Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ወንጀል የሠራ እንዲጠየቅ ማድረግ የማኀበረሰቡን ጥቅምና የግለሰቡን መብት በተቻለ መጠን በሚያስታርቅ መልኩ ሕጉ ሥራ ላይ የነበረው አሁንም ድረስ ፀንቶ ያለ ሲሆን በቅርቡ ተሻሸሎ ተግባራዊ ይሆናል ተብሎ ይጠ በቃል ይህ ነባሩ ህግ ዝርዝር ጉዳዮችን የላካተተ በመሆኑ ለሚነሱ የተለያዩ ጥያቄዎች ከህጉ ምላሽ ማግኘት ከባድ ነው ህጉ ሲሻሻል እነዚህ ክፍተቶች መሞላት አለባቸው እስከዚያው ያለውን ህግ እና አተገባበሩን እንመለከታለን የኢፌዲሪ ሕገመንግስት አንቀጽ ነፃ የተርጓሚ አገልግሎት የማግኘት መብት በአጠቃላይ በወንጀል ጉዳይ ምሥክር ሆነው በመቅረባቸው ወይም ሊቀርቡ በመቻላቸው የተነሳ ሊደርስባቸው ከሚችል ጥቃት ባሻገር በተጎጂነታቸው ራሱ ሊያጋጥማቸው የሚችል ማህበራዊ መሰናክል እንዲሁም ጥቃታቸውን በአደባባይ ለመግለፅ የሚያጋጥማቸው አእምሮአዊ ጫና አንዲሁም በፍርድ ሂደት ሊያጋጥሙዎቸው ከሚችሉና መንፈሣቸውን በማቁሰል ለዳግም ተጎጂነት ከሚዳርጓቸው ሁኔታዎችም ጥበቃ ያሻቸዋል የመወያያ ጥያቄ ከዚህ በለይ የተጠቀሱና የተጎጂዎች መብቶች ተብለው የተጠቀሱ ነጥቦች በኢትዮጵያ ሕጎች ምን ያህል የተሸፈኑ ናቸው። ኛነ ኖሮ ልዲስ አበቧ ኋ ፊዳ ር አ ጫቃ ኤዴ ፈዛ ዴኤ ደኣ ዝሣቨ በርህቅ ባየህ አበበ በጎክሰሰበት ጉላይ የተባራው የዎዶርወራ ወዝገበ በቀር በወኅ በዒያዝያ ፃገ ፆ በ ጎጻ።
ለክፍለ ትምሕርቱ የተያዘው ጊዜ ሰዓት ምዕራፍ ሁለት አጠቃላይ ዓላማዎች ሠልጣኞች በዚህ ምዕራፍ ማብቂያ ላይ የወንጀል ክሥ ወይም አቤቱታ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ የምርመራ መዝገብ በምን ዓይነት ሁኔታ መመራት እንዳለበት ይገነዘባሉ ተግባራዊም ያደርጋሉ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት በወንጀል የተጠረጠረን ሰው ሰብአዊ መብት ለማረጋገጥ ያለውን ሚና ተገንዝበው ተግባራዊ ያደርጋሉ በወንጀል የተጠረጠረ ሰው የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ከቀረበ በኋላ የሚፈጸሙ ስነ ስርዓቶችን አውቀው በሥራ ላይ ያውላለ ዋስትና ከሰብኣዊ መብት ጋር ያለውን ግንኙነት አውቀው ለተግባራዊነቱ በጽናት ይሰራሉ ዋስትና የሚፈቀድባቸው እና የሚከለከልባቸውን ምክንያቶች የተነትናሉ ክፍል አንድ መደበኛ የወንጀል ክስ ከመመስረቱ በፊት ውጤታማ የሆነ የፖሊስ የምርመራ መዝገብ አመራር በዚህ ክፍለ ትምህርት ሰልጣኞች ለክፍለ ትምህርቱ በአጋዥነት የቀረበውን ቻርት መሰረት በማድረግ ለመወያያ በቀረቡት ጥያቄዎች ላይ እንዲወያዩ ይደረጋል አሠልጣኙ ማጠቃለያ ከሰጠ በላ የክፍለ ትምህርቱ ማብቂያ ይሆናል ለክፍለ ትምሕርቱ የተያዘው ጊጌዜ ሰዓት ክፍል ሁለት በዚህ ክፍለ ትምህርት የጊዜ ቀጠሮ ላ ዋስትና በሚሉት ጉዳዮች ላይ በተዘጋጀው ማኑዋል መሠረት በአሰልጣኙ ማብራሪያ ይሠጣል በተዘጋጁ የመወያያ ጥያቄዎች ላይ ሠልጣኞች እንዲወያዩ ከተደረገ በኋላ አሠልጣኙ በሚሠጠው ማጠቃለያ የክፍለ ትምህርቱ ማብቂያ ይሆናል። ጋ ይዕፉፍ ፉምሠርም ጳጠናቃ ት የወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዓት ምን እንደሆነ ይተነትናሉ ሕገ መንግሥቱ እና የወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዓት ያላቸውን ግንኙነት አውቀው ለተግባራዊነታቸው በፅናት ይሠራሉ በሀገራችን ከወንጀል ህግ ሥነ ሥርዓት ጋር ግንኙነት ያላቸውን ህጎች ያብራራሉ የወንጀል ሥልጣን በፌዴራልና በክልል እንዴት እንደሚተገበር ተገንዝበው ለተግባር ይዘጋጃሉ በዚህ ክፍል ውስጥ ዋና ዋና ፅንሰ ሃሳቦች ምን እንደሆኑ በቅድሚያ መታወቅ ስላለባቸው እንዲብራሩ ይደረጋሉ በዚሁ መሰረት ራሱ የወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዓት ምንድነው የሜለው ይዳሰሳልሱ ከዚህ ሌላ ማንኛውም በአንድ አገር ያለ ሕግ የሕጎች ሁሉ የበላይ ከሆነ ከሕገ መንግሥት አንፃር መታየት ስላለበት የሥነ ሥርዓት ሕጉና ሕገ መንግሥቱ ያላቸው ትስስርም አብሮ እንዲታይ ይደረጋል በታዋቂው ብላክስ የሕግ መዝገበ ቃላት ትርጓሜ መሠረት የወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዓት የሚከተለው ፍቺ ተሠጥቶታል የወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዓት የወንጀል ጉዳዮች የሚመረመሩበት የሚከሰሱበት የሚዳኙበትና የሚቀጡበትን መንገዶች የሚገዙ ደንቦች ናቸው ይህም የተከሣሾችን ሕገ መንግስታዊ መብቶች ጥበቃ ያካተተ ነው ሕጎች በአጠቃላይ ከይዘታቸው አንፃር ዋና ሕጎች ህከበከፀ ዉ እና ቅፅል ሕጎች ልበቧበርከህ ህ ተብለው በሁለት ይከፈላሉ መሠረታዊ ሕጎች የሚባሉት መብት ግዴታ እና ተጠያቂነትንበከፎ የሚመለከቱ ሲሆን ቅፅል ሕጎች ደግሞ እነዚህ በሕግ ላይ የተመለከቱ መብት ግዴታና ተጠያቂነት በአግባቡ በተግባር ላይ የሚውሉበትን ሁኔታ የሚገዙ ናቸው ቅፅል ሕጎች እንደገና የሥነ ሥርዓት ሆሾርርህ እና የማስረጃ ነዘዐፀበር በመባል በሁለት ይከፈላሉ ከላይ ስለ ወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዓት ከተሰጠው ትርጓሜ ለመገንዘብ እንደሚቻለው ወንጀልን የሚያቋቁሙ መስፈርቶችን የሚደነግገው ዋናው የወንጀል ሕግን በሥራ ላይ የሚያውለው የሥነ ሥርዓት ሕጉ ነውፅ ወንጀል ተፈፀመ ከተባለ በዋነኛነት በፖሊስ ምርመራ ይጣራል በቂ ማስረጃ ከተገኘ በዐቃቤ ሕግ ክስ ይመሠረታል ከዚያም ጉዳዩ በፍቤት ታይቶ ጥፋቱ ከተረጋገጠ ተገቢው ቅጣት እንዲወሰን ይደረጋል። ተብሎ በዐህግ ና ዳኞች መወሰን አለበት በሕገ መንግሥቱ በወንጀል ሕጉ ና በወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዓት ሕጐቹ ተደንግገው የሚገኙት ሥነ ሥርዓት ነክ ድንጋጌዎች ብቻ ሣይሆኑ የወንጀል ማስረጃን ጭምር የሚመለከቱ ናቸው ማስረጃን በተመለከተ ሀገራችን የሲቪል ሎው የህግ ሥረዓትን ከሚከተሉት ሃገራት ተርታ ስለምትመደብ የኮመን ሉው የሕግ ሥርዓትን እንደሚከተሉ ሃገራት ራሱን የቻለ የማስረጃ ሕግ የላትም ከማስረጃ ጋር የተየያዙ ድንጋጌዎች በተለያዩ ሕጎች ውስጥ ተካተው ነው የሚገኙት ለማጠቃለል ከላይ ለመግለፅ እንደተሞከረው በሃገራችን ያሉት የወንጀል ሕግ ድንጋጌዎች በሁለት ዋና ዋና ክፍል ሊመደቡ ይችላሉ እነርሱም የሕገ መንግሥት መሠረት ያላቸው የወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዓት ድንጋጌዎች እና የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነ ሥርዓትን ጨምሮ በሌሎች ሕጎች ውስጥ ተካተው የሚገኙት የወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዓት ድንጋጌዎች ናቸው የመወያያ ነጥቦች የወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዓት ምንድነው ። አንዱን ሰው በሐሰት እንዲመሰክር መገፋፋት የማታለል ማጭበርበር ወንጀል እንዲሰራ ስለሚያደርግ እንዲህ ያለው ተግባር በወንጀል ሕግ ዓንቀፅ መሰረት የተከለከለና የሚያስቀጣ ነው በሐሰት እንዲመሰክር የመገፋፋት ተግባር ራሱ ወንጀል ሲሆን ይህ ወንጀል ከሁለቱ ኣንዱ ወንጀል በተፈፀመበት ስፍራ ስልጣን ባለው ፍርድ ቤት ሊሰማ እንደሚችል ይደነገግጋል የወመሕሰሰቁ ለምሳሌ በሰሜን ሸዋ ዞን ኣንድ ሰው ሌላውን በደቡብ ወሎ ዞን በሚታይ ክስ በሐሰት እንዲመሰክር ያደርገዋል ይህ ወንጀል ዓንቀፅ ን በመጣሱ በዞን ፍቤት መታየት የሚገባው በመሆኑና የወንጀል ስራው የተሰራ በሰሜን ሸዋ ዞን ሲሆን ከስራው ጋር ግንኙነት ኖሮት ወይም በስራው ምክንያት የተፈፀመው ወንጀል የተሰራው በደቡብ ወሎ ዞን በመሆኑ ኣጥፊው በሰሜን ሸዋ ዞን ፍቤት ወይም በደቡብ ወሎ ዞንፍቤት ሊከሰስ ይችላል ቀጥሎ የሚነሳ ጉዳይ ደግሞ ወንጀሉ የት እነደተፈፀመ ለማወቅ የማይቻል ሲሆንስ ክስ መሰማት ያለበት የት ነው የሚለውን ነው ለዚሀ ጥያቄም የወመሕስስቁ ሀሀ ያሰቀመጠው መፍትሄ አለ በአንቀፁ እንደተመለከተው ወንጀሉ የት እንደተፈፀመ ለማወቅ የማይቻል ሲሆን ክሱ ስልጣን ባለው በኣንድ ስፍራ በሚገኝ ፍርድ ቤት ሊሰማ እንደሚቻል ነው ለምሳሌ አንድ ሰው የወንጀል ሕግ ዓነቀፅ ን በመተላለፍ አንድ በሬ ቢሰርቅ ወንጀሉ መሰማት የሚገባው በወረዳ ፍቤት ነው ነገር ግን ተከሳሹ ከየት እንደሰረቀው ለይቶ ባያውቅና ከዳንሻ ወረዳ ወይም ከፀገዴ ወረዳ ከሁለቱ ኣንዱ መሆኑ ግን ግልፅ ቢሆን ተጠርጣሪው በዳንሻ ወይም በፀገዴ ወረዳ ፍርድ ቤት ሊከሰስ ይችላል በሌላ በኩል ደግሞ ወንጀሉ በከፊል ግማሹ በኣንድ ስፍራ ግማሹ ደግሞ በሌላ ስፍራ ሲፈፀም የወመሕስስቁ ለ ወይም ወንጀሉ በብዙ ስፍራዎች ያለማቋረጥ ሲፈፀም የወመሕስስቁሐ ወይም ወንጀሉ በልዩ ልዩ ቦታዎች በተሰሩ ልዩልዩ ተግባሮች የተፈፀመ ሲሆን ቁመ ክሱ በኣከባቢው ካሉት ስልጣን ባለው ፍርድ ቤት በማንኛውም ሊሰማ ይችላል ምሳሌ በትግራይ ክልል ውስጥ የሚገኙ የደቡብና የደቡብ ምስራቅ ዞኖች ብንወስድ አንዱ ሰው ሌላውን መጀመርያ በደቡብ ዞን ውስጥ ወሰን ኣከባቢ በጩቤ ወግቶ ጥሎ ከዚያም ወደ ደቡብ ምስራቅ ጎትቶ በመውሰድ እንደገና በጩቤ ወግቶ የግድያ ሙከራ ቢፈፅምበት ወንጀሉ በከፊል ደቡብ ዞን በከፊል ደግሞ ደቡብ ምስራቅ ዞን ውስጥ ስለተፈፀመ በደቡብ ወይም በደቡብ ምስራቅ ዞን በሚገኝ የዞን ፍቤት ሊሰማ ይችላል ምሳሌ ተከሳሹ ያለኣግባብ ኣንዱን ሰው በኣላማጣ ወረዳ ቢይዘውና መሆኒ ወረዳ ወደ ሚገኘው ፓሊስ ጣቢያ ቢወስደው የወንጀል ሕግ ዓንቀፅ በመጣስ ወንጀል ስለሚሰራና የወንጀሉ ስራ ሰውየውን ያለ ሕግ በግድ መያዙ ያለማቋረጥ ስለቀጠለ ክሱ በኣላማጣ ወይም በመሆኒ ወረዳ ፍርድ ቤት ሊታይ ይቻላል ምሳሌ ተከሳሹ በምስራቅ ሸዋ ዞን ሆኖ በምዕራብ ሸዋ ዞን ላለ ሰው የያዘው ግመል የእርሱ መሆኑን በመግለፅ የሐሰት ደብዳቤ ይፅፍለታል ቀጥሎም ወደ ምዕራብ ሸዋ ዞን ሄዶ በማታለል ግመሉን ይረከባል የሰራውም ወንጀል የወንጀል ሕግ ዓንቀፅ ይጥሳል ወንጀሉ ሁለት ክፍሎች ያሉት ሲሆን ኣንደኛው የሐሰት ደብዳቤ መፃፉ ሁለተኛው ደግም ግመሉን በዚሁ በማጭበርበሪያ ደብዳቤ መሰረት መረከቡ ናቸው ደብዳቤው የተፃፈው በምስራቅ ሸዋ ዞን ስለሆነ ክሱ በምስራቅ ሸዋ ወይም በምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሊሰማ ይቻላል በቁ መሰረት ወንጀሉ የተፈፀመው ተጠርጣሪው በጉዞ ላይ ሳለ ቢሆን ተጠርጣሪው ወይም ወንጀሉ ተየፈፀመበት ሰው ወይም ነገር በጉዞው በሚያልፍበት ስፍራ ውስጥ ክሱን ለመስማት ስልጣን ባለው ፍርድ ቤት ክሱ ይታያል ተጠርጣሪው ወንጀል የፈፀመበት ሰው ወይም ሌላ ነገር ንብረት በስፍራው ካለፈ ወንጀሉ በዛው ስፍራ ባይፈፀምም ስልጣን ያለው ፍርድ ቤት በነገሩ ሊፈርድ እንደሚችል ነው ምሳሌ በአንድ ከየካ ክፍለ ከተማ ባኣራዳና በአዲስ ክፍለ ከተማ ኣድርጎ ወደ ኮላፌ ቀራንዩ በሚሄድ ኣውቶብስ ውስጥ ኣንድ ሰው በየካ ተሳፍሮ ሌላውን መንገደኛ ተሳፍሮ ደብድቦ በዚያው በየካ ክፍለ ከተማ ቢወርድና ተበዳዩ ተደብዳቢው ደግሞ ኣራዳ ክፍለ ከተማ ቢወርድ ወንጀሉ የተፈፀመበት ሰው በጉዞው ጊዜ በኣራዳ ክፍለ ከተማ ስላለ ኣጥፊው የወንጀል ሕግ ዓንቀፅ ተላልፎ በሰራው ወንጀል በየካ ወይም በኣራዳ ምድብ ችሎት ሊከሰስ ይችላል ምሳሌ በኮምቦልቻ ወረዳ በመኪና የተጫነ የንግድ እቃ በደብረሲና ኣቋርጦ ደብረብርሃን ሲደርስ ቢሰረቅ እቃው በሶስቱም ወረዳዎች ውስጥ ስላለፈ ወንጀለኛው ከሶስቱ ወረዳ ፍርድ ቤቶች በማንኛውም ሊከሰስ ይችላል ኣንድ ወንጀል ከኢትዮጵያ ግዛት ውጭ በኢትዩጵያ መርከብ ላይ ወይም ኤሮፕላን ውስጥ ቢፈፀም ኢትዮጵያ ውስጥ እንደተፈፀመ ይቆጠራል ይላል የወመሕስስ ቁብ ይህ ቁጥር ክሱ በየትኛው የኢትዮጵያ ፍርድ ቤት መታየት እንደሚገባው ኣይገልፅም ሆኖም ቁ ከቁ እስከ የተመለከቱትን ዓይነት ወንጀሎች ሁሉ ክሱ በየትኛው ፍርድ ቤት መታየት እንዳለበት ዓቃቤ ሕጉ ሊወስን እንደሚችልና ክሱ የቀረበለት ፍርድ ቤት በጉዳዩ ላይ ስልጣን እንደሚኖረው ይገልፃል ስለዚህ ኣንድ ክስ በብዙ ፍርድ ቤቶች ሊታይ የሚችል ሲሆን በየትኛው ፍርድ ቤት መታየት እንደሚገባው ዓቃቢ ሕጉ ይወስናል ማለት ነው ለምሳሌ ኣንድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤሮፕላን በሱዳን ላይ ሲበርና በወረዳ ፍርድ ቤት መታየት የሚገባው ወንጀል በኤሮፕላኑ ውስጥ ቢፈፀም ጉዳዩ ዓቃቤ ሕግ በሚመርጠው በማንኛውም የኢትዩጵያ ወረዳ ፍርድ ቤት ሊታይ ይቻላል ይሁን እንጂ የወመሕስስቁ በአሁኑ ወቅት ተፈፃሚነት እንደሌለው መገንዘብ ያስፈልጋል ከፌዴራል ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ ኣዋጅ ቁ ዓንቀፅ መረዳት እንደሚቻለው ከኣንድ ክልል በላይ ወይም በዓለም ኣቀፍ ደረጃ ኣገልግሎት በሚሰጡ መገናኛዎች ፀጥታና ነፃነት ላይ በሚፈፀሙ ወንጀሎች የበረራ ደህንነትን በሚመለከቱ ወንጀሎች የሚታዩ በፌዴራል ፍርድ ቤቶች ስለሆነ የወመሕስስቁ ተሽሯል ማለት ይቻላል ከክልላዊ ስልጣን ጋር ተያይዞ መታየት ያለበት ነገር ቢኖር ኣንድ ክስ ካንድ ነገሩን ለማየት ስልጣን ካለው ፍርድ ቤት ወደ ሌላው ፍርድ ቤት የመዛወሩ ጉዳይ ነው የወመሕስስቁ ባለጉዳዩ ጉዳዩን በሌላ ፍርድ ቤት እንዲታይለት ሲፈልግ ማመልከቻውን ለከፍተኛ ፍርድ ቤት ማቅረብ እንዳለበት የተጠቀሰው የሕጉ ቁጥር ይደነግጋል ማመልከቻውን ከፍተኛው ፍርድ ቤት ከተቀበለው ጉዳዩ ክሱን ለማየት ስልጣን ወደ ኣለው ፍርድ ቤት ወይም ወደ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይዛወራል በዚህ አኳኃን ጉዳዩ በወረዳ ፍርድ ቤት የሚታይ ሲሆን ከፍተኛው ፍቤት ራሱ ተቀብሉ ሊሰማው ወይም ወደ ሊላ ወረዳ ፍርድ ቤት ሊያዛውረው ይችላል ይህ ዓንቀፅ ድሮ ለነበረው የፍርድ ቤቶች ኣወቃቀር ስርዓት ታሳቢ በማድረግ የተቀረፀ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት ላለውን የፌዴራል ኣወቃቀር ስርዓት እንዳለ የሚያገለግል ኣይመስልም ፍርድ ቤቶች በፌዴራልና በክልሎች ደረጃ የተዋቀሩ በሆናቸው የክስ ይዛወርልኝ ጥያቄም ይህንን ግምት ውስጥ ያስገባ መሆን አለበት ስለሆነም የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ስልጣን በሆነው ጉዳይ ላይ የክስ ይዛወርልኝ ጥያቄ የቀረበ እንደሆነ ጥያቄው መቅረብ ያለበት ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወይም ክልሎች በውክልናቸው መሰረት በሚያዩት ጉዳይ ሳይ ከሆነ ደግሞ ለክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይሆናል ማለት ነው እንዲሁም የክልል ጉዳይ ሲሆን ሁለት ሁኔታዎች ይኖራሉ ይኸውም የወረዳ ፍርድ ቤት በያዘው ጉዳይ ላይ ሲሆን ጥያቄው ለሚመለከተው ማእከላዊ ፍርድ ቤት የማእከላዊ ዞን ፍርድ ቤት በያዘው ጉዳይ ላይ ደግሞ ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሊቀርብ ይገባዋል የሚመለከተው ፍርድ ቤት ኣንድ ክስ ከአንድ ፍርድ ቤት ወደ ሌላ ለማስተላለፍ የቀረበለትን ማመልከቻ የሚቀበልበት ኣራት ሁኔታዎች እንዳሉ ቁጥር ያመለክታል እነዚህም የሚከተሉት ናቸው ሀ ዝቅተኛው ፍርድ ቤት በልዩ ልዩ ምክንያቶች ኣድልዎ የሌለበት ትክክለኛ ፍርድ ለመስጠት እንደማይችል ግልፅ ሲሆን ለ ክሱ በጣም ኣስቸጋሪና ከባድ የሆነ ለውሳኔ የሚያዳግት የሕግ ጉዳይ ሲኖርበት ሕ የክሱ መዛወር ለባለጉዳዩችና ለምስክሮች በቦታው ቅርበትም ሆነ በሌላ ምክንያት ምቹ ወይም ተፈላጊ ሲሆን እና መ በአጭር ጊዜ ትክክለኛ ፍርድ የሚገኘው በክሱ መዛወር ብቻ ሲሆን ወይም የክሱ መዛወር በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ስነ ስርዓት የተፈቀደ ሲሆን ነው ለምሳሌ በአንድ ስፍራ ኣንድ ጧሪ የሌላቸዉ የ ዓመት ኣዛውንት ሸማግሌ ከኣከባቢው ነዋሪ ህዝብ በእርዳታ ያገኙትን እህል ሰርቀሃል ተብሎ የተከሰሰ ሰው ስርቆቱ በተፈፀመበት ቀን በሌላ ቦታ ነበርኩ ነገር ግን የአከባቢው ህዝብ በሽማግሌው መሰረቅ በጣም ስለተቆጣ በሌላ ቦታ እንደነበርኩ የሚያውቁልኝ ምስክሮች የማስፈራሪያ መልእክት ስለደረሳቸው እዚህ ሊመሰክሩልኝ ኣይችሉምና ወደ ሌላ ፍርድ ቤት ይዛወርልኝ ሲል ለዞን ፍርድ ቤት ቢያመለክት ፍርድ ቤቱ ምክንያቱን ከተቀበለ ነገሩን ራሱ ሊሰማው ወይም ወደ ሌላ ፍርድ ቤት ሊያዛውርለት ይችላል ለምሳሌ አንድ ሰው የወንጀል ሕግ ዓንቀፅ በመተላለፍ ለአካለመጠን ያልደረሱ ልጆችን የግብረ ስጋ ተፈጥሮአዊ ዝንባሌ ከልክ በላይ የሚቀሰቅሱ የሚያበላሹ ወይም የሚያነሳሱ ፅሑሮችን ኣሳይቷል ተብሎ ቢከሰስ የዚህ ዓይነት ክስ የሚታየው በወረዳ ፍርድ ቤት ነው ተከሳሹ ለህዝብ ያሳየሁት ፅሑፍ በዓንቀፅ ኣተረጓጎም የግብረ ስጋ የተፈጥሮአዊ ዝንባሌ ከመጠኑ በላይ አላነሳሳም ብሎ ቢከራከር የግብረ ስጋ ተፈጥሮአዊ ዝንባሌ ከመጠኑ በላይ ማነሳሳት የሚለው ከባድ የሆነ የሕግ ክርክር ለመፍጠር ስለሚችል ተከሳሹ ቢያመለክት የዞን ፍርድ ቤት ክሱን ራሱ ለማየት ሊወስን ይችሳላል ለምሳሌ አንድ በኮምቦልቻ የተጫነ የንግድ ዕቃ የያዘ መኪና በደብሰሲና ወረዳ አልፎ በደብረብርሃን ወረዳ እንደቆመ ዕቃው ተሰርቆ ዓቃቤ ሕጉ ክሱ በደብረሲና ወረዳ እንዲታይ ቢወስንና ተከሳሹና ምስክሮቹ የሚኖሩት በደብረብርሃን ወረዳ በመሆኑ ክሱ ወደ ደብረብርሃን እንዲዛወር ማመልከቻ ቢቀርብ መዛወሩ ለተከሳሹና ለምስክሮች ምቹ ስለሚሆን የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክሱ ይዛወር ብሎ ሊያዝዝ ይችላል ክፍል አንድ መደበኛ የወንጀል ክሥ ከመመስረቱ በፊት ውጤታማ የሆነ የፖሊስ ምርመራ መዝገብ አመራር እንደሚታወቀው ስለ አንድ የወንጀል ጉዳይ ክሥ ወይም አቤቱታ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ የወንጀል ምርመራ ሥራ የቀጥላል ውጤታማ የሆነ የመጨረሻ ግብ ላይ ለመድረስ ግን አንድ ጊዜ ፖሊስ ሥራዬን ጨርሻለሁ ብሎ በወመሕሥሥቁጥር መሠረት በተዘጋጀ ራፖር የላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ ከመወሰን ባሻገር በምርመራ ሥራው ላይ ፖሊስና ዐቃቤ ሕግ በመቀናጀት መሥራት ያለባቸው ተግባራት ይኖራሉ ይህን ማድረጋቸውም በመጨረሻ ላይ ሊደረስበት የታሰበውን ግብ ውጤታማና አስተማማኝ ከማድረግ አንፃር የሚኖረው ድርሻ ከፍተኛ ነው ከዚህም በተጨማሪ በምርመራ ወቅት ፍርድ ቤቶች የጊዜ ቀጠሮን ዋስትናን ብርበራን ወዘተ በተመለከተ የሚሰጧቸው ትዕዛዛት አንድ የምርመራ ሥራን ፈር ከማስያዝ ባሻገር የዜጎችን ሰብዓዊ መብቶች ከማስከበር አንፃር ከፍተኛ ድርሻ ኖራቸዋል ከዚህ በታች የሰፈረው ቻርት በቅርቡ እየተደረገ ባለው በፌዴራል መንግስት የወንጀል ፍትሕ አስተዳደር አቤቱታን መመርመር ክሥ መመሥረት መከራከርና ውሣኔ መስጠት የሥራ ሂደት መሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ ጥናት የፖሊስ የምርመራ ሥራ አካሄድን ነባር የአሰራር ሂደት ል የሚያሳይ ነው ቻርቱን በሚገባ ከተመለከቱ በኋላ በመጨረሻ ላይ በቀረቡት የመወያያ ጥያቄዎች ላይ ተወያዩባቸው የመወያያ ጥያቄዎች በቻርቱ በተመለከተው መሠረት ዋና ዋና የምርመራ ሥራ ሂደት ተግባራት የትኞቹ ናቸው። ችሎት ፀሐፊ ፋይሉን ለችሎት ማቅረብ ዱ ፍርድ ቤት ጉዳዩን መመርመር ለተጠርጣሪው መጥሪያ በመላክ የቀጠሮውን ቀን መጠባበቅ አቀረበ አቀረበ የተፈቀደ ከሆነ የተከለከለ ከሆነ መርማሪው ቃሉን መቀበል በመዝገብ ላይ ቃሉን በማስፈር ለኃላፊ አቅርቦ ማስወሰን የዋስትና ፎርም ሞልቶ መልቀቅ እና ፎርሙን ከመዝገቡ ጋር ማያያዝ ስለ ቀጣይ አቅራረብ ለመመሪያ ማቅረብ ትዐዛዝ ተገለብጦ ዳኛ ፈርሞበት ወጭ ሆኖ ለፖሊስ መስጠት ወደ ታክቲክ ምርመራ በመፄድ ተፈላጊው እንዲያዝ ለክትትል ማስተለለፍ ብርበራ ማካፄድ ኃላፊው ተጠርጣሪው በፍቤት ትዕዛዝ የፍቤት ፋይሉ ተዘግቶ መዝገብ ቤት ማስቀመጥ እንዲያዝ ውሣኔ መስጠት ክትትል በተጠርጣሪው ላይ ማስረጃ በማሰባሰብ ፍለጋ ማድረግ ካገኘ ይዞ ለመርማሪ ማስተላለፍ በዕለት ሁኔታ እና በእስር መዝገብ ማስመዝገብ ተፈትሾ እንዲታሰር ለጥበቃ ኃላፊ ማስረከብ ፍተሻ የግል ንብረቱን መዝግቦ በመያዝ ወደ እስር ክፍል መውሰድ የጊዜ ቀጠሮ መጠየቂያ ደብዳቤ ማዘጋጀት እና ኃለፊውን አስፈርሞ ወጭ ማድረግ የሚያዝ ኤግዚቢት ካሣ በመቅድም ተመዝግቦ ለኢግዚቢት ክፍል መስጠት ኤግዚቢት ክፍል መዝግቦ ታግ በመለጠፍ ማስቀመጥ ደብዳቤውን በፍርድ ቤቱ ሬጅስትራር ማቅረብ ነ ሬጅስትራር ፋይል ከፍቶ ለችሎት ፀሐፊ መምራት ሃ ችሎት ፀሐፊው ፋይሉን ለችሎት ማቅረብ ኘ መርማሪው ተጠርጣሪውን በመያዝ ችሎት ቀርቦ ቀጠሮ እንዲፈቀድለት ማስረዳት ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን መርምሮ ውሣኔ መስጠት ጊዜ ቀጠሮ ካለተፈቀደ ስለተጠርጣሪ አቆያየት መዝገቡን ለኃላፊ ማቅረብ እና ኃላፊ በሚሠጠው ውሣኔ መሠረት መፈፀም ተጠርጣሪውን በዋስ ያለዋስ ፎርም በማስሞላት መልቀቅ በመቅድም በማስፈረም የዋስትና ፎርሙን ከመዝገብ ጋር ማያያዝ ጊዜ ቀጠሮ ከተፈቀደ ት ተጠርጣሪውን ይዞ በመመለስ ምርመራ መቀጠል ኘ የዕምነት ቃል ማስጠት የሚያስፈልግ ከሆነ ዳብዳቤ አዘጋጅቶ ወደ ፍርድ ቤት መሄድ ን ደብዳቤውን ለፍርድ ቤቱ ሬጅስትራር ማቅረብ ሬጅስትራር ፋይል አስከፍቶ ለችሎት ፀሔፊ መምራ ኘ ችሎት ፀሐፊው ፋይሉን ለችሎት ማቅረብ ኘ ዳኛው የዕፅመነት ቃሉን ለመቤት ማስተላለፍ ዐቃቤ ሕግ የዕምነት ቃል ከፍርድ ቤት በመውሰድ ከሌሎች ማስረጃበዎች ጋር ለሚመለከተው ፍርድ ቤት ማዕረብ ወደፊት ነ መርማሪያው የዕምነት ቃል መቁጥሩን በምርመራ መቅድም ማስፈር መርማሪው የተጠርጣሪውን የጣት አሻራ ሪከርድ አስደርጎ ምርመራ መዝገቡን ማጠናቀቅ መዝገቡን ለኃላፊው አቅርቦ ማስወሰን ኛ መዝገቡ ለዐቃቤ ሕግ ይላክ ከተባለ ዋና እና ቀሪ መዝገብ ለይቶ መሸኛ አዘጋጅቶ በማስፈረመ ለመቤት መስጠት መመሪያ ከተሰጠ በመመሪያው መሠረት ለማሟላት ለኃላፊው ማቅረብ ቤት ሠራተኛ በማስፈረም ማስረከብ ዥ ምርመራ መዝገቡን ወደ ዐቃቤ ሕግ መላኪያ መዝገብ ላይ መመዝገብ የተጠቀቀ የምርመራ መዝገብ ለዐቃቤ ሕግ መሥሪያ ቤት አንዲሰጥ ለመዝገብ መዝገቡን ቆጥሮ በማስፈረም ለዐቃቤ ሕግ መቤት ማስረከብ ክፍል ሁለት የጊዜ ቀጠሮና ዋስትናን የሚመለከቱ ችግሮች የጊዜ ቀጠሮ የሚጠበቁ ውጤቶች ይሀ ዑዕ ፍሳ ጠናፇቋ ሪዕጂማዎቻ ሁ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት በወንጀል የተጠረጠረን ሰው ሰብአዊ መብት ለማረጋገጥ ያለውን ሚና ተገንዝበው ተግባራዊ ያደርጋሉ ሁ በወንጀል የተጠረጠረ ሰው የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ከቀረበ በኋላ የሚፈጸመ ስነ ስርዓቶችን አውቀው በሥራ ላይ ያውላሉ በወንጀል የተጠረጠረ ሰው በፖሊስ ከተያዘ በኋለ ፍቤት መቅረብ ያለበት ሲሆን የዚህን አሰራር ጠቀሜታና ተጠርቶ ፍቤት ከቀረበ በኋላ የሚፈጸሙ ስነስርዓቶችን እንመለከታለን ፖሊስ ከወንጀል ጉዳይ ጋር በተያያዘ ዜጉችን ያለአግባብ በመያዝ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተግባር እንዳይፈጽሙ ለመከላከል ሐገራት በህግ ከሚያደርጉት ጥበቃ አንዱ በህገ መንግስት መሰረት የተያዘ ሰው ፍቤት በህግ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ እንዲቀርቡ ማድረግ ነው በሀገራችንም ይህ መብት በ ሕገ መንግሥስቱ አንቀፅ እና በወመህሥሥቁ መሰረት በወንጀል ተጠርጥረው ለተያዙ ሰዎች የተረጋገጠ መብት ነው ተጠርጣሪው ከተያዘ በኋላ ፍቤት ወዲያውኑ እንዲቀርብ የሚያስፈልገው የእስሩን ህጋዊነት ለማረጋገጥ ነው ተጠርጣሪው እንደቀረበ ፍቤቱ ማንነቱን አረጋግጦ ከመዘገበ በኋላ በምን ዓይነት ወንጀል ተጠርጥሮ እንደተያዘ ለተጠርጣሪው ሊገለፅለት ይገባል ከዚህ በኋላ ፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ የሚጠይቅ መሆኑን ፍቤቱ አረጋግጦ ተጨማሪ ጊዜ የሚጠይቅ ከሆነ ምክንያቱን ከፖሊስ ማጣራት አለበት የተጠርጣሪውም ሐሳብ መሰማት አለበት ተጨማሪ ጊዜ የሚፈቀድበት በቂ ምክንያት ከሌለ እና የተጠረጠረበት ወንጀል ዋስትና የማያስነፍግ ከሆነ ተጠርጣሪው በዋስትና እንዲለቀቅ ፍቤቱ ማዘዝ አለበት የጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ፖሊስ ያቀረበው ተጨማሪ ምርመራ የማጣሪያ ጊዜ ላይ ትእዛዝ ከመስጠቱ በፊት የተጀመረ የፖሊስ ምርመራ የደረሰበትን ደረጃ ለማወቅ የቀረውን ምርመራ ለማጠናቀቅ ተጠርጣሪው በእሰር ላይ መቆየት አስፈላጊነት እና የሚያስፈልገውን ተጨማሪ ጊዚ ለማረጋገጥ ፖሊሱን በመጠየቅ እና እንደአሰፈላጊነቱ የፖሊስ ምርመራ መዝገብን በመመልከት ማጣራት ይጠበቅበታል የተጠርጣሪው የመደመጥ መብትን ምንጊዜም ቢሆን መዘንጋት የለበትም በተግባር ጥያቄ የሚያስነሣው የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ስልጣን ወሰን ነው ችሎቱ ተጠርጣሪው ያለ አግባብ የተያዘ መሆኑን ቢያረጋግጥ ያለ ዋስትና ሊለቅው ይችላል ወይ። የሚለው ያከራክራል በህጉ ላይ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ከመፍቀድ እና በዋስትና ከማሰናበት ውጪ የተቀመጠ ሌላ ኛ አማራጭ የለም ከዚህ አንጻር ችሎቱ ተጠርጣሪውን በዋስትና ብቻ ነው መልቀቅ ያለበት ሊባል የችላል ነገር ግን በስህተት መያዙን ፖሊስ ጭምር እያረጋገጠ ዋሰትና አቅርብ ማለት ትርጉም የለውም ዋስትና እራሱን በቻለ የተለየ ክፍል በቀጣይነት የሚስተናገድ ይሆናል ከጊዜ ቀጠሮ ችሎት ሥልጣን ጋር በተያያዘ ሌላ ሊነሣ የሚገባው ነጥብ ፖሊስ ምርመራውን ያለበቂ ምክንያት ባያጠናቅቅ ወይም ዓሀግ የምርመራ መዝገቡ ደርሶት በወቅቱ ውሣኔ ሣይሰጥበት ቢቀር እና ተጠርጣሪው የተጠረጠረበትን የወንጀል ጉዳይ ዋስትና የሚያስነፍግ ቢሆን የሚፈጠር ሁኔታ ነው የጊዜ ቀጠሮ መዝገብ ተጠርጣሪው እንዲለቀቅ ወይም በእስር እንዲቆይ ትእዛዝ ሣይሰጥ የመዝጋት አሰራሩን የሚከተሉ ዳኞች ያጋጥማሉ በዚህን ጊዜ ፖሊስ ተጠርጣሪውን የመልቀቅ ወይም ያለመልቀቅ ችግር ውስጥ ይገባል ተጠርጣሪው ህግን የሚያውቅ ወይም ጠበቃ ካለው ያለው አማራጭ አካልን ነጻ የማውጣት ክስ ከ ርዐዌህለፍብሔር ችሎት ማቅረብ ነው ይህ ዓይነቱ አሰራር ሊገመት ለማይችል ሁኔታ ተጠርጣሪውን የሚያጋልጥ ነው ተጠርጣሪው ለረጅም ጊዜ በእሥር ላይ ሆኖ ሊንገላታ የሚችልበትን በር ይከፍታል ከዚህ የተሻለው አማራጭ ለሚመለከተው ዓህግ ኃላፊ ፍቤቱ በትእዛዝ ለማሣወቅ ወይም በማስጠራት መፍትሔ እንዲገኝ ማድረግ ነው በዚህም መንገድ ውጤት ካልተገኘ እስከ መጨረሻ ዓህግ ኃላፊ ድረስ ሁኔታው እንዲታወቅ በማድረግ ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ መደረግ አለበት በሂደት ውስጥ የሥራ ግዴታውን የጣሰ ካለ ለሚመለከተው አካል በማሣወቅ ተጠያቂነት እንዲኖር ማስደረግ ይቻላል ፍቤቱ ተገቢ ነው ብሎ ያመነበት እንደነገሩ ሁኔታ ትእዛዝ መስጠት አለበት እንጂ የዜጎችን ሰብዓዊ መብት አደጋ ላይ በሚጥል ሁኔታ ጉዳዩን አንጠልጥሎ መተው የህግ የበላይነትን ጥያቄ ውስጥ እንዲገባ የሚያደርግ ነው የሚሆነው ፍቤት ምን ያህል ጊዜ የጊዜ ቀጠሮ ሊፈቅድ እንደሚችልም በህጉ ላይ በግልጽ ያልተመለከተ ቢሆንም ያለበቂ ምክንያት ተጨማሪ ጊዜ ሊፈቅድ አይገባም የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳይኖር የጊዜ ቀጠሮ ችሎት በጥንቃቄ እያንዳንዱን ጉዳይ እያጣራ መፍቀድ አለበት በአግባቡ ይህ ከተተገበረ የጊዜ ገደብ ማስቀመጥ አያስፈልግም የጊዜ ገደብ ማስቀመጥ ለሰብዓዊ መብት ጥበቃ ጠቀሜታ ቢኖረውም የራሱ የሆነ ችግር ሊያስከትል ይችላል ለምሳሌ ተጠርጣሪው ከህግ ውጪ ከሌሎች የወንጀል ተሳታፊዎች ጋር በመሆን ሴትን ጠልፎ የደበቀ ቢሆን እና የተጠለፈችው እንዳትለቀቅ የተያዘው ተጠርጣሪ ለመተባበር ባይፈልግ ወይም የተለዩ የተወሳሰቡ ጉይዮች ቢየጋጥሙ እና ምርመራው በህግ የተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ውስጥ ለማጠናቀቅ ባይቻል ሊፈጠር የሚችለውን አስቸጋሪ ሁኔታ አስቀድሞ ማሰብ ያስፈልጋል ቀን ተጨማሪ ምርመራ የማጣሪያ ጊዜ የእረፍት ና የበዓል ቀናትን ያካትታል ወይ። የሚል ጥያቄ በተጨማሪነት ከጊዜ ቀጠሮ አፈቃቀድ ጋር ተያያዞ ይነሣል የዋስትና ጉዳይ እራሱን ችሎ በቀጣይነት የሚታይ ቢሆንም ከጊዜ ቀጠሮ ችሎት ጋር ተያይዞ ሣይነሣ መታለፍ የሌለበት አንድ ነጥብ አለ ዋስትና በጊዜ ቀጠሮ እና በመደበኛ ሁኔታ ክስ በዓህግ ከቀረበ በኋላ ታይቶ የሚፈቀድበት አሰራር አለ ተጠርጣሪው ከመደበኛ ክስ ከተመሰረተበት በኋላ ባይቀርብ የጊዜ ቀጠሮ በተገባው ዋስትና መሰረት ተከሣሹን እንዴት ማስቀረብ እንደሚቻል በህጉ ላይ የተመለከተ ነገር የለም ተከሣሹ ከጠፋበት በጊዜ ቀጠሮ ላይ ዋስትናው የሰው ቢሆንና ዋሱ ሊያቀርበው ባይችል የዋስትናው ገንዘብ ገቢ እንደሆን መታዘዝ ያለበት በጊዜ ቀጠሮው መዝገብ ላይ ነው ወይስ በመደበኛው መዝገብ ላይ ማነው ጥያቄውን አቅርቦ ማስወሰን ያለበት ዓህግ ወይስ ፖሊስ ህጉ ምላሽ የለውም ከላይ የተጠቀሱት ችግሮች መቅረፍ የተዘጋጀው የወንጀል ሥነ ሥርዓት ህግ ረቂቅ አሁን ካለው ህግ መሰረታዊ ልዩነት የሌለውና የህጉን ችግሮች የማይቀረፍ በመሆኑ ይበልጥ ትኩረት ተሰጥቶ ተሻሽሎ ሊያሰራ በሚችል መልኩ መፅደቅ አለበት በረቂቁ ላይ ለጊዜ ቀጠሮ የጊዜ ገደብ ወር ተብሎ የተቀመጠ ሲሆን ይህ ከላይ በተገለጹት ምክንያቶች ችግር ሊፈጥር ስለሚችል ሊታሰብበት ይገባል የጊዜ ገደቡ ባይከበርስ ምን ውጤት ይኖረዋል የሚለው ምላሽ ያገኘ ባለመሆኑም እንደገና ሊፈተሽ ይገባል በመሆኑም አሁን ያለው ህግ ና ረቂቅ ህግ ያለባቸው ችግሮች በሚገባ ተጠንቶ የወንጀል ህግ ሥነ ሥርዓት ፀድቆ በስራ ላይ መዋል አለበት የመወያያ ነጥቦች የጊዜ ቀጠሮ ችሎት በፖሊስ በወንጀል ተጠርጥሮ የተየዘ ሰው እንደቀረበ ለተጨማሪ ጊዜ ተጠርጣሪው በማረፊያ ቤት እንዲቆይ ከማዘዙ በፊት ወይም በዋስትና እንዲለቀቅ ከማድረጉ በፊት ምን ማድረግ አለበት። በዚህ ጊዜ የታሰረውን ተጠርጣሪ ፖሊስ የዋስትና ወረቀት አስፈርሞ ካልለቀቀው ቁ ተጠርጣሪው የዋስ መብቱ እንዲጠበቅለት ለፍቤት ማመልከት ይችላል ቁ የሕገ መንግሥታችን አንቀጽ የተያዘ ሰው በ ሰዓት ውስጥ ፍቤት መቅረብ እንዳለበት እና ለመታሠር የሚያበቃ ምክንያት ያለ መሆኑ ሊገለጽለት እንደሚገባ ይደነግጋል የወሕሥሥቁ ም ተመሳሳይ ድንጋጌ አለው በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ፍቤት ያልቀረበ ተጠርጣሪ ፍቤት የአካል ነፃነቱን አእንዲያስከብርለት ሊጠይቅ ይችላል ሕገ መንግሥት አንቀጽ ከዚህም በተጨማሪ የሕገ መንግሥት አንቀጽ የተያዘ ሰው በዋስ የመለቀቅ መብት እንዳለው ያሳያል ይህ በመርህ ደረጃ የተቀመጠ በዋስ የመፈታት መብት ከሕገ መንግሥቱ አንቀጽ ጋር ተገናዝቦ ካልታየ የተሳሳተ ድምዳሜ ሊያደርስ ይችላል ምክንያቱም በዋስ የመፈታት መብት በሕግ በተቀመጡ ምክንያቶች ሊገደብ ይችላልና ነው የወንጀል ተጠርጣሪ ስለሚያዝበት ሁኔታ በመርህ ደረጃ አንድ ሰው ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሊያዝ ወይም ሊታሰር አይችልም የወሕሥሥቁ ኹ ይህ መርህ በሕገ መንግሥታችን አንቀጽ ላይ በግልጽ ተቀምጧል ነገር ግን በሕገ መንግሥቱም እንደተጠቀሰው ያለፍርድ ቤት ትፅዛዝ ተጠርጣሪን ለመያዝ ሕግ በፈቀደ ጊዜ መያዝ ይቻላል ማንኛውም ሰው ወይም ፖሊስ ከ ወር በማያንስ ቅጣት የሚያስቀጣ ወንጀል ሲፈፀም የተገኘን ሰው አጅ ከፍንጅ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ መያዝ ይችላል በወሕሥሥቁ መሰረት ደግሞ ፖሊስ ከአንድ ዓመት የማያንስ ቅጣት የሚያስቀጣ ወንጀል ለመሥራት የተዘጋጀን ሰው ስርቷል ተብሎ በሚገባ የተጠረጠረን ሰው የሕዝብን ፀጥታ በማበላሸት ላይ የሚገኝን ሰው ፖሊስ ሥራውን በሚሠራበት ወቅት የሚከላከለውን ሰው ለማምለጥ የሞከረን እስረኛ ከፖሊስ ወይም ከወታደርነት የከዳን ሰው ሕግ ያልፈቀደለትን የቤት መሠርሠሪያ ይዞ የተገኘን ሰው የተሰረቀ ፅቃ የያዘ ሰው ወይም ወንጀል በመፈፀም ረገድ ያገኘው ዕቃ በይዞታው የተገኘበት ሰው አደገኛ ሥራ ፈት መሆኑ የተጠረጠረን ሰው ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ መያዝ ይችላል የወሕሥሥቁ ሌሎች በሕግ ሥልጣን የተስጣቸው አካላት ለምሣሌ የፀረ ሙስና ኮሚሽን ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ አንድን ተጠርጣሪ መያዝ ይችላሉ ፖሊስም ሆነ ሌሎች ተጠርጣሪን ያለ ፍቤት ትዕዛዝ ለመያዝ ሥልጣን የተሰጣቸው አካላት ተጠርጣሪውን በ ሰዓት ውስጥ ፍቤት የማቅረብ ግዴታ ግን አለባቸው የፀረ ሙስና አዋጅ ቁ አንቀጽ ከ ሰዓት በላይ ለማዘግየት የሚቻለው ተጠርጣሪውን በአቅራቢያው ወደ ሚገኝ ፍቤት ለማቅረብ የቦታ ርቀትና የመገናኛ ሁኔታ ከገደቡ ብቻ ነው የህገ መንግስቱ አንቀጽ የወሕሥሥቁ የዋስትና ወረቀት አስፈርሞ ስለመልቀቅ ከላይ እንደተገለፀው ፖሊስ የያዘውን ተጠርጣሪ በዋስ ሊለቀው ይችላል ይህን ለማድረግ ወንጀሉ በጽኑ እሥራት የማያስቀጣ ሊሆን ወይም ደግሞ ተጠርጣሪው ወንጀሉን ለመፈፀሙ አጠራጣሪ ሆኖ መገኘት ይኖርበታል የወሕሥሥቁ ፖሊስ በወንጀል ጠርጥሮ በመያዝ ለፍቤት ያቀረበውን ተጠርጣሪ ፍቤቱ በዋስትና ወረቀት ሊለቀው ይችላል ሥፊ ይህን የሚያደርገው ተጠርጣሪው የተከሰሰበት ወንጀል የዋስትና መብት የማያስከለክለው ምርመራ እየተካፄደበት ከሆነ መለቀቁ በማስረጃ ማሰባሰቡ ሂደት ላይ እንቅፋት የማይፈጥር ቢለቀቅ ግዴታውን አክብሮ የሚቀርብ መሆኑን መለቀቁ ለሕዝብ ፀጥታና ሠላም አስጊ አለመሆኑና ሌላ ወንጀል የማይፈጽም መሆኑን በማገናዘብ ሊሆን ይገባል የወሕሥሥቁ የተያዘ ሰው የተከሰሰበት ወንጀል የሞት ቅጣትን ወይም ዓመት ወይም በላይ የሆነ ጽኑ እሥራት የማያስቀጣው ከሆነና ወንጀል የተፈፀመበት ሰው በደረሰበት ጉዳት የማይሞት የሆነ እንደሆነ ፍቤት የዋስትና ወረቀት አስፈርሞ ሊለቀው አንደሚችል ይደነግጋል በዋስትና ለመለቀቅ በሚቀርብ ማመልከቻ ላይ ፍቤት ቶሎ ውሣኔ መሰጠት እንዳለበት የሚደነግገው ደግሞ የወህሥሥቁ ነው በዚህ ሕግ መሠረት ፍቤቱ ማመልከቻው በደረሰው ሰዓት ውስጥ ውሣኔ መስጠት ያለበት መሆኑን የሚደነግግ ሲሆን ከውሣኔው በፊት የዓሕጉን ወይም የመርማሪውን ሃሳብና ትችት እንደሚጠይቅ ያስቀምጣል በተለያዩ ምክንያቶች ግን ይህ ሕግ ብዙ ጊዜ ሲተገበር አይታይም በዋስትና ማመልከቻው ላይ ፃሳብ እንዲሰጥ የሚጠየቅ ዓሕግ የምርመራ መዝገቡ በእጄ ስለሌለ የምርመራ መዝገቡን ከፖሊስ ወስጄና ተመልክቼ አስተያየቴን ለማቅረብ ጊዜ ያስፈልገኛል ይላል ፍቤቱም ማመልከቻውን ከዓሕግ አስተያየትና ከምርመራ መዝገቡ ጋር መርምሮ በተሰጠው የ ሰዓት ጊዜ ውስጥ ውሣኔ ለመስጠት በተግባር ችግር አለ ይላል የዋስትና ጉዳዮችን ለብቻው የሚያዩ ችሎቶች ባለመኖራቸው ዳኞች የጊዜ ገደቡን አክብረው ውሣኔ ለመስጠት ሲቸገሩ ይታያል የዋስትና መብት ጥያቄ መሠረታዊ ከመሆኑ አንፃር ሕጉ ሊተገበር ይገባል ክስ ለፍቤት በቀረበበት ጉዳይ ከሆነ ዓሕግ የምርመራ መዝገቡን አይቶ ክስ የሚያዘጋጅ እንደመሆኑ ከሕጉ ከተቀመጠው ጊዜ በላይ ጉዳዩን የሚያራዝም የተጨማሪ ጊዜ ሊጠይቅና ሊፈቀድለት የሚገባ አይደለም ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ውስብስብ ሁኔታዎች ሊያጋጥሙ ስለሚችሉ ዳኛችና ዓሕጐች ፍትህ እንዳይጓደል በጥንቃቄ ሊሰሩ ይገባል ክስ በፍቤት ያልተመሠረተበት ጉዳይ ከሆነም መርማሪው ምርመራ መዝገቡ በእጁ ያለ የነበረ አንደመሆኑ ወዲያውኑ አስተያየቱን ለመስጠት ይቸገራል ሊባል አይችልም ፍቤቶችም ቢሆኑ የዋስትና ማመልከቻ ከሌሎች ጉዳዮች በተለየ ሁኔታ በአጭር ጊዜ እንዲወስኑ ሕግ የሚጠይቅ በመሆኑ ቅድሚያ ሰጥተው ሊወስኑ ይገባል ሌላው በዋስትና ዙሪያ ትኩረት የሚሻው በወሕሥሥቁ ሥር የተደነገገው ነው በዚህ ሕግ መሠረት ዋስትና የጠየቀን ተጠርጣሪ ማመልከቻ መቀበል የማይቻለው ሀ በዋስትና ወረቀቱ የተመለከቱትን ግዴታዎች የማይፈፀም ነው ተብሎ ሲገመት ለ ሌላ ወንጀል ይፈጽም ይሆናል ተብሉ የሚገመት ሲሆን ሐ ማስረጃ ሊያጠፋ ይችላል ተብሎ ሲታሰብ ነው ተጠርጣሪው የተከሰሰበት ወንጀል ዋስትና የማይከለከል ቢሆንም ከላይ የተጠቀሱትን የማያሟላ ተጠርጣሪ የዋስ መብቱን ሊያጣ ይችላል በዋስትና ወረቀት የሚገለፀው ዋነኛው ግዴታ በቀጠሮ ቀን ያለመቅረት ነው ተከሳሹ ተመልሶ ወደ ፍቤት የማይመጣ ነው ተብሎ ከተገመተ አይለቀቅም ህብረተሰብን በተጠርጣሪው ሊፈፀም ይችላል ከሚባል ተጨማሪ ወንጀል ለመጠበቅ ሲባልም ዋስትና ሊከለከል ይችላል ሌላው ተጠርጣሪው ከዓሕግ ማስረጃዎች ጋር ካለው ቀረቤታም ይሁን በሌላ ምክንያት ማስረጃ ያጠፋል ምስክሮች ሊያባብል ይችላል የሚል ግምት ካለም የዋስትና መብቱ ተጠቃሚ ላይሆን ይችላል ማለት ነው በዚህ የሕግ አንቀጽ ሥር ከ ሀሐ የተጠቀሱትን ሁኔታዎች ለመቀበል ሕጉ ጥያቄው የቀረበለት ፍቤት ግምት ብቻ በቂ መሆኑን ያሳያል ግዴታዎቹን የሚፈጽም የማይመስል የሚለው ሐረግ ግምትን ያመለክታል ይህ ማለት ግን ፍቤት ከተባለው ግምት ላይ ለመድረስ ምንም መነሻ ሳይኖረው በዘፈቀደ የሚወሰነው ነው ማለት አይደለም ለምሣሌ ያህል አንድ ተጠርጣሪ የዋስ መብቱ እንዲከበርለት ለፍቤቱ ሲያመለክት ዓሕጉ ወይም መርማሪው ተጠርጣሪው ተደብቆ ከሀገር ሊወጣ ሲል መያዙን ቢያረጋግጥና በዋስትና መለቀቁን ቢቃወም ፍቤቱ ይህ ተጠርጣሪተከሳሽ ቢለቀቅ አይመለስም ብሎ ለመገመት በቂ መነሻ ምክንያት አለው ማለት ይቻል ይሆናል አንዳንድ ጊዜ ተከሳሹ ዋስትና የተነፈገበት ምክንያት ከተለወጠ በኋላም ያላግባብ የሚታሰርበት አጋጣሚ አለ በወሕሥሥቁ ሐ ሥር ማስረጃ ያጠፋል ምስክር ያባብላል ተብሎ የታሰረ ተከሳሽ ማስረጃዎቹ ተሰብስበው ካለቁ በኋላ አሥሩ ሊቀጥል የሚገባበት ምክንያት የለም ተጠርጣሪ ተከሳሽ ያቀረበው በዋስ የመለቀቅ ማመልከቻ ተቀባይነት ካገኘ ተከሳሹ ዋስ እንዲጠራ ወይም ገንዘብ አንዲያስይዝ ይታዘዛል የወሕሥሥቁ ነገር ግን የዋስትና ልክን በመወሰን ረገድ ለተመሳሳይ ጉዳዮች በተለያዩ ችሎቶችዳኞች ዘንድ ያለው ልዩነት ከፍተኛ ነው ብዙ ጊዜ እንደአብነት የሚጠቀሰው በቀድሞው የወመሕቁ ሥር በቸልተኝነት ሰው መግደል ለሚከሰሱ ሰዎች የሚጠየቀው የዋስትና ገንዘብ መጠን ነው አንዱ ችሎት ከብር ዐዐ የማይበልጥ ዋስትና ሲጠይቅ በተመሳሳይ ጉዳይ ሌላ ችሎት ብር ሺ ሲጠይቅ ማየት በጣም የተለመደ ነበር በወሕሥሥሥቁ ሥር ፍቤት የዋስትና ገንዘብ መጠንን በመሰለው እንደሚወስን ቢደነገግም የወንጀሉን ከባድነት ተከሳሹ ከቀጠሮ የማይቀር መሆኑን የተከሳሹንና የዋሱን ሀብት መጠን ሲለቀቅ ያለውን አደጋ በህዝብ ፀጥታ ላይ ማገናዘብ እንደሚገባም ሠፍሯራል ለአንድ ተከሳሽ የዋስትና ወረቀት ፈርሞ ዋስ የሆነ ሰው ተከሳሹ በየቀጠሮው ፍርድ ቤት እንዲቀርብ የማድረግ ግዴታና ኃላፊነት አለበት የዋስትና ግዴታ የሚገባ ሰው ይህ ግዴታው ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይ በፍርድ ቤት ይወሰናል ይህ በሥነ ሥርዓት ሕጉ የሠፈረ ቢሆንም ቁ ብዙ ጊዜ ፍርድ ቤቶች ሲጠቀሙበት አይታይም የዋስትና ወረቀት ፈርሞ ግዴታ የገባ ሰው ፍርድ ቤት ግዴታው የሚቆይበትን ጊዜ ካልወሰነ ጉዳዩ ፅልባት እስኪያገኝ ድረስ ይቆያል ነገር ግን ተጠርጣሪ ተከሳሽ በዋስ ከተለቀቀ በኋላ እንደገና ከተያዘ ወይም ዋሱ የዋስትና ግዴታውን ፍርድ ቤት ቀርቦ ካወረደ ጉዳዩ ከማለቁ በፊትም ግዴታው ቀሪ ሊሆን ይችላል በወሕሥሥቁ መሠረት የዋስትናው ግዴታ የሚቆይበትን ጊዜ የመወሰን ልምድ ባለመኖሩ አንዳንዴ ችግር ሊከሰት ይችላል ይህን ለማሳየት በሽግግሩ ዘመን የተፈጠረን ሁኔታ መጥቀሱ ጠቃሚ ነው በአዋጅ ቁ የተቋቋመው የልዩ ዓሕግ ጽቤት በሥልጣኑ ሥር የሚወድቁ የወንጀል ጉዳዮችን በሚመረምርበት ወቅት በወንጀል የሚጠረጠሩ ሰዎችን የመያዝ ሥልጣን ተሰጥቶታል በዚህ ሁኔታ የታሰሩ ሰዎች በፍርድ ቤት የአካል ነፃ ማውጣት አቤቱታዎችን ሲያቀርቡ ዓሕጉ ግለሰቦቹ የማይፈቱበትን ምክንያት ካላስረዳ ፍቤቶች በዋስ በርካታ ሰዎች እንዲፈቱ አድርገዋል ከእነዚህ ሰዎች ውስጥ ቁጥራቸው ቀላል ያልነበሩ ዓሕግ ክስ ሳይመሰረትባቸው ለዓመታት የቆዩ ወይም ጭራሹንም ክስ ያልተመሰረተባቸው ናቸው ለእነዚህ ሰዎች የዋስትና ወረቀት ፈርመው ግዴታ የገቡ ዋሶች የዋስትና ግዴታቸው የሚቆይበት ጊዜ ባለመወሰኑ በተለይ ንብረታቸውን ለዋስትናው ያስያዙ ሰዎች ዋስ ከሆነ ከዓመታት በኋላ እንኳን ንብረታቸውን ለመሸጥ ወይም በሌላ ሁኔታ ለማስተላለፍ የተቸገሩበት ሁኔታ ነበር ስለሆነም ፍቤት በተለይ ከክስ በፊት የዋስ መብታቸውን ለሚጠብቅላቸው ተጠርጣሪዎች የዋሶቹን የግዴታ ጊዜ በመወሰን የዋሶቹ የግዴታ ጊዜ ያላግባብ እንዳይራዘም ስለሚያደርግ የወንጀሉን ከባድነትና ነባራዊውን ሁኔታ በማገናዘብ ሕጉን መተግበሩ ጠቃሚ ነው የዋስትና ማመልከቻው ተቀባይነት ያላገኘ ተጠርጣሪ ለይግባኝ ሰሚ ፍቤት በሀያ ቀናት ውስጥ ይግባኝ ማመልከቻውን ማቅረብ እንደሚችል የተደነገገ ሲሆን በቁ ይህን አንቀጽ አስመልክቶ የሚነሳው ጥያቄ ይግባኝ ለማለት የተፈቀደው ለተከሳሽ ተጠሪጣሪ ብቻ ነው ወይ። ክፍል ሦሥት በዐቃቤ ሕግ የሚሰጡ ትዕዛዛትና ውሣኔዎች ዐቃቤ ሕግ የፖሊስ ምርመራ መዝገብ ተፈፀመ በተባለ ወንጀል ላይ ከተጣራ በኋላ ቢደርሰውም የወንጀል ክስ ለፍቤት ከማቅረቡ በፊት ሕጉ ክስ ማቅረብን የሚከለክልባቸውን ሁኔታዎች መኖራቸውን በሚገባ ሣያጣራ ክስ ማዘጋጀት ና ለፍቤት ማቅረብ የለበትም ክስ ማቅረብ የመጨረሻ አማራጭ ነው መሆን ያለበት ዐቃቤ ሕግ የፖሊስ የምርመራ መዝገብ እንደደረሰው በበቂ ሁኔታ ያልተጣሩ ነገሮች ካጋጠሙት መዝገቡን መልሶ ለተጨማሪ ምርመራ በወመሕሥሥቁሕ መሠረት መመለስ አለበት ክስ ለማቅረብ የሚያጠራጥር ነገር ካጋጠመ የበላይ ዐቃቤ ሕግ መመሪያ እንዲሰጥበት በወመሕሥሥቁ መሠረትም መተላለፍ አለበት በወመሕሥሥቁ ሥር የተመለከቱት ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ በዐቃቤ ሕግ የፖሊስ የምርመራ መዝገብን መዝጋት አለበት እነዚህም ክስተቶች የተከሣሹ መሞት የዕድሜው ከዘጠኝ ዓመት በታች መሆን በዓለም አቀፍ ሕግ የዲኘሎማቲክ ከለላ መኖር እና በልዩ ሕግ መብት የተሰጠው መሆን ናቸው በዐቃቤ ሕግ ክስ ማቅረብ የማይቻልባቸው ሌሉች ምክንያቶች በወመሕሥሥቁ ሥር ተዘርዝረዋል ጥፋተኛ ለማድረግ በቂ ማስረጃ ከሌለ ክስ መቅረብ የለበትም ማስረጃው መመዘን ያለበት ጥፋተኛ ለማስደረግ ከማስቻሉ አንፃር ነው አንድን ወንጀል ለማቋቋም ከሚያስፈልጉት ወሣኝ ነገሮች አንዱ የሆነው የፍሬ ነገር ሁኔታ መኖር ሣይረጋገጥ በምንም ዓይነት ሁኔታ ክስ መቅረብ የለበትም ለምሣሌ ምስክሮች ለፖሊስ የሰጡት ቃል እርስ በእርሱ የሚጋጭ ከሆነ ክስ ቀርቦ ፍቤትም ቢቀርቡ ውጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል ከወዲሁ መገመት ይቻላል ዐቃቤ ሕግ በጥንቃቄ በፖሊስ የምርመራ መዛግብት ውስጥ የሚገኙ ማስረጃዎችን አንዱን ከሌላው ጋር እያነፃፀረ በመመዘን ገለልተኛ በሆነ ሁኔታ ተመልክቶ ክስ ለፍቤት ቢቀርብ ውጤቱ ምን ለሆን እንደሚችል በማገናዘብ መወሰን አለበት የሕጉ አቀራረፅ ምንም ችግር የሌለበት ሆኖ ሣለ በረቂቁ ሕግ ላይ ጥፋተኛ ለማድረግ የሚለው ሀረግ እንዲወጣ መደረጉ ተገቢነት የለውም ጥብቅ መሥፈርትን ያስቀመጠው ሕግ እያለ እንኳን ሣይጣራ ክስ ሲቀርብ ይስተዋላል የባሰ የበለጠ የሳሳ መሥፈርት ማስቀመጡ በበቂ ሁኔታ ያልተጣሩ ክሶች ለፍቤት እንዲቀርቡ በር የሚከፍት በመሆኑ ረቂቁ ሕግ ሊስተካከል ይገባል የሌሎች ሀገሮች ተሞክሮም የሚሳየው ጥፋተኝነትን ለማረጋገጥ በቂ ማስረጃ ከሌለ ክስ መቅረብ እንደሌለበት ነው የተከሰሰውን ሰው ለማግኘት የማይቻል ከሆነ ና ጉዳዩም በሌለበት ሊታይ ካልቻለ ክስ ማቅረብ ትርጉም አይኖረውም በተለይ በዐቃቤ ሕግ በወቅቱ ክስ ተዘጋጅቶ ሣይቀርብ ጊዜ ካለፈ ክስ ከመቅረቡ በፊት በቅድሚያ የተከሣሹ መኖር መጣራት አለበት ክሱ ከቀረበ በኋላ ፍቤት ያፈላልገው በሜል ሂሣብ ክሱ ከቀረበ ትርፉ ያለ አግባብ የራሱም የዐቃቤ ሕግን ጨምሮ የሕዝብና የመንግሥት ጊዜ ና ሀብት ያለ አግባብ እንዲባክን ማድረግ ነው በመሆኑም ዐቃቤ ሕግ ክስ ከማቅረቡ በፊት ተከሣሹ ሊገኝ መቻል አለመቻሉንና ጉዳዩም ተከሣሽ በሌለበት ሊታይ መቻሉን ማረጋገጥ አለበት በይርጋ በታገደ ወይም ለተፈፀመው ወንጀል ምህረት ጠከርክ ተደርጐ እንደሆነም ክስ ማቅረብ አይቻልም በህገ መንግስቱ አንቀፅ መሠረት ኢትዮጵያ ባፀደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶችና በሌሎች የኢትዮጵያ ሕጎች በሰው ልጅ ላይ የተፈፀሙ ወንጀሎች ተብለው የተወሰኑትን ወንጀሉች የሰው ዘር ማጠፋት ያለ ፍርድ የሞት ቅጣት ዕርምጃ የሚወስድ በአስገዳጅ ሰውን የመሰወር ወይም ኢሰብዓዊ የድብደባ ድርጊቶችን በፈፀሙ ሰዎች ላይ ክስ ማቅረብ በይርጋ አይታገድም በሕግ አውጪው ክፍልም ሆነ በማንኛውም የመንግሥት አካል ውሣኔዎች በምህረት ወይም በይቅርታ አይታለፍም ይቅርታ ሀኮበበ በፍቤት የጥፋተኝነት ውሣኔ ከተሰጠ በኋላ የሚመጣ በመሆኑ ከክስ ማቅረብ ጋር በቀጥታ ግንኙነት የለውም ከላይ ከተዘረዘሩት ሁኔታዎች ውጪ ያሉት በሙሉ ቀደም ብሎ በሕግ የተሻሩ ናቸው በአስፈፃሚው ትዕዛዝ ክስን የማቋረጥ አሠራር የዐቃቤ ሕግን ነፃነት ለማስጠበቅ በአዋጅ ቁጥር እንዲሻር ተደርጓል ዐቃቤ ሕግ በማናቸውም ምክንያት መዝገብ ሲዘጋ ለበላይ ዐቃቤ ሕግ ለፖሊስና ለተበዳይ ማሣወቅ እንዳለበት በወመሕሥሥቁ እና ሥር ተደንግጐ ስለሚገኝ ሁልጊዜ መተግበር አለበት ይህ ግልፅነተ ና ተጠያቂነትን ለማስፈን ወሣኝ አሠራር በመሆኑ ሊታለፍ አይገባምቆ በተለይ ለተበዳይ ማሣወቁ ቅር ከተሰኙ ለበላይ ዐቃቤ ሕግ አቤቱታውን በማቅረብ ጉዳዩ እንደገና እንዲታይ ሊያስደርግ ስለሚችል ማስተላለፍ አለበት እራሱ የተበደለ ሰው ቀርቦ እስኪጠየቅ መጠበቅ የለበትም በፖሊስ አማካኝነት ወይም በቀጥታ በአድራሻው ለተበደለው ወገን የዐቃቤ ሕግ ውሣኔ ሊገለፅለት ይገባል እስከ መጨረሻው የዐቃቤ ሕግ ኃላፊ ድረስ በተዋረድ ሕጉ በሚፈቅደው መሠረት ተገልጋዮች ቅሬታቸውን እንዲያቀርቡ የሚያስችል ምቹ አሠራር መዘርጋት አለበት ክፍል አራት የወንጀል ክስ አቀራረብንና ክስ ማሻሻልን የሚመለከቱ ችግሮች ዐቃቤ ሕግ በወመሕሥሥቁ እና ዐ መሠረት ክስ ለማቅረብ የወሰነ እንደሆነ በወመሕሥሥቁ ከዐ ባሉት ድንጋጌዎች መሠረት ክሱን አዘጋጅቶ ሥልጣን ላለው ፍቤት ማቅረብ አለበት የወንጀል ጉዳዩን ለመመልከት ሥልጣኑ የሌለው ፍቤት ክሱ ከቀረበለት መቀበል የለበትም ለከፍተኛ ፍቤት የቀረበን ጉዳይ መመለስ የማይችለው ወንጀሉ በወሕአ ሥር የሚወድቀውን ስርቆትን የተመለከተ እንደሆነ ነው ይህ ዓይነት ሁኔታ ሲያጋጥመው ከፍተኛው ፍቤት ዝም ብሎ ጉዳዩን ማስተናገድ አለበት ከሥልጣን ጋር ተያይዞ የሚያጋጥመው ሌላው ችግር የተወሰኑ ወንጀሎች በአንዱ ፍቤት ሥልጣን ክልል ሥር ሌሎቹ ደግሞ በሌላ ፍቤት ሥልጣን ክልል ስር የሚወድቁ ሲሆን በምን ዓይነት ሁኔታ መስተናገድ አለባቸው የሚለው ነው ለምሣሌ በወሕአ ስር በስርቆት የተከሰሰ ሰው በተጨማሪ በደንብ መተላለፍ በወሕአ ዐ መሠረት የሚያስጠይቀውን ስለት ነገር ወይም በወሕአ ስር የሚያስጠይቀውን አጠራጣሪ ነገር ይዞ ቢገኝ ክሶቹ የት መቅረብ አለባቸው የሚለው ሊያወዛግብ ይችላል ለምሳሌ በአዲስ አበባ የደንብ መተላለፍ ጉዳዮችን የመመልከት ሥልጣን የተሰጠው ለአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት ነው የከተማው ፍቤት ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍቤት የበታች ሊባል የሚችል አይደለም። ምዕራፍ አምስት የወንጀል ተጠቂዎች በሚኖሩበት ጊዜ የችሎት አመራር አጠቃላይ ዓላማዎች ይህን ክፍለ ትምህርት ካጠናቀቁ በኋላ ሠልጣኞቹ በወንጀል ተጠርጣሪዎች እና በወንጀል ተጠቂዎች መካከል ያሉ ተነፃባሪ መብቶችን ይገነዘበሉ የወንጀል ተጠቂዎችን የሥነልቦናና ማህበራዊ ፍላጎቶች መሰረት ያደረገ የፍትህ አመራር ዘዴን ይለያሉ ዘዴዎችን ተግባራዊ ያደርጋሉ ዝርዝር ዓላማዎች በምዕራፉ የተመለከቱትን ክፍለ ትምህርቶች ከተከታተሉ በላ ሠልጣኞች በወንጀል ተጠርጣሪዎችና በወንጀል ተጠቂዎች መካከል ያሉ ተነፃፃሪ መብቶችን ይለያሉ የወንጀል ተጠቂዎች በወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱ እንዴት መስተናገድ እንዳለባቸው ይለያሉ የወንጀል ተጠቂዎችን የሥነ ልቦና እና ማህበራዊ ፍላጎቶችን ይለያሉ አነዚህ ፍላጎቶች ተግባራዊ የሚደረጉበትን ዘዴ ይለያሉ በመልመጃዎች ላይ ተግባራዊ ያደርጋሉ ዴዶይጩመሪ ሠ ክፍል አንድ የወንጀል ተጠርጣሪዎች እና የወንጀል ተጠቂዎች ተነፃፃሪ መብቶች ሕጎች በአጠቃላይ ከይዞታቸው አንፃር ዋና ሕጎች እና ቅፅል ሕጎች ሀከበከሃህ በበ ልዐዌፉበርከህ ዉ ተብለው እንደሚከፈሉ ከዚህ ቀደም ለማየት ተሞክሯል ከወንጀል አንፃር ያሉ ዋና ሕጎች ሕግ አድርግ ያለውን አለማድረግ ወይም አታድርግ ያለውን ማድረግ ሊያስቀጣ እንደሚችል የሚደነገግባቸው ናቸው በዚህ ረገድ ከወንጀል አንፃር ያሉ ዋና ሕጎች በወንጀል ተጠርጣሪ ወይም በወንጀል ተጎጂ መካከል ልዩነት የሚያደርጉ ናቸው ተብለው የሚወሰዱ አይሆኑም ምክንያቱም የእነዚህ ዋና ሕጎች ዓላማ አንድን ወገን መሠረት ያደረገ ሳይሆን ለአጠቃላይ ማኀበረሰቡ በመርህነትገዢ ሕግነት ሊወሰዱ የሚገባቸውን ፅንሰ ሃሳቦች ማስተላለፍ ነው የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ ዓላማና ግብ ለምሳሌ ያህል ብንመለከት የወንጀል ሕግ ዓላማ ለጠቅላላው ጥቅም ሲባል የአገሪቱን መንግሥት የሕዝቦቹን የነዋሪዎቹን ሰላም ደህንነት ሥርዓት መብትና ጥቅም መጠበቅና ማረጋገጥ ነው የወንጀል ሕግ ግብ ወንጀል እንዳይፈፀም መከላከል ሲሆን ይህንን የሚያደርገው ስለወንጀሎችና ስለቅጣታቸው በቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ማስጠንቀቂያነቱ በቂ ባልሆነበት ጊዜ ወንጀል አድራጊዎቹ ተቀጥተው ሌላ ወንጀል ከመፈፀም እንዲቆጠቡና ለሌሎች ማስተማሪያ እንዲሆኑ ወይም እንዲታረሙ በማድረግ ወይም ተጨማሪ ወንጀሎች እንዳይፈፀሙ እርምጃዎች እንዲወሰዱባቸው በማድረግ ነው ይላል አንቀጽ የወንጀል ሕጉ ዓላማና ግብ እንደሚያስረዳው ትኩረቱ ቅድመ ማስጠንቀቂያ መስጠት ሲሆን አጥፊም ሆነ ተጎጂ ከመኖራቸው በፊት ሊደረጉ የሚገባቸውን ወይም የማይገባቸውን ነገሮች አስቀድሞ በማሳወቅ ላይ ያተኮረ እንደመሆኑ ተደራሽነቱ የሕግ መተላለፍ እስከሚፈፀም ድረስ ለአከጥፊም ሆነ ለተጎጂ አኩል ሆኖ ይስተዋላል የወንጀል ሕጉ ወደሚፈፀምበት የሥነ ሥርዓት ድንጋጌዎች በምንመጣበት ጊዜ ዋናው ሕግ በማድረግም ሆነ ባለማድረግ ሊያስቀጡ ይችላሉ ብሎ ያስቀመጣቸው ጉዳዮች ተጥሰው በሚገኙበት ወቅት የሚወሰደውን ቀጣይ እርምጃ የሚመራበትን ሥርዓት የሚደነግግ እንደመሆኑ ለወንጀል ተጠርጣሪዎችም ሆነ ለወንጀል ተጠቂዎች ሊከበሩ የሚገቡ መብቶች ተካተውበት እናገኛለን የወንጀል ተጠርጣሪዎች መብቶች በበርካታ የዓለም አገራት እንደሚስተዋለው ከሕገ መንግስት ጀምሮ በዝርዝር የሥነ ሥርዓት ሕጎች ውስጥ ጥበቃ የሚደረግላቸው በርካታ የወንጀል ተጠርጣሪዎች መብቶች አሉ ለዚህም ቢያንስ ሁለት ምክንያቶችን መጥቀስ ይቻላል የመጀመሪያው አታደርግ የተባለውን በማድረጉ ወይም አድርግ የተባለውን ባለማድረጉ ከሕጉ ጋር ችግር ውስጥ የገባው ያው ተጠርጣሪው እንደመሆኑ በሂደት የመብት መጣስ ሊያጋጥመው የሚችለውም ራሱ ተጠርጣሪው ነው የሚለው አሳቤ ሲሆን ሌላኛው ነጥብ የኃይል ሚዛንን የሚመለከት ነው እንደሚታወቀው የወንጀል ድርጊት በአጠቃላይ በማህበረሰቡ ደህንነት ላይ የተፈፀመ ተደርጐ ከሚወሰድበት አሳቤ በመነሳት በአብላጫው የወንጀል ጉዳዮች እንደግል ተበዳይ ሆኖ የሚከራከረው መንግስትዐቃቤ ሕግ ሲሆን መንግስት ካለው አቅም አንፃር በወንጀል ተጠርጣሪው መብት ላይ ሊያሳድረው የሚችለውን ጫና ግምት ውስጥ በማስገባት እንደሆነ ይታመናል በአገራችን ሕጎች መሰረትም በሕገ መንግስቱም ሆነ በወመሕሥሥ ውስጥ የተካተቱ በርካታ የተጠርጣሪዎች መብቶች አሉ ከችሎት አመራር አንፃር አለፍ አለፍ አያሉ ለመመልከት ያህል የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል ሀ በፍርድ ቤቶችና በሌሎች የዳኝነት አካላት ፊት በእኩልነት መታየት ይህ መሠረታዊ መብት አንድ ተጠርጣሪ በዘሩ በኃይማኖቱ ፃታው የሀብት መጠት ወዘተ ልዩነት ሳይደረግበት ከሌላው ተከራካሪ ወገን አኩል በፍርድ ሚዛን ላይ መቀመጥ መቻሉን የሚመለከት መብት ነው ለ ንፁሕ ሆኖ የመገመት መብት ማንኛውም ተጠርጣሪ ከፍርድ በፊት ልክ እንደወንጀለኛ መቆጠር እንደሌለበት እና በተከሰሰበት ወንጀል ነፃ ሆኖ የመገመት መብት እንዳለው በኢፌዲሪ ሕገ መንግስት አንቀፅ ዐ ተደንግዓጓል የተፋጠነ ፍርድ የማግኘትና በግልጽ ችሎት የመዳኘት መብት የተከሰሱ ሰዎች ክስ ከቀረበባቸው በኋላ ተገቢ በሆነ አጭር ጊዜ ውስጥ በመደበኛ ፍርድ ቤት ለሕዝብ ግልፅ በሆነ ችሎት የመዳኘት መብት አላቸው የኢፌዲሪ ሕገ መንግስት አንቀፅ ዐ ማስረጃን የማወቅ ምሥክሮትን የመጥራትና የመመርመር መብት የተከሰሱ ሰዎች የቀረበባቸውን ማናቸውም ማስረጃ መመልከትና የቀረቡባቸውን ምሥክሮች የመጠየቅ ለመከላከል የሚያስችላቸውን ማስረጃ የማቅረብ ወይም የማስቀረብ እንዲሁም ምሥክሮቻቸው ቀረበው እንዲሰሙላቸው የመጠየቅ መብት አላቸው የኢፌዴሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ ዐ ከዚህም በተጨማሪ ሌሎች በችሎት አመራር ወቅት ሊከበሩ የሚባቸው የተጠርጣሪዎችተከሣሾች መብቶች አሉ ለምሣሌ በሰንሰለት ሳይታሰሩ የመቅረብ መብት የወመሕሥሥቁጥር የኢፌዲሪ ሕገመንግስት አንቀጽ ነፃ የተርጓሚ አገልግሎት የማግኘት መብት በመረጡት ጠበቃ የመከራከር ጠበቃ እንዲቆምላቸው የመጠየቅ መብት በዋስ የመለቀቅ መብት ራስን ከመወንጀል የመጠበቅ መብት የይግባኝ መብት ሊጠቀሱ ይትላሉ የወንጀል ተጠቂዎች መብቶች ስለ ወንጀል ተጠቂዎች በሚነሳበት ወቅት ጎልቶ የሚወጣ አንድ ጥያቄ አለ ይኸውም የወንጀል ተጠቂ ማን ነው።