Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ድብቁ እውነት ሲገለጥ ክፍል አንድ ተሻሽሎ የቀረበ ሦስተኛ ዕትም የአገራችን ዳኢዎች ሳዲቅ ሙሐመድና መሰሎቹ እንዲሁም አሕመድ ዲዳትና ተከታዮቹ በመጽሐፍ ቅዱስ እንደሰው የማያስብ እንደ ሰው የማይሳሳት ፍጡር አይደለም በዮሴፍና በአባቱ በያዕቆብ ታሪክም የታየው ይኸው ነው ያዕቆብ ነቢይ ነበር ከተባለ የልጁን ፍጻሜ ካቀደው ከእግዚአብሔር ካልሰማ በስተቀር ሊያውቅ የሚችልበት ምንም መንገድ ሊኖረው አይችልም ወደፊት የዮሴፍ ፍጻሜ ምን እንደሚመስል እግዚአብሔር የተናገረው ለያዕቆብ ሳይሆን ለራሱ ለዮሴፍ ነበር ያዕቆብ ሲሰማ የሕልሙ ፍች ቢገባውም ከዘለአለም አምላክ ዘንድ የመጣ ለመሆኑ ምንም ማረጋገጫ ስላልነበረው እንደ ቅዥት ቢመለከተው ሰው ነውና አልተሳሳተም እንዲህ እንዲያስብ የሚያደርጉት በርካታ ምክንያቶች ዙሪያውን ከበውት እንደነበር ማስተዋል አይሳንም ዐክ ዐፀሀጸክዐሰ ህዐ ዐዐፀፀ በጊዜው እርሱና ቤተሰቡ የነበሩበት የአኗኗር ሁኔታ ያዕቆብና ልጆቹ ምንም እግዚአብሔር እየኖሩበት ያለውን ምድር እንደሚያወርሳቸው ቃል ቢገባላቸውም በሕጋዊነት የራሳቸው የማሟሆንበት ጊዜ ገና ነበር ስለዚህ በሰው አገር በሌላ ሕዝብ ላይ ምጻተኛ ሆኖ ንግሥና ማሰብ ያውም ገና ወጣት ልጅ የማይታሰብ መሆኑ ኦሪት ዘፍጥረት ያለው የቤተሰብ ቁጥር ማነስ እንደ መንግሥት ተቋቁሞ ንግሥናው ቢታወጅ ራሱን ለመከላከል የሚችልበት የሕዝብ ብዛት ላይ ያልደረሰና ያልተደራጀ መሆነ ደግሞስ በማን ምድር ላይ። ብለው ከጥያቄ ጋር አሳባቸውን ያስቀምጣሉ አለማወቅ ኃጢአት አይደለም በትክክል እንኳን ሳያነቡ እንደ አዋቂ ብዙ ማውራት መልካም አይደለም የመጽሐፍ ቅዱሱ ክፍል የሚናገረው ስለምንድን ነው። በሚለው ሥራዬ እመለስበታለሁ አሁን ወደ አንድ የነቢዩ ሙሐመድ የጉብኝት ሥፍራ ልውሰዳችሁ ሳሂህ አልቡኻሪ ቅጽ ቁጥር ነቢዩ ሙሐመድ ጀነት ስለመግባታቸው እርግጠኛ አይደሉም ታዲያ ለእርስዎ ሊኖር የሚችለው ተስፋ ምንድን ነው። ወደ ጢሞቴዎስ ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው። እርሱም ስለ ምን ትደነግጣላችሁ። ስለዚህ ሙሴ የጠየቀው መንፈስ የሆነውን እግዚአብሔርን ስለማየት ሳይሆን ክብሩን ማየት ነበር የክብሩ መገለጫዎች በርካታ እንደሆነ ደግሞ ከዚህ በፊት ተነጋግረናል ያንንም የሚታይና የማይታይ ብሎ ከፋፍሏቸዋል የማይታየው የክብሩ ክፍል ማስረዳት ነበርና ጀርባዬን ታያለህ አለው ይህንን ደግሞ በሁለት መልክ መልሶለት እራሱን አሳይቶታል ይህ ምን ማለት ነው ለዚህ ነው ናትናኤል እንድርያስ ሲጠራው ከናዝሬት መልካም ነገር። እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ። ከክፉዎችም ጋር መቃብሩን አደረጉ ከባለጠጎችም ጋር በሞቱ ሆኖም ግፍን አላደረገም ነበር በአፉም ተንኮል አልተገንበትም ነበር። ዳዘዐክህ ዛፎ ዐ ክፀ ርዖሮዐቨዐያ ፀ ወዐፀገበዐዐያ ዐህፀ ርያፎዐህፎ የ ኛ የከፀ ክፀዐህፀዘ ዐበሪ የፀ ፀወ አሪ ፀዐ ዛብ ክፀ ርህ ርስዐዐያ ሀያ ዳሩዳስ ሀበዝ ለ ህዐ ርዐቦ ዐዐዐ ዛጠጠ ፐክፀ ያዐያሀ ሮያ ርስዐዐ ያ ሀየ ዕክወሃ ፐክዐሮ ዐ ህክዐ ህፀዐ የካሮ ፐክዐበፀ ማጣቀሻዎች የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ እትም ትምህርተ ክርስቶስ በቄስ ኮሊን ማንሰል የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፖብሊክ ሕገ መንግስት ህዳር ዶር ዩሱፍ አል ቀረዷዊ ኢስላምን ለመረዳት ትርጉም በሐሰን ታጁ ነጃሽ ማተሚያ ቤት ሳዲቅ መሃመድ አህመድ አቡ ሃይደር ላለመደናገር ማመሳከር ተሸሽሎ የቀረበ ኢቅራ ቁርአን ሶፍት ዌር ነጃሺ መልቲሚዲያ ፐሮዳክሽን የተዘጋጀ ዕዘ ስዐቤ ስፀ ፎ ዕ ለህስዐበገበገዐጩ ክዐዘበዐሀሮሪ ይሃ ሀሀበገ ዘገፀፀበዐ ዐሪ ዐ።
መጽሐፍ ቅዱስ ለምን ተበረዘ ተባለ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ አለመበረዝ በነቢዩ ሙሐመድ ሐዲሳትና በሙፈሲሮች የተሰጠ ምስክርነት ሙግት ሁለት መጽሐፍ ቅዱስ የሰው አዕምሮ ሊቀበለው የማይችላቸው አሳቦች በውስጡ መያዙ ልጄን ቀቅላ የበላች እናት ልጅ ከአባት በእድሜ መብለጡ « የአላህ ነቢይ የሰውን ፋንድያ እንደ ምግብ በወር አበባ ላይ ያለች ሴት ሳይወልድ ለሞተ ወንድም ስም የማስጠሪያ ሕግ አህያ በሰው ቋንቋ ስለ መናገሯ የዛፎች የንግስና ውይይት የጾታ ፍቅር በአላህ ቃል ውስጥ የሰው የግል መልእክት በአላህ ቃል ውስጥ ሙግት ሦስት መጽሐፍ ቅዱስና ቁርአን በአሳብም ሆነ በመልእክት ያላቸው አለመስማማትህህ አላህ ከሥራ ደክሞት አረፈ መባለ ዑ ያዕቆብ በልጁ በዮሴፍ ላይ ያሳየው ምቀኝነት ሙሴ የአላህን ጀርባ አይቷል መባለ ሙግት አራት መጽሐፍ ቅዱስ በውስጡ ሥህተቶችን መያዙ የኢየሱስ ክርስቶስ ናዝራዊነት የትንቢት ቃል ይሁዳ ኢየሱስ ክርስቶስን የሸጠበት የትንቢት ቃል አባሪኢ ክን ከ ከ ከ ከ ከ ከከከ ማጣቀሻዎች ን ከ ከክ ከን አ ከ ከ ከ አከክ ከ ምስጋና በመጀመሪያ የሥራው ባለቤት ለሆነው ታላቁን ተልዕኮ የወንጌሉን ሥራ ከእርሱ ጋር እንድሠራ ታማኝ አድርጎ ለቆጠረኝ ባለፍኩባቸው መንገዶች አብሮኝ ለነበረው ለውዱ ጌታዩና አምላኬ ለልኡል እግዚአብሔር ምስጋናዩን አቀርባለሁ በእርሱ ደስታዬ ወደር የለውም ይህንን ሥራ አምላኬ በእኔ መሥራት አስቦ ፅንሱን በውስጤ ማንቀሳቀስ ሲጀምር አውቀውም ይሁን ሳያውቁ በተለያየ መልኩ ከእኔ ጋር ለመሥራት ቀኝ እጃቸውን የሰጡ ወገኖች በቁጥር በርካታ ነበሩ በተለይም አንደኛ ሁለተኛ እያልኩ ስማቸውን መጥቀስ ተገቢ የሚሆንብኝ ወገኖች አሉ ሆኖም በአንዳንድ ምክንያቶች ያንን ማድረጉን አልፈለግሁትም ይህንን ሲያነቡ ግን ምን መልእክት ማስተላለፍ እንደፈለግኩ እንደሚገባቸው በእርግጠኛነት መናገር እችላለሁ ለእነዚህ የልኡል አምላክ ባሪያዎች ምስጋናዬ ይድረስልኝ አብረን በመሥራታችንም ደስታዬ ታላቅ ነው ወደር በሌለው የአምላካችን እርሻ ውስጥ ትንሽዋን ጠጠር አብረን መጣል ችለናል በመጨረሻም ይህንን ስናደርግ እንደ አንድ ቤተሰብ እየተገጫጨንም እየተያያዝንም ሊረሱ በማይችሉ ትዝታዎች እየታጀብን የተሰባሰብንባት በባእድ ምድር የጌታ ምስክር የሆነችው ያች ውቧ የክርስቶስ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ች በዚህች ቤተ ክርስቲያን ጥላ ውስጥ ላሉ የውዱ ጌታ ድንቅ ልጆች ያለኝን አክብሮትና ምስጋና ልገልጽ እወዳለሁ ዛሬም ፍቅራችሁ በልቤ ውስጥ አለ ይኖራልም መቅድም ማንኛውም ሰው ደስ ያሰኘውን ሃይማኖት መከተሉ በአገራችን ሕገ መንግሥታዊ መብቱ ሰብአዊ መብቱ ከአምላኩም የተሰጠው የመምረጥ ግላዊ መብቱ እንደሆነ አምናለሁ ይህንን በሦስት የተገመደ የሰው ልጆችን ሕጋዊ መብት ማክበር ግዴታዬም ብቻ ሳይሆን ፈቅጄና አምኘበት የማደርገው የግል አቋሜም ጭምር ነው ሰው ይህኛው የሃይማኖት መንገድ ወደ አምላክ ያደርሰኛል ብሎ አምኖ መከተል ከፈለገ ትክክለኛነቱ ላይ ጥያቄ ቢኖርብኝም የወደደውን መከተል መብቱ ስለሆነ የተከተለው መንገድ ክብር ሊሰጠው ግድ ነው እናንተም ሙስሊም ወገኖቼም ስለመረጣችሁት መንገድ ምንም ዓይነት ተቃውሞም ጥላቻም የለብኝም ምርጫችሁን አከብራለሁ ይህ ማለት ግን ሁሉም የሰዎች ምርጫ በዓለም ያለው ሁሉም ሃይማኖት በአምላካዊው እውነተኛ መነጽር ሲታይ ትክክለኛ ነው ማለት አለመሆኑን ሁላችንንም የሚያግባባን ነጥብ ይመስለኛል አሊያማ አንተም እኔም ትክክል ነን ተባብለን የራሳችንን መንገድ ብቻ በጠበጠብን ነበር ግን አልሆነም በሱረቱል አልማኢዳ ሳይ አላህ ተናግሮ እያለ እንኳን መቀበል የተቻለ አልሆነም ሱረቱል አልማኢዳ ወደ አንተም መጽሐፉን ከበፊቱ ያለውን መጽሐፍ አረጋጋጭና በርሱ ላይ ተጠባባቂ ሲሆን በውነት አወረድን በመካከላቸውም አላህ ባወረደው ሕግ ፍረድ እውነቱም ከመጣልህ በኋላ ዝንባሌዎቻቸውን አትከተል ከናንተ ለሁሉም ሕግንና መንገድን አደረግን አላህም በሻ ኖሮ አንድ ሕዝብ ባደረጋችሁ ነበር ግን በሰጣችሁ ሕግጋት ሊሞክራችሁ ለያያችሁ በጎ ስራዎችንም ለመስራት ተሸቀዳደሙ መመለሻችሁ በጠቅላላ ወደ አላህ ነው በርሱም ትለያዩበት የነበራችሁትን ነገር ይነግራችኋል ይህ የሆነው እውነት አንጻራዊ ሀሀህ ሳይሆን አንድና አንድ ብቻ ስለሆነ ነው መነጋገር ያለብንም ስለዚህ አንድና ብቸኛ እውነት ነው ይህን እውነት ካገኘነው ብቻ ነው የሃይማኖታችንን ግብ የምንጨብጠው ታዲያ ይህ አንድና ብቸኛ እውነት የት ነው ያለው። በየዘመናቱ ሰዎችን ቅን ከሆነችው ከአምላካችን መንገድ እንዲመልስ ለማገዝ ሠራተኛ ሆነው የተገኙለት ሰዎችም ቁጥር እጅግ ብዙ ነው ቢሆንም የዘመናት ሥራውና አላማው ምን እንደሆነ ያለፈው ዘመን የቤተ ክርስቲያንና የሰይጣን የውጊያ ውሎ ታሪክና የአምላካችን የእግዚአብሔር ቃል በምክሩ አስጠንቅቆናል ስለዚህ ሰይጣን በሚያስነሳቸው አንዳንድ ሁኔታዎች ስጋት አይገባንም እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና አሳቡን በጭራሽ አንስተውም የዮሐንስ መልእክት ወዳጆች ሆይ መንፈስን ሁሉ አትመኑ ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር ሆነው እንደሆነ መርምሩ ብዙዎች ሐሰተኞች ነቢያት ወደ ዓለም ወጥተዋልና የእግዚአብሔርን መንፈስ በዚህ ታውቃላችሁ ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደመጣ የሚታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደመጣ የማይታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም ይህም የክርስቶስ ተቃዋሚው መንፈስ ነው የዮሐንስ ራዕይ ሱረቱል ፋጢር ሰይጣን ለእግዚአብሔርና ለሰው ልጆች ያለውን ጠላትነት ከሚያንጸባርቅባቸው መንገዶች አንዱ እውነትን መሰወር ነው የእግዚአብሔር ቃል እውነት ነው ይህ እውነት የሰው ልጆች እውነተኛውን የጽድቅ መንገድ በማወቅ አምላካቸውን እየወደዱትና እየተገዙለት በመኖር እርሱ ወደ አዘጋጀላቸው የዘለአለም ደስታ እንዲገቡ መንገዱን ያሳያል አምላካችን እግዚአብሔር ፍቅሩን እውነቱን ለሰው ልጆች የገለጸው በእውነተኛው ቃሉ በመጽሐፍ ቅዱስ ነው ሰይጣንም ለክፋቱ አዋጭ ስለመሰለው በዚህ ዘመን ቅድሚያ ሰጥቶ እየሠራ ያለው በእግዚአብሔር ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ታማኝነት እንከን መፍጠሩ ላይ ነው ለዚህም የአገራችን ዳኢዎች ሳዲቅና መሰሎቹ እንዲሁም አህመድ ዲዳትና ደቀ መዝሙራቸው ዶር ዛኪር ናይክ መጽሐፍ ቅዱስንና ቁርአንን እናነጻጽራለን በማለት ሥራውን እየሠሩለት ይገኛሉ እነዚህ ወገኖች የመጽሐፍ ቅዱስን እውነት ለመሞገት የሚያነሷቸው ጥያቄዎች በርካታ ቢሆኑም ከእነዚያ መካከል የሚከተሉትን አራቱን በዚህ በክፍል አንድ መጽሐፍ ምላሽ እንዲሰጥባቸው መርጫቸዋለሁ መጽሐፍ ቅዱስ የተበረዘ መሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ የሰው አእምሮ ሊቀበለው የማይችል አሳቦችን መያዙ መጽሐፍ ቅዱስና ቁርአን በአሳብም ሆነ በመልእክት ያላቸው አለመስማማት መጽሐፍ ቅዱስ በውስጡ ሥህተቶችን አቅፎ መያዙ ቀሪዎቹን ጌታ ቢፈቅድና ብንኖር በተከታታይ በሚወጡት የመጽሐፉ ክፍሎች ምላሽ ይሰጥባቸዋል መጽሐፍ ቅዱስ አምላካችን ለሰው ልጆች ያለውን ፍቅርና የደህንነት እቅዱን የገለጠበት እንከን የሌለው የራሱ ቃል መሆኑን የእስልምናን የእምነት መጽሐፍትንም ጭምር በማጣቀስ የሥራው ባለቤት ከሆነው ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በመሆን አሳያለሁ ላነሷቸውም የመሞገቻ ጥያቄዎቻቸው አጥጋቢ ምላሽ እሰጣለሁ ሙግት አንድ መጽሐፍ ቅዱስ የተበረዘ መሆኑ ከቀድመው የእስልምና ዘመን ጀምሮ እስካለንበት ቀን ድረስ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተበርዚል ውንጀላ የሚያሰሙ የእስልምና ዳኢዎች ቁጥር በርከት ያለ ነው ለቀደመውም ዘመን ይሁን የአሁኑን ዘመን ሊወክሉ የሚችሉት የዓለም የእስልምና ምሁራን ፕሬዘዳንት ኢማም ዩሱፍ አል ቃራዳዊ ኢስላምን መረዳት በተሰኘው መጽሐፋቸው እንዲህ ሲሉ ያሰፈሩትን እናገኛለን በኢስላምና በሌሎች መለኮታዊ እምነቶች መካከል ያለው ልዩነት ኢስላም ለሰው ልጅ የተላከ የመጨረሻው መልእክት ከመሆኑ አኳያ አላህ መሠረታዊ መርሆዎችን መጠበቁ ነው እናም መበረዝና መከለስ አላገኘውም በሌላ በኩል የሌሎች ሃይማኖቶች ምንጮች የተጠበቁ አይደሉም ተበርዘዋል ተከልሰዋል ወይም ጠፍተዋል ኡስታዝ ሳዲቅ ሙሐመድም እንዲህ ብሏል ኦሪትም ሆነ ኢንጅል እንዲሁም ሌሎቹ ጥንታዊ ቅዱሳንና መለኮታዊ መጽሐፍት ከቅዱስ ቁርአን መውረድ በፊት ተበርዘዋል ለእነዚህ መጽሐፍት መበረዝ ዋናውና ትልቁ ምክንያት የመጽሐፍቱ መጠበቅ ከአላህ ቃልኪዳን አለመገባቱ ነው አላህ መጽሐፍቱን ሲያወርድ ጠብቁ ያለው ለነቢያቶቹና ለተከታዮቹ ነበር ይህ የሁሉ ድምጽ ነው ማለት ይቻላል ቁርአን ግን አላህ ራሱ ሊጠብቀው በሱረቱል አልሒጅር ቃል ኪዳን ገብቷል ይላሉ ሱረቱል አልሒጅር የሒጅር ምዕራፍ እኛ ቁርኣንን እኛው አወረድነው እኛም ለእርሱ ጠባቂዎቹ ነን ስለዚህ በአጠቃላይ መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል አይደለም ወደሚል መደምደሚያ ደርሰዋል እነዚህ ወገኖች መጽሐፍ ቅዱስ ተበረዘ ሲሌ የአበራረዙን ሁኔታ የቁርአን አንቀጾችን አባሪ በማድረግ አምስት ነጥቦችን ያቀርባሉ ፈፅምጋ መረዮ ድያ ዌ ቀመመድ ሀሠመያነታ ሯይደረጋ ታመሮና ማመጎያሰረ ሸተ ያሃረ ዐዐ ድ ዕዐዐፀ እውነትን ከውሸት ጋር በመቀላቀል ሱረቱል አልበቀራ የላም ምዕራፍ ሱረቱል አሊኢምራን የዒምራን ቤተሰብ ምዕራፍ በዋቢነት ተጠቅሰዋል ለዚህም ምሳሌ የማሆነን በኦሪት ዘፀአት የወርቅ ጥጃውን አሮን ሠራው ተብሎ የተጠቀሰው ነው በቁርአን በሱረቱል ጣሃ የጣሃ ምዕራፍ እንደተጠቀሰው ጣኦቱን የሠራው ሳምራዊው ሆኖ ሳለ በአሮን ቀይረውት መገኘቱ ነው ይላሉ እውነቱን መደበቅ ዋቢ የቁርአን አያዎች ሱረቱል አሊኢምራን ሆኢምራን ቤተሰብ ምዕራፍ ሱረቱል አልበቀራ የላም ምዕራፍ » እውነቱን መሸሸግ ሱረቱል አልማኢዳ የማእድ ምዕራፍ ምላስን ማጣመም ሱረቱል አሊኢምራን የኢምራን ቤተሰብ ምዕራፍ ሱረቱል አልኒሳእ የሴቶች ምዕራፍ « ቃላትን ከስፍራው መቀየር ሱረቱል አልበቀራ የላም ምዕራፍ ሱረቱል አልኒሳእ የሴቶች ምዕራፍ ሱረቱል አልማኢዳ ሆማእድ ምዕራፍ በእውነቱ እነዚህን የቁርአን አንቀጾች መጽሐፍ ቅዱስ እንደተበረዘ ለማሳየት መጠቃቀስ ጽንፈኝነቴንና አላዋቂነቴን እዩልኝ በሎ ራስን አደባባይ ላይ እንደ ማስጣት ይቆጠራል እነዚህ አባሪ ተደርገው የተጠቃቀሱ የቁርአን አንቀጾች የኋላ ታሪክ በእውነት ያሉትን ያሳይላቸዋል። መጽሐፍ ቅዱስ ወይስ ቁርአን። ተሟጋቾቹ ለእነዚህ ጥያቄዎች የሚሰጡት መልስ አበው እንደሚሉት ሞኝ ያሸንፋል አይነት እንደሆነ አውቃለሁ በእስልምና ምሁራኑ ዘንድ ተቀባይነት ያላቸው የመረጃ ምንጮች በጉልህ ድምጻቸውን አውጥተው የሚናገሩት የመጽሐፉ ሰዎች የቀደሙት መጻሕፍት መጽሐፍ ቅዱስ ማለት ነው መጀመሪያ ላይ አላህ ባወረደበት ሁኔታ ያለምንም እንከን አሁን ድረስ ይገኛሉ የሜል ነው እዚህ ላይ የአይሁዳውያኑንና የክርስቲያኑን ማሕበረሰብ የመረጃ ምንጮች የሜሰጡትን ምላሽ ለጊዜው አቆይቸዋለሁ ሌላው ሱረቱል አልሒጅር የሒጅር ምዕራፍ ምንም ስለ ቁርአን በአላህ መጠበቅ ያወራል ቢባልለትም ቁርአን የአላህ ቃል እንዳልሆነና ነቢዩ ሙሐመድም የእርሱ መልእክተኛ እንዳልሆኑ ከሚያረጋግጡልን በርካታ የቁርአን አንቀጾች መካከል አንዱ መሆኑን ምን ያክል ያውቁ ይሆን። ኡስማን ካልሆነ እጠብቀዋለሁ የሚለውን ቃል አላህ አልተናገረም ማለት ነው ስለዚህ የተዘበራረቀ ታሪክ ያለው ቁርአን የአላህ ቃል አይደለም ማለት ነው ቢሆንማ ኖሮ ማንም እየተነሳ ሊያስተካክለው እጁን አያነሳበትም ነበር አላህ ቁርአንን ሊጠብቀው ቃል ከገባ ይጠብቀዋል በየትኛውም ዘመን ስህተት ሊገኝበት ከቶውን አይችልም እየታዬ ያለው ግን ከዚህ የተለየ ነገር ነው እንግዲህ ቁርአን የሱረቱል አልሒጂር ን አፈጻጸም የሚቃረኑ ነገሮች እየተፈጸሙበት የነበር ከሆነ ከአላህ ማንነት ጋር ግጭት ስለሚያሳይ ቃሉ የአላህ ቃል ነው ብሎ በድፍረት መናገር አይቻልም ሔ ቁርአን ከጅምሩ ጀምሮ ሰፊ ልዩነት ባላቸው አራትና ከዛ በላይ በሆኑ ቅጂዎች ዛሬ ላይ መገኘቱ ከሁሉም ሙስሊም አንደበት ቁርአን እስካሁን ድረስ አንድ ቅጂ ብቻ እንዳለውና በእርሱም ምንም የነጥብ ስህተት እንኳን እንደሌለበት ይነገራል ነገር ግን እንዲህ እንደሚወራለት አለመሆኑ የአደባባይ ሚስጢር ነው በነቢዩ ሙሐመድ ዘመን የራሳቸውን ቁርአን ያዘጋጁ ሰዎች ቁጥር በትንሹ ይደርሳል ይላሉ ጀፈሪም ልሸበከዘ ቨርስባ የጥንት ጽሑፋቱን ቁጥር ያደርሱታል በመካከላቸውም ስላለ ልዩነት ብዙ ብለዋል ከከሊፋ ኡስማን ሞት በኋላም ቁርአን ሃያ የሚደርሱ ቅጂዎች እንዳሉት የታሪክ መዛግብት ያስገነዝባሉ ከእነዚያ ሃያ ከሚደርሱት ቅጂዎች መካከል በበርካታ ልዩነቶች ተሞልተው እዚህ ዘመን ላይ ከሚገኙት አራቱን ልጥቀስላችሁ ከአራቱ ቅጅዎች ሦስቱ እጄ ላይ እንደሚገኙም ሳልጠቅስላችሁ አላልፍም የዋርሽ ቁርአን ቅጂ ክገዐሪ ህዐበ ሀፀበያፎይ ሀሀዘገ ዐ ሀሆዐቤ ዐሪ ዕዐዐና « ሲክሆፎደሄባሪ ለዐፎዐ ዖዐያ ፐስፀ ዘዘየዐባ ዐ አፀ ፎየ ዐ ስፀ በህዐቢ ስፀ ዐሀ ርዐሪርፀ ርዐሆሬጨ ይህ የቁርአን ቅጅ ከአላህ ፈቃድ ካገኙት ከሰባቱ የአረብኛ ዝዬዎች መካከል በአንዱ በመዲናዊ ዝዬ የተዘጋጀ የቁርአን ቅጅ ነው በዚህ ዝዬ በአስተማሪነት ኢማም ናፊ አልመደንይ ሂ ይታወቃሉ እኒህ ሰው ከሊፋ ኡስማን በመካ የአረብኛ ዝዬ ብቻ እንዲነበብ ያዘጋጀውን ቁርአን በዛው በመዲና ካስቀመጠና የራሱ ቁርአን እንዲኖረው የሚፈልግ ሰው ከዛ እንዲገለብጥ ትእዛዝ ካስተላለፈ ከአስራ አራት ዓመት በኋላ የተወለዱ ሰው ናቸው በዚህ ዘመን ላይ ተወልደው ለትምህርት ደርሰው ተምረው አስተማሪ ሆነው ያስተማሩት ከከሊፋው በተቃራኒ በመዲና ዝዬ ነው እንዴት ሊሆን ቻለ። አልኩት ከብዙ ውትወታ በኋላ በቀረበው አሳብ ስምምነት ላይ ደርሰዋል በስምምነቱ መሠረት ቁርአንን ከተበታተነበት የማሰባሰብ ሥራው ቢጀመርም አብዛኛው የቁርአን ክፍል ጠፍቶ ስለነበር በነቢዩ ዘመን የወረደውን ሁሉንም የቁርአኑን ክፍሎች ማግኘት ግን አልቻሉም የቁርአን በርካታ ክፍሎች ስለመጥፋታቸውና ማሰባሰብ የተቻለው በጣም ጥቂቱን ብቻ መሆኑን ታማኝ የሆኑት ሃዲሳትና የተለያዩ የቁርአን ሙፈሲሮች ሱሃባዎችንና ከሊፋዎችን ምንጭ አድርገው እማኝነታቸውን ሰጥተዋል የእማኝነታቸውን ቃል ከራሱ ከከሊፋ ኡመር ልጅ ከአብዱላህ ኢብን ኡመር ልጀምር ኪታብ ፋዛኢል አልቁርአን ቅጽ ገጽ አብዱላህ ኢብን ኡመር ሲናገር ከእናንተ መካከል ሙሉውን ቁርአን እንዳገኘ የሚናገር የቁርአኑ አጠቃላይ ይዘት ምን ያህል እንደነበር ፀሀጸገዐሲ ለሀክዐበገፀፀ በ ፀገዐፎዕ ዐክክ ፀሀጸደክዐ ዐዘዐሮዐ ይሃ ለሸክዐበዝብዐሪ ለያክ ክዐቢ ዐዐብሪዐፀዘገ ዖሀዕክፀያ ዐበፀ ሀሀየዕ ጽስዐወስ ዐሀዐ ያሀዐሪኪ ሃዐ ዕዐዐፀ እውቀት የሌለው ነው ምክንያቱም አብዛኛው ቁርአን ጠፍቷል ይልቁን የቀረውን ወይንም ያለውን አግኝቸዋለሁ ቢል ይሻላልማ አቡ ጃፍር እንዲህ ሲናገር ሰምቻልሁ ከአሊ ኢብን አቢ ታሊብና በኋላም ከኢማሞቹ በስተቀር ውሸታም ካልሆነ በስተቀር ከአላህ ዘንድ እንደ ወረደ ሙሉውን ቁርአን እንዳሰባሰበ ሊናገር የሚችል አንድም ሰው የለም እንደ ኢብን ነዲም ዘገባ የአሊ ኢብን አቢ ታሊብ ቁርአን በከሊፋ ኡስማን ተቃጥሏል በአሁኑ ቁርአን ውስጥ ያሉ አምስት ሱራዎች አልነበሩትም ሌላም ሌላም በሌላ ተያያዥ ሐዲስ ከሊፋ ኡመርም እንዲህ ተናግሯል አልኢትቃን ፊ ኡሉም አልቁርአን ቅጽ ገጽ ኡመር ሲናግር ነቢዩ እንዲህ አሉ ቁርአን ፊደላትን የያዘ ነው ማንም ብድራትን አስቦ የሜያነባቸው ሰው በገነት በእያንዳንዱ ፊደሎቹ ልክ የገነት ሴቶችን ያገኛል አልኩላይኒ አልካፊ ቅጽ አቡ አብደላ አልሳዲቅ ሲናገር ገብርኤል ወደ ነቢዩ ሙሐመድ ያመጣው ቁርአን አንቀጸች ነበሩትማ እነዚህ ሐዲሳት በሁለቱ ታላላቅ የእስልምና ክፍሎች ማለትም በሱኒ እና በሽአ ኢማሞች ዘንድ ተቀባይነት ያላቸው ናቸው የሽአ ኢማሞች ነቢዩ ሙሐመድ ከሞቱ ከስድስት ወራት በኋላ በከሊፋ አሊ የተጻፈው የቁርአን ቅጅ ይህንን ያክል ፊደላት ይዞ እንደ ነበር ይናገራሉ ከሊፋ ኡመር እንደተናገረው በመጀመሪያ ነቢዩ ሙሐመድ ከገብርኤል ተምረው ያስተላለፉትና ተበታትኖ ተቀምጦ የነበረው ቁርአን ፊደላት ይዚል ይህም በ አንቀጾች የታቀፈ ነበር አሁን በዚህ ጊዜ የሚገኘው ቁርአን ደግሞ ከ ፊደላት ያልበለጠ እንደሆነ ይህም በ አንቀጾች እንደ ታቀፈ የመስኩ ምሁራን ይናገራሉ አንዳንዶች ይህንን የሚለውን አሃዝና የፊደላቱን ቁጥር ጭምር አይቀበሉም የማይቀበሉት ወገኖች የአንቀጸቹን ቁጥር በ እና በ አክዘቨዕስዐዐሮዘርዐበጊርዐበገህያሮስፀዘህዐክሮፎሂሀበበፎዐዐፔሀፎፎዐዘሀያዐበ ክከቭ ፖ ጽፀ ደበርሃርዐዐፀዐሆሃፀ ዐርየዐዕፀ ጽፀህዐ ዐበሀዐገ ዐዐ አክዘቨዕስዐዐሮዘርዐበጊርዐበገህያሮስፀዘህዐክሮፎሂሀበበፎዐዐፔሀፎፎዐዘሀያዐበ ክከቭ ክፀሃስ ለያስዐስገዘገዐሪ ሃዐሀ ጸህዐብ ቫዐዕሮ ዳ ጸዐ ሃ ርዛ « ሀ ዐፀፀፀ ዳደአየር ጸህፊ ሃሳዛቫዛሳ ያፐሊዘ ደ ዖዐደዕ ፀሀዐ ለዘሃገ ለ ዐ ዐዐዐ ዐበዐዐ ፀዐዐሮፀ ሪ መካከል እንደሆነ ይናገራሉ ልዩነቱ በመቶኛ ሲገለጽ በፊደል ማለትም የቁርአኑ ኛ በአንቀጽ ደግሞ ከ እስከ ማለትም ኛ ያህሉ የቁርአን ክፍል ጠፍቷል በቁርአን ቃላትና ፊደላት ብዛት ዙሪያ ያለውን የተመሰቃቀለና የተዘበራረቀ የኡለማዎች አመለካከት ሙፈሲር ኢማም ኢብን ካሲር በተፍሲር መጽሐፋቸው አስፍረውልን ይገኛል ተፍሲር ፍሲር ኢብን ካሲር ቅጽ ገጽ ቅዱስ ቁርአን ያቀፋቸው አያቶች ቁጥር ያህል ነው ሆኖም በቁጥሮቹ ዙሪያ የተለያዩ አመለካከቶች አሉ አንዳንዶቹ ቁጥሩ ነው ሲሉ ሌሎች አያት ይጨምራሉ ከነዚያ ሌላ ያሉ አያት ይጨምሩበታል በተጨማሪ ሌሎች አያት ይጨምራሉሌ አንዳንዶች ደግሞ አያት ወይም አያት ይጨምራሉሌ ከነዚህ በተጨማሪ ያሉት ደግሞ አያት ይጨምራሉ አልበያን በሜል ርእስ አቡ አምር አድዳኒ ከጻፉት መጽሐፍ የወሰዱት እንደ ሙፈሲር ኢማም ኢብን ካሲር ዘገባ በቁርአን ፊደላት ቁጥር ብዛት ያለው የአመለካከት ልዩነት ከዚህ የተለየ አይደለም ተፍሲር ኢብን ካሲር ቅጽ ገጽ ስለ ቅዱስ ቁርአን ቃላትና ፊደላት ብዛት አልፋድል ቢን ቫሻዛን ሲናገር አታ ቢን ያሳር እንዳለው ቁርአን ቃላትን ይዚል አለ አብደላህ ቢን ካቲር ሲናገር ሙጃህዲን እንዳለ በእኛ አቆጣጠር የቁርአኑ ፊደላት ቁጥር ብዛት ያህል ነው ብሏል በተጨማሪ አልፋድል ሲናገር አላ ቢን ያሳር እንዳለው ቁርአን ፊደላትን የያዘ ነው ብሏል ሳልም አቡ ሙሐመድ አልሃማኒ ጨምሮ አልሃጃጅ የቁርአኑን ሀፊዘሎች ሰብስቦ ቁርአን ስንት ፊደሎችን በውስጡ እንዳቀፈ ንገሩኝ አላቸው እነርሱም እኛ የቆጠርነው ፊደሎችን ነው አሉት አሁን ላይ ፊደላት ካለው ቁርአን ጋር በንጽጽር ሲታይ ከእነዚህ ሰዎች አቆጣጠር ጋር ከፍተኛ ልዩነትና የቁርአን ቃላት መጥፋት ይታይበታል ሩ በሙጃህዲንና ከእርሱ ጋር ባሉት ሰዎች አቆጣጠር ከቁርአኑ ላይ እስከ የሚያክል ፊደላት ጠፍተዋል ። አል በቀራህ ኡቤይ ቢን ካብ በቁርአን እውቀቱ ከሌሎች ሦስት ሰዎች ጋር በነቢዩ ሙሐመድ ለአስተማሪነት የተመረጠና ከዛይድ ቢን ሳቢት ጋር ለነቢዩ ይወርድ የነበረውን ወህይራዕይ ጸሐፊ የነበረ ሰው ነው ታዲያ ከሊፋ ኡመር ሌሌች ሰዎች ስለ ቁርአን ሚሰጡትን ምስክርነት ተቀብሎ የዚህን ሰው ቁርአናዊ መረጃዎች አለመቀበሉ ምን ማለት ሊሆን እንደሚችል አስቡት በዚህ ወቅት ከዛይድ ጋር በመሆን መስጊድ በር ላይ ቁርአኑን ሲያሰባስቡ ሱረቱል አልበቀራ ን ምክንያት በማድረግ ቁጥራቸው በውል ማይታወቅ ብዛት ያላቸው የቁርአን አንቀደጾች ከቁርአን አካልነታቸው ተወግደዋል ለዚህ እራሱ ከሊፋ ኡመር በአንደበቱ ቁርአን አንቀጾች አሉት በማለት ያስተላለፈው ሐዲስ ማስረጃ ሊሆን ይችላል አሁን በዚህ ዘመን ባለው ቁርአን ያሉት የቁርአን አንቀጸች ወይም ከዚህ በታች ናቸው ኢብን ካቲር የዘገቡት የተዘበራረቀው የቁርአን ፊደላትና ቃላት ቁጥር ሳይረሳ ማለት ነው ከሊፋ ኡመር ሱረቱል አልበቀራ ን በመጥቀስ የሰጠው ምክንያት ከኡቤይ ጋር ብቻ ሳይሆን ከሁለተኛው የቁርአን አሰባሳቢ ከከሊፋ ኡስማን ጭምር ይጋጫል ከሊፋ ኡስማን በሻሪና ተሻሪ አንቀጾች ላይ የነበረው አመለካከት እንደ ከሊፋ ኡመር አልነበረም ያንንም በአልቡኻሪ እንዲህ ሰፍሮ ይገኛል ሳሂህ አልቡኻሪ ቅጽ ቁጥር አልበቀራ ን በተመለከተ ኡስማን ቁርአኑን በሚያሰባስብበት ወቅት እንዲህ አልኩት ይህ አንቀጽ በሌላ አንቀጽ ተሽሯል ታዲያ የቁርአኑ አካል አድርገህ ለምን ትጽፈዋለህ። ኡስማንም የወንድሜ ልጅ ሆይ እኔ አንድንም ነገር ከቀድሞ ቦታው አልቀያይርም አለኝ ኢብን አዝዙቤይር እንደተናገረው ተመልከቱ ሱረቱል አልበቀራ የተሻረው በአንቀጽ ሱረቱል አልበቀራ ሲሆን አንዱ ሻሪ ሌላው ተሸሪ ሁሉም በቁርአኑ ውስጥ አሉ በሁሉም የቁርአን ሱራዎች ውስጥ ማለት ይቻላል ሻሪና ተሸሪ አንቀጾች በአንድነት ሰፍረው ይገኛሌ ሆኖም በሻሪና ተሸሪነት ምክንያት አንቀጾች ወጥተው ተጥለዋል የአመለካከት ልዩነትንም ፈጥሯል ታዲያ ይህ በከሊፋ ኡመር በኡቤይ ቢን ካብና በከሊፋ ኡስማን መካከል የሚታየው የአመለካከት ልዩነት በቁርአን ንጽህና ላይ ሌላ ጥያቄ በውስጣችን ይፈጥራል እንደ አል « ዐክ ፀሀጸክዐኋ ህዐ ዕዐዐፀ ዐክክ ፀሀደክዐ ህዐ ዕዐዐፀ ቡኻሪ ቅጽ ቁጥር ከሊፋ ኡስማን ቁርአኑን ያዘጋጀው በከሊፋ አቡበከር ዘመን ከሊፋ ኡመርና ዛይድ ቢን ሳቢት ካሰባሰቡት የቁርአን ቅጅ ነው እነዚህ ሃይማኖቱን የመሩና ያስተማሩ የነቢዩ የቅርብ ሰዎች እንዲህ ባለ ልዩነት የነበሩ ከሆነ ከላይ በተጠቀሰው ሐዲስ የተላለፈው የቁርአን አሰባሰብ ዜና ውድቅ ይሆናል ምክንያቱም በከሊፋ ኡመርና በዛይድ የመጀመሪያው የማሰባሰብ ሥራ ወቅት ተሻሪ የሆኑት አንቀጾች እየተለዩ ከቁርአኑ ጥራዝ ውስጥ ተወግደዋል ስለዚህ ሁለተኛው ላይ በምንም አይነት ሁኔታ ሻሪና ተሻሪ አንቀጾች በአንድነት መገኘት አይኖርበትም ሻሪውና ተሻሪው አንቀጾች መገኘት ካለባቸው ደግሞ ኡቤይ ቢን ካብ ያመጣቸው የቁርአን አንቀጾች ጥቅስ ተጠቅሶ ውድቅ መደረግ አልነበረባቸውም ነገር ግን የሆነው ከሊፋ ኡመር አል በቀራን ጠቅሶ ይጥላል ከሊፋ ኡስማን ደግሞ የተጣለውን አንስቶ የቁርአኑ አካል በማድረግ አካቶት ይገኛል ስለዚህ የቁርአን አሰባሰብ የአላህ ፈቃድና የነቢዩ አስተምህሮ ዋጋ ያጡበት የሰዎች አሳብና ፈቃድ የነገሰበት አንዱ ሲሄድ የሚመጣው የራሱን አመለካከት እያስፈጸመበት የኖረ መጽሐፍ ነበር ይህም በቁርአን ተአማኒነት ላይ የወደቀ ጥቁር ነጥብ ነው በሱሃባዎቹ መካከል በአሳብ መለያየቱ በእነዚህ ሰዎች ብቻ የሚያበቃ አልነበረም የሚለያዩበት አሳብም ቁጥሩ እጅግ በርካታ ነው በዚህ ላይ ግንዛቤያችሁን ያሰፋ ዘንድ በሁለቱም ቁርአንን የማሰባሰብ ሥራ ወቅት ዋና ሰራተኛ ስለነበረው ዛይድ ቢን ሳቢት አንዳንድ ጥያቄዎችን ላንሳ በሱረቱል አልበቀራ መሰረት ኡቤይ ያመጣቸው የቁርአን አንቀጾች ውድቅ ከተደረጉ ሌሎቹ ሱሃባዎች ያመጧቸውም ይህ እጣ እንደሚገጥማቸው ምንም ጥርጥር የለውም በእነርሱም ላይ ተግባራዊ መሆኑ የማይቀር ነው ታዲያ አሁን ባለው ቁርአን ውስጥ ያሉት ሻሪና ተሸሪ የሆኑ አንቀጾች የቁርአኑ አካል ተደርገው መካተታቸው የሱሃባዎቹን አንድ ልብ ለአንድ መለኮታዊ አላማ ይሠሩ የነበሩ መሆናቸውን ያሳያል። በዚህ ላይ ሌላው ተጨማሪ ሐዲስ የቁርአን አካል የነበሩ ሌሎች ሁለት ሱራዎች ከቁርአኑ ሳይካተቱ ቀርተው የመጥፋታቸው ጉዳይ ነው ይህንን የተመለከተው ሐዲስ እንዲህ የሚል ነው ኡቤይ ኢብን ካብ በነበረው የእራሱ የቁርአን ቅጅ ሁለት ሱራዎች ሱራ አልሁላ እና ሱራ አልሂፍድ የተባሉትን ጨምሮ ይዞ ነበር አል ኢትቃን ገጽ እነዚህ ሁለት ሱራዎች በሱራነታቸው የቁርአኑ አካል እንደሆኑ የታመ ነው በአንዱ በኡቤይ ቢን ካብ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ሦስት የነቢዩ ሙሐመድ ሱሃባዎችና የራሳቸውን ቁርአን ባሰባሰቡ በአቡ ሙሳ በኢብን አባስና በከሊፋ አሊም ጭምር ይታወቃሉ አራቱ ሱሃባዎች ሁሉም ለራሳቸው ባሰባሰቡት የቁርአን ቅጅ ውስጥ እነዚህን ሁለት ሱራዎች የቁርአኑ አካል እድርገው አካተዋቸው እንደነበር የታሪክ መዛግብቱ ያሳያሉ የሱራዎቹ ይዘት አንዱ ሀቨዛ ሃሊለዘ ደና ዖፖዐደ ዕዐፀፀ ክዘገፀሪ ሃዐ ዐፀበፎይ ሀህያገ ዐ ህዐ ስፀ ለያክሪ ዐ ሀዕሪ ይገ ጽ ሦስት አንቀጸች ሌላው ደግሞ ስድስት አንቀጸችን የያዙ ነበሩ እንግዲህ አራቱ ሰዎች በአንድነት ሊሳሳቱ አይችሉም ከዛይድም ይልቅ ለነቢዩ በጣም ቅርበት ያላቸው እስልምናንም በመቀበል ቀደምት ናቸው አንድ የቁርአን አንቀጽ የቁርአኑ አካል ሆኖ እንዲካተት የሁለት ሰዎች ምስክርነት እንዲያገኝ የሚጠይቀውን መስፈርትም አሟልተዋል ግን ደግሞ ከቁርአን አካልነታቸው ወጥተው ተጥለዋል ቁርአን የሱ አካል ያልሆኑ ሱራዎችንና አንቀጾችን አቅፎ መያዙ ቁርአንን ለህዝቡ ለማስተማር ስለተመረጡት ሰዎች ኢማም አልቡኻሪ የሚከተለውን አስፍረዋል ሳሂህ አልቡኻሪ ቅጽ ቁጥር አብደላ ቢን ኡመር አብደላ ቢን መስኡድን ጠቀሰና እንዲህ አለ የአላህ መልእክተኛ ሲናገሩ የሰማሁለትን ያን ሰው ምን ጊዜም እወደዋለሁ ከእነዚህ አራት ሰዎች ቁርአንን ተማሩ አብደላ ቢን መስኡድ ሳሊም ሙአዝና ከኡቤይ ቢን ካብ አሉ ማስሪቅ የተናገረው ሐዲስ ነው ቁርአን የተበረዘና ንጹህ ያልሆነ ስለመሆኑ የእስልምና የመረጃ ምንጮች የሚያቀርቡት ሌላው መረጃ የራሱ አካል ያልሆኑ ሱራዎችንና አንቀጾችን በውስጡ አካቷል የሜል ነው እነዚህ ለቁርአን አስተማሪነት ከተመረጡት መካከል የሆኑት ቁርአን የራሱ አካላል ያልሆኑ ሱራዎችንና አንቀጸችን በውስጡ አቅፎ ስለመያዙ የታመነ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል አብደላ ኢብን መስኡድና ከሊፋ አሊ እራሳቸው ባዘጋጁት ቁርአን አሁን ካሉት የቁርአን ሱራዎች የተወሰኑትን ባለማካተት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል ኢብን መስኡድ ሱረቱል አልፋቲሃን የመክፈቻይቱ ምዕራፍ ሱረተል አል ፈለቅን የተፈልቃቂው ምዕራፍ ኛ እና ሱረቱል አልናስን የሰዎች ምዕራፍኛ እነዚህ ዱአዎች እንጂ የቁርአኑ አካል አይደሉም ብሏል ከሊፋ አሊ ደግሞ ሱረቱል አልፋቲሃ የመክፈቻይቱ ምዕራፍ ሱረቱል ረድእ የነነድጓድ ምዕራፍ ኛ ሱረቱል አልኑር የብርሃን ምዕራፍ ኛ ሱረቱል አልተህሪም የማውገዝ ምዕራፍ ኛ እና ሱረቱል አልአለቅ የረጋ ደም ምዕራፍ ኛ የቁርአኑ አካል አይደሉም በማለት እራሱ ባዘጋጀው ቁርአን ሀ ፀሀዐ ህ ዐዐዐፀ ስዘገፀፀ ሃዐፀ ዐፀዘበያሮሩ ሀህስ ዐ ርፃሆሀቤ ክፀ ለክስሪ ዕ እበ ለሀ ውስጥ አላካተታቸውም በተለይ አብዱላህ ኢብን መስኡድ የሰጠው ምስክርነት እውነት መሆኑን በአጽንኦት የገለጸው እንዲህ በማለት ነበር ሳሂህ አልቡኻሪ ቅጽ ቁጥር በአላህ። ሌላው የቁርአን አካል ያልሆኑት በእስልምና ምሁራን ዘንድ ለአሥራ አራት ክፍለ ዘመናት ግራ አጋቢ ሆነው የቆዩና እስካሁን ድረስ አነጋጋሪ ሆነው ያሉት ሱረቱል አልተውባህ የንስሓ ምዕራፍ ናቸው እነዚህ አንቀጾች በምሁራኑ ዘንድ በልዩ መጠሪያቸው የሐሰት አንቀጸች ህ አንዳንዴም የሰይጣን አንቀጾች በመባልም ይጠራሉ ሱረቱል አልተውባህ ከጎሳችሁ የሆነ ችግራችሁ በርሱ ላይ ጥኑ የሆነ በናንተ እምነት ላይ የሚጓጓ በምእመናን ርህሩህ አዛኝ የሆነ መልእክተኛ በእርግጥ መጣላችሁ ቢያፈገፍጉም አላህ በቂዬ ነው ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም በእርሱ ላይ ተጠጋሁ እርሱም የታላቁ አርሽ ጌታ ነው በላቸው እነዚህ ሁለቱ አንቀጸች የቁርአኑ አካል እንዳልሆኑ በእስልምናው ምሁራን ዘንድ ለምን እንደሚታመን ምክንያቶችን ያስቀምጣሉ ን ውድ ን ን ውድ ን ውድ ን ውድ አንድ አንቀጽ የቁርአን አካል ነው ተብሎ ተቀባይነት የሚያገኘው የሁለት ሰዎችን ምስክርነት ማግኘት ከቻለ ብቻ ነው ይህንን በተመለከተ ሐዲሳቱ የሚከተለውን ብለዋል ሂሻም ቢን አርዋን ከአባቱ ሰምቶ የተናገረው ሙስሊሞች በያማማ በተሰው ጊዜ አቡበከር በመስጊድ መግቢያ ኡመር ቢን ኸታብንና ዛይድ ቢን ሳቢትን እንዲህ ሲል አዘዛቸው ማንም እናንተ ማስታዎስ ያልቻላችሁትን የቁርአን አንቀጽ ይዞ ከመጣ ሁለት ሰዎችንም ካስመሰከረ ተቀበሉት ይህ የሆነው በርካታ ቁጥር ያላቸው ቁርአኑን በልባቸው የሚያውቁ የነቢዩ ተከታዮች በያማማ ላይ በመገደላቸው ነበር በዚህ መስፈርት መሰረት ለአልተውባህ የንስሓ ምዕራፍ የቀረበው ምስክር አንድ ብቻ ስለነበር የመስፈርት አለመሟላት ስለታየበት ነው የቁርአን አንቀጾች ቦታ የሚወሰነው በአላህ ሆኖ ሳለ ለእነዚህ አንቀጾች ቦታ የወሰነላቸው ሰው መሆኑነ አንቀጾቹ በመካ የወረዱ ሆነው ሳለ ተመድበው የተገኙት ግን በመዲና ሱራ ውስጥ ነው ለዚህም አዲስ አንሳራዊ ሙስሊም የሆነው ሁዘኢማንን ከሊፋ ኡስማን ጠይቆት ቦታውን እንደወሰነው ይታወቃል አንቀጾቹም የተገኙት ከዚህ ሰው ብቻ መሆኑ ይታወቃል ስለ አንቀጾቹ የተሳከረ ሐዲሳዊ ዘገባዎች መሰጠቱ ሌላው ምክንያት ነው ሱና አቡ ዳውድ ኡቤይ ቢን አልተውባህ በማጻፍ ላይ ሳለ አንቀጽ ላይ ደርሶ ን ሲቀጥል ይጽፉለት የነበሩት ሰዎች ሱራው እንዳበቃ ሲነግሩት እነርሱ እንደተሳሳቱ ነግሯቸው አንቀጽ እና ሲጨምር ሲያሳይ ሳሂህ አልቢኻሪ ዛይድን በመጥቀስ ሁዘኢማ ከተባለ ሰው ላይ ብቻ ያገኘው መሆኑን ይናገራል ኡቤይና ዛይድ ለነቢዩ ሙሐመድ ይወርድ ለነበረው ወህይ ጸሐፊዎች ስለሆኑ ቁርአን በወረደ ጊዜ ይመዘግቡ ነበር ሆኖም በዚህ ሐላፊነት ላይ ኖረው ሁለቱ ጸሐፊዎች የሚሰጡት አሳብ የተሳከረ መሆኑ አንቀጾቹን ተአማኒነት አሳጥቷቸዋል በአስልምና ምሁራን ዘንድ የቁርአን ተአምራዊ ቁጥር በሚባለው በቁጥር ብዜት ስሌት ሲሰላ እነዚህ ሁለት አንቀጾች የዚህን የስሌት ስርአት ለተሰዐጠዘገዐሪ ለሀፀዐ ዳዐ በ ስፀ ስባ ዐ ሀያዐበር የፎየ ያያዐበገ ጽፀህፀዐዐዘ ያዕ ርዐፀገዐዐክዐጸለ ሀ በገር ዐርዐፀፀክገሄ ደለዕፈሳለ ዐዐ ዕዐዐፀ ዐ ዐ ፀሀዐ ህዐ ዐዐዐ በ ይሀ ዐዐሣሀፀ ህዐ ዐክ ዐ ፀሀደክዐ ህዐ ዩ ዐዐፀፀ የሚያዛቡ ሆነው ተገኝተዋልኞ ስለዚህ የተደረሰበት መደምደሚያ ቁርአን ከእነዚህ ሁለት አንቀጾች ውጭ ነው የሜል ሆኗል ታዲያ ቁርአን አልተበረዘም ብሎ ለመናገር እንዴት ያስደፍራል። በሱረቱል አልለይል የተጠቀሱ አንቀጾች ውስጥ ሰፍረው የሚገኙት በፈጠረው አምላክ የሚሉትን ቃላት የአሁኑ ቁርአን በመጨመር ይዞ ይገኛል ዐስ ፀሀደክዐ ህዐ ፀዐዐዐፀ « ህዐ ዕዐዐፀፀፖ ከከሊፋ ኡስማን ሞት በኋላ በቁርአን ላይ የደረሱ ሁለት አደጋዎች ሀ ቁርአን ለሁለተኛ ጊዜ በእሳት ቃጠሎ መውደሙ ቁርአን ከአላህ እንደ ወረደና ጠባቂው አላህ እንደሆነ ቢነገርለትም እንደ ነቢዩ ሙሐመድ ሐዲሳት ዘገባ የደረሰበት ችግር ከዚህ በፊት በተገለጹት የሚያበቃ አልሆነም ቀድሞ በከሊፋ ኡስማን የተፈጸመው ቁርአኑን የማቃጠል ተግባር ሳይበቃ ከከሊፋዎች ሞት በኋላ ሌላ አንድ ማን አለብኝ ባይና ስሙን ከቁርአን ጋር በተያያዘ በታሪክ መዝገብ ላይ ማስፈር በፈለገ ሰው እንደገና በእሳት የመቃጠል እጣ ወድቆበታል በሱረቱል አልሒጅር የተገለጸው የአላህ ጥበቃ የት እንደ ደረሰ ባይታወቅም እንደገና ለእሳት የመዳረግ እጣ የወደቀበት እንደ ቀድሞው ሁሉሌ ወደፊትን በመስጋት ነው ሲጀመር ሊያተርፈው ባይቻለውም ከሊፋ ኡመር መጥፋቱን ሰጋ ሁዛይፋ ኢብን አልየመኒ ሰጋ ከሊፋ ኡስማን አሁንም ስጋት በስጋት ሆነ ከዚህም በኋላ ሌላ የስጋት ሰው መርዋን ኢብን አልሃካም የሚባል በውክልና መዲናን ያስተዳድር የነበር ሰው የድርሻውን ሊወጣበት ተነሳ ይህ ሰው በእሳት ያቃጠለው በከሊፋ አቡበከር ትዕዛዝ ከሊፋ ኡመርና ዛይድ ቢን ሳቢት ያዘጋጁትን የመጀመሪያውን ቁርአን ነው ይህንን ለማድረግ ያነሳሳው ሃፍሳ ዘንድ የተቀመጠው የቁርአን ቅጅ በሕይወት ከኖረ በኋለኛው ዘመን የሚመጣው ትውልድ በከሊፋ ኡስማን ከተዘጋጀው ቁርአን ጋር በማነጻጸር ሌላ ችግር ሊያስነሳ ይችላል ብሎ ስለሰጋ ነበር ይህንን በሃፍሳ ዘመን ማድረግ ሞክሮ ሳይችል ቀርቷል ከእርሷ ሞት በኋላ ወንድሟን በማስገደድ ከተቀመጠበት ወስዶ በመቀዳደድ በእሳት አቃጥሎታል የዚህን ሰው አድራጎት ኢማም ኢብን አቢ ዳውድ ኪታብ አልመጻሒፍ በተባለው መጽሐፋቸው ታሪኩን አስቀምጠውታል እኒህ ሰው ሱና አቡ ዳውድ የተባለውን እውቅ የሱኒዎች የሐዲስ መጽሐፍን የጻፉ ሰው ልጅ ናቸው እንዲህ አሉ ሳሊም ኢብን አብዱላህ ኢብን ኡመር ሲነግረኝ መርዋን ወደ ሃፍሳ መልእክተኞችን ላከ ማለትም እርሱ በጊዜው ሙአውያን ወክሎ የመዲና አስተዳዳሪ ነበር ነገር ግን እርሷ ለእርሱ ለመስጠት አልፈለገችምና ከለከለችው ሳሊም ቀጠለና ሃፍሳ ሞተች እኛም ከቀብር ከተመለስን በኋላ መርዋን ለአብዱላ ኢብን ኡመር የቁርአኑን መጽሐፍ እንዲልክለት ማስገደጃ ላከለት ወዲያውም አብዱላህ ኢብን ኡመር ላከለት ከዛም መርዋን መልእክተኞቹን አዘዛቸው እነርሱም ቀዳደዱት እንዲህም አለ ይህንን ያደረግኩበት ምክንያት ወደፊት ከጊዜ በኋላ የማያምኑ ሰዎች መጽሐፍቱን በተመለከተ ክህደትን ሪ እንዳይፈጽሙ በማለት ብቻ ነው ከዛም እነርሱ ቀዳደዱትና አቃጠሉሌት አቡ ኡቤይድ የተናገረው ሱና ኢብን አቢ ዳውድ ኪታብ አልመጽሐፍ ቁርአን ለሰው ልጆች ደህንነት ከዘለአለሙ አምላክ የተላከ መገለጥ እንዳልሆነ በጉልህ የሚያሳዩ መረጃዎችን እስካሁን ሐዲሳቱ ሲያስነብቡን ቢቆዩም አሁንም አንድ ጨምረውልናል እነርሱን መሠረት በማድረግም ይህንን ሰው ድርጊቱን እንዲፈጽም በአነሳሳው ምክንያትና አጠቃላይ ሁኔታዎች ላይ አንዳንድ ጥያቄዎችን እስኪ ልጠይቅ ን ውድ ን ውድ ን ውድ ን ውድ የከሊፋ ኡስማን የቁርአን ቅጅ የተዘጋጀው ከሊፋ አቡበከር ካዘጋጀው ቁርአን እንደነበር የአልቡኻሪ ዘገባ ያስረዳል ሐዲሱ እውነት ከሆነ በከሊፋ ኡስማን በተዘጋጀውና በመጀመሪያው በከሊፋ አቡበከር በተዘጋጀው የቁርአን ቅጅ መካከል ልዩነት ሊኖር አይችልም ማርዋን ሁለቱም የቁርአን ቅጅዎች የተዘጋጁት በአንድ ሰው ዋና አዘጋጅነት መሆኑን እያወቀ በመካከላቸው ልዩነት ይፈጠራል ብሎ እንዴት ሰጋ። ቀ እንግዲህ መጽሐፍ ቅዱስ የተበረዘ ከሆነ አላህ ስለ ቁርአንና ስለ ነቢዩ ሙሐመድ ተልእኮ ይህንን ሁሉ ማለት ነበረበትን። ለመጽሐፍ ቅዱስ አለመበረዝ በአላህ በነቢዩ ሙሐመድ ሐዲሳትና በሙፈሲሮች የተሰጠ ምስክርነት ነገሩ አበው በአንድ እራስ ሁለት ምላስ እንደሚሉት እንደሚሆንባችሁ አምናለሁ ቁርአን የአላህ ቃል ከሆነ ነቢዩ ሙሐመድ ሱሃባዎቹና አላህ ምን ያህል ራሳቸውን በመቃረን የሚናገሩ እንደሆኑ ታስተውሉ ዘንድ ስለቀደሙት መጽሐፍት አለመበረዝ አለመሰረዝና አለመደለዝ ብሎም አለመጥፋት ከተናገሩት ሁለቱን ላስነብባችሁ በመጀመሪያ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ አለመበረዝ የምስክርነት ቃል የሰጠው በሱረቱል አልማኢዳህ አላህ ነበር ያንንም ነቢዩ ሙሐመድ ተቀብለወ አስተላልፈውት አሁን ባለው ቁርአን ውስጥ ቃሉ ይገኛል በቅድሜያ ይህ የቁርአን ክፍል ሊወርድ የቻለበትን ምክንያት በሚያትተው የነቢዩ ሐዲስ ልጀምር ሱና ማሊክ ሙዋታ ሳሂህ ሙስሊም ቅጽ ገጽ ሳሂህ አልቡኻሪ ቅጽ በዝሙት ኀጢአት የተከሰሱ አይሁድና አይሁዳዊት ወደ አላህ መልእክተኛ አቀረቡ ነቢዩም እንዲህ ሲሉ ጠየቋቸው በእናንተ በተወረደው በተውራቱ ለእንዲህ አይነት ኀጢአት የተወሰነው ቅጣት ምንድን ነው። « ፐሆ ሃበ ደዐክ ሀያዐ ዐበዜሆ ዐለብሀ በገበ ሆ ሀበ ሳጳይ ዐዐዐፀ ታማኞች እንዲሆኑ ያሳስባቸዋል በዘዳ በዘዳ በዘዳ ነቢይ እንደሚያስነሳላቸው ቃል ገብቶላቸው ነበር ይህም የተገባላቸው ቃል ነቢዩ ሙሐመድን ነበር ክርስቲያኖች ይህ የኪዳን ቃል ኢሳ ነው ይላሉ ሆኖም ኢሳ ራሱ በዮሐ እና በዮሐ ባለው ላይ ስለእርሱ እንዳልሆነ ተናግሯል ከቁርአን ቀድሞ በወረደው መጽሐፍ ተገልጸ እያለ ክርስቲያኖች ሌላ ቅርጽ ይሰጡና ይደብቁት ነበር በነቢዩ ሙሐመድ ዘመን የነበሩ ብዙ የአይሁድ መምህራንም በመጽሐፉ የሰፈረውን እውነተኛውን ቃል ያውቁ ነበር በማለት አብራርተዋል ሌላው አንቀጽ ሱራ ነው ስለዚህ አንቀጽም የተሰጡ ማብራሪያዎች አሌሉ ማብራሪያው ከአንቀጽ ጀምሮ እስከ አንቀጽ ባለው ይጠቃለላል ኢብን አባስ ለዚህ አንቀጽ ለሱራ የሰጠውን ማብራሪያ በቀጥታ ተጠቅሞበታል የሐሰተኛው ክርስቶስን ባህሪ ከነቢዩ ሙሐመድ ባሕሪ ጋር ለምን ትቀላቅላላችሁ በማለት አንቆቹ የወረዱበትን ምክንያት የዘገቡ አካላትም እንደገለጹት አንቀጾቹ የወረዱት ሙስሊሞችን ከእስልምና ለመመለስ የተደረጉ ጥረቶችን ለመመከት እንደሆነ ይገራሉ ውድ አንባቢ በዚህ ሁሉ ማብራሪያ ውስጥ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ መበረዝ የሚያሳይ ፍንጭ አንድም የለም አያቱላዎቹ የጠቀሷቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ስለ ነቢዩ ሙሐመድ የተነገሩ አይደሉም ስለ ነቢዩ ሙሐመድ የሚናገር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅስ አንድም የለም ነገር ግን አሉ ብለው ጠቃቅሰዋል የጠቀሷቸው ደግሞ አብዛኛው ሙስሊም ዳኢዎች የሚጠቃቅሷቸውን ጥቅሶችን ነው እንዳሉት መጽሐፍ ቅዱስ የተበረዘና ስለ ነቢዩ ሙሐመድ የሚናገሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች የተደበቁ ከነበር ይናገራሉ ብለው የጠቀሷቸውን ጥቅሶች ማግኘት ባልቻሉም ነበር ቁርአን ያለው ያልተደረገውን ስለሆነ ሊገያጂጃቸው ችለዋል ይህ የሚያሳየው ቁርአን እየዋሸ መሆኑን ነው ስለዚህ የአላህ ቃል አይደለም ወደሜለው ሊመራን ነው ማለት ነው ምክንያም አላህ እንዲህ አይሳሳትምና የነቢደ ሙሐመድን ባሕሪ ከሐሰተኛው ክርስቶስ ባህሪ ጋር መቀላቀል የተባለውም ቢሆን በንግግር ደረጃ ሊሆን ቢችል እንጂ መጽሐፍ ቅዱሱ ውስጥ የተካሔደ ስረዛና ድለዛ አይደለም ምክንያቱም ልድገመውና ስለ ነቢዩ ሙሐመድ የተነገረ አንድም ጥቅስ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለሌለ ሊሰርዙ ሊደልዙ ሊቀላቅሉ አይችሉም ክርስቲያኖቹ ከሐሰተኛው ክርስቶስ ጋር ሃወመሠሪዐስ ዐስዐ ለፎክቋ ዖዐዐሃፀ ዐፀ ለያ ጳክዘገፀሪ ሀያዐ ጳሀስሮሪዐ ይሃ ለዐ ለ ዖዐዐሃ ፍዱኒዳለቭርለሸሀሃርዐለቲ ዕዐዐሮ ዐበዜሆ ዐለሇቭሠ በገበ ዕበ ጳይህፅ ዕዐዐፀ ። በዚህ መለኮታዊ ቃል መለኪያ መሠረት ነቢዩን ከሐሰተኛው ክርስቶስ ጋር ቢያነጻጽሩ ተሳሳቱ ሊባሉ አይገባም መጽሐፍ ቅዱስ ሐሰተኛው ክርስቶስን የገለጠበት መግለጫ አሁን ላይ እስልምና የአላህ ሃይማኖት ቁርአንም የአላህ ቃል ስለመሆኑ ያረጋገጠበት ተአምር እንደሆነ የእስልምና ምሑራን በኩራት እየተናገሩት ያለ ጉዳይ ነው ዳኢ ሳዲቅ ሙሐመድ ላለመደናገር ማመሳከር በተሰኘው መጽሐፉ መጽሐፍ ቅዱስ እውነትን ከውሸት ጋር ስለመቀላቀሉ በሱረቱል ጣሃ የጣሃ ምዕራፍ ሳምራዊው የተባለው ሰው የሠራውን ሥራ አሮን ሠራው ተብሎ በኦሪት ዘፀአት መጠቀሱ ነው በማለት ገልጺል ይህ አባባሉ የቁርአንን መለኮታዊ ቃልነት ጥያቄ ውስጥ እንዲወድቅ ያደርገዋል እንጂ መጽሐፍ ቅዱስ ችግር እንዳለበት አመላካች ሊሆን አይችልም ሱረቱል ጣሃ የጣሃ ምዕራፍ ጠቅሶ ይኸው መረጃዬ ማለት ቁርአን በመቼታዊና በታሪካዊ ስህተቶች የተሞላ መጽሐፍ ለመሆኑ ቁልጭ ያለ መረጃ በእጅ እንደማቀበል ይቆጠራል ሁለተኛው ክስ እውነትን መሸሸግ የሚል ነው የመጽሐፍ ቅዱስ ሌላው ችግር ተብሎ የተጠቀሰው እውነትን መሸሸግ የሚል ነው በዚህ ክስ ሥር ለማገናዘቢያ የተጠቀሰው የቁርአን ጥቅስ ሱረቱል አል ማኢዳ ነው ሱረቱል አልማኢዳ የማእድ ምዕራፍ አክዘዕሀበፀያዐሀበክዐያከዝ ላለመደናገር ማመሳከር ተሻሸሎ የቀረበ ገጽ የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ ከመጽሐፉ ትሸሽጉት ከነበራችሁት ነገር ብዙውን ለእናንተ የሚገልጽ ከብዙውም የሚተው ሲሆን መልእክተኛችን ሙሐመድ በእርግጥ መጣላችሁ ከአላህ ዘንድ ብርሃንና ገላጭ መጽሐፍ በእርግጥ መጣላችሁ ቃ ከ አ በአን አው እር ። ቁርአን የአላህ ቃል ከሆነ አላህ ለምን ይዋሻል። ዐበዜሆ ዐለብሀሠ በገበ ሆ ሀ ጳይፅ ዕዐዐፀ ዐ ክፀ አ በሀያዐቤ ሀዐ የሀሆ ሀበ ዐአሀሀ ህዐ ዐዐዐፀ ዐ ዐዐዐ ሃዐ ዐዐዐፀ « ህዐ ዕዐዐፀ እነዚህ ሰዎች ይህንን የአምላካቸውን ቃል ጥሰው ይህንን አደረጉ እንኳን ቢባል ነቢዩንም ሆነ አላህን እንዲሁም በየዘመናቱ የኖሩትን ዳኢዎች መጽሐፍ ቅዱስ ተበርዚል ብሎ ለማለት አያስችላቸውም ምክንያቱም አሁን በእጃችን ላለው መጽሐፍ ቅዱስ የመጀመሪያ ቅጅዎች የግሪክና የእብራይስጥ የመጀመሪያ ቅጅ መጽሐፍ ቅዱሳት እንጂ የመዲና አይሁዶች እጅ የነበሩት መጻህፍት አይደሉም ለዚህ ነው የኢስላም ታሪክ ጸሐፊው ኢማም ዋሃብ ሙናቢሃ የአላህ ቃላት መጽሐፍ ቅዱስ አላህ ሲያወርዳቸው በነበረበት በቀደመው ሁኔታቸው አሉሌ አልጠፉም ማለት የቻሉት ሙፈሲር ኢብን አቢ ሃቲም የውሃብ ሙናቢሃን አሳብ ለመሞገት ሞክረዋል ሲሞግቱ እደተበረዘ ለማሳየት የሞከሩት በትርጉም ሥራዎች ላይ እንጂ በዋናው ቅጅ ላይ አይደለም አለመሆኑን ኢብን ካሲር አስነብበውናል ኢብን ውሃብ ሙናቢሃ እየተናገረ ያለው እርሱ እጅ ስላለው መጽሐፍ ቅዱስ ከሆነ አሉ አዎን የአላህ መጻህፍት ተጠብቀዋል ፈጽሞ ሊለወጡ አይችሉም ይህ የሚያሳየው ያልተበረዘ ንጹህ መጽሐፍ ቅዱስ ከነቢዩ መሞት በኋላም ቢሆን ሙስሊሞች እጅ ይገኝ እንደነበር ነው ሌላው እነዚህ አራት የመዲና አይሁዶች የአላህን የአላህ ራሳቸው የጻፉት የተባለውን መጽሐፍ ደግሞ የራሳቸው እንደሆነ መግለጻቸው መጽሐፍ ቅዱስ ከእነርሱ ሥራ ተለይቶ ይኖር የነበር መሆኑን ያመላክታል በዚህም ለአላህ ቃል የነበራቸውን አክብሮት አሳይተዋል ይህም ከደፋሮቹ ከእነ ከሊፋ ኡስማን ይልቅ እውነተኞችና ታማኞች ፈሪሃ እግዚአብሔር የነበራቸው መሆናቸውን አመላካች ነው ስለዚህ ሊደነቁ እንጂ ሊከሰሱ አይገባም ቁርአን ግን እንዲህ የኖረ መጽሐፍ አለመሆኑን ቀደም ብለን ተነመልክተናል የተበረዘ የተደለዘ አብዛኛው ክፍሉ የጠፋ ለትውልድ ያለምንም እንከን መተላለፍ ያልቻለ መጽሐፍ ነው ይህም መለኮታዊ ቃል ያለመሆን ማሳያ ነው ተጨማሪ አንድ ምስክር ስጨምር ከሊፋ ኡመር ከተናገረው ላስነብባችሁ ሐዲስ ሚሽካት አልሙሳቢህ ቅጽ ኡመር እንዲህ አለ እጅግ ታላቅ ደስታን የፈጠረብንን ትምህርት ከአይሁዳውያኑ ሰማን ታዲያ ከእነዚህ ውስጥ የተወሰነውን ብንጽፈው እርስዎ ምን ይላሉ። ሱረቱል አልሒጅር ጠቅሶ በሁለቱ መጻሕፍት መካከል ስለ አላህ ጥበቃ ማውራት ነቢዩ ሙሐመድና ቁርአን በዚህም ላይ የተመሰረተው እስልምና ሃይማኖት ከአላህ ዘንድ ለሰው ልጆች የተላኩ የደህንነት መንገዶች አለመሆናቸውን ማረጋገጥ ነው መጽሐፍ ቅዱስ ግን በዘመኑ ሁሉ በእስልምና ሃይላትም ሆነ በሌሎች መኖሩን በማይፈልጉት ሃይሎች ብዙ ስደት ቢደርስበትም እራሱ የቃሉ ባለቤት እግዚአብሔር አምላክ ጠብቆት እንደኖረ ሊታወቅ ይገባል የእስልምና የመረጃ ምንጮቹ የሰጡትን የምስክርነት ቃልም አንብባችኋል በዘለአለም አምላክ ጥበቃ ሥር የሚኖር በመሆኑ የሰው እጅ በፊትም ይሁን አሁን በዚህ ዘመን ሲኖር የመጀመሪያ ይዘቱን አላስለቀቀውም በውስጡ በተቃዋሚዎቹ ስህተት የተባሉ የመጽሐፉ ክፍሎች የመጽሐፉን ባሕሪ ሳያውቅ በገረፍታ ለሚያያቸው ስህተት በመምሰል ለመተቸት በር የከፈቱ አንዳንድ ሁኔታዎች እየታዩበት እንኳን ከትችት እንዲድን የእርዳታ ሥራ የሠራ እንደ ከሊፋ ኡስማን የደፈረ ደፋር የለም የመጽሐፍ ቅዱስ ተጠቃሚ የሆነ ሰው በጥናቱ ወቅት ለሚገጥሙት ችግር መሳይ ነገሮች መፍትሔውን ለማግኘት ይችል ዘንድ ላ ዐፀ ለብክጸዐ ሀለሀዐሀ ሃዐ ዐዐዐ እንዲያመሳክርባቸው የቀድሞዎቹ ቅጅዎች ዛሬ ድረስ ተጠብቀውለት ይገኛሉ እግዚአብሔር እራሱ ጠባቂው ስለሆነ ማንም አላቃጠላቸውም ለዚህ ነው በእያንዳንዱ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የግርጌ ማስታወሻ ላይ ስለ አንዱ አሳብ መረጃ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ እዚህኛው ቅጅ ላይ እንዲህ ይሳል ከዛኛው ደግሞ እንዲህ ይሳል እየተባለ ዋናው አሳብ ሳይነካ መግለጫ የሚሰጠው ይህም አንዱ የመጽሐፍ ቅዱስ የታማኝነቱ ልዩ መገለጫ ነው ቁርአን ግን ለዚህ የታደለ መጽሐፍ አይደለም ማብራሪያና ማመሳከሪያ ሲጠየቅ የሚያቀርበው የአላህ ቃል የሆነውን ነቢዩም ተጠባባቂና አረጋጋጩ ነኝ ያሉለትን የቀደሙትን መጻሕፍት ትክክለኛ የሆነውን አላህ ያውቃልልከ ዘበዐህ ከፀ ሀ በሚል መንፈሳዊ መሳይ የሽፋን ንግግር በመናገር ምንም ሊታረቁ የማይችሌ የራሳቸውን ከነፍሳቸው የወጣ ማላምት የሚናገሩ ኡለማዎችን አተረጓጎም ነው በዚህ ዘመን ያሉት የእስልምና ዳኢዎች በተለያዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁትን የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም መጻሕፍትን በመያዝ የሚያነሱት የመበረዝ ክስስ እንዴት ይታያል። የሚል ጥያቄ ይነሳ ይሆናል ቀደም ብሎ እንዳነበባችሁት ሙፈሲር ኢብን አቢ ሃቲምም ውሃብ ሙናቢሃን ለመሞገት የሚሜከሩት ዋና ቅጅዎች ላይ ሳይሆን ትርጉሞችን በተመለከተ ነው የዘመኑ ዳኢዎችም የነቢዩ ሙሐመድን ሱሃባዎች ንግግር ደጋፊ አድርገው መጽሐፍ ቅዱስ ተበርዚል በማለት ጩኸት የሚያሰሙት በእነዚህ በተለያዩ ቋንቋዎች በተዘጋጁት መጽሐፍ ቅዱሳት ላይ ነው ብረዛን በተመለከተ የሁለታችን ጥያቄዎች መሠረት የተለያዩ ናቸው የእኛ በቁርአን መበረዝ ዙሪያ ያለን ጥያቄ የተመሠረተው በትርጉሞች ላይ ሳይሆን ከነቢዩ ሙሐመድ አፍ እየወጣ ተጻፈ ስለ ተባለለት የመጀመሪያው ቅጂ ላይ ነው የእነርሱ ደግሞ መሠረቱ የትርጉም ሥራዎች ላይ ነው በበኩር ቋንቋ ለተጻፉት ግን የእስልምና ምሑራኑ ላለመበረዛቸው የሰጡትን ምስክርነት አንብባችሁታል ስለዚህ በእነዚህ የመከራከሪያ መሠረቶች መካከል ግዙፍ ልዩነት አለ እንግዲህ ለእንዲህ አይነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከፈለጉ መልሱ ያለው ጓዳቸው ውስጥ ነው መልሱን የሚሻ ሰው በ ቋንቋዎች በሙሉና በከፊል ተተርጉመው ወደተሰራጩት የቁርአን ትርጉም መጻሕፍት መሄድና እነርሱን መፈተሸ የተሻለ ነው የትርጉም ቅዱሳት መጽሐፍት የብረዛ ማሳያ መሆን ከቻሉ አሁንም በዚህ በኩል ቁርአን የተበረዘ መሆኑን ማረጋገጥ ይችላሉ የመጀመሪያው በአገራችን ቋንቋ የተዘጋጁት የእኛ አገር የእስልምናው ዳኢዎች የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስን በተመለከተ ከ ዓም እስከ ዓም ድረስ የታተሙትን የመጽሐፍ ቅዱስ እትሞች በማነጻጸር በመካከላቸው ያሉትን የቃላት ልዩነቶች የተለወጡ ቃላትን ቋንቋ ባለው የማደግ ባህሪ ምክንያት በአንዱ ሲኖር በሌላው አለመኖራቸውን እንዲሁም የትየባ ችግሮችን በማንሳት ተበርዚል ይሉናል እንግዲያውስ ቁርአንም ኢትዮጵያ ውስጥ ተበርዚል ብረዛውን የፈጸመው ደግሞ ነጃሸ አሳታሚ ድርጅት ነው ይህ አሳታሚ በአማርኛ ቁርአንን ከሦስት ላላነሰ ጊዜ አሳትሟል « የመጀመሪያው በሐጂ ሙሐመድ ሳኒ ሐቢብ እና በሸህ ሰይድ ሙሐመድ ሳቢቅ የተተረጎመው ሁለተኛው በ የታተመው ባለ ጥራዙ ቁርአን ሦስተኛው በኋላ የታተመው ባለ ጥራዙ ቁርአን አንድ የቁርአን አንቀጽ እንውሰድና ብረዛው ምን እንደሚመስል እንመልከት ሱረቱል አልሐጅ የሐጅ ምዕራፍ ከመልክተኛና ከነቢይም ከአንተ በፊት አንድንም አላክንም ባነበበ እና ዝም ባለ ጊዜ ሰይጣን በንባቡ ላይ ማጥመሚያን ቃል የሚጥል ቢሆን እንጅ ወዲያውም አላህ ሰይጣን የሚጥለውን ያስወግዳል ከዚያም አላህ አንቀጾቹን ያጠነክራል አላህም ዐዋቂ ጥበበኛ ነው ይህ በ ዓም በነሐጂ ሙሐመድ ሣኒ ሐቢብ ተተርጉሞ በ ዓም በድጋሚ በታተመው የአማርኛ ቁርአን ሰፍሮ የሚገኝ ነው ሳውዲ አረብያ ውስጥ በአራት ጥራዞች ተዘጋጂቶ ለአማርኛ ተናጋሪዎች በነጻ በመሰራጨት ላይ ባለው የአማርኛ ቁርአን ይኸው አንቀጽ እንዲህ ሰፍሯል ሱረቱል አልሐጅ የሐጅ ምዕራፍ ከአንተ በፊት አንድም ነቢይ ወይም መልእክተኛ አላክንም አንዳች ነገር በተመኘ ጊዜ ሰይጣን በምኞቱ ላይ ከንቱ ነገር የጣለበት ቢሆን እንጂ ግና አላህ ሰይጣን የጣለውን ከንቱ ነገር ያስወግዳል ከዚያም መልእክቱን ይበልጥ ያጸናል አላህ አዋቂ ጥበበኛም ነው በተለያየ ወቅት በተለያዩ ሰዎች ተዘጋጅተው በአንድ አሳታሚ በታተሙት በእነዚህ ሁለት የቁርአን የትርጉም ሥራዎች የሚሜታየውን ልዩነት እንመልከት የ እና የ እትም አዲሱ ባለ አራት ጥራዝ እትም ባነበበና ዝም ባለ ጊዜ የሚለው አንዳች በተመኘ ጊዜ በሚል ተተክቷል በንባቡ ላይ ማጥመሚያን ቃል በምኞቱ ላይ ከንቱ ነገር በሚል የሚለው ተተክቷል ወዲያውም የሜለው ወጥቶ ግን የሚል ቃል ገብቷል አላህ የሚለው ሲኖር አላህ የሚለው ወጥቶ ከንቱ ነገር የሚል ሐረግ ተጨምሯል አንቀጸቹን ያጠነክራል የሚለው ምልእክቱን ይበልጥ ያጸናል በሜል ወጥቶ ተተክቷል የትኛው ነው ትክክለኛ የአላህ ቃል። መዓ ራታ ሂ ሩ አሁንም የትርጉም ሥራቸው የአላህን ማንነት ሳይሸራረፍ በትክክል መግለጹን ለመፈተሸ አለመሞከራቸው ሌላው የተገለጠ ስህተታቸው ነው አላህ ሁሉን አዋቂ ሆኖ ሳለ በቁርአን እና በተርጓኒዎቹ ግን ሁሉን አዋቂ እንዳልሆነ እያሳዩን ነው ውድ አንባቢ እንግዲህ እነዚህን የቁርአን ትርጉም መጽሐፍት አንቀበልም የቁርአንን መበረዝ አያንጸባርቁም ካሌ እንደሚሉ የታወቀ ነው ለመጽሐፍ ቅዱሱም ተመሳሳይ ነው ስለ ቁርአን መበረዝ ስንናገር ከነቢዩ ሙሐመድ ስለተላለፈው የመጀመሪያው ቅጅ እንጂ አሁን ስላሉት የቁርአን የትርጉም መጽሐፍት እንዳልሆነ ሊታወቅ ይገባል አሁን በዚህ ዘመን ላይ በአረብኛ ቋንቋ ተጽፎ የሚገኘው ቁርአን ሌሎቹን የትርጉም ሥራዎች ማረምና ማስተካከል የሚችል ሥልጣን ያለው የመጀመሪያው ቁርአን አይደለም ነው እያልን ያለነው ይህንን ስናገር ከላይ እንዳያችኋቸው ተርጓሚዎችና የዘመኑ የሃይማኖት ንጽጽር ሊቆች እንደሆኑ እራሳቸውን እንደሚቆጥሩት ዳኢዎች በጭፍን ጥላቻና የሃይማኖት ጽንፈኝነት ተውጨ እንዳልሆነ አይታችኋል አንደኛ ሁለተኛ እየተባሉ በሚጠቀሱ በርካታ ኢስላማዊ የመረጃ ምንጮች ተደግፌ ነው መጽሐፍ ቅዱስ ግን እንደ ቁርአን እንዲህ የተዘበራረቀበት አይደለም በጌታችንና በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትእዛዝ መሠረት ወንጌልን በምድር ዙሪያ ለማዳረስና ሰዎች የአምላካቸውን ቃል በቋንቋቸው ያለምንም ችግር ይረዱት ዘንድ ታስቦ ወደ በሚደርሱ ቋንቋዎች ተተርጉሟል ሆኖም በሥራ ወቅት አንዳንድ ግድፈቶች ሊከሰቱ ይችላሉ በቁርአንም የትርጉም ሥራ ወቅትም ሊያጋጥም የሚችል ነው ነገር ግን የማረምና የማስተካከል ስልጣን ያላቸው በበኩር ቋንቋው የተጻፉ ቅጅዎች በቃሉ ባለቤት ተጠብቀው እስከአሁን ድረስ ያለምንም ችግር በሕይወት ስለሚገኙ የተፈጠረውን ችግር ማስተካከል ይቻላል መጽሐፍ ቅዱስን ለማጥናት የሚፈልግ ሰው በበኩር ቋንቋ የተጻፈ መጽሐፍ ቅዱስ ቢያስፈልገው አሁን ማግኘት ይችላል ይህም መጽሐፍ ቅዱስ ስህተት አልባና በእግዚአብሔር በራሱ የሚጠበቅ መጽሐፍ ለመሆኑ አንዱ ማረጋገጫ ነው ማጠቃለያ የቀደሙት መጽሐፍት ተበርዘዋል ተብሎ በነቢዩ ሙሐመድ ብሎም በከሊፋ ኡመርና በአባስ እንዲሁም በተከታዮቻቸው እየተነዛ የነበረውና ያለው ክስ የሐሰት ክስ እንጂ እውነትነት የነበረውና ያለው አይደለም እስካሁን ባየናቸው በቁርአንም ሆነ በሐዲሳቱ መልእክቶች ክሳቸውን አሳማኝ እንዲሆን « ሊያግዛቸው የሚችል ምንም መረጃ ማቅረብ አለመቻላቸው ታይቷል እንግዲህ መጽሐፍ ቅዱስ የተበረዘ ስለሆነ የእግዚአብሄር ቃል አይደለም የሚለው የዘመኑ የእስልምና የሃይማኖት ንጽጽር ሊቅ ነን ባዮቹ የመደምደሚያ አሳብ ምንም ሊያስኬድ አይችልም ደግሞም በትክክል ጥናት ተደርጎበት የተደረሰበት ድምዳሜ ሳይሆን የጭፍን ተሟጋቾች ከንቱ የስም ማጥፋት ወሬ መሆኑ ግልጽ ሆኗል በዚህ ሥራቸው የሚንጸባረቀው የተከበረው አምላክ ባህሪ ሳይሆን የሰው ልጆች ሁሉ ጠላት የሆነው የሰይጣን ሥራ ነው ብል ተሳሳትክ ሊለኝ የሚችል አለ አልልም ውድ አንባቢ በእስካሁኑ ንባባዎት መጽሐፍ ቅዱስ የዘለአለሙ አምላክ ያልተበረዘ ንጹህ ለሰዎች ሁሉ ደህንነት የተሰጠ ሕያው ቃል መሆኑን በበቂ ሁኔታ የተገነዘቡ ይመስለኛል ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ ተበረዘ ተብሎ ለተወራው ሐሰተኛ ክስ አሳማኝ ማስረጃ ሳይቀርብ እውነተኛነታቸው ብቻ በቁርአኑና በሃዲሳቱ ጎልቶ ተመስክሮለት አይተዋል ስለዚህ ለዘለአለም ህይወትዎ ደህንነት ትክክለኛ አመራር ያገኙበታልና አምነው ይጠቀሙበት የሚሰጥዎትንም ምክር ይስሙት አእላለሁ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሰው ልጆች ሁሉ ሲናገር ወደ ሮሜ ሰዎች ልዩነት የለም ሁሉም ኀጢአትን ሠርተዋል የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል ደግሞም ወደ ሮሜ ሰዎች የኀጢአት ደምወዝ ሞት ነውና የእግዚአብሔር ስጦታ ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የዘለለም ህይወት ነው ይላል ስለዚህ ሰው ሁሉ ኀጢአተኛ ነው አንድም ጻድቅ የለም ከተባለ እርስዎም ኀጢአተኛ ነዎት የኀጢአት ደሞዝ ደግሞ የዘላለም ሞት ነው ቢሆንም ዛሬ ለእርስዎ እድል አለ የሚወድዎት አምላክ ቅዱስ እግዚአብሔር ለዘላለም እንዳይሞቱ አስተማማኝ የደህንነት መንገድ አዘጋጅቷል እርሱም ጻድቅ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወትን ያገኛል ለዘላለምም በደስታ ከአምላኩ ጋር በገነት ይኖራል መጽሐፍ ቅዱስ በዮሐንስ መንጌል ላይ ሲናገር የዮሐንስ ወንጌል በአርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለምን ሁሉ እንዲሁ ወዶአልና ውድ አንባቢ ሁሉን ቻይ በሆነው አምላክ በእግዚአብሔር እጅግ የተወደዱ ሰው መሆነዎትን ምን ያክል ያውቃሉ። ከዚህ በኋላ የአምላከዎትን ቃል መጽሐፍ ቅዱስን የሕይወት ምግብ ነውና ያንብቡ ይታዘዙት ሙግት ሁለት መጽሐፍ ቅዱስ የሰው አዕምሮ ሊቀበለው የማይችላቸውን አሳቦች መያዙ እራሳቸውን እንደ ሃይማኖት ንጽጽር ሊቅ ቆጥረው ለሙግት የተነሱት የእስልምና ዳኢዎች መጽሐፍ ቅዱስ ተበርዚል ከሚለው መሞገቻቸው ቀጥለው የሚያነሱት ይህንን ክስ መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል አይደለም ምክንያቱም የሰው አዕምሮ ሊቀበላቸው የማይችላቸውን አሳቦች በውስጡ ይዚል የሚል ነው ዳኢ ሳዲቅ ሙሐመድ ላለመደናገር ማመሳከር በሚል ርዕስ ባሳተመው መጽሐፍ ለዚህ መሞገቻው እንደ ማስረጃ የጠቀሳቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች አሉት በጠላት ከበባ ምክንያት በተከሰተው ብርቱ ርሃብ ልጄን ቀቅላ ከጓደኛዋ ጋር የበላችውን እናት ታሪክ መጽሐፈ ነገስት ካልዕ የአባት እድሜ ከልጁ እድሜ በሁለት ዓመት ያነሰ የመሰለበት ታሪክ መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ ነቢዩ ሕዝቅኤል የሰውን አይነ ምድር እንደ ምግብ ተጠቅሞ ትንቢታዊ መልእክቱን እንዲያስተላልፍ የታዘዘ የመሰላቸው ክፍል ትንቢተ ሕዝቅኤል ሴት ልጅ በወር አበባ ጊዜዋ መደረግ ስለሚገባው የመንጻት ሥርአት ሕግን በተመለከተ የተሰጠው ትእዛዝ ኦሪት ዘሌዋውያን በወገኖቹ መካከል ለራሱ ስም ማስጠሪያ የሚሆን ዘር ሳይተካ ለሞተ እስራኤላዊ ስሙ እንዲጠራ ለማድረግ የሟችን ሚሜስት ስለማግባት የተሰጠውን ሕግ በተመለከተ ኦሪት ዘዳግም የነቢዩ አህያ ለነቢዩ እብደቱን ትነግረው ዘንድ የሰው ቋንቋ ተጠቅማ መናገሯን በተመለከተ ኛ የሌጥሮስ መልእክት ላፍለመደናገር ማመሳከር ተሸሸሎ የቀረበ ገጽ በምሳሌያዊ አገላለጽ ዛፎችን ለንግሥና እያወያየ ለሰዎች መልእክቱን በማስተላለፍ የተዋጣለትን የኢዮአታምን ታሪክ በተመለከተ መጽሐፈ መሳፍንት በጾታ ፍቅር ምሳሌ ቅኔን በመቀኘት መልእክቱን ያስተላለፈውን የንጉሥ ሰለሞንን መኃልይ የተመለከተ መኃልየ መኃልይ ዘሰለሞን ሐዋርያው ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ በላከው ደብዳቤ ላይ ስለተጠቀመው የመዝጊያ መልእክት ኛ ወደ ጢሞቴዎስ እነዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የያዙት መልእክት የሰው አዕምሮ ሊቀበላቸው የማይችል አስቸጋሪ ታሪኮችና መልእክቶች ናቸው ይላሉ በመሠረቱ ይህ አመለካከታቸው ከመሰሎቻቸው ውጭ ባሉ ሰዎችም ዘንድ ተቀባይነት ሊያገኝ የሚችል አመለካከት ነው ብዬ አላምንም ን ውድ ን ውድ ን ውድ ን ታዲያ የአምላክ ሁሉን ቻይነት ከሚገለጥባቸው መንገዶች አንዱ ከሰው አዕምሮ ያለፈ ነገር ማድረጉ ካልሆነ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል። ከፊሉን አስተባበላችሁ ከፊሉንም ትገድላላችሁ ቁርአን የአላህ ቃል ከሆነ በዚህ አንቀጽ እየነገረን ያለው ሰዎች ከአላህ የሆነውን መልእክተኛና መልእክት መቀበል አለመቀበል በነፍሳቸው ፈቃድ ላይ የተመሠረተ እንደሆነ ነው የሚወዱትን ይቀበላሌ የማይወዱትን ይጥላሉ ከመጀመሪያው አባት ከአዳም ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ የሰው ልጅ በአላህ ትዕዛዝ ፈንድቆ ደስታውን ሲገልጽ ታይቶ አይታወቅም የቁርአንም ንግግር ይኸው ነው አዕምሮው ነገሮችን ይቀበል ዘንድ ካስፈለገ ከስሜቱ ከፍላጎቱ እውነት ካለው ከእምነቱ ጋር በጥብቅ መማከርን ይፈልጋል እውነት ነው ብሎ የያዘው እምነቱ ከአላህ እውነት ጋር ሲነጻጸር እውነት ላይሆን ይችላል ሆኖም ከላይ የተጠቀሰው የቁርአን አንቀጽ የአላህ ንግግር ከሰዎች ፍላጎት ጋር ሊጣጣም የማይችልበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችልና የሰውም አዕምሮ ሊገፋው እንደሚችል ያስገነዝባል እንግዲህ ዳኢ ሳዲቅና መሰሎቹ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለሰፈሩት መልእክቶች ያቀረቡት መሞገቻ ተገቢ ሊሆን አይችልም ቁርአናዊ መሠረትም የለውም ያንንም እያንዳንዱን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ስንመለከት አብረን የምንመለከተው ይሆናል እንግዲህ ግራ የተጋቡ ኃይሎች እንዳሌት አምላክን አምላክ ያሰኘው በሰው አዕምሮ ልክ ተናግሮ መገኘቱ ከሆነ የአምላክ ነገር የሰው አዕምሮ ሊቀበለው በሚችለው ልክ ብቻ ተለቋል ማለት ይሆናል ይህ አመለካከት ሰው የአምላክ ነገር ከአእምሮው ልክ ያለፈ ስላልሆነ እርሱን በቀላሉ ማረጋገጥ ስለሚችል የእምነት ልዩነቶች መፈጠር አልነበረባቸውም ወደሚል መደምደሚያ ሊያደርሰን ነው ይህም ደግሞ ከሱረቱል አልማኢዳ እና ከሌሎች ተመሳሳይ የቁርአን አንቀጸች ጋር በቀጥታ ይጋጫል ከእስልምና የእምነት መሠረቶች መካከል አንዱ ከሆነው ከቀድር ጋርም የሚጋጭ ይሆናል እንደ እነዚህ ወገኖች አመለካከት አንድ የእምነት መጽሐፍ የሁሉን ቻይ አምላክ ቃል ነው ለመባል የሰው አዕምሮ ሊቀበለው መቻልና በውስጡ በቀላሉ ሊታመኑ የሚችሉ አሳቦችን መያዝ ሊኖርበት ነው እንዲህ ከሆነ ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አሉ ከተባሉት የሰው አእምሮ ሊቀበላቸው ከማይችላቸው አሳቦች ይልቅ አላህ አጥጋቢ ምክንያት ያልሰጠባቸው በቀደሙት መጻሕፍት ማረጋገጫ ያላገኙ ለአዕምሮ የማይመቹ ቁጥራቸው በርካታ አሳቦች ቁርአኑን አጨናንቀዋል የነቢዩ ሙሐመድ ሐዲሳትም በመሰል ሐሳቦች ተሞልተው ሙስሊሙ እጅ ይገኛሉ ታዲያ ቁርአን የአላህ ቃል አለመሆኑን ራሳቸው ማረጋገጣቸው አይደለምን። ሌላው በመጽሐፍ ቅዱስና በቁርአን መካከል ያለውን ልዩነት በቁርአን መነጽር ተመልክተው ድምዳሜ መስጠታቸው እነርሱም እንደሚያምኑት በቁርአንና በመጽሐፍ ቅዱስ መካከል ትልቅ ልዩነት አለ ለምሳሌ አዳምን እንውሰድ አዳም ያለኀጢአት ሞት ለሌለበት ደስታ ተፈጥሮ በገነት ይኖር እንደ ነበር ይህ ንጹሕ ሰው በሰይጣን ተታሎ ከመኖሪያው እንደተባረረበ ሁለቱም መጽሐፍት ይታወቃል መጽሐፍ ቅዱስ በዚህ ሞት እንደ ነገሠበት ሲናገር ቁርአን ሞት አብሮት እንደተፈጠረ ያወራል መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ለዚህ ሞት ለነገሠበት ሰው ያለውን ጥልቅ ፍቅር እንደገናም የሚድንበትን መንገድ እንዳዘጋጀለት ይህንን መንገድ የወደደ ሰው ወደ ገነት ተመልሶ ከአምላኩ ጋር በደስታ እንደሚኖር የተናገረበት አምላክ እራሱን ለሕዝቡ የገለጠበት የኪዳን መጽሐፍ ነው ቁርአን ግን አላህ ለፈተና የፈጠረውን ከመፈጠሩም በፊት የገሃነም ወይም የገነት ሰው መሆኑን ዐክ ዐፀሀጸክዐሰ ህዐ ዐዐፀፀ የወሰነበትን ተስፋ ቢስ ሰው ለማስፈራራትና ለማስጠንቀቅ የተላከ መጽሐፍ ነው ይህ በሁለቱ መካከል ያለ እጅግ ግዙፍና ሊገናኝ የማይችል ልዩነት ነው የአላማም የተልእኮም ዝምድና የላቸውም እንዲህ ሆኖ እያለ መጽሐፍ ቅዱስን በቁርአን መነጽር ለመመልከት መሞከር ይህ ነው የማይባል ስህተት ይሆናል መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ባህሪና ለኀጢአት ያለውን አቋም ሳይሸራርፍና ሳያቃርን በግልጽ የሚናገር የአምላክ ቃል ነው ቁርአን ደግሞ ለኀጢአት ያለውን አቋም በግልጽ ያላስቀመጠ የሚያቃርንና እራሱ የአምላክ ቃል ስለመሆኑ ማረጋገጫ የሌለው መጽሐፍ ነው እንዲህ በመሆኑም አንባቢ የታሪክ ፍሰቱን ተከትሎ በመሄድ መልእክቱን በመረዳት ሞጋች ነገሮችን እንዳያነሳ ለማድረግ ታስቦ የተሰደረ በወረደበት ቅደም ተከተል ሳይሆን በተዘበራረቀ መልኩ በኢራቃዊው በሃፍስ የተጠረዘ መጽሐፍ ነው የኢራቃዊውን የሃፍስን ስም የጠቀስኩት አሁን ያለው ቁርአን በከሊፋ ኡስማን የተዘጋጀው ባለመሆኑ ነው ይህንን በመጀመሪያው ገጾች በምስል አስደግፌ ባቀረብኩት ላይ ማስነበቤን አትዘነጉትም ብዩ አስባለሁ ስለዚህ ይህንን ውል የጠፋበትን በጭፍን የሚከተሉ በእርሱም ታንጸው ያደጉ በመሆናቸው ታማኝነት የጎደለው ማንነታቸው ሊታይ ግድ ሆኖባቸዋል አንዱ ሱራ በሱራዎች አቀማመጥ የአወራረድ ቅደም ተከተል ያለበት ደረጃና በአሁኑ ቁርአን ውስጥ የሚገኝበትን ምዕራፍ እንዴት እንደሆነ ናሙና ላሳያችሁ እንዲያውም በሌሎቹ ሱሃባዎች የቁርአን ቅጅ ምን አይነት ደረጃ እንደነበረው አያይዝ ባሳያችሁ ጥሩ አይመስላችሁም። አዕምሮ ሊቀበለው የማይችለው የአምላክ ቃል ነው በተባለ መጽሐፍ ውስጥ የጾታ ፍቅር መካተቱ ነው ይላሉ ይህንን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የሙግት መነሻ ነጥብ የሚያደርግ ሙስሊም ስለራሱ መጽሐፍትና ስለሚጠባበቀው ተስፋ እውቀቱ እዚህ ግባ የማይባል መሆን አለበት እነዚህ የዘመናችን የሃይማኖት ንጽጽር ሊቆች ነን ባዮች ከዚህ መደብ ውስጥ ሳይሆኑ አይቀሩም የእውቀት ባለጸጋ እና አስተዋይ ተችዎች ቢሆኑ ኖሮ ቁርአንን ለማሞገስ መጽሐፍ ቅዱስን ለማንቋሸሽ መኃልየ መኃልይን መጥቀስ አልነበረባቸውም ሆኖም እውቀቱም ብቃቱም ሆነ ሞራሉ እንደሌላቸው የእስካሁኑ ጉዚችን ያሳየን ይመስለኛል ስለዚህ አድርገዋታል ቀሩ መጽሐፍ ቅዱስ የአላህ ቃል አይደለም ለማለት ድፍረት ያገኙት መኃልየ መኃልይ የጾታዊ ፍቅር መግለጫ ተራ ቅኔ መስሏቸው ይሆናል የአላህ ቃል መለኪያው ይህ ከሆነ በሞራላዊ ይዘቱ የወረደ እና ራሳቸው የሚያፍሩበትን መልእክት ቁርአንና የነቢዩ ሙሐመድ ሐዲሳት ውስጥ ሲመለከቱ ለምን ቁርአን የአላህ ቃል አይደለም ነቢዩም የአላህ መልእክተኛ አይደሉም ማለት ተሳናቸው። ይህ ግልጥ ያለ ስህተት ነው ቁርአን የአላህ ቃል ቢሆን ኖሮ ይህንን ግልጽ ስህተት አይናገርም ነበር ቁርአን እርስ በእርሱ የሚጋጭ መጽሐፍ መሆኑን ይገልጣል እርስ በእርሱ የሚቃረን መልእክት ደግሞ ከአላህ ሊሆን አይችልም የሰው መልእክት በአላህ ቃል ውስጥ ያሉት የሃይማኖት ንጽጽር ሊቆች ነን ባዮቹ የጅኖችን ውሸት ቁርአን ውስጥ እያዩትና ሁሌ እየቀሩት የአላህ ቃል ብለውም እያስተማሩት ለያንኑ ጅን ከሰው ውስጥ ለማስወጣት እየቀሩ እንዴት መጽሐፍ ቅዱስን በዚህ ሁኔታ ሊተቹ አሰቡ። ሠ ዐታሀ ዐሀህሃሀክ ስፀ ዘየዐባ ዐ ሀ ጸክዐስ ጽፀህዐ ፀወከዐቢ ያዐበፎሮሪ ዕሃ አዐዐዐበገዐሪ ርጩጩፎል ዐዐ ዖሀፅዕክፀ የሂ ሂዐበፀዐበ ዕዐዐፀ ዐ ሙሐመድ ራሳቸው ታዲያ አላህ በነቢዩ ኸሊፋ ኡመር በኩል ካወረዳቸው የቁርአን አንቀጾች መካከል ሦስቱን አሁን እንመልከት ሳሂህ አልቡኻሪ ቅጽ ቁጥር ገጽ አላህ ከእኔ ጋር በሦስት ነገሮች ተስማማ ሀ እንዲህ አልኩ የአላህ መልእክተኛ ሆይ ለጥቂት ሶላቶቻችን የአብርሐምን መቋሚያ የሶላት ቦታችን ብናደርግ ብዬ ተመኘሁ አልኳቸው ወዲያው ሱረቱል አልበቀራ እናንተ ሰዎች ለአንዳንድ ሶላቶቻችሁ ምሳሌ በካባው ሁለት ረክአት ጠዋፍ ለማድረግ የአብርሐምን መቆሚያ የሶላት ቦታ አድርጋችሁ ውሰዱ የሚለው ወረደ ለ ስለ ሴቶች መሸፈን የወረደውን በተመለከተ እንዲህ አልኩ የአላህ መልእክተኛ ሆይ ከወንዶች ራሳቸውን እንዲሸፍኑ ሚስቶችዎትን ቢያዙ መልካም ነው ምክንያቱም መጥፎና መልካም ከሆኑት ጋር ያወራሉና አልኩ በዚህ ጊዜ ሂጃብን የተመለከተው ራዕይ ወረደ ሐ አንድ ጊዜ ነቢዩን ለመቃወም የነቢዩ ሚስቶች በፊታቸው ሕብረትን ፈጠሩ እኔም እንዲህ አልኳቸው ምናልባት ነቢዩ ሁላችሁን ቢፈታችሁ ጌታው በእናንተ ምትክ ከእናንተ የተሻሉትን ሚስቶች ይሰጠዋል ወዲያውም እንዳልኩት ያለ የቁርአን አያት ወረደ ሱረቱል አልተህሪም የማውገዝ ምዕራፍ መላችሁንም ቢፈታችሁ ከእናንተ የበለጡ ሚስቶችን ሙስሊሞች አማኞች ታዛገናች ተጸጻቾች ለአላህ ተገዢዎች ጸጾመኛዎች ፈቶች ደናግልም የኾኑትን ጌታው ሊለውጠው ይከጀላልሽ ከዚሁ ሰው ከከሊፋ ኡመር ጋር የተያያዘ ሌላ ሐዲስ ላስነብባችሁ ኢብን ማርዳውያህ ሲናገር ሙጃሁድ እንዲህ አለ ኡመር አስተያየት ሲኖረው በዛ ላይ ቁርአን ይወርዳል ያንን ለማረጋገጥ ኢብን አስካሪ ሲናገር አሊ እንዲህ አለ የኡመር የተወሰኑ አስተያየቶች ቁርአን ውስጥ አሌ ዐክክ ዐፀሀደክዐሰ ህዐ ዐዐፀፀ ፐስፀ ዘ ዐ ነፀ ጸክዐሃስ ዕዐዐፀ ይህ ማለት ቁርአን አላህና ኸሊፋ ኡመር ያዋጡት ነው ማለት ነው ታዲያ ራሳቸውን የሃይማኖት ንጽጽርሊቆች አድርገው የቆጠሩት ወገኖች ቁርአን የአላህ ቃል አለመሆኑን እያረጋገጡልን እንደሆነ አልታያቸውምን። ሱረቱል አል አዕራፍ የአዕራፍ ምዕራፍ ዐስ ዐፀሀደክዐሰ ህዐ ዐዐዐ ዐለሀሀ ይሳደ ሱረቱል አልሒጅር የሒጅር ምዕራፍ ሱረቱል ሳድ የሷድ ወይም የዳውድ ምዕራፍ ውድ አንባቢ ለአብነት ይህንን ያህል ካሳየኋችሁ ይበቃኛል ልቀጥል ብል ለመለኮታዊ ቃልነቱ ምንም አይነት ማረጋገጫ ማቅረብ በማይችለው ቁርአን ውስጥ የሰው አዕምሮ ሊቀበላቸው የማይችላቸውን በርካታ አንቀጾችን ማሳየት በቻልኩ እንግዲህ ራሳቸውን እንደ ሃይማኖት ንጽጽር ሊቅ የቆጠሩ ወገኖች የአላህ ቃል ማለት ምን ማለት እንደሆነ እናውቃለን ከሚሉበት ድፍረት አንዴ ቆም በማለት መጽሐፍትን በቅን ልብ ቢመረምሩ መልካም ነው እላለሁ ወደ መጽሐፍ ቅዱስ ስመለስ መለኮታዊ መጽሐፍ የሆነው መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል ኛ ወደ ጢሞቴዎስ የእግዚአብሔር ሰው ፍጽምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል። እናም ሐዋርያው ጳውሎስ ለወጣቱ መጋቢ ለጢሞቴዎስ የጻፈው መልእክትና የመዝጊያ ሰላምታ ተራ የሰው መልእክት ቢመስልም ተራ ግን አይደለም የኛ ጢሞቴዎስ ን ዓላማ የሰነቀ ድንቅ መልእክት ነው እግዚአብሔር ለጢሞቴዎስም ሆነ በየዘመናቱ ለሚኖሩት ልጆቹ አስተማሪ የሆነ ልብንም የሚያቀና መልእክት ነው ይህ ተራ የመሰላቸው የመልእክት ክፍል ለአንድ ክርስቲያን የሚያስተላልፈውን መልእክት ማወቅ ከፈለጉ ሩ ለወንጌል በጠላትነት ከሚመላለሱ ሰዎች ጋር እንዴት መኖር እንደሚገባ ከቁጥር ሩ ይህን ዓለምና በውስጡ ያለውን ትርፍ ወዶ ከእግዚአብሔር መንገድ ወደኋላ መመለስ የሚያመጣውን የሕይወት ኪሳራ በአንጻሩ በታማኝነት አገልግሎትን መወጣት የሚያስገኘውን ብድራት መዝኖ ስለመጓዝ ደግሞ ቁጥር ኛ የዮሐንስ ያዕቆብ ሩ በታማኝነት እግዚአብሔርን ማገልገል በመጨረሻ የሚያስገኘውን ብድራትና ሽልማት ቁጥር ሩ የወንጌሉን ሥራ ወንጌላውያኑ ከሐዋርያው ጳውሎስ ጋር እንዴት በትጋት እየሠሩ እንዳሉ ሌሎችም እንዴት ቀጣይነቱን ሊያስጠብቁ እንደማሚገባ በመካከላቸው የነበራቸው እጅ ለእጅ መያያዝ ለሥራው ያስገኘውን ጠቀሜታ ከቁጥር በሰላሙ ጊዜ ከጎን አብሮ የነበረ ወገን በመከራ ሰዓት ትቶ ሲሸሽ ሊሰጥ ስለሚገባ የፍቅርና የምሕረት ምላሽ ቁጥር ሰው ቢጥል በችግር ጊዜ አብሮ ባይቆም እግዚአብሔር አምላካችን ሁል ጊዜ ከአማኙ ጋር እንደሚሜሆን በመከራም ሆነ በደስታ ጊዜ ብቻን እንደማይተው አገልጋዩን ለጠላቶቹ መጫወቻ እንደ ማይጥለው እንዲያስተውል አማኙን ያስተምራል ከቁጥር የሉቃስ ወንጌል የማቴዎስ ወንጌል ይህን በሐዋርያው የመዝጊያ ሰላምታ ውስጥ ያለውን አስተምህሮ ከብዙ መቶ ዓመታት በኋላ ነቢዩ ሙሐመድ ስለመጨረሻው ፍርድ ባስተማሩ ጊዜ አንዳንዱን እንዳስተማሩ ሐዲሳቱና ቁርአን እራሱ ዘግበውት ይገኛል ለምሳሌ ሰው ከዓለም ትርፍን ፈልጎ መሄድ እንደሌለበትና ቢሔድ የሚቀበለውን ብድራት ሲያሳዩ ሱና አንናሳኢ ቅጽ ቁጥር ሳሂህ አልቡኻሪ ቅጽ ቁጥር የአላህ መልእክተኛ እንዲህ አሉ የሥራዎች ብድራት በአላማቸው ላይ ይወሰናል እናም ማንኛውም ሰው ዋጋውን የሚያገኘው አቅዶ በአላማ በሚሠራው መሠረት ነው ታዲያ ማንም ለዚህ ዓለም ትርፍ ወይም ሜስት ለማግባት የሚሰደድ የሱ ስደት ለተሰደደለት ነገር ይሆናል ኡመር የተናገረው ሐዲስ ነው ይህን የነቢዩን ቃል አምኖ የተቀበለ አዕምሮ ያለው ሰው የሐዋርያውን መልእክት መንቀፍ ቢጀምር ታማኝነቱ ይሞታል እንጂ በእውነተኞች ዘንድ ሰሟ አያገኝም ሙግት ሦስት መጽሐፍ ቅዱስና ቁርአን በአሳብም ሆነ በመልእክት ያላቸው አለመስማማት የሃይማኖት ንጽጽር ሊቆች እንደሆኑ እራሳቸውን የሚቆጥሩት የአገራችንና የውጮቹ ዳኢዎች መጽሐፍ ቅዱስ የአላህ ቃል አይደለም ብሎ ለመሟገት አዕምሮ ሊቀበላቸው የማይችላቸውን አሳቦች መያዙና የተበረዘ መሆኑ በሚሉት ስዘገዐፀሪ ህያ ጳበለዐሂ ሀበዐፀ ዘበለዐ ዐበዐሮፀ ፅሃ ለህዐዐ ዐጸክዐቨህ ዐዐህዐን ጸያዐዐ ህዐ ዕዐፀፀ ሪ« ዐክ ዐፀሀጸክዐሰ ህዐ ዐዐዐፀ ፈ መሞገቻዎች አልቆሙም ከቁርአን ጋር በአሳብም ሆነ በመልእክት የሚጋጭ መሆኑም ሌላው ተጨማሪው መሞገቻችን ነው ይላሉ ለዚህ ሙግት ከመጽሐፍ ቅዱስ ያወጧቸው ጥቅሶችም አሏቸው ሩ ኦሪት ዘፍጥረት ኦሪት ዘፀአት በእነዚህ ሁለት ጥቅሶች አላህ ከሥራው አረፈ ይሳል ማረፍ የሰው ባህሪ እንጂ ለአምላክ የሚመጥን ቃል አይደለም ሩሩ ኦሪት ዘፍጥረት በዮሴፍ ህልም ምክንያት አባቱ ያዕቆብ የቅንአት ስሜት ተፈጠረበት ነቢይ ሆኖ በልጁ እንደቀናበት መገለጹ ኦሪት ዘፀአት ሙሴ ሰው ሆኖ እያለ አላህን አየ መባሉ የሚሉትን ይጠቃቅሳሉ። ውድ አንባቢ ራሳቸውን የሃይማኖት ንጽጽር ሊቅ እንደሆኑ አድርገው የሚቆጥሩትን ወገኖች ቁርአን የአላህ ቃል አለመሆኑን እንደገና ማረጋገጫ ስለሰጡን ላመሰግናቸው እወዳለሁ ቁርአን እና መጽሐፍ ቅዱስ በአሳብና በመልእክት የሚለያዩ ከሆነ በርካታ የቁርአን አንቀጾች ከመለኮታዊ ቃልነታቸው ወጥተው ይወድቃሉ አላህንም ሐሰተኛ ያደርጉታል አላህ መቼም ቢሆን ሐሰት ከአንደበቱ አይወጣም ነቢዩ ሙሐመድና ቁርአን ግን ከአላህ የተላኩ አለመሆናቸውን ያሳያል ቁርአን ስለራሱ ተልእኮ በተመለከተ ሲናገር ሱረቱል አልብቀራ የላም ምዕራፍ ከናንተ ጋር ያለውን መጽሐፍ የሚያረጋግጥ ሆኖ ባወረድኩትም ቁርኣን እመኑ በርሱም የመጀመሪያ ከሓዲ አትሁኑ በአንቀጾቼም ጥቂትን ዋጋ አትለውጡ እኔንም ብቻ ተጠንቀቁ ገ ትሽ ከ ደዝከፐ ዜመጨመመመ ሱረቱል አሊኢምራን የኢምራን ቤተሶች ምዕራፍ ለመደናገር ማመሳከር ተሸሸሎ የቀረበ ገጽ ከርሱ በፊት ያሉትን መጻሕፍት የሚያረጋግጥ ። መጽሐፍ ቅዱስ አላህ ከሥራው አረፈም ተነፈሰም ይሳል ቁርአን ግን በሱረቱል አልቃፍ አልደከመውም ይሳል ሰርቶ መድከም የሰው ባህርይ እንጂ የአላህ አይደለም መጽሐፍ ቅዱስ የአላህ ቃል ቢሆን ኖሮ እንዲህ አይናገርም ነበር ይላሉ ሱረቱል አልቃፍ ሰማያትንና ምድርን በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ በእርግጥ ፈጠርን ድካምም ምንም አልነካንም የ መደ ሐመ ደኔ ይተ ቁርአን የአላህ ቃል እንዳልሆነ መልአኩ ገብርኤል እርሱን ወደ ነቢዩ ሙሐመድ በማድረስ ተግባር ላይ አለመሳተፉን እንዳምን ያደረጉኝ የቁርአን አንቀጾች ብዙ ናቸው ሱረቱል አልቃፍ የቃፍ ምዕራፍ ከእነዛ መካከል አንዱ ነው ቁርአን የአላህ ቃል ቢሆን ኑሮ ምንም አይነት እንከን ባልተገኘበት ነበር ሆኖም አይደለምና ከዚህ የጠራ ሊሆን አልቻለም አንዱ ማሳያ ይህ የቁርአን አንቀጽ ነው እንከኖቹን ከማሳየቴ በፊት አንቀጹ ለምን እንደወረደ ከሚተርከው ዘገባ ልጀምር ኢብን አባስ እንዲህ አለ አይሁዳውያን ወደ ነቢዩ መጡና ስለ ሰማይና ምድር አፈጣጠር ጠየቁ እርሳቸውም እንዲህ አሉ አላህ መሬትን እሁድና ሰኞ ፈጠረ ተራሮችን እና በውስጡ የያዛቸውን ማክሰኞ ፈጠረ ዛፎችን እና ውኃን ሮብ ላይ ፈጠረ ሰማይን ሐሙስ ፈጠረ አርብ ላይ ከዋክብትን ፀሐይን እና ጨረቃን ፈጠረ ሙሐመድ ሆይ እና ከዛ በኋላስ። በማለት አይሁዶች ጠየቁ እርሳቸውም እንዲህ አሉ ከዛ ራሱን በዙፋኑ ላይ አደሳደለ እነርሱም እንዲህ አሉ በትክክል ልትመልስ ይገባሃል ከዛም አረፈ የሚለውን ጨምርበት የአላህ መልእክተኛ ተናደዱ ከዛም ይህ አንቀጽ ወረደ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር በአሳብ እንደማይስማማ ያሳይልናል ተብሎ የተጠቀሰው የቁርአን አንቀጽ የወረደበት ምክንያት ደግሞ የመሠረታዊ አስተምህሮ መፋለስ ስለታየ የወረደ አለመሆኑን ያስተዋላችሁ ይመስለኛል አረፈ እና ተደላደለ በሚሉት ቃላት ጨዋታ ምክንያት የወረደ ነው ይህ ደግሞ ቁርአን የአላህ ቃል ላለመሆኑ ግልጽ ማረጋገጫ ነው ሁለት እንከኖቹን ላሳያችሁ የአላህ ቃል ቢሆን ኖሮ ለጨዋታው ትክክለኛ ምላሽ በመስጠት ይቋጨው ነበር እንጂ ድካምም ምንም አልነካንም በማለት የቃላት ጨዋታውን አይቀላቀልም ነበር ሲሠራ ደክሞት አረፈ አልተባለምና ከሥራው ደክሞት አረፈ የሚል ቃል በሙሴ በኩል እንዳላስተላለፈና እነርሱ ደክሞት ነው ያረፈው ሊሉ እንደማይችሉ ራሱ ያውቃል ተናጋሪው እውነተኛው አምላክ ቢሆን ኖሮ መጽሐፍ ቅዱስ ማረፍ የሚለውን ቃል ስንት ጊዜ እንደጠቀሰውና በዛም ምን ለማስተላለፍ እንደተጠቀመበት ያውቅ ነበር እንዲሁም ስለ ሰንበት እረፍት የተጠቀሱት ክፍሎች በአማኙ ዘንድና በመጽሐፍ ቅዱስ አስተምሕሮ በምን አግባብ ጥቅም ላይ እንደዋለ ያውቅ ነበር ስለዚህ መልሱ ይህ ሊሆን አይችልም ምናልባት አረፈ በል ሲሏቸው ነቢዩን እኔ ድካም አልነካኝም በል ያላቸው አላህ የሚችለው አረብኛ ቋንቋ ብቻ ስለሆነ ይሆናል የእውነተኛው አምላክ ቃል ቢሆን ኖሮ እርስ በእርሱ የሚሜቃረን መልእክት አያስተላልፍም ነበር ይህንን አንቀጽ ከማውረዱ በፊት ነቢዩ መካ ሳሉ ፍጥረትን በስምንት ቀናት ፈጥሮ እንደ ጨረሰ ተናግሮ ነበር መዲና ሲሔዱ ረስቶት ሳይሆን አይቀርም በስድስት ቀናት እንደፈጠረ ተናገረ ምናልባት ከ ወደ የወረደው የመጽሐፉ ሰዎች አላህ ለመፍጠር የወሰደበት ስድስት ቀናት እንደሆነ ሲናገሩ ስለሰማ ማስተካከያ አድርጎ ሊሆን ይችላል ይህንን ማረጋገጥ የምትፈልጉ ሱረቱል ፋሲላት ያለውን ማንበብ ትችላላችሁ በተጨማሪም አንቀጽ የወረደበትን ምክንያት የሚናገረውን ዘገባ መለስ ብላችሁ እዩ ስድስቱ ቀናት የሚያልቁት ሰው ሳይፈጠር ነው ቀሪዎቹ ቀናት በሰው መፈጠር ይሞላሉ ማለት ነው በዚህ በሱረቱል አልቃፍ አንቀጽ አልደከመውም ለሚለው ቃል ኢማም ኢብን ካቲር ቃታዳህ የተባሉትን ሱሃባ ዋቢ አድርገው እንዲህ ብለዋል አይሁዶች የአላህ እርግማን ይውረድባቸውና አላህ ሰማይንና ምድርን በስድስት ቀናት ፈጠረ ከዛም በሰባተኛው ቀን አረፈ አሉ ይህም ዐለህ ይዐፀፎ ሰንበት ነው ለዚህ ነው የተቀደሰ ቀን ብለው የጠሩት ከዚያም ከሁሉም በላይ ከፍ ያለው አላህ ስለ ተሳሳተው አሳባቸው ስህተታቸውን ገላጭ ቃል አወረደላቸው አሉ ይገርማል። እውነተኛ አምላክ እንዲህ ግራ አጋቢ አምላክ አይደለም በእስካሁኑ ጉዚችን ቁርአንን ሆነ መጽሐፍ ቅዱስን እንዲሁም ሕይወትም እውነትም መንገድም የሆነውን ጌታ ኢየሱስንና ነቢዩ ሙሐመድን ለመለየት የሚያስችልዎትን ትንሽ ብርሃን ያገኙ ይመስለኛል ስለዚህ ከዘላለማዊ ጥፋት ለመትረፍ አሁኑኑ ቆም ብሎ ማሰብ መጀመር ይኖርበዎታል ያለ ኢየሱስ ክርስቶስ ኖረው ዘላለማዊውን ደስታ ሊያገኙ አይችሉም አላህ እርሰዎን እንደሌሎቹ በሞት ከመውሰድ የታገሰበትን ምክንያት ደጋግሜ መናገሬን አልዘነጋሁትም ቢሆንም አሁንም ደግሜ እናገረዋለሁ የታገሰው ንስሃ እንዲገቡና በክርስቶስ ያዘጋጀልዎትን የዘላለም ሕይወት ተቀብለው ከዘለአለም ሞት እንዲተርፉለት እድል ለመስጠት አስቦ ነው ይህም ምናልባት ከተረዱለት ለእርስዎ ያለውን ጥልቅ ፍቅር ያሳያል በአጭር ቃል ያፈቅረዎታል ገነት ውስጥ ከቅዱሳኑ ጋር እርስዎንም ማየት ይናፍቃል ራሳቸውን እንደ ሃይማኖት ንጽጽር ሊቅ የቆጠሩት ወገኖች መጽሐፍ ቅዱስ አረፈ ሲል ቁርአን ድካምም ምንም አልነካንም ይላል እናም የአላህ ቃል አይደለም ላሉበት መሞገቻቸው ማብራሪያ ያቀርባሉለ አረፈ ወይም ሰርቶ ማረፍ የሰው ባህርይ መገለጫ እንጂ የአምላክ አይደለም ስለዚህ በሰው ባህርይ አላህን በመግለጡ መለኮታዊ ሊሆን አይችልም ይላሉ ድምዳሜያቸው በዚህ ላይ የተመሠረተ ከሆነ አሁንም ቁርአን የአላሀ ቃል አለመሆኑን ስላረጋገጡልን አሁንም ደግሜ ላመሰግናቸው እወዳለሁ ምክንያቱም አላህም ቁርአን ውስጥ በሰው መገለጫ ባህሪያት እራሱን ገልጺልና ሱረቱል አልበቀራ አላህ በነሱ ይሳለቅባቸዋል በጥመታቸውም ውስጥ የሚዋልሉ ሲኾኑ ያዘገያቸዋል « ጻን ሬኔ ሓ ይ ህ ፐከጩሃ ፐጪጩዜሄ ህፀ ህሺቪክ ሃዐህ ህፀቨቨሄ ህህፀ ዛዐ ሀ ጠርበ ልልከ ከበዕ ከከከ ተሳለቀ ማለት አፌዘ አላገጠ አሾፈ ቀለደ ዘበተ አሽካበበ ማለት ነው ይህ ደግሞ የሰዎችን ባህርይ በመልካም ሁኔታ የሚገልጽ አይደለም ቁርአንም ላይ የሰፈረው የሰዎቹን መልካምነት ለማሳየት ሳይሆን ዘባች ማንነታቸውን ለማሳየት የሚባል ነው ኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማእከል የአማርኛ መዝገበ ቃላት አርቲስቲክ ማተሚያ ቤት ኢአ ዩኒቨርስቲ ገጽ ታዲያ አላህ ይህንን የዘባችነት ባህርይ ከሰዎቹ ጋር ይጋራል ማለት ነውን። መጽሐፍ ቅዱስ ወይንስ ቁርአን። ሙግት አራት መጽሐፍ ቅዱስ በውስጡ ስህተቶችን መያዙ ራሳቸውን የሃይማኖት ንጽጽር ሊቅ እንደሆኑ በሚቆጥሩት ወገኖች መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል አይደለም ብሎ ለመሞገት የሚያነሱት ሌላው አሳብ መጽሐፍ ቅዱስ ስህተቶችን በውስጡ መያዙ ነው የሜል ነው ለዚህ መሞገቻቸው ከጠቀሷቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች መካከል ሁለቱ ፍ የማቴዎስ ወንጌል በዚህ ክፍል ኢየሱስ ክርስቶስ ናዝራዊ ተብሎ በነቢያት ቃል በየትኛውም ነቢይ ሳይጠራ የተባለው የትንቢት ቃል ይፈጸም ዘንድ ማለቱ ስህተት ነው ይሳሉ ሩፍ የማቴዎስ ወንጌል ይሁዳ ኢየሱስን ስለሸጠበት ሰላሳ ብር የትንቢቱ ቃል ዘካርያስ ላይ ተነግሮ እያለ ማቴዎስ ኤርምያስ ሳይ ማለቱ ሌላው ስህተት ነው ይላሉ የእነዚህ ወገኖች መጽሐፍ ቅዱስን ስህተትን ይዚል ለሚለው ሙግታቸው የጠቀሷቸውን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ስንመለከት ምላሽ የሚያገኝ ይሆናል ሆኖም ቁርአን ውስጥ ስላሉት ቁጥር ስፍር ስለሌላቸው ስህተቶች ምንይሉ ይሆን። መቼም አንድ ምላሽ እንደምትሰጡን አምናለሁ ምናልባት አንዱ መንገድ ነቢዩ ሙሐመድ በነበሩበት ዘመን የቁርአኑ አንቀጽ በሚወርድበት ጊዜ ከነበረው ሁኔታ በመነሳት ነው ማለታችሁ አይቀርም የምታውቁ ከሆነ እያንዳንዱ የቁርአን አንቀጽ የወረደው ከድርጊት በኋላ ነበር ስለዚህ የወረደው በጊዜው ድርጊቱን ይፈጽም ለነበረው ማሕበረሰብ ነበር ያም ማለት ቁርአን በተደጋጋሚ አስፈራሪ ሆኖ መላኩን እንደተናገረው የወረደው እንዲፈሩና እንዲጠነቀቁ ከነቢዩ አፍ ቃል በሚሰማው ሕዝብ የቃላት አጠቃቀም አካባቢያዊ ዘይቤ በሕዝቡ በራሱ ባህል የተለያየ እውቀትና የግንዛቤ ደረጃ መሠረት ነው ሱረቱል ዩሱፍ እኛ ፍቹን ታውቁ ዘንድ ዐረብኛ ቁርኣን ሲሆን በእርግጥ አወረድነው በተጨማሪም አላህ በሌላ ሐዲስ ሰዎች ቁርአንን እንዲረዱትና የበለጠ ግልጽ እንዲሆንላቸው በማሰብ በሰባት አይነት የዓረብኛ ዝዬዎች እንዲነበብ ትዕዛዝ መሰጠቱን ነቢዩ ሙሐመድ መናገራቸው ተዘግቧል ሳሂህ ሙስሊም ቅጽ ቁጥር ገጽ ስለዚህ የዛሬዎቹ ሙስሊም ወገኖች እነዚህን ጉዳዮች ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ቁርአንን እንዴት ሊተረጉሙ እንደሚገባቸው ያሳያል ቁርአን በሰባት የዓረብኛ ዝዬዎች እንዲነበብ የሚፈቅደው የአላህ ትዕዛዝ በከሊፋ ኡስማን ቢጣስም የቁርአንና የሐዲሳቱ አተረጓጎም ሳይንስ የሚያዘውና የመስኩም ምሁራን የሚጠቀሙበት ለተማሪዎቻቸውም የሚያስተምሩት የአተረጓጎም መንገድ ይህ ነው አለበለዚያ የአላህን ፈቃድ ማወቅና ለእርሱ በመገዛት መኖር አይቻልም እንግዲህ መጸሐፍ ቅዱስ ስህተትን መያዙ በማለት ለመሞገት የተነሱት ወገኖች ይህንን የሚያውቁ ይሆን።