Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ምዕራፍ አራት የእግዚአብሔር ባርያ አገልጋይ መሆን አያስፈልገንም ተአምረ ማርያም የተባለው ይህ መጽሐፍ እመቤታችን እንዲህ አደረገች በረከቷ በእኛ ይደርብን ሲል ቆይቶ ሊል የፈለገውን ዋና ዓላማውን እንዲህ በማለት አስፍሮታል። በሥላሴ ትምህርታችን በክብር በሕልውና በመሰኮት አንድ የሆነ ሦስት አካላት የሚለውስ ሊፋለስ አይደለምን መናፍቃን ምን ያህል በክህደት እንደስለጠኑ ያሳየናል ከዚህ የተነሣ ስብሐት ለእግዚአብሔር ተብሎ ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር እየተባለ ይዘመራል ይጻፋል ይህም ማለት እግዚአብሔር እንዲመለክ እንዲመሰገን የሚገባው ከሰው በወጣ መስፈርትና ፍላጎት ላይ በተመሠረተ መመሪያ ሳይሆን ሊመሰገንበት በሚሻው መንገድና ሁኔታ እንዲከበር ባለሥልጣኑ እርሱ ሆኖ እያለ እንደመሰላቸው ወይም ይህም መልካም ነው በሚል ሰውኛ እሳቤ ሊያመልኩት የሚወዱ ሁሉ ከእግዚአብሔር ፍርድ እንደማያመልጡ ሲናጋር እንደ እግዚአብሔርነቱ ስላላከበሩት አሰ ሕዝባችን እግዚአብሔርን የሚፈራ የሚወድ እየተባለ ረጅም ዘመን ተነግሮ ለታል ይመስላልም ይሁን እንጂ እግዚአ ብሔርን መፍራት ለእግዚአብሔር መታዘዙ ዕገሌ እንዳለው ዕገሊት እንዳላቸው በሚል የተንኮለኞች ፈሊጥ የተሞላ በመ ሆኑ በልቡ የራቀ በከንፈሩ የሚያመልክ ሆኗል ይህ የተሸፈነ መንፈሳዊነት ምንም ነገር ቀና ብሎ ለማየት ዕድል ስለማይሰጠው በሕይወቱ ላይ የተደገሰውን የጠላት እቅድ ያለተቃውሞ ሲያስተናግደው ኖሯል «ለሰው ልጆች ሲል በመስቀል ላይ የተሰቀለ የእሾህ አክሊልን በራሱ የደፋ መርቆሬዎስ ነው» ብለው ሲያዜሙለት አሜን ከማለት ውጪ አማራጭ የሌለው ሕዝባችን ክፉዎች ካስተማሩትና ካስለመዱት የተንኮል ትምህርት መላቀቅ የሞት ያህል ሆኖበት ዛሬም እንኳ ዕድሜውን በቪያው እንዲያሳልፍ ሆኗል በዚህ ድርሳነ ዑራኤል በተባለ መጽሐፍ እንዲህ የሚል ክህደት ይገኛል ልቡን በክፉዎች ትምህርት የተነጠቀው ሕዝ ባችን ይህንና ይህን መሰል በሃይማኖት ሽፋን የተለበደ ወንጀል አየተፈጸበት ሳይ ረዳ ቆይቷል ጽሑፉ ሲመዘን ጽንስን የሚሰጥ ማን ነው ። ጡታል በአዲስ ኪዳን መግቢያ መሸጋገሪያ ላይ የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ሰሞነኛ የነበረው የካህኑ የዘካርያስ ሚስት ኤልሳቤጥ መካን በነበረችበት ጊዜ ካህኑና ሚስቱ በእግዚአብሔር ፊት ተሰምቶልፃል » አለው ሉቃ ዘካርያስ ይጸልይ የነበረው ወደ ዑራኤል ነው ። ወይስ ወደ እግዚአብሔር።
ብንል ጌታችን በዮሐ እንደገሰጠው « የማይወደኝ ቃሌን አይጠብቅም » እንዳለው መሆኑ ይገልጥልናል ይህን በተጨባጭ ለማስረዳት የገድል የድርሳንና የተአምር ጸሐፊዎች እንደገለጡት እነርሱ ጻድቃን ሰማዕታት እያሉ የሚጠሩአቸው ሰዎች ከጌታችን ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ይልቅ ጸሐፊዎቹ እመቤታችን እያሉ ለሚገልጧት ፍቅር አክብሮት ምሥጋና ውዳሴ አምልኮ ይሰጡ እንደነበር በውዳሴ ማርያም ትርጓሜ እንዲህ ይነበባል « ቅዱስ ኤፍሬም የተባለው ሰው የውዳሴ ማርያሙ ጸሐፊ ያሉት ሲመጸውት በሥላሴ ስም በመላእክት በሰማዕታት ስም አይመጸውትም ነበር ለምን ቢሉ እመቤታችንን ከመውደዱ የተነሣ እመቤቴ ምሥጋናዋ እንደ ሰማይ ኮከብ እንደ ባሕር አሸዋ በዝቶልኝ እንደ ልብስ ለብሸው እንደ ምግብ ተመግቤው ጠግቤው እያለ ይመኝ ነበር እ» ብለው የሰውየውን ቅዱስነት አስፍረዋል ውዳሴ ዘሰኑይ ገጽ እንዲያውም ይላሉ ጸሐፊዎች ይህ ሰው « የድንግል ማርያምን ክብር ተናግሮ መፈጸም የሚቻለው አንደበት አስተውሎ የሚወስን አእምሮ የለም አንቺንም የሚመስል ማንም የለም » በማለት ሲያከብር እንደነበር ጽፈውለታል ከእግዚአብሔር ይልቅ እነርሱ ድንግል እያሉ ለሚጠሯት ሴት ፍቅር ክብር የነበራቸው እነኝህ ሰዎች እግዚአብሔርን ማገልገል ከንቱ ነው ለእግዚአብሔርም ባርያ መሆን አይረባንም በማለት የአላማቸውን ፍጻሜ የእመቤታችን ተአምር በማለት እነሆ እስከ ዛሬ ድረስ አሜን እያሰኙ ኖረዋል የእግዚአብሔርን የብቻው ባህርይ ሳይቀር ለእርሷ በመስጠት የሚታወቁት ጸሐፊዎች የምታደርጉትን ሁሉ በእግዚአብሔር ስም አድርጉት የሚለው የሐዋርያት ትምህርት ለእነርሱ የፌዝ ያህል ሆኗል የሚገርመው በዚህ ትዕዛዘ እግዚአብሔርን የማፍረስ ትምህርታቸው ከአንባቢዎች ሆነ ከሰሚዎች ለምን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እናፈረሳለን። የክርስትናችንና የመጽሐፍ ቅዱስ ማዕከል የሆነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆነ ሐዋርያት አባቶቻችን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ባስተላለፉልን መልእክታቸው ለትምህርት ምሥክር ወይም ለአብነት የቅዱሳንን ስም በድክመታቸው ሆነ በብርታታቸው አንሥተው ቢጽፉም ለፈውስ ለበረከት ለጽድቅ ለቅድስና ለዘላለም ሕይወት ዉዜተ የተጠቀሙበት ስም አንድ « ኢየሱስ ክርስቶስ » ብቻ ነበር የእኛዎቹ ግን « የድንግልን ስሟን ማውሳት ብቻ በቂ ነው » በማለት ይተርታሉ መጽሐፍ ቅዱስ ለምህረቱና ለፍቅሩ ወሰን የማይገኝለት ቸሩ አምላካችን እግዚአብሔር አንድያ ልጁን ሰጠ ይላል ቅዱስ መጽሐፍ ተአምረ ማርያም ደግሞ «እርሱ እርሷን ሰጠን» ይላል አያይዞም «የማርያም ባሪያዎች ለመሆን እንሽቀዳደም» ብሏል አምልኮ ባዕድን የሚያለማምደው አመንዝራው ደራሲ አብ እንኳ በማንም ላይፈርድ በረከታችንንም ሆነ ፍዳችንን ሊሰጠን የተመደበውን ጌታ ትተን ዕሩቅ ብእሲን እንድንከተል ይሰብከናል ሮብዓም በይሁዳ ሲነግሥ ኢዮርብዓም በሩ ነገድ በእሥራኤል ላይ ነገሠ «ኢዮርብዓም በልቡ ይህ ሕዝብ መሥዋዕት ለማቅረብ ወደ ኢየሩሳሌም ሲሔድ የዚህ ሕዝብ ልብ ወደጌታቸው ወደ ይሁዳ ንጉሥ ወደ ሮብዓም ይመለሳል እኔንም ይገድሉኛል አለ ንጉሥም ተማከረ ሁለትም የወርቅ ጥጆች አድርጐ አሥራኤል ሆይ ወደ ኢየሩሳሌም ትወጡ ዘንድ ይበዛባችኋል ከግብጽ ምድር ያወጡህን አማልክቶችህን እይ አላቸው አንዱን በቤቴል አንዱን በዳን አኖረ» ነገ ተብሏል ይህ ክፉ ንጉሥ እሥራኤልን ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት የተጠሉ ለማድረግና የራሱን ጥቅም ለማስከበር ሲል የቃል ኪዳነን ሕዝብ ከአምላኩ እንዳራቀውና በምትኩ የጥጃ ምሥልን እንዳቆመለት ሁሉ የእኛዎቹም ክፉዎች ከምህረቱ አዳራሽ እንድንወጣና እግዚአብሔር መድኃኒት ብሎ ያልሰጠንን እንድንቀበል ያባብሉናል ውሉደ ዓመፃ የሆኑት እነዚሁ ደራስያን «ከልጂ ጐን በፈሰሰ ደሟ ንጽሐን ታደርገናለች» ይሉናል « ወስማስ ለቅድስት ድንግል ጽሑፍ ውእቱ በቀለመወርቅ ውስተ ፍጽሞሙ ለኃጥአን ወእንዘ ይቀውም እግዚእነ ውስተ ዓውደ ፍትሕ ሶበ ይሬኢ ስማ ለድንግል ውስተ ፍጽመ ኃጥአን ይነሥት ዓውደ ወይገብእ ድኅሬሁ ምስለ መላእክቲሁ ቅዱሳን ወኩሎሙ ኃጥአን ይገብኡ ምስሌሁ ውስተ ገነተ ትፍሥሕት ዘእንበለ ሐተታ » ትርጉም « የቅድስት ድንግል ስም ግን በኃጥአን ግንባር ላይ በወርቅ ቀለም ተጽፏል ጌታችንም በፍርድ አደባባይ ሲቆም ሳለ የድንግልን ስም በኃጥአን ግንባር ላይ ተጽፎ ባየ ጊዜ ፍርዱን አፍርሶ ወደኋላ ይሸሻል ቅዱሳን መላእክቱም ከእርሱ ጋር ያለፍርድና ያለወቀሳ ደስታ ወዳለበት ገነት አብረው የገባሉ ስሟ በኃጥአን ግንባር ላይ ይጻፋል አግዚኦታ የሚያሻው ኪርያላይሶን የሚያስፈልገው ብቻ ሳይሆን የሥጋ ዘመናችን እስኪቆረጥና ጠደጌታ እስክንሰበለብ ድረስ ዓይኖቻችን ከእንባ እንዳይቋረጡ የሚያስገድድ በቤተክርስቲያናችን ላይ የተፈጸመው ወንጀል ይህ ነጦጡ የጸሐፊዎች የድርሰት ዓይነት ዛሬ ምናባዊ እየተባለ በሚነገረው የሥነ ጽሑፍ ዘዴ የተከሸነ በመሆኑ ሕሊናቸውና የሚያገለግሉት የዚህ ዓለም አምላክ ያቀበላቸጡን ሥዕል በብራና ላይ ሲያሰፍሩት ዛይማኖተኛ ለሆነው ሕዝባችን ለማስረዳት አይቸገሩም በበጎ መልኩ በቅዱሳን ግንባር ላይ ማኅተም አንዳለና እንደሚደረግ የራዕይ መጽሐፍ በምዕራፍ ሰባት ቁጥር ሦስት ላይ እንዲህ ያስረዳናል « የሕያው አምላክ ማኅተም ያለው መልአክ ምድርንና አየርን ሊጎዱ ለተሰጣቸው ለአራቱ መላእክት በታላቅ ድምጽ እየጮኸ የአምላካችንን ባሪያዎች እስክናትማቸው ድረስ ምድርን ቢሆን ወይም ባሕርን ወይም ዛፎችን አትጉዱ ቸው ኔ» ይላል እነዚህ በቁጥር ተለይተው ይታተሙ ዘንድ የተነገረላቸው ሰዎች ማኅተም « የሕያው አምላክ ማኅተም በሚባል ማኅተም እንደሚታተሙ ተገልጧል ሌላውና መጽሐፍ ቅዱስ ሐሰተኛው ክርስቶስ እያለ የሚጠራው የአግዚአብሔር ተቃዋሚ ለሆነው ተከታዮች በግንባራቸውና በእጆቻቸው መዳፍ ላይ የሚደረገው ማኅተም ሲሆን ይህም ምልክት « የአውሬው ስም ወይም የስሙ ቁጥር እንደሆነ ተገልጧልየአውሬው ስም የተባለው በግልጥ ምን እንደሚል ባይታወቅም ይህ ስሙ በቁጥር ሲገለጥ ነው ተብሏል ራእ እንግዲህ መጽሐና በሕያው አምላክ ማኅተም የሚታተሙና በሐሰተኛው መሚሕ ስም ቁጥር የሚታተሙ ባሪያዎች እንዳሉ እንዲህ ተለይተው አሉ እያለ የተአምረ ማርያም ጸሐፊዎች ደግሞ ሌላ ሦስተኛ የማኅተም ስምና የሚታተሙ ሰዎችን ፈጥረው የማርያም ስም በግንባራቸው ላይ ይጻፍባቸዋል » በማሰት ፈዋል አነዚህ ሰዎች ከሁለቱ አንዱ ካልሆኑ ሌላ ሦስተኛ ማኅተምና የማኅተም ስም አለ ብሉ መጽሐፍ ቅዱስ ያልገለጠ በመሆኑ ምናልባት ከሁለቱ ባንዱ ለመደባለቅ የሚጠሩበት ኅቡዕ የብዕር ስማቸው ይሆንን መቼም በሕያው አምላክ ማኅተም የሚታተሙት ማኅተ ማቸው የሕያው አምላክ ማኅተም ተብሉ ስለተለየና የሚያሳፍር ባለመሆነ በኅቡዕ ስም ሆነ በብዕር ስም ለመጠራት የሚያስፈልግ ባለመሆነ የጸሐፊዎቹ ማኅተምና የማኅተሙ ባለቤት እግዚአብሔር ወይም የእግዚአብሔር ወገኖች ሊሆኑ እንደማይችሉ ሚሊዮን ጊዜ ግልጥ ነው እንግዲያውስ ያልተገለጠውና ከባሕርዩውም እንደሚታየው መምሰል መለዋወጥ ልማዱ የሆነው አልያም በተቀያሪ ስም በቁጥር የተጠራው የሐሰተኛ ው ክርስቶስ ማኅተም መሆን ይኖርበታል ያም ሆነ ይህ ዓለም ከተፈጠረ ጆምሮ እስከ ፍጻሜ ዓለም ድረስ ያገለግል ዘንድ በተሰጠን መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ «ህሉ የድንግል ስሟ በቀለመ ወርቅ ሆኖ በኃጥአን ግንባር ላይ ይጻፋል» የሚል ወይም ሐዋርያት በየትኛውም የስብከትና የትምህርት ዘመናቸው ለሰከንድ እንኳ ያልተናገሩት ተቀባይነትም የሌለው ወንጀል መሆኑ ሊታወቅ ይገባል መቼም የፈጠራ ጽሑፍ በቤተክርስቲያናችን ተነስተው ለነበሩት መናፍቃን የማይነጥፍ ችሉታና ጸጋቸው ከአጋንንት ሆኖ ዓለም ቢያደንቅላቸውም ለልብ ወለድ ጽሑፍ በታሪክ ለሀገሪቱ አስተዋጽኦ እንዳደረጉ ቢደነቁም መንፈሳዊ ሽፋን እየቀቡ ወደ ቤተ መቅደስ ማስገባታቸውን ግን ያለርኅራጌዔ የምንቃወመው ነው ኢየሱስ በኃጥአን ግንባር ላይ ያለውን የድንግልን ስም ይፈራዋል እንደደራስያነኑ ሐሳብ ይህችው እነርሱ ማርያም የሚሏትን ሴት ስም በግንባራቸው ላይ የያዙ ኃጥአን ለፍርድ እንዲቀርቡ ሲደረግ ፈራጁ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፍርድ ወንበር ሲቀመጥ ታትሟል የተባለውን ስም ሲመለከት ደንግጦ ሊፈርድ የመጣበትን ጉዳይ ሁሉ ትቶ በአንድ ሰው ላይ እንኳ ሳይፈርድ ወደ መጣበት ይመለሳል ይሉናል እንዴት የትምህርት መፋለስን ወደ ቤተክርስቲያኒቱ እንዳስገቡ ያለክልካይም ያሻቸውን ማለት እንደቻሉ ተጨማሪ መረጃ ነው ሄቻሦ ፏ ደራዕ ሪም ፈራ ደራስያኑ እንዳስቀመጡት በኃጥአን ግንባር ላይ የተጻፈውን ስም ሲያየው ሳማቀመጥ እስኪያቅተው ድረስ ኃይል በግባንራቸው ላይ እንዳየ አሳይተውናል ይሁን እንበልና ተረቱ በሥጋ የወለደችው በቤቷ ያሳደገችው በመስቀሉ በስደቱ አብረው የነበረችው የእናቱን ስም ከሆነ ምን አስደነገጠው። ኛ ቆቁሮ የክርስትና እውነት ይህ ሆኖ ሳለ ይህንንም መመስከር ማስተማር ግብራችን ሆኖ እያለ በኋላ የበቀሉ ከዓሣ ጋር የተደባለቁ ጊንጦች ይህን የእግዚአብሔር ሐሳብ ወደ ጐን በመተው እንዲህ ይላሉ ማንም ስሙንና የልጁን ስም ወለተ ሚካኤል ገብረ ሚካኤል ወለተ ገብረ ማርያም ብሉ የሰየመ ሁሉ በዚህ ስም ምክንያት መንግሥተ ሰማያት ሰተት ብሎ ይገባል በማለት ይናገራሉ ድርሳነ ሚካኤል ተአምረ ማርያም ጽድቅ ቅድስና ጥበብና ቤዛነት «በክርስቶስ ሆነ ተብሎ በኛ ቆሮ እያለ በሚካኤልና በማርያም ስም ስሙን የጠራ ይጸድቃል የሚለው ክህደት መልከ ጥፉን በስም ይደግፉ እንዳሉ ሰይጣንን አንተ ቅዱስ ብንለው ከቶ ከባሕርዩ ፈቀቅ እንደማይል ሁሉ እንዲሁ መሆናቸው ነው እንኪያስ በስመ ሚካኤልና ማርያም ቀርቶ ወለተ ገብረ ኢየሱስ ወለተ ገብረ አብ ወለተ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ብለን ብንሰይም ማንም አይጸድቅም በብሉይ ኪዳን እንደነበረው ስም ግብርን ይገልጣል የሚባለው ዛሬ የሚሠራ አይደለም አይሆንምም ገብረ ኢየሱስ ሆኖ በአማናዊ ግብሩ ገብረ ዲያብሎስ ሞልተውናልና ስለሆነም በዚህ ትምህርት ተጠምደው ያሉ ቤተሰቦቻችን ስምን በሚወዱት ጻድቅና ቅዱስ መልአክና በእግዚአብሔር እየለጠፉ ቢያወጡት በኢየሱስ ብቻ አምኖ ካልኖሩ ጽድቅ እንደሌለ ያውቁ ዘንድ ይህን መጽሐፍ ለሚያነቡ ሁሉ ኃላፊነታቸው ነው እንላለን ሚስቱ መበለት ትሁን ልጆቹም ይበተኑ በዚህ ርዕስ ደስ ብሎት አሜን ይሁን ይደረግ ለማለት ከዚህ በፊት አልያም በኋላ ያለውን ሙሉውን ሐሳብ ካልተረዱ አሜንታዊ አደጋ ሊኖረው ይችል ይሆናል ምክንያቱም መጽሐፍ እንደሚለው ሰው የሚባለውን ሰምቶና ለይቶ ሲገባው የሚጠቅመው ከሆነ «አሜን» ይላል እንጂ ካልሆነ አለመተባበር እንደሚገባ ያስረዳሉ ሆኖም ብዙው የቤተክርስቲያናችን ምዕመን አገልጋዩቹን በእግዚአብሔር ፈንታ ስለተቀበላቸው ብቻ የአገልጋዮች ከንፈር ይንቀሳቀስ እንጂ ፈጥኖ እልል አሜን ማለት ፍጥነቱን መላእክት እንኳ አይቀድሙትም አንድ ጊዜ በአንድ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ሰባኪው አዳም አትብላ ተብሎ የታዘዘውን በመጣሱ እግዚአብሔር እርቃኑን አስቀረው ወደ ምድረ ፋይድ ሰደደው የታአባቱ ብለው ሞቅ ሲያደርጉት በሐሳብም በመንፈስም በእግዚአብሔር ፊት የሌለው ሕዝብ በአካል « እልልል » በሚል ድምፅ ጉባኤውን አቀለጠው በተገኘበት ቁጥር ቤተክርስቲያን ሆኖ ከሐሳቡ ሰመመን አለሁ ለማሰት ያህል እልል ይበል እንጂ ምን እንደተባለ እንኳ አያውቅም አንድ ሰው ከዓውደ ምህረቱ ራቅ ብሎ በቆመበት ሥፍራ ጓደኛው ዝግይቶ ሲደርስ ድንገት ቅልጥ ያለ ሳቅ ዓውደ ምህረቱን ሞላው ያ ዘግይቶ የመጣ ስውም «ለመሆኑ ምንድን ብሏቸው ነው ሰባኪው ሲናገር ሕዝቡ የሳቀው አለው እኔ እንጃ አለ ታዲያ አንተ ለምን ሳቅህ ሲለው እንዲያው በጸጋው ነው» አለው ይህ እንዲያው በጸጋው ነው በሚል ሽፋንና ከቤተመቅደስ መቼም ክፉ ነገር አይገኝም በሚለው የዋህነት አሜን ማለትና አብሮ መደለቁ ብዙዎችን ያለ ክርስቶስ እንዳስቀረ ምሥክር እንጠቅሳለን ያለ አስተርጓሚ በሚነበነበው ቋንቋ መጀመሪያና መጨረሻ ላይ በሚነገሩ ማደናገሪያዎች አልያም ከአማርኛ ጋር ቅርበት ያላቸው ቃላትን በመደባለቅ ተፈላጊውን ድጋፍ ለመቀበል በማድረግ ጥበብ ሕዝባችን ተታሎ ይኸው ያለ ክርስቶስ አለ ያላነበበውንና ትርጉሙን ያልተረዳውን መጽሐፍ እየተሳለመ ሰውነቱን እያሻሸ የሚፄደው ሕዝባችን መተኪያ የሌላትን ነፍሱን ለአገልጋዮቹ አደራ ሰጥቶ የሚኖር ነው ከዚህ የተነሣ እርሱ ያለ ክርስቶስ የሆነውን የመጽደቅ ሙከራ ማለትም በምግባር በትሩፋት ሊጸድቅ የሚደክምበትን ኃሳብ አልሳካ ሲለው በቅዱሳኑና በመላእክት በዓላት ዝክር ማድረግን ጨምሮ ዕረፍት ባለማግኘት በመጨረሻም ነፍሉ ከሥጋው ስትለያይ እንኳ ወዴት እንደሚሄድ ባለማወቁ ሲኦል እንዳይገባ በቀሪ ዘመዶቹ ላይ ተበድረው የማይጨርሱትን ዕዳ ከቀን ዓመት ጥሎላቸው ያልፋል ያሳደጉት አገልጋዩቹ ደግሞ የደነገጉትን ሥርዓተ ፍትሐት ቤተሰቦች ካሟሉ እንደ ቢሮ ሥራ የቆጠሩትን የፍትሐት ሥርዓት ለማድረግ ቃል ይገቡለታል ይህ የሙታን ፍትሐት ሥርዓት በሕዝባችን ዘንድ የተወደደ የተለመደና በሰባኪዎችም አስፈላጊነቱ ስለሚገለጥ ፍትሐት ከሚያጣ ራሱን ክርስቶስን ቢያጣው እንኳ የሚመርጠው ባህሉ ሆኗል ንድ ን በሠራተኞቹ አገላለጥ ፍትሐት አገልጋዮች የመቅደሱ ሟቹ ያልተናዘዘበት ኃጢአት ቢኖርበትና በዚህም ምክንያት ወደ ሲኦል ቢጣል በሚደረገው ጸሎትና ምልጃ ወደ ገነት ይዛወር ዘንድ እግዚአብሔርን የመለመን የመጠየቅ ሥርዓት ነው ይህም እናንተ ያሠራችሁት የታሠረ ይሆናል የፈታችሁት የተፈታ ይሆናል ተብሏልና ይላሉ ሆኖም ፍትሐት የሚለውን ሐሳብ የቀደሙትና ደጋግ የተባሉት ክርስቲያን አባቶች ይጠቀሙበት የነበረው ክርስቶስን በማመን ደህንነትን የተቀበለ አንድ ሰው ይህን ኅብረቱን በጥምቀቱ በአደባባይ በመመሥከር የቤተከርስቲያን ከቅዱሳን ጋር አባልነቱን ሲገልጥ ቤተክርስቲያን ለጌታ ሥራ እንደተቀበለችው እንዲሁ በምድር አገልግሎቱን ፈጽሞ ወደ ጌታ ሲሰበሰብ ቤተክርስቲያን ወደ እረፍት የሄደውን ሰው አስክሬን በክብር አምላካቸውን አያመሰገኑ እስከ ጊዜ ትንሣኤ ይቆይ ዘንድ ወደ ተዘጋጀለት ምድር ለመሸቼት የሚደረግ ሥርዓት እንጂ የጐደለ ጽድቅ ሰመሙላት ያልታረመ ኃጢአት ለማረም አልነበረም ይደረግ ቢባል እንኳ የሚደረግ አይደለም ይህን አባባል የሚደግፍልን ከጸሐፊዎቹ ዓይን ተጋርዶ ግን በፍትሐት የሟቹን ኃጢአት እናሰተሰርያለን በሚሉት ተጽፎ ያለፈ ጽሑፍ እንዲህ በማለት ያፈርስባቸዋል « እምድኅረ ሞቱ ለሰብእ አልቦቱ ንስሐ » መጽሐፈ ግንዘት ይህ አንቀጽ በአንዳንድ የግንዘት መጻሕፍት ፍቀው በማውጣት አንዳይታይ አድርገዋል ሆኖም በዚያው በያዙት መጽሐፍ ላይ የዚህ ተመሳሳይ እንዳለ ማሳየት እንጠዳለን « አስመ አኮ በውስተ ገፃነም ዘቦ ንሥሐ ወአኮ አምድኅረ ሞት ዜና ፅረፍት » ትርጉም « በገዛፃነም ንሥሐ የለም ከሞት በኋላ እረፍት የለም » መጽሐፈ ግንዘት ገጽ እንዲሁም በትዕዛዙ ገጽ ላይ በዚሁ መጽሐፍ እምድኅረ ሞቱ ለሰብእ አልቦቱ ምሕረት » ያሠራችሁት የታሠረ የፈታችሁት የተፈታ ይሆናል የሚለውን ቃል እውነተኛ የቤተክርስቲያን መምህራን ሲተረጉሙት ሰውየው በሕይወቱ እያለ ቃለ ወንጌልን ሰምቶ ተረድቶ ወደ ክርስትና ቢቀላቀል ይህ ሰው በትምህርተ ወንጌል ከነበረበት የኃጢአት እስር ተፈትቶ መጥቷልና ጌታችን ፈታችሁት አላቸው ይህ ሰው የእናንተን ምስክርነት የሰማ እኔን ሰምቷል እንዳለ ጌታ በሰማይም የተፈታ ነው አላቸው እንዲሁም የወንጌልን ቃል ሰምቶ ግን አቃሎ በክርስቶስ ማመንን አሻፈረኝ ቢል በቤተክርስቲያን የተነቀፈ በእግዚአብሔርም ጽድቅ ያልታሰበ ሆኗልና ከቤተክርስቲያን ተለይቷል በዚህ ዓለም ኃጢአትና አገዛዝ ተይዚል ማለት ነው እናንተ ያልተቀበላችሁት ወንጌልን ባለመቀበሉ በሰማይም እንዲሁ ነው ሲል ያሠራችሁት አለ ይላሉ የእኛዎች ግን የሚካኤል ዕለት አርሠፃል እንጨት ሰብረፃል የገብርኤል ፅለት ሥራ ሠርተሃል ወ ቭ ተ እያሉ ገዝቸፃለሁ አስሬዛለሁ በማለት ማሰርና ከኀቨፐዝቨሸ ሽ መፍታትን የሥልጣን ባሕርይና የግለ ሹመታቸው አድርገው ተጠቅመውበታል የቤተክርስቲያናችን ሕዝብ ግን ይህን ሳይረዳ የካህናት ጸሎት ሳይደርስለት እንዳይቀበር በማለት አስከሬን በመያዝ ቤተክርስቲያን ይመጣል በመጣው አስክሬን ላይ ምን እንደተባለ ሳያውቁ እንበል አቡነ ዘበሰማያት ሲባል ብቻ አሜን ይላል የመጽሐፈ ግንዘት አፈጣጠር አንድ ክፉና ጨካኝ እግዚአብሔርንም የማይፈራ ዘመኑን ሁሉ በዝሙትና በርኩሰት እያሳለፈ የነበረ ሰው ነበር ይህ ሰው በሞተ ጊዜ በጊዜው ኤሏስ ቆፅስ የሆነ ልጅ ነበረው ይላል የፈጣሪዎቹ ትረካ ልጁም ኤስ ቆጸሱ ለሞተው አባቱ ለፅ ቀናት ያህል አለቀሰለት በዚህ ጊዜ ነፍሱ በሲዖል እንዳለች አወቀ በመጨረሻም መልአኩን በጠየቀው ጊዜ ክፉዎች ንሥሐ ያልገቡ እዚህ ገፃነም እንደሚገቡ ሲነግረው ለ ቀናት ያሀል ቁርባን እያስወጣ አስቀደሰለት አስጸለየለት ወይም አስቆረበለት የሚበላ ድግስ እያስደገደሰ ማለት ነው በዚህ ሥርዓት መሠረት በሲዖል ነበረ የተባለ አባቱ ከሲኦል ውስጥ ከአንገት በላይ ብቻ ብቅ ብሉ ታየው በዚህ የተነሳ እስከ ዓመት እየጾመ ሲያስቆርብለት ነፍሱ ከገዛነም ሙሉ በሙሉ ወጥታ ገነት መንግሥተ ሰማያት ገባች ይላል ተረቱ ስለዚህ ይህ የግንዘት መጽሐፍ አገልግሎቱ ለሕዝቡ ደርስ ዘንድ ይህን እንደጻፉ ጸሐፊዎቹ ሳያፍሩ ጽፈውታል ግንዘት ገጽ ጦር ሜዳ አውሬ በልቶት ውኃ ወስዶትአስክሬኑ የጠፋ ሰው ካልሆነ በስተቀር ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ደርሶ ጸሎተ ፍትሐት ሳይደረግለት የተቀበረ ሰው በቤተክርስቲያን አለ ብንል ምናልባትም በዘመነ ሶሻሊዝም ብቻ ነበር ያም ቢሆን አስከሬኑ ቅጥረ ቤተክርስቲያን ባይገባም ጠበል ጣዲቁ ተዘጋጅቶ በየስማቸው ፍትሐት ሳይደረግላቸው አይቀሩም በፍትሐት ሕግ መሠረት ታንቆ የሞተ ገደል ገብቶ የሞተ ዛፍ ሲቆርጥ ወድቆ የሞተ ውኃ የወሰደው ሰው ፈጽሞ ፍትሐት የማይደ ረግለት እንደሆነ የታወቀ ነው የፍትሐቱ ዓላማና ፋይዳ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ድጋፍ የሌለው ከመሆኑም ባሻገር እውነተኛውን የእግዚአብሔር ቃል የሚቃረን መሆኑ ነው የፍትሐት ሥርዓት ባለሙያዎች እንደ ሚሉት የሟቹን ኃጢአት ለማስተሰረይ ካህናት በተሰጣቸው ሥልጣን መሠረት ማስፋቅ ስለሚችሉ የእነርሱ ፍትሐትና የሟቹ ቤተሰብ ከቀንዓመት ድረስ ያለው ድግስ ተደምሮ እንኳንስ ተረስታ ያልተናዘዚትን ትንሸዋን ኃጢአት ይቅርና ሲኦል እንኳ ገብቶ ቢሆን ወደ ገነት እንዲገባ ሊያደርጉ እንደሚችሉ ይናገራሉ ፍትሐቱን ፈላጊዎችና የሟቹ ቤተሰቦች ይህን ስብከት ተቀብለው ሰው ደካማ ነውና በካህናቱ ጸሎት ኃጢያቱ ተሰርዮለት ገነት መንግሥተ ሰማያት ይገባል በማለት የደንቡን ፈጽመው ያስፈታሉ በእርግጥ ካህናቱ ፍትሐቱ ምንም ፋይዳ እንደሌለው ቢያውቁም ሥርአተ ፍትሐቱ «ደጀ ሰላሙ እንዳይዘጋ» የሚያደርግ በመሆኑ ከመተዳደሪያም አቅም ማነስ አኳያ የዕለት ጉርስ ማግኛ ዘዴ በመሆኑ ቢሰለቹም ሥር አቱን ማከናወን አይተውም ወንጌላችን «በአንዱ በአግዚአብሔር ልጅ ስም ስለማያምኑ አሁን ተፈርዶባቸዋል ይላል »ዮሐ የመቅደሱ ሰዎች ይህ ሰው ቢሞት እንኳ በፍትሐቱና በድግሱ ጥምረት እንደሚያድኑት ያሳስባሉ « ዘይገብር ተዝካረከ ኩሉ ስብእ እምድኅረ ሞቱ አቡሁ ወእሙ ወወረዱ ውስተ ሲኦል አወጽኦሙ እም ውስተ እሳት »ትርጉም « መታሰቢያህን የሚያደርገውን ሁሉ እናትና አባቱ ቢሞቱ ወደ ሲኦልም ቢወርዱ በእሳት አወጣቸዋለሁ » ብሏል በማለት ይቀልዳሉ ጊመ ስለፍትሐትና ድግሱ ብዙ ማለት ብንችልም ለዛሬው ግን ለሟቹ የሚደረገው የፍታት ጸሎት ምንነት በማሳየት ምን ያህል ሕዝባችንምዕምናን በማያውቁት ከንቱ ነገር ሲረገሙና ሲያስረግሙ እንደኖሩ እናያለን በቤተክርስቲያናችን የመቅደስ ሠራተኞች ሕግ መሠረት የሟቹን ኃጠአት ለማስተስረይ ሁለት አይነት የፍትሐት ሥርአት ይደረጋሉ ኛጉዞ ፍትሐት ይህ ፍትሐት ለቤተክርስቲያን አገልጋዮችለሊቃ ውንት ለመምህራን ለባለሥልጣናት ለነገሥታቱ የሚደረግ ከ ከግማሽ ቀን በላይ የሚደርስ ሰዓት የሚፈጅ የጸሎት ሥርዓት ሲሆን ከሟቹ ቤት ተነሥቶ እስከ ቤተመቅደስ ድረስ የሚፈጸም ነው በዚህ የጸሎት የትዞ ፍትሐት ደግሰው የሚያበሉ ሁሉ እንደተደ ረገላቸው በተለምዶ የሕግ ያህል ጸድቀዋል ኛ ተራ ፍትሐት ምንም እንኳ በጉዞ ፍትሐት ጊዜ ያለው የመሣርያው የካህናት ብዛ ትና ድምቀት በተራ ፍትሐቱ ጊዜ አንድነት ባይኖርም የሚጸለየውና የሚወረበው ቀለም ግን አንድ ሆኖ በነጠላ በአጭር የሚደረግ ፍትሐት ነው ለሟቹ የሚጸለይለት የጸሎት አይነቶች ውዳሴ ማርያም አንቀጸ ብርፃን ወንጌለ ዮሐንስ ቱ የነቢያት ጸሎት መዝሙራት መስተብቁዕ ሁሉንም የጸሎት አይነቶች ለሟቹ ሥርየትን ለማስገኘት እንደሚደገሙ የታወቀ ሲሆን ጎልቶ የሚታወቀው መዝሙረ ዳዊት ነው የሚሆነውን መዝሙረ ዳዊትን በመከፋፈል በአስከሬኑ ላይ ይጸለያል ጸሎቱ ከሟቹ ጉዳይ ጋር የማይገናኝ ከመሆኑ ባሻገር ሬሳውንና ቤተሰብን በመርገም በዘመዶቹ ሁሉ የስድብ መአት እንዲወርድባቸው የሚደረግ ሆኖ እናገኘዋለን ጸሎቱ በግዕዝ ሆኖ ምዕመኑ እዝል አቡነዘበሰማያት ሲሉ ተቀብሎ አሜን ይሁን ይደረግ ከማለት ያለፈ ምሥጢሩን የመረዳት እድል ባለመኖሩ እርግማኑ እንደ ኃጢአት ሥርዬት ተቆጥር ያለ የሌለን ንብረት እያሟጠጡ በመደገስ እርግማንን ተቀብሎ ይሄዳል መዝሙረ ዳዊት ለሟቾች የኃጢአት ሥርየት እንዲያመጣ የተጻፈ ጸሉት ሳይሆን አማኝ በሕይወተ ሥጋ ሳለ አንብቦ አስነብቦ ተረድቶ እርሱን የሚመለከተውን ሕግ የሚጠብቅበት በመከራው እንዲጽናናበት የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንዲያውቅበት ለትምህርት የተጻፈ ድርሰት ነው ገበዘ መቅደስ የሆኑቱ የእኛዎቹ ግን ይህን መዝሙር በላዩ ላይ ስንጮህበት ኃጢአቱ ይሰረይለታል ይሉናል እስኪ ከሚጸለየው ጸሎተ ዳዊት እንይ መዝሙር « ሁል ጊዜ በመተላለፍ አንደበትህ ኃጢአትን ያስባል እንደተሳለ ምላጭ ሽንገላን አበዛህ ሞክኦሠክቹኮጮቕጐ ከመልካም ይልቅ ክፋትን ጽድቅን ከመናገር ይልቅ ዓመፃን ወደድህ የሚጠፋ ቃልን ሁሉ የሽንገላን ሞገስ ሁሉ ወደድህ ስለዚህም እግዚአብሔር ለዘላለም ያፈርስፃል ከቤትህም ይነቅልዛል ያፈልስህማል መቺም ማንም ፍትሐት የተደረገለት ሰው ይህን ውርጅብኝ ሰምቶ አያውቅ ይሆናል ለምን ቢሉ የምናዜመው በግእዝ የምናነበው በግእዝ ነውና ከምዕምናን ጆሮ የራቀ ነው እስኪልብ በሉ የሞተን ሰው አስከሬኑን ከፊት ለፊት አስቀምጦ ይህ ሲጮህበት ምሕርት እየለመኑለት ነው ብሎ ቤተሰብ አሜን አሜን ይላል ይህ ብቻ አይደለም የባሰውን እንመልከት መዝ በላዩ ኃጢያተኛ ይቁም በተሟገተ ጊዜ ተረቶይወጣ ጸሎቱም ኃጢያት ትሁንበት ዘመኖቹ ጥቂት ይሁኑ ሹመቱን ሌላ ይውሰዳት ልጆቹም ድኃ አደግ ይሁኑ ሚስቱም መበለት ትሁን ልጆቹም ተናውጠው ይቅበዝበዙ ይለምትም ከሥፍራቸው ይባረሩ ባለ እዳም ያለውን ይበርብረው እንግዶች ድካሙን ሁሉ ይበዝብዙት የሚያግዘው አይገኝ ለድኃ አደግ ልጆቹ የሚራራ አይኑር ልጆቹም ይጥፉ በአንድ ትውልድ ስሙ ይደምሰስ የአባቶቹ ኃጢአት በእግዚአብሔር ፊት ይታሰብ የእናቱም ኃጢአት አትደምሰስ በእግዚአብሔር ፊት ይኑር የተከበራችሁ አንባቢዎች ሆይ የሟቹን ኃጢአት ለማስተስረይ ለቀብር የመጣውን ከ የሚደርሰውን የዋህ ሕዝብ አቁመው በግእዝ ዝዝ ተ መመ ጩዘ በተሸፈነ ሥርአት ራሱንና ቤተሰቡን በመርገም ቆይተው ይምሐረነ ወይሣፃለነ በሚል ማደናገሪያ ሕዝቡን ይሸኙታል በእርግጥ ከጥቂቶች በስተቀር አብዛኞቹ ካህናቶቻችን ዜማና ንባቡን በልምድ ጸሎቱን ያድርሱ እንጂ ምን እንደተናገሩ ምን እንደጸለዩ ግንዛቤ የላቸውም ከመካከላቸው አንዱ እንኳን በሟቹ ላይ ለምን እንዲህ እንደሚጸልዩ ራሱንም ሆነ ጓደኞቹን የጠየቀ የለም ታዲያ ይህ የፍትሐት ጸሎት ሥርዬተ ኃጢአት እያስተሰረየ ነው ወይስ እርግማን እያስተላለፈ ። ሰው የሚጸድቀው የጌታ ቃል እንደሜለው በሕይወት ዘመኑ ከጌታችን ጋር በመስማማትና ከኃጢአት እየራቀ በመኖር በሥጋ ድካም በሰይጣንና በዚህ ዓለም ተጽእኖ በሕይወቱ ኃጢ አት ቢያልፍ ወይም ቢያደርግ ኃጢአት የለብኝም ሳይል ከአመጻ ሥራ አንኳ ሊያነጸውና ሊታደገው ወደሚችል ወደታመነው ሊቀ ካህናትና ጠበቃ እንዲሁም አራቂ እግዚአብሔር ወሰብእ ጠደ ሆነው ወደ አምላካችንና መድኃኒታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ በመቅረብ ሥርዬተ ኃጢአቱን ሊያገኝ ይችላል እንጂ ሌላ መንገድ ሆነ ምክንያት የሌለው መሆኑን ሊገነዘብ ይገባል በዮሐ ሀ ዕብ እፈታለሁ ብሉ መርገም አስፈታለሁ ብሎ ማስረገም ከአኛ ይራቅ ሕጋመስጠ ዛያጨጭ ልመዌሯሮድም ዊሞሥላሌኤ ዝጡውበፎ ጮጋባጭቸጭል በቤተክርስቲያናችን የነበሩት ጸሐፊዎች በእጃቸው የወደቀውን የዋሕ ሕዝብ ወደ ፈለጉት አቅጣጫ ለመውሰድ በተሞሉበት መንልፈስ ርካሽ በመነዳት ያሻቸውንና ደስ ያላቸውን መጻፍ መናገር ተቃዋሚ የማይገኝለት መብታቸው አድርገው የተቀበሉት ነው አገድነትን በሦስትነት ሦስትነትን በአንድነት ሳትበትን ሳትደባልቅ የምታምነውን ቤተክርስቲያን መቅደስ የጸሎት ቤት ምሽግ አድርገው ከዚያም በመነሳት በዚሁ መንፈላዊ ካባ ተሸፍነው እግዚአብሔር እንዲህ ብሏል ቅዱሳን አንዲህ ነግረውናል ዉዚተ በማለት ጸሐፍቱ የመንፈሳዊ ትምህርት እውቀት የሌለውን ሕዝባችንን ቀርቶ ሊቅ መምህር የተባሉትን ሁሉ በነገር ክታባቸው ማርከው የትምህርታቸው አስተናገጅ አድርገዋቸው ነበር ጸሐፌ ድርሳን ጠገድል ወተአምር የሆኑት እነዚያ ሰዎች እንደ እግዚአብሔር «ንግበር» እንፍጠር ማለት ለእነርሱ ቀላል በመሆኑ እርሱ እግዚአብሔር ያልሠራውን ያልፈጠረውን ነገር በጽሑፋቸው መፍጠር ተግባራቸው ነው ጸሐፍቱ ሰኞን ረቡዕ ሆኗል ማለት ከፈለጉ ረቡፅ ያደርጉታል ጨለማውን ብርፃን ነው ካሉም ይታመናሉ በመጽሐፍ ቅዱስ ፈጽሞ ያልተገለጠና መነሻ የሌለውን ታሪክ መጽሐፍ ሲፈልጉ ማቴዎስ ረስቶት ነው ሉቃስ ዘንግቶት ነው ቢሉም ይሆንላቸዋል እንደምሳሌ ብንወስድ ተአምረ ኢየሰስ የሚባል መጽሐፍ ተጽፎ በሰፊው በገበያ ላይ ይገኛል የመጽሐፉ አዘጋጅ ለመላው ዓለም ምዕመናን የዘላለም የሕይወት ምግብ አዘጋጅና አከፋፋይ ነኝ ያሉ ሰው ናቸው ሰውየው ከቤተክርስቲያናችን ገዳማትና አድባራት ውስጥ ከሚገኙ መጻሕፍት ጋር አመሳክረው በእርሳቸው አባባል ኦሪጅናሉ አለ ለምዕመናን አዝነው በ ዓመታቸው ጽፈው እንዳበረከቱ በመጽሐፋቸው መግለጫ በሚለው አንቀጽ ጽፈዋል መጸሕፍት የሚጻፉት ያው በዛይማኖት ሽፋን በመሆኑ ሰውየው በጻፉት በዚህ ተአምረ ኢየሱስ ውስጥም ከመጽሐፍ ቅዱስ የተቀዱ እውነተኛ የሆኑ ታሪኮች ይገኙበታል ይህም ማደናገሪያ ሲሆን ዓላማቸው እግዚአብሔር ያላለውን ያልተናገረውን በመጨመር ሕዝቡን በበደል ማስያዝ ስለሆነ እንዲህ የሚል ተረት አስገብተውበታል « አስመ አልቦ ነገር እ በምትለው ፈሊጥ ጻድቅ ዕገሌ በአንዲት ቀን ስንዴ ዘርተው አፍርቶ አበራይተው አስፈጭተው አቡክተው ጋግረው ለቅዳሴ ጊዜ ቅዱስ ቁርባን የጌታ ራት አዘጋጅተዋል እንዴት ሲባሉ ለአግዚአብሔር ምን ይሳነዋል በማለት አማኝ ይመስላሉ ለእግዚአብሔር ቅንጣት ታህል የማይችለው አለ ብለን አናስብም እርሱ ሕፃሌ ኩሉ» ነውና ግና ያላሳየንን አየን ልተናገረንን ተናገረን ብንል እግዚአብሔርን ማክበር ሳይሆን በእግዚአብሔር ላይ መቀለድ ይሆናል ሮሜ በብሉይ ኪዳን ከነበሩት ነቢያት አንዳንዶቹ የተናቁበት አንዱ ምክንያት ያልተናገረውን ቃል የሚናገሩ ወይም ከልባቸው አፍልቀው የሚያወሩ በመሆናቸው እንደሆነ ቅዱስ ቃሉ ያስረዳናል ኤር በዚህ በተአምረ ኢየሱስም እንዲህ ያለ ነገር ተጽፎ ይገኛል መጽሐፍ ቅዱስ ስለጌታችን ስለመድኃኒታችን ስለኢየሱስ ክርስቶስ እናውቅ ዘንድ የሚገባንን ብቻ እንድናውቅ ፈቀደ እንጂ ገና ያላወቅነው ነገር እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ « በድንግዝግዝ እንደማይ ነኝ ከእውቀት ከፍዬ አውቃለሁ » በማለት ተናግሯል ለምሳሌ ልደቱ በበረት እንደተወለደ እንጂ የድንግል ማርያም የአወላለድ ሁኔታ አልተገለጠልንም እንበለ ሕማም ወጻእር ይሁን አይሁን አልተጻፈም ይህም ለእኛ አልተነገረም ግዝረቱ ለእግዚእነ እንደልማዳቸው በ ቀኑ ወደ ቤተመቅደስ እንዲወስዱት እንጂ እንዴት ሥርዓቱ እንደተፈጸመ ለእኛ አልተጻፈም ጥምቀቱ በእደ ዮሐንስ በማየ ዮርዳኖስ እንደተጠመቀ እንጂ ዮሐንስ እንዴት እንዳጠመቀው ምን እያለ እንደተናገረ እንዴትስ እንደነበር በዝርዝር የተጻፈ ነገር የለንም በተለይ ከ ዓመቱ ዓመቱ የት እንደኖረና ምን እያደረገ እንደነበር ለምን ታሪኩ እንዳልተዘገበ ለእኛ አልተገለጠም መጽሐፍ አምናችሁ ትድኑ ዘንድ ይህ ተጽፏል በማለት ሲናገር እነዚህ ከላይ ያልናቸው ጥያቄዎች ባይገቡንም እንኳ ሰው ለደህንነት የሚያበቃው መልእክት በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ምሪት ተጽፎልናል ማለት ነው ብዙዎች የፈላስፋዎችን ጥያቄ ለመመለስ ታሪክ አጥንተናል አይሁድን ጠይቀናል በማለት መላምት የሆኑ ምላሾችን በመጨመር ለመጻፍ ቢሞክሩም በተጻፈው ላይ አትጨምር ባለው ሕግ መሠረት ውድቅ ይሆንባቸዋል ጌታችን በቤተመቅደስ ከታየበት ከ ዓመቱ ጀምሮ በጥምቀት ጊዜ እስከተገለጠበት ዓመቱ የት ነበር ። ጸሐፊዎቻችን ይሁኑ ያሏቸው ሁለቱ ፍጡራን ቅዥት እንጂ ከፈጣሪ ጋር የሚተካከሉ አይደሉም የታምርህን መጽሐፍ ዝታ ሽፋዝ የተሳለመ ዓመት ሙሱ የሠራው ኃጢአቱ ይሰረይለታል በኢትዮጵያ የክርስትና ታሪክ ውስጥ የሕይወት ወንጌልን በመስበክ ስመ ጥር የነበረውንና የመጀመሪያው ሊቀ ጳጳስ ሆኖ የተሾመውን የፃይማኖት አባት ፍሬምናጦስን በኋላም ከሣቴ ብርዛን የተባለውን ሰው ስምና ታሪክ ለማጉደፍ እንዲሁም ዛሬ በቤተክርስቲያናችን የታጐሩትን ከንቱ መጻሕፍት ከጥንት ጀምረው ነበሩ ለማለት እንዲያመቻቸው «ተአምረ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን በማለት በጻፉት ጽሑፍ የተለመደውን የክሕደት ጽሑፍ አስፍረዋል መቼም አልቦ ዘይሰአኖ ለእግዚአብሔር የሚለውን ጥቅስ እየነጠቁ በመለጠፍ እግዚአብሔር የ ሣንቲም ዳቦ የሰጠውን ለቤተክርስቲያን ማሰሪያ አንዲት ድንጋይ የተሸከመውን የዘሳለም ሕይወትን ይሰጠዋል ሲኦልንም አያሳየውም የሚሰውን ክህደት ለማስጠበቂያ የሚናገሩት ጓደኛሞች ደራሲዎች የከሣቴ ብርሃን አቡነ ሰላማ ተአምር ይህ ነው ብለው የጻፉትን እንይ በነዚያው መጻሕፍቶቻቸው እንደሚገለጠው ለሞት ተቃረበ ያሉትን ሰው ሁሉ ቅድስናውን ብቃቱን ለማሳየት እንዲህ ይላሉ ፅገሌ የተባለው ጻድቅ ቅዱስ ለሞት በተቃረበ ጊዜ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሦስትነቱ ሥላሴ ከቅዱሳን መላአክት ጋር በኪሩቤል በሱራፌል ላይ ሆኖ አልፍ አዕላፍ መላእክት በግራው አልፍ አዕላፍ መላእክት በቀኙ ሆነው እየበረረ ይመጣል ይላል መቼም ሁል ጊዜ በየቤተክርስቲያኑ ደጃፍ የቀበርናቸውን ሰዎች ሁኔታ ስንመለከት እንኳንስ ጌታና መላእክት ወይም ሥላሴ መጥተው ሊስሙት ሊዳስሱት ቀርቶ እድርተኛ እንኳ ደመቅ ያላለበት የቀብር ሥርዓት እንዳሳለፍን የሚረዳ ቅዱስ ጻድቅ እያሉ የጠሯቸውን ሰዎች የቀብር ሥነሥርዓት ተአምረኛ በማድረግ እየጻፉ የዋሁ ያለ ተቃወሞ እንዲህ ከሆነ በማለት ለማቾቹ ይገዛል በማቾቹ ይማጻናል መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስረዳን ደጋጉ ሐዋርያት መምህራን በዚያ በመከራው ጊዜ ሲያልፍ በአንደኛው የቀብር ሥነሥርዓት ላይ ሥላሴ ነበሩ የሚል የተገለጸ ጽሑፍ የለምየእኛዎቹ ግን ቅዱሳን እያሉ በሚጠሯቸው ሰዎች ሞትና ቀብር ላይ መገኘት ብቻ ሳይሆን ጌታችን እግዚአብሔር የማቹን ከንፈር ሳመው በማለት ነውር ነገር በእግዚአብሔር ላይ ይናገራሉ ጸሐፊዎቹ አቡነ ስላማ ከሣቴ ብርፃን የሚያርፍበት ሰዓት በደረሰ ጊዜ ጌታችን ወደ እርሱ መጥቶ ሞቱን ባበሠረው ጊዜ አቡነ ሰሳማ ጌታችንን እንዲህ አለው የሚል ፈጠራ ጽፈዋል « መታሰቢያየን ለሚያደርጉ ኃጥአንን ትምርልኝ ዘንድ እለምንዛለሁ አንተ በሰጠኸኝ ቃል ኪዳን እነሱን ስሜን የሚጠሩትን ትምርልኝ ዝንድ እለምንፃለሁ አለው ይላሉ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ጥንተ አመሠራረቷ በእውነት ወንጌል ላይ ነው የሚለውን ታሪክ በማጉደፍ ቀደሞውንም በዝክርና በተዝካር በሟች ሰዎች ጸሎትና ምልጃ የተመሠረተች ቤተክርስቲያን ናት በማሰኘት መናፍቃን የጻፉት እንጂ ከሣቴ ብርፃን ሰላማ ይህን እንዳለ የሚያረጋግጥ የተጨበጠ ታሪክ የለንም መናፍቃኑ እንደተለመደው መታስቢያዬን የሚያደርጉ በሚሉት ሐረጋቸው በሟች ስዎች ስም የሚደረገውን የድሆች ቤት ብዝበዛ በብዙ መረጃ ለማስረገጥ እንዲሁም ከጥንት ጀምሮ የነበረ ነው ለማሰኘት የተደረገ እንጂ በማንም ተዝካር መታሰቢያ ጸበል ጸዲቅ እየተባለ በሚደረግ ድግስ እግዚአብሔር የዘላለም ሕይወት እሰጣለሁ አላለም «በአርሱ የሚያምን» አለ እንጅ ስሜን ለሚጠሩ የሚለው የመናፍቃኑ ወንጀል የጽሑፍ ሥሕተት ያለመረዳት ውጤት ሳይሆን ብዙ ጊዜ እንዳልነው የእግዚአብሔር ስም ከሕዝቡ ኅሊና እንዲስረዝ የሰይጣንን ዓላማ ማስፈጸም ነው መጽሐፍ « እስመ ኩሉ ዝጸውዐ ስመ እግዚአብሔር የሐዩ » የጌታን ስም የሚጠራ እርሱ ይድናል ሮሜ ሀ የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል ኢዩ አለ እንጂ የዕገሌንና የዕገሊትን ስም የጠራ ኃጢአቱ እንዲሠረይለት ቃል ኪዳን አልገባም ሐዋርያው ጳውሎስ በቆርንቶስ ቤተክርስቲያን ውስጥ የየራሳቸው ቅዱሳን የሚሏቸውን ሰዎች እየመረጡ ሲቧደኑ አይቶ በጳውሎስ ስም ተጠመቃችሁን ጳወሉስ ስለ እናንተ ተሰቀለን ኬፋስ ዮሐንስስ ምንድር ናቸው። ቢላት የሉኝም ብላ ዋሸችው እርሱም የደበቀቻቸውን ሁሉ ረገመባት በዚያው መናፍስት ሆነው ቀሩ » በማለት በመስበካቸው ዛሬም እንኳ በአንዳንድ የቤተመቅደስ ሙያተኞች ስለሚነገር ሊታረም ያልቻለ እንቶ ፈንቶ ትምህርት ነው ይህም ብቻ አይደለም ድንግል ማርያም ጌታን በሕፃንነቱ ይዛ ወደ ግብጽ ስትሰደድ በመንገድ ሳይ ውኃ አጠጡን ብላ የለመነቻቸው ስዎች ስለተከፉባት በእቅፏ የያዘችው ጌታ ሰዎቹን በረገማቸው ጊዜ ጦጣና ዝንጀሮ እየሆኑ ገደል ገቡ በማለት ስነፍጥረትን እግዚአብሔር ሁለት ጊዜ እንደፈጠረ አስመስለው ደግሞም ሁሉ እንደወገኑ ያውጣ የሚለውን ቃል ሽሮ የሰውን ዘር ዝንጀሮና ጦጣ አደረጋቸው ወደሚለው የሰነፎች ፍልስፍና ሊያስጠጉን ሞክረዋል ይህ ሁሉ የሚያሳየን ጸሐፊዎቻችን ለምን እንዴት መቼ የት የሚሉ ጥያቄዎችን ከዚህ ሕዝብ ባለማግኘታቸው እአንደፈለጉት ለመሆን የነበራቸውን አድል የሚያሳይ ነው ድርሳነ ሩፋኤል እየተባለ በሚጠራ በፈጠራ ጽሑፍ ውጤታቸው ደግሞ እንዲህ የሚል ክህደትን አስፍረዋል አንድ ቀን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያቱን ለወንጌል አገልግሎት ባርኮ በላካቸው ጊዜ ወንጌልን እንዲሰብኩ ብቻ ሳይሆን የድርሳኑ ጸሐፊዎች እነርሱ ሩፋኤል እያሉ የጠሩትን መልአክ እነርሱ እንዳሉት ክብርና ገናናነት የስሙንም ትርጉም አውቀው ከወንጌሉ ጋር እንዲሰብኩት መፍቀዱንና ማዘዙን ጽፈዋል ከዚህ የተነሳ ሩፋኤል እያሉ የጠሩት መልአክ ሐዋርያትን ጠርቶ የስሙ ትርጓሜ የዋህና ሰውን አስደሳች ማዕረጉ ኛ ኃጢአተኞችን በኃጢአታቸው በእግዚአብሔር ፊት የማይከስ ይልቁንም ሰውን ከመውደዱ የተነሳ ኃጢአተኞች ንስሐ ይገቡ ዘንድ እድሜን በአድሜ ላይ የሚጨምር የ ነገደ መላእክት አለቃ የሆነ ሁልጊዜ ጳጉሜ ቀን የሚከበር በዚህ ቀንም በእርሱ ስም መታሰቢያውን የሚያደርግ ሰው ሁሉ ወደ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ማስገባት የሚችል መልአክ እንደሆነ ለሐዋርያት አስተማራቸው ሰበከላቸው በመጨረሻም በጸሐፊዎቹ ሩፋኤል የተባለው መልአክ የጌታ ተከታዮች የሆኑት ሐዋርያቱ ለተልአኮ በሚፄዱበት ሁሉ ያደርጉት ዘንድ ያላቸውን ሲናገር በግዕዙ « ጎኅጮ እምኔየ ኦ ሐዋርያት ኅሩያኒሁ ለእግዚአብሔር ኩሎ ጊዜ ከመ ዕቀብክሙ እስከ ትቀዉሙ ቅድመ እግዚአ ብሔር ወስብኩ ለኩሎሙ ሰብእ እለ ውስተ ኩሉ ዓለም ክመ ይግበሩ ተዝካርየ ወአነ አእተነብል ኀበ እግዚአብሔር በእንቲአሆሙ ወአድኅኖሙ እምንዳ ቤሆሙ ወእምኩነኔ ለግሙራ » በአማርኛ እናንተ እግዚአብሔር የመረጣችሁ ሐዋርያት ሆይ በዚህ ዓለም ስብከተ ወንጌልን አስፋፍታችሁ ወደ እግዚክ ብሔር መንግሥት እስክትጠሩ ድረስ ሁል ጊዜ እጠብቃችሁና እራዳችሁ ዘንድ ከእኒ የምት ፈልጉትን ሁሉ ጠይቁ አሁንም በዚህ ዓለም ያሉ ሰዎች መታ ሰቢያን ያደርጉ ዘንድ አስተምሯቸው ስለእነ ርሱ ወደ እግዚአብሔር እየማለድሁ ከችግራ ቸውና ከጭንቀታቸው አድና ቸዋለሁ አላቸው ፎርሳነ ሩፋኤል ዘጳጉሜን ቁጥር ዜመ ለመሆኑ ይህን የሚያህል ጌታችን ራሱ ተሳትፎበታል የተባለውን ታሪክ ሐዋርያት እንዴት ሳያስተምሩት ሳይናገሩት አለፉ ያውም ሰሌሎች ሰዎች እንዲያስተምሩ ታዝዘው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስስ ሐዋርያቱን ለተልእኮ ባርኮ ሲሸኛቸው « እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችሁ ደቀ መዝሙሬ አድርጓቸው ሲል ለሩፋኤልም መታሰቢያውን እንዲያደርጉ አስተምሩ ያላላቸው ለምንድን ነው ። የጌታ ተከታዮች ሐዋርያት አንገታቸውን ለሰይፍ ሕይወታቸውን ሙሉ ለስቃይና ለመከራ አሳልፈው በመስጠት በጥም በረኃብ በአርዛት የሰበኩት ክርስቶስን እንጂ ሌላ እንግዳና ባዕድ ፍጡር አልያም አሉ የተባሉ መላእክትና ሰዎች ስምና ዝና አልያም የመታሰቢያ አከባበር ሆነ በእነርሱ ስም የሚደረግ ልመናና ምልጃ አልነበረም በእርግጥ በወቅቱ የነበሩ ፈላስፎች አዲስ አዲስ ነገር የሚወዱና ስለተለያዩ አማልክት አውቀትና አምልኮ የነበራቸው ቢሆንም የተወደዱት የጌታ ተከታዮች ግን « እኛስ የተስቀለውን ክርስቶስን እንሰብከለን እ» እያሉ የስብከታቸውን ርዕስ ይናገሩ ነበር ጸሐፌ ድርሳን ወገድል የሆኑት አገር በቀል መናፍቃኑ ግን ጌታችን ራሱ ከወንጌሉ ጋር ሩፋኤል የተባለ ሰው ክብርና ዝና ገናናነትም እንዲሰበክ ሕዝቡም ሁሉ መታስሰቢያውን እንዲያደርግ ስበኩ ብሎ ለጥፋት ተልዕኮአቸው ተባባሪ አድርገው ቢያቀርቡትም እኛ እንላለን « ሐዋርያት ካስተማሩት ወንጌል የተለየ ወንጌል የሚሰብኩ ሁሉ የተረገሙ ይሁኑ » ገላ ዕ አሜን አንዲህ ዓይነቱ የፈጠራና የክህደት ጽሑፍ በቤተክርስቲያኒቱ የመጻሕፍት ታሪክ የጎላ ድርሻ አለው ተብሎ በሚነገርለት « ዲድስቅልያ » እየተባለ በሚጠራው መጽሐፍ ውስጥ ሳይቀር ገብቶ ጠርገን የማንጨርሰው የሚመስለን እዳ በሀገርና በሕዝብ ላይ አዝንበውብናል ሰዶምን ያቃጠሏት ሐዋርያት ናቸው በመጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነበበው በሰዶምና በገሞራ ይኖሩ የነበሩት የሰው ልጆች በእግዚአብሔር ፊት ባበዙት ኃጢአት ምክንያት እግዚአብሔር በዚያ የሚገኙትን ኃጢአተኞች ሊቀጣ የወሰነበትን ውሳኔ ለወዳጁ ለአብርፃም እንደነገረውና ወደከተማዋ የገቡት ሁለቱ መላእክት በዚያ ይኖር የነበረውን ሉጥን ከነቤተሰቡ በከተማዋ ላይ ሊደርስ ካለው ጥፋት ለማዳን በእግዚአብሔር እንደታዘዙት በአቅራቢያቸው ወደሚገኘው ተራራ በማሸሽ እንዳወጧቸው በዘፍ ና ላይ በግልጥ ሰፍሯል ሆኖም በእኛዎቹ ጸሐፊዎች ይህ በእግዚአብሔር መንፈስ የተነዱ ቅዱሳን ሰዎች የጻፉትን ታሪክ በማጣረዝ በዘመነ አበው ማለትም አብርዛም በምድር በሕይወተ ሥጋ እያለ የተሠራውን ሥራ ከ ዓመት ያላነሰ ርቀት ከላቸውና በሐዲስ ኪዳን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዛሙርት ሆነው የተሾሙትን ሰዎች በሕይወተ ሥጋ ካሉበት ዘመን ጋር በማጣመር ሎጥን ከሰዶም ጥፋት ያወጡትና ሰዶም እንድትቃጠል እሳትን ከሰማይ ያዘነቡት ቱ ሐዋርያት ናቸው በማለት አስፍረዋል ሠ ከመ መሙ ደ ሠ ፍሙ መ የፈጠራ ታሪኩ እንደሚለው ሐዋርያት ወደ ሎጥ ቤት ገብተው ክርስቶስን እንደሰበኩለትና ሎጥም በጌታ እንዳመነ በዚያ የሚገኙት የሰዶም ሰዎች በሐዋርያት ላይ መከራ እንዳጸኑባቸው በዚህም ምክንያት የሰዶም ሰዎች ወንጌልን ለመቀበል ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ሐዋርያት ተመልክተው ሀገሪቱን ረግመዋትና የእግራቸውን ትቢያ አራግፈው እንደወጡ ተጽፏል እንግዲህ የወደዱትን ማንገሥ ያልወደዱትን መሻር በጊዜው በሥነ ጽሑፋቸው ሥልጣን የነበራቸውና ቤተመቅደሱን የሙጥኝ ይዘው ወንጀልን በመንፈሳዊነት ስም ይሠሩ የነበሩት ጸሐፊዎች እንዲህ ዓይን ያወጣን የታሪክ ክህደት ያለ ሐፍረት በረከተ ሐዋርያትን ለማግኘት የሚነበብ የሚጸለይ የሚሳለሙት ቅዱስ መጽሐፍ ተብሉ እየተሰበከ በማንም ሳይጠየቁ ዘመን በማስቆጠራቸው በሕዝባችን መንፈሳዊና ማኅበራዊ ኩሮ ውጥንቅጥ መሆን ዳርገውታል ሲኖዶስ ዘሐዋርያት ምንባብ ዘሐሙስ በቅዱሳን ስም እየተደረገ ያለው ይህ ወንጀል ቤተክርስቲያናችንን ምን ያህል እንደጎዳትና ለዛሬው አለመረጋጋት እንደዳረጋት መገንዘብ ይቻላል አባቶች ይህን የሚያህል ክህደትና ወንጀል የተሸከመችውን ቤተክርስቲያን ምንም እንከን እንደሌለባት በማስመሰል ለእርምት ከመነሣት ይልቅ ሕዝቡ ያለውን ወንጀል ተሸክሞ እንዲቀጥል ያሳዩት ቸልተኝነት የእረኞች አለቃ በሚገለጥበት ጊዜ አንገታቸውን እንዲደፉ እንደሚያደርጋቸው መገንዘብ ይኖርባቸዋል ወንጀል ይብቃን እግዚአብሔር ሆይ እውነተኞች እንሆን ዘንድ እርዳን »ቓቻ ጽ ችኪኬ ጭኬሆክ ታሮክ አዝጨው ሯመሸዝ ው ሯ ውሕድክ ጽ የሆየጢ በቤተክርስቲያናችን የሚገኑትን አገልጋዮች ካህናት ሕዝቡ ምዕመናኑ በአግዚአብሔር ምትክ ያያቸዋል የሚባለው ወይም እንደ እግዚአብሔር አምኖ ይቀበላቸዋል እየተባለ የሚነገረው አባባል እውነታው ያመዘነ ነው ምክንያቱም ካህናቱ ያሉት ሁሉ ያለተቃውሞ ያለጥርጣሬ አሜን ይሁንልን ይደረግልን በማለት አባቶቹ የአባቶቹም አባቶች ዛሬም እርሱ ራሱ ሕዝቡ እየፈጸመው ያለ ግብር በመሆኑ በቂ ማስረጃ ይሆናል ከዚህ የተነሣ ለኃጢአት ሥርየት ያገለግላል የተባለውን ማንኛውም አይነት ነገር አዎ ያስተሰርያል በማለት እየተቀበለ ያንንም አየፈጸመ የሚኖር ከመሆኑም ባሻገር ሰው ይሁን መልአክ እንጨትም ይሁን ድንጋይ ተራራም ይሁን ወንዝ ካህናቱ ኃጢአት ያስተሰርያል ካሉት አዎ ያስተሰርያል ብሎ መቀበል በራሱ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ ባህልና የአባቶቼ ብሎ የሚኮራበት ታሪክ እየሆነለት ይገኛል አንደ ጸሐፊዎቻችን ብዛት ያድናል ያጸድቃል ኃጢአት ያስተሰርያል ይራዳል ከሞት ያድናል ከውርደት ይታደጋል ገበያ ያቀናል ሰላቢ ቡዳ ዓይነጥላ ወዘተ ይከላከላል የተባለውን ሁሉ ይሞክራል ጠጀሣር ይሁን ጥንጅት ቄጠማ ይሁን ዕጣን የቅጥረ ቤተክርስቲያን አፈር ይሁን የሙጋድ አእንጨት አመድ የደመራ አመድ ሆነ ታቦታቱ ያደሩበትን ሜዳ አፈር በየሸለቆው ዛሬ ዛሬ ደግሞ በየአውራ ጎዳናውና በየከተማው የፈነዳ ቧንቧ ሳይቀር ፍሳሹን ተከትለው በተፈበረኩ ውኃዎች በአገልጋዮቹ ስያሜ ጠበል ጭምር ፊቱን የተቀባ በቤቱ በራፍ ያንጠለጠለ ሰውነቱን ያሻሸ ወዘተ ያለ የሌለ ኃጢአትን ሆነ መከራን ጥርግ ሙልጭ አድርገው ያጠፋሉ እየተባለ ስለሚስበከው ይኸው የዓለም መድኃኒት ክርስቶስ ስለሁላችን በደል ሥርዬት ለባሕርይው የማይስማማውን ሞት በመቀበል ወደር የማይገኝለትን ሥርዬት አፍስሶልን በሚገኝበትና በእርሱም ምክንያት ከሚወደድ አባቱ ጋር ታርቀን በምንገኝበት በዚህ በምህረትና በጸጋ ዘመን ይህን መከረኛ ሕዝብ እንደ ባለዛር እንደጠንቋይ እንደሟርተኛ እንደ አስማተኛ እንደ ጋኔን ሳቢ ልማድና ትምህርት ከቅጠል ከውኃ ከአፈር ከአመድ ጋር ደኅንነታችንን በማቆራኘት የአዲሱን ኪዳን ጸጋ ከሕዝባችንና ከሀገራችን ለማባረር ታጥቀው በተነው ደላሎች ተጠምዶ ይገኛል ውዳሴ ማርያም እየተባለ በሚጠራው መጽሐፍም ምንም እንኳ በውስጡ መልካም የሚመስሉ በርካታ ጽሑፎችን የያዘ መጽሐፍ ቢሆንም ፈጽሞ ከጽሑፉ ጋር ግንኙነት የሌላቸውን አንቀጾች በፈጠራ በመጨመር በጌታ ስም ሽፋን የፈለጉትን መናፍስታዊ አምልኮ ቀላቅለው ሕዝባችንን ሥርየተ ኃጢአቱ መገኛው የካህናቱ ቅርስ አጥንት አስከሬን ነው በሚል ማሠሪያ የአንዲት ሴትን ሥርዬተ ኃጢአት ታሪክ ይተርካል መጽሐፉ የስኞ ንባብ እያለ ባስቀመጠው ገጽ ከነገሥታት ወገን የሆነች አንዲት ሴት ነበረች በማለት ትረካውን ይጀምራል ይህች ሴት በዘመኗ ሁሉ የምትሠራውን ኃጢአት እየጻፈችና እየመዘገበች በመዝገብ ታስቀምጥ ነበር ይህን ያደረገችበትም ምክንያት መጽሐፉ እንደሚለው ኃጢአቷ ብዙ ስለሆነባት ኃጢአቷንም ለሌላ ሰው መንገር ስላፈረች ነበር ይለናል መጽሐፉ ይቀጥልና ይህች ሴት ከዕለታት በአንድ ቀን ዕድሜ ልኳን በወረቀት ያሠፈረችውን ኃጢአቷን ይዛ ቅዱስ ባስልዮስ ወደተባለው ጳጳስ ዘንድ ደረሰች እርሷም ወረቀቱ እንደተጠቀለለ አቡን ሆይ በዚህ ወረቀት የጻፍሁት ኃጢአትሽ ይፋቅልሽ በለኝ አለቺው ጳጳሱም ወዲያው ይፋቅልሽ አላት ገልጣ ከፔ ህመ መጽ በተመለከተችበት ጊዜም አንዲት ኃጢአት ብቻ ስትቀር ሁሉ ኃጢአቷ ተፍቆላት አገኘችው ሴቲቱም ይህች የቀረችው ኃጢአትስ ብላ ስትጠይቀው ጳጳሱም ይህንስ እኔ የምችለው አይደለም ቅዱስ ኤፍሬም የሚባለው ጳጳስ ነው እንጂ አላት በማለት የሥርዬተ ኃጢአቷን ታሪክ ሊያስተምረን ሞክሯል ከየትኛው የፃይማኖት መጽሐፍ እንደተገኘ የትኛው ሐዋርያ እንዳስተማረው ወይስ በየትኛው የቤተክርስቲያን ሥርዓት እንደተገለጠ የሚታወቅ ነገር ባይሆንም በእነ ፈጠራ እንደልቡ ግን ኃጢአት በላጴስ የሚጠፋ አፍ ሲሉት የሚበን አቧራ ፀሐይ ሲመታው እንደሚደርቅ ርጥበት ቀላል ነገር በማድረግ እንበለ ኑዛዜ እንደለ ቃለ ወንጌል እንበለ ክርስቶስ በጳጳሱ የይፋቅልሽ ቃል ከልቧ ሳይሆን በወረቀት ላይ የነበረ የኃጢአት ዝርዝር ሙልጭ ብሎ ተሰርዮላት በሙላት ለኃጢአት ሥርዬት የፈሰሰውን ክቡር የክርስቶስ ደም ከንቱ በማድረግ የሰጡ ሰዎች እንደሆኑ መረዳት አያዳግትም ለከፍተኛ የኃጢአት ሥርዬት ወደ አባ ኤፍሬም አባ ባስልዮስ በተባሉት ጳጳስ ሳይቻል ቀርቶ አንዲት ኃጢአት በመዝገቧላይ የቀረባት ሴት ለከፍተኛ ሥርዬት አባ ኤፍሬም ይባላሉ ወደተባሉ ሰው እንድትፄድ ትዕዛዝ የተቀበለችው ሴት ቀርቷል የተባለችውን ኃጢአት በያዘችው ወረቅት እንዳለ በመሄድ አባ ኤፍሬም ከተባሉት ሰው ፊት ደርሳ እንደተለመደው አባ ይፋቅልሽ በለኝ በማለት ስትናገር ጳጳሱም ይህስ ኃጢአት ለእኔ አይቻለኝም ለቅዱስ ባስልዮስ ነው እንጂ በማለት እንድትመላለስ ተናገራት ያንጊዜ ሴቲቱ ወደተጠቆማት ሰው ልትፄድ ፊቷን ስታቀና አባ ኤፍሬም እንዲህ አላት አሁን ስትመለሺ አባ ባስልዮስን እንደቀድሞው በሕይወተ ሥጋ አታገፒውም ነገር ግን ሳትጠራጠሪ የያዝሽውን ወረቀት በአስከሬኑ ላይ ጣይው ያን ጊዜ የቀረው ኃጢአትሽ ይፋቅልሻል አላት ይላል ሴቲቱም ስትፄድ አስቀድሞ ለከፍተኛ ሥርዬት ልኳት የነበረው ሰው አባ ባስልዮስ ሞቶ ሊቀብሩት ሲፄዱ መንገድ ላይ አገኘችው እርሷም አንደተባለችው በእጂ የያዘችውን ወረቀት ኃጢአቷ ያለበትን አስክሬኑ ላይ ስትጥለው ቀርታ የነበረችው ኃጢአቷ ተፍቆላት እንደተመለሰች የሚተርከውን ተረት ያገባድዳል እንዴት ያለ ቀልድ እንዴት ያለ ወንጀል በቤተክርስቲያንና በሕዝቡ ላይ በቅዱሳን ስም ይፈጸም እንደነበር በክርስቶስ አምናለሁ የሚል ክርስቲያን በቀላሉ ሊረዳው ይችላል እንላለን ጸሐፊው በሴትዮዋ ላይ የተደረገውን ትያትር ምክንያት ሲያስረዳ ወደ ከፍተኛ ሥርዬተ ኃጢአት የተላከችበት ምክንያት ቅዱሳን የራሳቸው ክብር እንዲገለጥ ሳይሆን የጓደኞቻቸው ጽድቅ እንዲገለጥ ስለሚወዱ ነው ሴቲቱ ወዲያና ወዲህ ስትመላለስ ድካሟ ንስሐ እንዲሆንላት ነው ይለናል ይህም ታሪክ የሚያስረዳን ይላል መጽሐፉ ካህናት በሕይወት እያሉ ብቻ ሳይሆን ከሞቱም በቷሳ ኃጢአትን ማስተስርይ እንደሚችሉ ለማስረዳት ነው ይላል ይህን የፈጠራ የኃጢአት ማስተስረያ መንገድ በመጽሐፍ ቅዱስ ስንመዝነው መጽሐፋችን ወንጀልና ድብቅ ሜራ ቁልጭ አድርጎልናል የኃጢአት ሥርዬት በመጽሐፍ ቅዱስ አስቀድሞ ሁላችንም በእግዚአብሔር ፊት ኃጢአተኞች በመሆናችን ከእግዚአብሔር ጋር የነበረን ግንኙነትና ኅብረት ተበላሽቶ ነበር ነ ማንም ደግሞ ይህን የተበላሸ ኅብርት ለማስተካከል በራሱ ባለመቻሉ እግዚአብሐር ራሱ የሚበጀንን የምህረት ኪዳን በፍጡር ሰው ወይም በመላእክት ሳይሆን በባሕርይ በመልክ በሚተካከለው አንድያ ልጁ በኩል በሥጋ ተዛምዶን ስለሁላችን በደል ተወክሎ በሥጋው በመቀጣት በመሞት ን በእርሱ ሞት ምክንያት ከእርሱ ከአባቱና ከመንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ ጋር ታረቅን አስታረቀን ስለሆነም የመጀመሪያው ሥርዬተ ኃጢአት የማንም ፍጡር ሰውና መልአክ እጅ ሳይኖርበት ወይም ሳይገባበት በራሱ በእግዚአብሔርነቱ ፈቃድና ውሳኔ ተፈጸመልን እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበር በደላቸውንም አይቆጥርባቸውም ነበር ቆሮ እንደተባለው ነው ይህን በራሱ በእግዚአብሔር ፈቃድ የተፈጸመ ሥርዬተ ኃጢአት ለመቀበል እግዚአብሔር የላከውን ልጁን ማወቅ ማመንና መቀበል ይገባዋል ዮሐፀፎ ምንም እንኳ ከእግዚአብሔር ለይቶን የነበረውን የጥል ግድግዳ ኃጢአት ሥርዬት በእርሱ ውሳኔና ፍርድ እንዲህ ሳንደክም በጸጋው በኩል የተቀበልን የአግዚአብሔር ልጆች ተብለን የተጠራን ነን ብንልም በኃጢአትና ከሥጋ ጋር የምንኖር ስለሆንን በዕለት ተፅሰት ተግባራችን ላይ ሕይወታችን ከስሕተት ሊያመልጥ ባለመቻሉ እግዚአብሔር ቀሪ በሥጋ ልንኖርባት የተሰጠንን ዕድሜ እንዴት ተጠንቅቀን እንደምንኖር መፍትሔውን ጭምር ሠርቶልናል በዕለት ተዕለት በሚከናወነው ኑሮአችን ላይ የሚፈጸም የገቢርና የኃልዮ ኃጢአት ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ኅብረት ስለሚያበላሽ ኛ ዮሐ ይህን ኃጢአት የሚያበላሸውን ኅብረት በየጊዜው ለማስተካከል ወይም ለማደስ መፍቴው በሠራነው ኃጢአት በመጸጸት በእግዚአብሔር ፊት መናዘዝ ብቻ እንደሆነ ተገልጾልናል « በአውነት ብንናዘዝ ከኃጢአታችን ሁሉ ከአመጻም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው » በማለት ገልጦ እርሱም ክርስቶስ ነው ይለናል ስለ ሥርዬተ ኃጢአቱ አፈጻጸም ሲያስረዳ « ልጆቼ ሆይ ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ ማንም ኃጢአት ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን አርሱም ክርስቶስ ነው » ዮሐ ካለ በኋላ የልጁ የኢየሱስ ክርስቶሰ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻል ዮሐ ብሎ ኃጢአትን ለማስተስረይም በአብ ፈቃድ የተሾመልን ሊቀ ካህናት እርሱ ብቻ እንደሆነ ሲያስረዳ « በብሉይ ኪዳን ኃጢአትን ሊያስተሰርዩ የቆሙ ካህናት ብዙ ናቸው እነርሱ ግን ሞት ስለከለከላቸው ካህናት እየተባሉ የተሾሙ ብዙ ናቸው እርሱ ግን ለዘላለም ስለሚኖር የማይለወጥ ክህነት አለው ብሎ ስለዚህ ለአነርሱ ሊያማልድ ሊታይ ሊከራከር ይችላል ይሉታል የቤተክርስቲያን ሊቃውንት በህይወት ይኖራል ስለዚህ በእርሱ በኩል የሚቀርቡትን ፈጽሞ ሊያድን ይችላል በማለት የኃጢአት ሥርዬት ሁኔታን ያስረዳናል በሌላም ሥፍራ የሚያስፈልገን ሊቀ ካህናት እንዲህ ያለው ነው በማለት ሰዎች ሁሉ እግዚአብሔር ይሁንላችሁ ብሎ ወደ ሾመልን ሊቀ ካህናት እየቀረበ የበደሉን ሥርዬት እንዲቀበል ሐዋርያት ይመክሩናል የውዳሴ ማርያምን መጽሐፍ ጽፈነዋል ያሉትን ኢትዮጵያውያን መናፍቃን ግን የኃጢአት ሥርዬት ለማግኘት በሟች ሰው አስከሬን ላይ ኃጢአትን ጽፎ በመጣል ነው በማለት ለዚህ ሥራ ያስቀመጣቸው ካህናት ናቸውና በህይወታቸውም በሞታቸውም ቢሆን ኃጢአትን ማስፋቅ ይችላሉ በማለት ታሪከ ቧልቱን ለቅልቆልናል ሌላው ተራራ በመውጣትና በመውረድ በሚፈጠር ድካም ንሥሐና ሥርዬተ ኃጢአት ይገኛል በማለት በድፍረት በጌታ ደም ላይ የተነሳሱ ሰዎች በመጻፋቸው ጽድቅ ፍለጋ ከገዳም ገዳም ከደብር ደብር እየተንከራተቱ ላቡን ጠፍ እያደረገ በአካሉና በሕይወቱ ላይ አደጋን የፈጠሩ ሰዎቻችን ቀላል አይደሉም ይህም ጉዳት የጽድቅ ምልክት ሆኖ እንዳገለገሳቸው ስለሚሰበክ ከክርስቶስ ደም ይልቅ የመናፍቃኑ ትምህርት አይሎ ዛሬም እንኳ ይኸው ትምህርት ቤተክርስቲያኒቱን ገዝቶ ይዚት ይገኛል የእግዚአብሔር ልጅ በፈቃዱ ከዙፋኑ ፍቅር አስገድዶት ለሞት ያውም ለመስቀል ሞት ራሱን ሰጥቶ በከበረች ሞቱና ደም ማፍሰሱ ጽድቅ ቅድስና ቤዛነት ሥርዬተ ኃጢአት ተሰብኮልን እግዚአብሔር አብም አንድያ ልጁን በመስጠት የገለጠውን ፍቅር ከንቱ ለማድረግ በተደረገ የመናፍቃን ጫራ የሟች አስከሬን የኃጢአት ሥርየትን ይሰጣል ብሎ መስበክ የእግዚአብሔርን ጸጋ ማክፋፋት አይሆንምን ። አሏት ከሰባት ወር በኋላም ልጅ ወለደችና በክንዲ ታቅፋ እግዚአብሔርን አመሰገነች ስለ እምነቷም የተወደደ ልጅን አገኘች ወልዳ ሦስት ወር ከሆናት በኋላ ወደ ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ዘንድ ፄደችና የከበሩ ልብሶቿን የወርቅ ጌጣ ጌጧን ሌላም ሌላም ብዙ መባን ሰጠች ቀሳውስቱ ንና ዲያቆናቱንም አመሰገ ነቻቸው እንዲሁም ተአምር ሠሪ በሆነ በቅዱስ ዑራኤል አማላጅነት ልጅን ስለሰጣት እግዚአብሔርን አመሰገነች ከዚያም ፅለት ጀምራ እስክ ዕለተ ሞቷ በመልካም አገልግሎት ቤተክርቲያኗን ስታገለግል ኖረች የመላእክት አለቃ የሚሆን የቅዱስ ዑራኤል ልመናውና በረከቱ ሰዘለዓለሙ ከወዳጁ ጋር ይሁን አሜን ድርሳነ ዑራኤል ዘየካቲት ኛ ተአምር ተአምር ይሏል እንዲህ ነው እግዚአብሔር ተአምር ሠሪ አምላክ መሆኑን ሰማይና ምድር በውስጣቸው ያሉ ፍጥረታትም ሳይቀሩ አሜን የሚሉት እውነት ነው መዝሙረኛው ዳዊት አንዳለ «ያለ ቃል ያለፊደል አሜንታቸውን እስከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ያሰማሉ» መዝ በእውነትም አምላካችን ከአዕምሮ በላይ የሆነ ተአምር ይሠራል ለሰው የማይቻል ሁሉ ለአግዚአብሔር ይቻላል የሚለው ቃል እውነት ነውና መልአከ ብሥራት የሆነው ቅዱስ ገብርኤል ለድንግል ማርያም ሲናገራት ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና ሉቃ አሉ ራሱ እግዚአብሔር በወዳጁ በአብርፃም ቤት በገባ ጊዜ የአብርሃም ሚስት ሣራ ልጅ የመውሰለዲ ነገር በአግዚአብሔር አፍ ሲነገር ሰምታ ዕርጅናዋ ይህን የእግዚአብሔር ተአምር ለመቀበል ሲያግዳት በሳቀች ጊዜ በውኑ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለን ብሏታል ዘፍ ጌታችንም በመዋዕለ ስብከቱ ሲናገር ለስው የማይቻለው ለእግዚአብሔር ይቻለዋል ብሏል ማቴ ስለሆነም የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ከምንለው በላይ ተአምር ይሠራል እንደሚሠራው በነፍሳችን ተወራርደን የቆምንበት ዓላማችን ነው አዎ ልዑል እግዚአብሔር ተአምረኛ አምላክ ነው ይሁንና «አስመ አልቦ ነገር» የምትለውን ሐረግ ስቦ ለክፋትና ለአመፅ እንዲሁም ለሰይጣን ግብር መሸፈኛ ማድረግ ግን እምቢ ልንለው የሚገባ ትምህርት እንደሆነ እገገልጻለን አተካከሏ በእውነት ወንጌል በደጋግ መምህራን እንደነበር የሚነገርላት ቤተክርስቲያናችን ዘመንና የጠላት ስይጣን ዕቅድ ያሰለጠናቸው ክፉዎች ከላይ እንደገለጥነው «እስመ አልቦ ነገር ዘይሰአኖ ለእግዚአብሔር» በሚለው ሽፋን ባዕድ ትምህርት ባዕድ ባሕልና ሥርዓት ወደ ቤተመቅደስ በማስገባታቸው ከጨለማው ዘመን ጀምሮ እስከዛሬ ያልተነቀለ አሳፋሪ አስነዋሪ ወንጀሎች በቤተ ክርስቲያናችን ስም ተለጥፈው ለዛሬ አንገት መድፋት ምክንያቶቻችን ሆነዋል ብዙዎችን ያታለለውና ያሳሳተው ነገር ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም የሚለው ጥቅስ ነው ነገሩን በመንፈ ሳዊነት በቃለ እግዚአብሔር እውነት ካልመረመርነው ለሀገራችን ምዕመናን ሸክምና ዕዳ ነው ብዙ የቤተክርስትያናችን ምዕመናን ሰይጣን እግዚአብሔር ብሎ ለመጥራት የሚፈራ ይመስላቸዋል ስለዚህም እግዚአብሔር ብሎ ከቅድመ አያቶቻችን ከዚያም በፊት ጀምሮ እየተንከባለለ የመጣ የአመፅ ዕዳ ያለ ተቃውሞ ተቀብለው ይኖራሉ የሚያሳዝነው ዛሬም እንኳ ለዚህ ጥፋታችን ባለመንቃት ለገጠመን ችግር ምክንያት ሌላ አዳዲስ ነገሮችን እየፈጠርን እነሆ ከእግዚአብሔር ጋር ሳንታረቅ መኖራችን ነው ደጋግመን እንደገለጽነው የሀገራችንም ሆነ የቤተ ክርስቲያናችን ችግር መንግሥ ታቶቻችን ድኅነታችን ኋላቀርነታችን የቀለም ትምህርት አለመማራችን አ ዜታ ው ዓመ መ ኣንድ ን ን መሽ መሙ እ ዘፀ ግግ ከመሙ መመ ገ በቴክኒዮሎጂ አለመራቀቃችን ወዘተ አይደለም ምናልባት ለብዙ ምሁራን ላይዋጥ ይትላል እኛም መሰልጠን በተክኒዎሥሉሎጂ ማደግ በቀለም ትምህርት ማደግ ይጎዳል አላልንም አንልምም ልንረዳው የሚገባ ግን አንድ ታላቅ ምሥጢር አለ ሀገራችን ወደድንም ጠላንም ከእግዚአብሔር ጋር ያላት ቁርኝት ምሥጢር ነው ሀገራችን በቅዱስ መጽሐፍ ታሪክ ውስጥ በቁጣና በበረከት ከተጠቀሱ ሀገራት መካከል አንዲ ነች እውነት ነው አባት ልጅን እንዲቀጣ ሀገራችን በእግዚአብሔር በትር የምትቀጣባቸው ምዕራፎች ተገልጠዋል ደግሞም ይሆናሉ ከተጻፈ ልናመልጥ አይቻለንምና ደግሞም የበረከት ምዕራፎች አሉን እነዚህ ምዕራፎች ዓቢይ ዓላማቸው ለእኛ ለሀገራችን ብቻ ሳይሆን ለዓለማችን የሚተርፍ ጸጋና ምህረትን ሊያመጡ የሚችሉ የእግዚአብሔር ስጦታዎች ናቸው በተለይም ኢትዮጵያ ከቅጣት ከግሣፄ በኋላ ወደ እግዚአብሔር በምትቀርብበት ጊዜ የእግዚአብሔር የወንጌል ሠራዊት ከላይኛው የአፍሪካ ክፍል ግብጽ ጀምሮ ኑብያን ሱዳንን ይዞ የዛሬይቱን ኢትዮጵያንና ላይኛውን ሶማልያ እንዲሁም እስከ የመን ዳር ድረስ ካለው ምድር እንደሚነሣ የታመነ ትንቢት አለን «ይምጽኡ ተናብልት እምግብጽ ኢትዮጵያ ታበጽሕ እደዊፃ ኀበ እግዚአ ብሔር »አማላጆችመኳንንቶች ከግብጽ ይምጡ ኢትዮጵያ አጆቿን ወደ እግዚአ ብሔር ትዘረጋለች መዝ ይላልና አሜን ይሁን ይደረግ ይህን የእግዚአብሔር ተስፋ ኢትዮጵያውያን እንዳያዩ አሊያም እንዳያስተውሉ ሰይጣን በብዙ አይነትና ጎዳና ስልፍ ከከፈተባቸው ተቆጥሮ የማያልቅ ትውልድ አልፏል ጦርነት ረኃብ የእርስ በእርስ ግጭት የቋንቋ የብሔር የጎሣ የነገድ ልዩነቶች እነዚህ የዋናው ኃጢአታችን ቅርንጫፍ ምልክቶች እንጂ በራሳቸው ኃጢአት ሆነው የተገለጡ አይደሉም ብዙዎቻችንም ያልተገለጠልን ነገር ይህ ነው ሃይማኖተኞች የተባሉት እነዚህን ነገሮች ለማጥፋት ዘዴ ሲቀይሱ እምነት አልባ የሆኑት ደግሞም ችግራችን አለማደጋችን አለመማራችን አለመሰልጠናችን ወዘተ ናቸው በማለት ጊዜና ጉልበት ያባክናሉ እስራኤልን ልብ ይሏል እስራኤል በእግዚአብሔር የታሪክ መዝገብ ከፍ ያለውን ሥፍራ ይዛ የምትገኝ ሀገርና ሕዝብ ናት ግና ትዕዛዛቱን ባለመከተል በአመጸኝነቷ በመግፋቷ ልዑል እንደተናገረ እንደ ምድር አሸዋ በዓለም ሁሉ በተናት ይህን ያደረገባት አለመሠልጠኗ በቴክኖሎጂ አለማደዓ ሳይሆን በእግዚአብሔር ሕግ አለመኖሯ ነው እንደተጻፈባትም የተቀጠረላት ቀን እስኪደርስ በዓለም ሁሉ ተበተነች ተሰቃየች እንደተነገረላትም ትሰበሰብ ዘንድ ሰዓቱ ሲደርስ ከተበተነበት ይሰበሰቡ ዘንድ የዓለም መንግሥታት ዓይኖቻቸው እያዩ ከመንደር ከዓለማት ጥግ ሳይቀር በዘምባባ ዝንጣፊ ሆ እየተባሉ ይሸኛሉ ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን ዳሩ ልዑል ከተናገረ ማን እምቢ ሊል ኢትዮጵያ በራሱ በእግዚአብሔር አፍ ከአስራአል እኩል እንዲያውም ከፍ ባለ ንግግር የተጠራች ሀገር ናት ልብ ይሏል ይኸኔ ነው መዝ ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በሀገራችን እንዳይገለጥ ሰይጣን ያልከፈለው ዋጋ የለም በጠበብቶች በአጥኝዎች በውጭ ኤክስፐርቶች የተጠኑት ችግሮች ናቸው የተባሉትን በመቅረፍ በመቁረጥ የምንገ ላገል አይደለም ሰልጥነንም በልጽገንም ከአግዚአብሔር ካልታረቅን የሰለጠኑ ስደተኞች የሰለጠኑ መከረኞች የበለጸጉ ባለመከራዎች መሆናችን አይቀሬ ነው በጥቅሉ የሀገራችን ችግር እንዳይገለጥ እንዳይወገድም ጋርዶና ሽፍኖ የያዘው ምሥጢር ኮሚኒስትነት ሶሻሊዝምነት ኢምፔሪያሲዝምነት ለዘብተኛነት ዲሞክራትነት ግራ ወይም ቀኝ ክንፍ የፓለቲካ አመለካከት አይደለም በዘመኑ የሶሻሲዝምን መመሪያ ወደ አፍሪካ ይዘው በመጡ ጊዜ አፍሪካን በኪህ ሥርዓት ለመሸፈን ከሰለጠኑት ይልቅ አስቸጋሪ እንደሚሆንባቸው ይናገሩ ነበር ምክንያቱም አፍሪካውያን ሁሉ ነገራቸው ፃይማኖተኝነት የተጠናወተው በመሆኑ ፃይማኖት የለም ብለው የኮሚኒዝምን ሓሳብ በሕወታቸው ለማዋፃሃድ የማይቻል በመሆኑ ነው ይላሉያኖም አንዳንድ የሰለጠኑ ሀገሮች የአፍሪካ ችግር ያለመሰልጠን ነው ብለው የሚያስቡም አሉ ስለሆነም እንሰለጥን ዘንድ እኛ በሌለንበት ስብሰባ ያደርጉልናል ያስቡልናል ብንሰለጥን ከችግራቸው ይላቀቃሉ ብለው መልካም የሚመስል እውነት ነው አፍሪካውያን ግን ከሥልጣኒው ይልቅ እነሱ እንደሚሉት ዘመናትን ተሻግሮ የመጣን ምንም ይሁን ምን ፃይማኖት ያሉትን ሥርዓትና ትምህርት ያለጥያቄና ያለማጉረምረም አሜን ይሁን እያሉ መኖርን ይመርጣሉ ሀገራችንም ተመሳሳይ አቋም ያላት ሀገር ናት የኢትዮጵያም ይሁን የአፍሪቃ ችግር ሃይማኖተኝነት ያለ እውቀት መሆኑ ነው እውቀት ማለት በሰማይ ለመብረር የሚያበቃው ጥበበ ዓለም ብቻ ማለታችን አይደለም የእምነት እውቀት ማለታችን እንጂ ሃይማኖተኝነት ያለ ፃይማኖት እውቀት ሕዝብንም ሀገርንም ያጠፋል «ሕዝቤ ፅውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቷል» እንደተባለ መጽሐፍ እናንተ እውነት ታውቃላችሁ ሲል የሚታወቅ እውነት መኖሩን ሲያስረዳ እውነትም አርነት ያወጣችኋል ሲል ደግሞ ያወቅነው እውቀት የሆነ ነገር እምነት ከማናቸውም መንፈሳዊ ክስረት የተጽዕኖ ነጻነትን ማሰጠት የሚያስችል ብቃት ያለው ይሆናል ይህም እውነትና ነጻ አውጪ ክርስቶስ ነው እምነትና የእምነት እውቀት በአንድነት ካልተገናኙ እናያለን ትላላችሁ ግን አታዩም እንደተባሉት የአይሁድ ካህናት መሆናችን አይቀሬ ነው አፍሪካ በድኅነቷ እያደገች በመከራ እየበለጸገች እንዲህ የምትታየው የኤቢሲዲ ችግር ብቻውን ሊሆን እንደማይችል አፋችንን ሞልተን እንናገራለን ሥልጡናኑ አፍሪካን የሥልጣኔ ችግር ቢሏትም አፍሪካውያን ራሳቸውን በራሳቸው ለማጽናናት ባለቸው ምኞት የሰው ዘር መገኛ ቀደምት ፍጡር የሥልጣኔ አሻራ የድንቅየ አራዊት መኖሪያ በማለት ሲያሞካሹዋት ይገኛሉኦ ለንዲያውም በቅርቡ በቲቪ አፍሪካ ላይ በሚታይ ገስታወቂያ በጠጠር የሚደረግ ጥንቆላን የመጀመሪያው የሕክምና መገኛ ምንጭና የሂሳብ ቀመር መነሻ በማለት የአፍሪካን የፃይማኖተኛነት ጉዳይ ተናግረውላታል በሃገራችን በኢትዮጵያም ችግራችን መንፈሳዊ ሽፋን ተላብሶ ያደገ በመሆኑ መሪዎቻችንም ሆኑ ጠበብቶቻችን ሊደርሱበት የማይችሉት የተሰወረ ገፃድ የተደበቀ ግልጥ ሆኖባቸው ተቸግረዋል ቀናት በሚከበሩ በዓላትና ተደግሦ በሚበላበት በሚጠጣበት ሀገር በምግብ ራስን መቻል የሚለው የመንግሥታችን መመሪያ በባሕር ላይ የወደቀ ኩበት አስመስሉታል ሕዝባችን መንፈሳዊ የሚመስሉ ቃላቶችን የተናገረ ሁሉ ጻድቅ እየመሰለው በተለይም የሕዝቡን ስህተት እስካልነካ ድረስ ነው የተናጋሪውን ቅድስና ታይቶና ተሰምቶ በማያውቅ ርቀት ከፍ እያደረገ ቅዱስ ዕገሌ የበቁ የነጡ የጠደቁ እዝጌር የሚናገራቸው እመቤቴ የምታነጋግራቸው እያለ በራሱ ላይ ታሥሮ የኖረ ሕዝብ ነው አንድ ሰው የኢትየጵያን ሕዝብ ለመምራት የሚፈልግ ሁሉ የጦር መሣሪያ ይዞ ከሚዋጋ ይልቅ ጥሩ የሰለጠነ ወሮበላ ባሕታዊ ቢያሰማራ ያለምንም ደም ኢትዮጵያ ትገዛ ነበር አሉ ለምን ሲባሉ ለሃይማኖተኛው ሕዝባችን እመቤቴ ተገዙ ብላለች እመቤቴ እንዲህ ብላለች እያለ በመስበክ ሕዝቡን ይይዝለት ነበር በማለት ተናግረዋል ነገሩ እውነትነት ያያዘ ትዝብት ነው በአርግጥ አባቶቻችን አዝዘዋል ሠለስቱ ምዕት ደንግገዋል እመቤታችን ተገልጣ እንዲህ ብላለች ጻድቁ አባ ዕገሌ ይህን ተናዘው አልፈዋል የሚል ጮሌ ሁሉ ከጳጳስ ይልቅ ቦታ ያለው በመሆኑ የሀገራችንን ችግር ውል ውስብስብ እንዲል አድርጎታል ፃይማኖተኝነታችን በበጎ ጎኑ ሊታይ የሚችለው የዘላለምን አምላክ እግዚአብ ሔርን የዘላለም አምላክ ስንስብከውና ስናስከብረው ብቻ ነው መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥ እንደሚ ያስረዳን የዚህ ዓለም ሰዎች የእግዚ አብሔር ቁጣ በላያቸው ላይ የሆነበትን ምክንያት ሲናገር አግዚአብሔርን እንደ እግዚአብሔርነቱ ስላላከበሩት ነው ይለናል ሮሜ እነዚህ ሰዎች ሃፃሃይማኖተኞች ናቸው የሚጠሩትም እግዚአብሔርን ነው ነገር ግን እንደ እግዚአብሔርነቱ አይደለም ይህም ማለት እግዚአብሔር እንዲመለክ እንዲመሰገን የሚገባው ከሰው በወጣ መስፈርትና ፍላጎት ላይ በተመሠረተ መመሪያ ሳይሆን ሊመሰገንበት በሚሻው መንገድና ሁኔታ እንዲከበር ባለሥልጣኑ እርሱ ሆኖ እያለ እንደመሰላቸው ወይም ይህም መልካም ነው ያም መልካም ነው በሚል ሰውኛ እሳቤ ሊያመልኩት የሚወዱ ሁሉ ከእግዚአብሔር ፍርድ እንደማያመልጡ ሲናጋር እንደ እግዚአብሔርነቱ ስላላከበሩት አሰ ሕዝባችን እግዚአብሔርን የሚፈራ የሚወድ እየተባለ ረጅም ዘመን ተነግሮ ለታል ይመስላልም ይሁን እንጂ እግዚአ ብሔርን መፍራት ለእግዚአብሔር መታዘዙ ዕገሌ እንዳለው ዕገሊት እንዳላቸው በሚል የተንኮለኞች ፈሊጥ የተሞላ በመ ሆኑ በልቡ የራቀ በከንፈሩ የሚያመልክ ሆኗል ይህ የተሸፈነ መንፈሳዊነት ምንም ነገር ቀና ብሎ ለማየት ዕድል ስለማይሰጠው በሕይወቱ ላይ የተደገሰውን የጠላት እቅድ ያለተቃውሞ ሲያስተናግደው ኖሯል «ለሰው ልጆች ሲል በመስቀል ላይ የተሰቀለ የእሾህ አክሊልን በራሱ የደፋ መርቆሬዎስ ነው» ብለው ሲያዜሙለት አሜን ከማለት ውጪ አማራጭ የሌለው ሕዝባችን ክፉዎች ካስተማሩትና ካስለመዱት የተንኮል ትምህርት መላቀቅ የሞት ያህል ሆኖበት ዛሬም እንኳ ዕድሜውን በቪያው እንዲያሳልፍ ሆኗል በዚህ ድርሳነ ዑራኤል በተባለ መጽሐፍ እንዲህ የሚል ክህደት ይገኛል ልቡን በክፉዎች ትምህርት የተነጠቀው ሕዝ ባችን ይህንና ይህን መሰል በሃይማኖት ሽፋን የተለበደ ወንጀል አየተፈጸበት ሳይ ረዳ ቆይቷል ጽሑፉ ሲመዘን ጽንስን የሚሰጥ ማን ነው ።