Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ሕይወተ ወራዙት ብሎ በጻፈ ዜም ወጣቶች ጎበዞች» እንደሚባሉ ማጠናከሪያ ሰጥቷል ዮሐ «ክፉውንም ስለ አሸነፋችሁ» ማለቱም «ክፉ» የሚባለውን የወጣትነት ምኞት ስለ አሸነፋችው ማለቱ ነው ቅዱስ ጳውሉስ «ከክፉ የጎልማስነት ምኞት ሽሸቨ በማለት የክርስትና ልጁ ጢሞቴዎስን እንደመከረው የወጣትንት ምኞት ዘፉ» ይባላልና ወጣቶች ፈጣሪያቸውን ማሰብ እንደሚኖርባቸው ተለይተው የተጠቀሱት ለምንድር ነው። ፈጣሪን ማሰብ የሚኖርባቸው ወጣቶች ብቻ ። ወይስ ፈጣሪ በመጣ ጊዜ አስበኝ ብለኽኝ ነበር» እንዲለው ብቻ ነበርን።
አይደለም «ከሁለት ዓይነት ነገር ቀለም የተሠራ ልብስ አትልበስ» ማለቱ ሁለት ዓይነት ሰብእና አትላበስ በተጨማሪም «በአንድ ራስ ሁለት ምላስ» እንደሚባለው ቃሉና ሐሳቡ ተለዋዋጭ የሆነ ሁለት ዓይነት ሰው አትሁን ማለቱ ነው ይህን የመሰለ «ከተልባ እግርና ከበ ጉር በአንድነት የተሠራ ልብስ አትልበስ» የሚል ትእአዛዝም አለ ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ አርእስትና ኅዳጉ እየታየ በሚገባ ይተረጎማል እንጂ በዘፈቀደ የሚነገር አይደለምና መጠንቀቅ ያሻል ዘዳ ዘሌ ከበግ ጠ ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል በዚህ መልኩ በመተርጎመሥ ጠባብ አመለካከት ያላቸው እጅግ በጣም በርካታ ሴቶች ሱሪ ለመልበስ መግቢያ ያገኙ ይመስላቸው ይሆናል ምክንያቱም አብዛኞቹ ሴቶች «ሴት የወንድ ልብስ አትልበስ» የሚለውን ቃል የሚረዱት ሴት «ሱሪ መልበስ አይገባትም» እንደሚል ብቻ አድርገው በመሆኑ ነው ከዚህ ቀደም «ሱሪ» የማይለብሱ ሆነው ይህን ትርጓጫ በማወቃቸው ሕይወተ ወራዙት መ ብቻ «ሱሪ» ለመልበስ የሚነሣሠ ሴቶች እውነት አይነገረን ከተነገረን ግን ዋ። የአስተማሪዎቼንም ቃል አልሰማሁም ጆሮቼንም ጠደ አስተማሪዎቼ አላዘነበልሁም ምላጻእ ሕይወተ ወራዙት ይልቁንም ለመማር የሚያስችል ሁኔታ ተመቻችቶ ላለ ለመሥራትና ንብረት ለማካበት መሽቀዳደም የከበረች ጥበብን ዋጋ ማሳጣት ነው ከገንዘብ ተግሣጽ ይበልጣልና ተግሣጽ ደግሞ ጥበብም ትምህርትም ነው ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ «ተግሣጴን እንጂ ብርን አትቀበሉ ከምዝምዝ ወርቅም ይልቅ ዕውቀትን ተቀበሉ ጥበብ ከቀይ ዕንቁ ትበልጣለችና የከበረ ነገር ሁሉ አይተካከላትም ምሳ በማለት ትምህርት በገንዘብ እንደማይለካ ምስክርነቱን ይሰጣል ሲራፅ የትምህርት ዓይነቶች ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ምድራዊና ሰማያዊ ሥጋዊና መንፈሳዊ በማለት ጥበብን በሁለት በመክፈል ጸፏል ስለምድራዊ ጥበብ ሲናገር «ይህ ጥበብ ከላይ የሚወርድ አይደለም ነር ግን የምድር ነው የሥጋም ነው» በማለት ሲገልጸው ሰማያዊውን ጥበብ ደግሞ «ላይኛይቱ ጥበብ ግን በመጀመሪያ ንጽሕት ናቸ በኋላም ታራቂ ገር እሺ ባይ ምሕረትና በጎ ፍሬ የሞላባት ጥርጥርና ግብዝነት የሌለባት ናት በማለት ይገልጻታል ያፅጾማግ ጥበብ ለሁለት ወገን ተከፈለች ማለት ትምህርትም ለሁለት ይከፈላል ምክንያቱም ጥበብ የሚገኝ ከትምህርት ነውና ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ ትምህርትን ትምህርተ ክርስቶስና ትምህርተ ሰብእ የሰው ትምህርት በማለት ለሁለት ከፍሉ አስረድቷል ይህም «አንደ ክርስቶስ ትምህርት ሳይሆን እንደ ሰው ወግና እንደ ዓላማዊ አንደ መጀመሪያ ትምህርት ባለ በናባልስናና በከንቱም መታለል ማንም እንዳይማርካችሁ ተጠበቁ ባለው ይታወቃል ቀቆላ ሬክ መ መ መ እ መ ው መ ው መ የወቶች ሕይጦት ከለዚህ መንፈሳዊውን ትችምህሮች የክርስቶስ ችምህሮች መንፈሳዊ የቤተክህነት ስማያዊ ጥንታዊ በማለት ስንጠራው ዘመናዊውን ትምህርት ደግሞ ዓለማዊ ምድራዊሰብአዊ ወግ ፍልስፍና ሥጋዊ ትምህርት በማለት ልንጠራው እንትላለን ከቤተ ክርስቲያን የጸሎት መጻሕፍት መካከል አንዱ የሆነው መስተብቁዕ መንፈሳዊውን ትምህርት «የመለኮት ትምህርት» በማለት ይጠራዋል «ወሴሲ ልበነ በመለኮተ ትምህርት ወበለብዎ ዘእምገኀቤከ» ዓፍዊውም በመለኮት ትምህርት ልቡናችንን መግብ ከአንተ ዘንድ የሚገኘውንም ማስተዋል» ማለት ነው መስተብቁፅ በእንተ ዝናማት በአሁኑ ጊዜ ሥጋዊውን ትምህርት በሀገራችን ለማዳረስ ኃላፊነት የተሰጠው ክፍል በሚኒስቴርች መሥሪያ ቤት የትምህርት ሚኒስቴር ሲሆን እውነተኛውን መንፈሳዊ ትምህርት ለዓለም እንድታዳርስ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ሙሉ ኃላፊነትና ትዕዛዝ የተቀበለች ቤተ ክርስቲያን ናት ይሁን እንጂ ቤተ ክርስቲያን በሀገራችን ለመንፈሳዊውም ሆነ ለሥጋዊው ትምህርት መሠረት እንደ መሆና መጠን ዘመናዊውንም ትምህርት በሀገራችን ከማስፋፋት የቦዘነችበት ጊዜ የለም በሀራችን በኢትዮጵያ ዘመናዊ ትምህርት በማይታወቅበት ጊዜ አንኳን ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቷን በአስደናቂ መልኩ ቀርጻ ከፍልስፍና በዘህሠሠናዊ ጥበብ ጋር ጉን ለጉን ስታስተምር ቆይታለት ከዚህም በተጨማሪ ለሀገርና ለአህጉር መኩሪያ የሆነ ብቱ ፊደል ቀርጻ ማስረክከቧ ሳያንሳት የፊደላቱን ምሥጢር መልክና ቅርጽ በማስለየት አስከዛሬ ድረስ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተች ነው ይህን ሁሉ ሕይወተ ወራዙት የመረመረ ሰው በተ ክርስቲያን ለሠንፈሳዊ ችምህርት ብቻ ሳይሆን ለሥጋዊ ትምህርት መሠረት መሆኗን ለማወቅ አይቸገርም ሕንፃ ከማነጽ ፍትሕት ከመፍታት ከማጥመቅ ከመቀደስ ይልቅ ቀዳሚው የቤተ ክርስቲያን ተልዕኮ ማስተማር ነው። ቅዱስ ዳዊት ለጆቼ ኑ ስሙኝ እግዚአብሔርን መፍራት አስተምራችኋለሁ» ሠመዝ በማለት የተናገረው ቃል ለዚህ ምስክር ነው «ከእሾህ ወይን ከኩርንችትም በለስ» እንደማይለቀም ሁሉ ሰው ሁሉ እግዚአብሔርን እንዲፈራ ለማድረግ ዓላማ ይዞ ያልተቀረጸ ትምህርት ሁሉ እግዚአብሔርን ስለመፍራት ሊያስተምር አይችልም ስለዚህ በጥሩ ሥነ ምግባር ተኮትኩቶ ለማደግ አስቀድሞ መንፈሳዊ ትምህርትን መማር ይገባልር «የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነውዓ» ምሳ መዝ መንፈሳዊ ትምህርት እንደ ራት ሲሆን ሥጋዊ ትምህርት ግን እንደ ዳረጎት ነው ከእራትና ከዳረጐት ዳረጎትን የሚመርጥ ማንም የለም ዳረጐት እራት አይሆንምና እንደዚሁም ሁሉ ጊዜያዊ እንጂ ዘለዓለማዊ ጥቅም የሌላት ሥጋዊ ጥበብ ከመንፈሳዊ ጥበብ መቅደም የለባትም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማንኛውም ሰው በሕይወት ዘመ ማስቀደም ያለበት ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመግባት የሚረዳውን ነገር መሆን እንዳለበት ሲገልጽ «አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ ይህም ሁሉ ይጨመርላችቷል በማለት ተናግሯል ማቴፅ ሠለስቱ ምዕት ልጆችና ወጣቶች አስቀድመው ምን መማር እንዳለባቸው በትእዛዝ መልክ እንዲህ ብለዋል «ቅድመ መሀርዎሙ ለውሉድክሙ መጽሐፈ ሲራክ ወሰሉሞን ወመዝሙረ ዳዊት» ይህም አስቀድማችሁ ለልጆቻችሁ የሲራክን የሰሉሞንን መጻሕፍትና የዳዊትን መዝሙር አስተምራቸው» ማለት ነው ይልቁንም መመ የወጣቶች ሕይወት «አስቀድማችሁ» ና አስተምራችው» የሚሉ ቃላተ ል ከዘመናዊ ትምህርት አስቀድመው መንፈሳዊውን ትምህርት እንዲማሩ የማድረግ ኃላፊነት የወደቀው በወላጆች ላይ መሆኑን ይጠቁማሉ ይህ የአበው ትፅዛዝ መንፈሳዊው ትምህርት ከሥጋዊው ትምህርት መቅደም እንዳለበት ብቻ ሳይሆን ከመንፈሳዊ መጻሕፍትም ለወጣቶች ከላይ የተጠቀሱት መጻሕፍት መቅደም አንዳለባቸው ያስረዳል ምክንያቱም እነዚህ መጻሕፍት ወጣቶች በአእምሮ የበሰሉ እንዲሆኑ ከማድረጋቸውም በላይ ሥጋዊውንና መንፈሳዊውን ጥበብ አጣምረው ለመረዳት እንዲችሉ ያደርጓቸዋል ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሉሰ ለዛይማኖት ልጁ ለጢሞቴዎስ በላከው መልእክቱ «ማንም ባልቴት ግን ልጆች ወይም የልጅ ልጆች ቢኖሩአት እነርሱ ዳፅዖድመው ለገዛ ቤተሰቦቻቸው እግዚአብሔርን መምሰል ያሳዩ ዘንድ ለወላጆቻቸውም ብድራትን ይመልሱላቸው ዘንድ ይማሩ» በማለት ልጆችና ወጣቶች አስቀድመው ምን መማር እንዳለባቸው በግልጽ ተናግሯል መማር ያለባቸውም ተገልጦ ሊታይ የሚችል «እግዚአብሔርን መምሰል» እና ወላጆቻቸውን በመጦር መንከባከብ ማለትም «ብድራትን መመለስ» መሆን እንደሚገባው አስረድቷልወላጆችን መርዳትና እግዚአብሔርን መምሰል የሚገኝበት ትምህርት መንፈሳዊ ትምህርት መሆኑ ግልጽ ነው ይህን ተረድቶ መንፈሳዊውን ትምህርት አስቀድሞ መማር ምን ያህል እግዚአብሔርን እንደሚያስደስተው ይህ በእግዚአብሔር ፊት መልካምና የተጠደደ ነውና» በማለት ጨምሮ ገልጧል ጢሞ አንድ ክፉ ሱስ ከተጸናጠተህ በኋላ ምንም እንኳን ጉጂነቱን በበቂ ሁኔታ ብታውቅ ካንተ ለማራቅ እጅግ ይቸግርፃል እንደዚሁም ሁሉ ዓለማዊ ትምህርትን አስቀድመህ ተምረህ ከዛይማኖትህ ጋር ሕይወተ ጦራዙት የሚጣረሱትን ጽንሰ ሐሳቦች ከተለማመድካቸው በኋላ አፃቪህን አስወግደህ ፃይቶይፃኖተኛ ለመሆን መቸገርህ አይቀርም። ፅውቀት ከምትገበይባቸው ሰዎችና ነገሮች ጋር ያለህ ግንኙነት እንዲጠብ ወይም እንዲቋረጥ በማድረግ ትኩረትህ ወደ አንድ ፆታዊ አቅጣጫ ብቻ እንዲሆን ያደርግና በዕውቀት እንዳታድግ ትሆናለህ ስለዚህ ይህን ከመሳሰለ አካፄድ ለጊዜው ብትቆጠብ እዕቀትን ከመራብ ትድናለህ ለሁሉም ገዜ አለውና የትምህርት ጥቅም መማር የሚኖርብህ ልጅ በመሆንህ ተገደህ ወይም ምንም ምርጫ ስላጣህ መሆን የለበትም ትምህርት ብዙ ጥቅም እንዳለው ዐውቀህ ከልብ በመነጨ ፍላጉትና ጥረት ብትማር ለጠደፊት ኑርኽ ምን ዓይነት ባልንጀራ ማፍራት እንዳለብህቨኛ ምን ብትሠራ እንደምትጠቀምና በሕይወትህ ዙሪያ ለሚፈጠሩ የሕሊና ጥያቄዎች በቀላሉ መልስ እንድታገኝ ጥሩ መሠረት ይጥልልፃል የወጣቶች ሕይወት በመሥራት ላይ ያሉትን ነገሮች ለማወቅ ያስችላል በሥራቸውም የተሳካላቸውንና ውድቀት ያስከተለባቸውን አካሄድ በመለየት በሙከራ ጊዜ ሳታጠፋና በእነርሱ ላይ የደረሰውም ውድቀት ሳይደርስብህ የትኛ ውን ጉዳና መከተል እንዳለብህ ለመወሰን ይረዳሃፃል ከልብ የተማረ ሰው ጊቢውን ጠብቅ መጠቀመሙ አይቀርም የተማረውን ትምህርት ለሌሎች በማስተማር የፈጠራ ሥራዎችን በመሥራት ወይም ተምሮ ባገኘው ሙያ ምንደኛ ሆኖ በሚያገኘው ገቢ ራሱን ማስተዳደር ይችላል ከዚህም በተጨማሪ የሙያ ተሰጥኦቹን በመጠቀም ያለአግባብ የሚያወጣውን ወጪ መቀነስና ለራሱ የተመቻቸ ሁኔታን ሊፈጥር ይችቸላል ለምሳሌ የምግብ አዚጋጃደት ትምህርትን የተከታተለ አንድ ሰው የሚፈልገውንና የሚስማማንው የምግብ ዓይነት በማዘጋጀት ጤናውን ለመጠበቅ ከመቻሉም በላይ መመገቢያ ቤቶችን ሆቴሎችንነ በመጠቀም የሚያወጣውን ያልተመጣጠነ ጦጪ በመቀነስ ራሱን ለመርዳት ይችላል በተመሳሳይ ሁኔታ አንድ የቴክኒክ ሙያ ሥልጠና የወሰደ ሰው በዙሪያው ከሚገኙ ገሮች በመጠቀምና ወጪ ሳያስፈልገው ልዩ ልዩ መገልገያዎችን ለራሱ ማበጀት ወይም የተበላሹ ንብረቶቹን ያለተጨማሪ ወጪ ራሱ ሊጠግናቸውና ሊያድሳቸው መቻሉም ከመማር የሚገኝ ጉልህ ጥቅም ተደርጐ ሊጠቀስ ይችላል አንድ ሰው የተማረውን ትምህርት በቀጥታ በሥራ ላይ ለማዋል በማይችልበት ሁኔታ ውስጥ ቢገኝ እንኳን ትምህርት አይጠቅምም ለማለት አይቻልምነ እንደቪህ ዓይነት ሰው ምንም አንኳን በተማረው ትምህርት በቀጥታ ገቢ አግኝቶ ተጠቃሚ ባይሆንም ትምህርቱ በሌላ አቅጣጫ ተጠቃሚ አንደሚያደርገው ማስተዋል ይገባል ምክንያቱሯ መማር ለመሠማር ከተዘጋጀንበት ሒሕይወተ ወራዙት መደበኛ ችምህርት ውጭ በሂደቱ ትፅግሥችን ትጋትን ሐሳብን ሰብስቦ የመከታተል ችሎታን መጠየቅንና የማንበብ ልምድን እንድናዳብር ከማድረጉም በላይ አእምሮአችን እንዲሰፋ ያደርጋል የሠሩበት አካል እንደሚጠነክር ሁሉ የተማሩበትም አእምር መዳበሩ አይቀርም ይህም በዋጋ ሊተመን የማይችል የትምህርት ሁለ ገብ ጥቅም ነው በትምህርት መኖር «ጥበቃ» ነው። ተግባራት የተመረዙ ባልንጀሮችህን ጨምር በርካታ ሰዎች በዙሪያህ ይገኛሉ ይህን ከመሳሰሉት ሰዎች ጋር መዋል ቀር ሳያሰኝህ የወጣቶች ሕይወት ለማስቀረት ያስቸገረህ ቢሆንም ትምህርትህን ብሚገባ ብትከታተል ግን አንዲህ ካሉ መጥፎ ሰዎች ጋር ያለህን የጠበቀ ግንኙነት ቀስ በቀስ ለመቅረፍ ትችላለህ ለትምህርት ጥሩ ትኩረት በምትሰጥበት ጊዜ ሰፊ ጊዜህን ይይዝልፃል ይህም ሥነ ሥርዓት ከጉደላቸው ሰዎች ጋር የሚኖርህን ግንኙነት ውስን ያደርገዋል እንደዚህ ያሉ ሰዎች ፍላጐትህ ትምህርትህን በሚገባ መከታተል ብቻ መሆኑን ሲያዩ ከጊዜ በኋላ ሊተዉህ ይችላሉ ይህም ከትምህርት የምታገኘው «ጥበቃ» ነው መጽሐፈ መነኮሳት የማንበብ ልምድና ትምህርት በንጽሕና ተጠብቆ ለመኖር አጋዥ መሆናቸውን እንዲህ ሲል ይገልጻል «ዓማ ሥጋዊት ወአንብቦ መጻሕፍት አሞላካውያት የዐቅብዊ ለንጽሕና» በአማርኛ «በሥጋ መድከምና አምላካዊያት መጻሕፍትን ማንበብ ንጽሕናን ይጠብቋታል» ማለት ነው ማርይስአንሣልስምዕ የመንፈሳዊ ትምህርት ጥቅም ያለንበት ዘመን ከየትኛውም ጊዜ ይልቅ የትምህርት ጥቅም ጉልቶ የሜታይበት ዘመን ሆኗል ከላይ በጥቂቱ የተገለጹት ዕሜቶች ከሥጋዊ ትምህርት የሚገኙ ናቸው ሥጋዊ ትምህርት እንደዚህ የሚጠቅም ከሆነ መንፈሳዊ ትምህርት ደግሞ እጀግ በተሻለ ሁኔታ እንደሚጠቅም ጥርጥር የለውም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሉስ ማንኛ ውም ሥጋዊ ነገር ያለው ጠቀሜታ ከመንፈሳዊ ነገር ጠቀሜታ ጋር ሊነጻጸር እጅግ ጥቂት እንደ ሆነ እንዲህ በማለት ይገልጻል ሰውነትን ለሥጋዊ ነገር ማስለመድ ለጥቂት ይጠቅማልና አግዚአብሔርን መምሰል ግን የአሁንና የሚመጣው ሕይወት ተስፋ መ መ መ ሕይወተ ወራዙት ስላለው ለክ ሁሉ ይጠቅማል ገጢሞ ስለዚህ መንፈሳዊ ትምህርት የሚሰጠው ጠቀሜታ ከሥጋዊ ትምህርት እጅግ የላቀ ነው በስሐተታቸው ጸንተው የሚኖሩ ሰዎች ሥራዬ ትክክል ነው ብለው የሚያምኑ ወይም መሳሳታቸውን በውል ያልተረዱ ናቸው ከዚህ ካለፈ ደግሞ ስሕተታቸውን ቢያውቁም ከዘለቄታዊ ጥቅም ይልቅ ለጊዜው የፍላጐታቸውን መሳካት የሚወዱ ከመሆን አይዘሉም ካለማወቅ የተነሣ የተሳሳቱ ሰዎች መላልሰው ሥራቸውን ቢመረምሩትና በቂ ግንዛቤ እስኪያገኙ ድረስ ስለ ሥራቸውም አስከፊነት ቢማሩ ከሕህተት ይታረማሉ መማር ከመሳሳት ያድናልዓና የማይሳሳት የለም ከስሕተት ሁሉ የሚከፋው ግን በሃይማኖታችን ላይ የምንፈጥረው ስሕተት ነው ለምን ቢባል ጉዳቱ የነፍስ ስለሆነ ነው ከዚህም ዓይነት ስሕተት ቢሆን መዳን የሚቻለው በመማር ነው አለማወቅ ለሕህተት መንሥኤ ከሆነ መማርና ማወቅ ከስሕተት ለመዳን መፍትሔ መሆኑ ግድ ነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በትንሣኤ ላይ ባላቸው እምነት ችግር ለነበረባቸው ለሰዱቃውያን የስሕተታቸው መነሻ ምን እንደ ነበር ሲነግራቸው «መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችው» ብሏቸዋል ማቴ ስለዚህ ትምህርት ካሉት ዋና ዋና ጥቅሞች መካከል «ክስሕተት ለመዳን የሚለው በአንደኛነት ይጠቀሳል ከስሕተት ለመዳን ብቻ ሳይሆን ለማመንና እግዚአብሔርን ፈርቶ ለመኖርም ትምህርት ወሳኝ ነገር ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሳይማሩ ሃይማኖተኛ ሰው መሆን እጅግ አስቸጋሪ እንደ ሆነ ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ። » የወጣቶች ሕይወት በማለት ተናግሯል ሮሜዐ ቅዱስ ዳዊት ደግሞ «ልጆቼ ሆይ ስሙኝ እግዚአብሔርን መፍራት አስተምራችኋለሁ» መዝ በማለት ማመን ከትምህርት እንደሚገኝ ተናግሯል በዓይን ያላዩትን እግዚአብሔርን መፍራት ማመን ይባላል ለማመን ብቻ ሳይሆን መልካም ሥራ ለመሥራትም መማር ያስፈልጋል የማያውቁትን መሥራት ስለሚያስቸግር ለመሥራት ማወቅ ለማወቅ ደግሞ መማር ግድ ነው ማወቅ ለመሥራት ብቻ ሳይሆን በሥራችን የትክክለኛለነት ስሜት እንዲሰማንና ያለማቋረጥ በጉጉት እንድንሠራው ያግዘናል በአጠቃላይ በመንፈሳዊም ሆነ በሥጋዊ ጐዳና የሚሠሩ ሥራዎችን ለማከናወን መማር ያስፈልጋል ለዚህም ነቢዮ ኢሳይያስ «መልካም መሥራትን ተማሩ» በማለት የተናገረው ቃል በቂ ማስረጃ ነው ኢሳ መንፈሳዊ ትምህርት ለበጎ ሥራ ያዘጋጃል «የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ» በማለት ቅዱስ ጳውሎስ የተናገረው ቃል ከላይ የተጠቀሰውን ሐሳብ ይደግፋል ጢምሩ መንፈሳዊ ትምህርት ለበጎ ሥራ የሚያዘጋጅ የዛይማኖት ሰው እንድንሆን የሚያደርግ በመሆኑ በነፍስም ሆነ በሥጋ እጅግ ጠቃሚ ነው የመንፈሳዊን ትምህርት ጥቅም በጭር ቃል ስናጠቃልለው «መዳን የሚገኝበት ጥበብ» እንለዋለን ጢሞ ምክንያቱም ይህ ጥበብ ሰው የእምነትንና የምግባርን እርካብ እየረገጠ ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመውጣት ስለሚያስችለው ነው ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ መንፈሳዊ ትምህርት ወደ አእምሮ የሚገቡትን የዘመናዊ ትምህርት ፅንሰ ሐሳቦችንና ማንኛውም ዓይነት ዕውቀቶችን ምን ያህል እውነተኛና ጠቃሚ አንደሆኑ ለመመዘን ይረዳል መንፈሳዊ ትምህርት ከዘመናዊ ትምህርት መቅደም ሕይወተ ወራዙት የሚኖርበትም ስፅዚህ ነው አንድ ሰው አስቀድሞ መንፈሳዊውን ትምህርት በሚገባ የተማረ ከሆነ ለወደፊት ሕይወቱ የሚበጀውንና ከእግዚአብሔር አንድነት እንዳይለይ የሚረዳውን ነገር ሁሉ ለይቶ ያውቃል «ሥራ» ተብለው ነገር ግን ከመንፈሳዊ ሕይወት ጋር ፍጹም የሚቃረኑ ብዙ መስኮች አሉፊ አንድ ክርስቲያን አስቀድሞ መንፈሳዊ ግንዛቤ ካለው አከፈጣሪ አንድነት የሚለዩትን እነዚህን ነገሮች እየተማረና እያጠና ገንዘቡንና ጊዜውን አያባክንም ለምሳሌ ቤተ ክርስቲያን ከመጽሐፍ ቅዱስ መረጃ በመጥቀስ ዘፋኝነትን» ታወግዛለች አንድ ሰው ደግሞ ደግሞ መንፈሳዊነትን መላበስ እየፈለገና የቤተ ክርስቲያን ልጅ ሆኖ ሳለ አንድን የሙዚቃ መሣሪያ አጨዋወትና ጥሩ ዘፋኝ ለመሆን የሚያስችል የድምጽ አወጣጥ ጥበብን ቢያጠና በሕይወቱ ብዙ ነገሮች አይቃወሱበትም። በዚሁ ሥራው ተሰማርቶ እንዳይኖር ደግሞ ከፈጣሪው ጋር ያለው ግን በእጅጉ ይበላሽበታል ለዚህ ሁሉ ችግር መፍትሔ የሚሆነው በምን መልኩ ብንጓዝ እንደምንጠቀም ከወዲሁ ለይተን እንድናውቅ የሚረዳንን መንፈሳዊ ትምህርት አስቀድመን ብንማር ነው ብዙ ክርስቲያኖች ጥሩ መንፈሳዊ ሰው መሆን ያልቻሉት ከላይ የተጠቀሰው ዓይነት ውስብስብ ችግር ስላጋጠማቸው እንጂ መሆን ሳይፈልጉ ቀርተው አይደለም እንዲህ ያለ ችግር ያጋጠማቸው ሰዎች ቀስ በቀስ ሥራቸውን በሌላ አማራጭ እየተኩ ከፈጣሪ ጋር ያላቸውን ቨሸምድና ከማጠናከር ውጭ ባሉበት ሁኔታ ጥሩ መንፈሳዊ ሰው መሆን የሚችሉበት ምንም ዓይነት መንገድ የወጣቶች ሕይወት ፌሴ ር ን የለም ከዚህ ሁሉ የሚከፋው ደግሞ ካፈርኩ አይመልሰኝ» እንደሚባለው ሥራቸው በቅዱስ መጽሐፍ የተወገዘ ሆኖ ሳለ አንድ ጊዜ ስለገቡበት ብቻ ሥራቸውን መጽሐፍ ቅዱስ እንደማይቃወመው አድርገው ለማስረዳት የሚሞክሩ ሰዎች መኖራቸው ነው ተሳስቻለሁ። ጹ ይህም የዘመናዊ ትምህርት ዋነኛና ቀጥተኛ ጉዳት ተደርጐ ይጠቀሳል ሃይማኖት የሌላቸውና የወጣቶች ሕይወት መንፈሳዊ ነገር ግድ የለላቸው ስዎች በመናዊ ትምህርት ጥቅም ብቻ እንጂ ጉዳት ያለው አይመስላቸውም ነገር ግን ዘመናዊ ትምህርት በመንፈሳዊ ትምህርት ከተመዘነ በብዙ ጎዳና ሊጎዳ እንደሚችል መታዘብ ይቻላል የትምህርት ተዛማጅ ጉዳቶች ከላይ ከተጠቀሰው በተጨማሪ በዘመናዊ ትምህርት ምክንያት ሲከሠት የሚስተዋለው ጉዳት ሰዎች ለትምህርት ከሚሰጡት ጊዜ ጋር የተቆራኘ ነው ይኸውም አንዳንድ ሰዎች ትምህርት ለሰው ክሚያስፈልጉት ነገሮች እንደ አንዱ ብቻ በነጠላ ሊታይ የሚገባው ነገር መሆኑን ይዘነጉታል ለሚያስፈልጓቸው ሌሎች ተግባራት ማዋል ያለባቸውን ጊዜ በሙሉ ለትምህርት ብቻ በማዋል የኋላ ኋላ ሲጸጸቱ ይታያል ለምሳሌ አንዲት ልጃገረድ ትምህርቷን ባለመመጠንዋ ምክንያት የመውለጃ ዕድሜዋ ቢያልፍባት ተምራ ያገኘችው ማዕረግ የተሳናትን ልጅ መውለድ ሊመልስላት ወይም ትሮዋን ደስተኛና የተሟላ ሊያደርገው አይችልም ስለዚህ ጊዜን አስፈላጊ ለሆኑ ነገሮች ማብቃቃት እንጂ መላ ዕድሜን ለትምህርት ብቻ መስጠት ብልህ አያሰኝም ትምህርት ሰው እራሱን ካልመጠነ በቀር ፍጻሜ የሌለው ነገር ነው። ሆኖም እንዲህ ያለ የምናኔ ሐሳብ የሌላቸው ሰዎች በመንፈሳዊ ትምህርትም ላይ ቢሆን ያለ አግባብ ጊዜ ማጥፋት የለባቸውም ብዙ ተምሮ ምንም ሳያገለግሉ የሚሹትንም ሳያገኙ እየተቆጩ ኖረው ከመሞት በመጠኑ ተምሮ የተማሩትንም በአግባቡ ተጠቅመውበት ማለፍ ይመረጣል ቤተ ክርስቲያን ሕይወት የሚገኝበትን ጥልቅ መንፈሳዊ ትምህርቷን ለሰው ሁሉ እንዲዳረስ የበለጠ ጥረት ማድረግ አለባት አግረ መንገዴንም ሳልጠቁም የማላልፈው ነገር ቢኖር የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ ቢያስቡበት ሰፋ ያለ ገዜ የሚጠይቁት የንባብ የቅዳሴ የዜማ የአቋቋም የቅኔና የመጻሕፍት ትርጓሜ ትምህርቶቿ አሁን ከሚወስዱት እጅግ በጣም ባነስ ጊዜ ውስጥ መጠቃለል የሚችሉ መሆናቸውን ነው ይህ መፖግ መፍ የወጣቶች ሕይወት ሸከሚሆን ድረስ ደግሞ የመንፈሳዊ ትምህርት ጥማት ያለባቸው ምእመናን ሁኔታዎች እስከ ፈቀዱላቸው ድረስ በግላቸውም ቢሆን እንኳን ትምህርተ ቤተ ክርስቲያንን ከማጥናት መቦዘን የለባቸውም ሰው ምንም ቢማር ራሱን እንደ አዋቂ መቁጠር አይገባውም አዋቂ እንደ ሆነ የሚሰማው ሰው በትዕቢት ይይዛል ማንም አንዳች ያወቀ ቢመስለው ሊያወቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም ቆሮ በማለት ቅዱስ ጳውሎስ ተናግሯል መታወቅ ያለበትን ትህትናን ሳያውቃት ሰው አዋቂ ሊባል አይችልምቆ ትሕትና ደግሞ አዋቂ ነኝ አታሰኝም በዚህ ዓለም ካሉት ነገሮች ከቁጥር የማይገባን ጥቂት ነገር አውቆ አዋቂ ነኝ ማለት እጅግ የሚያሳፍር ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ «ዕውቀት ያስታብያል ቆሮ በማለት እንደተናገረው ዕውቀት ሲያስታብይ ፍቅር ግን ያንጻል ከዕውቀት ፍቅር በብዙ ይበልጣል ስለዚህ አንተ ብዙ ዕውቀት ቢኖርህ ትንሽ ፍቅር ያለው ሰው ይበልጥፃልና መታበይ አይገባህም ሰው ሁሉ ከትዕቢት ለመዳን ያወቀውን ፅውቀት ከሌሎች ሰዎች እንዳገኘውና በዕውቀት ከርሱ የተሻሉ በርካታ ሰዎች እንዳሉ ቢያስብ በጣም ይጠቀማል ከዚህም በላይ ዕውቀትን እንደ ገበቴ ውኃ ማፍሰስ ማጥፋት የሚቻለው ፈጣሪም እንዳለ ባይዘነጋ ጥሩ ነው ከአንተ አስቀድሞ የነበሩ ብዙ አዋቂዎች እንደ ቀለም ቀንድ ተሰብረው ተቀብረዋል ሌሎችም የትምህርት ማስረዳቸውን እያሳዮ የሚለምኑ ሆነዋል ከፊሉቹ ደግሞ አብደውና አእምሮአቸውን አጥተው የሚናገሩትን እንኳን አያውቁትም ታዲያ አንተ ከእነዚህ እንደ አንዱ ባለመሆንህ ማመስገን ሲገባህ የምትኩራራው ከእግዚአብሔር እጅ የምታመልጥ ይመስልዛልን። » ቆሮ መንፈሳዊ ትምህርት መንፈሳዊ ዓላማ ሲኖረው ሥጋዊ ትምህርት ደግሞ በአመዛኙ ሥጋዊ ዓላማ አለውፎ መንፈሳዊ ትምህርትን ከዓላማው ወጥቶ መብያና መጠጫ ቢያደርጉት ፈጣሪን ማስደሰት አይችልም አልፎ ተርፎም እንደ ቅኔ ባሉ መንፈሳዊ ትምህርት ፈጣሪን ለማመስገን መራቀቅ ሲገባ ፍጡርን ሲሹ እንደፈጣሪ ለማወደስ አልያም ደግሞ እንደ ዲያብሎስ ለመደምሰስ ቢጠቀሙበት ያለ ዓላማው ነውና ማስጠየቁ አይቀርም ስለዚህ በተማሩት ትምህርት ከመጠየቅና ከመጉዳት በአግባቡ በሥራ ላይ በማዋል መጠቀም ያሻል መኮትኮቻን መፍለጫ መፍለጫን ደግሞ መኮትኮቻ ማድረግ ያለፋል እንጂ ምንም አይጠቅምም እንደዚሁም ሁሉ መንፈሳዊ ትምህርትን ያለ ዓላማው ቢያውሉት ያስጐዳል እንጂ አይጠቅምም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «የሰው ሕይወት በገንዘቡ ብዛት አይደለምና ተጠንቀቁ ሉቃ በማለት አስተምሮርአል የሰው ሕይወት በገንዘቡ ብዛት አይደለም ማለት ባለው ነገር መጠን አይደለም ማለት ነው ስለዚህ የሰው ሕይወት በጉልበቱ በመልኩ በወገኑ በዕውቀቱ ልክ አይደለም አንዳንድ ሰዎች ግን ዛሬ ዛሬ ሕይወት በትምህርት ልክ መስሏቸዋል በዚህ ምክንያት በትምህርታቸው ማነስ ተስፋ በመቁረጥ በእጅጉ ያዝናሉ በዚህ ጉዳይ ብዙ ከማዘን መማር የሚችለብት መንገድ ካለ መማር የሌለ ከመሰላቸውም ምንም ሳይማሩ የተሻለ ኑር የሚኖሩትን ሰዎች ብ ዴዴ መ መ ዱዱ መ ኤበ ሓበ መ መ ሕይወተ ወራዙት በመመልክቾ አነርሱም አንደዚያ ከመኖሮ የሚያግዳቸው ነገር አንደሌለ በማመን ጠንክሮ መሥራት ይኖርባቸዋል ስለ ትምህርት ባለን የተዛባ አመለካከት የምንጉዳው እኛው ራሳችን ነን «ያልተማረ ይታሰር ወይም ይገደል። ነገር ግን ብዙ ወጣቶች «መልካም ስም» ያለውን ከፍተኛ ዋጋ አያውቁም እንዲህ የሚያስብለው ስማቸውን በክፉ የሚያጠፋ ርካሽ ተግባር ዘወትር ሲፈጽሙ መገኘታቸው ነው መጥፎ ነገሮች ምን ጊዜም ክፉ ስም ያስገኛሉ በሥውርና በድብቅ ቢፈጸሙ እንኳን ከጥቂት ቆይታ በኋላ በአደባባይ መውጣታቸው የማይቀር ነው «ድብቁን የምትገልጽ የውስጡን ወደ ውጭ የምታወጣው ሆይ» የሚባል እግዚአብሔር ሥራውን አይዘነጋምና መልካም ስም ከመልካም ሽቶ ጋር የተነጻጸረው ያለ ምክንያት አይደለም መልካም ሽቶ ርቆ ሄዶ ከመሸተቱም በላይ ስሜትን ይማርካል ይስባል መልካም ስምም አንተ ካላሰብከው ቦታ ደርሶ ያሳውቅሃል ያስወድድሃል ክፉ ስም ደግሞ እንደ ክፉ ሽታ ነው ያ ከሩቅ መጥቶ እነደሚበክል ተደብቆ የተሠራም ክፉ ሥራ ርቆ ሽ የወጣቶች ሕይወት ሙዴ ዴድ መው ሄዶ ስምን ይበክላል ስለዚህ በዘመንህ ሁሉ ከቁሳዊዋና ከብልጭልጭ ነገሮች ይልቅ ጥሩ ስም እንዲኖርህ ተጣጣር መልካም ስም ካለህ የተመኘኸውን ሁሉ ሳታገኝ አትቀርምና መልካም ስም የመልካም ሥራ ነው እንጂ የፈጠራና የማስመሰል ውጤት አይደለም መልካም ስም ያለውን ጠቀሜታ ለመረዳት ቀላል ነው እንኳን በብዙ አቅጣጫ ብዙ መልካም ስም ኖርህ ይቅርና «እገሌ ታማኝና እውነተኛ ነው» በሚል ስም ብቻ ብትታወቅ ብዙ ጥቅሞች ይከቡሃል ለምሳሌ እውነተኛ ሰው በብዙዎች ዘንድ ታማኝነትና አክብሮትን ያተርፋል የሚያገኛቸው ወዳጆቹ እውነተኝነቱን አድንቀውና ወደው የሚቀርቡ በመሆናቸው አብዛኞቹ ራሳቸው እውነተኞች መሆናቸው የማይቀር ነውና እውነተኛ በመሆንህ እውነተኞች ጓደኞችን እንድታገኝ ረዳህ ማለት ነው ይህ ደግሞ ታላቅ ትርፍ ነው የሰው ሁሉ ችግር ታማኝ ባልንጀራ ማፍራት አለመቻል ነውና ከዚህም ሌላ በመልካም ስም መታወቅ ሌላም የሚያስገኘው ጥቅም አለ የንግዱ ዓለም ብዙ ማጭበርበር ያለበት መሆኑ ይታወቃል ሆኖም አሠሪዎችና ሠራተኛ ቀጣሪዎች ለታማኝነት ከፍ ያለ ዋጋ ሰጥተው እውነ ኞችንና ታማኞችን መቅጠር ይፈልጋሉ ስለዚህ አንተ በታማኝነት መታወቅህ ብቻ በሥራ ችሉታ ብዙ የሚበልጡህ ሰዎች ቢኖሩም እንኳን ሥራ የማግኘትና ሌሉች ከሥራ በሚባረሩበትም አጋጣሚ በሥራህ የመቆየት ፅድል ይገጥምሃል ይህም «ታማኝ» የሚል መልካም ስም ማትረፍ ብቻ ምን ያህል አንደሟጠቅም ያስረዳል ሕይወተ ወራዙት ባልና ሚስት በታማኝነት የሚተዋወቁ ከሆነ ጥርጣሬንና አለመተማመንን አስወግደው በፍቅር ለመኖር ይረዳቸዋል ታማኝ ልጆችም በወላጆቻቸው ዘንድ ሙሉ አመኔታን ያተርፋሉ ልጆች በወላጆች ዘንድ «ታማኝ» በሚል መልካም ስም ከታወቁ ቀስ በቀስ ሰፊ ነፃነት እያገኙ ይመጣሉ እውነቱን መናገር ተግሣጽን እንኳን ቀላል የሚያደርግበት ሁኔታ አለ አንድ ታዳጊ አጥፍቶ በሚቀጣበት ጊዜ ቢክድ የቅጣቱ መጠን ሊጨምር ይችላል። ቢያምንና ይቅርታ ቢጠይቅ ግን ቅጣቱ ይቀልለታል በወኅኒ ቤትም ሆነ በእግዚአብሔር ዘንድ ቢሆን ሐቁ ይህ ነው ሰው ሁሉ በሕይወት ዘመኑ ሌሎች እንዲያምኑትና ቃሉን እንዲቀበሉት በብርቱ የሚፈልግበት አንድ አጋጣሚ ሳይመጣበት አይቀርም ታማኝ የሚል ስም ያለው ሰው በዚህ ሁሉ ሳይቸገር ነገሩን ሌሎች በቀላሉ ሊያምኑለት ይችላሉፎ በአጠቃላይ «ታማኝ» የሚል መልካም ስም ያተረፈ አንድ ሰው ተዘርዝረው የማያልቁ ብዙ ጥቅሞችን ያገኛል ከላይ የተጠቀሰው ስለ «ታማኝነት» ብቻ ነው ከዚህ በተጨማሪ ሐቀኛ የተከበረ ጨዋ ሰው አክባሪ ቁጥብ ቁም ነገረኛ ዐዋቂ ትሑት የሚሉ ሊሎች መልካም ስሞችን ብታተርፍ ምን ያህል በነፍስና በሥጋ እንደምትጠቀም ገምት እነዚህ ነገሮች ያሉት ለሥራ ለጓደኝነት ለትዳር በአጠቃላይ ለሁሉም ጉዳይ በመብራት እንደሚፈለግ ጥርጥር አይኑርህ መልካም ስም እንዲሁ በቀላሉ አይገነባም ብዙ ድካምና ጥረት ከመጠየቁም ሌላ ብዙ ጊዜ ይወስዳል የሚያስደንቀው ግን ጥሩ ስም ሲበላሽ ምንም ጊዜ አለመፈለጉ ነው ስለዚህ መልካም የወጣቶች ሕይወት ስምን እንደ ዓይን ብሌን ሊጠነተቱለት ይገበል መልካም ስም ገንዘብ የትምህረት ደረጃ ወይም ሌላ መስፈርት አይጠይቅም ፈቀደኛ ከሆንክ የነፍስህ ዕውቀት ብቻ መልካም ስም አንዲኖርህ ለምትሠራው ሥራ ሁሉ በቂ ናት የመልካም ስምን ጠቀሜታ መዘርዘር በአንፃሩ የመጥፎ ስምን ጉዳት መዘርዘር ነው በመጥፎ ስም ከታወቅህ የእናትህ ልጅ እንኳን አያቀርብሀም ስለዚህ በሰካራምነት በቅብጠት በአባካኝነት በውሸት በቀልድና በመዘበት በመልከስከስ በገንዘብ ወዳድነት በትዕቢት በክህደት በስሜታዊነት በተናጋሪነትና በመሳሰሉት መጥፎ ስሞች እንዳትታወቅ ተጠንቀቅ በገዛ እጅህ ሁሉ ነገር ርቆብህ ቁጭ ብለህ የምታለቅስበትን የኀዘን ገመድ ለምን ትጎትታለህ።