Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
» ይህ ትምህርታቸው አዋልድ መጻሕፍትን እየጻፉ እና እየተ ቀበሉ ተጉዘዋል ይህ ማለት ግን በመጻሕፍቱ ላይ ፈተና አልደረሰም ማለት አይደ ለም ፈተናዎቸን በጥቂቱ ቀጥለን እናያለን ፅ ቅሰጣ የቅሰጣ ሥራ የተጀመረው በአሥራው መጻሕፍት ላይ ነው አሥራው መጻሕፍትን በመተቸት ግኖስቲኩች እና ሐዲሳን ፕላቶናውያን ከኛው እስከ ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሠይፋቸውን መዝዘው ነበር ለዚህም የተጠቀሙበት መንገድ አስመ ስሉ መጻፍ ከመካከላቸው እየነቀሱ መተቸት እርስ በርስ እንደሚጋጩ አድርጉ ማሳየት በፍልስፍና መንገድ ማሄስ ወዘተ ናቸው በተለይም በዘመነ ሐዋርያውያን አበው ቤተ ክርስቲያንን ሲያዉኩ የነበሩት ግኖስቲኮች የራሳቸውን የፈጠራ እምነት እየጻፉ በሐዋር ያት ስም እየሰየሙ ያሰራጩ ነበር በዚህም መሠረት የቅዱ ሳን ሐዋርያትን ወንጌላትና መልእክታት ከግኖስቲኮች የፈጠራ ድርሰቶች በመለየት በልዩ ልዩ ጉባኤያት መጻሕፍቱን መርጠው በቀኖና ቤተ ክርስቲያን ደነገጉዋቸው የአዋልድ መጻሕፍት ዋናው ተጋላጭነታቸው የሚመነጨው በቀኖና ያልተወሰኑና ተሰፍረውና ተቆጥረው ያልተቀመጡ ከመሆናቸው ነው ከዚህም የተነሣ በባለቤትነት ከያዚቸው አብያተ ክርስቲያናት ወይም ግለሰቦች የእምነትና የአመላካከት ተጽእኖ ሥር የመውደቅ ዕድላቸው ሰፊ ነው መጽሐፍ ቅዱስ ጀምረው ቅዱሳት መጻሕፍትን ማብጠልጠል ሞያ አደረጉት ቀደም ብለን በዓለም አቀፍ ደረጃ አዋልድ መጻሕፍት ያለፉበትን ሒደት ተመል ከተናል ለመሆኑ በእኛ ሀገርስ የገጠማቸው ምንድን ነው።
የመጽሐፍ ቅዱስ መጻሕፍት «ቀኖናውያት መጻሕፍት» ይባላሉ ቀኖ ናውያት የሚባሉበትም ምክንያት ቁጥራቸው እና ይዘታቸው ተሰፍሮና ተቆጥሮ የተወሰ ነና የታወቀ ስለሆነ ነው ቀኖና የሚለው ቃል መለኪያን ወይም መሥፈሪያን የሚገ ልጽ የግሪክ ቃል ነውሳጋ ስለሆነም መጽሐፍ ቅዱስ የተቀነነ የተወሰነ መጻሕፍት ስብ ስብ ነው እንዲሁም የመጽሐፍ ቅዱስ መጻሕፍት «አሥራው መጻሕፍት» ይባላሉ አሥ ራው ማለት ሥርች ማለት ሲሆን አሥራው መጻሕፍት ማለትም የሌሎች መጻሕፍት ሥርች ወይም መገኛዎች መሠረቶች ማለት ነው ስለዚህ አዋልድ መጻሕፍት በአሥራው መጻሕፍት ሥርነት ላይ የሚበቅሉና የሚያድጉ ቅርንጫፎች ናቸው ከመጽሐፍ ቅዱስ ሐሳብና አውነታ ሳይወጡ በአርሱ ላይ ተመሥርተው የመጽሐፍ ቅዱስን ኃይለ ቃልና ውስጠ ምስጢር ለመተርጎም ለማብራራት ለማተትና ለመተን ተን ለልዩ ልዩ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውሉትን በአንድ ላይ ለማሰባሰብ በመጽሐፍ ቅዱስ በተገለጸው መሠረት ተዛማጅ እና አስረጅ የሆነ ነገሮችን ለማዘጋጀት ወዘተ የሚጻፉ መጻሕፍት አዋልድ መጻሕፍት ይባላሉ ይህም ማለት በምስጢርና በይ ዘት በመንፈስና በሐሳብ አስገሂያቸው እና ወላጃቸው መጽሐፍ ቅዱስ ነው ይህን መሠ ረታዊ ወላጃቸውን መጽሐፍ ቅዱስን መስለው የተወለዱና የተገኙ መጻሕፍት ናቸው አዋልድ መጻሕፍት የሚባሉት ምንም እንኳ በአንዳንድ ይዘታቸው መጽሐፍ ቅዱስን ቢመስሉም ከመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህር በጌታችን ከተገለጠውና ከሐዋርያት ጀምሮ ሲያያዝ ከመጣው የቤተ ክርስቲያን እምነትና ትምህርት ጋር ተቃርኖ ያላቸው መጻሕፍት የመጽሐፍ ቅዱስ ልጆች አዋልድ መጻሕፍት አይደሉም እንዲህ ያሉት መጻሕፍት «ዲቃላ መጻሕፍት» ናቸው ቅድስት ቤተክርስቲያንም ከመሠረታዊ አስተምህሮዋና እምነቷ እና ከቀኖናውያት መጻሕፍት ጋር የማይስማሙትን እንዲህ ያሉትን ማንኛውንም መጻሕፍት ታወግዛቸዋለች አንጂ አትቀበላቸውም አዋልድ መጻሕፍትን በተመለከተ በሚከተሉት ነጥቦች መለየት እንደሚቻል ሕንዳዊው የነገረ መለኩት ሊቅ ጢሞቴዎስ አለን ይገልጡታል ዓላማቸው መንግሥተ እግዚአብሔር የሆነ በሃሳብ በመንፈስ በምስጢር በነገረ መለኩት ከአሥራው መጻሕፍት እና ከቅዱ ሳት የቤተ ክርስቲያን ትውፊት ጋር የማይጋጩ ሟ ለክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ሞራል ሕይወት እና አነዋወር ተስማሚ የሆኑ ። ለሚለው ጥያቄ አብዛኞቹ የብሉይ ኪዳን ሊቃውንት የተስማሙበት መልስ እነ ዚህ መጻሕፍት ሠፊ ዝርዝር እና በየዘመናቱ የሚመዘገብባቸው በመሆናቸው አልተጠናቀቁም ነበር ከዚህም በተጨማሪ በእነርሱ የተገለጸው ታሪክ በአጭሩ በነገሥታት እና በዜና መዋዕል ስለቀረበ ነው የሚል ነው ከላይ ከተገለጡት በተጨማሪ የአይሁድ ሊቃውንት በየዘመናቱ ያሰባሰቧቸው የሐተታ የትርጓሜ እና የትምህርት መጻሕፍትም ነበሩ ሚሸናህ በዕብራይስጥ ቋንቋ ዘዳግም» ማለት ነው የረበናተ አይሁድን የአይሁድ መም ህራን ሐሳብ አስተያየት እና ትምህርት የያዘ ሲሆን በቃል ሲወራረስ ቆይቶ በ ዓም ረቢ ጃዳድሃናሲ አሰባስበው ጠርዝረውታል ገማራ መደምደሚያ ማጠናቀቂያ» ማለት ነው ገማራ የሚሸናህ አንድምታ ሲሆን ሁለት ዓይነት ጥራዝ አለው የመጀመሪያው የኢየሩሳሌም ጥራዝ የሚባለውን በኛው መክዘ ከጌል በፊት የተጠረዘው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የባቢሎናውያን ጥራዝ የሚባ ለውና በትርጓሜ ስልት ከመጀመሪያው የሚለየው ነው ከእነዚህም በተጨማሪ «ዜናሁ ለሙሴ»ን የመሳሰሉ የቅዱሳንን ታሪክ የመዘገቡ መጻሕፍት በብሉይ ኪዳን ዘመን ነበሩ ይሁዳ በዘመነ ወንጌል በሐዲስ ኪዳን ዘመን በሐዲስ ኪዳን ዘመን ቅዱሳን ሐዋርያት ከብሉይ ኪዳን እየጠቀሱ የተነገረው ትንቢ ትና የተሰጠው ተስፋ በኢየሱስ ክርስቶስ የተፈጸመ መሆኑን በማስረዳት ያስተምሩ ነበር ኢየሱስ ክርስቶስ በሕግ እና በነቢያት የተጻፈውን ለመፈጸም የመጣ መሆኑን ለማስ ረዳት ሐዋርያት የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን መሠረት አድርገው ያስተምሩ ነበር የሐዋጳ ማትያስን ሲሾሙ የሐዋቿ ለኢየሩሳሌም ተሳሳሚዎች ቅዱስ ጴጥሮስ ሲያ ስተምር የሐዋቿ ቅዱስ እስጢፍኖስ ከአይሁድ ጋር ሲከራከር ሐዋርያት በየመልእክ ቶቻቸው የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን ጠቅሰው እየተረጐሙ አስተምረዋል ሮሜ ቆሮ ኤፌ ቿ ዕብራ ጴጥ ይሁዳ ሐዋርያት በቃል ያስተማሩትን በመጽሐፍም መጻፍ ጀመሩ በዚህም አራቱ ወንጌሎ ችና የተለያዩ የሐዋርያት መልእክታት የክርስቶስን ሰው መሆንና የማዳን አገልግሎቱን በመግለጽ በቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረታዊ ቀኖናውያት መጻሕፍት ሆኑ ጌታችን ካረገ ከዐሥር ዓመታት በኋላ ወንጌላት እና የሐዋርያት መልእክታት እየተጻፉ በምእመናን እጅ መግባት ጀመሩ በዚህም ክርስቲያኖች በቃል የተማሩትን በጽሑፍ ለማግኘት ቻሉ ይህም ቤተ ክርስቲያን የምትቀበላቸው ቀኖናውያት የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን አሰገኘ ሆኖም ቅዱሳን ሐዋርያት በእነዚህ የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ብቻ አልተወ ሰኑም በእነዚህ ላይ የተለያዩ አልዋድ መጻሕፍትን እንዳስፈላጊነታቸው ይጠቀሙ ነበር በዘመነ ሐዋርያት የብሉይ ኪዳን አዋልድ መጻሕፍት ለማስተማሪያ አገልግሎት ውለው ነበር ለምሳሌም ሐዋርያው ቅዱስ ጳዉሎስ በጢሞ ቿ «ኢያኔስ እና ኢያንበሬስ» ብሎ የጠራቸው የፈርዖን ጠንቋዮች ስማቸው በሙሴ የአሪት መጻሕፍት በአንዱም አል ተጠቀሰም ነገር ግን ከአይሁድ የትውፊት መጻሕፍት በመውሰድ ጠቅሶታል ወንጌ ላዊው ማቴዎስም በማቴ «በነቢያት ናዝራዊ ይባላል» በማለት በዐበይት ነቢያት እና በደቂቅ ነቢያት መጻሕፍት ያልተጠቀሰ ትውፊታዊ ትንቢት መዝግቧል ሐዋር ያው ይሁዳም «ዜናሁ ለሙሴ» ከተሰኘው የሙሴ ገድል ወስዶ ጠቅሷል ይሁዳ በሐዋርያት ዘመንና በራሳቸው በሐዋርያት የተጻፉ መጻሕፍትና መልእክታት የመጽ ሐፍ ቅዱስ የቀኖናውያት መጻሕፍት አካላት ናቸው መጽሐፍ ቅዱስ የምንለው ከብ ሉይ ኪዳን መጻሕፍት ጋር በሐዲስ ኪዳን ሐዋርያት ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ከቃሉ የተማሩትንና በዓይናቸው ያዩትን በመንፈስ ቅዱስ ኃይልና ጥበቃ ሆነው የጻፏቸውን መጻሕፍት ነው ከሐዋርያት በኋላ በተነሠ የተለያዩ የቤተ ክርስቲያን አባ ቶች የተጻፉ መጻሕፍት የሚመደቡት ከሐዲስ ኪዳን አዋልድ መጻሕፍት ውስጥ ነው እነዚህ በተለያዩ የቤተ ክርስቲያን አባቶች የተጻፉ መጻሕፍት ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ባይቆጠሩም ነገር ግን የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት የመጻፍ ሂደት በመጽሐፍ ቅዱስ ያበቃና የተደመደመ አይደለም ጌታችን ከሐዋርያት ጋር እንደነበረ ሁሉ ከዚያ በላ በሐዋርያት ቦታ ከሚተኩ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ጋርም አለና «ጳ ኋዕ ፍልም ፍጃዳማ ድረዕ ሥልሰ ዕቋናታ ጋረ ቀኝ እንዳለ ማቴ ቿ መድኃኒታችን በምሳሌ ሲያስተምር ወንበዴዎች ደብድበው በሞትና በሕይወት መካ ከል ጥለውት ስለፄዱ አንድ መንገደኛ አስተምሮአል ይህን ቁስለኛ አንድ ርኅሩኅ ሳም ራዊ ወደ እንግዳ ማደሪያ ቤት ወስዶ ከጠበቀው በኋላ በማግሥቱ ለእንግዶች ማደሪያ ቤት ጠባቂው ሁለት ዲናር አውጥቶ ሰጠውና ሪጋፇው ደ ፀ ቦያምታፖሥረው ሥታ ዕመኃሰ አሕፍጳሃፅሥ» አለው ሉቃወ ይህ ምሳሌ ነው በወንበዴዎች የቆሰለው ቁስለኛ አዳም በአጠቃላይ በኃጢአት መርዝ የተለከፈና የቆሰለ የሰው ልጅ ሁሉ ሲሆን ወንበዴው ደግሞ ዲያብሎስ ነው የአዳምን ቁስል የፈወሰው ርኅሩጉ ሳምራዊ ራሱ መድኃኔዓለም ሲሆን ይህን ቁስለኛ ወስዶ ያሳደረበት የእግዶች ማረፊያ ቤት የተባ ለችው ደግሞ ቤተ ክርስቲያን ናት በዚህ ዓለም የኖሩና የሚኖሩ የእግዚአብሔር ወዳጆች ሁሉም እንግዶች ናቸውና ነቢዩ ዳዊት «አስመ ፈላሲ አነ ውስተ ምድር ወነግድ ከመ ኩሉ አበውየ እኔ በምድር ላይ መጻተኛ ነኝና እንደ አባቶቼም አንግዳ ነኝና» እንዳለ መዝወ የግብጽ ንጉሥ ፈርዖን ያዕቆብን ዕድሜውን በጠየቀው ጊዜ የአንግድነቴ ዘመን መቶ ሠላሳ ዓመት ነው» አለው ዘፍ ማጂከ ስለዚህ እንግዶች የተባሉት ምአመናነ ክርስቶስ ክርስቲያኖች በሙሉ ሲሆኑ የአን ግዶች ማደሪያ የተባለችው ቤተ ክርስቲያን ናት የማደሪያው ቤት የቤተ ክርስቲያን ጠባቂዎች የተባሉት ደግሞ የቤተ ክርስቲያን መምህራን ናቸው « ሄጎጩሴጨረ ይፉ ረዕሂያሃ ጎዳ ደሃ ፅዕዖድም ጋዎርቦሥ። አዋልድ መጻሕፍት የተለያዩና ብዙ ከመሆናቸውም በተጨማሪ በየጊዜው እየተጻፉና አየተጨመሩ የሚሄዱ ስለሆነ ቁጥራቸው ይህን ያህል ተብሎ ሊወሰን አይችልም የአን ድን ነገር ቁጥር ለማወቅ ማቆምን ይጠይቃልና በተለይም ደግሞ አዋልድ መጻሕፍት አንደ ቀኖናውያን መጻሕፍት እገሌ መጽሐፍ አንድ እገሌ መጽሐፍ ሁለት ተብለው ተለይተውና ተወስነው ሊቆጠሩ ያስቸግራል ምክንያቱም በተለያዩ ዘመናት በተለያዩ ቦታዎችና በተለያዩ ጸሐፍያን የተጻፉ ስለሆነ ነው የሚያገኛቸውም ሰው ዐይቶና ተመ ልክቶ ከመሠረታዊው የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮና የቤተ ክርስቲያን ትውፊት የሚስ ማሙ ከሆኑ ይጠቀምባቸዋል እንጂ እያንዳንዱ መጽሐፍ በተጻፈ ቁጥር እየታየ በቀኖና ተወስኖ የሚዘለቅ አይደለም ጠቢቡ ሰሎሞን አዋልድ መጻሕፍት ቁጥራቸው እጅግ ብዙ መሆኑን ሲገልጽ «አዋልድ አለ አልቦን ጉልፉጐ ቁጥር የሌላቸው ብዙ የሆኑ ልጆች» ብሏል መኃ ሕ መሠረታዊው መርህና መመዘኛ የሆነው መጽሐፍ ቅዱስና የቤተ ክርስቲያን ትምህ ርት እስከተቀመጠ ድረስ በነዚህ መመዘኛዎች መመዘን የእያንዳንዱ ድርሻ ነው ሆኖም ግን አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለመንፈሳዊ አገልግሎቷ የምትጠ ቀምባቸውን መጻሕፍት በቅዱስ ሲኖዶስ መዝናና ለይታ መወሰን ትችላለች በተለይም በቤተ ክርስቲያን የዕለት ተዕለት አገልግሎት ውስጥ ጥቅም ላይ የሚውሉትንና በስሟ የሚጠሩትን ወይንም የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት እንደሆኑ የሚነገሩ ካሉ እነዚህን መርምራ የቤተ ክርስቲያን ከሆኑ ማጽደቅ ካልሆኑ ደግሞ ስህተታቸውን መግለጥና መለየት አስፈላጊ ነው የሐዲስ ኪዳን አዋልድ መጻሕፍት ሃመዕታ ኃጋዎርቦውፆጋ ዲያው ሐዋርያውን አበው አሥራው መጻሕፍትን በመናፍቃን እንዳይቀሰጡ ከመጠበቃቸ ውም በላይ እነርሱም በበኩላቸው ብዙ መጻሕፍትን ፈዋል ለምሳሌም ቀሌምንጦስ ዘሮም በልዩ ልዩ ከተሞች ለሚኖሩ ክርስቲያኖች መልእክታትን ፏል ሊካርፐስ ለፊልጵስዩስ ሰዎች ለሰርምኔስ ክርስቲያኖች መልእክታትን ጽፏል አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለኤፌሶናውያን ለማግሬስያውያን ለጥራልያንስ ለሮ ማውያን ለፊላዶልፊያውያን ለሰርምኔሳውያን ለሊካርፐስ ለጠርሴሳውያን ለአ ንጾኪያውያን ለፊልጵስዮሳውያን መልእታትን ጽፏል ፒያስ ዛሬ ሙሉው ጽሑፍ ጠፍቶ ከፊሉ ቢገኝም በዘመኑ ለነበሩ ክርስቲያኖች መል እክት ጽፏል ሄርሜን «ኖላዊ» የተሰኘ መፍሐፍ ጽፏል። ጫ ዘመነ ሊቃውንት ዐራት ዓይነት አዋልድ መጻሕፍት የተገኙበት ዘመን ነው መልእክታት የቤተ ክርስቲያን አበው ሊቃውንት ሃይማኖትን የሚያስተምሩ ልዩ ልዩ መልእክታትን ጽፈዋል ለምሳሌ ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊው ከ በላይ መልእክ ታትን ጽፏል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በስደቱ ዘመን ከ በላይ መልእክታን ጽፏል እነ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ባስልዮስ ዘቂሣርያ ሌሎችም አባቶች ብዙ መልእክታትን ፈዋል ትርጓሜያት በዘመነ ሊቃውንት የተነሥ የቤተ ክርስቲያን አባቶች የቅዱሳት መጻሕ ፍትን መጽሐፍ ቅዱስን ትርዓሜና ምስጢር በማተትና በማብራራት መሠረታዊ አሳባቸውንና ይዘታቸውን በመተንተን ብዙ የትርጓሜ ሥራዎችን ሠርተዋል በዚያ ዘመን የተነ መናፍቃን በተለይም ግኖስቲኮች መጻሕፍትን ለራሳቸው እያጣመሙ በመተርጉማቸው አበው ሊቃውንት የመጽሐፍ ቅዱስን መጻሕፍት በሚገባ እየተረ ጐሙ አስቀምጠዋልጹ ከታላላቆቹ መተርጉማንም ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ቅዱስ ኤሏፋንዮስ ቅዱስ አምፊሎቅዮስ አባ ሄሮኒመስ ቅዱስ ቄርሎስ ዋና ዋናዎቹ ናቸው ገድላት በዚያ ዘመን የነበሩ አበውን እና እማትን ገድል አበው ሊቃውንት እየጻፉ አስቀምጠዋል ለምሳሌ የብዙዎች ሐዋርያት ገድል ከየቦታው ተሰባስቦ የተጻፈው በዚህ ጊዜ ነው የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊው አውሳብዮስ የብዙዎቹን ሐዋርያት ገድል ጽፎልናል አግናጥዮስ የፖሊካርፐስን የሰማዕትነቱን ገድል ሲጽፍ ይህንንም አውሳ ብዮስ መዝግቦታል የአግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ የተፍጻሜተ ሰማዕት ጴጥሮስ ገድ ላት በዚህ ዘመን የተጻፉ ናቸው ቅዱስ አትናቴዎስ የአባ እንጦንስን ታሪክ ሲጽፍ አባ ሄሮኒመስ የአባ ጳውሊን የቅዱስ ሂላርዮስን የአባ ማልኮስን ገድላት ጽፏል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ከርሱ በፊት ስለነበሩና ሰማዕትነትን ስለተቀበሉ ቅዱሳን ለምሳሌ ስለ ሰማዕቱ ባቢላስ ስለ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ስለ ቅዱስ መላጥዮስ ስለ ቅዱስ ኤዎስጣቴዎስ ዘአን ጾኪያ በዕለተ ዕረፍትቸው በበዓላቸው ቀን ተጋድሎአቸውንና ሕይወታቸውን በተመለ ከተ ያስተማራቸው ትምህርቶች ይገኛሉ እንዲሁም ስለ ቅዱሳኑ ስለ ሮማኖስና ስለ በረላም ስብከቶችን ሰብኳል ፀፀ ገዳማዊ ጽሑፎች የገዳማዊ ኑሮ በየቦታው የተስፋፋው በዘመነ ሊቃውንት በመሆኑ ገዳማዊ ሕይወትን የተመለከቱ መጻሕፍት በዚህ ዘመን ተጽፈዋል የበረሃ አበው ንግግ ሮች መጽሐፈ ገነት የባስልዮስ ቀኖና የጳኩሚስ ሕግ ወዘተ ተጽፈዋል የአዋልድ መጻሕፍት ዓይነት ከላይ የተለያዩ የአዋልድ መጻሕፍት ዓይነቶችን ያየን ቢሆንም ከላይ ያልተገለጹትንም ጨምረን በአጠቃላይ አዋልድ መጻሕፍት ሲባል የሚወክሏቸውን መጻሕፍት እንደሚከተ ለው ጠቅለል አድርን እናያለን የትርጓሜ መጻሕፍት አነዚህ ከላይ አንደተገለጹት የቅዱሳት የቀኖናውያት መጻሕ ፍትን ውስጠ ምስጢር የሚያስረዱ መጻሕፍት ናቸው በተለይም የቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ የትርጓሜ መጻሕፍት እጅግ በጣም የሚደነቁና ጠቃሚ የሆኑ ናቸው እንዲሁም የቅዱስ አትናቴዎስና የቅዱስ ቄርሎስ የሦስቱ የቀጳዶቅያ አባቶች ባስልዮስ ዘቂሣርያ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስና ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ትርጓሜዎችም ታላላቅ ሥራዎች ናቸው በየዘመኑ የተነጮ የሌሎች አበው ትርጓሜያትም ያሉ ሲሆን ቅዱሳት መጻሕፍትን በሚ ገባ ለማወቅና ለመረዳት እነዚህ ድርሳናት ወሳኝ ናቸው በመናፍቃን ላይ የተጻፉ መጻሕፍት በተለያየ ዘመን የተነሥጮ መናፍቃን ለሚያነ ሷቸው የተሳሳቱና አወናባጅ አስተሳሰቦችና እምነቶች መልስ ለመስጠት በየዘመኑ የተነ አባቶች ብዙ መጻሕፍትን ጽፈዋል ለምሳሌም ቅዱስ አትናቴዎስ በአርዮስ ላይ አባ ጄሮም በፄሊቪዲየስ ላይ የእመቤታችንን ዘለዓለማዊ ድንግልና በተመለከተ ለጻፈው አስጸያፊ ነገር ሄሬኔዎስ በዘመኑ በነበሩ በሁሉም መናፍቃን ላይ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በአ ርዮሳውያን ላይ እና መለኮታዊ ጥበቃን በሚጠራጠሩ ሰዎች ላይ ቅዱስ አውግስቲን በፔላጊዮስ ላይ ቅዱስ ኤሏፋንዮስ በተለያዩ መናፍቃን ላይ ቅዱስ ቄርሎስ በንስጥሮስ ላይ አና ሌሎችም ናቸው ገድላት የአንድን ሰማዕት ወይም ጻድቅ ሕይወት ሥራና ተጋድሎ ዘርዘር ባለ ሁኔታ የያዘ መጽሐፍ ገድል» ይባላል «ገድል» በክርስትና ሕይወት ከተለያየ አቅጣጫ የሚመጡና የሚገጥሙ ፈተናች ጋር የሚደረግ መንፈሳዊ ተጋድሎን የሚያመለክት ነው ሐዋርያው «መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና ከአለቆችና ከባለ ሥል ጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዢዎች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካሉ ከክፋት መንፈሳዊያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ» በማለት እንደገለጸው ኤፌ ስለዚህ ገድ ላት የክርስቶስ አገልጋዮች ከክፉዎች ሰዎችና ከአጋንንት ጋር ያደረጉትን ተጋድሎ የሚገ ልጹ መጻሕፍት ናቸው ገድል የዚያን ጻድቅ ወይም ሰማዕት ዜና ሕይወት ከመነሻው አስከ ፍጻሜው ያሳለፈውን ሕይወት የደረሰበትን ፈተናና እንዴት አእንደተወጣው በመጨረሻም ይህን ዓለም ድል አድርጎ ወደ ፈጣሪው የመሄዱን ነገር ያስረዳል ሐዋ ርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለተሰሉንቄ ክርስቲያች በላከው መልእክቱ «መራ ፖቃዝቋጳ ። እንዲያውም ሆኖ ከቋንቋ ወደ ቋንቋ ሲተረጎም እንዲሁም በተለያየ ዘዴ ክፉዎች ሰዎች አልፎ አልፎ አንዳንድ ቀዳዳ ማግኘታቸው አልቀረም መንገድና አጋጣሚ ካገኙ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የሚፈልጉ ትን ከማድረግ ወደ ኋላ የማይሉ ከሆነ በአዋልድ መጻሕፍት ላይ ለውጥ ቢያደርጉና ቢቀስጧቸው አያስደንቅም ዲዮናስዮስ የተባለው በሦስተኛው መቶ ዓመት መጀመሪያ ገደማ የነበረው የቤተ ክር ስቲያን አባት አርሱ ጽፎ የላካቸውን መልእክታት ከውስጣቸው ቀንሰውና ቆርጠው አውጥተው ሌላ የራሳቸውን የጨመሩባቸው መሆኑን በመግለጽ ምአመናንን እአንዲጠነ ቀቁ አስገንዝቦአል ዲያብሎስ የሚነዳቸው የቤተ ክርስቲያን ጠላቶች በአዋልድ መጻሕ ፍት ላይ የራሳቸውን ኑፋቄ ካስገቡ በኋላ ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮኻል እንደሚባ ለው እንደገና መልሰው ቤተ ክርስቲያንን ለማሳጣትና ለመንቀፍ ይህን እንደ አንድ መንገድ ለመጠቀም መሞከራቸው አልቀረም ከዚህም ጋር የቀኖናውያት መጻሕፍት አውነተኛ ልጆች ሳይሆኑ በግንዛቤ ጉድለት ምክንያት አዋልድ መስለው አእንዳያሳስቱ ጥንቃቄ ያስፈልጋል የቤተ ክርስቲያኒቱ የበላይ አካል የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተ ክርስቲያን ናቸው የሚባሉትንና በውስጧ ያሉትን የተለያዩ መጻሕፍት መርምሮ ትክክለ ኞቹን አዋልድ መጻሕፍት የማጽደቅ በቅሰጣና በልዩ ልዩ ምክንያት ችግር ያለባቸውን የማስተካከል ወይም ስህተታቸውን በመግለጥ ቤተ ክርስቲያን የማትቀበላቸው መሆኑን መወሰንና ለምእመናን ማሳወቅ ይጠበቅበታል በዚህ ረገድ ቅዱስ ሲኖዶስ በጣም ብዙ ሥራ ይጠበቅበታል ምእመናንም መሠረታዊውን የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በመማ ርና የሁሉም መለኪያ ቀኖና የሆኑትን አሥራው መጻሕፍትን መጽሐፍ ቅዱስን በመ ማር የተለያዩ ድርሳናትን ከመሠረታቸው አንጻር ለመመዘን እንዲችሉ መሆን ይገባቸ ዋል በአዋልድ መጻሕፍት ላይ በቅሰጣም ይሁን በሌላ ምክንያት ይህ ስህተት ነው የሜል ነገር ሲነሣ መደናገጥና መናወጥ አይገባም የቤተ ክርስቲያን እምነት የተመ ሠረተው በአዋልድ ላይ ሳይሆን በቀኖናውያት መጻሕፍት ላይ ነውና ጥፋት በዘመነ ሰማዕታት ብዙ ቅዱሳት መጻሕፍት እንዲቃጠሉ ተደርገዋል ከአብያተ ክርስቲያናት እና ከምእመናን ቤት እየተሰበሰቡ ጋይተዋል ይህ በቅዱሳት መጻሕፍት ላይ የተነሣው ዘመቻ በኛው መቶ ክፍለ ዘመን ኃያል ሆኖ በተነሣው የእስ ልምና ንቅናቄ ምክንያት ጋብ ብሎ እስከ ኛኛው መቶ ክፍለ ዘመን ቆየ በኛኛው መቶ ክፍለ ዘመን የቡርዣውን አብዮት ተንተርሶ በተነሳው የፕሮቴስታንት ንቅናቄ ደግሞ እንደ ገና አገረሸበት ፕሮቴስታንቶች አይሁድ ከክርስቶስ ልደት በኋላ በወሰኑት ውሳኔ በመ መራት የመጽሐፍ ቅዱሳቸውን ቀኖና የሐዲሳን አይሁድ ቀኖናን እንዲከተል አደረጉ። አሁንስ ያሉ ተሐድሶዎች የሚያነሷቸው ጥያቄዎች የየትኞቹ ሒደቶች ውጤቶች ናቸው የሚለውን ደግሞ በአጭሩ እንደሚከተለው እናያለን በኢትዮጵያ የገጠማቸው ሁኔታ አዋልድ መጻሕፍት በኢትዮጵያ መኖር የጀመሩበትን ጊዜ በትክክል ማወቅ ባይቻ ልም ከብሉይ ኪዳን ዘመን እንደሚጀምር ግን መገመት ይቻላልሱ በየዘመኑ መጻሕፍት እንደመጡት ሁሉ እነ ዜናሁ ለሙሴን የመሰሉ የብሉይ አዋልድ ቀደም ብለው እንደ መጡ መገመት ይቻላል በሐዲስ ኪዳን ከዘጠኙ ቅዱሳን መምጣት ጋር ተያይዘው ቢመጡም በጉልህ የተጻፉ በት ዘመን ግን መካከለኛው ዘመን ነው ተሰዓቱ ቅዱሳን ሥርዓተ ጳኩሚስን የመሰሉና በሀገራቸው በሶርያ የነበሩ የቅዱሳን ታሪኮችንና አኗኗራቸውን የሚያስረዱ መጻሕፍትን ይዘው እንደገቡ የሚያሳዩ ብዙ አሻራዎች አሉ በመካከለኛው ዘመን በተለይ በመተርጉም ሰላማ ዘመንና ከእርሱ በኋላ ባሉት ግን ብዙ ገድላት ተተርጉመዋል የቅዱሳንና የገዳማውያን አኗኗርና ትምህርቶችን የሚያስረዱ መጻሕፍትም ተጠናቅረውና ተጠርዘው የተዘጋጁት ብዙዎቹ ተተርጐመዋል ከዚህ ጊዜ በኋላ ደግሞ የኢትዮጵያውያን ቅዱሳን ገድላትም በብዛትና በስፋት እየተዘጋጁ በየገዳማቱ የሚገኙ ሆኑ በአጭሩ የአዋልድ መጻሕፍት የኢትዮጵያ አኗኗራቸውን በዚህ ጥቁምታ ዘግተን ወደ ገጠሟቸው ነገሮች እንለፍ የርተጊዞችን መምጣት ተከትለው የገቡት ካቶሊኮች በራሳቸው ከደከሙት በላይ በልጆቻቸው በቅባቶችና በጸጐች ካደረሱብን ጥፋቶች መካከል መጻሕፍት ላይ የደረሰው የማይዘነጋው በደል ነው እነዚህ ሰዎች መጻሕፍትን በተለይም ወንጌላትን ከራሳቸው አሳብ ከጸጋና ከቅባት ሦስት ልደት ጋር ለማጣጣም ብዙ ጥፋት አድርሰዋል የቀነ ሱለት አለ የፋቁት አለ የለወጡት አለ ብቻ ብዙ ብዙ በደሎችን አድርሰዋል ለዚህ አንደ ዐቢይ ማስረጃ ሊሆን የሚችለው የኋላ ተርጓሞያን ትርጓሜያቸው ላይ «እንዲህ የሚል ንባብም አለ» እያሉ ሌላውን ቅጂ መጥቀሳቸው ነው አዋልድ መጻሕፍትም በዚህ መከራ ውስጥ አልፈዋል ሥርዋጽ የገባባቸው አንዳን ዶቹ ጥላቻቸውንም ያሸከሟቸው የፋቁአቸው ለነቀፋ የሚያመች ነገር የጨመሩባቸው ከአንዱ ምንጭ ሲገለበጡ በእጅ የሚገለበጡ በመሆናቸው ምክንያት ታሪክ የተጐጉረደባ ቸውና የመጥፋትና የመቀነስ ሁኔታ የገጠማቸው ለመተካት በተደረገው ጥረትም ደግሞ ምን አልባት ጭማሪ የገጠማቸውም ሊኖሩ ይችላሉ ከዚህም በላይ የግራኝ አሕመድ ወረራን ተከትሎ ብዙዎቹ በቃጠሉ ወድመዋል ፈጸመው ከመጥፋታቸው የተነሣ አሁን በስም የማይጠቀሱም ሊኖሩ ይችሉ ይሆናል ይህ ሁሉ በብዙ ችግሮች ማለፋቸውን የሚያሳየን ጉዳይ ነው አሁን ደግሞ መልኩን የለወጠ ፈተናም ገጥሟቸዋል ጭራሽ አያስፈልጉም ባዮች ተነ ሥተውባቸዋልና አንዳንዶቹማ የበለጡ እየመሰላቸው ቤተ ክርስቲያን የማትቀበላቸውን የጥንቆላና የተሳሳቱ መጻሕፍትንም በመጥቀስ ሁሉንም ከእነዚህ ጋር በመፈረጅ «በመስ ኩት የገቡ» በማለት የ«ረይውጡ» መፈክራቸውን ይሰነዝሩባቸዋል በመሠረቱ የተሳሳቱና የቤተ ክርስቲያን ያልሆኑ መጻሕፍት በየትኛውም ዘመን አሉ ይህ ደግሞ በመጻሕፍትም ብቻ አይደለም በነቢያት አንጻር ሐሰተኞች ነቢያት ነበሩ በሐዋርያትም አንጻር ደቄቀ አስቄዋን የመሰሉ ሐሰተኞች ሐዋርያት ተነሥተው ነበር ከዚህም በላይ ሰይጣን በሰማይ ባሉት በብርሃን መላእክት አምሳል የሚመጣው ተመሳ ሳይ ነገር የሌለው ቅዱስ ነገር ስለማያስደስተውና በእነዚህ ሐሰተኞች ምክንያት እውነ ተኞቹን እንድንጠላለት ስለሚሻ ነው ሰይጣን በፍጡራን ብቻ ሳይሆን በጌታችንም አን ጻር ሐሰተኞች ክርስቶሶችንም አስነሥቷል እስከዚህ ዓመትም ድረስ ሰዎች እኔ ክርስቶስ ነኝ ሲሉ እንሰማቸዋለን ታዲያ በእነዚህ በሐሰተኞቹ ምክንያት እውነተኞቹን እንጥላን።