስማት በጣም ቢያስጠላኝም የውሸት ለመውደዴ ማስረጃ ብዙ ጊዜ በፈገግታ አያቸዋለሁ በዕድሜ አነስ ያለችዋ ሜሪ በፍቅር ዓይን ታየኛለች ክሬስ ግን አይኖቿን በጥላቻ ታሰፋቸዋለች ለዚሁ መፍትሔ እንዲሆነኝ ከሥራዬ ውጪ ክሬስን ልረዳ ብሞክርም ሙከራዬ ሳይሳካ ቀልረ ይልቁንም ይበልጥ እንድርቃት በሁኔታዋ አስረዳችኝ ችግሩ እርሷን ብቻ እንድርቃት ብቻ ሳይሆን ሜሪንም እንዳናግር አለመፈለጓ ነው ሜሪ ከመተኛቷ በፊት እኔ መኝታ ቤት መጥታ ልታሳስቀኝ ስትሞክር ክሬስ ከስነስርዓት ውጪ በሬን በርግዳ ሜሪን ጐትታ መውሰዲን ልማድ አደረገች ሜሪም እየሳቀች «ምን ያህል ተፈላጊ እንደሆንኩ አየሽ ትልና ተጐትታ ለመወሰዲ ምንም ቅሬታ አይታይባትም ብቻ በነጋታው ከሥራ መልስ እንደገና ብቅ ብላ ታዋራኛለች እየቆየን ስንፄድ የሜሪ ወሬ የሚናፍቀኝ አይነት እየሆነ መጣ ብቻ ብቻ የሜሪ ከልክ ያለፈ ፍቅርና የክሬስ ከልክ ያለፈ ጥላቻ ምክንያቱ አልገባኝ አሰ ሜሪ ስለሀዝቦቿ ብዙ አወራችልኝ ስለአረብኛ ሙዚቃ ያላትን አስተሳሰብ ግን ተቃወምኩ ስለወንድ ደግሞ የተለየ ኣገላለፅ አላት ቴፔ የሚጫወተውን ዘፈን ፀጥ ብላ ስትሰማ ቆየችና «ታውቂያለሽ። ከምትጐጂ አቸው ይልቅ ያን የወደድሺውን ባትሸሺ ትልቅ ደስታን ታግፒ ነበር» «ለወንድ የምትክራከርን ደካማ ሴት እጠላለሁ «ጥይኝ እንጂ ህይወቴን የከበቧት ወንዶች ናቸው ከአባት ፍቅር ጀምሮ የወንድም ፍቅር ለእኔ በህይወቴ እጅግ ጠቃሚ ነው በዚያ ላይ ብዙ አልሞከርኩም እንጂ ፈራኋት «አዝናለሁ አባትሽ ወንድ ልቤን ስንጥቅ ያደርጋታልፁ ደግሞም ወንድ ሁሉ አንድ አይደለም «አዎን ወንዶች ይለያያሉ ግን ባንድ ነገር ብቻ አንድ ናቸው ለኛ ለሴቶች ያላቸው አስተያየት አንድ ነው» ሜሪ ለወንድ ያላት ጥላቻ አሁን የደረሰችበት ቦታ ያደርሳታል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር የአባቷንና የእናቷን ታሪክ በዝርዝር ባትነግረኝም የጥላቻዋ መንስኤ አባቷ መሆኑ ነው ይኸው ያስተዳደጓ ሚስጥር በህይወቷ ገንፍሎ ወጣ ጁ ጁ ጁ ጁችጁ ጁ ጁ የአለባበሏ ጉዳይ ሙቀቱን በተመለከተ እንደሆነ ገመትኩ አልያም ፊሲፒኖች ሴት ለሴት አይተፋፈሩ ይሆናል እኔ እንጃ ብቻ ሁኔታዋ ልክ አንድ ለዓመታት የናፈቀችው ፍቅረኛዋ የሚመጣና ልብስ በማወላለሰቅ እንዳይደክምባት ያሰበች ያስመስላታል እራቁቷን ነች እንዳይባል ብቻ ለይምሰል ቅንጥብጣቦ ጨርቆች ጣል አድርጋለች «ሄይ ሜሪ ኬፊክ» አልኳት በጣም ገርማኛለች «ሙዚቃችንን ወደድሺው ባኞ ቤት እያለሽ እንድትሰሚው ፈልጌ ነው ጮኽ ያደረግኩት በእርግጥ የባኛ ቤት ሙዚቃ ነው» ። እኔም ሴት። ግን ለምን። አይበርድም አይደል ይሞቃል ስለዚህ ወሲብ የስሜት መናር ነው ሙቀት ነው ባጭሩ በንክኪ ወይም ንክኪን በማሰብ የሚፈጠር ስሜት ነው እነዚህ ንክኪዎች በተለያየ ቦታ የተለያየ ደረጃ አላቸው ጭኖችሽ ሲነኩ የሚሰማሽ ሙቀት አጀሽ ጫፍ ላይ ስትነኪ ከሚናረው ሙቀት እጆግ ይበልጣል አና ሙቀቶች የተለያየ ቦታ የተሰያየ ደረጃ ካላቸው ሴት የቱ ስትነካ በጣም ሞቋት ለእርካታ እንደምትጋበዝ ከጠንዱ ይልት ሴት ታውቃታለች የቱጋ ስትነካ እንደሚነዝራትም ልታውቅላት የምትችለው እርሷው ሴት ናት እንጂ ወንዱ ሊሆን አይቸልም ምክንያቱም ሴት ሌላዋን ሴት የምትነካው እራሷ እንዲነካላት የምትፈልገው ቦታ ነው በእርግጥ ለወንዶቹ ቦታዎቹን ማሳወት ይቻላል ያውቁታልም ምናልባት በተፈጥሮ ቢሆንም አነካካቸው አንደሴቷ ፍፁም አይደለም ታዲያ የወንድ አስፈላጊነት ምኑ ላይ ነው ከሴት ጋር ክወንድ የበለጠ አርካታ ማግኘት እየተቻለ ደግሞ ወንድ ብዙ ጊዜ በራሱ ስሜት ስለሚገዛ እራሱን ብቻ ሊያዳምጥ ይችላል ሴት ግን እንዳንቺው ሴት ነች ስሜታችሁ አካላችሁ ይመሳሰላል የሚያስጮህሸ ቦታ ያስጮሀታል በቀላሉ በስሜት ትግባባላችሁ አንድ ስለሆናችሁ ክሬስ ተቀብላ «ተያት ይህ ምን ተብትቦአታል» ሜሪ የክሬስን ንግግር ከምንም ሳትቆጥር ትላንት ባየችኝ አስተያየት እያየችኝ ይገባታል ያገሪ ባህል «ለምን ማታ አትሞክሪም የወንድ ይበልጣል ወይስ የሴት ሞክሪ ከዛ እነሜሪ እውነታቸውን ነው ወይም ውሸታቸውን ነው ትያለሽ ሞክሪ» «አእ አልኩና እራሴን ወደ ጠረጴዛው ደፋሁ ክሬስ በጥርጣሬ አየችኝና «ለመሆኑ ከወንድ ጋር ተኝተሽ ታውቂለሽ። » እራሴን በእሽታ ነቀነቅኩ ሁሌ ማታ ማታ አንድ ስዓት ላይ ሽርጥ ያሸረጡ የሆቴል ሰዎች መጥተው ላንድ ትንሽ ድግስ የሚበቃ ጣፋጭ ምግቦችን ትተው ይሄዳሉ ሊነጋጋ ሲል እንደገና መጥተው ያልታጠቡ እቃዎችን ሰብስበው ይመለሳሉ በሳምንት አንዴ የላውንደሪ ቤት ሰዎች መጥተው የቆሸሸውን የቤቱን ልብስ ሰብስበው አጥበው ተኩሰው ይመለሳሉ እንዲህ አይነት ቤት አጋጥሞኝ አያውቅም ሴትዮዋ በጣም ሀብታም ሆና ግን ድሀ ለመሆን እየጣረች ያለች ትመስላለች የምግቦቹ የሆቴሉ ወጪ ቀላል አይመስለኝም ለምን እንደሌሎቹ የወጥ ቤት ሠራተኛ ቀጥራ እቤቷ የጣፈጠ ምግብ በቀላል አስቤዛ የማድረግ ሀሳብ እንደሌላት አላውቅም ገንዘቧን ለማውጣት መንገድ የምትፈልግ ዓይነት ናት እርሷ እንዳለችው ሀውልት የማፅዳት ሥራዬን በሚገባ አከናውናለሁ ሀውልቶቹ ከሥራቸው የወከሉት ሬሳ ባይኖርም በየቦታው በሰው ቁመት ልክ ተገትረዋል ምናልባት በሀውልቶቹ ብዛት ያህል በየቦታው ተሰቅለው የሚታዩት የቀን መቁጠሪያዎች ቤቱን የተለየ አድርገውታል ምን ዓይነት ቤት ነው ሰዓት ቁጥር ቀን ቁጥር ሀውልት ሰዓት የቀን መቁጠሪያ ማለት የፈለጉት ሞትን ይሆን። ዘር ማንዘሮችሽ ሊረሱት የማይችሉት አይነት ሀውልት ልቀርፅልሽ ቃል እገባልሻለሁ» «በስመአብ ምን ገፊዋ ናት» አልኩኝ በሆዴ አኔ ገና ሀያዎቹን ዓመታቴን በደንብ ሳላጣጥም ለወደፊቴ በማሰብ ደፋ ቀና ስል ባጭር ልትቀጨኝ ሀውልት ልቅረፅልሽ የሚለው ጥያቄዋ ያስገርመኛል የተለያየ ቤት የተለያየ የሕይወት ልምድ አለው እኔም ለሥራ የምቀያይራቸው ቤቶች በገንዘብ ብቻ ሳይሆን የህይወትን ድሎትን ሀዘንን ችግርን ተስፋን በመጠኑም በሌሎች እያየሁ ብቻ ለራሴ ኖራዋለሁ ለምን እንደሆነ እኔንጃ ይህ የቤት ሠራተኝነት ሥራዬ ወደፊት ለሚኖረኝ ህይወቴ የማይበገር ጥንካሬን የካበልኝ ይመስለኛል የብዙ ህይወቶች ቅንብርም ጥሩ ትምህርት ሰጥቶኛል ልጅ ሳልወልድ የሕፃን አያያዝን የምታውቅ እናት ሚስት ሳልሆን የባል አያያዝን አውቄአለሁ ለሴት ትልቁ ልምዲን ማለት ነው የሰው ሚስጥር የማወቅ ጉብዝናዬን ተጠቅሜ ከዚህ ድብርታም ቤት ለመውጣት ብጥርም ማወቅ አልቻልኩም ብቻ ብዙ ሚስጥሮች እንዳሉ ይሰሙኛል አንደኛ የባልና ሚስቶቹ የእድሜ መራራቅ ሁለተኛ የሀውልቶቹ ሦስተኛ የእመቤቴን የመኝታ ክፍል እንዳይም ሆነ እንዳፀዳ ያለመፈቀዱ ሁኔታ አራተኛ የእመቤቴ ፀባይ እንዲህ አንዲሆን ያደርገውና የገፋፋው ምክንያት ዋና ዋናዎቹ ናቸው ጓደኞቼ እነ ቅድስት የሰው ሚስጥር ላይ የማድፈጤን ጉዳይ ከአወራሬ ስለሚያውቁ አጉል ፀባይሽን ትተሽ የራስሽ ህይወት ላይ ብታደፍጪ ይሻልሻል ብለው ይገስፁኛል እግዜር ለዚህ ግርድና ባይዳርግሽ ኖሮ ጥሩ የወንደል መርማሪ ወይ ሚስጥር ፈልፋይ ሰላይ ይወጣሻል« አፅምሮሽ ነገር ለመገጣጠም እግሮችሽም ኮቴ የማያሰሙ ጆሮዎችሽም ሳተላይቶች ናቸው» ብለው ይተርቡኛል አኔም የሚያስደስተኝ ልማድ ስለሆነ ሳላፍር በተለያየ መልኩ ልጠቀምበት ወደኃኋላ አልልም የሥራዬ መጨረሻ አመድ አመድ ቀለም ቀለም ብረት ብረት ወደሚሸተው ቀፋፊ ክፍል ገብቶ ጅምር ሀውልቶችን ማለቅ አለማለቃቸውን ማየት ነበር ካለቁ የሚሰጣቸውን ቦታ እመቤቴን ጠይቆ እንደሌሎቹ ሀውልቶች የፅዳት አገልግሎት እንዲሰጣቸው የማድረጉ ጥብቅ ትዕዛዝ ተሰጥቶኛል ግራ የሚያጋባው ነገር የሀውልቶቹን ማለቅ አለማለቅ እራሴው አውቄ ሥራ መጀመሩ ነው ሴትየዋ በቪህ ጉዳይ ገና ስገባ አስጠንቅቃኝ እኔም ተስማምቼአለሁ ይህን ካላደረግሁ ግን በደሞዝ እንደምትቀጣኝ ተነግርኛል እራሷን የምትመስል ሴት ምስል እየሰራች ባለችበት ሰሞን ከመቅረጪያ ክፍሏ ስትወጣ እንባዋን ስትጠርግ አንድ ሦስቴ አጋጥማኛለች ሰው ለራሱ ሀውልት ማዝን ቢችል በርግጥ ከእርሷ የበለጠ ለማዘኑ ጥርጥር የለውም ደግነቱ ሰው ለራሱ ሀውልት እንዲያዝን ዕድል አልተሰጠውም እና ለምን ይህች ሴት አድሉን ያገኘት ይመስል ስለራሷ ምስል ሀውልት ቀርፃ ታነባለች። የተቀየረ ነገር የለም ብቻዬን ሆቼ ረጅም መንገድ ተጓዝኩ ረጅሙ መንገድ አዲስ ሀሳብ አስተማረኝ በደረቴ የያዝኩትን በሽታ እንደያዝኩት ቁጭ ማለት ያለመፈለግ እዲስ ሀሳብ ውስጤ ሲያድግ ተሰማኝቹ ሚስኪኑ ሰሚርን ለምን አሰቃየዋለሁ ብዬ ባሌቴሄ የማኮራ ጠንካራ ሴት መሆን አለብኝ አልኩ ሯ እቤት ስገባ ጥሩ እራት አዘጋጅቼ ለሰስ ባለ ውዌጄ ተነከርኩና ተቆነጃጅቼ ሰሚርን ጠበቅኩት ምንም አዲሺ ነገር እንዳልተፈጠረ ሁሉ ተሳስቀን ጥሩ ለሊት አሳለፍን ጠዋት ላይ ስለበሽታዬና ቀዶጥገናዬ በርጋታ አወራን በሚቀጥለው ቀን ሆስፒታል አብረን ፄድን የመረመረኝ ዶክተርም ለቀዶጥገናው ብቸኛ ወሳኝ እኒው መሆኔን ነገረኝ በነገሩ ለማሰብ ብዙ ጊዜ ባልወስድም እንደሚያዋጣኝ መከረኝ አኔ ግን ተስፋ በመቁረጥ መሞቴ ላይቀር ለምን ጡቴን አቆረጣለሁቡ ሳልቆረጥ ከነሙሉ አካሌ ብሞት እመርጣለሁ» አልኩ ሀኪሙ ለበሽታዬ የጥርስ ህመምን ምሳሌ ሰጠኝ በጣም የሚጠዘጥዝሽን ጥርስ ብትነቅይው እፎይታን ታገኛለሸ ይኸም እንደዛ ነው አለኝ ከዚህ በፊት ታምሜው በማላውቀው መልኩ የሚያሳብድ ስቃይ በጡቴ ላይ ይሰፍራል ያኔ አሁን በቀን አራት ጊዜ የምትወስጂው የስቃይ ማስታገሻ ክኒኖች ስቃይሽን መቆጣጠር ያቅታቸዋል ። መፍትሄ ነው ያሉት የጡትሽን መቆረጥ ከሆነ እኔን የጡትሽ መቆረጥ አይቀይረኝም ምንም ነገር ቢሆን በጣም እንደምወድሽ እወቂልኝ እወድሻለሁ በጣም ብሎ ባሌ ጥብቅ አድርጐ አቀፈኝ አይኔን ጨፍቼ ለጡቴ መቆረጥ ፈጥቼፔ ተስማማሁ ቀዶጥገናውን በማላውቀው አገር ማድረጉን ባለመውደዴ በዚያው ሳምንት ሽርሽራችንን አቋርጠን ወደ ቤታችን መጣን የምርመራ ወረቀቴን የተቀበለኝ ሀኪም እላዩ ላይ ተቀባ ልዩ ነገር አለው ልብ ያሰክናል በቀላሉ ሳንዳምነው አደረገኝ ለቀዶ ጥገናው ስኬታማነት መጀመሪያ በሽተኛው ዶክተሩን መውደድ አለበት ካልወደደው ወደ ሌላ ዶክተር ይሄድ ዘንድ ይመከራል እኔ ግን የመደመሪያውን ዶክተሬን ወድጀው አምኘፔዋለሁ አድለኛ ነኝ እንደሚሉት ከሆነ ጡቶቼን በየቀኑ መቆጣጠር ይገባኝ ነበር ይኽን ባለማድረጌ ነቀርሳው ከቁጥጥር ውጭ ሆኖ ጡቶቼን ጐድቶአቸዋል አየሾለ ለመጣው ጡቴ ደስተኛ ነበርኩ ስፖርት ቤት እየፄድኩ ስፖርት እሠራ ስለነበር አስፖርቱ የሰጠኝ ውበት እንደሆነ ነበር የገባኝ በክንዴ ላይ ለሚወጥረኝ ህመም ቁብ መስጠት አልፈለግሁም ወጣትነቴን አስከመጨረሻው ብቻዬን እየቦረቅሁ አፍላ ጉልበቴን በስፖርት መገምገም በጣም ያስደስተኝ ነበር ልጅ ውለጅልኝ እያለ የሚለምነኝንም ባሌን ቀጠሮ እስጠዋለሁ ሰላሳ ሁለት ወይ ሦስት ሲሞላኝ እወልድልሀለሁ እያልኩ እስከዛ ግን ልጄ አንተ ነህ ብዬ ጥያቄውን እንዲረሳ እየሳምኩ አባብለው ነበር የሚገርመው ነገር ስለዚህ በሽታ የተፃፈውን የዶክተሮች አባባል ሳነብ ከሰላሳ ዓመቷ በፊት ልጅ ወልዳ ያጠባች ሴት ለዚህ በሽታ የመጋለጧ ዕድል የቀነሰ መሆኑ ነው ቆጨኝ ጥሩ ዕድል አመለጠኝ ቢያንስ ባሁኑ ወቅት ፀጉሩን እያሻሸሁ የማስተኛው ህፃን ይኖረኝ ነበር ካሁን በኋላ ልጅ የመውለዱ ነገር የማይታሰብ ነው ፈፅሞ ዶክተሬን ስለበሽታው መንስኤ ጠየቅሁት ለበሽታው መንስኤ ከግምት በቀር ትክክለኛ መልስ አልተገኘለትም ብቻ ግምቶቹ ወደእውነተኛው መንስኤ የቀረቡ ዓይነት ናቸው ጭንቀት የሚፈጥረው የሰውነት መኮማተርም ይህን በሽታ ያመጣ ይሆናል ተብሎ ተገምቶአል አንቺ በምን መጣብኝ ብለሽ አራስሽን አታስጨንቂ ይኹ መሺአትላህ የአምላክ ትዕዛዝ ነው ብሎ ነገረኝ እኔ ግን የእናቴ ነቀርሳ ተከትሎኛል ባይ ነኝ ሐኪሜ አማራጭ የቀዶጥገና ዘዴዎችን አንድ በአንድ ዝረዘረልኝ እኔም ጡንቻዎችን በመጠቀም የሚካፄደውን ዘዴ መረጥኩ ምክንያቱም ይህ ዘዴ የሆድ ስብን ከመጠቀሙ ዝዴ ያጠረ ቀዶጥገና ስለሆነ ነው ስለቀዶጥገናው የማስታውሰው ክንውን ወይም ህመም የለም ከዛ በኋላ ግን ከታሸገው ግራ ጡቴ ይልቅ ግራ ክንዴን ቀፍድዶ ያያዘ ሀይለኛ ህመም ተሰማኝፊ ሀኪሜም ሙሉ ጡቴንና ባካባቢው ያሉትን ስቦች ሙሉ ለሙሉ ማስወገዱን ነገረኝ ፋሻው ሲፈታ ስለሚኖረው ጎድጓዳ ቦታ እንደውም በቀዳዳው ሳንባዬን ወይም ልቤን ስመለከት ብዙ ጊዜ አለምኩ በሕልሜ ያየሁትን በውኔ ላለመድገም ያ ፋሻ ለዘለዓለም እላዬ ላይ ተጠምጥሞ እንዲቀር ተመኘሁ እንደኔ ላለች ሀያ አራት ሰዓት ሙሉ ስለሰውነቷ ቅርፅ ለምትጨነቅ ሴት የጡት መቆረጥ ምን ዓይነት የቀን አስፈሪ ቅዥት እንደሆነ መገመት አያዳግትም እጄን ወይም አንድ እግሬን ባጣ ከሚሰማኝ ስሜት የበለጠ ውስጤ ሲቆስል ተስማኝ ባዶ የሆንኩ መሰለኝ ሴትነቴም ትርጉም እንዳጣ ይገባኛል የቀዶጥገናውን ጨርሼ በቀላሉ አልተገላገልኩም ራዲዮቴራፒ በየቀኑ ለተወሰነ ጊዜ ማድረግ ነበረብኝ ይህ የህክምና ክትትል ውስጤን እየረበሸው በማስመለስ ብዙ ተቸግሬ ነበር። ንብረቱ የሚስቱ ነው እርሷ የፈለገችውን የማድረግ ሙሉ መብት አላት ብሎ ምንም አድል ሳይሰጣቸው የሰሚር ብቸኛ ወራሽ አደረገኝ በርግጥ አኔ ይህን ሁላ ንብረት ባለው አጭር ጊዜዬ ምንም ልጠቀምበት አልችልም ለራሴ አብዛኛውን ጊዜዬን የማሳልፈው በሆስፒታል ሆኗል ግን የሰሚር ቤተስቦች ያደረጉት ነገር በጣም ስላናደደኝ ከሰሚር ንብረት አንዲት ሚስማር እንኳን ለእነሱ ትቼላቸው አልሞትም ብዬ ቀዶጥገናዬን አፋጠንኩ በሰሚር መሞት ቅስሜ ተሰብሮ ፈጥፔጌ እንድከተለው የሁለተኛ ቀዶጥገና ችላ የማለት ሀሳብ ነበረኝ ስቃዩንም የምወደው መስሎኝ ነበር አሁን ግን እነዚህን ጨካኝ ሰዎች መቅጣት አለብኝ ብዬ ለማስተካከል ስል ብቻ መኖር ፈለግኩ ከባሌ ሞት በኋላ በሽታዬን አስታኮ ሲጐዳኝ ወይ ሊጠቀምብኝ የመጣን ሰው በበቂ ሁኔታ የመበቀል አዲስ ፍላጐት አደረብኝ የሁለተኛው ጡቴ ሲቆረጥ ከበፊቱ የባሰ ስቃይ ነበረው ሦስተኛው ሙሽራም በቀኝ ክንዴ አውጡኝ እያለ አሞጥሙጧል ለሶስት ወራት ያህል በየቀኑ ለህያ ደቂቃ ያህል በራዲዮቴራፒ ስር ደረቴን ሰጥቼ እተኛለሁ ልብስ ማውለቅ ልብስ መልበስ እራሱ ለጉዳተኛ ክንዶቼ አሰልቺ ነበር ያን ሁላ ጥርሴን ነክሼ ቻል አደረግኩ በፊት የቀረፅኳቸውን የደስታ ቅርዓ ቅርፆቼን ሰባብሬ ለመጀመሪያ ጊዜ የነቀርሳን ምስል ያዘሉ ሁለቱን ሀውልቶች ቀርጩ ከበሬ በራፍ ግራና ቀኙን አቆምኩ አንዱ የባሌ ህይወት ላይ የሆነ የውስጤ በሽታ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ አኔው ውስጥ አልወጣም ብሎ ስብዙ የንብረቱን ጉዳይ መድኃኒቶችና ቢላዎች አልበገር ብሎ እገድልሻለሁ የሚለኝን ጭራቅ መሳይ ነቀርሳን ይወክላሉ ባለ ብዙ እጆቹ ይህ ሀውልት ባሌን አዘናግቶ የመኪና አደጋ ላይ የዳረገውን ስራስራሙን ሙሽራ በትክክል ይመስሳላል ይህን በሽታ ከያዝኩበት ጊዜ አንስቶ በየአራት ሰዓቱ የምወስደው የስቃይ ማስታገሻ ቀለቤ ሆኖአል ሁለተኛውን ባሌን ረገብን እዚያው ሆስፒታል ነው ያወቅኩትፁ የሰሚርን ቤተሰቦች የማደማበት ብትር እየፈለግኩ ነበር ወጣቱን ጥሩ ማድሚያ ባል ወዲያውኑ አግብቼ እቤቴ ይዝው ገባሁ ጋብቻችንን የፈፀምነው እዚያው ሆስፒታል ነበር የሰርጉ እለት ዶክተሬ ነርሴ እና የማላውቃቸው ምስክሮች «መእዙን በእስላም ሕግ የሚያስተሳስር የመስጊድ ተወካይ እና ሙሽራው እኔ ብቻ ሆነን በብርቱካን ጭማቂ ደገስን ለነርሴ ሁሉን ነገር እነግራት ነበር የዚህን ጋብቻ ዋና ምክንያት የምታውቀው አሷ ብቻ ነበረች የሰሚርን ንብረት ለዚህ ወጣት ትቼለት ብሞት ፅድቅም ይሆናል ብዬ አስቤ ነበር ምን ያረጋል። ረገብ አዲሱ ባሌ ሊያታልለኝ ታሪኬን ክነርሷ ሚስቱ ሰምቶ በኔ ላይ ሻጥር ተማክረው ኮንትራት ጋብቻ ከኔ ጋር ለመፈፀም ሚስትየው የገዛ ነርሴ ስቃዬን ሕመሜን ያየችው ሴት ፈቅዳለት መሆኑን ደረስኩበት ሁለቱንም ልቀጣ አሰብኩ እርሷን ባሏን በማታስበው መንገድ ነጥቄ የራሴ ብቻ ላደርገው እርሱን ደግሞ ገንዘቤን በማይወደው መንገድ ልግተው ይህንንም እንዳይ አምላኬን እድሜ ጠየቅኩ ለነርሴም ሆነ ለረገብ ባለና ሚስት መሆናቸውን ማወቂን አላስታወቅኳቸውም ሲመስሉ እየሳቅሁ ፊልማቸውን አደነቅሁ የፊሙ መጨረሻ የኔ ተራ አንደሚሆን ሳስብ ፈነደቅሁ ሀውልቶቼን ከመቅረፅ በኋላ የሚተርፈኝን ሰዓታት ረገብን በመበቀል አሳልፋለሁ ብዬ ወሰንኩ በጫጉላ ጊዜአችን ቡና እያፈላሁለት በውድ ዋጋ የገዛሁለትን ስጦታ አደንዛዣን ፅፅ ከስኳር ጋር አማስዬ አጠጣዋለሁ እርሱም ቡናዬን እጅግ እየወደደው መጣ ሱስ እንደሆነበት ሳውቅ ከለክልኩት ለመነኝ ሚስቱን በፊት ለፊቴ እንዲፈታ አዘዝኩት ትዕዛዜን ያለማወላወል ፈፀመ ነርሴ የምትወደው የአምስት ዓመት ባሏን አጣች ብልጣ ብልጥ ባሏም ከቀን ወደ ቀን እየተጃዳጃለ ስውነቱ እያለቀ እግሬ ስር እንደውሻ ረገጥኩት የማሸትተው ሀሺሽ የትም እንዳይንቀሳቀስ አደረገው በቀሌን ጨረስኩ ብሞት ግድ የለኝም ጁ ጁ ጁ ጁ ጁ ጁ የሚስጥሩ ማስታወሻ ደብተር ጉዳይ ከግብፃዊቷ እመሰዒድ ጋር አቃቃረን ከዚያች ሴት ጋር ልቃቃር ወይስ ልፋቀር የቱን መምረጥ አንዳለብኝ አላውቅም የሆቴል ሠራተኛው ባሏ ሥራ እንዲያፈላልግልኝ ስል ልጣላት አልፈልግም ግን ደግሞ በነዓ እያሳሳቀች በምታሰራኝ ሰበብ እቤቴ ስገባ እራሴን መስታወቴ ላይ ሳይ ሞኛ ሞኝ ምስል ስለማይ እበሳጫለሁ እራሴን መስታወት ላይ ሳየው የተለያየ ይሆንብኛል ይህ ሁኔታ ሌሎች ላይ ደርሶ ነግረውኝ ስለማያውቁ ነው መሰለኝ አኔ ላይ ብቻ ያለ ልዩ ልማድ አድርጌ እቆጥረዋለሁ አሙሰዒድ አጃጅላኝ ልብሷን ሙልጭ አድርጌ አጥቤላት አቤቴ ገብቼ ፊቴን በመስታወት ሳይ ለሀሟጧ የተዝረከረከ ጅላጅሏ እኔነቴን አያለሁ አብዛኛው ጊዜ ግን ጥንካሬዬንና በራስ መተማመኔን ማየቴ ለስደቱ ምስቅልቅል ህይወቴ ኃይልን ይሰጠኛል ታዲያ እመሰዒድ የደብተሩን ዝርዝር ትርጉም ሰለሰጠችኝ ብዙ አስባበት ለእመቤቴ እንደምትናገርብኝ አስፈራርታ የወር ድፍን ደሞዜን ደፍራ ጠየቀችኝ ይመስለኛል ተመሳሰለብኝ ብላ የምታማርረውን ህይወቷን በኔ ደሞዝ ለመቀየር የወሰነች ትመስላለች ሞቷን እየተጠባበቀች ያለችው እመቤቴ የጠቀሰችው አረፍተ ነገር ትዝ አለኝ «ከባሌ ሞት በኋላ በሸታዬን አስታኮ ሊጐዳኝ ወይ ሊጠቀምብኝ የመጣን ሰው በበቂ ሁኔታ የመበቀል ልዩ ፍላጐት አደረብኝ» የሚለው ታዲያ ሚስጥራን ያለፍቃዲ ሰርስሬ አውቄ ሌሎቹንም አሳውቄ እመሰዒድ ከነገረቻች ምኔ ሊተርፍ ነው በሰው አገር ብዬ ፈራሁ የግብፃዊቷን ፉከራ ለማክሸፍ ተነኮልኩ ለእረፍቴ ስወጣ ተዘጋጅቼ ግብፃዊቷ ቤት ፄድኩና «አንቺ ስለተረጐምሽልኝ ደብተር ለሴትየዋ ልትነግሪ ከወሰንሽ አኔም ለእመቤቴ የምለው አለኝ የቀልድ ሳቅ ሳቀችና በርከክ ብለሽ «ሰም ሂኒ ሰም ሂኒ» ይቅር በይኝ ብለሸ ልታለቅሺ ያ አይሆንም የምትምርሽ ይመስልሻል። » ጠየቀ «አይዋ አዎን» አለችው ከአይኑ ስር ሊሸሸገው ያልቻለ ፈገግታ አየሁበት በጣም እረጅምና ደልዳላ አካል አለው ልቤ ወዲያውኑ መጨፈር ጀመረ ግን ቁመቱን ችላ እንዳለ ሰው አይኔን ወደመሬቱ አደረግኩ ተስማምቼ ሥራ ጀመርኩ ልጆች ስለሌሉ ብዙ የሚያደክም ሥራ አልገጠመኝም ብቻ ወጣትነቴን የሚፈታተን ውበትን ፈርቻለሁ ቀስ በቀስ ከሰውዬው ጋር ሳላስበው የአይን ንግግር ጀመርኩ የዓይን ጨዋታ ባይኑ ብቻ ከወደመሀል ጥቁር ሰማያዊ የሆነውን የዓይኑን ብሌን ወደ አመዳማ ግራጫ የሚያደላ ወፍራም ክብ ሰርቶ አድምቆታል የተቀረው የዓይኑ ክፍል ነጭ ነው የንጣት መጨረሻ ነጭ እንቅልፉ እንኳን ቢመጣ ይቀንሳሉ እንጂ አይደፈርሱም ሁሌ የነፁ ናቸው በእግር ጣቶቹንና እጆቹን የወረሰው ፀጉሩ አካሳቱ በሙሉ ፀጉር ብቻ እንደሆነ ይናገራሉ ፀጉር የሞላው ወንድ ውድድ የማደርግ ይመስለኛል ልክ ሕፃናት እያለን አባ ጨጓሬ እያልን የምንጠራው ተክልን ቆርጠን እጆቻችን ላይ ስናነካካው የሚፈጥረውን ልስላሴ ዓይነት ልስላሴ መላ አካሌን ገላዬን በመላ በፀጉሩ የሚያጫውተው ይመስለኛል ሁሌ ማታ ማታ ሥራ ጨርሼአሰሁ ብዬ ለመኝታ ስሰናበት እመቤቴ አይኗን ከቴሌቪዥን ላይ ሳትነቅል «ነሚ ተዢፒ» ስትለኝ ባሏ ግን ስርቅ አድርጐ የሚያጠግብ ፈገግታ በዓይኑ ይሰጠኛል ባይኑ ፈገግ የሚል ሲያሰኘው የሚፈነድቅ ቆንጆ ነው ብዬ ተመኘሁት በማያገባኝ በሚስቱ ስቀና ተሰማኝ «ለምን አትወፍር ይህን የመሰለ ገላ እያቀፈች» አንዳንዴ በህልሜ በዚያ ወንዳወንድ ቁመናው በጣም ሲጫነኝ ደክሞኝ አድራለሁ የእውነት አብሮ ያደረ ያክል ሰውነቴ በምኞት ድቅቅ ሲል ይውላል ምኞቴ ምኞት ሆኖ አልቀረም አንድ ቀን አይኔን ስከፍት የእውነት ክፊት ለፊቴ ቆሞ አየሁት ያን የመሰለ ወንድ የክፍሌን በር ከፍቶ ካልጋዬ አጠገብ የምሆነው ጠፋኝ ረጋ ብሎ አልጋዬ ጫፍ ተቀመጠ «ባህቢክ አወድሻለሁ አለኝ እኔ ዝም «ምን አወል ነዝራ በመጀመሪያ እይታ አለኝ እኔ ዝም «ኢንቲ ጀሚላ ወቡኒ ቆንጆና ቡናማ ነሽ አለኝ እኔ ግን ዝም ብድግ ብዬ አልፌው ልወጣ ስል ወገቤን ያዘኝ ጠንከር አድርጐ መተንፈስ አቃተኝ ወደ ላይ ብድግ አደረገኝና እንደሕፃን አየኝ ደግሞ አወረደኝ መፍዘዜን እርግጠኛ ሲሆን ቀስ አድርጐ አስተኛኝ ረጅም የመኝታ ቀሚሴን ከእግሩ ጀምሮ እስከ አንገቱ ቀደደው በመንገብገብ ዓይነት ቢጃማዬ ሲቀደድ ያሰማው ድምፅ ሚስቱን ከእንቅልፏ የሚቀሰቅስ የመድፍ ድምፅ ሆኖ ጐልቶ በጆሮዬ አንጣረረ። እኔ ግን በግማሽ ፍቅር ተጠምጄ ወይ ጉድ ማለት ጀምሬአለሁ እፄ የማፈቅረው ሲዋብ አይኖቹ ሲፈዙ ብቻ የመሆኑ ጉዳይ ገርሞኛል ነገሮቹ ሁላ በፍጥነት አድገው በፍጥነት ሊጠፉ ነው ብዬ ብዬ ስለሚስቱ እንዲነግረኝ ጠየቅኩት ለምን እንደሆነ እራሴም አላውቅም ከሁለት ላንዱ ሁኔታዬ እንደሚሆን ግን እርግጠኛ ነኝ ስለሚስቱ ሲያወራልኝ በቅናት ነድጄ እየከሰመ ሊፄድ የተቃረበውን ፍቅር እፍ ብዬ ለማንደድ ወይ ደግሞ ስለ ሚስቱ ሲያወራልኝ ምንም ሳልቀና እየጠፋ የሄደው ፍቅር እፍ ብሎ ጨርሶ ለማጥፋት እራሴን አዘጋጀሁ «ስለሚስትህ ንገረኝ» «ሚስቴ እንዳየሻት አስቀያሚና ወፍራም ሴት ነች» «ታዲያ ምኗ ነው «ታውቂያለሽ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለሚስቴ ለሌላ ሴት ፍላጐት ሲኖረኝ ምናልባት በህይወትሽ የመጀመሪያው ወንድ ስለሆንኩ ይሆን እንዲህ ስለሁሉ ነገር የማወራልሽ። » የደስታ ፊቱ ቦግ አለ «አይ ሳይሆን «አሺ ልቀጥልልሽ ሚስቴ ይቅርታ ናዲያ ሁለት ወንድማማቾች የወለዱን የአጐት ልጃማቾች ነን በልጅነታችን ጊዜ ብቻዋን የመሆን ልማድ ስለነበራት ምንም የልጅነት ትዝታ ከእርሷ ጋር የለኝም ስንጋባ የመረጥኳት እኔው ነበርኩ እናቴ በተለይ አስቀያሚነቷን እንደ ትልቅ ነውር ቆጥራ ለሰርጉ እንዲሰናከል ብዙ ጥረት አድርጋ ነበር እፄ እንግዲህ እንዲህ ነኝ ሚስት ስመርጥፁ ሚስቴ ለእኔ ብቻ መሆን አለባት ባይ ነኝ ቆንጆ ከሆነች ብዙ ነገሮች ይጋሩኛል ወንድ ማለቴ አይደለም የሳውዲ ሴቶች የሚያደርጉት ግብዣ ብዙ ነው እንደውም ብዙዎቹ ግብዣ ህይወታቸው ነው ይጋብዛሉ ይጋበዛሉ ይለብሳሉ ይፈነድቃሉ ይህ ሁላ ባላቸው ትከሻ ላይ ነው እንደምታውቂው ሚስቱን የሚያሠራ ወንድ ወንድ አይደለም የሚል ባህላዊ ተፅእኖ አለ ወንድ ይሠራል ሚስት የሠራውን ሁላ በግብዣ ምሽት ውድ ቀሚሶች አፍሳ ትጨርሳለች በተለይ በተለይ ለእራሳቸውና ለልጆቻቸው በቂ ነው ብለው የገመቱትን ሀብት ከያዙ የተትረፈረፈ ሀብት የሚያመጣባቸውን ሰበብ ለመቅጨት ጥሩ የገንዘበ መበተኛ ዘዴአቸው ግብዣቸውን ማብዛት ነው በግብዣ ወቅትም ተሰብስበው የባላቸውን ንብረት የመቀነስ ወይም በራሳቸው ስም ለማድረግ ውጥን ይወጥናሉ ሞኞች ናቸው በርግጥ ሁለተኛ ሦስተኛ ሚስት ለማግባት ገንዘብ ወሳኝነት አለው ይህን የሚያደርጉት ባሎቻቸውን ጠልተው ሳይሆን ሀይማኖቱ እና ሕጉ የሚፈቅደውን ከአንድ በሳይ ጋብቻ እንዳይፈጠር ለመከላከል ነው ታዲያ በሌላ ጐኑ ሚስት እንዲያገባ መገፋፋታቸውን አያውቁትም ሌላ ጋብቻ የመፍጠሩ ሁኔታ የሚፈጠረው በገንዘብ ብቻ ይመስላሳቸዋል በዚህ መንገዳቸው የባላቸውን ህይወት አሰልቺ ማድረጋቸውን አያገናዝቡም ይህን ሕይወት ከማግባቴ በፊት በታላላቅ እህቶቼ በእናቴ በአጐቶቼ በሁሉም አይቼዋለሁ ታዲያ ቆንጆ ሴት ካገባሁ እንደፈለግኩ ላደርጋት አልችልም ብዬ ናዲያን አገባኋት ካገባኋት በኋላ ግን ይህችን ሴት የሴቶች ሁሉ ቁንጮ አድርጌ እንዳከብራት የሚያደርገኝ ብዙ ባህሪያቶችን አገኘሁ። በርግጥ በሁሉም ወቅት ስህተትን መሥራት ሀይማኖቱ ቢከለክልም ይህ ወር ግን የተለየ የሚያደርገው የሰው ልጅ ለጌታው አራሱን በሕግጋቱ ተገዢ ለማድረግ አክብሮቱን የሚገልፅበት ልዩ ወር ነው በመፆምም ይቅርታን ይጠይቃል ወንድ ያሰጋብቻ ከሴት ጋር መተኛቱ ሀጢያት ነው ይህንን ስህተት እንዳይሠራ አላህ ወንድ ያማረችውን እንዲያገባ የጋብቻ ቁጥርን ለወንድ ከፍ አድርጐአል በፆታ ጥያቄ ወንድ ከሴት ደካማ እንደሆነ አላህ ስለሚያውቅ ወንድ ከአንድ ሴት በላይ እንደምታስፈልገውም ለእኛ ተረድቶልናል ግን ከጋብቻ ውጪ ሀራም ሀጢያት ነው እኔም ይህን ሀጢያቴን ማፅዳት አለብኝ ስለዚህ እኔና አንቺ በሰላም እንለያያለን ጥሩ ልጅ ነሽ ምክንያቱ ይህ መሆኑን አልጠበቅኩም እንጂ ከሁለት አንዳችን የመዝጊያ ንግግር እንደሚጠ አውቄው ነበር የፍቅሩም ነገር ሲያልቅ ታውቆኛል እኔም የምፈልገው ውሳኔ ይህ ነበር መለያየት ብቻ ከዩስሪ ጋር መቀያየሙን አልፈለግኩትም ጠንካራ ምክንያት ሰጥቶኛል ረመዳን ፈገግ አልኩና የውሸቴን «በቃ አ ረመዳን ሲያልቅ እንደገና አንገናኝ» በአላህ ልታሾፊ አየሞከርሽ ነውን። ሽው አድርጐ ፎቅ የሚያወጣ እያሰ «የላ ክልሲ ቶሎ ጨርሺ» አለኝ የገዛ ሚስቱን እንደሚያዝ አባወራ የሱቁ ተላላኪ አይኔ ያረፈበትን ቦርሳ አውርዶ «ማዳም ኩዲያ ኢንቲ አህበብቲያ ኣመቤቴ ውሰጂአት ወደሻታል አለኝ የተከተለኝ ሰውዬ ዓይን ዓይኔን እያየ ዋጋ ተዋዋለ ከፈለ ቦርሳው ውድ ነው ሰውዬው ለመክፈል አላወላወለም ሰውዬው ሀብታም ነው ማለት ነው ተከትዬው ወደ መኪናው ገባሁ «ጥቁር ሴት ጣፋጭ ናት» የንግግሩ ሁኔታ ደስ አላለኝም ስሜን ይጠይቀኛል ብዬ ገምቼ ነበር ለስሜ ግድ የለውም ማን ልሁን ለማወቁ ምንም ስሜት የለውም ግንኙነታችን የታወቀ ሆኖ እርሱ ሴት ፈልጐ እኔ ገንዘብ ፈልጌ ቢሆንም እኔ የእርሱ ቦታ ብሆን ስሙን እጠይቅ ነበር እቤቱ ይዞኝ ሲገባ አምስት ጊዜ ያህል በመኪናው አሽከረከረኝ ሁለት ጊዜ እቤቱ ገብቶ እየተቁነጠነጠ ተመለሰ ለሁኔታው አዲስ ነው ብዬ ገመትኩና ዕድለኛ ነኝ አልኩ ቁንጅናዬን ለማድነቁ ከአይኑ አነበብኩ ይህ ደግሞ ትንሸም ቢሆን ጥሩ ስሜት ይሰጠኛል ፍቅርን ለመመሰሉም ይረዳኛል «ከገመትኩሽ በላይ ነሽ ይህ አጭር ቁመት ይህን ሁላ የሰውነት ውበት ይዚል። » ታዲያ ገንዘቡን ከየት አመጣሽ እውነቱን ንገሪኝ» «ምን ለውጥ ሊያመጣ» አንገቴን ደፋሁ ችቹ ጁ ጁ ጁ ጁ ጁ ላገባ መወሰኔን እነአይሻ ሲሰሙ ገና ካሁኑ ልትታጠሪ ነው» ብለው «ታጠረች አሉ በትዳር እያጨበጨቡ ዘፈኑልኝ አስመሮም መጀመሪያ ያየኝ የቅድስት ዝክመድ ቤት ስሰራ ነበር ብዙ አላወራንም እርሱ ግን ጥሩ አድርጐ ሳያስተውለኝ አልቀረም እንደሌሎች ለጓደኝነት ሳይሆን » የሚለውን ዘፈን ለጋብቻ ስለጠየቀኝ ደስ ብሎኛል ትዳር እዚህ አገር እንደማይጥም ባውቅም አንድ ቀን የሚያማምሩ ልጆቼን ይዢ አገሬ እገባለሁ ደግሞም ፍቅር ከተጋባን በኋላ ሊመጣ ይችል ይሆናል ብዬ አመንኩ እርሱም በዛ ያመነ ይመስሳል እሰራባት የነበረችው አበሻ ሴትም ስለ እሱ ስታወራ ሁሌ ጥሩነቱን ታወሳ ነበር ትልቁና ዋናው ነገር ያገሬ ልጅ ነው ሁለተኛው ለጋብቻ መስማማቴን ቶሎ ያጠነከርኩበት ጉዳይ የፈራሁት ነይ እያለ የሚጐተጉተኝን አሳሳች መንገድ ለማምለጥ ነው በቀደም ተሳስቼ ወጥቼ ያን ቦርሳ የገዛልኝ ሰው ጋ የደረሰብኝ እንዲደገም አልፈልግም ስራ መስራቱም በጣም አስጠልቶኛል ስለዚህ አግብቼ አዲስ ህይወት ቢኖረኝ አይከፋም ይህ ትዳር ከአሳሳቹ መንገድ ያድነኛል ቤተሰብ መስርቼ ከባሌ ጋር ሆነን አገራችን መግባቱ ትልቅ እድል ይሆነኛል ቁጭ ብለን ስለቤተሰባችን ስናወራ ስበሳጭ ሳዝን በጥብቅ እቅፉ ተስፋን እንዲሰጠኝ ብቸኝነቱን ጥሶ አብሮኝ እንዲሆን ባል ማግባት መረጥኩ አስመሮም ስራው ሸፋጥ ነው ሸፋጥ የሚለው ቃል መሸፈጥ ከሚለው አረብኛ የተወሰደ ነው ሸፋጣ የሚባሉት እዚህ አገር በሽንት ቤት መጣጭ መኪኖች በሹፌርነት ወይም በባለቤትነት የሚሰሩ ናቸው ታዲያ እዚህ ያለ ሀበሻ ወንድ ዘጠና አምስት በመቶ በዚህ ስራ የተስማራ ነው ላገባው ያሰብኩት ሰው ታዲያ የሽንት ቤት መጣጭ መዚኪና ባለቤት ነው። እናም ሸፋጣ አለው ከተባለ ሀብታም ነው ማለት ነው የሰርጌን ምክንያት በደንብ ያወቀች ቅድስት ብቻ ናት አኔ አስመሮምን ለምን ልታገቢ እንዳሰብሽ አውቃለሁ አዕምሮሽ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሊያሰላስል የፈለገውን ነገር እንዳያስብ አስመሮም ጀርባ ልትሸሸጊ ነው እራስሽን ሸጠሽ ስራ ጠልተሽ በቀላሉ ገንዘብ ልታገፒ የምትችይበትን መንገድ ፈልገሻል ግን ደግሞ ያን እንዳታደርጊ የሚከለክልሽ ከባድ እንቅፋት በመፍጠር እራስሽን ከዚህ ሀሳብ ትገላግያለሽ እመፒኝ ይህ ጥረትሽ ላሁኑ ሁኔታሽ ለጊዜው መከላከያ ይሆንሽ ይሆናል ግን ወደፊት አንድ እኩይ ሀሳብ በመጣልሽ ቁጥር ከራስሽ ሀሳብ ለመሸሽ ጠንካራ ምክንያት ስትሺ መኖር እንዴት ትችያለሽ ለምሳሌ አንድ ሰው ለመግደል አስበሽ ግን ደግሞ ያን ሰው ላለመግደል መልአክ መጥቶ «ተይ አትግደይ» ብሎ እንዲያግድሽ ትመኛለሽ ለምን ከራስሽ ጋር አትስማሚም። እንዴት ሰው የገዛ ሀሳቡን ይፈራል አለችኝ ቅድስት የዋዛ አይደለችም የሰርጉ ቀን ተፋጠነ ከድግሱ በፊት የሚፈረም የጋብቻ ውል አለ አስመሮም ከሽማግሌዎች ጋር እያለን የጋብቻ ውሉ ጮክ ተብሎ እንዲነበብ ጠየቀ የጋብቻ ውሉን የፃፈው አራሱ መሆን አለበት «የሕይወት ጓደኛዬን ከመምረጤ በፊት ያፈራሁት ንብረትም ሆነ እርሷ እኔን ከመምረጧ በፊት ያፈራችው ንብረትም ሆነ ገንዘብ ከጋብቻችን ውጭ ሆኖ አብረን በሆንበት ጊዜ ብቻ የምናፈራው ገንዘብ በሁለታችን እኩል የሆነ ንብረትነት እንዲኖረው ይቀል ዘንድ የራሴን ንብረት ብእንዲህ ሁኔታ ስዘረዝር የእርሷንም በሽማግሌ ፊት እንድትዘረዝርልኝ በትህትና እጠይቃለሁ የኔ አነስተኛ ተመኗ አርባ ሺ ሪያል የሆነ የቤት መኪና በባንክ ንብረቱን መዘርዘር ቀጠሰ በእውነቱ ንብረቱን አባዝቶ ስለካልሲው ሁላ የሚናገር ሰው ሳይሆን አይቀርም እኔ ኑሮን ፈርቹ ሕይወቴን ሕልሜን እርሱው እንደፈለገ እንዲያንቀሳቅስ ልፈቅድለት ስዘጋጅ አርሱ በንብረቱ ጠረጠረኝ እዛው በሽማግሌዎች ፊት ጋብቻዬን መሰረዜን አስታወቅኩ ጁ ች ጁ ጁ ጁ ጁ ከዚያን ቀን በኋላ የቅድስት ምክር ጭቅጨቃ ሆነና እየሰለቸኝ መጣ ስንት አጠያይቃ ያመጣችልኝን ስራ ደክሞኛል ብዬ ሳልቀበለው ቀረሁ በዚህ መሀል ወደ መረጥኩት የህይወት መንገድ ይበልጥ የሚያበረታኝ ወሬ ዱብ አለ ጀሚላ ለቅድስት ስራዋ ቦታ ደውላ ጥሩ ቦታ ማግኘቷንና ከነአይሻ ጋር የነበረች ጊዜ የነበራትን ፍሪጅና ልብሶቿን ሁለ ነገሯን ለሳልዋና አይሻ እኩል እንዲካፈሉ ብላ መልዕክት ነገረቻት እኔና ቅድስት መልዕክቱን ለነ አይሻ ልንነግር የፄድን ጊዜ የጀሚላን ቦታ ለመተካት ሀሳብ መጣልኝ በዚያ ሰሞን የጀሚላ ሁኔታ በጣም ያስገረማት ሳልዋ ወሬ ለማጠናከር የአበሻ ፀጉር ሰሪዋ ቤት ፄዳ ብዙ ብዙ ወሬ ይዛልን መጣች «ስለ ፀጉር ሰሪዋ ሴት እንዴት ሀሳብ መጣልሽ። » «ላ አንቺ ወጣትና ጠንካራ ነሽ በአንድ ኩላሊት መኖር ትችያለሽ ብቻ ተናደሽ በማንወደው መንገድ ከቆምሽ ፖሊስ ህግ ምናምን ጥሩ አይሆንም ለኛ በጥቂቱ ላንቺ ግን በትልቁ እኛ ከዚች ወንጀል ምንም ሳንነካ እንወጣለን አንቺ ግን ሁሉን ነገር ትከስሪአለሽ ኩላሊትሽን የምንከፍልሽን ገንዘብ ብሎም አፅምሮሽን ኩላሊትሽን የሰጠሻት ሴት በገንዘቡ ብዙ ነገር የሚያናጋ የእጅግ ሀብታምና ታዋቂ ሰው ሚስት ናት ብዙ ደምም ሰጥተሻታል ህይወት ሰጠሻት ማለት ነው ታዲያ ለዚህ ውለታሽ ባሏ የተቀረ ህይወትሽን ሊቀይርልሽ ቃል ገብቷል ስለሄደው የአካል ክፍልሽ እአርሺ አይመለስም ስለሚመጣው ህይወትሽ አስቢ አንቺ ካሁን ወዲያ የሚያደክም ስራ እና አድካሚ የህይወት ውጣ ውረድ መሸክሙ ቀላል ላይሆንልሽ ይችላል ጤንነትሽን ለመጠበቅ የተደላደለ ገንዘብ ያስፈልግሻል ጥሩ ልጅ ሆነሽ የተወሰኑ ወረቀቶች ላይ መፈረም ብቻ ችግርሽን ይወጣልሻል እንዳልኩሽ ጥሩ ልጅ ሁፔኔ ትተውኝ ወጡ ስለምን ላልቅስ።