Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ጓድ ማለት ማን ነው። ከላይ የተዘረዘረው ጥፋት ለሞት የሚያበቃ ነበር። ይህ ጥያቄ እስከ አሁን ድረስ እያነጋገረ ያለ ጉዳይ ነው አንዳንድ ወገኖች እንደሚሉት የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሚስተር ጂሚ ካርተር ሁለቱን ወገኖች ለማሸማገል የጀመሩት ጥረት የኢህዲሪን መንግሥት አዘናግቶት ሊሆን ይችላልያም ሆነ ይህ ሰራዊቱ የማጥቃትን ስትራቴጂ እርግፍ አድርጎ ትቶ በሰፈሩ ተገድቦ እንዲቆይ መደረጉ ለታላቁ ለሽንፈት አሳልፎ እንደሰጠው ይታመናል የኢህዲሪ መንግሥት በኤርትራ ምድር እጅግ ወሳኝ የሆነ ውድቀት የሚባለው በምጽዋ የደረሰው ነው እንጂ በአፋቤት የታየው አይደለም የምጽዋው ውድቀትስ ምን ይመስል ነበር።
በማለት ጮኸዋል የራዛ ዘመቻ ዓላማ የጀብሃና የሻዕቢያን ሀይል ከጎጃም ጎንደር ወሎ እና ትግራይ በተውጣጡ ገበሬዎች መምታት ነበር እነኛ ገበሬዎች በቂ ስልጠናና የዝግጅት ጊዜ ሳይወስዱ ነበር የዘመቱት ገበሬዎቹ የታጠቋቸው መሳሪያዎችም አልቤን መውዜር ቺኮዝ ምንሸር ዲሞትፈር የመሳሰሉት ኋላቀር ጠመንጃዎች ነበሩ በቂ ጥይትም ሆነ የስንቅ አቅርቦት አልነበራቸውም ከሁሉም የሚያሳዝነው ደግሞ እነኝህ የውትድርና ልምድ ጨርሶ የሌላቸውን ገበሬዎች በደፈጣ ጥቃት በተካነው የጀብሃና ሻዕቢያ ሰራዊት ላይ ማዝመቱ ነበር እነዚህ ገበሬዎች ለዘመቻቸው እንዲነሳሱ ጀብሃ እና ሻዕቢያን አባርረው የማረኩት ንብረት በጠቅላላ የናንተ ይሆናል ወንበዴዎቹ የለቀቁት መሬትም የናንተ የግል ንብረት ስለሚሆን እንደሻችሁ ትገለገሉበታላችሁ የሚል ቃል ተሰጥቶአቸው ነበር ዘማቾቹ በሶስት ግንባር ነው ወደ ኤርትራ የነጎዱት አንደኛው ቡድን ተነስቶ ተከዜን ተሻግሮ ከኡምሀጀር ጀምሮ ጀብሃን እየመታ ተሰነይ እንዲገባ ነበር የታሰበው ሁለተኛው ቡድን ከኢንቲጮ ተነስቶ መረብን በመሻገር ሻዕቢያን እየመታ እስከ ሰንአፌ እንዲደርስ ነበር የተፈለገው ሶስተኛው ቡድን ከሸሬ እንዳሥላ በመነሳት በጾረና በኩል ወደ መንደፈራ እንዲዘምት ታስቦ ነበር ሁለቱ ሽምቅ ተዋጊዎች ወደነርሱ የሚጎርፈውን የገበሬ ማዕበል ለመመለስ ምሽግ መቆፈር አላስፈለጋቸውም ቦታ ቦታ ጠብቆ በአርፒ ጂ ሮኬትና በመትረየስ መምታት ብቻ በቂአቸው ነበር በዚህም አኳኋን ከሁመራ የተነሳው ዘማች ሀይል ገና ተከዜን እንደተሻገረ በኢንቲጮ በኩል የዘመተው ከትግራይ ድንበር ሳያልፍ በሮኬትና በመትረየስ ተደበደበ ይህ ቀረሽ የማይባል የኢትዮጵያዊያን እልቂት ተከሰተ ብዙዎች ተማረኩ ከእልቂትና ምርኮ የተፈረው መንገድ ጠፍቶት ሲዳከር በውሃ ጥም አለቀ ጥቂቶች በጥንካሬ ወደ ትግራይ ከተሞች ለመድረስ ቢችሉም ከደረሰው ውድቀት አንጻር ቁጥራቸው ይህ ነው አይባልም በሁለቱ ቡድኖች ላይ የደረሰውን እልቂት ያስተዋለው ወታደራዊ ደርግ ሶስተኛው ቡድን ከሽሬ ሳይንቀሳቀስ ወደመጣበት እንዲመለስ ሸኘው በዘመቻው ተሳትፈው በሰላም ለተመለሱ ገበሬዎች የያዙት ጠመንጃ በነጻ ተሰጥቶአቸዋል በ እዚህ ግባ የሚባል ወታደራዊ እንቅስቃሴ በኤርትራ ምድር አልተካሄደም የዚህም ምክንያት በሶሻሊስት ሀገራት አሳሳቢነት በግንባሮቹና በደርግ መንግሥት መካከል ሰላማዊ ድርድሮች መካሄድ መጀመራቸው ነው በዚህም መሰረት የቀድሞዋ ምስራቅ ጀርመን በህዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ ሻዕቢያ እና በደርግ መንግሥት መካከል የሚካሄደውን የሰላም ድርድር አመቻችታለትች በውይይቱ ላይ የሻዕቢያው መሪ አሳያስ አፈወርቂ ተሳፏል በተጋድሎ ሓርነት ኤርትራና በደርግ መንግሥት መካከል የተካሄደውን ድርድር የሸመገለችው ደግሞ ሶቪየት ህብረት ነበረች አብደላ ኢድሪስ ጀብሃን በመወከል ሞስኮ ተገኝቷል ይሁንና ሁለቱም ውይይቶች ፍሬ አላፈሩም በሌላ በኩል በዚያ ዓመት የተጀመረው የኢትዮሶማሊያ ጦርነት ደርግ ሙሉ ትኩረቱን በኦጋዴን ላይ ብቻ እንዲያደርግ ስላደረገው በኤርትራ ምድር የነበረውን ወታደራዊ ዘመቻ እንዲያቀዘቅዝ ምከንያት ሆኗል የሶማሊያው ጦርነት በ አጋማሽ ላይ በድል ሲጠናቀቅ የደርግ መንግሥት ከድል አድራጊው ጦር ግማሽ ያህሉን ሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት በማለት አደራጀ ይህ ሺህ ያህል የሰው ሀይል ያቀፈው ትኩስ ሀይል የምስራቁ ድል በሰሜንም ይደገማል የሚል መፈከር በመጨበጥ ወደ ኤርትራ ምድር ተመመ ጦር ሰራዊቱ በአምስት ግብረሀይሎች ተከፋፍሎ ነበር ወደ ኤርትራ የዘመተውየግብረሀይሎቹ መነሻና ግብ እንደሚከተለው ነበር ሀ ኛ ግብረ ሀይል ከሁመራ ተነስቶ በኡምሐጀር በማድረግ ተሰነይ ይገባል ለ ኛ ግብረ ሀይልቡ ከሽሬ ተነስቶ በሸምበቆ አድርጎ ባሬንቱን ከጀብሃ ያስለቅቃል ከዚያም ከኘ ግብረኃይል ጋር ይጋጠምና ወደ አቆርዳት ይገባል ሐኛ ግብረ ሀይልሀ ከመረብ ድልድይ ተነስቶ አዲኳላን በማስለቀቅ አረዛ ከተማ ይገባል መ ኛ ግብረኃይልለ ከገርሁ ሰናይ ተነስቶ በጾረና በኩል በማድረግ ከዘላአምበሳአስመራ የሚያደርሰውን ጎዳና ማጽዳት ሠ ኛ ግብረ ኃይል ከአስመራ ተነስቶ ኃይሉን በሶስት አቅጣጫ በማነቃነቅ በዙሪያው ያለውን የጠላት ኃይል ወደ ውጪ በመግፋት አረዛ ላይ ከኛሀ ደቀምሐረ ላይ ከለ ከረን ላይ ከኛ ግብረኃይሎች ጋር መገናኘት ነበር ረ ኛ ግብረሀይል ምጽዋን ሙሉ በሙሉ ከጠላት ከበባ ካላቀቀ በኋላ ኃይሉን ለሁለት ከፍሎ አንዱ ወገን ዶጋሊን ተቆጣጥሮ ከምጽዋ አስመራ መንገድን ነጻ ማድረግ ሌላው ወገን ደግሞ በመርከብ ወደ መርሳ ጉልቡብ ተጉዞ አልጌናን መያዝና ከናቅፋ ጀርባ መግባት ነው በሁሉም ግንባሮች የዘመቱት ግብረሀይሎች የተሰጣቸውን ግዳጅ በከፍተኛ መስዋእትነት ፈጸሙ ሻዕቢያና ጀብሃም በጦር አውሮፕላኖች የተጠናከረውን የሁለተኛ አብዮታዊ ሰራዊት ጥቃት ለመመከት በብርቱ ሞከሩ በተለይ ኤላበረድ በምትባለው አነስተኛ ከተማ አቅራቢያ የሻዕቢያ ሀይሎች ከአብዮታዊ ጦር ሰራዊት ጋር ለሶስት ተከታታይ ቀናት የዘለቀ ከባድ ውጊያ አካሄዱ ሆኖም የጦር ሰራዊቱ ጥቃት ከአቅማቸው በላይ በመሆኑ ከረን የተሰኘችውን ቁልፍ ስትራቴጂካዊ ከተማ ለመልቀቅ ተገደዱ አብዮታዊ ሰራዊት ግብሀይሎችም በአማጺያኑ የተያዙትን የኤርትራ ከተሞች ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠሩ ሆኖም የተሰጣቸውን የመጨረሻ ግብ ማሳካት አልቻሉም ሻዕቢያና ጀብሃን ከናቅፋ ማባረር እንዲህ በቀላሉ የሚደረስበት ሆኖ አልተገኘም ስለዚህ ሰራዊቱ በተጨማሪ ስልጠናና ትጥቅ እስኪደራጅ ድረስ ይዞታውን እያጠናከረ እንዲቆይ ተደረገ በ መጨረሻ ገደማ ሁለት አነስተኛ ዘመቻዎች ተደርገዋል በ አጋማሽ ላይ አብዮታዊ ሰራዊት ናቅፋ ከሻዕቢያ ለማስለቀቅ ከባድ ዘመቻ ከፈተ ሆኖም ሻዕቢያ በሰላዮቹ አማካኝነት ያገኘውን መረጃ በመጠቀም ተዋጊዎቹን በደፈጣ ስልት በማሰለፉ ከተቃጣበት ጥቃት ተረፈ ይባስ አብዮታዊ ሰራዊቱ ተዘናግቶ በሰፈሩ ሲከትም ሻዕቢያ የተበታተነውን ሀይሉን በማሰባሰብ ድንገተኛ ጥቃት ከፈተበት በአብዮታዊ ሰራዊት ላይ ብርቱ ጉዳት ደረሰበት የሰፈረበት የናቅፋ መሬት ለጥቃት እንዳጋለጠው በመታመኑ ወደ አፋበት እንዲያፈገፍግ ተደረገ ሻዕቢያም የሚያፈገፍገውን ጦር እየተከላከለ ወጋው ከሶማሲያ ወረራ ወዲህ ታላቅ የተባለውን የመጀመሪያ ድሉን ተጎናጸፈ በምዕራብ ኤርትራ የነበረው ሁኔታ ደግሞ ከዚህ ይለያል በከፍል ሰባት እንደገለጽኩት ጀብሃ በርሱ ላይ የዘመተውን ብዙ ሺህ ሰራዊት ከመሸሸ ይልቅ በመጋፈጡ ሀይሉን አስጨርሷል ለከፉ ቀን ይሆነኛል ብሎ የያዘው የባርካ ቆላ ሜዳማ በመሆኑ ከሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት ጥቃት ሊያድነው አልቻለም ስለዚህ ያለው አማራጭ ልክ እንደ ሻዕቢያ ወደ ሳህል መሸሽ ነበር ከ ድረስ በነበሩት ዓመታት የተደረጉት ጦርነቶች እዚህ ግባ የሚባሉ አልነበሩም ሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት ሻዕቢያ ከናቅፋ ተራሮች አንዳይወርድ በማድረግ ብቻ ተወስኖ ነበር በሌላ በኩል በነኝህ ዓመታት ሻዕቢያና ጀብሃ በመካከላቸው የነበረውን ስምምነት አፍርሰው መተላለቅ በመጀመራቸው ሻዕቢያ ጀብሃን ከኤርትራ ምድር በማባረር ወደ ሱዳን እንዲገባ አድርጎታል ጀብሃን በመምታቱ ረገድ ህወሐትም ከሻዕቢያ ጋር በትብብር ሰርቷል የኤርትራ አማጺያንን ለማጥፋት ከተደረጉ ዘመቻዎች መካከል ብዙ የተባለለት ነው የቀይ ኮከብ ዘመቻ ታዋቂ የጦር ጠበብት እየደጋገሙ አውስተውታል በጋዜጣና በሬድዮ ብዙ ተለፍፎለታል አጀማመሩም ሆነ አፈጻጸሙ ትንግርተኛ መሆኑ እስከ ዛሬ ድረስ ብዙዎችን እያነጋገረ ነው ዘመቻው የተካሄደበት ለየት ያለ ድባብና በርሱ ሳቢያ የተፈጠረው ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ኦሮማይ የተሰኘው ተወዳጅ ድርሰት እንዲጻፍ ምከንያት ሆኗል ያ ዘመቻ በኦፊሴል የቀይ ኮከብ ሁለገብ አብዮታዊ ዘመቻ ተብሎ ነበር የተሰየመው የዘመቻው ዓላማዎችም ሁለት ናቸው አንደኛው ሻዕቢያን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መደምሰስ ነው ሁለተኛው በጦርነቱ የፈራረሱ መሰረተልማቶችን መገንባት ነው ለዘመቻው ቀይ ኮከብ የሚል ስም የተሰጠው ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለማሪያም የአሜሪካ ባህር ሀይል ብሩህ ኮከብ ሀን በሚል ስም በቀይ ባህር ላይ ላደረገው ወታደራዊ ልምምድ ምላሽ መሆን አለበት በማለት ባደረጉት ውሳኔ መሰረት እንደሆነ በወቅቱ የኤርትራ ከፍለሀገር ኢሠፓአኮ ተጠሪ የነበሩት ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ቀይ እምባ ፐ በተሰኘው መጽሐፋቸው ገልጸዋል የቀይ ኮከብ ሁለገብ አብዮታዊ ዘመቻ ይፋ የተደረገው በሀገር አቀፍ ደረጃ በታወጀ ልዩ አዋጅ ነው ዘመቻውን በበላይነት የሚያስፈጽም ከፍተኛ ስልጣን የተሰጠው ሀገር አቀፍ ምከር ቤት ተቋቁሞለታል የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም ሲሆኑ ዋና ጸሓፊው ኤርትራዊው አቶ አማኑኤል አምደሚካኤል ነበሩ የሀገሪቱ ምርጥ ምሁራን የተሳተፉበትና ድርጅታዊ ሀይሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተሟላለት የምከር ቤቱ ጽሕፈት ቤትም አስመራ ላይ ተሰይሞም ነበር ለዘመቻው ማስፈጸሚያ ከሁለት ቢሊዮን ብር የሚበልጥ በዛሬው የምንዛሬ ተመን ወደ ሀያ ቢሊዮን ብር ያህል የሚሆን በጀት ተመድቦለታል ዘመቻውን ለማስፈጸም በሜልም ከሊቀመንበር መንግሥቱ ጀምሮ ሀገሪቷ ያሏት ከፍተኛ ወታደራዊና የሲቪል ባለስልጣናት አስመራ ላይ ከትመዋል የቀይ ኮከብ ሁለገብ አብዮታዊ ዘመቻ በይፋ የተከፈተው ጥር ነበር የዘመቻውን መከፈት በሚያበስረው ጉባኤ ላይ ከሁሉም የኢትዮጵያ ከፍለ ሀገር የተወከሉ የሀገር ሽማግሌዎች ሙያተኞች መለዮ ለባሾች የገበሬ ተወካዮች ወዘተ ተሳትፈዋል ሊቀመንበር መንግሥቱ ጉባኤውን የከፈቱበት ንግግር በሬዲዮ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ በቀጥታ ተላልፏል የአስራ አራቱ ከፍለ ሀገር ተወካዮችም በጉባኤው ላይ ንግግር አድርገዋል ጉባኤው ጥር ሲጠናቀቅ ሰባት ነጥቦች ያሉት የአስመራ ማኒፌስቶ በአቋም መግለጫ መልክ ይፋ ተደርጓል የቀይ ኮከብ ዘመቻ ጉባኤ በተከፈተበት ማግስት በቀይ ባህር ዳርቻ በምትገኘው ጉርጉሱም የተባለች ሰርጥ ላይ የተዘጋጀው የምጽዋ ኤክስፖ በሊቀመንበር መንግሥቱ ተመርቋል ዶጋሊ ላይ ሊገነባ ለታቀደው የራስ አሉላ መታሰቢያ ሀውልት የመሰረት ድንጋይ ያስቀመጡትም ሊቀመንበር መንግሥቱ ነበሩ በምጽዋ ከተማ በሚገኘው አጹ ካሌብ አዳራሸ ታሪካዊው የምጽዋ ሲምፖዚየም ተካሂዷል በአስመራና በምጽዋ ከተሞች የሚገኙ በርካታ ፋብሪካዎችም ተጠግነው የማምረት ተግባራቸውን እንዲጀምሩ ተደርገዋል ከምጽዋአቆርዳት የተዘረጋው የባቡር መስመርም አገልግሎት መስጠት ጀምሯልይህ ሁሉ ከተገባደደ በኋላ ነው ወታደራዊው ዘመቻ የተካሄደው የቀይ ኮከብ ወታደራዊ ዘመቻ በአራት ግንባሮች ነበር የተከናወነው በብርጋዴር ጄኔራል አበራ አበበ የሚታዘዘው ውቃው እዝ በአልጌና በኩል በሰሜናዊ ቀይ ባሕር ጠረፍ ከናቅፋ ጀርባ እንዲያጠቃ በብርጋዴር ጄኔራል ውበቱ ጸጋዬ የሚታዘዘው ናደው እዝ ከከረን ጀርባ ወደ ናቅፋ በር በከርከበት ግንባር ከናቅፋ ደቡባዊ ምሥራቅ በኩል እንዲያጠቃ በብርጋዴር ጄኔራል ቁምላቸው ደጀኔ የሚታዘዘው መብረቅ እዝ በቃሮራ ግንባር ከናቅፋ ሰሜን ምዕራብ እንዲያጠቃና የሻዕቢያን መውጫ እንዲዘጋ በብርጋዴር ጄኔራል ከበደ ጋሼ የሚታዘዘው መከት እዝ የአስመራን ዙሪያ እንዲያጥር የሚል ትዕዛዝ ተቀብለው ለውጊያ ዝግጁ ሆነ የካቲት ጎህ ከመቅደዱ በፊት በሁሉም ግንባሮች ወደ ናቅፋ የመጠጋት እንቅስቃሴ ተጀመረየናቅፋ ተራሮች በቢኤም እና በሞርታር ተደበደቡ ከሰማይ በሚወርዱ የአውሮፕላን ቦንቦች ታረሱ ሮኬቶችና ካሊበሮች ተወናጨፉ ናቅፋ እሳተ ጎመራ የፈነዳባት መሰለች ሻዕቢያ መጥፊያው የተቃረበ መሆኑን ገምቶ ከናቅፋ ምሽጉ ሊወጣ ሲሰናዳ በሁሉም አቅጣጫዎች ዝግ ሆነበት ስለዚህ ተራሮቹን የሙጥኝ ብሎ መከላከሉን ቀጠሰለ የእግረኛና ሜካናይዝድ ውጊያ እንዲጀምር የታዘዘው በሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ የተሰለፈው መብረቅ እዝ ነበር ይሁን እንጂ እዙ በታቀደለት ሰዓት ባለመንቀሳቀሱ ሻዕቢያ በርቀት ያሉ ሀይሎቹን እንዲያሰባስብ ጊዜ ሰጠው በሌላ በኩል ለዚሁ የመብረቅ እዝ ግንባር ቀደም ሆኖ የማጥቃት ግዳጅ የተሰጠው ኛ ተራራ ክፍለጦር በብቃቱ እንደተጠበቀው ሆኖ አልተገኘም ከፍለጦሩ በተያዘለት አቅድ መሰረት ወደ ናቅፋ ተራሮች ምዕራባዊ ከፍል ተጠግቶ ሻዕቢያን ማባረር አቃተው ይባስ ብሎም ጠላት በሰራለት ቀለበት ውስጥ ገብቶ ተከበበ ሻዕቢያም ባለ በሌለ ኃይሉ ተረባረበበት የተራራ ክፍለ ጦርም ተፍረከረከ ሺዎች በሜዳ ላይ እንደ ቅጠል ረገፉ የውቃው እና የናደው እዞች የተሻለ ጀግንነት አሳይተው ከናቅፋ ስምንት ኪሎሜትር ርቀት ላይ ደረሱይሁንና ባልታወቀ ምከንያት በተሰጠ ትዕዛዝ እንቅስቃሴአቸው ተገታ ከዚያ በኋላ እንንቀሳቀስ ቢሉ የማይቻል ነገር ሆነ ሻዕቢያ ተዋጊዎቹን ከያሉበት አሰባስቦ ወደ ኋላ ይገፋቸው ጀመር ለሶስት ተከታታይ ቀናት ባደረገው መልሶ ማጥቃት በአፋቤት ከርከበት ግንባር በዘመተው ናደው እዝ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አደረሰ ሺዎች ሙትና ቁስለኛ ሆኑ በትልቅ ሞራልና የድል ጉጉት የተጀመረው የቀይ ኮከብ ዘመቻም በከፍተኛ ሽንፈት ተፈጸመ የውቃውና የናደው እዞች ከናቅፋ አጠገብ ደርሰው እንዲቆሙ የተደረገበት ምከንያት እስከዛሬ ድረስ በግልጽ አይታወቅም ሻለቃ ጌታቸው የሮም በጻፉት መፅሐፍ አንድ ከፍተኛ የኢሠፓ ባለስልጣን ሻዕቢያ እያዘናጋችሁ ሊፈጃችሁ ስለተዘጋጀ መቆም አለባችሁ የሚል ትዕዛዝ ስለሰጠ ነው ይላሉ ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ በበኩላቸው የጦር ሀይሎቹ መዋጋት ያቆሙት ናቅፋን የመያዙ ተግባር ሊቀመንበር መንግሥቱ ረጅም ዕድሜአቸውን ባሳለፉበት አንበሳው ሶስተኛ ከፍለ ጦር እንዲፈጸም ስለተፈለገ ነው በማለት ጽፈዋል ኮሎኔል መንግሥቱ ግን ይህንን አባባል በከፍተኛ ቁጣ አስተባብለዋል ከሁሉም ጦሮች ቀድሞ ናቅፋ የደረሰውና ያለቀው ሶስተኛ ከፍለጦር ነው በማለትም ተከራከረዋል ለዘመቻው አጠቃላይ ውድቀት መንስኤ የሆነው ምክንያትም በታሪከ ጸሐፊዎችና በወታደራዊ ጠበብቶች ስምምነት አልተደረገበትም ይሁንና አቶ ገስጥ ተጫኔ ዘነበ ፈለቀ በጻፉት ነበር የተሰኘ መጽሐፋቸው ውስጥ የሰነዘሯቸው ነጥቦች ብዙዎችን የሚያስማሙ ይመስሰላሉ አነርሱም የመብረቅ እዝ በተሰጠው ሰዓት መሰረት ግዳጁን አለመፈጸሙ ለኤርትራ መሬት እንግዳና ባዳ የሆነውና በቅርብ ጊዜ ከማሰልጠኛ የወጡ ሀይሎች የተሰባሰቡበት ኛው ተራራ ክፍለጦር ግንባር ቀደም መቺ ሀይል ሆኖ ወደ ናቅፋ እንዲዘምት መደረጉ ሊቀመንበር መንግሥቱ ለድል በመቸኮላቸው የውጊያው እቅድ ሲከለስ ከወታደራዊ አዛች የተሰጡትን የእርማትና የማሻሻያ ሐሳቦች ጨርሶ ለመቀበል ፈቃደኛ አለመሆናቸው ለምሳሌ ጄኔራል አበራ አበበ ኛው ተራራ ክፍለጦር አስተማማኝ ባለመሆኑ ግዳጁ ለሌላ ጠንካራ ከፍለ ጦር እንዲሰጥ ያቀረቡትን ሐሳብ ጨርሶ ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመሆናቸው የእዞቹ አዛች በእቅዱ ሳያምኑበት ወደ ውጊያ የገቡ መሆናቸውና ሌሎችም ምክንያቶች ናቸው የቀይ ኮከብ ዘመቻ በውድቀት ከጨነገፈ በኋላ የውድቀቱ መንስኤ ተጠንቶ ለውሳኔ እንዲቀርብ ታዘዘ በዘመቻው የውጊያ ኢኒስፔከሽን መምሪያ ሃላፊ የሚመራ ቡድን የመብረቅ እዝ ወደ ሚገኝበት ቃሮራ ግንባር ተላከ ቡድኑ ማጣራቱን ካከናወነ በኋላ የኛው ተራራ ከፍለ ጦር አዛዥ የነበሩት ኮሎኔል ውብሸት ማሞ እና የከፍለጦሩ ኛው ብርጌድ አዛዥ የሆኑት ሌኮል ስለሺ አስፋው የውድቀቱ ተጠያቂዎች ናቸው ተባሉ ሁለቱ መኮንኖች በልዩ ትዕዛዝ ከተቋቋመ የጦር ፍርድ ቤት ፊት ቀርበው በተላለፈባቸው ፍርድ መሰረት ኮል ውብሸት ማሞ ተረሸኑ ሌኮል ስለሺ አስፋው ደግሞ ማዕረጋቸውን ተገፍፈው ወህኒ ወረዱ የመብረቅ እዝ ዋና አዛዥ የነበሩት ብርጋዴር ጄኔራል ቁምላቸው ደጀኔ ወደ አስመራ ተጠርተው በቁም እስረኛነት ለረጅም ጊዜ ተቀመጡ አንድ ዓመት ሙሉ ዝግጅት የተደረገበት የቀይ ኮከብ ዘመቻ በዚሁ መልክ ነበር የተደመደመው ሁለት ቢሊዮን ብር በሁለት ወር ተንኖ ውስጥ ተንኖ ቀርቷል ታዲያ ሊቀመንበር መንግሥቱ የባሰ አልህ ይዞአቸው ቀይ ኮከብ ሁለት እና ቀይ ኮከብ ሶስት የተሰኙ ዘመቻዎችን ሞከረው ነበር ውጤቱ ግን ሊሰምርላቸው አልቻለም በርካታ ታዛቢዎች አንደሚሉት ኮል መንግሥቱ ዘመቻው እንዳበቃ የናደውና የውቃው እዞች የናቅፋን ዙሪያ አጥረው እንዲቆዩ ቢደረግና ለኤርትራ ችግር ሰላማዊ መፍትሔ ወደ ማፈላለጉ ቢሄዱ ኖሮ ጥሩ ውጤት በተገኘ ነበር ምከንያቱም ዘመቻው ሻዕቢያንም ከፉኛ ያደከመ በመሆኑ ምናልባት አማጺው ሀይል ሰላማዊውን አማራጭ ይቀበል ነበር ተብሎ ይታሰብ ነበርና የቀይ ኮከብ ዘመቻ በኢትዮጵያ ታሪከ ውስጥ ጥቁር ነጥብ ጥሎ ነው ያለፈው አብዮታዊ ሰራዊት በዘመቻው ማብቂያ ላይ ባጋጠመው ውድቀት ክፉኛ ተናግቷል የወታደሮቹ ስነልቦናም በጣም ተቃውሲሷል ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ማንኛውም የጦር ሀይል ወደ ናቅፋ መጠጋት ይፈራ ነበር ዘማቾች ናቅፋ ከተባለ ሞት ብቻ ነበር የሚታያቸው በአንጻሩ ደግሞ የቀይ ኮከብ ዘመቻ ለሻዕቢያ ሀይሎች ከፍተኛ የሞራል ስንቅ ሆኖአቸዋል ሆነን ከ የሚልቅ አጅግ ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀና በአውሮፕላንና በቢኤም የተጠናከረ ግዙፍ ሰራዊት ድል አድርገናል በማለት እንዲኩራሩ አድርጎአቸዋል ናቅፋንም ምልከት ጽናትና የጽናታችን ምልክት በማለት አእንዲጠሯት መንስኤ የሆናቸው ይኸው ነው ደሄራይይ ሶሉ የቀይ ኮከብ ዘመቻ በሽንፈት ከተቋጨ በኋላ የዘመቻውን መጀመር በከፍተኛ ፕሮፓጋንዳ ያበሰሩት የመንግሥት ሚዲያና ፕሬሶች በዝምታ ተዋጡ በኤርትራ ምድር ስለሚካሄድ ወታደራዊም ሆነ ሰብዓዊ እንቅስቃሴ ደፍሮ የሚናገር ጠፋ የቀይ ኮከብ ዘመቻም ይፋዊ ባልሆነ መንገድ በሰኔ ተሰረዘ የዘመን አቆጣጠሩ እንደ አውሮጳ ቀመር መሆኑን አትርሱን አንዳንድ ጸሐፍት ዘመቻው እንደታቀደው በድል ቢደመደም ኖሮ ሻዕቢያ ከኤርትራ ምድር ይነቀልና ኤርትራም በማያሻማ ሁኔታ የኢትዮጵያ አካል መሆኗ ይረጋገጥ ነበር ይላሉ ሌሎች ግን ይህንን አባባል ይቃወማሉ የኤርትራ ችግር በሰላማዊ መንገድ እስካልተፈታ ድረስ የሻዕቢያ መጥፋት ብቻውን የኤርትራን ኢትዮጵያዊነት አያረጋግጥም በማለትም ያከላሉ ታዲያ ለችግሩ ሰላማዊ መፍትሔ ለማስገኘት የተደረገው ጥረት በጣም አነስተኛ ነበር ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለማሪያም ከወታደራዊ እርምጃ በስተቀር የሰላሙን መንገድ መከተልን አንደ አማራጭ አልወሰዱትም አንዳንድ ከፍተኛ የደርግ ባለስልጣናት ለችግሩ ሰላማዊ መፍትሔ ለማስገኘት በራስ ተነሳሽነት ያደረጉት ጥረት ከግብ ሳይደርስ የቀረው ሊቀመንበር መንግሥቱ ችግሩን በወታደራዊ መንገድ ብቻ ለመፍታት በመወሰናቸው እንደሆነ ይነገራል ለምሳሌ የቀድሞው የሀገርና ህዝብ ደህንነት ሚኒስትር ኮል ተስፋዬ ወልደሥላሜ በግላቸው ያደረጉት የሰላም ጥረት በሊቀመንበሩ ግትርነት እንደተሰናከለባቸው በምሬት ተናግረዋል በመጋቢት ወር አንዳንዶች ጸጥተኛው ዘመቻ በማለት የሚጠሩት ወታደራዊ ኦፕሬሽን ተጀምሮ ነበር ዘመቻው ጸጥተኛ ተብሎ የተጠራው በህዝብ ሚዲያ ምንም ዓይነት ቅስቀሳ ስላልተደረገለት ነው በዚህ ዘመቻ የተካፈለው የወታደር ብዛት በቀይ ኮከብ ጊዜ ከነበረው እጅግ በጣም ያንሳል የዘመቻው ትኩረትም ከከረን ከተማ በስተሰሜን ያለችው ሐልሐል የተሰኘች ስትራቲጂካዊ መንደር ነበረች ሐልሐል በ የጀብሃ እውቅ ኮማንደር የነበረው ዑመር አዛዝ የሞተባት መንደር ናት በዘመቻው የአብዮታዊ ሰራዊት ሀይሎች የሻዕቢያ ተዋጊዎችን አሸንፈው ለማባረር ችለዋል ሆኖም በሻዕቢያ ላይ የደረሰው ሽንፈት የአማጺውን ቅስም ለመስበር የሚችል አልነበረም በ የኢትዮጵያ መንግሥት ሰራዊት በታሪኩ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በከፍተኛ ቁጥር ጨምሮ ነበር የዚህም ምከንያት የብሄራዊ ውትድርና አገልግሎት መታወጁ ነው በዚህ መሰረት የመጀመሪያው ዙር ዘማቾች በጥር ወር ወደ ማሰልጠኛ ጣቢያ ገብተዋል ታዲያ ሻዕቢያም አልሰነፈም መከላከልንና ማጥቃትን እያፈራረቀ የመንግሥት ሰራዊትን አስጨንቆ ይዞአል ይባስ ብሎም የአብዮታዊ ሰራዊት አዛች ባልጠበቁት መንገድ የውጊያ ቀጣናውን ፊት ወደማይታወቅበት የምዕራብ ኤርትራ ቆላማ መሬት አስፋፍቷል በቀድሞ ጊዜ በዚህ ግንባር ጀብሃ እንጂ ሻዕቢያ ተዋግቶ አያውቅም በተለይም በሱዳንና ኤርትራ ድንበር ላይ የምትገኘውን የተሰነይ ከተማን በመቆጣጠር የመንግሥት ሀይሎችን ስጋት ላይ ጥሏል አብዮታዊ ሰራዊት ከተማዋን በአውሮፕላን ደጋግሞ ቢደበድባትም ከሻዕቢያ ሊያስለቅቃት አልቻለም እንዲያውም በአንደኛው ድብደባ ላይ ከፍተኛ የአብራሪነት ልምድ ያካበቱትና በሰሜን አሜሪካ አሪዞና ስቴት የሰለጠኑት እውቁ አብራሪ ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ በሻዕቢያ አየር መቃወሚያ ተመትተው ለመማረከ በቅተዋል እኝህ ኮሎኔል በሻዕቢያ እጅ ለስድስት ዓመታት ከቆዩ በኋላ የደርግ መንግሥት ከስልጣን ሲወገድ በምህረት ተለቀዋል በ የኢትዮኤርትራ ጦርነት ሲቀሰቀስ እንደገና ዘምተው በአየር ላይ በመመታታቸው በሻዕቢያ ተማርከዋል በሌላ በኩል በሀምሌ ወር ሻዕቢያ የጋሽና ሰቲት አውራጃ ዋና ከተማ የነበረችውን ባሬንቱን በመቆጣጠሩ ምዕራባዊው የኤርትራ ከፍል በአብዛኛው ከመንግሥት ቁጥጥር ውጪ ሆኖ ነበር ሻዕቢያ ምዕራብ ኤርትራን በመቆጣጠሩ በሱዳን ካሉት ደጋፊዎቹና ኤርትራዊያን ስደተኞች ጋር እንደ ልብ የሚገናኝበት ሁኔታ ተፈጥሮለታል በተለይ የኤርትራ አርዳታ ማህበር ለኗርቪቨክኬጀቪለ የተሰኘው ድርጅት ሻዕቢያ በሚቆጣጠራቸው ከልሎች ለሚኖሩትና በቱ ድርቅ ለተጎዱ ዜጎቸ እንዳሻው እርዳታ ማቅረብ የቻለው በተሰነይ በኩል ወደ ሱዳን የሚዘልቀው ጎዳና በሻዕቢያ ቁጥጥር ስር ስለዋለ ነው ከዚያ በፊት ጀፒለ ለአርዳታ አቅርቦቱ የሚጠቀመው ከፖርት ሱዳን ወደ ሰሜናዊ ኤርትራ የሚያመራውን ረጅም ጎዳና ነው እንደሚባለው ከሆነ የደርግ ሀይሎች ለኤርትራዊያን ዜጎች አርዳታ እንዳይደርስ አግደው ቆይተዋልአእርዳታው በጀላ በኩል አንዲደርስ የተፈለገው ለዚህ ነው መፖያራንጋጃ አብዮታዊው ሰራዊት ሻዕቢያን ከምዕራብ ኤርትራ ለማባረር በቂ ዝግጅት ሲያደርግ ከቆየ በኋላ በሐምሴ ወር ለመልሶ ማጥቃት ተዘጋጀ በአንደኛው ዙር የብሄራዊ ውትድርና አገልግሎት የተመለመሉ ሺህ ዘማቾችን ጨምሮ ከመቶ ሀምሳ ሺህ የማያንስ የጦር ሰራዊት ለውጊያው ተሰለፈ የዘመቻው ፕላን በሶቭየት ህብረት ሀ ወታደራዊ ኤክስፐርቶች ተዘጋጀ ከሶስት መቶ የማያንሱ ታንኮችና ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎች ዝግጁ ሆኑ ዘመቻውም ባህረ ነጋሽ ተብሎ ተሰየመ ዘመቻ ባህረ ነጋሽ ሻዕቢያን ከምዕራብ ኤርትራ አባርሮ ወደ ሳሕል በረሃ የመመለስ እቅድ ነበረው የዘመቻው እቅድ በመገናኛ ብዙሃን በይፋ ባይታወጅም እንኳ ለዘመቻ በተሰለፈው የሰው ሀይልና በተመደበለት የጦር መሳሪያ ዓይነትና ብዛት ከቀይ ኮከብ ሁለገብ ዘመቻ ጋር ይስተካከላል ሀገሪቷ የነበሯት ምርጥ የጦር መኮንኖችም በአዛዥነት ተሰልፈዋል የዘመቻው የበላይ አዛዥ እውቁ የጦር ሰው ሜጀር ጄኔራል መርዕድ ንጉዔ ሲሆኑ በርሳቸው ስር ሜጄ ደምሴ ቡልቶ ሜጄ አበራ አበበና ሜጄ ረጋሳ ጅማ ተሰልፈው ነበር የአየር ሀይሉ ሜጀር ጄኔራል ፋንታ በላይም ከምርጥ አብራሪዎችጋር ተሰልፈዋል ዘመቻው በታቀደለት ፕሮግራም መሰረት በሰኔ ወር ተጀመረ ሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት በከፍተኛ ወኔ ሻዕቢያን ከምዕራብ ኤርትራ እያባረረ በድል ገሰገሰ ሻዕቢያ በታሪኩ አይቶት የማያውቅ ሀያል ሰራዊት ገጠመው ከ እስከ የሚሆን ተዋጊ አለቀበት በዚህም የተነሳ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ባሬንቱና ተሰነይን ለመልቀቅ ተገደደ ለአስራ ስምንት ወራት የገነባው መከላከያ ስላልሰራለት በስልታዊ ማፈግፈግ ስም ወደ ሳህል በረሃ መሸሸ ግድ ሆነበት አብዮታዊ ሰራዊትም ማንንም ባስደነቀ ፍጥነት እየተጓዘ ከናቅፋ በር ላይ በድጋሚ ደረሰ ሆኖም በዚህኛውም ጊዜ በግልጽ ባልታወቀ ምክንያት ውጊያውን እንዲያቆም ታዘዘ የዘመቻ ባህረ ነጋሽ አፈጻጸም ሲገመገም ውጤቱ ጥሩ ሆኖ በመገኘቱ ሊቀመንበር መንግሥቱ ቀጣይ ዘመቻዎችንም በተመሳሳይ ስልት ለማካሄድ ከውሳኔ ላይ እንዲደርሱ አድርጎአቸዋልለ ይሁን እንጂ በዘመቻው ከፍተኛ የሰው ሀይል መስዋእት ሆኖአል በተለይ ከአስር ሺህ የማያንሱ የአንደኛው ዙር ብሄራዊ ውትድርና ዘማቾች አልቀውበታል በዚህም የተነሳ በኢትዮጵያዊያን የጦር አዛዥች ልብ ውስጥ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል ጄኔራል ፋንታ በላይ እንደተናገሩት ሊቀመንበር መንግሥቱን ከአመራር ለማስወገድ የመፈንቅለ መንግሥት ሴራ ማውጠንጠን የጀመሩት በዘመቻ ባህረ ነጋሽ ወቅት የተከሰተውን የወገን ጦር እልቂት ካዩ በኋላ ነው ጄኔራል ፋንታ ሁኔታውን ሲገልጹት እንዲህ ብለው ነበር ሊቀመንበር መንግሥቱ እኛ ያዘጋጀነውን የውጊያ እቅድ ትተው የኛን ወታደሮች እንደ ጭራሮ በሚቆጥሩት የሶቪየት አዛች የተዘጋጀውን የውጊያ እቅድ በመቀበል ከፍተኛ መስዋእትነት እንድንከፍል አስደረጉን መስዋዕትነት መከፈላችን ካልቀረም ውጊያውን በጀመርንበት ፍጥነት መቀጠል ሲገባን አለምንም ምክንያት እንድናቆም አዘዙን ዘነበ ፈለቀ ነበር ቁጥር ሁለት ገጽ ከዘመቻ ባህረ ነጋሽ ፍጻሜ በኋላ በነበሩት ሁለት ዓመታት በኤርትራ ምድር የሚደረገው ውጊያ ጋብ ብሏል በነዚያ ዓመታት ሁለቱም ተዋጊ ወገኖች አጣዳፊ ለሚሏቸው ጉዳዮች ቅድሚያ ሰጥተዋል በዚህም መሰረት የደርግ መንግሥት የመንደር ምስረታ እና ህገመንግሥት ማርቀቅን ለመሳሰሉ ጉዳዮች ቅድሚያ ሰጥቶ በነርሱ ላይ አተኩሯል ሻዕቢያ ደግሞ ሁለተኛውን ድርጅታዊ ጉባኤ በማዘጋጀቱ ላይ ነበር ያተኮረው ደርግ ያረቀቀው ህገመንግሥት በነሐሴ ወር ጸደቀ ኢህዲሪ የኢትዮጵያ ህዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ተመሰረተ ሊቀመንበር መንግሥቱ በብሄራዊ ሸንጎ ምርጫ ፕጥሬዚዳንት ሆኑ አዲሱ ህገጉመንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ሰኤርትራ ችግር ዘለቄታዊ መፍትሔ እንደሚሰጠውም ተገለጸ ሆኖም ቃል የተገባው ሁሱ የጉባኤ ላይ ልፈፋ ሆኖ ቀረ የጦርነት አማራጭ የመንግሥቱ ብቸኛ ምርጫ መሆኑነ ሳይውል ሳያድር ታወቀ ሆኖም የደርግ አካሄድ የሚያዛልቅ ሆኖ አልተገኘም ከደርግ ይልቅ መንገዱ ቀና ሆኖ የተገኘው በሚያዚያ ባካሄደው ጉባኤ ኢሳያስ አፈወርቂን በዋና ጸሓፊነት ለሰየመው ህዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ ዕቢጸ ነውለሳላሳ ዓመታት በዓላና ናቅፋ በረሃዎች ሲፋለሙ የቆዩት የኤርትራ አማጺያን ለመጨረሻው ግብ የሚያበቃቸውን ወታደራዊ ስልት በተግባር ላይ የሚያውሉበት ጊዜ ተቃርቦ ነበር ቀጣዮቹ ሶስት ዓመታትም የኢትዮጵያና ኤርትራን የታሪከ አቅጣጫ ከመሰረቱ የቀየሩ ታላላቅ ፍልሚያዎች የተካሄዱባቸው ነበሩ እነዚያ ታላላቅ ፍልሚያዎች ምን ይመስላሉ። በሚቀጥለው ከፍል እናያቸዋለን ድሪራ ፖሪታ ዲፀኔ ምጾ በሳህል በረሃ ደቡባዊ ጠርዝ ላይ አፋቤት የምትባል አነስተኛ ከተማ ትገኛለች በዚህች ከተማ እጅግ ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎችን የታጠቀውና በሎጂስቲክስ አቅራቦት የተደራጀው የናደው አዝ ጠቅላይ መምሪያ ይገኝ ነበር የናደው እዝ ከተማዋን ለመቀመጫነት የያዘው በበርካታ መንገዶች መጋጠሚያ ላይ ስለነበረች ነው ተብሎ ይወሳል በተጨማሪም ከተራሮች ወርዶ ወደ መሬት ውስጥ እየገባ የተጠራቀመ ከፍተኛ የከርሰ ምድር ውሃ ስለነበራት በርካታ የውሃ ጉድጓዶች እየተቆፈሩ የሰራዊቱን የውሃ ፍላጎት ለማሟላት በሚያስችል ሁኔታ ስለነበረች ለሰራዊቱ መቀመጫነት እንደተመረጠች ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም በትዝታቸው ውስጥ ገልጸውታል ናደው እዝ በአፋቤት ላይ የተቋቋመው እኤአ በ ግድም ነው ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ከከተማዋ አየተወናጨፈ ወደ ናቅፋ በመገስገስ ሻዕቢያን ለማጥፋት የሚቻለውን ሁሉ አድርጓል በቀይ ኮከብ ዘመቻ ወቅት ከናቅፋ እስከ ሰባት ኪሎሜትር ድረስ በሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ አገላለጽ ሁለት ኪሎ ሜትር ድረስ ተጠግቶ የነበረ ቢሆንም ሻዕቢያን ለመደምሰስ አልተቻለውም በፕሬዚዳንት መንግሥቱና በኢሠፓ ዋና ዋና አለቆች ጣልቃ ገብነት ውጊያውን እንዲያቆም እየታዘዘ ለሽንፈት ተዳርጓል ቢሆንም ሻዕቢያ ከናቅፋ ወርዶ ወደ ደጋማው የኤርትራ ከፍል እንዳይተላለፍ ገትሮ ይዞታል በነገራችን ላይ ሻዕቢያ በ ተሰነይን የተቆጣጠረው በአፋቤት ግንባር በኩል አይደለም የባርካን ቆላማ አውራጃ አቋርጦ ነው ከሰሜን ወደ ደቡብ የዘመተው በናደው እዝ ስር ይገኝ የነበረው ሰራዊት ከአምስት ከፍለ ጦር በላይ ይሆናል ወደ ሃምሳ ሺ የሚሆን የሰው ሀይል ነበረው ምርጥ ምርጥ የጦር መሳሪያዎችን ታጥቋል የነዳጅና የመለዋወጫዎች ከምችቱ በጣም ከፍተኛ ነው በምግብና በሌሎች መሰረታዊ ፍላጎቶችም ይህ ቀረሽ የማይባል እንከብካቤ ይደረግለታል የእዙ አዛዣሦች ተለዋውጠዋል በቀይ ኮከብ ዘመን አዛዥ ሆነው የተሾሙት ጄኔራል ወብቱ ጸጋዬ ነበሩ በ ደግሞ ጄነራል ታሪኩ አይኔ ተሹመውለታል በከፍል አስራ አንድ ጽሑፌ አንደገለጽኩት ለሁለት ዓመታት ያህል በኤርትራ ምድር ጠንከር ያለ ውጊያ አልተደረገም በታሕሳስ እንደኛ አቆጣጠር ህዳር ግን ህዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ ሻዕቢያ ሳይጠበቅ ከባድ የማጥቃት እርምጃ ሰነዘረ የጊጓኛው ከፍለ ጦር እና የኛው ተራራ ከፍለ ጦር ተዋከቡ ለሶስት ቀናት በተደረገ ውጊያ በርካቶች ሙትና ቁስለኛ ሆኑ የየከፍለጦሮቹ የመገናኛና የመረጃ መኮንኖችም ተማረኩ ሻዕቢያ ይህንን ድንገተኛ ጥቃት ያደረሰው የናደው እዝ አዛዥ ጄኔራል ታሪኩ አይኔ ዝውውር አንዲፈቀድላቸው ለመጠየቅ አስመራ ውስጥ በነበሩበት ጊዜ ነው ይህ ጥቃት መድረሱ እንደተሰማ ኮሎኔል መንግሥቱ እብድ ሆኑነ በናደው እዝ የደረሰውን ውድቀት መንስኤ ለማጣራት በሚልም ወደ አስመራ በርረው የሀገሪቱን ዋና ዋና የጦር አዛሦችን ሰበሰቡ በዚያ ስብሰባ ላይ የተገኙት አዛች ሌጄ ተስፋዬ ገብረኪዳን የኤርትራ ከፍለ ሀገር የአስቸኳይ ጊዜ የበላይ አስተዳዳሪ ሜጀር ጄኔራል ኃይለ ጊዮርጊስ ሀብተማሪያም የሀገር መከላከያ ሚር ሜጀር ጄኔራል መርዕድ ንጉሜ የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኤታማፐር ሹም ሜጀር ጄኔራል ረጋሣ ጅማ የሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት ዋና አዛዥ ነበሩ በአስረጅነትም ጄኔራል ታሪኩ አይኔ የናደው እዝ ዋና አዛዥ ጄኔራል ከበደ ጋሼ የመከት እዝ ዋና አዛዥ ተገኝተው ነበር ስብሰባው በዋናነት የናደው እዝ ጥቃትን የሚመረምር ሆኖ ሳለ በመከት እዝ ላይም ሻዕቢያ ከመስከረም እስከ ጥር ወር ድረስ ተደጋጋሚ ጥቃቶችን ያደረሰ መሆኑ ስለተነገረ ነው የእዙ አዛዥ ጄኔራል ከበደ ጋሼ በስብሰባው ላይ እንዲገኙ የተደረገው ስብሰባው ከሞላ ጎደል በመግባባት መንፈስ እየተካሄደ ሳለ ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ጥፋቶችን በጄኔራል ታሪኩ አይኔ ላይ ማላከከ ጀመሩ ጄኔራሉም ለጥፋቱ እኔ ተጠያቂ አይደለሁም እኔ እየተበደልኩ ነው እዚህ ያለሁት ህመም እየተሰማኝ በረሃ ላይ ጥላችሁኝ ተጎድቻለሁ እስከዛሬ ዝውውር ስጠይቅ መቼ ፈቀዳችሁልኝገ። በቀጣዩ ከፍል እንዳስሰዋለን መጋቢት መጋቢት እኩለ ሌሊት በዚያች ደረቅ ሌሊት ሻዕቢያ ሳይጠበቅ የናደውን እዝ ወረረ አብዮታዊ ሰራዊትም ይዞታውን ለማስጠበቅ ተከላከሰ ይሁንና በለስ ሊቀናው አልቻለም ሻዕቢያ ቀደም ብሎ ያገኘውን መረጃ በሚገባ ሊጠቀምበት ስለቻለ የአብዮታዊ ሰራዊትን ማዘዣና የግንኙት መስመሮችን በጣጠሰ ተዋጊ ብርጌዶችን ከእዙ መሀል አስገብቶ በሰራዊቱ ላይ ወደ ውጪ ተኮሰ ከውጪ በኩል ደግሞ ዙሪያውን ከቦ በመትረየስና በከባድ መሳሪያ አዋገደው በዚህም የተነሳ ከእዙ ጠቅላይ መምሪያ ራቅ ብለው የሰፈሩ ከፍለ ጦሮች ወደ መሐል ተመልሰው እገዛ ማድረግ አቃታቸው ሁሉም ከፍለ ጦር በያለበት በራሱ ውጊያ ተጠመደ አብዮታዊ ሰራዊት በዚያ ትንፋሽ በሚያሳጥር ውጊያ ለሶስት ቀናት ከተዋከበ በኋላ ሁሉም ነገር ተበላሸበት መጋቢት መንፈቀ ሌሊት ላይ የናደው እዝ ሙሉ በሙሉ ተናደ የእዙ ምከትል አዛዥ ኮሎኔል ግርማ ጌታነህ ከሶስት የሶቪየት ህብረት የጦር አማካሪዎች ጋር ተማረኩ ዋናው አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ውበቱ ጸጋዬና ዘጠኝ የሶቪየት የጦር አማካሪዎች ከውጊያው አምልጠው ሲሸሹ የወገን ሄሊኮፕተር ደርሶ አነሳቸው ሌሎች ከፍለ ጦሮች ከዋናው ማዘዣ የሬድዮ ግንኙነት እንደተቋረጠባቸው ሲረዱ የውጊያ ቀጣናቸውን እየለቀቁ ወደ ከረን አፈገፈጉ ሻዕቢያም የአፋቤትን ከተማ በእጁ አስገባ የናደው እዝንም ከሙሉ ግምጃ ቤቱ ጋር ተቆጣብጠረ ይህ የናደው ሸንፈት ብዙ ተብሎለታል ብዙም ተጽፎበታል በታወቁ የዓለም ዜና ማሰራጫዎች ግንባር ቀደም ወሬ ሆኖ ተዘግቧል በርካታ የአውሮጳና የአሜሪካ ጋዜጠኞች ጦርነቱ የተካሄደባትን የአፋቤት ከተማ በመጎብኘት ዶከመንታሪ ፊልሞችን ሰርተውበታል የታወቁ የጦር ኤከስፐርቶች ሻዕቢያ በአፋቤት ያገኘውን ድል የቪየትኮንግ ሽምቅ ተዋጊዎች በፈረንሳይ ቅኝ ገዥዎች ላይ ከተጎናጸፉት የዲየን ቢየን ፉ ድል ጋር አወዳድረውታል በአጠቃላይ የናደው ሽንፈት ስለሻዕቢያ የሚያውቁትንም ሆነ የማያውቁትን የውጪ ዜጎች አደገኛ የጎሪላ ተዋጊ ሀይል ነው እያሉ በአድናቆት እንዲመለከቱት የጋበዘ ከስተት ሆኖ አልፏል በሌላ በኩል የናደው ሽንፈት በሀገር ውስጥ ከፍተኛ የፖሊሲ ለውጥ አስከትሏል በናደው ሽንፈት ማግስት የኢህዲሪ መንግሥት በይፋ ያልታወጀ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመላ ሀገሪቱ በስራ ላይ አውሏሷል ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለማሪያም መጋቢት ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ቀርበው በኤርትራ ስለሚካሄደው ጦርነት ተናገሩ ሰፊው ህዝብ ኤርትራን ከመገንጠል እንዲያድናት ጥሪ አቀረቡ መንግሥት በሚመድበው በጀት ብቻ ጦርነቱን ማካሄድ ስላልተቻለ ህዝቡም የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ አለበት በማለት ማሳሰቢያ ሰጡ የአዲስ ዘመን እና የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ጋዜጦች በፊት ገጾቻቸው ጥግ ላይ ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር የሚል መፈክር በቋሚነት ማስነበብ ጀመሩ የኢትዮጵያ ሬድዮም በምሽት ስርጭቱ ከሚያስተላልፈው ዜና ቀጥሎ አንድነት ሀይል ነው ሁሉም ለእናት ሀገሩ ዘብ ይቁም የአባቶቻችንን አደራ አናስደፍርም እና ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር የሚሉ አራት መፈከሮችን በመደበኛነት ማሰማት ጀመረ ኤርትራ በአስቸኳይ ጊዜ አስተዳደር ስር ወደቀች በኤርትራ መሬት የሚደረገው ቁጥጥር እንዲጠብቅ ትእዛዝ ተላለፈ ከፍለ ሀገሩን ከሱዳንና ከቀይ ባህር ጋር የሚያገናኙ መሬቶች ለሲቪል እንቅስቃሴ ተከለከሱ በናደው እዝ ላይ የደረሰው ሽንፈት በአብዮታዊ ሰራዊት ውስጥ ትልቅ ቀውስ መፍጠሩ እርግጥ ነው በዘመኑ የነበሩ የታወቁ ወታደራዊ አዛችም የፍጻሜው መጀመሪያ በማለት ገልጸውታል በጦርነቱ የተሰለፈው አብዮታዊ ሰራዊት ሃምሳ ሺህ ተዋጊዎችን ይዞ ከአስር ሺህ ያልበለጠ ሀይል በነበረው የሻዕቢያ ሰራዊት መሸነፉ በጣም አነጋጋሪ ሆኖ ነበር በሌላ በኩል ሻዕቢያ የጦርነቱን ውሎ አለም አቀፍ ዝና ለማግኘትና የአብዮታዊ ሰራዊት ሞራልን ለመስበር በሰፊው ተጠቅሞበታል የሬድዮና የህትመት አውታሮቹ የሻዕቢያን ሀያልነት የሚያሳይ ፕሮፓጋንዳ እየደጋገሙ ሰርተውበታል ለመሆኑ አስራ አምስት ሺህ ያህል የኢትዮጵያ ወታደሮች ሙት ቁስለኛና ምርኮኛ የሆኑበት የአፋቤት ሽንፈት እንዴት ተከሰተ። በርካታ አስተያየቶች ተሰጥተዋል ከነዚህ ሁሉ ሚዛናዊ መስለው የታዩኝ አቶ ገስጥ ተጫኔ ዘነበ ፈለቀ ነበር የሚል ርዕስ በሰጡት መጽሐፋቸው ያሰፈሯቸው ነጥቦች ናቸው በገስጥ ተጫኔ አመለካከት የአፋቤት ሽንፈት ምክንያቶች የእዙ አዛዥ የነበሩት ጄኔራል ታሪኩ አይኔ መገደላቸውና በርሳቸው ምትከ የተመደቡት ጄኔራል ውበቱ ጸጋዬ የየከፍለጦሮቹን የውጊያ ቀጣና በደንብ ሳያጠኑና ተለዋጭ የውጊያ ስልት ሳይነድፉ ሻዕቢያ ፈጥኖ በማጥቃቱ ሻዕቢያ በታሕሳስ ወር መጀመሪያ በሐበሻ አቆጣጠር ህዳር ወር መጨረሻ ላይ ባደረሰው ጥቃት ከማረካቸው መኮንኖችና የሬድዮ ሰራተኞች ስለናደው እዝ የጠራ መረጃ በማግኘቱ ወደ ውስጥ ዘልቆ በማጥቃት የማዘዣ ጣቢያውን መበተኑ ውጊያው ጠላትና ወገን የተደባላለቀበት ስለነበር ለድጋፍ ሰጪ ከባድ መሳሪያዎች ታንክ እና መድፍ አና ለአውሮፕላኖች ድብደባ አለማመቸቱ የአዙ ጠቅላይ መምሪያ ሻዕቢያ በታህሳስ ወር ያደረገውን ማጥቃት ተከትሎ ወደ አፋቤት እንደሚያመራ በመገመት ለጠንካራ መከላከል ዝግጅት አለማድረጉ ሻዕቢያና ህወሐት የማዘዣ ጣቢያዎችን ቀድሞ መምታታቸው የተለመደ ስልት ሆኖ ሳለ የእዙ ዋና አዛዥ ምናልባት ማዘዣዬ ቢመታብኝ በማለት በሚስጢር የተሰናዳ ተለዋጭ የማዘዣ ጣቢያ አለማዘጋጀታቸው ብሎም ሻዕቢያ ማዘዣቸውን እንዲለቁ ሲያስገድዳቸው እዚህ ነኝ ሳይሉ ግንኙነታቸውን አቋርጠው ወደ ከረን መሸሻቸው የመሳሰሉት ናቸው የአፋቤት ውድቀት ከደረሰ በኋላ የሻዕቢያ አስመራ መግባት የጊዜ ጉዳይ እንደሆነ ሁለቱም ወገኖች ተረድተዋል ኢትዮጵያና ኤርትራ ተነጣጥለው ሁለት ሀገር እንደሚሆኑ መተንበይ የተጀመረውም ከዚያ በኋላ ነበር የደርግ ከፍተኛ የጦር አዛዞች በአፋቤት የደረሰው ውድቀት የወገን ጦር በመዘናጋቱና የሻዕቢያን አቅም አሳንሶ በማየቱ የተከሰተ አንደሆነ ይገልጻሉ በሽንፈቱ ማግስት የሻዕቢያ ሲሳይ የሆነው ግዙፍ የጦር መሳሪያና የቁሳቁስ ከምችት ለአፋቤት ወታደራዊ ጠቀሜታ በተሰጠው የተጋነነ ግምት ሳቢያ የተከሰተ እንደሆነ ያወሳሉ ሻዕቢያ ታንከና ከባድ መድፎች ለመማረከ ችሎ ነበር ከተማዋና ዙሪያዋ በተራሮች የተከበቡ ሆነው ሳሉ አካባቢው ከሚችለው በላይ አምስት ክፍለ ጦር የሚሆን ሰራዊት ተፋፍጎ አንዲቀመጥበት ስለተደረገ ለሻዕቢያ የከባድ መሳሪያ ድብደባ መጋለጡንም ጨምረውይናገራሉ የጄኔራል ታሪኩ አይኔ መገደልም የወታደሮቹን ሞራል እንደሰበረ ያከላሉ ሻዕቢያዎች ግን ይህንን አይቀበሉም የአፋቤት ድል በነርሱ ጀግንነትና የጦር መላ አዋቂነት የተገኘ እንደሆነ ነው የሚናገሩት ጄኔራል ታሪኩ ባይረሸን እንኳ አፋቤትን ከመያዝ የሚገድባቸው ሀይል እንዳልነበረ ይከራከራሉ ወጣም ወረደ ግን ሁሉም በአንድ ነገር ይስማማሉ የአፋቤት ሽንፈት የጦርነቱን አቅጣጫ ከመሰረቱ የቀየረ መሆኑን ያለ ምንም ማመንታት ይቀበሉታል ከዚያ በኋላ የነበረው የአብዮታዊ ሰራዊት ጉዞ በኋላ ማርሽ የመጓዝ ዓይነት ነበር ይላሉ በዚህ ረገድ የተለየ አስተያየት የሰጡት ኮል መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም ብቻ ናቸው እሳቸው እንደሚሉት የአፋቤትን ሸንፈት ያጋነኑት የዓለም ሚዲያዎች ናቸው እንጂ በወቅቱ የሰራዊቱ አቅም አልተነካም ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ለብሄራዊ ሸንጎ ባደረጉት የመጨረሻ ንግግራቸው በናደው እዝ ላይ የደረሰውን ውድቀት ትተው ስለአፋቤት ከተማ ከንቱነት ነበር የተናገሩት በኢትዮጵያ ስታንዳርድ ቀበሌ አይደለም አልማዝ አይቆፈርበት ቤንዚን አይወጣበት ሀገር አይደለ በከ እያሉ ተሳልቀውባታል በፕሬዚዳንት መንግሥቱ አባባል በኤርትራ ምድር እጅግ ወሳኝ የሆነ ውድቀት የሚባለው በምጽዋ የደረሰው ነው እንጂ በአፋቤት የታየው አይደለም የምጽዋው ውድቀትስ ምን ይመስል ነበር። ከልዩ ልዩ ምንጮች በተገኘው መረጃ ላይ በመመርኮዝ ታሪኩን እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ በቀይ ኮከብ ዘመን የአስመራን ዙሪያ ይጠብቅ የነበረው የመከት እዝ የስምሪት ጠገጉ ሰፍቶ ከአስመራ በስተምስራቅ ያሉትንም አውራጃዎች እንዲያካልል ተደርጓል የመጠሪያ ስሙም ኛ ኮር በሚል ተቀይሯል በዚህ ኮር ስር አራት ክፍለ ጦሮችና ሶስተኛው ሜካናይዝድ ከፍለ ጦር ይገኙ ነበር የኮሩ ዋና መምሪያ የሚቀመጠው በአስመራ ከተማ ነው ሆኖም ዋነኛ ትኩረቱ የምጽዋን ከተማ ከጥቃት መከላከል ነው ታዲያ አብዮታዊው ሰራዊት ምጽዋን የሚጠብቃት በከተማው ብቻ በመመሸግ አልነበረም በከተማው ዙሪያ ከ ኪሜ ራዲየስ ላይ የሚገኘውን መሬት በድርብርብ ተዋጊ ከፍለ ጦሮች በማጠር ነው ከተማዋን ከሻዕቢያ ለማትረፍ የተሰናዳው በዚህ መሰረት ከምጽዋ በስተደቡብ ባለችው ዙላ የተሰኘች ጥንታዊት ወደብ አቅራቢያ ሁለት ተዋጊ ብርጌዶች ነበሩ ከምጽዋ ወደ አስመራ በሚወስደው መንገድ ላይ ባለችው ጋህተላይ የተሰኘች መንደር ላይም ሶስት እግረኛ ብርጌዶችና አንድ ሜካናይዝድ ብርጌድ ነበር ከምጽዋ በስተሰሜን ባሉት ሸዒብ እና ሰለሙና የተሰኙ ኩታገጠም መንደሮችም ላይ አራት ብርጌዶችና የኛው ነበልባል ከፍለጦር ቀዳሚ መምሪያ ሰፍሯል በምጽዋ ከተማ ውስጥ ከአራት ብርጌድ የማያንስ ተዋጊ ጦር ነበር በዚህ ግንባር ባጠቃላይ ከ የማያንሱ ታንኮች ተሰልፈው ነበር የኢትዮጵያ ባህር ሀይልም በብዙ ባህር ወለድ ተዋጊዎችና የጦር ጀልባዎች ተጠናከሮ በምጽዋ ዙሪያ ከትሟል የኛው ኮር ዋና አዛዥ የነበሩት ብጄኔራል እንግዳ ወልደአምላክ በግንቦት በተሞከረው መፈንቅለ መንግስት ውስጥ እጃቸውን አስገብተዋል ተብለው በመከሰሳቸው ከቦታው ተነስተው ነበር በርሳቸው ምትክ ጄኔራል ጥላሁን ከፍሌ ተሹመዋል የኛው ሜካናይዝድ ከፍለ ጦር አዛዥ በነበሩት ጄኔራል ካሳዬ ጨመዳ ምትክም ብጄኔራል ዓሊ ሐጂ አብዱላሂ ተተከተው ነበር ይህ ኮር በአዲስ ሁኔታ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ጠንከር ያለ ውጊያ አላጋጠመውም ሻዕቢያ በባህር ወለድ ኮማንዶዎቹ ምጽዋን እየመታ ጦሩን ለማስደንገጥ ያደረጋቸው ሙከራዎችም በባህር ሃይሉ እየከሸፉ ተመልሰዋል የካቲት ጥር ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ሆኖ ነበር ምጽዋ ሰላማዊ አንቅልፏን መለጠጥ ጀምራለች በከተማው የሚገኙ የአብዮታዊ ሰራዊት አባላትም ሀገር አማን ብለው ሌሊቱን በጸጥታ እያሳለፉ ነው የስድስተኛው ከፍለጦር ዋና አዛዥ የነበሩት ብጄኔራል ተሾመ ተሰማ ግን ሁኔታው ከብዶአቸዋል ከምጽዋ በስተሰሜን ባለው የሸኢብ ግንባር ሻዕቢያ አዘናግቶ ጥቃት ይከፍት ይሆናል እያሉ ዘወትር ይሰጉ ነበር ታዲያ በዚያች ደረቅ ሌሊት የፈሩት ነገር ደረሰ ሻዕቢያ እጅግ ጠንካራ የሆኑ ተዋጊዎችን አሰልፎ በሸዒብ ከተማ የነበረውን የኛ ከፍለ ጦር ቀዳሚ መምሪያ አንደወረረ በሬድዮ መልዕከት መጣላቸው ወዲያውኑ ወደ ማዘዣ ጣቢያቸው ሄደው ከግንባሩ አዛዥ ጋር ግንኙነት ፈጠሩ ያለውን ሁኔታ ከተረዱ በኋላ ረዳት ሀይል አስከሚላከላቸው ድረስ ጠንከረው እንዲዋጉ ትዕዛዝ ሰጡ ከዚያ በመለጠቅም አስመራ ለሚገኙት የኛው ኮር አዛዥ ለብጄጥላሁን ከፍሌ ስልክ ደወሉ ሆኖም ጄኔራሉን ሊያገጂቸው አልቻሉም በርሳቸው ፈንታም ለሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት አዛዥ ለነበሩት ለሜጄ ሑሴን አሕመድ በመደወል ሁኔታውን አስታወቁ ጄኔራል ሑሴንም ረዳት ጦር እስከሚላከላቸው ድረስ ባለው ሀይል ሁኔታውን ለመቆጣጠር እንዲሞከሩ ትዕዛዝ ሰጧቸው ጀኔራል ተሾመ በዚያች ቅጽበት በምጽዋ ዙሪያ የነበሩት የብርጌድ አዛሦች ጦራቸውን ለጠዋት እንዲያዘጋጁ ነገራቸው ንጋት ላይም ከረዳቶቻቸው ጋር ወደ ውጊያው ቦታ ተንቀሳቀሱ ሆኖም ያዩት ነገር ከጠበቁት ውጪ ሆነባቸው ሻዕቢያ የሰለሞናን ግንባር ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር በአካባቢው በነበሩት ተዋጊ ብርጌዶች ላይ ከባድ ጉዳት እንዳደረሰ ተረዱ የሰራዊቱ ብርጌዶችም ከሰለሞና በማፈግፈግ በምጽዋአስመራ መንገድ ላይ ወደምትገኘው ጋህተላይ እያፈገፈገ እንደሆነ ለማወቅ ቻሉ ጄኔራል ተሾመ ባደረጉት ወታደራዊ ቅኝት የሻዕቢያ ግብ የምጽዋአስመራን መንገድ መቁረጥ ሊሆን እንደሚችል ገመቱ ስለዚህ ሻዕቢያን በዚህ መስመር ገትረው ለመያዝ ወሰኑ በአካባቢውም ከአራት ብርጌድ ያላነሰ እግረኛ ሰራዊት አስቀመጡ ሆኖም የሻዕቢያን የግስጋሴ ፍጥነት ለመቆጣጠር ሳይቻል ቀረ ከእኩለ ቀን ጀምሮ እስከ ቀኑ ድረስ ከባድ ውጊያ ከተደረገ በኋላ ሻዕቢያ ጋህተላይን ተቆጣጠረ የአስመራምጽዋ መንገድም በእጁ ወደቀ አብዮታዊ ሰራዊትም ለሁለት ተቆረጠ የሰራዊቱ አዛች ሻዕቢያ በያዘው ይዞታ ብቻ ተብቃቅቶ የሚገታ መስሎአቸው ነበር በዚህም የተነሳ ረዳት ጦር እስከሚደርስላቸው ድረስ ዶጋሊ የተሰኘችውን ታሪካዊ አምባ በመያዝ መከላከልን መረጡ ሆኖም ሻዕቢያ ግስጋሴውን አልገታም ዋናውን ጎዳና ተከትሎ ሰራዊቱን ከኋላው እየተከታተለ ወጋው ሰራዊቱ በዶጋሊ ላይ እልህ አስጨራሽ ትንንቅ አደረገ ሻዕቢያም በዚያች ቀን ምጽዋን ከመያዝ ተገታ ከጋህተላይ ወደ ምዕራብ የተንቀሳቀሰው የሻዕቢያ ሰራዊት ግን ምሸቱ ከመድረሱ በፊት ደንጎሎ የተሰኘችውን አነስተኛ መንደር ተቆጣጠረ ከዚያም አልፎ ወደ አስመራ የቀረበችውን የጊንዳዕ ከተማ ለመያዝ ከፍተኛ ውጊያ ከፈተ የኮሩ ወታደራዊ አዛችና የፖለቲካ ሰዎች ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ ምጽዋ ባለው የኛው ከፍለ ጦር መሰብሰቢያ አዳራሽ በጄኔራል ጥላሁን ከፍሌ ሰብሳቢነት ተሰበሰቡ የሻዕቢያን ግብና ዓላማ ምን ሊሆን አንደሚችል ተነበዩ አንዳንዶቹ ሻዕቢያ ውጊያውን የከፈተው ለጊዜው ሽብር ለመልቀቅ ነው የሚል ግምት ሰነዘሩ ከፊሎቹ ደግሞ ሻዕቢያ ምጽዋን ለመቆጣጠር ያለመ ይመስላል በማለት ግምታቸውን አስቀመጡ በዚህ ዙሪያ ከርከር ተደረገ የኋላ ኋላም ሻዕቢያ ምጽዋን ለመቆጣጠር ያልማል በሚለው ሃሳብ ተስማሙ ይሁንና በአዛፐቹ መካከል በነበረው አለመጣጣም ሳቢያ የሜረባ የውጊያ እቅድ ሳይነድፉ ተበታተኑ ከስብሰባው የሚረባ ነገር ያጡት የኛው ክፍለጦር አዛዥ ብጄ ተሾመ ተሰማ ምጽዋን ለማዳን የራሳቸውን እርምጃ መውሰድ ጀመሩ ከምጽዋ በስተደቡብ ራቅ ምሽግ ይጠብቁ የነበሩ ብርጌዶች ወደ ምጽዋ ተመልሰው ከተማዋን እንዲጠብቁ ለማድረግ ወሰኑ በዕለቱ ከተያዘ አንድ የሻዕቢያ ምርኮኛ ከወሰዱት መረጃም ሻዕቢያ ምጽዋን ለመያዝ እጅግ ተጠናክሮ እንደዘመተ ለማወቅ ቻሉ በቀጥታ ወደ ጄኔራል ሁሴን አሕመድ በመደወል ሁኔታውን ካስረዱ በኋላ ሁለት ከፍለ ጦር የሚሆን ረዳት ጦር እንዲላከላቸው ጠየቁ ረዳት ጦር በአስቸኳይ ካልተላከ ግን የሻዕቢያ ድል አይቀሬ መሆኑን አስረግጠው ተናገሩ ጄኔራል ሁሴንም የተባለው ጦር እንደሚላከ በመግለጽ እስከዚያው ባለው ሀይል እንዲከላከሉ አዘዙ በዕለቱ የተማረከው መሐሪ ዮሐንስ የሚባል የሻዕቢያ ተዋጊ ነው ይህ ልጅ በሰጠው ቃል በጦሩ ውስጥ የሀይሊ አዛዥ እንደነበረ ተናግሯል ከርሱ በተገኘው መረጃ ለማወቅ እንደተቻለው ዘመቻው በከፍተኛ ደረጃ የታቀደ ሲሆን አፈጻጸሙን በበላይነት የሚከታተሉትም ኢሳያስ አፈወርቂ እና ስብሐት ኤፍሬም ነበሩ መሐሪ እንዳለው ሻዕቢያ ለውጊያ ያሰለፈው ሀይል አምስት እግረኛ ብርጌድ ሜካናይዝድ ብርጌድ አንድ ኮማንዶ ብርጌድ ነበሩ በከባድ መሳሪያ በኩል ሰባ ያህል ፐ ታንኮች ሶስት መድፈኛ ሻለቃ አራት የአየር መቃወሚያ ሻለቆች ተሳታፊ ነበሩ ዘመቻው ፈንቅል የሚል ስያሜ ተሰጥቶት የነበረ ሲሆን ዓላማውም የምጽዋን ወደብ መቆጣጠር እና የአስመራምጽዋን መንገድ ከነአካቴው መቁረጥ ነው የሻዕቢያ ሀይል የተሰማራው ከአፋቤት ከተማ ነው ስምሪቱ ሲጀመርም ጥር ከቀኑ ስድስት ሰዓት ላይ ኢሳያስ አፈወርቂና ስብሐት ኤፍሬም ንግግር አድርገውለታል ከዚያም ለግዳጁ በሶስት አቅጣጫ በሰለሞና ሸዒብ እና ውቅሮ ግንባሮች ተንቀሳቀሱ አኩለ ሌሊት ላይ ሰለሞና አቅራቢያ ደርሰው ከላይ የተገለጸውን ድንገተኛ ጥቃት ከፈቱ ጦሩን አሸንፈው ካባረሩ በኋላ ዱካውን እየተከተሉ ጋህተላይን ያዙ ዋናው መንገድም ተቆረጠ ይፉዕፖ « መጋቢት መጋቢት እኩለ ሌሊት በዚያች ደረቅ ሌሊት ሻዕቢያ ሳይጠበቅ የናደውን እዝ ወረረ አብዮታዊ ሰራዊትም ይዞታውን ለማስጠበቅ ተከላከሰ ይሁንና በለስ ሊቀናው አልቻለም ሻዕቢያ ቀደም ብሎ ያገኘውን መረጃ በሚገባ ሊጠቀምበት ስለቻለ የአብዮታዊ ሰራዊትን ማዘዣና የግንኙት መስመሮችን በጣጠሰ ተዋጊ ብርጌዶችን ከእዙ መሀል አስገብቶ በሰራዊቱ ላይ ወደ ውጪ ተኮሰ ከውጪ በኩል ደግሞ ዙሪያውን ከቦ በመትረየስና በከባድ መሳሪያ አዋገደው በዚህም የተነሳ ከእዙ ጠቅላይ መምሪያ ራቅ ብለው የሰፈሩ ከፍለ ጦሮች ወደ መሐል ተመልሰው እገዛ ማድረግ አቃታቸው ሁሉም ከፍለ ጦር በያለበት በራሱ ውጊያ ተጠመደ አብዮታዊ ሰራዊት በዚያ ትንፋሽ በሚያሳጥር ውጊያ ለሶስት ቀናት ከተዋከበ በኋላ ሁሉም ነገር ተበላሸበት መጋቢት መንፈቀ ሌሊት ላይ የናደው እዝ ሙሉ በሙሉ ተናደ የእዙ ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ግርማ ጌታነህ ከሶስት የሶቪየት ህብረት የጦር አማካሪዎች ጋር ተማረኩ ዋናው አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ውበቱ ጸጋዬና ዘጠኝ የሶቪየት የጦር አማካሪዎች ከውጊያው አምልጠው ሲሸሹ የወገን ሄሊኮፕተር ደርሶ አነሳቸው ሌሎች ከፍለ ጦሮች ከዋናው ማዘዣ የሬድዮ ግንኙነት እንደተቋረጠባቸው ሲረዱ የውጊያ ቀጣናቸውን እየለቀቁ ወደ ከረን አፈገፈጉ ሻዕቢያም የአፋቤትን ከተማ በእጁ አስገባ የናደው እዝንም ከሙሉ ግምጃ ቤቱ ጋር ተቆጣብጠረ ይህ የናደው ሽንፈት ብዙ ተብሎለታል ብዙም ተጽፎበታል በታወቁ የዓለም ዜና ማሰራጫዎች ግንባር ቀደም ወሬ ሆኖ ተዘግቧል በርካታ የአውሮጳና የአሜሪካ ጋዜጠኞች ጦርነቱ የተካሄደባትን የአፋቤት ከተማ በመጎብኘት ይከመንታሪ ፊልሞችን ሰርተውበታል የታወቁ የጦር ኤከስፐርቶች ሻዕቢያ በአፋቤት ያገኘውን ድል የቪየትኮንግ ሽምቅ ተዋጊዎች በፈረንሳይ ቅኝ ገዥዎች ላይ ከተጎናጸፉት የዲየን ቢየን ፉ ድል ጋር አወዳድረውታል በአጠቃላይ የናደው ሽንፈት ስለሻዕቢያ የሚያውቁትንም ሆነ የማያውቁትን የውጪ ዜጎች አደገኛ የጎሪላ ተዋጊ ሀይል ነው አያሉ በአድናቆት አንዲመለከቱት የጋበዘ ከስተት ሆኖ አልፏል በሌላ በኩል የናደው ሽንፈት በሀገር ውስጥ ከፍተኛ የፖሊሲ ለውጥ አስከትሏል በናደው ሽንፈት ማግስት የኢህዲሪ መንግሥት በይፋ ያልታወጀ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመላ ሀገሪቱ በስራ ላይ አውሏል ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለማሪያም መጋቢት ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ቀርበው በኤርትራ ስለሚካሄደው ጦርነት ተናገሩ ሰፊው ህዝብ ኤርትራን ከመገንጠል እንዲያድናት ጥሪ አቀረቡ መንግሥት በሚመድበው በጀት ብቻ ጦርነቱን ማካሄድ ስላልተቻለ ህዝቡም የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ አለበት በማለት ማሳሰቢያ ሰጡ የአዲስ ዘመን እና የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ጋዜጦች በፊት ገጾቻቸው ጥግ ላይ ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር የሚል መፈከር በቋሚነት ማስነበብ ጀመሩ የኢትዮጵያ ሬድዮም በምሽት ስርጭቱ ከሚያስተላልፈው ዜና ቀጥሎ አንድነት ሀይል ነው ሁሉም ለእናት ሀገሩ ዘብ ይቁም የአባቶቻችንን አደራ አናስደፍርም እና ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር የሚሉ አራት መፈክሮችን በመደበኛነት ማሰማት ጀመረ ኤርትራ በአስቸኳይ ጊዜ አስተዳደር ስር ወደቀች በኤርትራ መሬት የሚደረገው ቁጥጥር እንዲጠብቅ ትአዛዝ ተላለፈ ክፍለ ሀገሩን ከሱዳንና ከቀይ ባህር ጋር የሚያገናኙ መሬቶች ለሲቪል እንቅስቃሴ ተከለከሉ በናደው እዝ ላይ የደረሰው ሽንፈት በአብዮታዊ ሰራዊት ውስጥ ትልቅ ቀውስ መፍጠሩ እርግጥ ነው በዘመኑ የነበሩ የታወቁ ወታደራዊ አዛሦችም የፍጻሜው መጀመሪያ በማለት ገልጸውታል በጦርነቱ የተሰለፈው አብዮታዊ ሰራዊት ሃምሳ ሺህ ተዋጊዎችን ይዞ ከአስር ሺህ ያልበለጠ ሀይል በነበረው የሻዕቢያ ሰራዊት መሸነፉ በጣም አነጋጋሪ ሆኖ ነበር በሌላ በኩል ሻዕቢያ የጦርነቱን ውሎ አለም አቀፍ ዝና ለማግኘትና የአብዮታዊ ሰራዊት ሞራልን ለመስበር በሰፊው ተጠቅሞበታል የሬድዮና የህትመት አውታሮቹ የሻዕቢያን ሀያልነት የሚያሳይ ፕሮፓጋንዳ እየደጋገሙ ሰርተውበታል ለመሆኑ አስራ አምስት ሺህ ያህል የኢትዮጵያ ወታደሮች ሙት ቁስለኛና ምርኮኛ የሆኑበት የአፋቤት ሽንፈት እንዴት ተከሰተ። በርካታ አስተያየቶች ተሰጥተዋል ከነዚህ ሁሉ ሚዛናዊ መስለው የታዩኝ አቶ ገስጥ ተጫኔ ዘነበ ፈለቀ ነበር የሚል ርዕስ በሰጡት መጽሐፋቸው ያሰፈሯቸው ነጥቦች ናቸው በገስጥ ተጫኔ አመለካከት የአፋቤት ሽንፈት ምከንያቶች የእዙ አዛዥ የነበሩት ጄኔራል ታሪኩ አይኔ መገደላቸውና በርሳቸው ምትክ የተመደቡት ጄኔራል ውበቱ ጸጋዬ የየከፍለጦሮቹን የውጊያ ቀጣና በደንብ ሳያጠኑና ተለዋጭ የውጊያ ስልት ሳይነድፉ ሻዕቢያ ፈጥኖ በማጥቃቱ ሻዕቢያ በታሕሳስ ወር መጀመሪያ በሐበሻ አቆጣጠር ህዳር ወር መጨረሻ ላይ ባደረሰው ጥቃት ከማረካቸው መኮንኖችና የሬድዮ ሰራተኞች ስለናደው እዝ የጠራ መረጃ በማግኘቱ ወደ ውስጥ ዘልቆ በማጥቃት የማዘዣ ጣቢያውን መበተኑ ውጊያው ጠላትና ወገን የተደባላለቀበት ስለነበር ለድጋፍ ሰጪ ከባድ መሳሪያዎች ታንክ እና መድፍ እና ለአውሮፕላኖች ድብደባ አለማመቸቱ የአዙ ጠቅላይ መምሪያ ሻዕቢያ በታህሳስ ወር ያደረገውን ማጥቃት ተከትሎ ወደ አፋቤት እንደሚያመራ በመገመት ለጠንካራ መከላከል ዝግጅት አለማድረጉ ሻዕቢያና ህወሐት የማዘዣ ጣቢያዎችን ቀድሞ መምታታቸው የተለመደ ስልት ሆኖ ሳለ የእዙ ዋና አዛዥ ምናልባት ማዘዣዬ ቢመታብኝ በማለት በሚስጢር የተሰናዳ ተለዋጭ የማዘዣ ጣቢያ አለማዘጋጀታቸው ብሎም ሻዕቢያ ማዘዣቸውን እንዲለቁ ሲያስገድዳቸው እዚህ ነኝ ሳይሉ ግንኙነታቸውን አቋርጠው ወደ ከረን መሸሻቸው የመሳሰሉት ናቸው የአፋቤት ውድቀት ከደረሰ በኋላ የሻዕቢያ አስመራ መግባት የጊዜ ጉዳይ እንደሆነ ሁለቱም ወገኖች ተረድተዋል ኢትዮጵያና ኤርትራ ተነጣጥለው ሁለት ሀገር እንደሚሆኑ መተንበይ የተጀመረውም ከዚያ በኋላ ነበር የደርግ ከፍተኛ የጦር አዛች በአፋቤት የደረሰው ውድቀት የወገን ጦር በመዘናጋቱና የሻዕቢያን አቅም አሳንሶ በማየቱ የተከሰተ እንደሆነ ይገልጻሉ በሽንፈቱ ማግስት የሻዕቢያ ሲሳይ የሆነው ግዙፍ የጦር መሳሪያና የቁሳቁስ ከምችት ለአፋቤት ወታደራዊ ጠቀሜታ በተሰጠው የተጋነነ ግምት ሳቢያ የተከሰተ እንደሆነ ያወሳሉ ሻዕቢያ ታንክና ከባድ መድፎች ለመማረከ ችሎ ነበር ከተማዋና ዙሪያዋ በተራሮች የተከበቡ ሆነው ሳሉ አካባቢው ከሚችለው በላይ አምስት ከፍለ ጦር የሚሆን ሰራዊት ተፋፍጎ እንዲቀመጥበት ስለተደረገ ለሻዕቢያ የከባድ መሳሪያ ድብደባ መጋለጡንም ጨምረው ይናገራሱ የጄኔራል ታሪኩ አይኔ መገደልም የወታደሮቹን ሞራል እንደሰበረ ያከላሉ ሻዕቢያዎች ግን ይህንን አይቀበሉም የአፋቤት ድል በነርሱ ጀግንነትና የጦር መላ አዋቂነት የተገኘ አንደሆነ ነው የሚናገሩት ጄኔራል ታሪኩ ባይረሸን እንኳ አፋቤትን ከመያዝ የሚገድባቸው ሀይል አንዳልነበረ ይከራከራሉ ወጣም ወረደ ግን ሁሉም በአንድ ነገር ይስማማሱ የአፋቤት ሽንፈት የጦርነቱን አቅጣጫ ከመሰረቱ የቀየረ መሆኑን ያለ ምንም ማመንታት ይቀበሉታል ከዚያ በኋላ የነበረው የአብዮታዊ ሰራዊት ጉዞ በኋላ ማርሽ የመጓዝ ዓይነት ነበር ይላሉ በዚህ ረገድ የተለየ አስተያየት የሰጡት ኮል መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም ብቻ ናቸው እሳቸው እንደሚሉት የአፋቤትን ሸንፈት ያጋነኑት የዓለም ሚዲያዎች ናቸው እንጂ በወቅቱ የሰራዊቱ አቅም አልተነካም ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ለብሄራዊ ሸንጎ ባደረጉት የመጨረሻ ንግግራቸው በናደው እዝ ላይ የደረሰውን ውድቀት ትተው ስለአፋቤት ከተማ ከንቱነት ነበር የተናገሩት በኢትዮጵያ ስታንዳርድ ቀበሌ አይደለም አልማዝ አይቆፈርበት ቤንዚን አይወጣበት ሀገር አይደለ ከከበ እያሉ ተሳልቀውባታል በፕሬዚዳንት መንግሥቱ አባባል በኤርትራ ምድር እጅግ ወሳኝ የሆነ ውድቀት የሚባለው በምጽዋ የደረሰው ነው እንጂ በአፋቤት የታየው አይደለም የምጽዋው ውድቀትስ ምን ይመስል ነበር።