Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convert to Pdf
  • Reading List
  • Summary
  • Audiobook
  • Search
  • Upload
  • myzon
  • Log in
  • Register
English  አማርኛ  Français  العربية
Book of the day

እሳት_ወይ_አበባ_በ_ጸጋዬ_ገብረ_መድኅን.pdf


  • word cloud

እሳት_ወይ_አበባ_በ_ጸጋዬ_ገብረ_መድኅን.pdf
  • Extraction Summary

ቀጥሎም ኪነጥበብ ከቀዋሚ የኑሮና የመደበኛ ሥራ ክፍሎችም ጋር እያደር ተደጋግፎ ሲጠና እንደየሥራው አንፃር ለምሳሌ በሠርግና በቀብር ሥርዓት አማካዩን የዘፈንና የሙሾ ግጥሞች በግብርና የግብርና ጠቀስ ግጥምና ዜማዎችን በሃይማኖትና በአምልኮ ባዕድም የኒሁኑ ጠቀስ ባስመዝሙር ባለጸሎት ባለወረብ ባለወሸባና ባለዝየራ ግጥሞችን ተከባክቦ ይታያል እዚህ ሳላይ ዋና ዋናው ተግባር ያው ሠርጉ ቀብሩ ግብርናው ሃይማኖቱና እምልኮባዕዱ ሲሆን ለየጉዳዩ የተደረደረው ግጥም ግን ለየተግባሩ ተቀጥላነትንና ማሞካሸትን ይዞ ኖረ ማለት ነው። ምክንያቱም በጠቅላላው የኪነ ጥበብ መልእክት ከሰው ተፈጥሮ ወደስው ሆኖ ተቀባይነቱም እንደየዘመኑና እንደየትውልዱ የጣዕምና የዝንባሌ ዳኝነት የሚመጠን ስለሆነ ነው። የሁለቱ የታሪክ ልዩነት ይኸ ነው። ሰለሆነም ለምሳሌ አብዛኛዎቹ የኔ ግጥሞች ካሁን ቀደም ብዙዎች ጠይቀውኝ እንደመለስኩት ሁሉ እሰካሁን ከተለመዱት ከዋነኞቹ ከግዕዝ እስከ አማርኛ ውርሰ የሥነግጥም ድንጋጌዎች ውሰጥ ማለት የወል ቤት እንዳልነው ባለሰድስት ሁለት ባለሦስት ሐረግ እንደሆያሆዬና እንደ ሰንጎ መገንና ከቡሄ በሉ ቤት አፈራርቆ እንደሚደረደረውና እንደሚደረደሩት ብዙዎች የኩሽና የሳባውያን አረብ ዲቃላ ቋንቋዎች የዘልማድ ሕግጋት ሳይሆን የቁጥሩን መለያ መሠረት አንድ ራሱን በስምንት የሰንኝ ሰልት ድንጋጌ ላይ ስለምደረድረው ብቻ ነው። እንዳይነግርህ አንዳች እውነት። ምንድነን እኮ። ያለፈ ጥረታችንን ሳስታምመው ትዝ ሲለኝ ከሞከርነው ነገር ይልቅ ያልሞከርነው ነው እሚቆጨኝ።

  • Cosine Similarity

ቃል እውነት ነውና። ቃል ሕይወት ነውና። ያቺ ዓድዋ ሕይወት ቢራ ቢሮ መሸ ደሞ አምባ ልውጣ። አባይ ለየኔታ አሥረስ የኔስው መሄዴ ነው ዶጋሊ ቦረን ያሙርቲ ጸሎት ጥሪ ለማዳ ጋልማአባ ጋዳ ውሸታም ክፋ እሳት ዐመድ ወለደ ለተማሩለማይምሩ አፈሊቃውንት ሐረር ለከበበው አሻግሬ እውነት አሁን አንቺ እሷ ነሽ በራ የመስቀል ደመራ ጌራ ማይጨው ድሬዳዋ ተወኝ አራት ኪሎ ፅ አምቦ ሀ ቴቤስ ሙታን ከተማ ቤልግሬድ ጉርጉስም ብ ዲሬ ስድስት ኪሎ ሀፃሀ ጂማ ፅ አዲሳባ ሇ ሐረር ሀ አዳማ መስቀል አደባባይ ፓሪስ ብ ሀፃ ግይጨው ሀ ድሬዳዋ ኒውዮርክ ድንቅም ኣደል። ለብቸኞች አብረን ዝም እንበል አሥመራ ወንድ ብቻውን ነው እሚያለቅሰ ለዘውዴ ሸዋሞልቶት አዘቦን ዳግም አየኋት እንዳይነግርህ አንዳች እውነት። ይኸ ይሆን አሰቀድሞ ቃል። ያንቺሳ ምሥጢር ምንድነው ቢራ ቢሮ እንወያይ አንቺ የዕፀዋት አዋዋይ ከፀደይ ጋር ፀደይ መሳይ ከአበባም አበባ መሳይ ምን አለበት ላንዲት ሰሞን ቢራ ቢሮ እኔ አንቺን ብሆን በፍስሃሽ ብጥለቀለቅ ብነግሥባት ባንቺ ጽዮን። ነይ ብር በይ እንወያይ አንቺ የዕፅዋት አዋዋይ ከፀደይ ጋር ፀደይ መሳይ ከአበባም አበባ መሳይ ምን አለበት ላንዲት ሰሞን ቢራ ቢሮ እኔ አንቺን ብሆን። እና እምታውቁት ንገሩን እውነት ራብ ሰንት ቀን ይፈጃል። ስንት ያዘልቃልገ እውነት ራብ ስንት ቀን ይፈጃል። የኔ እጅ እኮ እርፍ አይጨብጥም የኔ ክንድ ተልም አይተልምም የኔ ጣት አረም አይነቅልም በፊደል መፈደል በቀር ጉልጓሎ እኮ አይጐለጉልም ለስልሻለሁ ሠልጥኛለሁ ሰይጥኛለሁ አልሆንሽም አቴቴ ዱብራ ቦረና መቸም ሁሉን ቻይ ነሸና አጥንቴ ከአጥንትሽ ማዕድን ቢመነጭም ተቀምሞ ከዝና ከኢልሐዱ በፊት ከቃል በፈት አስቀድሞ ዛሬ በዓይንሽ በዓይኔ መሀል አጉል ሥልጣኔ ቆሞ ሰየጠንኩና አልሆንሽ አልኩ አቴቴ ዱብራ ኦሮሞ አዎን መቻል ባንቺ ያምራል ያን የትዝታ ሰቀቀን ያን የልጅነት ሰመመን ምንም በውል ባንደርስበት ጭላንጭሉ እየታወሰን ውል ሲል እንዳልጠፋ ቀን ከዓመት ዓመት ተሸጋግረን አዳዲስ ዘመን ሲስለፍ ስንበሌጡ ሲንተረከክ የአዝመራ እሸት ሲትረፈረፍ የማር እሸት እንቁረጥ ተይ የጥቅምት አበባ እንቅጠፍ ነይ ሸጎዬ አብረን እንግዘፍ ጣት ለጣት እንቆላለፍ በዓይን ጥቅሻ እንገራረፍ ከአውድማችን አፋፍ ሰአፋፍ በዳሰሳ እንጠላለፍ ተይ ፍቅር እንዘራረፍ በሕልም እንኳ እንተቃቀፍ እቴቴ ዱብራ ቦረና አቴቴ ዱብራ ኦሮሞ የቀን የጊዜ እንቆቅልሽ በሕልም መርፌ ተጠቅሞ በየመከሩ ተተልሞ ከትዝታ ጋር አሰታምሞ እንደዘነጉት የእናት ጡት ከዘመን ጋር አገግሞ ምንም ቢርቅ ምንም ቢሸሽ ሕልሜ ከሕልምሽ ተዛሞ በዓይንሽና በዓይኔ መሃል አጉል ሥልጣኔ ቆሞ ባንተያይ ባንወያይ እንደጥንቱ እንደቀድሞ እንደልጅነት ስመመን ዕድሜም እኮ ያማል ደሞ አዎን ዕድሜም ያማል ከርሞ አቴቴ ዱብራ ኦሮሞ። እስከመቼ ይሆን አዋሽ። እሰከመቼ ይሆን አዋሽ። አዋሸ አባ ሮሮ ቅርሱ የዘለዓለም ንዳድ ጉርሱ አዋሽ ቡቡ በረኸኛ የአረህ ሸለቆ በረኛ የአሸዋ ዋሻ መተኛ የበረሀ ዋነተኛ የምድረ በዳ ብቸኛ የዘለዓለም መንገደኛ የአበቅቴ መወራረሻ የዕፀዋት ዕድሜ መቁጠሪያ በፀደይ የአልባሳት ማዕጠንት የዘመን ላቦት ወዝ ማጥሪያ የእንቁጣጣሽ ማዳበሪያ የአዝርእት ሰብል ማጥለያ በክረምት የዶፍ ረከቦት የሰማይ ምጥ መቀበያ የደመና እምባ ማጠቢያ የማዕበል ሰደድ ማከያ የተራሮችን ለቅሶ ቻይ የጅረት የምንጮች አዋይ ጭምት መሳይ ያለዐመሉ ዘራፍ ባይ በመስክ ሙሉ አባ ጭራቅአክናፍ ቀንዶ አዋሽ ዘጠኝ ራሳ ዘንዶ ቁልቁል እንደምሽት ጥላ ከሰማየ ሰማይ ወርዶ ሞልቶ ተንደላቆ ኮርቶ የሰንት ዓለም ምድር ጐርዶ ቀይ ደመና ተክናንቦ ጋራ እንደአሻንጉሊት አዝሎ ስንቱን በረት እንደጉድፍ አውተፍትፎ አንጠልጥሎ አውድማውን አንገዋልሎ ወርካውን ግቻ አሳክሎ አመንምኖ አስልሎ እንደዘጠኝ በገና አውታር በየረድፉ ተሰድሮ በአገር ምድር ዙሪያ ጥምጥም እንደመቀነት ተቋጥሮ አዋሽ ቁጣ አባ ዱታ የሰማይ ጥጉ ቱማታ አዋሽ አባ ሻኛው ጋራ ኩሩ እንደነማታ ሐራ የግርማ ሞገስ መርገፉ እስከነምድረአቀፍ ዘርፉ አባ ገርስስ ሞልቶ ደራሽ አባ አደፍርስ አባ ኩርፋድ ከተፍ እንደመብረቅ ግማድ በምድር ቁና ድንገት ሲጣድ አዋሽ ንፉግ አባ መዓት የገጠሬ አታምጣ ምጣት አዋሽ ደርሶቀማውመብረቅ አባ መዝረፍመውሰድመንጠቅ ግሣንግሱን አግበባስብሶ በምድረ በዳ ለማጨቅ ህሩር ጉረሮ ለማመቅ የአሸዋ ሆድ ለመጠቅጠቅ ህራም ብሎ አብሮ ስመጥለቅ እምድረ ከርስ መቀመቅ እስከመቼ ይሆን አዋሽ። አዋሸ ብኩን ምሥጢረኛ የጠፍፋኖ አባ ብቸኛ የበረሃ መንገደኛ የጨረቃ ግዞተኛ ካገር ሞት ወዲያ ላትሞት ካገር ምጥ ወዲያ ላታምጥ እስከመቼ ይሆን አዋሽ ራስክን በራስህ እምትውጥ። አዋሽ አባ ሮሮ አገሩ ያሸዋ ማኅፀን ድንበሩ የምድረ ዓለም ኬላ በሩ ኩሩ ብሶት እንደልቡ ቅምጥል የሸዋ ቡቡ የሰማይ አድማስ ግድቡ ንዳድ ስንቁ አረህ ግቡ እስከ መቼ ይሆን አዋሽ። እስክመቼ ይሆን አዋሽገ መቸም ሌላ ንግርት የለህ እንደ ሴቴ ሸረሪት ፅንስ ራስክን በራስህ ዋጥ ያለህ እስከመቼ ይሆን አዋሽ። ማኅፀንሸ ጽዋው መረዘኝ ዘጠኝ ወር ያጠባኝ ገንቦ ጡትሽ የደም ወተት ዘንቦ ሆድሽ የቁስል ምጥ ታልቦ ባዳ ቅሪት ተመትሮብሽ የእንብርቴ እልባት ተስብሮ ደሜ በፋፋበት እትብት ገፊ ዲቃላ ተቋጥሮ በቃ እማማ እማማዬ መቀነቴ ገበናዬ በቃሁሽ አድባሬ መቅኔ ከእንግዲህስ ላንቺ መጥኔ እዬ ላንቺ አዬ ለኔ ጫቅላዬን ባዘለ እቅፍሽ ገፊ ጉግ ማንጉግ መፅነለሸ ጐምቱ ሾተላይ ማብቀልሽ አይሆንም እንጂ ከሆነሸ ካለልሽ ካዘለቀልሸ እግዚአብሔር ያሳድግልሽ አዎን ቃል ለምድር ለሰማይ ደኅና ዋይ በቃ ደኅና ዋይ ዓይኔ ዓይንሽንም አያይ ክፉም በጐም አናሰማ እንዲያው ደኅና ዋይ እማማ እናት ዓለም የስሜ አርማ የሕይወቴ ወዝ የዓይኔ ማማ እማትነፍጊ እማታቅማሚ እማታሳጪ እማታሟ እኔን በራበኝ በጠማኝ አብረሽኝ እምትጠሚ ጥቃቴን እምትጠቂ ቁስሌን እምትታመሚ ፍሥሃዬን ፈገግታዬን ሳቄን ብቻ እምታልሚ አንቺ እማማ አንቺ የነፍሴ ልብ ዓልማ የዓይኔ ማማ ምነው ጡትሽ ተጣረረኝ። ለኳስ አርበኛ አዴ አዳዬ አዴ አዳዬ እመምኔቴ የትውልድ መስታየቴ የዘመን ቅርሴ መክሊቴ የዕድሜ አንቀልባዬ ሞግዚቴ ቀን ማገረሽ አንቺ እጣዬ ጃጀሽ አሉኝ አዴ አዳዬ በሥጋትሽ ተንጠልጥዬ በአንገትሽ ማተብ ታዝዬ በዓይንሸ ጢሎሽ ተንጠልጥዬ በጮጮሽ ተሞካሽቼ በጉርሻሽ ውሽን ተብዬ በእንጐቻሽ ተከባክቤ በእንኮኮሽ ተደሳድዬ ካፍ ከወጣ አፋፍ ነው ሲባል ለካለሰ ነገር ይገለማል አዴ አዳዬ የአባዬ እናት ለምን ይሆን ያሉሽ አያትያ ባፍ ዝምድናሽን ሲያቀርቢት ስምሽን ሦስት እጥፍ ያራቁት። አዴ አዳዬ እመምኔቴ የትውልድ መሰታየቴ የዘመን ቅርሴ መከሲቴ የዕድሜ አንቀልባዬ ሞግዚቴ ቀን ማገረሽ አንቺ እጣዬ ጃጀሽ አሉኝ አዴ አዳዬ። ጊዜ የጊዜ ነው እንጂ አንቺ እኔ ነሽ እኔ አንቺ ነኝ ብልሽ ላንደበት ወግ በቀር እኔም አንቺም አንጠቀም ሕመሜን ሳትታመሚ ሕመምሽን ላልታመም የዘመን አጥር ክፍሎናል አውቀነዋል አንደለል ታድያን ጊዜ የጊዜ እንጂ ድሮም የዘለቄታ አደል እና የነገ ጥሪዬን ዛሬ በጥሪሽ አየሁት አዴ አዳዬ እመምኔቴ ጭንቄን በጭንቅሽ ለየሁት እንጂ ካንቺ አልክፈልም እኔ ቁሰልሽን አልቄስልም ጣርሽን አልጣጣርም በጉልበትሽ እንደጠናሁ አንቺ በጉልበቴ አትጠሂም በወዝሽ አንደለመለምኩ በወዜ አትለመልሚም ቁቤ ያንቺን መንጠቅ እንጂ ዕዳ መክፈሉን አያውቅም በጉርሻሽ መጥናቱንም በቀር መጠንጠኑን ከቶ አያይም አዴ አዳዬ ብቻሽን ነሽ ጣር እሚካፈልም የለሽ። ከዋክብቱ እንደችቦ በነበልባል ወርቀ ዘቦ ከፅንፍ ፅንፍ አውስብልቦ ደመራው እየተመመ እየፋመ እየጋመ ደመና እንደ ንዳድ ሲነድ መንጸባርቅ ሰደድ ሲወርድ በራሪ ኮክብ ተኩሶ በአድማሳት እሳት ለኩሶ ይኸ እንደኔና እንዳንቺው የውበት ዓይኑ የሰለለ ሰማይ ጨለማ ነው እንጂ እሳት እኮ አደለም አለ ያልታደለ ይቅር ብቻ አንናገርም እኔና አንቺ አንወያይም ለውይይት አልታደልንም እንዲያው ዝም እንጂ ዝም ዝም። ከዋክብቱ እንደችቦ በነበልባል ወርቀ ዘቦ ከፅንፍ ፅንፍ አውለብልቦ ደመራው እየተመመ እየፋመ እየጋመ ደመና እንደንዳድ ሲነድ መንጸባርቅ ሰደድ ሲወርድ በራሪ ኮከብ ተኩሶ በአድማሳት እሳት ለኩሶ ይኸ እንደኔና እንዳንቺው የውበት ዓይኑ የሰለለ ለማይ ጨለማ ነው እንጂ እሳት እኮ እደሰም ኣለ ያልታደለ ይቅር ብቻ አንናገርም እኔና እንቺ አንወያይም ለውይይት አልታደልንም ራሪ እንዲያው ዝም እንዲያው ዝም ዝም። መስከረም መስቀል አደባባይ ጌራ ጌራ ነበልባል ዘለሳ እንደመንጸባርቅ ጥሳ ሽልም ሽፋልሽ ሲያጠሳ ጌራ የፈተና መከር የቁንጅና ራዕይ በር እድብተሽ እንዳረህ ደለል በልብ እሳት ለመዋለል ሰቀቀን እስኪዘነበል ጣር ለጣር ለመቀላቀል ድንገት ደርስሸ ለመንጣለል ጌራ የልጅነት ፍቅር ድብቅ የዕድሜ ልክ ምሥጢር አይሆንም እንጂ ቢሆንሽ ነፍሳችን ይኳረፍ እባክሽ። ጌራ ብኩን ጌራ ብካይ ጌራ ከንቱ ጣር አሰልሳይ ጌራ የሕልም ዓለም ሰቃይ ጌራ ሰቀቀን መከራ በቅዥት ከምንጣራ አይሆንም እንጂ ቢሆንሽ ነፍሳችን ይኳረፍ እባክሽ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Comments:


memezon

Download options | Convert to Pdf | Book of the day

© dirzon | Terms of Service | Privacy | About | Services | Contact