Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ሳቁ ርዕስ ገጽ መግቢ ክፍለ ትምህርት መሠረታዊ የዜማ ጽንሰ ሀሳብ ቬኬማ የድምጾች ቅንብር ውጤት ነው ቋንቋዎችን ለመጻፍም ሆነ ለማንበብ ፊደሎች አስፈላጊዎች ናቸው ለምሳሌ የአማርኛን ቋንቋ ለማንበብና ለመጻፍ የየቋንቋዎቹን ፊደላት ማወቅ ያስፈልጋል የፊደላቱን ቅርጽ በማየት የፊደላቱን ድምጽ በመስማት በማንበብና በመጻፍ መነጋገር ይቻላል በሁሉም ቋንቋዎች ለመናገር ግን ፊደላትን ማወቅ ግድ አይደለም ቋንቋ የሰው ልጆች ፃሳባቸውን ኀዘናቸውንና ደስታቸውን ከሚገልጹበት መንገዶች አንዱ ዜማ ነው ይህ ዜማ በተለያዩ ሰዎች ንደ ባህላቸውና እምነታቸው እአንደፍላጎታቸውና እንደየአቅማቸው በድምጽ ብቻ እና በዜማ መሣሪያ ሲዜም ይሰማልፎ የምንሰማቸው ንግግሮች የተለያዩ ፊደላት ቅንብር እንደሆኑና ፊደላቱም የራሳቸው ቅርጽና ድምጽ ። ሊለ የዜማ ድምጽ ዐ ለጆሮ ተስማሚ የሆኑ ስሜትን የሚገዙየማይረብሹ ድምጾች ናቸው የዜማ ድምጾች የሚባሉት እነማን ናቸው።ደፍል ጆ ሀር ሪ ባቲ ማይነር ር ጀክ ሺ ር « አንቺ ሆዬ ለኔ ዒቢ ደል ር ለሊ ር ሦ ፅ አምባሰል ቅኝት ር ያ ለ።
ሳቁ ርዕስ ገጽ መግቢ ክፍለ ትምህርት በገና በመጽሐፍ ቅዱስ በገና በኢትዮጵያ የበገና ዓይነቶች የበገና አካል ክፍሎች ምሳሌ በገና የሚሠራበት ቁስ ክፍለ ትምህርት ለበገና ድርደራ የጣት ስያሜ የበገና አያያዝና አደራደር ። ዓላማህ እንደ ኮከብ የፀና ይሁን ተወው ዓለም እንደፈለገው ይነታረክ ይጨቃጨቅ ጥቃት ይደርስብህ ትበደል ትሰደብ ትታማ ትቆስልና ትናቅ ይሆናል ኃይለኛ ያጎሳቁልህ ወዳጆች ይተዉህ ሰዎችም ይንቁህ ይሆናል አንተ ግን በፀና ውሳኔ የማያወላውል ቅናት በመጨረሻ ላይ ጸንተህ የሰጠኸኝን ሥራ ፈፀምኩ ሃይማኖትንም ጠበቅሁ ለማለት አስክትችል ድረስ የሕይወትህን ዓላማ እና የተፈጠርክበትን ግብ ተከተል ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ምንጭ ሐመር መጽሔት ሚያዝያ ዓም መግቢያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በዜማ በሥነ ጹሑፍ በሥነ ሥዕል በሥነ ሕንፃ በሌሎችም የጥበብ ዘርፎች ለአገራችን እንዲሁም ለዓለም ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክታለች ዚአብሔር ሰማያዊውን ምሥጢር የገለጠለት ኢትዮጵያዊው ጻድቅ ማህሌይ ቅዱስ ያሬድ አምስቱ ጸዋትወ ዜማ ድጓ ጾመ ድጓ ዝማሬ መዋሥዕት እና ምዕራፍ በመድረስ በዓለም የዜማ ታሪክ ተቀዳሚ ተጠቃሽ ነው ቅድስት ቤተክርስቲያን በሕገ ልቡና በሕገ ኦሪት እግዚአብሔር ሲመሰገንበት የነበሩትን የዜማ ዕቃዎች በቅዱስ ያሬድ እና ከእርሱም በኋላ በተነሱት ቅዱሳን ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን አማካኝነት በአዲስ ኪዳን ለቤተክርስቲያን አገልግሎት እንዲውሉ አድርጎ እስከ አሁን እግዚአብሔርን እያመሰገነች ትገኛለች በብሉይ ኪዳን የዜማ መገልገያ መሣሪያ ከሆኑት አንዱ የነበረው በገና አንደሌሎቹ የዜማ መገልገያ ፅቃዎች በቤተክርስቲያን አገልግሎት ቦታ ተወስኖለት ለመማርም ሆነ ለማስተማር ምቹ ሁኔታ ባለመኖሩ «እየጠፋ ነው» «እየሞተ ነው» ዝከ ሃክ ላዘር ለመባል በቅቷል ስለዚህ ይህ በኢኦተቤክ ብቻ የሚገኘ ውን የአገራችንና የዓለማችን ቅርስ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ታሪኩን ጥቅሙን ክብሩንና አጠቃቀሙን ተረድተን ኛ ም በዘመናችን አእውቀታችንን ጉልበታችንንገንዘባችንንና ጊዜጣችንን አስተባብረን በገዳማት በአድባራት በአብነት ትቤቶችና በመንፈሳዊ ተቋማትና ኮሌጆች ትምህርቱ እንዲስፋፋና በቤክ በሚካሄዱ መንፈሳዊ ጉባኤያት ላይ በበገና እግዚአብሔርን የማመስገን ባህሉ እንዳይጠፋና በግልም ለጸሎትና ለምስጋና ለተመስጦ ንድንጠቀምበት ጥረት እንድናደርግ ይህ የበገና መማሪያ መጽሐፍ ተዘጋጀ ይህ መጽሐፍ በአምስት ምዕራፎች የተከፈለ ነው ይኸውም ምዕራፍ ፅ ስለበገና አጠቃላይ ታሪክ ስለ በገና ዓይነቶች የበገና አካል ክፍሎች የበገና አያያዝና አደራደር የሚሉትን ርዕሶች የያዘ ሲሆን ከምፅራፍ ያሉት ደግሞ ሰላምታ ትዝታና አንቺ ሆዬ ለኔ ቅኝቶችን ባህላዊ በሆነ መንገድ መዝሙሮችን በቁጥር የሚያሳይ ነው በምዕራፍ መሠረታዊ የዜማ ጽንሰ ፃሳብ ተማሪዎች ሰለዜማና ስለ ቅኝት ግንዛቤ አንዲኖራቸው ታስቦ በቀላሉ ሊረዱት በሚችል መልኩ ቀርቧል ይህ ግን ስከ አሁን ለተማሩት ተማሪዎች መደበኛ ሆኖ አልተሰጠም በዚህ መጽሐፍ ከምዕራፍ ያለው ትምህርት በአቡነ ጎርጎርዮስ የአብነትና የዜማ ትምህርት ቤት ለበገና ተማሪዎች በሳምንት ሁለት ቀን በቀን ለ ሰዓታት ለ ወር ያህል ጊዜ መጽሐፉ በሚያዝዘው መሠረት ተሰጥቶ ተማሪዎች ጥሩ ውጤት አሳይተወበ። ል ይኸው ትምህርት በምሑር ገዳም ኢየሱስ ገዳም ከሰኞ እስከ እሑድ በቀን ለ ሰዓታት ለ ወር ያህል ጊዜ የትምህርትና የልምምድ ጊዜ ተሰጥቶ ተምረው ጅግ በጣም ጥሩ ውጤት አሳይተዋል ገዳም በገናን ለመማርም ሆነ ለማስተማር እንዲሁም ለመደርደር በጣም ምቹ ቦታ እንደሆነ አረጋግጫለሁ በአነዚህ በገናን ባስተማርኩባቸው ቦታዎች ልክ እንደ ሌሎቹ የአብነት ትምህርት ቤቶች ትምህርቱ በጸሎት ተጀምሮ በጸሎት ይፈጸማል ያለ እፄ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና ብሎ ጌታችን በወንጌሉ እንዳስተማረን አባቶቻችን አድርገው እንዳሳዩን እኛም አድርገን ተጠቅመናል ተማሪዎች ፈቃደ እግዚአብሔርን በጸሎት አየጠየቁ በአስተማሪ ድጋፍ መጽሐፉ በሚያዘው መሠረት በትዕግሥትና በትጋት ከተጠቀሙበት በገናን መደርደር ይችላሉ የሚል እምነት አለኝ አዘጋጁ ክፍለ ትምህርት በገና በመጽሐፍ ቅዱስ በገና ለመጀመሪያ ጊዜ በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሰው በዘፍ ሲሆን የላሜሕ ልጅ ዮባል በገና እና መለከት ለሚይዙ አባት እንደሆነ ተጠቅሷል ይህ ታሪክ ሌሎች በገና አና መለከትን የሚይዙ ሰዎች ንደነበሩና ዮባል አለቃቸው እንደነበረ ያስረዳል ከዚያን ዘመን ጀምሮ በገና እግዚአብሔርን የማመስገኛ የዜማ ፅቃነቱ ታውቆ እንደሌሎቹ የቤተ መቅደስ የዜማ ዕቃዎች መለከት መሰንቆ ጸናጽል በሌዋውያን በተመረጡ አለቆች አማካኝነት አገልግሎት ይሰጥ ነበር የአግዚአብሔር ታቦት ከአሚናዳብ ቤት ወደ አቢዳራ ቤት በገባ ጊዜ ኛ ሳሙ ዳዊትና የአስራኤልም ቤት ሁሉ በቅኔና በበገና በመሰንቆ በከበሮም በነጋሪትና በጸናጽል በእግዚአብሔር ፊት በሙሉ ኃይላቸው ይጫወቱ ነበር የአግዚአብሔር ታቦት ከአቢዳራ ቤት ወደ ዳዊት ከተማ በመጣች ጊዜ ኛ ዜና ዳዊትም በዜማ ዕቃ በመሰንቆና በበገና በጸናጽልም እንዲያዜሙ ድምጻቸውንም በደስታ ከፍ እንዲያደርጉ መዘምራኑን ወንድሞቻቸውን ይሾሙ ዘንድ ለሌዋውያን አለቆች ተናገረ ቼ ዜና ስምንት አውታር ባለው በገና ይዘምሩ ነበር መዢ አግዚአብሔርንም በመሰንቆ አመስግኑት ዐሥር አውታርም ባለው በገና ዘምሩለት» ቭ ዜና አስራኤል ሁሉ ሆ እያሉ ቀንደ መለከትና እምቢልታ እየነፉ ጸናጽልና መሰንቆም በገናም እየመቱ የአግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦት አመጡ የአግዚአብሔር ታቦት ከዳዊት ከተማ ሰሎሞን ወደ ሠራው ቤተመቅደስ ሲገባ ኛ ዜና መዘምራንም የነበሩት ሌዋውያን ሁሉ አሳፍና ኤማን ኤዶታምም ልጆቻቸውም ወንድሞቻቸውም ጥሩ በፍታ ለብሰው ጸናጽልና በገና መሰንቆም እየመቱ በመሰውያው አጠገብ በምሥራቅ በኩል ቆመው ነበር ከእነርሱ ጋር መቶ ሣያ ካህናት መለከት ይነፉ ነበር አግዚአብሔር ቸር ነውና ምሕረቱም ለዘላለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ እያሉ በአንድ ቃል ድምጻቸውን ወደ ላይ ከፍ አድርገው በመለከትና በጸናጽል በዜማም ዕቃ ሁሉ እግዚአብሔርን ባመሰገኑ ጊዜ ደመናው የአግዚአብሔርን ቤት ሞላው ገዚአብሔር በጠላቶቻቸው ላይ ደስታን በሰጣቸው ጊኬ ኛ ዜና «የይሁዳና የኢየሩሳሌም ሰዎች በፊታቸውም ኢዮሳፍጥ እግዚአብሔር በጠላቶቻቸው ላይ ደስ አሰኝቶአቸዋልና በደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ይሄዱ ዘንድ ተመለሱ በበገናና በመሰንቆ በመለከትም ወደ ኢየሩሳሌም ወደ እግዚአብሔር ቤት ገቡ» ያፅዋብ ከላባ በኮበለለ ጊዜ ላባ ለያዕቀብ ሲናገረው ዘፍ ስለምን በስውር ሸሸህ። » ከላይ በተጠቀሱት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች በገና አንደ ሌሎች የቤተ መቅደስ የዜማ ዕቃዎች የአግዚአብሔር የቃል ኪዳን ታቦት ከአቢዳራ ቤት በምትመጣበት ጊዜ በዳዊትም ከተማ ገብታ በድንኳን በኖረችበት ጊዜ ሁሉ ንጉሥ ሰሎሞን የአግዚአብሔርን ቤት ሠርቶ በጨረሰ ጊዜ ከዚያም በኋላ እግዚአብሔር በጠላቶቻቸው ላይ ድልን በሰጣቸው ጊዜ አገልግሎት ይሰጥ እንደነበረ ተገልጧል በገና በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ላይ አገልግሎቱ ቢጠቀስም በይበልጥ የታወቀውና አገልግሎቱ የሰፋው በቅዱስ ዳዊትና እርሱ በነበረበት ዘመን ነው ቅዱስ ዳዊት ከአግዚአብሔር በተሰጡት ሰባት ሀብታት መካከል ሁለቱ ሀብተ በገና እና ሀብተ ፈውስ ናቸው ሀብተ በገና አንጨት ጠርቦቁርበቱን ጎልቦጅማቱን ወጥሮ መደርደር ሲሆን ሀብተ ፈውስ በገናውን ደረደሩ ድውይ መፈወስ ነው ይህስ ሀብተ በገና ካለው ይገባል ቢሉ ሀብተ ፈውስ መንፈሳዊ አመታት ድርደራ ነው ኛ ሳሙ መዝሙረ ዳዊት አንድም። ሴይ ልጅ ቅዱስ ዳዊት አንደሆነ ታውቋል ኛ ሳመ በተለያየ ወቅት ንጉሥ ሳኦል ክፉ መንፈስ ባሰቃየው ጊዜ ቅዱስ ዳዊት በገና በእጁ እየመታ ሳኦልን ደስ ያሰኘው ከጭንቀትም ያሳርፈው ነበር ክፉ መንፈስም ከሳኦል ይርቅ ነበር ይህ ሪክ ደግሞ በገና ሲደረደር ሰውን ደስ አንደሚያሰኝ ከጭንቀትም እንደሚያሳርፍ ክፉ መንፈስም አንደሚርቅ ያሳያል ኛሳመ በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት በገና በብዙ ቦታዎች ላይ የተጠቀሰ ሲሆን ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው ዘፍ ዘፍ ኛ ሳሙ ዐ ኛ ዜና ኛ ዜና መዝ በገና አዲስ ኪዳን መጽሐፍት በብዛት ባይገለፅም የአዲስ ኪዳን የትንቢት መፅሐፍ በሆነው በዮሐንስ ራዕይ መጽሐፍ ውስጥ የበገና ሰማያዊ አገልግሎት ተገልዷል ዮሒራዕይ «መጽሐፉንም በወሰደ ጊዜ አራቱ እንስሶችና ፃያ አራቱ ሽማግሌዎች በበጉ ፊት እያንዳንዳቸውም በገናና የቅዱሳን ጸሎት የሆነ ዕጣን የሞላበትን የወርቅ ዕቃ ያቡ» ዮሒራዕይ ቁ « ደርዳሪዎችም በገና እንደሚደረድሩ ያለ ድምፅ ሰማሁ ዮሒ ራዕይ » በአውሬውና በምስሉም በስሙም ቁጥር ላይ ድል ነስተው የነበሩት የእግዚአብሔርን በገና ይዘው በብርጭቆ ባህር ላይ ሲቆሙ አየሁ በገና ከብሉይ ኪዳን የመጀመሪያ መጽሐፍ ከኦሪት ዘፍጥረት እስከ መጨረሻው የአዲስ ኪዳን መጽሐፍ ዮሐንስ ራዕይ ድረስ አገልግሎቱ የተጠቀሰ ሲሆን በአጠቃላይ አገልግሎቱ ሲታይ በኅብረትም በአለቃ እና በግል ለብቻ ሆኖ አገልግሎት ሊሰጥ የሚችል የዜማ መሣሪያ እንደሆነ እንገነዘባለን በመጽሐፍ ቅዱስ ከኦሪት ዘፍጥረት ጀምሮ የዜማ ዕቃዎች አገልግሎት የተጠቀሰ ሲሆን በጥንት ጊዜ ሦስት ዓይነት የዜማ ዕቃዎች እንደነበሩ ተጠቅሰዋል ይኸውም አውር ያለው የዜማ ዕቃ ዘማሪው በእጅ ወይም በመከርከሪያ ሲመታው ድምጽ ይሰጣል በገና ክራርና መሰንቆ ከባለ አውታር የዜማ ዕቃ ክፍል ናቸው የሚነፋ የዜማ ዕቃ በዚህ ዓይነት የዜማ ዕቃ ውስጥ መለከት እምቢልታና ዋሽንት ተጠቅሰዋል ፅቃዎችን እርስ በርስ በማማታት ወይም በእጅ በኃይል በመምታት የሚጠቀሙባቸው ዕፅቃዎች ነዚህም ከበሮ አታሞ ነጋሪትና ጸናጽል ናቸው የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት የዜማ ዕቃ በዘመናዊ ሙዚቃ ውስጥ የዜማ መሣሪያዎችን በአምስት ምድብ ይከፍላቸዋልእኒህም ርስ በርስ በመጋጨት ድምጽ የሚሰጡ በፀዐሀከ የክር አውታር መሣሪያዎች ርከዐከ ለመምታት ታስበው በቆዳ ወይም በሌላ ነገር የተሸፈኑ የዜማ ዕቃዎች ጠበቱከ የትንፋሽ መሣሪያዎች ላጩዐሀከ በኤሌትሪክ አማካኝነት ድምጽ የሚፈጥሩ መሣሪያዎች በርኩዐዐከ ከላይ በተጠቀሰው የዜማ መሣሪያዎች አመዳደብ መሠረት በገና አውታር ካላቸው የዜማ ዕቃዎች ርከዐከዐክ የሚመደብ ሲሆን በእድሜው ትልቅነትም ለአውታር መሣሪያዎች አባት ሊባል የሚችል ነው በገና በመጽሐፍ ቅዱስ በተጠቀሰው ታሪኩ ስምንት አውታርና አሥር አውታር ያለው ሁለት ዓይነት በገና ንዳለ ተጠቅሷል ቅዱስ ዳዊት ግን ይጠቀምበት የነበረው በገና አሥር አውታር ያለው እንደሆነ በመዝ ላይ ተጽፎ እናገኛለን መጽሐፍ ቅዱስ አንደ ቅዱስ ንጉሥ ዳዊት ከአርሱም በፊት ከእርሱም በኋላ በበገና ደርዳሪነት ስሙ የገነነ የለም ሽጂ ብዙ በገና ደርዳሪዎች በየዘመኑ እንደነበሩ ያስረዳል በገና በኢትዮጵያ ኢትዮጵያ በሕገ ልቡና እና በሕገ ኦሪት እግዚአብሔርን ታመልክ የነበረች ሀገር ስለነበረች ሕዝበ ዚአብሔር ከሚባሉት ከእስራኤላውያን አንድ ዓይነት የአምልኮ ሥርዓት ነበራቸው ሙሴ ኢትዮጵያዊት ሚስት ማግባቱ ኢትዮጵያውያን ከእስራኤላውያን ጋር በአምልኮ አንድ መሆናቸውን አስረጂ ነው የአግዚአብሔር ሕዝቦች ከአሕዛብ ጋር አይጋቡም ነበርና «የእስራኤል ልጆች ሆይ እናንተ ለእኔ እንደ ኢትዮጵያ ልጆች አይደላችሁምን። ገዚአብሔር በዚህ ጭንቀትሐዘንመከራ በበዛበት ዘመን በገናን ያስነሳበት የራሱ ዓላማ አለውና መልካም አድርጎ በገና መደርደር ሀብተ በገና በገና ደረደሩ መፈወስ ሀብተ ፈውስ ከእግዚአብሔር የሚሰጥ ስጦታ መሆኑን አምነን ስጦታውን ለራስ ክብር ሳይሆን ለእግዚአብሔር ክብር እና ለቤተክርስቲያን ጥቅም በፍቅር ልንጠቀምበት ይገባል « የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል ኛም ባሪያዎቹ ተነስተን እንሠራለን ነህ የበገና ዓይነቶች በገና በመጽሐፍ ቅዱስ ዓይነቱና ቅርጹ በውል ባይታወቅም ስምንት አውታርና አሥር አውታር ያላቸው በገናዎች እንደነበሩ ያስረዳል ኛዜና መዝ በዓለማችን ላይ በተለያዩ አገሮች በገና ወይም ሀርፕ የሚባል የዜማ መሣሪያ ቢኖርም እንደየአገሩ ሁኔታ ቅርጹና የክሩ አው። ሩን እየመቱ ድምጹን ሰምቶ በድምጽ ብቻ ማለት ዓ ሁለት ሁለት አውር ደረደሩ ድምጽን ሰምቶ ማለት ዓ ሦስት ሦስት አውር የደረደሩ ድምጹን ሰምቶ ማለት ፍ ዚህ ትምህርት ላይ ዋናው የድምጽ ጥናት ሰስለሆነ በገናው በትክክል መቃኘት አለበት የተግባር ሥራ አውሩን መቃኛ ላይ ማሰር አውሩን መወጠሪያ ላይ ማሰር አውሩን በመቃኛ ቀንበር ላይ መጠምጠም የበርኩማ በድምጽ ሳጥን ላይ አቀማመጥ የእንዚራ በበርኩማ ላይ አቀማመጥ በበገና ድምጽ ላይ ተጽዕኖ ሊያሳድሩ የሚችሉ ነገሮች መቃኛ ጅማት ጀዚራ በርኩማ ናቸው ክፍለ ትምህርት ሰላምታ ቅኝት ሰላም የሚለው ቅኝት ሰላምታ ከሚለው የበገና ዜማ የተገኘ ነው መ ዋ ጭ ር ል ር ትተ አውታር በገና ጀ ር ሽኸከ ለ ድምጽ ጣት አውር የመዝሙር አጠናን ሂደት የሚከተሉት የመዝሙር አጠናን ሂደቶች ለሁሉም የመዝሙር ዓይነቶች ተግባራዊ ይሆናሉ በገናውን በትክክል መቃኘት የበገናውን ቅኝት ማስጠናት ዓዓ ዓ ተማሪዎች መዝሙሩን ሰምተውት የማያውቁ ከሆነ በበገና ደረደሩ ማሰማት አደራደሩን ቃል በቃል ያለድምጽ በቁጥር በምት ማሳየት ሐረጉን ያለድምጽ በቁጥር በምት ማሳየት ስንኙን ያለድምጽ በቁጥር በምት ማሳየት አዝማቹን ከላይ በተለማመዱት መሠረት ድምጽ ሇወጡ መዘመር ደጋግሞ መደርደር ችግር ያለበትን ቦታ ደጋግሞ በመደርደር ማስተካከል ችግር ያለበትን ተማሪ መለየትና ተስፋ እንዳይቆርጥ መርዳት በቂ እረፍት ካደረጉ በኋላ ሙሉውን መዝሙር የምት ጊዜውን በመጠበቅ ድምጽን በትክክል ሇወጡ መዘመር ቀዛባባፃዓ ዛባፃዓ መዝሙር ፅ ሆዴ ልመድ ዜ ሆዴ ልመድ ዐንጊዜ የለህምና ዘመድ ከመልመጃ ልደ ባሉት መልመጃዎች ጣት በደንብ ከተፍ በኋላ ዜማ ን መጀመሪያ ያለ ድምጽ በበገና ብቻ በቁጥሩ መሠረት ቀስ ብሉ መደርደር በድምጽ ከበገናው ጋር አብሮ ማዜም ትክክለኛ ድምጽ ማውጣት የምት ጊዜ ጠብቆ መደርደር የመጀመሪያ ዜማ ስለሆነ ድምጽ ከበገናው ጋር በደንብ እስኪዋሃድ ድረስ የምት ጊዜ ጠብቆ ደጋግሞ መደርደር በሕብረትና በግል መዝሙር በጌቴ ሴማኒ በጌቴ ሴማኒ በአትክልቱ ቦ ለኛ ሲል ጌታችን በዓለም ተንገላ። ፉ ዒፍ ዉል ዉኢሥፉሬፌቆጸር በገና በሁሉም የኢትዮጵያ ቅኝቶች ሊደረደር የሚችል የአውታር የክር የማ መሣሪያ ነው እስከ አሁን ድረስ በሀገራችን በኢትዮጵያ በበገና የተደረደሩ ዜማዎችን ስናይ በሚከተሉት በሦስት ቅኝቶች የተደረደሩ ሆነው እናገኛቸዋለን ነ ሄ ጻኣኔ ለ ር ዣ ዲ ኮ ር ከሽ ጀ ር ለ ር ዘነተቁዣ ሞሎ ሙ በኢትዮጵያ ቅኝቶች የድምጽ አደራደር ሕግ ኛው አንቺ ሆዬ ለኔ ቅኝት ኛው ትዝታ ቅኝት ሲሆን ኛውን ግን አንቺ ሆዬ ለኔ ሜጀር አምባሰል ሜጀር ግልብጥ ትዝታ ሲባል ይሰማል የተለያዩ የዜማ ሰዎች ይህንን አንቺ ሆዬ ለኔ ሜጀር አምባሰል ሜጀር ቢሉትም አንቺ ሆዬ ለኔ እአና አምባሰል በሜጀር ደረጃ የለም ስለሚባል ለተማሪዎችም ይህን ቅኝት አንቺ ሆዬ ለኔ ሜጀር ወይም አምባሰል ሜጀር ብሎ ማስተማር አግባብ ስላልሆነ ትዝታና አንቺ ሆዬ ለኔ ቅኝቶች ታዋቂ ከሆኑ ዘፈኖች ስያሜያቸውን እንዳገኙ ይህም ቅኝት ተማሪዎች ቅኝቱን በቀላሉ እንዲያስተውሉትና እንዲረዱት «ሰላም ለኪ» በሚለው ዜማ የመጋቤ ስብሐት አለሙ አጋ የበገና መዝሙር ዜማ «ሰላምታ ቅኝት» የሚል ስያሜ ሰጥቼዋለሆ ስለዚህ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ሰላምታ ቅኝት የሚለው ቅኝት አንቺ ሆዬ ለኔ ሜጀር ወይም አምባሰል ሜጀር ተብሎ የሚጠራውን ቅኝት የተካ መሆኑን ያስተውሉ የአንቺ ሆዬ ለኔ ሜጀር አምባሰል እና የሰላምታ ቅኝቶች የድምጽ አደራደር ሕግ እንደሚከተለው ነው አንቺ ሆዬ ለኔ ር ነ ር ር ፍጭ ። ህል ሐጅ አምባሰል ቅኝት ር ነ ጳባ ር ክረ መጠ ው ሰላምታ ቅኝት ር ሠ ተጋ ጋ ተሠ ትዝታ እና አንቺ ሆዬ ለኔ ቅኝትን ለማስታወስ ትዝታ እና አንቺ ሆዬ ለኔ የሚለውን ዘፈን በማስታወስ ቅኝቶችን መለየት ማስታወስ እንደሚቻል ሁሉ በበገና መዝሙር ደግሞ ዋኔን» የሚለውን የአቶ ታፈሰ ተስፋዬን የበገና መዝሙር ትዝታ ቅኝትን ለማስታወስ እንጠቀምበታለን ንዲሁም «ስለቸርነትህ አምላክ ተመስገን የሚለውን የዘማሪ ይልማ ኃይሉን መዝሙር አንቺ ሆዬ ለኔ ቅኝትን ለማስታወስ እንጠቀምበታለን በዚህ መሠረት በዚህ መጽሐፍ ውስጥ «ዋኔን» የሚለው ስያሜ የትዝታ ቅኝትን ለማስታወስ የገባ ሲሆን ስለቸርነትህ» የሚለው ደግሞ አንቺ ሆዬ ለኔ ቅኝትን ለማስታወስ የገባ መሆኑን ያስተውሉ ማጠቃለያ ሻዚአብሔር ሰውን በአርአያውና በአምሳሉ አክብሮ የፈጠረው ለምስጋና ነው አንድናመሰግነውም ዜማን የምናዜምበት ድምጽ ሰጠን ሰው እግዚአብሐየር በሰጠው ጥበብ የዜማ ድምጾችን ፈልጎ አገኘ »ሺዲ የዜማ ድምጾችን አልፈጠረም ሰው በነፃ ፈቃዱ እነዚህን የዜማ ድምጾች በሰይጣን መሪነት ለኃጢአት ይጠቀምባቸዋል እንጂ ሰውም ሆነ የዜማ ድምጾች የተፈጠሩት ለምስጋና ነው በዜማ ላይ ብዙ ሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር የተሠራው በምዕራባውያን ስለሆነ ሁሉ ነገሩ ምዕራባዊ ሆነ »ጂ በዓለም ላይ ኢትዮጵያዊውን ቅዱስ ያሬድን የቀደመ የዜማ ሰው የለም ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ይህን የዜማ ጥበብ ያገኘው በጥናትና ምርምር ሳይሆን በፈቃደ እግዚአብሔር ወደ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ተነጥቆ ከፃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ሰምቶ ነው የኢኦተቤክንም እስከ ዛሬ እየተጠቀመችበት ያለችው ቅዱስ ያሬድ ያየውን ሥርዓትና የሰማውን ዜማ ነው ቤክናችን በኪዳኑ በቅዳሴው በማሌቱ በሰዓታቱ በግልና በሕብረት በሚዘመሩ መዝሙሮች አሥራ ሁለቱን የዜማ ድምጾች ትጠቀማለች ቤተክርስቲያን የዜማ ድምጾችን በቅዱስ ያሬድ አማካኝነት ከእግዚአብሔር ተቀብላ ለዓለም አበረከተች እንጂ ቤተክርስቲያን ከዓለም የወሰደችው አይደለም ስለዚህ በቅኝቶቻችን ላይ በቂ ጥናት አድርገን ስያሜ የተሰጣቸውንም ሆነ ያልተሰጣቸውን ቅኝቶች የመዝሙር ወይም የዘፈን ስም ሳይሆን በሊቃውንተ ቤክ እና በኢትዮጵያውያን የዜማ ሳይንስ ተመራማሪዎች ትክክለኛ ስያሜ ሊሰጣቸው ይገባል ሙዚቃ» የሚለው ቃል የመጣው «ሚውዚክ እጠር» ከተባለው የግሪክ ቃል ሲሆን ይህንን ቃል ግሪኮች በኪነጥበብ ስም ከሰየሟቸው ሚውዚክር ለተባሉ ዘጠኝ አማልክት ከሰጡት ስም የተወሰደ ስለሆነ የዜማው ሳይንሱን ሳይሆን «ሙዚቃ» የሚለው ስም የጣኦት ስም ስለሆነ በኢኦተቤክ እምነት ሥርዓትና ትውፊት ጣዖታት እድል ፈንታ ስለሌላቸው ይህ ስም በዚህ መጽሐፍ ለትውልድ እንዲተላለፍ አልተፈቀደለትም ዋቢ መጻሕፍት ሰማንያ አሐዱ መጽሐፍ ቅዱስ በኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤክ የተመ ዓም የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት በኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማከር በንግድ ማተሚያ ድርጅት የተመ ኛ ዙም ዓም የክራር መልመጃ ብሥራት ታመነ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ዓም አዲስ አበባ ሙዚቃ የመማሪያ መጽሐፍ አምስተኛ ክፍል ሜጋ ማተሚያ ኢንተርፕራይዝ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ዓም ክብረ ነገሥት።