Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ባለቤት አልባ ከተማ ሃደክ። አናም በማስታወሻዎቹ ላይ የሰፈሩት ቁምነገሮች የግልና ቤተሰብ ወግ ብቻ ሳይሆን በከተማዋ ምርጫ የሚካሄድበትን ቀን በታቀደና በተጠና መንገድ የቀየረ ሆነ ወትሮ የከተማዋ ምከርቤት ምርጫ ከፌደራልና ከልሎች ጋር አብሮ የሚካሄድ ነበር በቡድኑ ጥናት መሰረት እነዚህ ውድድሮች በተመሳሳይ ጊዜ በመካሄዳቸው ምክንያት የአዲሳባ ምርጫ የፓርላማው ላይ አሉታዊ ተጵእኖ አሳድሯል የሚል ነበር። በምርጫ ኢህአድግ በሩን በልበ ሙሉነት ገርበብ አድርጐ የከፈተበት ዋነኛ ምክንያት ምንጩ ይሄ ነበር። ተቃዋሚዎችን ህዝቡ አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት የአብዬታዊ ዲሞከራሲን ትከክከለኛነት ያፀናል በሚል ውጤቱ በተቃራኒው ቢሆንም ነጫጮቹ ዝሆኖች ከምርጫ በኃላ የኢህአድግ የፕሮፐጋንዳና ፓለቲካ ስራ በአቶ መለስና ድርጅቱ እና በረከት ስትራቴጂስቱ መካከል መግባባት ያልተደረሰበትና በጭቅጭቅ የተሞላ ነበር። አልፎ ተርፎም እስከ መዘላለፍና እጅ እሰከ መቀሳሰር የተደረሰበት ነበር። በኢህአድግ ካድሬነት ዘመኔ በሁለቱ ሰዎች መካከል ለወራት የዘለቀ አለመግባባት ያየሁት ለሁለት ያህል ጊዜያቶች ሲሆን ይህ የመጀመሪያው ነበር። አቶ መለስ መዳፉን በሌላኛው ጣቱ አየጠበጠበ በረከት። ኢህአድግን ከዳንኪራና አሼሼ ገዳሜ የምታወጣው መቼ ነው። በመንግስት ውስጥ የድርጅት ስራ መስራት በአንድ በኩል ኢህአድግን ወደ ቢሊየነርነት ቢያሸጋግረውም በሌላ በኩል የፓርቲው የመጀመሪያ መጨረሻ መዳረስ የሚያመላከት ፊሽካ የተነፉበት ሆነ።
ቾቹ በአቶ በረከት የሁለት ምርጫዎች ወግ መፅሀፍ ላይ አሊ ሲራጅ ሳይጠቀስ ጓድ በሚል የወል ስም እንዲተካ ተደርጓል አሊ ሲራጅ የኦህዴድ ማእከላዊ ኮሚቴና የአዲሳባ ኢህአድግ ከንፍ ስራ አሰፈፃሚ ነበር በእርግጥም አቶ በረከት እንደገለፀው አሊ የምርጫ ማታ የአዲሳባ ህዝብ ለምን ይጠላናል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢህአድግ ከፍተኛ ካድሬዎች ድርጅቱ ብለው ሲጠሩ አቶ መለስ ማለታቸው ሆኗል የአቶ መለስ የወል ስም ድርጅቱ ነው አቶ መለስ ራሱ አንድ ነገር ሲፈቅድ ድርጅቱ ፈቅዷል ሲከለከል ደግሞ ድርጅቱ አልፈቀደም ይላል። ይህ ከመዲናይቱ ህዝብ ሉአላዊነት ጋር የሚጋጭ ነው የከተማዋ ህዝብ ሉአላዊነት ፓለቲካዊ ተረጋግጧል የሚባለው ነዋሪዎቿ የመጨረሻዉን የወሳኝነት ስልጣን ባለቤቶች ሲሆኑ ነው ፓለቲካዊ ሉአላዊነት የህዝብ ስልጣን እየተለካ የሚሰጥ ሳይሆን ከራሱና መራጩ ህዝብ የሚመነጭ ነው በተጨባጭ የታየው ግን የከተማው ህዝብ የሚያስተዳድሩትን ተወካዬች የሚመርጥበት ሲያሻው ደግሞ የሚሽርበት ስርአት ተሸራርፉል ሥ ከምርጫ ውጤት በኃላ በአዲሳባ ኢህአድግ እንዴት ይቀጥል የሚለውን ለመወሰን ሶስት ቡድኖች ተቋቁመው ጥናት በማካሔድ የተናጠል ውሳኔ አስተያየት አምጥተው ነበር ከእነዚህ ቡድኖች አንዱ የሆነውና በአርከበ እቁባይ የሚመራው ቡድን ይህንን ጊዜ ጠብቆ እንዲፈነዳ የተዘጋጀ አንቀፅ በማጣቀስ ቅንጅት መዲናይቷን በተረከበ በሁለት አመት ውስጥ የተለያዩ አመፆችን በማስነሳት ፀጥታውን መቆጣጠር አልቻሉም ብለን የከተማውን ምክር ቤት በፓርላማ እንበትነው የሚል አማራጭ አቅርቦ ነበር የሚገርመው ነገር ቅንጅት ሊወነጀልበት የተዘጋጀው የፀጥታ ችግር ለአሱ ተጠሪ ካልሆነው ከፓሊስ ጋር የተያያዘ መሆኑ ነበር። የተፈፀመው ሌብነትና ህግን ያልተከተለ አሰራር በገለልተኛ ኦዲተር ቢጣራ በቅድሚያ የፍርድ ቤት ሳጥን ውስጥ የምናገኛቸው አቶ መለስና አርከበ አቁባይ ይሆኑ ነበር ቾፍች በምርጫ እነ ዶከተር ብርሀኑ አስተዳደሩን ቢረከቡት እንደፈለጉ ወስነው ከተማዋ ከተዘፈቀችበት አረንቋ ሊያወጧት አይችሉም የተባለበት ሌላኛው ምከንያት ይህ ነበር የፌዴራል መንግስቱ ከሀገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማት እንዲበደሩ አንደማይፈቅድላቸው ሳይታለም የተፈታ ነው ከወጭ ተቋማት ፌዴራል እንደበደርላቸው መጠየቅም አፍን ከማበላሸት አያልፍም የፌደራል መንግስቱ በህግ የሚገደድበት የድጐማ ስርአት በሌለበት ሁኔታ እጁን ፈታ አድርጐ በተቃራኒው ለቆመው ከተማው አስተዳደር መና ይወረውራል ብሎ መጠበቅ ማሞ ቂሎነት ነው አስተዳደሩ የሚያመነጨው ገቢ ደግሞ እንኳን ትላልቅ ካፒታል ፕሮጀከቶችን ሊሰራ ቀርቶ የሰራተኛ ደሞዝ ለመሸፈን በየአመቱ የሚንገታገት ነው በእንቅርት ላይ እንዲሉ በምርጫው ማግስት በአቶ መለስ ቀጭን ትእዛዝ የከተማዋ ውልና ማስረጃ እንዲሁም የአንድ ከተማ የደም ስር ተደርገው ከሚቆጠሩት አንዱ የሆነው ትራንስፓርት ከፍል ተቀምቷል አቶ መለስ አጥር ሲያፈርስ የተመለከቱት እነ አባዱላና ግርማ ብሩ የግዛት ማስፉፉት አቅድ አውጥተው ሲሶውን የአዲሳባ መሬት ለመውረር ተንቀሳቀሰዋል ይህም አልበቃ ብሎአቸው በህገመንግስቱ መሰረት ኦሮሚያ ልዩ መብት አላት የሚለውን ዝርዝር አፈፃፀም አስደንጋጭ በሆነ መልኩ እና የአዲሳባን ህዝብ ሉአላዊ መብት ለመንጠቅ በሚያስችል ደረጃ ዶሴ አዘጋጅተው ነበር ይህ አስገራሚ ታሪከ ለኃላ ወግ ይቆይልን። ይህ ሁሉ የማጭበርበር ስራ ተሰርቶ በነጋዴውና ህዝቡ የተቀናጀ ስራ እነ አሊ አብዶና ምከትሉ የነበረው ካሊድ አብድርሀማን የሸንፈት ፅዋ ተጐንጭተዋል ምንም አንኳን በቆጠራው ሰአት በሰሩት አከሮባት ወደ ምከርቤት ቢገቡም በአብዛኛው ምርጫ ጣቢያዎች የተቃዋሚ ታዛቢዎች ባለመኖራቸው ቆጠራ ተጀምሮ ሳይጠናቀቅ ለሊት ዘጠኝ ሰአት ተቋረጠ ምከንያቱ ደግሞ ታዛቢዎች ስለተዳከሙ እረፍት አድርገው ይምጡ የሚል ነበር በከተማዋ የተሰማራን ካድሬዎች በየዞናችን በማደር የአዲሳባን ውጤት በየደቂቃዋ አንከታተል ስለነበር አስደንጋጭ ውጤቶችን መስማት ጀመርን የመጀመሪያው መርዶ የተፈራ ዋልዋ መሸነፍ ሆነ ለተፈራ ከልቤ አዘንኩኝ የዲሞከራሲያዊ ማእከላዊነት እስረኛ ቀጥሎ የደረሰን የአሊ አብዶና ካቢኔዎቹ ሆነ ሁሉም ላይ ህዝቡ በትሩን አሳርፉል ካሊድ ም ል ፕሬዝዳንት ታጋይ ማሚት አስተዳደር ዘርፍ ጣይቱ የምከር ቤት ሀላፊ ቶፊቅ ኢኮኖሚ ዘርፍ ጠዋት ታዛቢዎች ተመልሰው ቆጠራ ሲካሔድ የነበረው እንዳልነበር ሆነ ኮሮጆዎች ግልብጥብጣቸው ወጣ አሊና ካሊድ ቶፊቅና ጣይቱን ትተው አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ከመሀል ኮከብ ያላትን ባንዲራ እያዉለበለቡ ማዘጋጃ ቤት ገቡ። በዚህ አሳዛኝ ታሪከ ወስጥ እኔን ጨምሮ አቶ በረከት ህላዌ ዬሴፍ አዜብ መስፍን አያት የመኖሪያ ቤት ስራ ድርጅትና አዲስ ነገር ጋዜጣ ተሳታፊ ሆነናል። ወደዚህ የህሊና ሸከም ወደ ሆነ ታሪክ ከመግባቴ በፊት ከላይ በአቶ በረከት የምርጫ የአዲሳባ ውጤትን አስመልከቶ በቀረበው ወግ ላይ ተዛንፈው የቀረቡ ታሪኮች በትከከለኛው ገፅታው በማስቀመጥ ልጀምር አንድ ለእናቱ ምርጫ ሊካሔድ የሁለት ሳምንት አድሜ ሲቀረው አራት ኪሎ የሚገኘው የኢህአድግ ቢሮ በሽብርና ጭንቀት ተዋጠ የአዲሳባን ምርጫ እንድናስተባብር የተመደብን ሀያ ከፍተኛ ካድሬዎች በየቀኑ ማታ ማታ ከአቶ በረከት ጋር ግምገማ ማካሔድ ጀመርን የከተማው ነዋሪ ከኢህአድግ በተቃራኒ መሰለፉን ያልተገነዘበው አቶ በረከት አህያ የማይሸከመው ስራ በየቀኑ መቆለሉን አጠናከሮ ቀጠለ እነዚህን አንኳን ለመፈፀም በወረቀት ላይ ለማስፈር የሚከብዱ እቅዶች ሳይጀመሩ ይወድኃሉ ይህንን ተከትሎ በአቶ በረከት የሚቀርበው ዘለፉና ስድብ ለጆሮ የሚሰቀጥጥ ሆነ ካድሬዎቹም ኢህአድግ ቢሮ በየምሽቱ መምጣት ምድራዊ ሲኦል ደርሶ እንደመመለስ ቆጠረ በተለይም አውነቱን ከመናገር ወደ ኃላ የማይሉ ጥቂቶች ይህ የመከራ ጊዜ የሚያጥርበት ቀን በጉጉት እየተጠባበቁም ቢሆን የህብረተሰቡን ተጨባጭ ፍላጐት ከማንፀባረቅ ወደ ኃላ አላሉም ነበር ከእነዚህ ካድሬዎች አንዱ ተከሌ ይባላል። አሱን ማፅከል ተደርገው የተቀረፁ እቅዶች ደራሸ ውሀ ወሰዳቸው በአዲሳባ ምክር ቤት አንድ ለእናቱ ተብላ የተሰየመችው የኢህአድግ መቀመጫ ባዶዋን ቀረች ሀቁይህ ሆኖሳለ አቶ በረከት ጵፎ ባስነበበን ወግ ላይ የኢህአድግ ተወካይ የአዲሳባ ምከር ቤት አባል ሆኖ ቅንጅት በሚመራው ምከር ቤት ሊሳተፍ ተዘጋጅቶ ነበር ብሎናል። ያደራጃሉ የማአከላዊ ኮሚቴ ምርጫ ሲካሔድ የሁሉም ሩጫ የቄዬውን ካድሬ ለማስመረጥ ይሆናል የሻሸመኔ ካድሬዎች ኮሚሽነር ወርቅነህ እስከኪጠቆም ይጮሀሉ አዳራሹን ይቀውጣሉከተጠቆመ በኃላ አፍና እጃቸው ወደ አፎቱ ይመለሳል የአርሲ ሙስሊም ካድሬዎች ለጁነዲን ጅማዎች ለሙከታር የራሳቸው መንደር የሌላቸው አሊያም አስቀድመው ሳያደራጅ በችሎታና ምግባራቸው አንመረጣለን ያሉ ምስኪኖች ቀልጠው ቀርተዋል በቅንነቱና ሀገር ወዳድነቱ የሚታወቀው ሚኒስትር ሶፊያን አህመድ ከእነዚህ ሰወቸ አንዱ ነውበነቀምት በተካሔደው ጉባኤ ጥቆማው ሊጠናቀቅ ሶስት ሰው ሲቀረው በአርባ ሰባተኛ ተራ ቁጥር ተጠቁሞ ነበር የጠቆመው አባዱላ ነበር አቶ መለስና በረከትን በመፍራት ኦህዴድ አራት ኪሎ ኢህአድግ ቢሮ በስራ አስፈፃሚነት የመደባቸው እነ እሸቱና የአብዬታዊ ዲሞከራሲ ጋዜጣ የኦሮምኛ ከፍል ሀላፊው ጋቢሳ ከነጭራሹም ለውድድር አልቀረቡም ከመንደርተኝነቱ በተጨማሪ በኦህዴድ ካድሬዎች ዘንድ ኢህአድግ ቢሮ መስራት እንደ ጠላት ያስቆጥራል። ለድህረ ምርጫ ሁከትና ብጥብጥ ተጠያቂዎች አከራሪ ተቃዋሚዎች ናቸው የሚል መግለጫ በማውጣትና መኢብን የኢህአድግ ታማኝ ተቃዋሚ ሆኖ እንደሚቀጥል በኢቲቪ ቀርቦ መግለጫ ሰጠ አቶ መስፍን በማዘጋጃ ቤቱ ክርክር ሰአት ታማኝነቱን አረጋግጦ የዘንድሮ የአዲሳባ ምርጫ ብርቱ ፉክክር የሚደረገው በመኢብንና ኢህአድግ መካከል ብቻ እንደሚሆን ሌሎቹ ተቃዋሚዎች ህዝቡ አንቅሮ አንደተፉቸውና እዚህ ለከርከር ከተቀመጡት ውጪ ሌላ አባል እንደሌላቸው በኩራት ተናገረ። የከተማው ኢህአድግ ስራ አስፈፃሚ በረከት ቢሮ አስቸኳይ ስብሰባ ተጠራን እኔና ፀጋዬ ከርከሩን ወዳልሆነ አቅጣጫ መምራታችንን ተነገረን የመኢብኑ አቶ መስፍን ኢህአድግ ቢሮ መጥቶ ቅሬታ ማቅረቡ ተነገረን። በረከት በተቃራኒው ድርጅቱ አዲስ አቅጣጫ ማስቀመጡን ነገረን አዲሱ ስትራቴጂ በምርጫው ውጤት ላይ ለውጥ የማያመጡ ፓርቲዎች በውድድሩ እንዲሳተፉ ማበረታታት እንደሆነ ተገለፀልን ይህም በአንድ በኩል በምርጫ ቦርድ በኩል የሚመደበውና ለፓርቲዎች የሚከፉፈለው ገንዘብ በአጩ ብዛት እንዲሆን ኢህአድግ ድርሻውን ውድድር ለሚገቡ ፓርቲዎች እንደሚያከፉፍል ነገረን በመንግስት የተያዙት የሚዲያ ውጤቶች ለተቃዋሚዎች ሰፊ ሽፉን እንዲሰጡ አቅጣጫ መቀመጡን አስረዳን የዚህ ሁሉ ምከንያቱ ኢህአድግ ብቻውን ሮጦ አሸናፊ ሆነ ከሚለው ወቀሳ ለመዳን መሆኑን ማብራሪያ ሰጠ። በአዲሳባ የዘረጋነው ኔትወርከ አንድ መራጭ ድምፅ ሰጥቶ ሲወጣ የምናውቅበት ነበር ለዚህ እንዲረዳ ከአንድ ሚሊዬን ብር በላይ በማውጣት የሞባይል ካርድ ገዝተን አከፉፈልን በከተማዋ ከ ያላነሱ ምርጫ ጣቢያዎች ሲኖሩ በእያንዳንዱ ጣቢያ አባላት እንዲመደቡ ተደረገ አባላት በምሳ ሰበብ ጣቢያቸውን ለቀው እንዳይሔዱ ተመሳሳይ መጠን ያለው የምሳ አበል ወጪ ተደረገ እነዚህ አባላት አንድ ሰው መርጦ በወጣ ቁጥር ቀበሌ ላይ ላለው ኮሚቴ በሞባይል መልእከት ያስተላልፉል። ሐፋፋቱ የአዲሳባ ኢህአድግ ስራ አስፈጳሚዎች በረከት ቢሮ ለስብሰባ ተቀምጠናል። ናየየየየየ ምእራፍ የጥፉቱ ቅብብሎሽ ከመመሪያ ቁጥር አንድ ወደ ሁለት ወደ መመሪያ ቁጥር አንድ ። መመሪያ ቁጥር አንድ በከተማዋ የሚገኙ ህገ ወጥ ይዞታዎችን ወደ ህጋዊ ለመለወጥ በሚል ሽፉን ተዘጋጀ በተቃራኒው መመሪያውን ለማፅደቅ አንድ ሳምንት ሲቀረው የተዘረፈው መሬት ብዛት በሁለት አመት ውስጥ ያለው በአጠቃላይ ተደምሮ በአጥፍ ይበልጥ ነበር በወቅቱ የካቢኔ አባል የነበረው አበበ ዘልኡል ያቀረበው ጥናት አመላከተ አበበ በቁጭት ተሞልቶ መመሪያውን ማውጣት አልነበረብንም። በመመሪያ ቁጥር አንድ ላይ ቀጥሉ የተነሳዉ ለምን ቁጥር አንድ ተባለ የሚለው ነበር። መመሪያ ቁጥር አንድን ተከትሎ የተዘረጋው የጥፉት ቅብብሉሽ በዚህ አላበቃም በመንግስት ስልጣን ላይ ያለው ህገ ወጥ ሀይል የግለሰብ ቤት ኪራይና የቤት ችግር አናቱን አዙሮት የጨረቃ ቤት በመግዛት ቤተሰቡን ሰብስቦ የሚኖረውን የከተማው ነዋሪ ለሁለት ከፍለው ቀይ መስመር ያሰምራሉ ከመስመሩ ወዲህ በመመሪያ ቁጥር አንድ የሚሸፈኑ ወዲያ ደግሞ በቅርብ ጊዜ የሚፈርሱ የሚል ትእዛዝ ያስተላልፉሉ የማፍረሻ ማስጠንቀቂያዎች ይዥጐደጐዳል ጥሪቱንሽጦ ተበድሮና ተለቅቶት የጨረቃ ቤት በመግዛት ኑሮ የጀመረውና ከመስመሩ ወዲያ ያለው ህዝብ ከፓሊስና አፍራሽ ግብረ ሀይሉ ጋር ለመፉለም በየቦታው መደራጀት ጀመሩ የጦር መሳሪያ እስከመታጠቅ ደረሱ በከተማዋ በሚገኙ ማስፉፊያ ወረዳዎች የተሰሩትን የጨረቃ ቤቶች ለማፍረስ የፌዴራል እና የአዲሳባ ፓሊስ ከአፍራሽ ግብረ ሀይሉ ጋር በመቀናጀት ዘመቻ ጨረቃ መግባት ለማስፈፀም ተንቀሳቀሱ። በጨፌው ግምገማ የደህንነቱ ዘካርያስን የሚስጥር ስራ ሳንገልፁ ሴትየዋን ለማሸሽ አሊ አብዶ ያደረገውን ሩጫ አነሳን ሰፊ ውይይት ተካሂዶት ጥፉቱ የእሱ አንደሆነ ተደመደመ ከሁለት አመት በኃላ ነገሮች ተረጋግተዋል በሚል ሴትየዋሁለተኛ ዲግሪዋን ጨርሳ ከባህር ማዶ መጣች አርከበን ቀርባ አወያየቸው የመብረቅ ማህበር ችግር በመመሪያ ቁጥር ሁለት ተመልሷል በማለት የመሬት አስተዳደር ከፍተኛ ባለስልጣን አድርጐ ሾማት የቀድሞውን ዶሴ እንደማስፈራሪያ አየተጠቀመ በርካታ ህገ ወጥ ደብዳቤዎች አስፈረማት አንድ ጊዜ በሌብነት የተነካካ ባለስልጣን አፉን ለጉሞ የተባለውን አየፈፀመ እንደሚኖር ከራሱ ልምድ ያውቀዋልአሷም ብትሆን ድመት መንኩሳ ነበረችና የቀድሞ ወዳጄ የቀበሌ ካድሬ ዘርሙ ይዛ በድጋሚ ሌብነት ውስጥ ተዘፈቀች ተያይዘው ወህኒ ወረዱ። ኢህአድግ ቢሮ የአዲሳባ ኢህአድግ ስራ አስፈፃሚ አያለሁ ከቃሊቲ የመጣ መልእከት ደረሰኝ። አጀንዳው በሙሉ መመሪያ ቁጥር ሁለት በአስቸኳይ መውጣት አለበት ሆነ ይህን ተከትሎ አርከበ ለአማካሪ ምከርቤቱ ባቀረበው የሁለት አመት የከተማው የልማትና መልካጳም አስተዳደር እቅድ ላይ የሚከተለውን ጵፎ ቃል በቃል አነበነበ አስተዳደሩ ህገ ወጥነትን በማያበረታታና ከማስተር ፕላኑ ጋር በማይጋጭ መልኩ ህገ ወጦችን ህጋዊ የሚያደርግ መመሪያ ቁጥር ሁለት ያወጣል። መመሪያ ቁጥር ሁለት በተግባር ላይ ዋለ አሊ አብዶ ነፃ ወጣ ። ከውስጥ ወደ ወጭ ስለሆነ የተሸራረፉና ያልተነገሩ ታሪኮች አይጠፉበትም ከምርጫ በኃላ የተካሄደው የመሬት ወረራ በታቀደ መልኩ በአቶ መለስ ቀጭን ትእዛዝና በአርከበ ቀጥታ መሪነት የተከናወነ ነበር ይህ የውንብድና ስራ እኔ ከሞት ሰርዶ አይብቀል አንዳለችው አህያ የተፈጳመ መንግስታዊ ንቅዘት ነው የከተማው ባዶ መሬት ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ ተዘርፉል እዚህ ቦታ ራቁቱን የተቀመጠ መሬት አለ በሚል ጥቆማ የተሰረቀ ይህን ተከትሎ አዲሳባ መሬት አልባ ሆናለች የአዲሳባ መሬት ወረራ የመጨረሻው ጫፍ ላይ የደረሰው አርከበ አቀባይ ስልጣኑን ለባላደራው ከማስረከቡ አስቀድሞ በነበሩት ወቅቶች ነበር። ቁጥር ሁለት። እነ ግርማሏዩዬን አራት ኪሎ ኢህአድግ ቢሮ ተቀምጠው የአፉርን ጋንቤላንቤኔሻንጉልንና ሱማሊያ ክልሎችን አቅድ ያወጣሉበጀት ይመድባሉ ካቢኔ ይሾማሉ ያባርራሉ ለኢህአድግ ቢሮ የስራ አፈፃፀማቸውን ለማሳየት የሚያዘጋጁትን ሪፓርት እንደ አኔ ለማየት ያገጠመው ሰው በቀላሉ አንድ ነገር ይታዘባል ለአብነት የሱማሊያ ከልል ሪፓርት ይህን ይመስላልምዕራፍ አንድ የሱማሊያ ከልላዊ መንግስት ከመደገፍ አኳያ ከፍል አንድ የከልላዊ መንግስቱንና የሶህዴፓ ፓርቲ አመታዊ እቅድ ማውጣት ከፍል ሁለት በጀት ማዘጋጀትና ማደላደል ከፍል ሶስት የአመራር ሀይል መመደብና ሽግሽግ ማድረግ ክፍል አራት ልማታዊ ባለሀብቶችን መፍጠር ነከፍል አምስት ፀረ ሰላሞችን ከመከላከል አንፃር የተሰጠ ድጋፍ በግለሰብ ደረጃም የኢህአድግ መደጋገፍ አቅጣጫ ተመሳሳይ ነው የፌዴራል ጉዳዬች ሚኒስትር ዶከተር ሽፈራው ከላይ አባይ ፀሀዬ ከጐን በሽማግሌው ስብሀት ነጋ ከታች ደግሞ የህውሀት ነባር ታጋይ የነበረው መራሳ ይደግፉታል የመከላከያ ሚኒስትሩ ሲራጅ ፈርጌሳ ከላይ ጀነራል ሳሞራ ከጐን ኩማ ደመቅሳ ይደግፉታልየፍትህ ሚኒስትር የነበረው ብርሀን ሀይሉ በአቶ በረከት ስምኦን ይደገፉል ነገር ነገርን ይወልዳልና አንድ ጊዜ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና የሚባልየግል ፕሬስ ባለቤት ለፍትህ ሚኒስቴር የጋዜጣ የፍቃድ ጥያቄ ያቀርባል ሚኒስትር ብርሀን ምላሽ ከመስጠቱ በፊት ድጋፍ ፈልጐ አኛ ጋር ይመጣል አቶ በረከት እሳት ጐርሶ ኢህአድግን ከቀበርከ በኃላ ለሾቪኒስቱ ፍቃድ መስጠት ትችላለህ ። ፆ የአዲሳባ ስራ አስኪያጅነት ሙያ ተኮር በመሆኑ አለም አቀፍ ማስታወቂያ ወጥቶ ከፍተኛ ፕሮፌሽናሎችን በማወዳደር ይፈፀም የሚል አስተያየት አቶ መለስ ጋር አስኪደርስ ድረስ ተቀባይነት አግኝቶ ነበር አቶ መለስ ይህን አስተያየት እንደሰማ በቁጣ የአዲሳባን ስራ አስኪያጅነትን አሳልፎ መስጠት ማለት ወደ ጥልቅ ጉድጓድ ኢህአድግን ከመወርወር አይተናነስም አለ ርግጥም አቶ መለስ እንዳለው የአዲሳባ ስራ አስኪያጅነት ስልጣን ከከንቲባው በላይ ነው። ም» ኢህአድግ መዲናይቱን በተቆጣጠረ ወቅት አቶ በረከት ቢሮ ውስጥ እኔህላዌካሚልፀጋዬና ፍሬህይወት ተሰብስበን ከንቲባ ስራ አስኪያጅ የካቢኔ አባል አየመለመልን ነበር ስብሰባው ሳይጠናቀቅ ከቤተ መንግስት የአቶ መለስ ስልከ ተንጫረረ አርከበ ለስራ አሰኪያጅ የሚሆን ይዞ አየመጣ ስለሆነ ተቀበሉት የሚል አጭር ትእዛዝ ሰጠን ስልኩ ሲዘጋ ሀላዌ ህሆዩ ርዐገፀ። ወቅቱ ለአርከበ ወሳኝ ነውና በድል አድራጊነት ሰሜት የምንግዜም ባላንጣው ቢሮ ተገኘጊዜ ሳያጠፉ መለስ ስራ አስኪያጅ የሚሆኑ ሰወች መልምል ባለኝ መሰረት ሁለት ጠንካራ ካድሬዎች ይዜ መጥቻለሁ የመጀመሪያ ምርጫዬ መኩሪያ ሀይሌ ነው የደኢህዴን ሊቀመንበሩ ሀይለማርያምን አስተያየት ጠይቄው ደቡብን ባዶ ተደርግብናለህ እንጂ ሁነኛ ሰው መርጠሀል ብሎኛል በሁለተኛ ደረጃ ሀይሌ ፍስሀ ቢሆን የሚል አስተያየት አለኝ የህውሀት ቢሮ ለመስጠት አንገራግረው ነበር ግን አዲሳባ ላይ ጠንካራ ሰው መመደብ ወሳኝ መሆኑን ነግሬያቸው ፍቃደኛ ሆነዋል። የጨለማው ዘመን መሪ ወደ ነበረው አሊ አብዶ ግምገማ ሀብቱ የሚባል የአዲሳባ የትምህርት ቢሮ ሀላፊና የካቢኔ አባል አሊን አንድ ጥያቄ ጠየቀው ከፉይናንስና ኢኮኖሚ ቢሮ ሀላፊዋ ገነት አበራ ጋር ያለህ ግንኙነት እስከምን ድረስ ነው። ሴትየዋ የኢህአድግ አባል ስላልነበረች በግምገማው አልተገኘችም ስጋዋ ከመቦጨቅ ግን አልዳነም የከተማውን ፉይናንስ በተለይም የበጀት ዝግጅትና ገቢ መቀመቅ የከተተቸው አሷ መሆኗ መግባባት ላይ ተደረሰ ግን ደግሞ እንደዚህ ከፍተኛ የብቃት ማነስ ችግር እንዳለባት እየታወቀ እንዴት ከተፈራ ዘመን አስከ አሊ አብዶ አገለገለች የሚለው የካድሬው ያልተገለፀ ሀሜት ሆነ በኢህአድግ ቤት መኖር ሁሌም ከኃላ እንደ ጅራት የሚጐተት ጉድ አለውና ቀኑን ጠብቆ ብቅ አለ ወይዘሮ ገነት አበራ የአዲሱ ከንቲባ አርከበ እቁባይ የፉይናንስና ኢኮኖሚ ቢሮ ሀላፊ ሆና ካቢኔውን ተቀላቀለች ታሪከም ራሱን ደገመ መጀመሪያ አሳዛኝ ቀጥሎ ቧልት በሚመስል መንገድ። በዚህ ጉዳይ የመጀመሪያው ተጠያቂ አቶ መለስ ሲሆን አርከበ የማስፈፀም ሚና ብቻ ነበረው በመሆኑም በአርከበ የከተማ ካቢኔ ውስጥ የጉራጌ ተወላጅ የሆነ ካድሬ አልነበረም ከከፍለ ከተማ ከነበረው ስራ አሰፈጳሚ ውስጥ ሁለት ካድሬዎች ብቻ ነበሩ የላፍቶው ሚፍታህ አብዶና የጉለሌው ዳንኤላ አርጋው ከአመታት በኃላ ሚፍታህ ወደ ቃሊቲ ሲወረወር ዳንኤል ከስራና ከድርጅት ካድሬነት ተባሯል የለውጥ ኮሚቴ አባላት ስራቸውን አጠናቀቁ ይህንን በማስመልከት አርከበ በቴሌቪዥን ቀርቦ መግለጫ ሰጠ። የአቶ መለስም ሆነ አባይ ንግግር ትከክል ነበር የአዲሳባ ኢህአድግ መዋቅር እንኳን የመሪነት ሚና ሊጫወት ቀርቶ ለህዝብ ጭራነት ብቁ አልነበረም ካድሬውና አባላቱ በተግባር ኢህአድግ አልነበሩም ዘባተሎውን አሊ አብዶ ጨምሮ የአብዬታዊ ዲሞከራሲ ምንነትና ግብ ምን አንደሆነ የማያውቁ ነበሩ አቶ መለስ ይሄንን ከፍተት በማየት የተማረ ሰው ፈልጉ ያለው። ደመማ ቋሜሮረፇያልዷ በአራት ኪሎ ኢህአድግ ቢሮ በረከት በመራው ግምገማ ይህንን አባባል የሚጣሉ ግኝቶች ተደምጠዋል ምንም እንኳን በመጵሀፉ የትኛውም ገጵ ላይ ባይጠቀሱም በረከት አንድ ጊዜ ፓናዶል ሌላ ጊዜ ኖባልጅን እየዋጠና ቁና ቁና እየተነፈሰ ያዳመጣቸው ወጐች የሚከተለውን ይመስላሉ የሚጨመሩ አቃዊ አባዱላ ገመዳ ህ ጣይቱ ገሬ ባለቤቷ ቀቅራንዬአቃቂ ሰጥቷል የሚባል ካድሬ። ገ ተንሳይ ከብዙ አውጫጭኝ በኃላ የገለፀው ተጠቃሎ ሲታይ የሚከተለውን ይመስላል መጀመሪያ የሚኖርበትን የቀበሌ ቤት በሀምሳ ሺህ ብር ሸጠ ቀጥሎ አሊ አብዶን አስፈራርቶ ቦሌ ላይ አይን መሬት ወሰደ የትምህርት ቢሮ ቁሳቁስና ማቴሪያል በመጠቀም ቪላ ቤት ሰራ። በወቅቱ ዶከተሩ የስራና ከተማ ልማት ሚኒስትር የነበረ ሲሆን አርከበ ደግሞ የዶክተሩ ምከትል ነበር ዳንኤል ለሶስት አመታት ስራ አጥቶ ተንከራተተ ቅሬታዉን ለማሰማት ያልረገጠበት ቦታ የለም በመጨረሻም ሰአቶ መለስ የጉራጌ መራሹ አብዬት እንዲቀለበስ ግንባር ቀደም ሚና እንደነበረኝ ከአንተ በላይ ምስከር የለኝም የሚል ደብዳቤ ላከ የአቶ መለስ ቅርጫት ውጦ አስቀረው ሀገር ጥዬ ከወጣው ከአመታት በኃላ ጓደኛዬ ዳንኤል እቤቴ ድረስ በቴሌቭዥን መስኮት ብቅ አለ ያውም ቤተመንግስት ግቢ ውስጥ ወቅቱ ደግሞ የአቶ መለስ ዜና አረፍትን አስመልከቶ ህዝቡ ለቅሶ የሚደርስበት ነበር አናም ዳንኤል የአልቃሽ ሰራዊት አሰልፎ አንዴ ከፊት ሌላ ጊዜ ከኃላ ይመራል። የምርጫ ኮሮጆ ግልብጥብጡን በማውጣት አሊን ከመሸነፍ ታደገው አሊ አብዶም ቢሆን የሉሌን ውለታ መርሳት አልፈለገም ራሱን የማልረባ ዝርከርከ ዘባተሎ ባለ በወሩ የተካሄደ ምደባ ላይ አውራ ሆኖ ተገኘ ለነባሩ የአዲሳባ ካድሬ በከፍለ ከተማ ለመመደብ የመጀመሪያ ዲግሪ እንደ ቅድመ ሁኔታ ቢወሰድም ለሉሌ አንደ ህውሀት ካድሬዎች ኛ ከፍል በቂው ተደርጐ እንዲያዝለት አደረገ በዘመነ አርከበ የአዲስ ከተማ ከንቲባ እንዲሆን አደረገ በአፍሪካ ትልቁ ገበያ የሆነችውን ውስብስቧን መርካቶ መምራት በሉሌ አቅም የሚሆን አልነበረም የታቀዱ ስራዎች ዘጭ ብለው ወደቁ በተለይ ከፍተኛ ግብር ይሰበሰብበታል ተብሎ ተስፉ የተጣለበት የንግዱ ዘርፍ ነጠፈ አርከበና ሉሌ ግብግብ ገጠሙ አፍታም ሳይቆይ አርከበ ከትግራይ ሮማን ተስፉይ የምትባል ካድሬ አምጥቶ ስራ አስኪያጅ ሾመ ሮማን ወፍ ከሰማይ የምታረግፍ በንግግሯ አራት ነጥብ የማታውቅ የመቀሴ ጩልሌ ናት። አዲሳባ ከንቲባ አንዲሆን ፈልጐ የነበረውን መላኩ ፉንታ የጉምሩክ ሹሙን ገ ዋህድየኤርትራውያን ንብረት የዘረፈውን የደህንነት ሀላፊ ወልደስላሴንበሚሊዬን ብር ምልጃ ልጆቻቸውን ቻይና ያስተማሩት ሽማግሌው ስብሀት ነጋና አርከበ የስብሀት ነጋ የአጐት ልጅ የሆነውና በሚሊዬን ዶላር የኤፈርት ገንዘብ ይዞ የተሰወረውን ጌታቸው በላይ የሁለት ቪላ ቤት ባለቤቱን አባዱላ ሞላጫ ሳሙና አያለ የሚጠራቸውን አምባሳደር ግርማ ብሩና ሚኒስትር መኩሪያ አቶ ሽጉጤን በስተርጅና የቡና ልማት ስራ አስኪያጅ ስላደረገው ሽፈራው ሽጉጤ የዛፍ ላይ እባብ ብሎ የሚጠራውን አርከበ የጨለማው ዘመን ንጉስ አሊ አብዶን ቪላቸውን በዶላር አከራይተው ግብር የማይከፍሉትን አምባሳደር ተሾመ ቶጋንና አምባሳደር ገነት ዘውዴን የደሀ አጥንት የጋጠውን አምባሳደር ቶፊቅ አብድላሂንጀነራል ገ ተንሳይንዶከተር አብርሀምን ሀይሌ ፍስሀንአዜብ መስፍንንምትኩ ሀበነን ሮማን ተስፉይን እናም አቶ በረከት ከራስ ተሻግሮ ስሌላ በጥቅሉ መናገር ውጤቱ አስከፊ ይሆናል። የጡት አባቷ የሆነውን አርከበ አቀባይ አጅባ ወደ ስራና ከተማ ልማት ሄደችባላንጣዋ ሉሴ ደግሞ ወደ ኢህአድግ ቢሮ የአዲሳባ ከንፍ በመመደብ ወደ ህላዌ መጣ በኢህአድግ ቢሮ የካድሬነት ዘመኔ የሮማን ስም በተነሳ ቁጥር አብሮ የሚደመጥ አስደማሚ ታሪከ አላት አማተር ሌብነቷን ያሳበቀችበት ነበር ሚስጥሩን ፈልፍሎ ያወጣው ይሳቅ ቆሪጥ በመሆኑ ዘመን ተሻጋሪው ካድሬ በሚለው ማስታወሻ ላይ እንዲካተት ተደርጐ ነበር። ዘመን አለፈና አዲሱ ለገሰን ለማገዝ ኢህአድግ ቢሮ የስልጠና ማእከል ተመደበ የአዲሳባ ልጆች የሆኑ ፀጋዬ ፈለቀና ፀጋ የሚባሉ የላፍቶና የቦሌ ካድሬዎች አንድ መሬት ወስዳችኃል ተብለው ከካድሬነትና የመንግስት ስራ ተባረዋልበተቃራኒው ቀራንዬ ላይ የተንጣለለ የመንግስት ቤት የወሰደውና ቦሌ ላይ መሬት የወሰደው ነጋ በርሔ በሳይናሳዊ መተካካት ማእቀፍ ውስጥ ተካቶ አዲሱ ለገሰን ለመተካት እየተዘጋጀ ነው ምስኪኑ አባተ ድራማውን የተገነዘበው ውሎ ካደረ በኃላ ነበር። የውስጠ ድርጅቱ ግምገማ ግልጵ ነው ለህዝቡ በሁለት ምርጫዎች ወግ የተገለፀበት አግባብ ደግሞ ውስጠ ወይራአርከበን በተመለከተ የድርጅቱ ከፍተኛ ካድሬዎች ያላቸው አመለካከትና ለህዝቡ እንዲሰርጵ ያደረጉት አስተሳሰብ ተቃራኒ ናቸው ከአቶ መለስ ጀምሮ ሌሎቹ ዝሆን ካድሬዎች በውስጠ ድርጅት ስብሰባ የአርከበን የፓለቲካ ድህነትመርህ የሌለው መሆኑን ውግንናው ኢህአድግ ቆሜለታለሁ ከሚለው ማህበተሰብ በተቃራኒ እንደሆነ የራሱን ገጵ ሲገነባ መከረሙን በግልጵ ይናገራሉ አቶመለስ የአዲሳባ ካቢኔ አባላትና ካድሬዎች በተሰበሰቡበት ቀለም ቀቢ። ይህን ድርጊቱን የአዲሳባ ምርጫ የምናስተባብር ካድሬዎች ኢህአድግ ቢሮ በሚኖረን የምሽት ስብሰባ ላይ ተናገረ። በመሆኑም የኢህአድግ ካድሬዎች አርከበን በተመለከተ ያላቸው የውስጥ እይታ ዝናውን ለማግዘፍ የተቀየሱ እስትራቴጂዎችና ያስገኙትን ውጤት ወደ መመልከት እንግባ የአዲሳባ ለውጦች ክንዴ የአካባቢ ልማት ሀላፊ ሁሉም ነገር ወደ አዲሳባኢኮኖሚ ሸራተን ከአሊ አብዶ ጋር ረየጐብልስ ቲዎሪ ፕሮፐጋንዳው ጐብልስ በአዲሳባ ታፔላው ዘጠኝ ድስት የፓለቲካ ደሀ ሐይለማርያም የሚመልሳቸው ቀላል ጥያቄዎች ዝዋይ ንግግር የአዲሳባ ለውጦች አዲሳባን የለውጥ ምከንያቶች በማስታወሻው የመጀመሪያው ከፍል ለመግለጵ ተሞከሯል የአርከበን ቡድን ከትግራይ ማስወጣት የአዲሳባ ህዝብ በምርጫ የወሰደው አርምጃ አገራዊ አደጋን እያስከተለ መሄዱና አነ ጋዳፊን በመሰሉ የአፍሪካ መሪዎች አዲሳባ እየደረሰባት ያለው ጫና በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው አነዚህ ምክንያቶች በምንም መልኩ የኢህአድግን ከተማን በገጠር ስሌት መምራትና የነፍጠኛ ከተሞችን ማዳከም የሚለውን እቅድ የቀየሩ አይደሉም በተመሳሳይ የአዲሳባ ህዝብ ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሉአላዊ መብቶችን ያጐናፀፉ አይደሉም ተደጋግሞ እንደተገለፀው ከ ሚሊዬን በላይ የሚሆነው ህዝብ የመረጠውን ምከርቤት ፓርላማው ፀጥታ ማስከበር አቅቶሀል ብሎ የመበተን ስልጣን አለው ። ውይይቱ ነዋሪዎች ሴቶችና ወጣቶች በሚል አንዲከፉፈልና ሶስት መድረኮች እንዲሆኑ አቶመለስ አሳሰበን የተወያዬች ዋነኛ መመዘኛ በግልጵ ተመዝግበው ከሚንቀሳቀሱ የተቃዋሚ አባላት ውጪ ሁሉንም የህብረተሰብ ከፍል የሚወክሉና ነዋሪው ወኪሎቼ ናቸው ብሎ ከሚያምንባቸው ጋር ብቻ እንዲሆን አቅጣጫ ተቀመጠ ይህም ከዚህ በፊት ሲሰራበት የነበረው ሰዎችን በብሔር ማንነታቸው የመከፉፈልና ማወያየት ስራ አዲሳባ ላይ አንዲቋረጥ በምትኩ በማህበራዊና አድሜ አደረጃጀታቸው ብቻ እንዲሆን ተደረገ ከአቶ መለስ ጋር በተሰበሰብን ወቅት የብሄር አዘል ስብሰባ ይሻላል የሚል አስተያየት ቀርቦ የነበረ ሲሆን አቶ መለስ ንዴት በተቀላቀለበት ሁኔታ ወደድንም ጠላንም የብሔር ፓለቲካ አዲሳባ ላይ አፈር ልሶ የማይነሳበት ደረጃ ላይ ደርሷል የሚል አስገራሚና ያልተጠበቀ አስተያየት ሰጠ። የፌደራሉን አስቀድሞ በሁለት አመቱ የአዲሳባ ቢሆን የከተማው ህዝብ በፌዴራል ደረጃ ኢህአድግ መንግስት ሆኖ እያየ ከተማዋን እንዲያስተዳድሩ ተቃዋሚዎችን የመምረጥ ፍላጐት አያድርበትም በመዲናይቱ የሚኖሩ የኢህአድግ አባላትም በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የፌዴራል መንግስት ኢህአድግ በሆነበት ሁኔታ ለከተማዋ መስተዳድር ተቃዋሚዎችን ብትመርጡ ልማቱ ወደኃላ ይቀለበሳል። በአጠቃላይ ሲታይ ኢህአድግ ለ ሚሊዬን ህዝብ ከፅሚሊዬን በላይ አባላትና የምከር ቤት ካድሬዎችን በማሰማራት በአባላት ብዛት በአለም ተወዳዳሪ የሌለው ፓርቲ ሆኗል። ኢህአድግ ከባለሀብቶች ራቅ በማለት ነጳነቱን ጠብቆ መኖር እንዳለበት በማስገንዘብ ከምርጫ በኃላ በምሁራንና ባለሀብቶች ላይ የተቀመጠው ጥብቅ መመዘኛ ባልተጳፈ መልኩ የተቀየረ ቢሆንም የእነ ህላዌ ቡድን ይዞ የመጣው መደበኛ አሰራር ሆኖ እንዲፀድቅ በማሰብ ነበር ቡድኑ አብዬታዊነትን ከቁልፍ መመዘኛ በማሰናበት በፉንታው በህብረተሰቡ ዘንድ ታዋቂነት ያላቸውን ምሁራንና ባለሀብቶችን በአጩነት መመልመል ጊዜው የሚጠይቀው እንደሆነ አመላከተ ቡድኑ የምርጫ ሽንፈትን ተከትሎ ባሰአደራ አስተዳደሩ ስልጣኑን በተረከበ ወቅት ኢህአድግ በከተማዋ ላሰማራቸው ከ በላይ የሙሉ ጊዜ ምድብተኛ ካድሬዎች ደሞዝ የከፈሉትን ባለሀብቶች በምሳሌነት በማንሳት የድርጅቱ የጀርባ አጥንት እንደሆኑ አስታወሰ በተለይም የሼህ መሀመድ አልአሙዲ ሸሪከ የሆኑት አቶ አብነት ገ መስቀል ለዞን ሶስት ኢህአድግ ጵ ቤት ግማሽ ሚሲዬን ብር በመስጠት ከ በላይ ለሚሆኑ ካድሬዎች ለአንድ አመት ያህል ወርሀዊ ደሞዛቸውን በመቻላቸው የድርጅቱ የቁርጥ ቀን ተደርገው መወሰድ እንዳለባቸው በምሳሌነት ተነስተዋል። በሁለት ሳምንት አንድ ጊዜ በማዘጋጃ ቤት በመገኘት የሚያደርገው ስብሰባ ራሱን አንደ አስፈጳሚ እንዲቆጥር አድርጐታል። የከተማው ኢህአድግ ስራ አስፈፃሚ በረከት ቢሮ አስቸኳይ ስብሰባ ተጠራን እኔና ፀጋዬ ከርከሩን ወዳልሆነ አቅጣጫ መምራታችንን ተነገረን። በመሆኑም መድብለ ፓርቲ ስርአት ለመመስረት ከሁለት እስከ አስር የፓለቲካ ፓርቲዎች መገኘትን እንደ መሰረታዊ ነገር የተቀመጠው በኢትዬጺያ የሚሰራ አይደለም ከሁሉም በላይ ኢህአድግ የሚመራበት አብዬታዊ ዲሞከራሲ ርእዬተ አለም የተፈጥሮ ባህሪው መድብለ ፓርቲን የሚያበረታታና የሚፈጥር አይደለም ዜጐች ሲነሱና ሲቀመጡ ሲበሉና ሲተኙ በህልማቸው ሳይቀር ስለአንድ ነገር ብቻ እንዲያስቡ ማድረግን እንደ ግብ የሚወስድ ፍልስፍና የተለየ አማራጭን ሊቀበል የሚችል ተከለ ሰውነት ሊኖረው አይቸልም ይህ አስተሳሰብ ገዥ ሆኖ የበላይነት ካላረጋገጠ በስተቀር ሀገሪቷ የመበታተን አደጋ ሊያጋጥማት ይችላል ከዚህ በፊትም ኢትዬሏያ አጋጥሞት የነበረውን መስቀለኛ መንገድ በድል የተሸጋገረችው በአብዬታዊ ዲሞክራሲ ነው ብሎ የሚያምን ድርጅት አብዛህነትን ሊከተል የሚቸል መተከል የለውም ፋቶፋ ኢህአድግ እንደ መድብለ ፓርቲ ሁሉ አብዬታዊ ዲሞክራሲን አስመልከቶ የሚሰጠው ትርጉምና መፃኢ እድል ከሁኔታዎች ጋር የሚለዋወጥና ከዘመን ዘመን የሚለያይ ነው ኢህአድግ ባጋጠመው የውስጠ ድርጅት ቀውስና የአለም አቀፍ ሁኔታ መቀያየር ምከንያት አብዬታዊ ዲሞክራሲ ለሶስት ያህል ጊዜያት ሙሉ ልብሱን ቀይሯል። በኃላ ያለው ኢህአድግና አብዬታዊ ዲሞክራሲ አንድ አይነት አይደሉም ከ አ ም። አቶ መለስ በከተማይቱ ኢህአድግ የሚባል ፍጡር ስለሌለ ዋነኛ አቅጣጫ ጥራት ያለው ድርጅት መፍጠር ይሆናል የሚል አቀረበ።