Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
አንፀባራቂው ኮከብ ፕሮፌሰር አሥራት ለዲሞክራሲ መርሆዎች የተጋደሉ ብቻ ሳይሆን ማንነታቸውንም ለኢትዮጵያ መስዋዕት ያደረጉ ታላቅ ሰው ናቸው ዓርማቸውን አንስተን መስዋዕት ለመክፈል ለጠላትም ለወዳጅም ለመግለጽ እንወዳለን ብለው ነበር ይህ ግን የለቀስተኛው ሁሉ ስሜት ነበር ቃል ኪዳኑም ከዳር እስከ ዳር ባስተጋባው ጭብጨባ ተገልጧል የሚከተለው ግጥም የፕሮፌሰር አስራት ኛ ሙት ዓመት ሲከበር በፓልቶክ ሩም ውስጥ ሲነበብ የሰማሁት ነው።
እደ እርሳቸው ህሙማንን እጅግ የሟወድ ፅው ነፍሰ ጸጥቭብቆ የሟጨነየቅ አያሁም» ፕሮፌሰር አሥራት መዐሕድ በባሕር ዳር በጠራው ስብሰባ ላይ የሙያቸውን መርሕ በተመለከተ ያደረጉትን ንግግር እዚህ ላይ ማውሳቱ ተገቢ ነው ረእንደ ሕክምና ዶክተርነቴ እና ማንኛውም ዶክተር እንደሚፈጽመው ቃለ መሃላ ከሆነ ዕርዳታየን ፈልጎ የመጣን ሰው ሁሉ ያለ ምንም አድሎ ማከም ግዴታየ ነው በዚህ መሠረት በዶክተርነቴ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ጨምሮ የመንግስቱ ኃይለማርያምን ቤተሰብም አክሜያለሁ በተመሳሳይ በሕይወት ዘመኔ እጅግ ብዙ አቅመ ደካማና በራሳቸው ከፍለው ለመታከም አቅም የሌላቸውን ሰዎችም አክሜያለሁ እስካሁንም ድረስ ይህን እያደረግኩ እገኛለሁ ደግሞም የሰውን ልጅ ሁሉ በእኩልነት ማከም የሙያ ግዴታየ ነው በዚህም መሠረት አስታዋሽ የሌላቸውንና ጎዳና ወድቀው የኖሩ ድሆችንም ቢሆን የእኔን ዕርዳታ ፈልገው እስከመጡ ድረስ ሳክም ኖሬያለሁ እኔ እስከቻልኩት ድረስ ማንኛውንም ሰው ያለ አድሎ ማከም ሙያው ያስገድደኛል ፍላጎቱ ካላቸው እና የእኔን የሕክምና ዕርዳታ ፈልገው የሚመጡ ከሆነ የፖለቲካ አስተሳሰባቸውን ግንዛቤ ውስጥ ሳላስገባ አሁን በሥልጣን ላይ ያሉትን የኢሕአዴግ ባለሥልጣናትና ቤተሰቦቻቸውንም ለማከም ወደኋላ የምል ሰው አይደለሁም ከዶክተሩ አንደበት እድሜያቸው በመካከለኛ ጎልማሰነት ደረጃ ላይ ይገኛል ግዙፍ ሊባል የሚችል ቁመና በተመጣተነ የሰውነት ክብደት ታድለዋል ደልዳላ ቁመናን የተላበሱት ዶክተር እንዲሁ ከሩቅ ሲያዩዋቸው አስፈሪ ግርማ ሞገስ አላቸው ቀርበው ሲያነጋግሯቸው ግን ቀላልና ተግባቢ ሰው መሆናቸውን ለማወቅ ጊዜ አይጠይቅም ፀጉራቸው ሙሉ ለሙሉ ነጭ ወደሚባል ደረጃ ተሸጋግሯል የፀጉራቸው መሸበት ከግዙፉ ቁመናቸው ጋር ተዳምሮ ሰውየውን አንዳች ግርማ ሞገስ አላብሷቸዋል ፕሮፌሰር አሥራት ካፈሯቸው ዕንቁ የቀዶ ሕክምና ባለሙያዎች ፊታውራሪው መሆናቸውን የሚያውቋቸው ሁሉ ይመሰክሩላቸዋል እንዲያውም አንዳንዶች ፕሮፌሰር አሥራት እንዲተኳቸው ሆነ ብለው አዘጋጅተዋቸዋል ሲሉ ይደመጣሉ ራሳቸውን ቢሆን በዚህ ጉዳይ ላይ በተወሰነ ይስማማሉ ፕሮፌሰር አሥራትን እንደ ትልቅ ሞዴላቸው ይጠቅሷቸዋል ቀዶ ሕክምና እንዳጠና የአሥራት ተጽዕኖ ከፍተኛ ነበር ብለውኛል እያወራሁ ያለሁት ስለ ጥቁር አንበሳው ዶክተር ደረጀ ጉልላት ነው ዶክተር ደረጀ በተደጋጋሚ ሳገኛቸው በደስታ አስተናግደውኛል ለመጀመሪያ ጊዜ ስለ ፕሮፌሰር አሥራት ጥናት እያደረግኩኝ እንደሆነ ስገልጽላቸው ሁሉም ሰው እንዲህ እያለ መረጃ ይወስዳል እስካሁ ግን አንዱም እንኳን እዚህ ግባ የሚባል ነገር ሲሰራ አላየንም ካሉኝ በኋላ የእውነት መጻፍ እንደፈለግኩኝ ስንግባባ የሚያውቁትን ሁሉ ለማካፈል ወደ ኋላ እንደማይሉ አስረድተውኝ ተለያየን በተጣበበው ጊዜያቸው መካከል ቀጠሯችን አክብረው ተገናኝተን ስለ ፕሮፌሰር አሥራት የነገሩኝን ሙሉ ለሙሉ ርአንዳንድ በእንግሊዘኛ የተናገሯቸውን ወደ አማርኛ ከመለወጥ በስተቀር ከመቅረጸ ድምፄ እንደሚከተለው ገልብጨዋለሁ ጥሩ እንግዲህ ስለ ፕሮፌሰር አሥራት ከጠየከኝ ያው እርሳቸውን ያውቋቸዋል ከሚባሉት ተማሪዎቻቸው አንዱ ስለሆንኩ የማውቃቸውን ያህል ከሙያው ጋር በተያያዘ ልነግርህ እወዳለሁ እኔ እንግዲህ ፕሮፌሰር አሥራትን የማውቃቸው ተማሪ ሆኘ ነው አንደር ግራጁየት ተማሪ ሆኘ ሲገቡና ሲወጡ ፕሮፌሰር አሥራት እኝህ ናቸው ሲባል ነው የማውቃቸው በዚያን ጊዜም በጣም ሙሉ ሰው ነበሩ ፀጉራቸው ትንሽ መሸበት ጀምሯል በጣም ጠንካራና ሲራመዱም በጣም ፈጣን ናቸው በጣም የተከበሩ ሐኪም እንደነበሩ አስታውሳለሁ በዙሪያቸው ላሉ ሰወች የሚያስፈሩ የሚመስሉ ሐኪም ናቸው በኋላም በትምህርቱ ገፋ እያልን እንመጣና ወደ ኪሊኒካል ዲፓርትመንትና ወደ ማከም ቦታ ስንመጣ ፕሮፌሰር አሥራትን ማወቅ በጣም ግልጽ እየሆነ መጣ ምክንያቱም በቀጥታ ፊት ለፊት መገናኘት ጀመርን ሲያስተምሩ በቀጥታ ሌክቸርም ይሰጣሉ እኔ በጣም የማስታውሰው ግን በትንንሽ ቡድን በበሽተኛ ዙሪያና በኦፕራሲዮን ክፍል የሚያስተምሩትን ነው ፕሮፌሰር አሥራት ሲያስተምሩ ሕክምና ብቻ አይደለም የሚያስተምሩት ስነ ስርዓት አለባበስ ሰውን እንዴት መቅረብ እንዳለብህ እንዴት መጥራት እንደላብህ ሁሉ ነው የሚያስተምሩኒ ስለሆነም ፕሮፌሰር አሥራት ጋ ስንማር ሕክምናውን ብቻ አይደለም የምናውቀው በጠቅላላው ዲሲፕሊን ትማራለህ በትምህርቱ መካከል ጥቅስ ከተለያየ ቦታ ይጠቅሳሉ ከአባቶች አነጋገር ይጠቅሳሉ ከመጽሐፍ ቅዱስ ይጠቅሳሉ በዓለም ታላላቅ ከሆኑ ሰዎች ቀንጭበው ያመጣሉ ይሄ እንግዲህ እያዝናኑ ቁምነገር የሚያስጨብጡበት ስልት ነው በአንጻሩ ሲቆጡ ደግሞ በስነ ስርዓት ይቆጣሉ ሆኖም የትምህርቱ ጊዜ ሳናውቀው ነው የሚያልቀው በተፈጥሮው የትምህርቱ ጸባይ ብዙ ሰዓት ነው የሚቆመው እኛ ግን ያን ያክል ሰዓት መቆማችን እንኳን ትዝ አይለንም ነበር የሕክምና ትምህርቱ ይቀጥላል ኦፕራሲዮን ክፍል ይገባል በዚያን ጊዜ እንዳሁኑ አይደለም የሕክምናም ተማሪም ሆኖ ጠጋ ብሎ ፕሮፌሰር አሥራትን መርዳት ይቻላል በኦፕሲዮን መርዳት ማለት ነው ይለበስና አጠገባቸው ይቆማል አጠገባቸው ሲቆም በኦፕራሲዮን ላይ ትንሽ ቆጣ ሲሉ ሁሉም ሰው ነው የሚፈራው ያ ትልቅ ትውስታ አለው እያንዳንዱ ተማሪ ውስጥ የሚቀር ትውስታ ነው ኦፕራሲዮኑ ሲያልቅ እኛም ተማሪዎቹ ወደ ማደሪያ ክፍላችን እንሄዳለን ፕሮፌሰር አሥራት ግን አንዳንዴ ከኦፕራሲዮን ክፍል ወጥተው ለማስተማር ይመጣሉ በአለቀ ሰዓት ለማስተማር ይወጣሉ ይህም ሰውየው ምን ያክል ጠንካራ ሰውና ደከመኝ ሰለቸኝ የማይሉ ብርቱ ሰው እንደነበሩ ግምት ውስጥ መግባት ያለበት ነገር ነው በትምህርቴ እያደኩኝ መጥቸ ተለማማጅ ሐኪም ስሆን ጠዋት ጠዋት ፕሮፌሰር አሥራት ጋር ስብሰባ አለን ይህ ስብሰባ እንግዲህ በ ሰዓት የመጡትን ድንገተኛ ነገሮች የገቡትን ሰዎች የሞቱም ካሉ ሁሉም በዝርዝር በስብሰባው ላይ ይነሳል በዚህ የጠዋት ስብሰባ ላይ ፕሮፌሰር አሥራት ሁልጊዜም በጣም ጠቃሚ የሆነ ማሳሰቢያ አላቸው አንዳንዱን ከሕግ አንጻር አንዳንዱን ከዲሲፕሊን አንጻር አንዳንዱን ደግሞ ከሰብዓዊነት አንጻር እንዴት መወሰን እንዳብን ታካሚዎቻችን እንዴት መያዝ እንዳለብን ልክ በየቀኑ እንደሚነገር የወንጌል ስብከት ያለመሰልቸት ይነግሩናል ይህ ምክር በጣም ጠቃሚ ነው በመጽሐፍት ላይ የሌለ ጆርናል ላይ የማይገኝ ላይበራሪ ተሂዶ የማይጠና ከሰው አንደበት የሚገኝ ለሰዎች ስብዕና እና ስነምግባር የሚረዳ ትልቅ ትምህርት ነው ሰለቸኝ አይሉም ደከመኝ አያውቁም በየጠዋቱ ሁልጊዜ አሉ ለትንሹም ለትልቁም የሚሆን ምክር አዘል ትምህርት ይሰጣሉ በአሁኑ ጊዜ ያንን አይነት አካሄድ ለመቀጠል አዳጋች ነው ምክንያቱም የሰዎች አረዳድ አሁን አዲስ ሆኗል የዚያን ጊዜ ግን ሶሻል ሚዲያ የለም ሞባይል የለም ጆርናሉም እስከዚህ የለም ካለም ከሰዎች ነው የሚገኘው ትምህርቴን ጨርሸ ወደ ስራ ዓለም ገባሁ ከስራ ዓለም ተመልሸ የመጣሁት ወደ ቀዶ ሕክምና ዲፓርትመንት ነው ወደዚህ ዲፓርትመንት እንድመጣ አርአያ የሆኑኝ ፕሮፌሰር አሥራት ናቸው ምክንያቱም በሚሰሩት ስራ እረካ ነበር በሚድኑት ሰዎች እረካ ነበር በሙያው ጥልቀትና ስፋት እረካ ነበር ምንድን ነው ፕሮፌሰር አሥራት የማያክሙት እስከምል ድረስ ይገርሙኝ ነበር የአንድ ቀን ሕፃን ኦፕራሲዮን ያደርጋሉ አዋቂ ሴት ወንድ በጣም ያረጀ ሰው ሁሉንም በብቃት ያክማሉ አንጎል ኦፕራሲዮን ያደርጋሉ ደረት ኦፕራሲዮን ያደርጋሉ አጥንት ይሰራሉ አንጀት ይሰራሉ በአጠቃላይ በጣም ብዙ ነገር ይሰራሉ የተለያየ ቦታ ስለሚሰሩ የማይችሉት ነገር ያለ አይመስለኝም ነበር ሰውየው በትክክልም ሰፊ ክህሎት ነበር ያላቸው ከዚያም በተረፈ የሕክምና እውቀታቸው አሁን ኢንተርናል ሜዲስን ምን ምን እያልን እንደከፋፈልነው አይነት አይደሉም ሰፊ የሆነ እውቀት ይዘው የሚሄዱ ሰው ነበሩ ያ ብቃታቸውም ይመስለኛል ወደዚህ ሙያ እንድመጣ ያደረገኝ ሙያውንም በፍቅር ወድጀው ነው የመጣሁት ከዚያ በኋላም ቀዳጅ ሐኪም የመሆን ጉዞው ሲጀምር እዚህ በማስተማር ላይ ካሉ ሰዎች ሁሉ በብዛት ቅርብ ሆኘ የሰራሁት ከፕሮፌሰር አሥራት ጋር ነው ሌሎችም እነ ፕሮፌሰር ታየ ጆንሰን የሚባሉ ነበሩ እነሱ ጋር ጥቂት ጊዜ ብሆንም ረጅም ጊዜ ግን ከፕሮፌሰር አሥራት ጋራ የመስራትና የመማር አጋጣሚ ስለነበረኝ በደንብ እቀራረባለሁ ማለት ይቻላል። እና ይሄ በጣም ደስ ይላል ከዚያ በተጨማሪ የሕክምና ስራ እንደምታውቀው በሕብረት የሚሰራ ሥራ ነው ፕሮፌሰር አሥራት ቡድኑ ውስጥ ያለውን ሰው አቅፎ የመስራት ልዩ ችሎታ አላቸው ፕሮፌሰር አሥራት ጋ ነርስ በጣም የተከበረ ነው ነርስን መናገርም አይቻልም ለነርሶቹ ዋጋ የሚሰጡ ሐኪም ነበሩ ወደ ሌሎቹም ስንሄድ ወደ ቴክኒሻኖቹ ዝቅ ስንል አንስቴዢያን ሌላም ቦታ ስናይ በጣም የቅርብ ነገር አላቸው በጣም ይከታተላሉ እነዚህን ሁሉ በቡድን የማሰራት ብቃት አላቸው በተለይ የበታች ናቸው የሚባሉትን ሰራተኞች አንድም ሐኪም አንድም ተማሪያቸው እንዲህ እንቃለሁ አይልም ይሄ በጣም ለየት ያለ ባህሪያቸው ነው ቀደም በየ እንደነገርኩህ በነርሶች ዘንድ በጣም የተለየ ፍቅር ያላቸው ሐኪም ናቸው ምክንያቱም ለነርሶቹ አክብሮት ስላላቸው ነው ነርሶቹ ለሚሰሩት ሥራ እውቅና ስለሚሰጡ በጣም ይወደዳሉ ይህ ባህሪያቸው በቡድን የመስራት ክህሎትን በዚህ ሆስፒታል ውስጥ ያቆየ ነገር ነው ብየ አምናለሁ በዚህ አመራራቸው ይህንን የቀዶ ሕክምና ትምህርት ክፍል ለሰላሳ ዓመት ገደማ መርተዋል መሪነት ማለት ዝም ብሎ ወንበር ላይ መቀመጥ ማለት ብቻ አይደለም ምን አልባት እንደዚህ ዓይነት አመራር ባይኖረው ኖሮ ይህን የመሰለ የትምህርት ክፍል ባልነበረን ነበር አሁን የቀዶ ሕክምና ትምህርት ክፍሉ ከሁሉም ትምህርት ክፍሎች በጣም ትልቅ ስፔሻሊቲ ያፈራ ክፍል ነው ይሄ ከጥሩ አመራር ባይነሳ ኖሮ እንዲህ ይሆናል ብየ ለመገመት አልችልም ስለዚህ እንደ አስተማሪ እንደ ሐኪም ብቻ ሳይሆን እንደ መሪም በጣም ተቀባይነት ያለው ስኬት ያስመዘገቡ ሰው ናቸው ፕሮፌሰር አሥራት ቀዶ ሕክምና ትምህርት ክፍሉን ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ የሕክምና ፋካሊቲውን የመሩ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ዲን ነበሩ በመጀመሪያ ከፈረንጆቹ ተረክበው ያስተዳድሩት የነበሩት ዲን ፕሮፌሰር አሥራት ነበሩ አንደኛውን ዙር ዲን ሲሆኑ ባልደርስም እንኳን ለሁሉተኛ ጊዜ ዲን ሲሆኑ ግን እኔም ነበርኩኝ ከእርሳቸው በኋላ ነው የፋካሊቲው አመራር ኢትዮጵያዊ እየሆነ የመጣው ፋካሊቲውን እንደዛ በጣም ትንሽ ከሆነበት አሁን ወዳለበት ሁኔታ ያደረሱት እርሳቸው ናቸው ያኔ እንግዲህ ከዐ እስከ የሚሆኑ ተማሪዎችን ብቻ ነበር የሚያስተናግደው አሁን ባለንበት ወቅት ይህ ፋካሊቲ ከፀዐዐ በላይ ተማሪ አለው ለዚህ ትምህርት ክፍል ማደግ ከጥንት የጀመረው ስርዓት የያዘ አመራር ወሳኝ ነው ብየ አምናለሁ ፕሮፌሰር አሥራት ሰዎች እንዲያድጉ ክፍሎች በእግራቸው እንዲቆሙ በጣም የተጣጣሩ መሪ ናቸው የቀዶ ሕክምና ትምህርት ክፍል ኃላፊ ነበሩ ማለት የሚያስተዳድሩት የቀዶ ሕክምናውን ብቻ ነው ማለት አልነበረም የማሕጸንና ፅንስ ስፔሻሊስቱን የራጅ ክፍሉን የአንስቴዢያን ክፍሉን የአጥንት ክፍሉን ሁሉም በስራቸው ነበር ቀስ በቀስ በመጀመሪያ የማሕጸንና ፅንስ ክፍሉ ተወለደ ቀጠለና አንስቴዢያን ክፍሉ ከዚያ ቀጠለና የአጥንት ክፍሉ ዲፓርትመንት ሆኖ ተወለደ አሁን ደግሞ በዙሪያችን ስናይ በጣም ብዙ ዲፓርትመንት የሚያካክሉ የከፊል ስቴሻሊቲ ፕሮግራሞች ለሕፃናት ለአዋቂዎች የሽንት ቧንቧ የደረትና የልብ የአንጀት የፕላስቲክ ብዙ ዓይነት ስፔሻሊስቶች እንዲመረቱና ያለንበት ደረጃ ላይ የደረስነው በፕሮፌሰር አሥራት ብልህ አመራር ነው በዚያን ጊዜ ኢትዮጵያዊያንን ማበረታታት በጣም ለሚቀብጡ ፈረንጆችም ገንቢ የሆነ ሒስ በመስጠት ወደ ትክክለኛው መስመር ያስገቧቸው ነበር እንዲያውም አንዳንዴ ፈረንጆቹን ምን እንደሚሏቸው በሩ ላይ ተጠግተን በሰማን እንል ነበር ምክንያቱም ከእርሳቸው ጋር ገብተው ሲወጡ በጣም ያስቸግሩ የነበሩ የውጭ ዜጎች ሁሉ አንገታቸውን ደፍተው ይወጡ ነበር ፕሮፌሰር አሥራት እኔ በማውቃቸው ጊዜ እንደ አስተማሪ እንደ ሐኪም እንደ መሪ በትክክል ምትክ የማይገኝላቸው በጣም የሚፈሩ ግን የፍቅር ሰው እንደነበሩ በስራቸው የነበረን ሰራተኛ ከለላ በመስጠት ደግሞ ማንም የማይስተካከላቸው ሲቀጡም ቢሆን ያለ ማንም እርዳታ መቅጣት የሚችሉ መሪ ነበሩ ችግሮችን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው የሚያውቁ በጣም ብልህ ሰው እንደነበሩ አስታውሳለሁ እኔ በአጋጣሚ ከቤታቸውም አንዳንድ ቀን እጋበዝ ነበር በተለይ ቀዳጅ ሐኪም ሆኘ ስመረቅ ከቤታቸው ተጋብዝ ሄጀ ነበር እና ከቤታቸው ሄደን እኔና ጓደኞቸን የሚያስተናግደን ሌላ ሰው አልነበረም እራሳቸው ነበሩ ትንሽየ ሽርጥ ነገር አድርገው ለእያንዳንዳችን ሻይ ቡና የሚቀዱልን እባክወን ቁጭ በሉ ራሳችንን እናስተናግድ ብንላቸው የሚሰሙ አልነበረም የእውነት ትህትናቸው እንዲሁ ከምናውቃቸው እጅግ የተለየ ነው ይህንን ዓይነት የተጣበበ ጊዜ ያላቸው ፕሮፌሰር አሥራት የትም ይገኛሉ ለቅሶ ሲኖር እዛ ናቸው ሰርግም ሲኖር ይገኛሉ ብቻ እንዴት እንደሚያመቻቹት ያስገርመኛል ለማሕበራዊ ሕይወት የነበራቸው ከበሬታ እጅጉን የሚደንቅ ነበር በዚህ ሙያ አካባቢ ምን አልባት አንድ ትልቅ ሰው የሙያ ክህሎቱንና መልካም ስነ ምግባርን እንደ ወንጌል ደግሞ አሳደገን ብየ የማስባቸው ሰው ፕሮፌሰር አሥራት ናቸው እና በዚህ አድራጎታቸው በእውነት በእኔም ሆነ በሌሎች ተማሪዎቻቸው ልብ ሁልጊዜ ይታወሳሉ በዚህም የተነሳ ማንኛውም ቀዳጅ ሐኪም የፕሮፌሰር አሥራትን ችሎታ ሳያወራ የሚያልፍበት ጊዜ የለም በኢትዮጵያ የሕክምና ማሕበር በየ ዓመቱ ፕሮፌሰር አሥራትን የምናስታውስበት ሳይንሳዊ አስተምህሮ አለን ፕሮፌሰር አሥራት ለዚህ ሐገር የቀዶ ሕክምና ትምህርት ፈር ቀዳጅ በመሆናቸው ያንን ደግሞ በእኛ በተማሪዎቻቸው ውስጥ ማስረጽ መቻላቸው በየዓመቱ ይታወሳል ፕሮፌሰር አሥራት በጣም ቁጡ ሰው ናቸው አንድ ነገር ከጠፋ ይቆጣሉ ሲቆጡ ደግሞ ልክ ነብር ተቆጥቶ እንደተነሳ ነው የሚያስመስሉት ለፈረንጁም ለሐበሻውም ለማንም አንድ ዓይነት ናቸው ሆኖም ግን አንድ ነገር ካልተበላሸ በስህተት ካልተሰራ በፍጹም አይቆጡም ሲቀርቡና ሲወዱም እንደዚያው ናቸው በጣም አዝናኝ የሆነ ቀልድ አላቸው ደስ ሲላቸው ይቀልዳሉ ያስቁሃል እርሳቸውም ይስቃሉ ጥቃት ቢደርስብህ ደግሞ እርሳቸው የመጀመሪያው ሰው ናቸው ከአንተ ጋር ቆመው ለመከላከል ሲመክሩም እንደዚያው ናቸው እኔንም መክረውኝም ያውቃሉ የእውነት አግባብ ያለው ምክር ነው የሚመክሩህ ስለዚህ ጠጋ ብሎ ላያቸው ሰው ፍቅራቸው ብዙ ነው ነገር ግን ዛሬ ወደዱህና ካንተ ጋር ሆኑ ማለት ብታጠፋ በወዳጅነትህ ትዘለላለህ ማለት አይደለም ሁሉንም አጣምረው የያዙ ሰው ናቸው አንድ ነገር ጠፋ ተብሎ እርሳቸው ጋ ሪፖርት ሲደረግ ልክ እንደ ፍርድ ቤት ነው የሚጣራው እከሌ አንተን አጥፍተሃል ቢልህ ወዲያውኑ ዘለው አይቆጡም እንዴት ሰራኸው። ተብሎ አብረው የሰሩት ሰዎች ተጠርተው ተጠይቀው እነርሱ ምስክርነት ሰጥተው ከዚያ በኋላ ነው ውሳኔ የሚሰጥህ እንደዚህ አይነት ነገሮች ሁልጊዜ በእኔም ላይ በመጡ ክሶች አጋጥመውኛል በመሆኑም ሳያጣሩ ምንም ሳይሉ ዝም ብለው አይቆጡም ግን አጣርተው ደግሞ ውሸት መሆኑን ካወቁ በጥፋትህ ልክ ቅጣትህን እንድታገኝ ያደርጋሉ በምክር የሚታለፉ ነገሮችን ያውቃሉ መቀጣት ያለብህንም ያውቃሉ ማስጠንቀቂያ መሰጠት ያለበትን ነገርም እንዲሁ ያውቃሉ አንዳንዴ አንድ ሁለት ቃል ብቻ ይናገሩና እያንዳንዱ ሰው ያደረገውን ነገር በትንሽ ጽሁፍ ሰነድ ላይ እንዲቀመጥ ያደርጋሉ ምንም ፍርድ አይሰጥበትም እንደ መጀመሪያ ደረጃ ማጠንቀቂያ እከሌ እንደዚህ ዓይነት ጥፋት ነበረው በዚህ በዚህ ጊዜ አጥፍቷል ተብሎ መረጃው ብቻ ይቀመጥ ነበር ይሄ ስርዓት የያዘ አቀጣጥ ነው እንዲሁ የዐይንህ ቀለም አላማረኝም ብለው የሚጠሉት ሰው የለም ጥሩ ከሰራህ ሁል ጊዜም ይወዱሃል ጥሩ የሚሰሩ ነርሶችን ይወዳሉ ጥሩ የሚሰሩ ሐኪሞችን ይወዳሉ ይህ ጸባያቸው ልዩ ያደርጋቸዋል ጥቁር አንበሳ ወደ አዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ገብቶ እንኳን ያልቆመ አንድ ጭቅጭቅ አለ እርሱም ተጠያቂነቱ ለሁለት ሚንስቴር መስሪያ ቤቶች መሆኑ ነው አንደኛው በትምህርቱ ዘርፍ ለትምህርት ሚንስቴር ሲሆን ሌላኛው በሕክምናው ዘርፍ ለጤና ጥበቃ ሚንስቴር ነው አንድ ሰው እዚህ ጋር ባለስልጣን ሆኖ ሲቀመጥ ሁለቱንም በእኩል መስራትና ማርካት ይጠበቅበታል ለሁሉም የሚገባቸውን ሪፖርት መስጠት ይኖርበታል ይሄ አንድ ወጥ አመራር ስላልሆነ ያስቸግራል ፕሮፌሰር አሥራት ግን በጣም ለረጅም አመታት ያለችግር ነበር የመሩት አሁን ግን ለጥቂት ዓመት እንኳን ይህን ሥራ ለመሥራት ብዙ ውጣ ውረድ አለው እና የዚያን ጊዜ እርሳቸው ተሰሚነታቸውም ሊሆን ይችላል የሚያቀርቡት ነገር ሁሉ የትም ቦታ ሂዶ ውድቅ ሊሆን ይችላል ተብሎ አይታሰብም በዚያን ጊዜ ይሞግታቸዋል የሚባል የሰው ኃይልም አልነበረም ምን አልባት እሱም ሊሆን ይችላል የረጅም ጊዜ አመራራቸውን በብቃት እንዲወጡ የረዳቸው በነገራችን ላይ ፕሮፌሰር አሥራት በመሪነት ቦታው ላይ እንዲቆዩ ያደረጋቸው የባለስልጣኖች ፍላጎት አልነበረም እኔ ተማሪ ሆኘ ፕሮፌሰር አሥራት ከዚህ ኃላፊነታቸው እንዲነሱ ብሎ ኢሰፓ ይወስናል በምትኩ ሌላ የኢሰፓ አባል የሆነ ቀዳጅ ሐኪም ተመደበ ተማሪውም ሰራተኛውም ሊቀበለው አልቻለም በወቅቱ ተማሪዎቹ ፊርማ በማሰባሰብ ጠቅላይ ሚንስትሩ ጋር በማስገባት ፕሮፌሰር አሥራት ወደ ቦታቸው እንዲመለሱ አደረግን እንግዲህ ይህ የሚያሳየው ሰውየው ያንን ያክል ተፈላጊነት እንደነበራቸው ነው በሰራተኛውም በተማሪውም ማኅበረሰብ ዘንድ በጣም ይወደዱ ነበር በዚህ የተነሳ ነው የመንግስት ፍላጎት ሆኖ አይደለም አመራሩን ይዘውት እንዲቆዩ የተደረገው ያልኩህ ፕሮፌሰር አሥራት የአስተዳደር ሥራቸውን እያከናወኑ የማስተማርና የማከም ተግባራቸውንም አላቆሙም ነበር አንድም የሚጓደል ሥራ አልነበረም ዲን ሆነው ኦፕራሲዮን ይሰራሉ ሌክቸር ይሰጣሉ የተመረጡ በሽተኞችን ያክማሉ ብዙውን ጊዜ በሽተኞች አሥራት በእጃቸው እንዲነኳቸው ይፈልጉ ነበር ሕክምናውን ሌሎቹ ዶክተሮች ብንችለው እንኳን አሥራት በአጠገባቸው መቆምና መታየት ነበረባቸው ስለዚህ ያን ሁሉ ለመሸፈን ችግር አልነበረባቸውም ወደ መጨረሻ አካባቢ አቅማቸው እየደከመ ሁሉንም ዙሮ መቆጣጠር እያቃታቸው ሲመጣ የባሰ ችግር ያለባቸውን በሽተኞች ብቻ አሳዩኝ በማለት ያክሙ ነበር ይሁን እንጅ ዲፓርትሚንቱን መምራትና ዲን ሆኖ መስራት አስቸግሯቸው አያውቅም በአጠቃላይ ሁሉም የእርሳቸው ተማሪዎች የምንጋራው አንድ ነገር አለ እንደ ቡድን መዋሃድ ለመርህ መቆም ስህተት የሆነውን ስህተት ነው የማለት እውነት የሆነው እውነት ነው የማለት ነገር ይህ በዋናነት የፕሮፌሰር አሥራት ተጽዕኖ ነው ፕሮፌሰር አሥራት አጋጣሚውን ለማለፍ ብለው ዋሽተው ወይም አታለው የሚሄዱ ዓይነት ሰው አልነበሩም ለሚያምኑበት ብቻ የሚኖሩ ሐኪም ነበሩ አስራትን በአንዳች ማስፈራራት ወይም በሌላ ነገር ከአመኑበት አንድ እርምጃ እንኳን ወደ ኋላ እንዲሉ ማድረግ አይቻልም እንግዲህ ፕሮፌሰር አሥራት እግዚአብሔር በሰጣቸው ዘመን ሕዝባቸውን አገልግለዋል ትውልድን ለማስተማር ተግተዋል የአደረጉት አስተዋጽኦም አሁን ጎልቶ ይታያል በእኛ ሐገር ሐኪሞች የሚጠቀመው ኢትዮጵያዊው ብቻ አይደለም አፍሪካዊው ይጠቀማል ከዚያም አልፎ አሜሪካ ብንሄድ የአሥራትን ተማሪዎች በጣም ብዙ ቦታ ማግኘት ይቻላል አፍሪካም ቢሆን በተለይ ደቡብ እና ምዕራብ አፍሪካ ብዙ የእኛ ቀዳጅ ሐኪሞች ይኖራሉ እነዚህን ተወዳዳሪ ሐኪሞች በብቃት እንዲማሩ ያደረጓቸው ፕሮፌሰር አሥራት ናቸው ይሄ ደግሞ ለኢትዮጵያዊነት ብቻ ሳይሆን ለሰብዓዊነትም ጉልህ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን የሚመሰክር ተግባር ነው ታምረ አሥራት ረየቀዶ ሕክምናው ሐኪም አሥራት በፈዋሽ እጃቸው ሙተዋል የተባሉትን ሳይቀር ከአልጋቸው ላይ ተነስተው ወደ ቤታቸው እንዲገቡ የሚያደርጉ ታምረኛ ሆኑ ይላል እሸቴ እስቲ እንቀንጭበው እንደ ገድል ያየኾቆቭሩ ሥራዎቻቸው ምተዎል» ክጉባሉ ወዲያ አፍ እያሐ ያዳድቸው እፅ እኳ የሰማኋቸው ሰረክቱቭብኝና ማንኛውን እንደምጽፍ ቻገረቻ ትን። ሮች የመያ ብቃትን ጉዳይ ጥያቄ ውሰጥ ጎያሰገቡ በሐገራቸው መቅጠር አጳያቅማሙም ዎናው ጉዳያቸው ዶክሮቹ ክውጭ የመጦ መሆናቸው ቻ ነውኖ በማለት አሥራት ለደርግ ካድሬዎች ልክ ልካቸውን ነግረዋቸው እናገኛለን በእርግጥ ዶክተር አሥራት እርሳቸው ከቆሙለት እውነት ምንም ነገር ቢመጣ ወደኋላ አያፈገፍጉም የሚለው የብዙወች እምነት ነው የተማሩትንና ቃል የገቡለትን የሙያ ስነ ምግባር ጠንቅቀው የሚያውቁና ተግባራዊ የሚያደርጉ ትጉህ ሐኪም ነበሩ በእርግጥ ይኸ ለመርሕ የመቆማቸው ጉዳይ በየዘመኑ ከሚመጡ ባለጊዜዎች ጋር ፊት ለፊት እንዲላተሙ አድጓቸዋል በሌላ በኩል ይህ ለእውነትና ለመርሕ የመቆማቸው ነገር ፕሮፌሰር አሥራትን ትምክህተኛ ወግ አጥባቂና ፊውዳል የሚሉ ስድቦችን እንዲያስተናግዱ አድርጓቸው ቆይቷል ፕሮፌሰር አሥራት ግን በሚመጣባቸው ቅጣትና ስም ማጥፋት ይልቅ እውነትን ማስቀደማቸው በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ እንዲሆኑ ከማድረጉም በላይ የሕዝብ ልጅ የሚል የክብር ስም እንዲጎናጸፉም ረድቷቸዋል ሞት ያዘለው ግዳጅ ከላይ እንዳየነው ፕሮፌሰር አሥራት የደርግን ካድሬዎች አደንቋሪ ትዕዛዝ አልቀበልም በማታለቸው የተነሳ በደርጉ አመራሮች አካባቢ ጥርስ ተነክሶባቸው ነበር ለሙያቸው ክብር በመቆማቸውና ከእውነት መርሕ ባለማፈግፈጋቸው እንዲሁም በሌሎች ሁኔታዎች ፕሮፌሰር አሥራትን ወደ ግዳጅ ልኮ ማስገደል በደርግ መንደር አይነተኛ መፍትሄ ሆኖ አገኙት አንድ ቀን ጠዋት ፕሮፌሰር አሥራት በአንድ የሥልክ ጥሪ ለግዳጅ ወደ ምጽዋ እንደሚላኩ ተነገራቸው ምንም እንኳን ፕሮፌሰሩ ከዚያ በፊት በተደጋጋሚ የዘመቱ ቢሆንም የአሁኑን ለየት የሚያደርገው ዘመቻው ከጀርባው ያዘለው ክፉ ተንኮል ነው ፕሮፌሰሩ ላይ ቀደም ብሎ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሐኪም ናቸው የሚል ስም ማጥፋት በመሰራቱ የተነሳ ማንም ተራማጅ» ነኝ ባይ ሁሉ እንዲገድላቸው ታስቦ የተደረገ ዘመቻ ነበር ፕሮፌሰር አሥራት በአጠቃላይ በወቅቱ ስለነበረው ሁኔታ ለሙዳይ መጽሔት ሶስተኛ ዓመት ቁጥር መስከረም ፖ ዓም እትም የሚከተለውን ተናግረው እናገኛለን እንደምታውቄት የመጀመሪያዎቾቹ መናት ሰዎች ልዩ ለልዩ ፅም ያሟሰጥሰትቶ ግድያም ነበር እፅይማ ፈርዶብ ቀዳማዊ ኃይ ሥላሴን ሰማክሜ መሰቻ በተራማጂ ክፍጳ እድ አድሃሪ ወሰድኩች ጥዊት ቆመፓት ሰእፅ ላይ የታሰቦ ነገሮች እንደነበሩ አውቃሁ በእውነኙ ደረግ ራሱ ጎይሆን ያኔ ብቻ ድረርሯቶች ሰነበሩ ብ መንግሰታት እንዳሐ ነው የሟቆጠረው። ይህም በሐኪሙና በታካሚው መካከል የሚፈጠረውን አለመግባባበት እጅጉን ይቀንሰዋል በሌላ አባባል መልካም የሆነ ተግባቦት ይኖራቸዋል ማለት ነው ብዙ ጊዜ እንደ ቀልድ የሚነገር አንድ የሕክምና ቁምነገር አለ ለምሳሌ አንድ ሰው ምኑን እንደሚያመው ለሚጠይቀው ሐኪም ይሸቀሽቀናኛል አናቴን ይከፍለዋል ደረቴን ይገምሰዋል ቆሽቴን ያሳርረኛል ከዚህ ጀምሮ እስከዚህ ድረስ ያርሰኛል ወዘተን ብሎ ቢነግረው ሐኪሙ የሐገሬውን ብሂል ካልተረዳው የሰውየው ሕመም እንዴት ብሎ ሊገባው ይችላል የውጭ ሐኪሞቹ ዋነኛው ጉድለትም ይሄ ነው የእነ ፕሮፌሰር አሥራት ሙግትም ከዚህ የሚመነጭ ነው ይህንን እድል ነው እንግዲህ የውጭ ሰዎች ለማዘግየት ወይም ለማስቀረት ጥረት ሲያደርጉ የነበረው በእርግጥ ሁሉም የውጭ ሐገር ሰዎች ምክር አፍራሽ ነበር ማለት አይቻልም ብዙ ባለሙያዎች ራሳቸውን መስዋዕት አድርገው ያለ ምንም ዕረፍት እና ራስ ወዳድነት ያገለግሉ ነበር ለምሳሌ የዴች ተወላጅ የሆኑት ዶክተር ዴከር ከሃያ አመታት በላይ ኢትዮጵያን በማገልገል ሊጠቀሱ የሚችሉ ባለውለታችን ናቸው ምስጋና ለፕሮፌሰር አሥራት እና ለባልደረቦቻቸው ይድረሳቸውና አይሆንም» የተባለውን ነገር በከፍተኛ ትግል የኢትዮጵያውያን የመጀመሪያው ሕክምና ኮሌጅ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩንቨርሲቲ ሥር ተከፈተ እኤአ ዓም ዓም ከፕሮፌሰር አሥራት ጋር እንደ ፕሮፌሰር እደማርያም ጸጋ ዶክተር ጳውሎስ ቀንዓ ዶክተር ነቢያት ተፈሪ እና ዶክተር ደምሴ ሀብቴ የመሳሰሉ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ተጀመረ ሕክምና ፋካልቲውም በቀዶ ሕክምና በውስጥ ደዌ ሕክምና ጋይናኮሎጂ እና ኦብስተተሪክስ ኦፕታልሞሎጂ እና ፔዲያትሪክስ በመሳሰሉ የሙያ መስኮች ሥልጠናውን ጀመረ ኢትዮጵያን ሪቪው እኤአ ሰኔ ዓም እትም እንዳተተው ከሆነ እኤአ በ ዓም የቀዶ ሕክምና ተባባሪ ፕሮፌሰር በመሆን የመጀመሪያው የፋካሊቲው ዲን ሆኑ ክብር ለእነዚህ የሐገር ባለውለታዎች ይግባቸውና ኢትዮጵያዊያን ለዘመናት ሲጠቀሙበት የነበረውን በውጭ ሐኪምና ከውጭ ሰልጥኖ በመጣ ኢትዮጵያዊ በመታከም ፋንታ በራሳቸው ሐገር በሰለጠኑ ባለሙያዎች ለመታከም ዝግጅታቸውን አንድ ብለው ጀምረዋል ሙሉ ጊዜያቸውን ያለምንም ስስት መስዋዕት ያደረጉት ፕሮፌሰር አሥራትና ባልደረቦቻቸው የኢትዮጵያዊን መመኪያ የሆነ የሐገር ውስጥ ተቋም ለመገንባት በነበራቸው ህልም መሠረት የጥቁር አንበሳ የሕክምና ማሰልጠኛ ተቋም በዩኒቨርሲቲው ሥር እውን አደረጉ ለህዝባቸው ከነበራቸው ቀናኢ ሃሳብ በመነሳት ሙያቸውን ለሐገራቸው ልጆች በማስተላለፍ ጉዚቸውን ጀመሩ ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ስለ ጥቁር አንበሳው የሕክምና ኮሌጁ አጀማመር ለሪፖርተር ጋዜጣ ጥቅምት ቀን ዓም እትም የሚከተለውን ተናግረው አግኝተናል ርበዚህ ሆስፒታል ጥቁር አንበሳን በሐኪምነት ብቻ ሳይሆን ከምስረታው ጀምሮ የተካፈልኩበት ነው በእኔ ሊቀ መንበርነት የሚመራ ኮሚቴ ነው ሆስፒታሉን ለፍጻሜ ያደረሰው ከመጀመሪያው ከሃሳቡ ጽንስ ጀምሮ የተካፈልኩበት ነው ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚጠቅም መታሰቢያ ይሁን ተብሎ ከተወሰነ በኋላም የቴክኒካል ኮሚቴውን በሊቀ መንበርነት የመራሁት እኔ ነኝ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዳር እስከ ዳር ገንዘብ አዋጥቶ ስለነበር ለልዑል መኮንን መታሰቢያ ነበር የታቀደውን ምን አይነት መታሰቢያ ይሁን። እነሆ ረበእውነት ማንም ኢትዮጵያዊ በእኔ ግምት ወርቅ ቢያነጥፍ ከዚያችው ጎስቋላ ሐገራችን መኖርን የማይመርጥ የለም የትም ያለ ኢትዮጵያዊ ይሁን ሐገር ውስጥ ያለው በሐገሩ ሲኮራ አነሰም በዛ ሐገሬ ብሎ ሲል ደስ ይላል እንደው ለሁለታችሁም ታላቅ ነኝ ምክርም ጭምር ነው ብዙ ነገር ሊደረግ ይችላል በርካታ ሰዎች ታስረው አንዳንዱም ትክክለኛ ፍርድ ሳይሰጣቸው ይገኛሉ እንዲህ ያሉት ነገሮች የአያት ቅድመ አያቶቻችን ታሪክ አይደለም ይሄ ነገር መላ ይመታለት ሁለተኛ ሽማግሌ ይደመጥ እስቲ ንጉስ በአልጋ ይታማል ይባላል ሽማግሌወችን አማክሩ እንዲህ አይነቱ ነገር የግድ መደረግ አለበት ሐኪምም ነኝ አውሮፕላንም አበራለሁ ነፍጠኛም ነኝ እንግሊዝ ሐገር አንድ ጥሩ ፓይለት ለማሰልጠን ገ ሚሊዮን ፓውንድ ይፈጃል ስለዚህ ምሁራኖቻችን ወርቆቻችን ናቸው ስንት የተማረ በየሐገሩ አለ ስንት ነገር ሊደረግ ይችላል እኛ ሐገር ውስጥ የፈሰሰውንም ንብረት መመለስ ያስፈልጋል የቆረጣው ምክር ቤት ረአንድ ልበ ሙሉ ሰው አንድ ብቻውን እንደ ብዙሃን የሚቆጠር ነው ጆን ኦፍ ኬኔዲ ርከዚያ ስብሰባ ላይ በወቅቱ በፍጹም ያላሰብኩት ነገር ይካሄድ ጀመር ለካ ከእኔ በስተቀር በኤርትራ መገንጠል ጉዳይ አቋም ተወስዶ ቤቱ ውስጥ ተሳታፊ የነበረ በሙሉ ተስማምቶ ኖሯል እኔ ዘንድ ሲደርሱ ሐገር ለማስገንጠል ውክልና ተሰጥቶኝ አልመጣሁም ብየ ተናገርኩ ሪፖርተር ጥቅምት ቀን ዓም ቀድሞ ባለቀ ነገር የተሳተፉት ፕሮፌሰር አሥራት በጉባኤው ምን እንደሚካሄድ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ከላይ የሰፈረው ሃሳባቸው ያስረዳል ይህን ሃሳብ በሰኔው ኮንፈረንስ ላይ በታዛቢነት የገቡት ዶክተር መኮንን ቢሻውም ይጋሩታል ርየሐገሪቷን ችግሮች በመገንዘብ በኮንፈረንሱ ወቅት የሚቀርቡት ጉዳዮች ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ ከመጠርጠር በቀር ወደ ኮንፈረንሱ እስክንሄድ ድረስም ሆነ እዚያ ከደረስን በኋላ በየእለቱ ከሚገለጽልን በቀር የውይይት አጀንዳው ምን እንደሚሆን አስቀድመን የምናውቀው ነገር አልነበረም አዕምሮ መጽሔት ህዳር ፀ ዓም የሽግግር መንግስቱ ተመሰረተ ተባለና የኮንፈረንሱ ተሳታፊዎችም በዚያው የሽግግር መንግስቱ ምክር ቤት አባል ሲሆኑ ለከፍተኛ ትምሕርት ተቋማት ተሰጥቶ የነበረው አንድ ወንበር ግን ክፍት ሆኖ ነበር ወንበሩ ክፍት የሆነበት ምክንያትም ፕሮፌሰር አሥራት በወቅቱ የከፍተኛ ትምሕርት ተቋማት መምህራን የወከሏቸው በኮንፈረንሱ ለመሳተፍ እንጂ የምክር ቤት አባል ሆነው እንዲሰሩለት አልነበረምና ነው ስለዚህ ጉዳይ የኮንፈረንሱ ታዛቢ የነበሩት ዶክተር መኮንን ቢሻው እኔም ሆንኩ ፕሮፌሰር አሥራት ውክልናውን ተቀብለን የሄድነው በኮንፈረንሱ ላይ ሃሳብ ማቅረብና ከሌሎችም የሚቀርቡትን ማዳመጡ ከመጥቀም ሌላ አይጎዳም በሚል እምነት እንጅ የምክር ቤት አባል ሆኖ ለመሥራት አልነበረም የመረጡንም መምህራን ለምክር ቤት አባልነት እንዳልነበር በወቅቱ ግልጽ ነው እንዲያውም ኮንፈረንሱ ወደ ምክር ቤት እንደሚቀየር ከመካከላችን የሚያውቅ አልነበረም በተለይ ፕሮፌሰር አሥራት የወሰዱት አቋም ትክክል ነበር ይህን አቋም መውሰዳቸው ብሔር ብሔረሰቦች የራሳቸውን እድል በራሳቸው ለመወሰን ያላቸውን መብት እንደማይቀበሉ ተደርጎ መተርጎሙ ትክክል አልነበረም በማለት ስለ ምክር ቤቱ ሕዝብ ውክልና አልባነት ያስረዳሉ የኤርትራን መገንጠል ያልደገፉት የብሔር ብሔረሰቦችን የራስን ዕድል በራስ መወሰን ስለማይቀበሉ ነው ተብሎ ስለሚወራው ነገር ከሙዳይ መጽሔት መስከረም ዓም እትም ጋር ሰፊ ቃለ ምልልስ ያደረጉት ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ሁኔታውን በግልጽ አብራርተዋል ርየብሔር የቋንቋ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ጉዳይ ከሆነ እንደ ማንም ኢትዮጵያዊ ሆኘ ነገሮችን ባያቸው መጀመሪያ አስፈላጊነታቸውን ነው የማየው በኢትዮጵያ ውስጥ ኢትዮጵያ ሕዝብ ይኸን ያህል አብሮ የኖረውን በጋብቻ በዝምድና በሥራ በሁሉ ነገር የተዋሃደውን አሁን መሐሉ ገብቶ እነዚህን ያልጠየቃቸውን ጥያቄዎች አምጥቶ ማማሰል ትክክል አይደለም። ለነገሩ አምባገነኖች የአንድ እናት ልጆች ነው የሚመስሉት አምባገነኖች አድራጎታቸው ሁሉ ዘመንና ቦታ ሳይለያቸው ተመሳሳይ ነው ፕሮፌሰር አሥራትም አንድ ድምፅ ብቻ በመሆናቸው ምንም እንኳን ሰነዱን ከመጽደቅ ኤርትራንም ከመገንጠል ባያስቀሯትም በኢትዮጵያውያን ልብ ግን አርበኝነታቸው ሁሌም ታትሞ ይኖራል ታሪክም ሲያስታውሳቸው ይኖራል በአጠቃላይ በዚያ ጦሰኛ ኮንፈረንስና የሽግግር መንግሥት ምሥረታ ወቅት ባደረጉት ተሳትፎ ፕሮፌሰር አሥራት በሻዕቢያና በወያኔ ጥምር የአዞ መንጋጋ ውስጥ ገብተዋል አማራን እንደ ቃየል ረየሕወሓት ትግል ጸረየአማራ ብሔራዊ ጭቆና ነው የሚል ዓላማ አንግቦ ጫካ የገባው ተገንጣይ ቡድን በትረ ሥልጣኑን ሲይዝ የተነሳለትን ሰንካላ ዓላማ ለማሳካት በአማራ ሕዝብ ላይ የበቀል ዶፍ ማውረዱን ጀመረው ሕወሓት በአማራ ሕዝብ ላይ ከሰራቸው በደሎች ለዚህ ርዕሰ ጉዳይ የሚቀርበው ትልቁና ዋነኛው አማራውን በሽግግር መንግስቱ ያለ ምንም መቀመጫ ያስቀረበት ጉዳይ ነው ሕወሓት ሻዕቢያና ኦነግ የደርግን ሥርዓት አስወግደው በአሜሪካኖች በመታገዝ የሽግግር መንግሥት ለማቋቋም ሲዘጋጁ በአንድ ወር ውስጥ በተደረገ ሽርጉድ ምንም እንኳን ሁሉንም ባያካትትም የተወሰኑ ትጥቅ አንግበው ደርግን ሲፋለሙ የነበሩትን ጨምሮ ሁሉም ብሔሮች እንደ አቅማቸው ተወካዮቻቸውን በመላክ ሰኔ ቀን ዓም በተጠራው ኮንፈረንስ እንዲሳተፉ ሲደረግ በወቅቱ የሐገሪቱን ሕዝብ አንድ ሶስተኛ ይሸፍን የነበረው የአማራ ሕዝብ ግን ያለ ምንም ተወካይ እንዲቀር ሆነ አብዛኞቹ የኮንፈረንሱ ተወካዮች ከዚሁ ከተማ ውስጥ ተጠራርተው ተደራጅተናል በማለት የቀረቡ መሆናቸው ይታወቃል ሌሎቹ ህዝቦች እንደ አቅማቸው ውክልና ሲያገኙ ከሐገሪቱ ሕዝብ አንድ ሶስተኛውን የሚሸፍነው የአማራ ሕዝብ ግን ምንም ውክልና በሌለበት የሽግግር መንግሥት እንዲተዳደር ተደረገ በአማራ ሕዝብ ላይ ከተፈጸሙ በደሎች ሁሉ ይሄን ግፍ የሚስተካከለው ያለ አይመስለኝም ያልኩትም በዚህ ምክንያት ነው እንደ ሕዝብ አስተዳድርሃለሁ በሚለው መንግሥት ውስጥ አንድም እንኳን ተወካይ ሳይኖረው ያን ሕዝብ እንዴት ማስተዳደር እንደሚቻል የሚያውቁት በወቅቱ ሥልጣን ላይ የነበሩ ሰዎች ብቻ ናቸው አማራው ለምን ያለ ተወካይ እንዲቀር ሆነ ተብሎ የተጠየቀው የሽግግሩ መንግሥት ፕሬዚዳንት የነበረው መለስ ዜናዊ ርአማራውን በውስጡ አልፈን ስለመጣን ችግሩን ተገንዝበንለታል በማለት ነበር የመለሰው ይህ መቸም በአንድ ትልቅ ሕዝብ ላይ የተሰነዘረ ከስድብ የማይተናነስ መሪር ቀልድ ነው በዚህ አመክንዮ ሎጅክን ከሄድን ደግሞ በውስጡ አልፎ መምጣት ብቻ አይደለም እንደ ዋሻ ሲገለገሉበት የቆዩትና አብረውት የኖሩት የትግራይ ሕዝብ ተወካይ አያሻውም እንደ ማለት ነው የሌላው አካባቢ ሕዝብና ድርጅትም ሁኔታ ተመሳሳይ ነበር ጦቢያ መጽሔት ሁለተኛ ዓመት ቁጥር ረየሽግግር መንግሥት አቋቁሜ አገሪቱን እመራለሁ ያለው ኢሕአዴግ በመንግስቱ ሥርዓት ውስጥ አማራውን ለማሳተፍ ፍላጎቱ ያለው አይመሥልም ካለ በኋላ የሚከተለውን ሐተታ አስፍሮ እናገኘዋለን ረአቶ መለስ ወደ አዲስ አበባ ሲገሰግሱ በነበረበት ወቅት ለአሜሪካዊው አማካሪያቸው ለሚስተር ፖልሄንዝ በሰጡት ኢንተርቪው ትግላቸው በአማራው በተለይ በሸዋው አማራ ላይ መሆኑን ገልጠው ነበር ይህን መግለጫ በጥሬ ቃሉ መቀበል አያመች ይሆናል ፖልሄንዝ ምን አልባት የገዥ መደብ ጽንሰ ሃሳብ አስተካክለው ስላልገባቸው ካልሆነ አገላለጡ አንድን ብሔረሰብ የመጨረስ ከዘር ርፀፀበፍከፀን ሊመሥል ይችላል ኮሊን ሊጀም የተባለ በዜግነት እንግሊዛዊና በትውልድ ደቡብ አፍሪካዊ የሆነ ጋዜጠኛ በአንድ የአሜሪካ አውደ ጥናት ላይ ስለ ኢትዮጵያ ባቀረበው ሰፊ ጥናታዊ ሪፖርት አማራውን ከማለቅ ለማዳን የሚል ርዕስ መርጦ ነበር ምን አልባት የፖልሄንዚ ዘገባ አስደንግጦት አለዚያም የፖለቲካውን ሂደት በመከታተል ወደዚህ መደምደሚያ በመድረሱ ይሆናል ሲል ያትታል ጦቢያ የነሐሴ ዓም ዕትም ከዚህ በተጨማሪ የኢሕአዴግ መሪዎች በተለያየ ወቅት የተናገሩት አማራን እንደ ሕዝብ የመካድና የማጥላላት ሁኔታ በአማራው ሕዝብ ላይ ለሚወሰድው እርምጃ ሁሉ እንደ ቅድመ ፈቃድ ተቆጥሮ ነበር በጣም ከበዛው ምሳሌ ለመጥቀስ ያክል የኢህዴን በኋላ በመለስ ዜናዊ ቀጭን ትዕዛዝ ብአዴን የሚል የዳቦ ስም የተቀበለው ድርጅት መሪና የሽግግሩ መንግስቱ ጠቅላይ ሚንስትር የነበረው ታምራት ላይኔ ወደ ሶማሌ ክልል ሄዶ ነፍጠኛው ሽርጣምምንትስ ሶማሌ ሲልህ የኖረ ስለሆነ የመበቀያ ጊዜህ አሁን ነው ብሎ በአማራ ሕዝብ ላይ የሞት አዋጅ ሲያውጅ የሽግግር መንግስቱ በሰውየው ላይ ምንም ዓይነት እርምጃ አለመውሰዱ የአማራን ሕዝብ በሐገሩ እንደ ቃየል ተቅበዝባዥ እንዲሆን እና ማንም ድንጋይ አንስቶ ይወግረው ዘንድ የይለፍ ፈቃድ የሰጠ ነበር እነዚህ ነገሮች ተደማምረው ተወካይ አልባውን አማራ ተወልዶ ባደገበት ሐገር እግሩን ለጠጠር ደረቱን ለጦር ሰጥቶ ባቀናው መንደር መጤ ተብሎ እንዲሳደድ ተደረገ ደሙም የውሻ ደም ሆኖ የትም ይፈስ ዘንድ ተበየነበት አማራን ማሳደድ መግደል እና ማፈናቀል የሚያሸልም እንጂ የሚያስከስስ ተግባር አልሆን አለ በአጠቃላይ አማራው ባለቤት የሌለው ዕቃ ሆኖ ተገኘ ምንም እንኳን አማራው በአንጻራዊነት ከሌላው ማኅበረሰብ በተሻለ የተማሩ ልጆች ቢኖሩትም ቅሉ አንዲት ኢትዮጵያንን በምትባል ሐገር ፍቅር ተነደፍን በሚሉት ፈሊጥ ህዝባቸው ላይ የሚዘንበውን የመከራ ዶፍ ሊመለከቱበት የሚችለው መነጽራቸው አላሳያችሁ አላቸው በወቅቱ እያንዳንዱ ሕዝብ ተወካይ ያለው በመሆኑ እና አማራው ምንም ዓይነት አደረጃጀት ስላልነበረው ይህ ትምክህተኛነታችሁ ነው እንዳትሰባሰቡ ያደረጋችሁ በሚል ክስ አቅም ያለው ሁሉ በዚህ መከረኛ ሕዝብ ላይ ፈርጣማ ክንዱን ሰነዘረ አማራው ኢትዮጵያን ጠንካራና የታፈረች ሐገር ለማድረግ ሲባል በተደረገው የግዛት መልሶ ማዋሃድ ሂደት ሰፊ ድርሻ ነበረው ይህ ሊያስመሰግነው የሚገባ ደርጊቱ ግን እንደ ወራሪ ነበር የተቆጠረበት ዳር ድንበርን ለመጠበቅ በነበረው ከፍተኛ ፍላጎትና ስሜት ነፍጥ አንግቦ ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር በመሆን ሉዓላዊነቱን ከጠላት ወረራ ሲጠብቅ ኖሯል ለዚህ አገር አቅኝ የገበሬ ወታደር ነፍጠኛን በወቅቱ እንደ ደመወዝ ሆኖ የሚያገለግለው ደግሞ መሬት ነበር በመሆኑም በየደረሰበት ያገኘውን ጠፍ መሬት አልምቶ በመኖሩ ነፍጠኛ ወራሪ» የሚል የዳቦ ስም ተሸለመ ነፍጠኛ ማለት ግን በመሳሪያ አንጋችነት የሐገሩን ዳር ድንበር የሚጠብቅ የዘመኑ ወታደር ማለት እንጂ ወራሪ ማለት አልነበረም ስሙን ሰጭዎቹና አሳዳጆቹም ቢሆኑ ይሄን ቁምነገር አጥተውት አልነበረም ይልቁንስ የወደቀ ዛፍ ምሳር ይዛበታል የሚለውን አባባል ተግባራዊነት ለማስረገጥ እንጂ የዘመኑ ልሂቃን ግን ነፍጠኛነትን ከወራሪነትና ከጨቋኝነት አቆራኝተው በመለንቀጥ ነፍጠኛነትን በሐገር ግንባታው ሂደት ትልቅ አስተዋጽኦ ለነበረው ለአማራው ሕዝብ ለብቻው ሸለሙት እነዚህ ብሔርተኞች የአማራን ሕዝብ ለመክሰስ እንዲያመቻቸው ሲሉ ብቻ የሁሉም አካባቢ ታላለቅ ሰዎች በሐገር ግንባታው ሂደት የነበራቸውን ጉልህ ሚናም አፈር ድሜ የሚያስበላና ታሪካቸውን የሚያደበዝዝ ድርጊት መሆኑ አልገባቸውም ወይም ሆነ ብለው ዘንግተውታል የታሪኩ እውነታ ግን ምንም እንኳን አማራው በወቅቱ ጎላ ብሎ ይታይ እንጂ ነፍጠኛው ከሁሉም አካባቢ የተውጣጣ ባሕላዊ ወታደር መሆኑን ነው የሚያሳየው የዘመኑ ብሔርተኞች አላወቁትም እንጂ ነፍጠኛነት የሚያኮራና የሚያሸልም ተግባር ነበር በዚህ የተንሻፈፈ የታሪክ አተያይ አማራውን ነፍጠኛ ወራሪ በማለት በቀደሙት አያቶቹ ታሪክ እንዲያፍርና እንዲሸማቀቅ ከፍተኛ የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ ተደረገበት በሽግግር መንግስቱ የአማራ ሕዝብ በያለበት መሳሪያውን እየተነጠቀ ትጥቅ እንዲፈታ ተደረገ የአማራ ገበሬዎች ቤት ተቆልፎባቸው ተቃጠሉ ነፍሰ ጡር ሴት ሳትቀር ሆዷ እየተቀደደ ሽሏ እንዲወጣ ተደረገ አማራው በራሱ መሳሪያ እንዲጨፈጨፍ ተደረገ አቤት ባይ የሌለው የሐገሩ ባይተዋር ሕዝብም ሆነ ከዋለልኝ መኮንን ኢትዮጵያ የብሔረሰቦች እሥር ቤት ናት ከንፋስ የቀለለ ትርክት የሚነሳው የብሔርተኞች መከራከሪያ መደምደሚያው የሚያርፈው አማራ ብሔራዊ ጨቋኝ ነበር ከሚል ስንኩል የፈጠራ ታሪክ ላይ ነው በእርግጥ አማራው ከየትኛውም ኢትዮጵያዊ ባላነሰ ሁኔታ አንዳንዴ በተሻለ ሁኔታን የሐገሩን ዳር ድንበር ሲጠብቅ ኖሯል አንዳች ወራሪ በመጣ ጊዜ ና ዝመት ሲሉት ነፍሰ ጡር ሚስቱን ልጆቹንና ደካማ ወላጆቹን ትቶ ግንባሩን ለእርሳስ ደረቱን ለጦር እግሩን ለጠጠር ሲሰጥና ሲዋደቅ እንደኖረ ዓለም የሚስማማበት ሐቅ ነው ርአማራ የሚባለው ሕዝብ ፈሪሃ እግዚአብሔር ያለው ሐገሩን የሚወድ እና ምርጥ አርበኛ ሕዝብ ስለሆነ ከሌሎቹ ኢትዮጵያዊያን ነጥሎ ማጥፋት ብቸኛው አማራጫችን ነው ምክንያቱም አማራ እስካለ ኢትዮጵያን ወረን መያዝ አንችልም ይላሉ ጣሊያኖች የሕወሓት አማራን የማጥፋትና የማዳከም ጥንስስ መነሻም ከዚህ የቅኝ ገዥዋ ጣሊያን እይታና ትርክት የሚመነጭ ነው በእርግጥ ጣሊያንን ከሐገራችን ነቅሎ በማስወጣቱ ሂደት ላይ የአማራው ድርሻ ክሱት ነበር ለዚያም ነው የጣሊያን የጥፋት ማዕከል አማራው ላይ ያነጣጠረው ሐገር ተደፈረች በተባለ ጊዜ እንደ ተርብ የሚናደፈውንና ዳር ድንበሩን ለማስከበር አንዳች ሰበብ የማይደረድረው ምስኪን አማራ በትግሉ ባቆያት ሐገር እንደ መጻተኛ ተቆጠረ የአማራ የሆነ ባህሉ የእምነት ተቋማቱ የሚተማመንበት ሁሉ ውጉዝ ከመ አሪወስ ተባለየማንነቱ መገለጫ የሆኑ ቅርሶቹ በፀሐይ ግባት ሲቸበቸቡ ጀግናየ ያላቸው አባቶቹ ሀውልታቸው ፈርሶ በጋሬ ሲጎተት አለውልህ የሚለው አንዳች ኃይል አልነበረም በጣም የሚገርመውና የሚያስደንቀው ነገር ደግሞ አማራው የሚደርስበት ግፍ ሁሉ ቀድሞ የበደለውን እንደ ማወራረድ ነው በሚል ሰሚ አለማግኘቱ ነበር ይባስ ብሎ በአማራ ሕዝብ ስም በእነ ታምራት ላይኔ እና እንድሪያስ እሸቴ አዝማችነት ልንደ ዶክተር አበባ ፍቃዴ አጠራር ባንዶችን የተመራ የልዑክ ቡድን ወደ ኤርትራ ተልኮ በሚሊዮን በሚቆጠረው የአማራ ሕዝብ ስም እስካሁን በኤርትራ ምድር የተደረገው ጦርነት ሁሉ አማራው ኤርትራን ቅኝ ለመግዛት ያደረገው የወረራ ጦርነት በመሆኑ ለጠፋው ሁሉ ይቅርታ እንጠይቃለን ብሎ መመለሱ ነበር የወደቀ ግንድ ምሳር ይበዛበታል ይሉሃል ይሄ ነው ይሄ ሁሉ ድርብርብ በደል የአማራን ሕዝብ ከፍተኛ ለሆነ የሥነ ልቦና ቀውስ ለመዳረግ ታስቦ የተቀመረ መሆኑ ነው ዳሩ ግን የአማራ ሕዝብ አስተዋይና ነገን መመልከት የሚችል ነበርና በትግሉ ከተጋረጠበት ዳፋ መዳን ችሏል ጨቋኝ በዝባዥና ቅኝ ገዥ የተባለ ሕዝብ ግን እስካሁን ድረስ የእንጨት ድልድይ የሚሰራለት እንኳን ባለማግኘቱ ወንዝ ሲያቋርጥ የውኃ ሲሳይ ይሆናል በድህነት በዓለም ላይ የሚስተካከለው አንድም ሕዝብ የለም ሲል ኦክስፎርድ በቅርቡ አሳውቋል ለነገሩ ስለ አማራ ሕዝብ ድህነት ለማወቅ ኦክፎርድን ማስለፋት ላያስፈልግ ይችላል ማንም ወደ አማራ ክልል የገጠር መንደሮች ወጣ ቢል በድህነት የተጎሳቆሉና ልብሳቸው ላያቸው ላይ ያለቀ አርሶ አደሮች ገጽታ ድህነታቸውን አፍ አውጥቶ ይመሰክራልና የቀደሙት ነገስታትም ከሌላው አካባቢ ሕዝብ በባሰ ሲገርፉትና ሲበዘብዙት ከረሙ እንጂ እነ እንድሪያስ እሸቴ እንደሚሉት ቅኝ ገዥ አልነበረም ይህን ድሃና ጎስቋላ ሕዝብ ነው ሕወሓት ብሔራዊ ዕረፍት መንሳት አለብኝ ሲል በቀረጸው ማንፌስቶው መሠረት ሥልጣኑን ሲጨብጥ የጥፋት ዓላማውን ተግባራዊ ያደረገበት ምዕራፍ አምስት አማራን የመታደግ እንቅስቃሴና የመዐሕድ መመስረት አንደበት ላጣ ሕዝብ ካልተናገርክለት ወንጀል አይሆንም ወይ ወገኑ ነኝ ማለት ገጣሚ ኃይሉ ገሞራውን ረከአራት የማንበልጥ ሰዎች ሆነን ሐምሌ ቀን ዓም ነው የመሠረትነው የፖለቲካ ሥርጭቱ እንዳሁኑ በየጎጡ እንደሚደረገው የመንደር ስብስብ ለማድረግ ዕቅድና ዓላማ አልነበረንም የመጀመሪያው ዕቅዳችን የኢትዮጵያን አንድነት ሊያስጠብቅ የሚችል ፕሮግራም መንደፍ ነበር እኛ ያሰብነው የፖለቲካ ድርጅት አቋቁመን ውሳኔ ከመስጠታችንና መርሃ ግብሩን ከማስታወቃችን በፊት በኢትዮጵያ አንድነት የሚያምኑና የሚጸጸቱ ምሑራንን ሰበሰብን ረርይህ በእንዲህ እንዳለ በጥቅምት ወር ዓም አንድ ወዳጀ የሆነ ሰው ከጋራ ሙለታ መጥቶ መሳሪያችን እየተነጠቅን በገዛ መሳሪያችን እየተደበደብን ነው ተጨፈጨፍን አለቅን ችግሩን ለኢሕአዴግ ስናስረዳ ለኦነግ ንገሩ ተባልን ለኦነግ ስንነግር ደግሞ ለኦህዴድ ንገሩ ተባልን ለኦህዴድ ስናመለክት እነሱ ደግሞ እንደ ቀደሙ ለኦነግ አመልክቱ አሉን ተስፋ ሳንቆርጥ ኦነግ ጋ ተመልሰን ለአቤቱታ ቀረብን ኦነግም ለእናንተ መሣሪያ አይሰጣችሁም ብሔራችሁ ሰብሳቢና አደራጅ ስለሌለው ለግለሰብ መሣሪያ አንፈቅድም አሉን ብሎ ከነ ነፍሳቸው በእሳት የተቃጠሉ ዘጠና ስድስት ሰዎችን ስም ዝርዝር ከነ አድራሻቸው የተጻፈበት ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚንስትሩና ለማስታወቂያ ሚንስቴር ለመስጠት ያዘጋጀውን አሳየኝ ይህን ነገር ስመለከት አለቀስኩ ወዲያውም አማራ የሚሰበስበው አጥቶ ነፍጠኛ በመባል በያለበት በመታጨድ ላይ መሆኑን ለስብሰባችን ሪፖርት አደረኩ አማራ በነፍጠኝነቱ አገርና ወሰን እንዳላስከበረ ሁሉ በአሁኑ ጊዜ እንደ አገሪቱ ጠላት ታይቶ በደል ሲሠራበት እንዴት ዝም ብለን እናያለን በሚል ውይይት አደረግን አቶ አበበ ወንደሜነህ የተባሉ የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት መዐሕድን መሥራችና ምሊቀመንበር ለአብሲኒያ መጽሔት ቅጽ ገ ቁጥር ገ ጥር ዓም ዕትም ከተናገሩት የተወሰደ የእነ አቶ አበበ ወንድሜነህ ቡድን አዲስ አበባ ላይ ምን መደረግ አለበት በሚለው ላይ በሚመክርበት ወቅት ሌላው በናዝሬትና በአርሲ አካባቢ ይኖሩ በነበሩ የአማራ ተወላጆች የሚመራ ቡድን ደግሞ በአካባቢው ይኖሩ በነበሩ አማራዎች ላይ ይደርስ የነበረውን ግፍ ለማስቆም ምን መደረግ አለበት በሚለው ላይ የራሳቸውን አስተዋጽኦ በሚያደርጉበት ዙሪያ ይመክሩ ነበር የናዝሬቱ ቡድን በእነ ቀኛዝማች ነቅዐጥበብ በቀለ የሚመራ ሲሆን እነ ፊትአውራሪ ተዘራ ወልደ ጊዮርጊስ አቶ ጸጋየ ገብረ ሚካኤል አቶ ክንፈ ክብረት አቶ ታየ ተሰማ የመሳሰሉትን ያቀፈ ነበር አዲስ አበባ ላይ የነበረውን የእነ አቶ አበበ ወንድሜነህን ቡድን እና የናዝሬቱን የእነ ቀኛዝማች ነቅዐጥበብ በቀለን ቡድን አቶ ግርማ ማንአግደው በተባሉ የሕግ ባለሙያ አማካይኝነት ነበር የተገናኙት አቶ ግርማ ማንአግደው ከሁለቱም ቡድን ጋር የመተዋወቅ አጋጣሚ ስለነበራቸው በቀላሉ እንዲገናኙ አደረጓቸው አቶ ግርማ ማንአግደው የናዝሬቱን የእነ ቀኛዝማች ነቅዐጥበብ በቀለን ቡድን ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ ካደረጉ በኋላ በተለምዶ ሰሜን ማዘጋጃ የሚባለው አካባቢ ይኖሩ ከነበሩት ወይዘሮ አልማዝ ኃይለማርያም ቤት ወሰዷቸው በጊዜው የወይዘሮ አልማዝ ኃይለማርያምን መኖሪያ ቤት እንደመሰባሰቢያ ይጠቀሙ የነበሩት የእነ አቶ አበበ ወንደሜነህ ቡድን በዚያው ነበሩና ከነ ቀኛዝማች ቡድን ጋር ተገናኙ ወይዘሮ አልማዝ ኃይለማርያም ለመዐሕድ መመስረት እና ለአማራ ሕዝብ ትግል ከፍተኛውን አስተዋጽኦ ያደረጉና ዘላለማዊ ክብር የሚገባቸው እናት ናቸው አቶ ገብረጻድቅ ኃይለማርያም የተባሉ የመዐሕድ መስራች እንደነገሩኝ ከሆነ ረርየመዐሕድ የመመስረት ጽንሰ ሐሳብ በወይዘሮ አልማዝ የተወጠነ እንደሆነ ነው እኝህ እናት ለአማራ ሕዝብ ትግል በበረሃ የተገኙ ምንጭ ልንላቸው እንችላለን ቤታቸውን ለመሰብሰቢያነት ከመፍቀዳቸውም በላይ የመዐሕድ መሥራቾች ስብሰባ በሚያደርጉበት ጊዜ በራቸው ላይ ቁጭ ብለው ወደ ውስጥ የሚገባውንና ወደ ውጭ የሚወጣውን በመመልከት የስለላና የደህንነት ሥራም ይሰሩ ነበር እኝህ ሴትዮ አንደበት ላጣው የአማራ ሕዝብ አንደበት ይሆኑ ዘንድ ሁለመናቸውን የሰጡ የዘመኑ ጣይቱ ብጡል ነበሩ ቢባል አይበዛባቸውም የአማራ ሕዝብ ትግል ሲነሳ የፊትአውራሪነቱን ቦታ የሚይዙት ደልዳላዋ ወይዘሮ በግፉዓን የአማራ ሕዝብ ልጆች ልብም መልካም ሥራቸው ታትሞ ለዘላለም የሚኖሩ ኩሩ ሴት ናቸው ወይዘሮ አልማዝ ወገኖቻቸው ጥረው ግረው ካፈሩት ንብረት ጋር በቤታቸው በእሳት ሲነዱ አይተዋል ሰምተዋል ታዲያ ወገናቸው እንዲህ እየተገፋ የማን ዘር ጎመንዘር ወይዘሮ አልማዝም ለወገኖቻቸው ለመድረስ ቤታቸውን ብቻ ሳይሆን ሁሉ ነገራቸውን ለአማራ ሕዝብ ትግል እንካችሁ ብለው አሳልፈው ሰጡ መልካም ሥራቸውና ለወገኖቻቸው ያደረጉት አስተዋጽኦ ዘላለማዊ ክብር አጎናጽፏቸዋል የአማራ ሕዝብ ታሪክ ሲነገርም ከፊት ለፊት አብሪ ኮከብ ሆነው ለዘላለም ይኖራሉ። እያሉ ይጠይቁ ጀመር ሰዎች እየመሯቸው እስቲ እነሱ ጋ ሞክሩ እየተባሉ ወደ እኛ መምጣት ጀመሩ እኛ አዲስ አበባ ተቀምጠን ምንም ሳናውቅ ከየጠቅላይ ግዛቱ እኛጋ ይረባረቡ ጀመር ከፍተኛ ችግር ውስጥ ገባን ለመንግሥት አቤት ለማለት ምላሽ ለመስጠት ፈቃድ ላይሰንስን አስፈለገን ኢትዮጵያዊ ድርጅት ስም ይዘን በዚያን ሰዓት የአማራውን አቤቱታ ብናቀርብ እናንተ ለምንድን ነው የአማራውን ብቻ ነጥላችሁ የምታቀርቡት የሚል ጥያቄ ሊመጣ ሆነ ስለዚህ በአማራው ላይ ብቻ የተቃጣውን ጭፍጨፋ ለማስቆም የእሳት አደጋ ሥራ ለመሥራት ብለን ድርጅት ልናቋቁም በቅተናል ሲሉ መልስ ሰጥተው ነበር በዚህ ሁኔታ መሥራት የጀመረው መዐሕድ በአጭር ጊዜ ውስጥ በከፍተኛ ፍጥነት ተቀባይነት እያገኘ መጣ ምንም እንኳን መዐሕድ በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት ቢያገኝም አባላቱና አመራሮቹ ግን እንደፈለጉ መንቀሳቀስ አልቻሉም ነበር በወቅቱ የነበረው የሽግግር መንግሥት ከሚያደርሰው ባልተናነሰ መልኩ የሽግግር መንግሥቱን ጥሎ በሕወሓት ሴራ ተበልጦና በካልቾ ተጠልዞን የወጣው ኦነግም በመዐሕድ ላይ የሚችለውን ያክል ክንዱን ለማሳረፍ ጥረት አድርጎ ነበር ከዚህ በተጨማሪ ግን ሌላው የመዐሕድ ፈተና አማራ ለምን በዘር ይደራጃል የሚሉ የአማራ ተወላጆችም ሰፊ ፕሮፖጋንዳና ዘመቻ ያደርጉበት ነበር የወገናቸው መጨፍጨፍ ያስቆጫቸው ሰዎች ግን በመዐሕድ ዙሪያ እየተሰባሰቡ በየአካባያቸው የሚገኘው የአማራ ተወላጅ ወደ ድርጅቱ እንዲታቀፍ ተደርጎ አዲስ አበባ ውስጥ ባሉ አሥራ ሶስት አውራጃዎች አባላት የማሰባሰቡ እንቅስቃሴ በስፋት መካሄድ ተቻለ የድርጅቱ እንቅስቃሴ እንደ ሰደድ እሳት ከአዲስ አበባም ውጭ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች ተዳረሰ በተለይ በአማራው ላይ ከፍተኛ ጭፍጨፋ ይደርስ ወደነበረበት ወደ ተለያዩ የሐገራችን ክፍሎች ማለትም ወደ ናዝሬት አርሲ ባሌና ሀረር ደቡብ ሸዋ ፊቱን አዙሮ የማደራጀት ሥራውን ቀጠለ ለዚህ የማደራጀት ሥራ ይጠቅም ዘንድ በማሰብም ሁለተኛ መሥራች ጉባኤውን በናዝሬት ከተማ በማድረግ በአብዛኛው የችግሩ ሰለባ በነበረው ሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ድጋፍና መነቃቃት መፍጠር ቻለ በአዲስ አበባም የተለያዩ አውራጃዎች መሥራች ጉባኤውን ማድረግ ቻለ ከአዲስ አበባ ውጭም በደብረ ብርሃን በሸዋ ሮቢት በቅምብቢት በጅሁር በእንሳሮ በእነዋሬ በባሕርዳር በድሬዳዋና በሌሎችም አካባቢዎች መሥራች ጉባኤ ማድረግ ተቻለ በዚህ ፈጣን የሆነ ወገንን ከጥቃት የማዳን እንቅስቃሴ በፕሮፌሰር አሥራት የሚመራው መዐሕድ ከአርባ በላይ ጽቤቶችን በመክፈት በአማራው ላይ የሚደርሰውን ግፍና መከራ ለሽግግር መንግስቱና ለመላው ዓለም በማጋለጥ ሰቆቃውን ፈጽሞ ማጥፋት ባይቻል እንኳን መጠኑን መቀነስ ተችሎ ነበር የሐገር ቤቱ እንቅስቀሴ እንዳለ ሆኖ ከሐገር ውጭ ያሉ የአማራ ተወላጆችን ማደራጀት አስፈላጊ በመሆኑና ለትግሉ ያለው አጋዥነት በመታመኑ ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ በሰኔ ወር ዓም ወደ አውሮፓና አሜሪካ ጉዞ እንዲያደርጉ ግድ አላቸው በዚሁ የውጭ ጉዞ በአውሮፓ ስዊድንና አሜሪካ የሚኖሩ የአማራ ተወላጆችን በማደራጀት መዐሕድ በገንዘብ እንዲጠናከር ከማድረጉም በላይ በዕውቀትና በዲፕሎማሲ ዘርፍ ዓለም አቀፋዊ እውቅና እንዲጎናጸፍ አድርጎታል የውጭ ድጋፍ ሰጭ ቻርተሮችን በማቋቋም በሐገር ቤት ለሚደረገው ትግል ከፍተኛ እገዛ እንዲያደርግ ተደርጓል ምንም እንኳን በሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች ካናዳን ጨምሮ ያሉ ኢትዮጵያውያን ፕሮፌሰር አሥራት ንግግር እንዲያደርጉላቸው በከፍተኛ ጉጉትና ስሜት ጥሪ አቅርበው ቢጠባበቁም ቀደም ብሎ ባለመያዙ በፕሮግራም መጣበብ ምክንያት በኒዮርክ በዋሽንግተንና በሎሳንጀለስ ብቻ ንግግር በማድረግ ከፍተኛ የሕዝብ አቀባበል አትርፈው ነበር የተመለሱት በሌላ በኩል እንደ ሐገር ቤቱ ሁሉ ውጭ ሐገርም አማራ በዘር አይደራጅም የሚሉ ሰዎች አልጠፉም ነበር የእነዚህ ሰዎች መከራከሪያ አማራው ወያኔ በቀደደለት ቦይ አይፈስም» የሚል መከራከሪያ ነበር ፕሮፌሰር አሥራት ግን ረቤት እየተቃጠለ እያየህ የእሳት አደጋ ሰራተኛ እስኪመጣ ብለህ ቆመህ አታይም በማለት ይመልሳሉ ይህን ጉዳይ በደንብ ሊገልጸው የሚችለው የመዐሕድ ኛ ዓመት ምስረታ በዓል ሲከበር ፕሮፌሰር አሥራት አድርገውት የነበረው ንግግር ነው። መዐሕድ የሟያምነው ቫብሰም በደምክራሲና በጳድነት ተቻችሎ ሰመኖርረ ነውኖ ጸሲሷኒያ መድሔት ጥር ም ዕትም በእርግጥ መዐሕድ ላይ የተከፈተበት የስም ማጥፋትና የማሳደድ ዘመቻ የሶስትዮሽ ጥምር ጥቃት ነበር ኦነግና ኦህዴድ በኦሮሚያ ክልልና አቅራቢያው ሲቀሰቅሱበት በመለስ ዜናዊ ትዕዛዝ ከህብረ ብሔራዊ ድርጅትነት ወደ አንድ ክልል ባለሟልነት በደቂቃ የታጠፈው ኢህዴን ብአዴንን በአማራ ክልል የሕወሓትን ተልኮ ሲያስፈጽም ብአዴንን አንዳንድ ሰዎች አማርኛ ተናጋሪ ሕወሓት ይሉታልን በሌላ በኩል ኢሕአዴግ እንደ ድርጅት በተለያዩ አቅጣጫዎች የፕሮፖጋንዳ ዶፍ ያወርድበት ጀመር መዐሕድ ግን ይህን የሶስትዮሽ ጥምር ጥቃት እየተከላከለና ህዝቡን ስለ ሁኔታው እያሳወቀ በሌላ በኩል ለመንግሥት አቤቱታውን እያሰማ በኃይል ሊያጠፋው ያሰፈሰፈውን ሕወሓትኢሕአዴግ ሲታገል ቆይቷል ጦሰኛው የደብረብርሃን ንግግር የሰሜን ሸዋና ደብረ ብርሃን ሕዝብ ለመዐሕድ ባደረገው ጥሪ መሠረት ከአካባቢው አስተዳደር ፈቃድ ተጠይቆ ይሁንታ በማግኘቱ ታህሳህ ቀን ዓም በደብረ ብርሃን ከተማ ዘርያዕቆብ አደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ተዘጋጀ በወቅቱ የድርጅቱ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር አሥራትን ጨምሮ ብዙ የመዐሕድ አመራሮች በቦታው ተገኙ መዐሕድን ከምድረ ገጽ ለማጥፋት የሚኳትነው ኢሕአዴግ የደብረ ብርሃኑን ህዝባዊ ስብሰባ አንዳች ሰበብ ፈልጎ ከማሰናከል እስከ መወንጀል ድረስ የዘለቀ አሜካላውን ሁሉ አደረገ በወቅቱ የስብሰባ ቀን ሲደርስ የኢሕአዴግ ካሬዎች ሰብሰባውን ለማወክ ይረዳናል ያሉትን ወረቀት በትነው አደሩ መዐሕድ ትምክህተኛ ነው የነፍጠኞችና የደርግ አሰባሳቢ ነው የባለዘውዶች ቅጥረኛ ፓርቲ ነው ይላል በእለቱ የተበተነው ወረቀት በሌላ በኩል በዚያው ስብሰባ አካባቢ የወቅቱ ጠቅላይ ሚንስትርና የመከላከያ ሚንስትሩ በቦታው በድብቅ ተገኝተው ፕሮፌሰሩን በሄሊኮፕተር አስረው እንዲያመጧቸው ትዕዛዝ ተላልፎ ነበር ነገር ግን ሁኔታውን በማጤንና የህዝቡን ቁጣ በመፍራት ሳያስሯቸው ተመልሰዋል ምንም እንኳን ኢሕአዴግ መዐሕድን ለማጥመድ አሽከላውን ቢዘረጋም የድርጅቱ አመራሮች ግን ያቀዱትን ህዝባዊ ስብሰባ ለማድረግ አላመነቱም በዕለቱ ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ በዘርያዕቆብ አደባባይ ለተሰበሰበው ብዙ ሺህ ሕዝብ ዘመን ተሻጋሪ ንግግር አድርገው ነበር ይህ ንግግራቸው ነው ፕሮፌሰሩን ጦር ቀስቃሽ የሚል ውንጀላ ያላበሳቸው የፕሮፌሰሩን ረጅም ንግግር ያነበቡና ያዳመጡ ሰዎች ግን ሁኔታው ቢገርማቸው እስካሁን ድረስ አማርኛ አንችልም ነበር ማለት ነው» እስከማለት ደርሰው ነበር የጦርነትን አስከፊነትና የሰላምን አስፈላጊነት የሚሰብከው የፕሮፌሰር አሥራት ረጅም ንግግር የሚከተለው ነው ከሁሉ በፊት በእናንተ ውድ ወገኖቸ መካከል በዚህ አደባባይ ላይ ተገኝቸ ስለ ሐገራችን ስለ ኢትዮጵያ ሕልውና እንዲሁም በየቦታው በግፍ በመጨፍጨፍ ላይ ስለሚገኘው ወገናችን ስለ አማራው ሕዝብ የወደፊት መኖር ወይም አለመኖር ጉዳይ ለመወያየት ላበቃኝ ሁሉን ማድረግ ለሚቻለው አንድ አምላክ ምስጋና አቀርባለሁ የሽግግር መንግሥት ከተቋቋመ ጀምሮ ብሔር ብሔረሰቦች እንዲደራጁ ሲደረግ ስለጋራ ጉዳያችን የምንወያይበት ይህን ስብሰባ እንድናዘጋጅ ስለተባበረን በመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት ስም ምስጋናየን አቀርባለሁ ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ የሰሜን ሸዋ አቀፍ ስብሰባ በዚህ በደብረ ብርሃን አደባባይ ለማድረግ የተቻለው በሕዝብ ጥያቄና ግፊት ሲሆን ይህም ስብሰባ መአህድን እንደፈረሰ አድርገው አሉቧልታ የሚነዙትን የአማራውን ቀንደኛ ጠላቶች እና የወኪሎቻቸውን ከንቱ ሙከራ እንደ በጋ ጉም እንዲበን የሚያደርግና ስለ ወደፊቱም ትግላችን የጋራ ግንዛቤ የምናገኝበት እንደሚሆን አምናለሁ ከዚህ በቀር ይህ በሕዝብ ሙሉ ቃል እና ፍላጎት ላይ የተቀናጀው ስብሰባችን የሰሜን ሸዋ መዐሕድ እንቅስቃሴን በመገምገምና ህዝቡ ከመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት ጋር ያለውን ግንኙነት በሚመለከት ያለውን የጠራ አቋም የምንዳስስበት ለወደፊትም እንቅስቃሴያችን የጋራ ዕውቀትና ትምሕርት እንድንተነብይበት ታስቦ የተዘጋጀ ነው ይህ የአለንበት ዘመን ሐገራችን ኢትዮጵያና የኢትዮጵያ ሕዝብ በከፍተኛ ችግር ላይ የወደቁበትና ፈታኝ ከሆነ የጥፋት ማዕበል የገቡበት ወቅት መሆኑ ይታወቃል በተለይ የኢትዮጵያ የታሪክ ጠላቶች ኢትዮጵያን ለማጥፋትና ለማዳከም ሲያውጠነጥኑ የኖሩበት ዕቅድና ሥልት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መሆን የጀመረበት ወቅት ስለሆነ በኢትዮጵያዊነታችን ለምናምን ሁሉ አሳሳቢ ብቻ ሳይሆን እጅግ ፈታኝ የሆነ ወቅት ላይ እንገኛለን ይህ ሐገራችንንና ህዝቦቻችንን ከጥፋት ውስጥ ያስገባ ችግርና ወጥመድ በኢትዮጵያኖች የተጠነሰሰና የተፈጠረ ሳይሆን በውጭ ጠላቶቻችን የረቀቀና ለተግባራዊነቱም ገንዘብ ዕውቀትና ቁሳቁስ ተመድቦለት በከፍተኛ ደረጃ ክትትል የሚደረግበት ከመሆኑም በላይ ዓለም በአንድ ኃይል መዳፍ እጅ የመግባቷን ሁኔታ ሲያበሥር የኢትዮጵያ ጉዳይ ደግሞ ከራሷ ሕዝብ በቀር ሌላ ዳኛና ተቆርቋሪ የሌላት መሆኑን መገንዘብ ይኖርብናል የኢትዮጵያ ጠላቶች ኢትዮጵያን ለማጥፋት ሲያቅዱና ሲዘምቱ ለረጅም ጊዜያት ሲያቅዱ የኖሩ ቢሆንም እንደ ዛሬው ኢትዮጵያን ባዶዋን ያገኙበት ጊዜ በታሪክ አልታየም ይህ የሐገራችን ባዶነት ሊከሰት የቻለውም ከረጅም ጊዜ የጠላቶቻችን የውስጥ ቡርቦራ ህዝቡ እንዲከፋፈል እና በራሱ ልጆች ላይ እምነት እንዲያጣ ሞራሉን ታሪኩንም ሀይማኖቱንም በአጠቃላይ ሁለንተናውን ሁሉ እንደ ምስጥ ውስጥ ውስጡን ሲበሉት የቆዩ በመሆናቸው ነው ከዚህ በቀር በአሁኑ ወቅት በአለም ላይ የተከሰተው የፖለቲካ ሁኔታ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ችግር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑ ይታያል ከዚህ የተነሳ ለዓለም ሕዝብ የጋራ ህልውና እና የታናናሽ አገሮችን ደህንነት በማጠበቅ ረገድ ከፍተኛ ሀላፊነት የሚጠበቅበት የተባበሩት መንግስታት ደርጅትም የዓለም ታላላቅ ኃይሎች ሚዛን ባልታሰበ ሁኔታ በድንገት ስለተዛባ በአንድ ኃይል አመራር ሥር ወድቆ ለዳግመኛ የታሪክ ትዝብት ተጋልጦ ይገኛል የራሱን ሚዛን በመለዋወጥ ላይ የሚገኘውን የዓለም ሁኔታ በብቸኛ ኃያልነት የሚመሩት ወገኖች በየትኛውም አካባቢ ያለውን ፍላጎታቸውን ለማርካትና ጥቅማቸውን ለማመቻቸት የሚችሉ ቡድኖች በሥልጣን ላይ እንዲቆናጠጡ ከማድረግ ባሻገር የሐገሩን ሕዝብ ጩኸት የሚሰሙበት ጆሮአቸውን ይሁነኝ ብለው ደፍነውታል ስለሆነም በማንኛውም ሐገር ወስጥ ምንም አይነት ችግርና በሕዝብ ላይ የሚፈጸም እልቂት ከእነሱ ሥልትና ጥቅም አንጻር የሚያሳስባቸው ሆኖ እስካላዩት ድረስ ሰሜት የሚሰጣቸውና የእልቂቱም ሰቆቃ የሚቀሰቅሳቸው አይደለም ይህ የውጭ ኃይሎች ሥልት ይህችን የምንኖርባትን ክፍለ ዓለም ማለትም የአፍሪካን ቀንድና እንዲሁም በአውሮፓና በዩጎዝላቪያ ምድር ሕዝብን እርስ በርስ በማፋጀት የሚፈጽሙበት ደባ በገሃድ እየታየ ነው ጥበባ አመለካከትና ቡድናዊ ስሜት ያላቸውን ኃይሎች በማስታጠቅና የእነሱ ደጋፊ ትክሻ በመሆን በሌላ በኩል ደግሞ የመሳሪያ ፋብሪካቸው ገበያ እንዲያገኝ የጦር መሳሪያዎች በገፍ በማቅረብ ህዝቡ እርስ በርሱ በማፋጀት ረገድ ወኪሎቻቸው የእነሱን አላማ ለማራመድ የሚችሉበትን በረቀቀ ጥናት የተደገፈ ተክህኖ ይሰጧቸዋል እርስ በርስ የማፋጀት ሥልታቸውም ትኩረት የሚያደርገው በረጋው ማኅበረሰብ ውስጥ ጎሳን ቋንቋንና ሀይማኖትን ለህዝቡ አጉልቶ በማሳየትና በዚህ አንጻር በመከፋፈል ነው በኢትዮጵያ ላይ የውጭ ኃይል ትኩረት ማድረግ ከጀመረ ብዙ ምዕተ ዓመታት ያለፈ ቢሆንም በይበልጥ ሥልታዊ እቅዱን ይፋ ያደረገው በዳግማዊ ምኒልክ መሪነት ኢትዮጵያ በአድዋ ላይ ካስመዘገበችው ድል በኋላ ነበር በነጮች ዕውቀት የተገነባውን ያንን የወቅቱን ሃያል ሐገር ጦር በአፍሪካ ምድር የሚቋቋመው ኃይል የለም በሚባልበት በዚያ ጨለማ ዘመን ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው የጦር ሜዳ ድል ወደ አፍሪካ ያነጣጠረውን የውጭ ኃይል እንደገና እንዲያሰላሥልና እንዲያስብ ስላደረገው ሕዝብን ማሸነፍና መያዝ የሚቻለው በጦርነት ብቻ ሳይሆን እራሱን በራሱ እንዲጎዳና እዲከፋፈል በማድረግ ህዝቡን ኃይል በቀላሉ ሊፈራርስ የሚችልበትን ሥልት በመቀየስ ጭምር መሆኑን እንዲያምኑበት አድርጓቸዋል ስለሆነም ኢጣሊያ በአድዋ ላይ የደረሰባትን አሳፋሪ ሽንፈት መነሻ በማድረግ ዐ ዓመት ሙሉ ሲጠናበት እና ሲታቀድበት ቆይቶ ከሞላ ጎደል ከሰሜኑ ኢትዮጵያ በተወሰደው የኢትዮጵያ አካል የሆነውን የኤርትራን መሬት መቆናጠጫ በማድረግ የኢትዮጵያን ሕዝብ እርስ በርሱ የማባላት ተግባር በግንባር ቀደምትነት ተጀምሮ ነበር ኢጣሊያ ይህን ዓላማዋን ለማራመድ እንዲያስችላት የኢትዮጵያ አካል በሆነው የኤርትራ መሬት ላይ ከተቆናጠጠች በኋላ ወደ ደጋማው የኢትዮጵያ መሬት ከመንቀሳቀሷ በፊት ከምዕራባውያን ኃያላን መንግስታት ጋር ምስጢራዊ ስምምነት ማድረጓንም ከታሪክ እንማራለን በወቅቱ በነበረው የኃያላን መንግስታት አሰላለፍ ስትራቴጂ መሠረት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን መያዚ በእነርሱ መካከል የቅርጫ ድርሻዋ መሆኑን በማሳመን ጭምር ሲሆን ቀደም ብሎ በይዞታ ሥር ከነበረው የኢጣሊያ ሶማሊያ ይልቅ የኤርትራን ምድር የተደላደለ የጦር ሰፈር በማድረግ የወረራ እንቅስቃሴዋን ባፋፋመች ጊዜ ህዝቡን ለማሰልጠንና ሐገሩን ለማልማት የተደረገ በጎ እንቅስቀሴ እንደሆነ ተደርጎ እንዲታይ በሐገር ውስጥም ሆነ በውጭው ሐገር ፕሮፖጋንዳ ለመንዛት ተሞክሯል ይህ ፕሮፖጋንዳ ዛሬም ቢሆን መልኩንና ቅርጹን ለውጦ ኢትዮጵያ ኤርትራን በቅኝ ገዥነት እንደያዘችና ኢጣሊያን ደግሞ አገር አልሚ እንደነበረች ተደርጎ እየተነገረ ነው ኢጣሊያኖች በዚህ ሁኔታ የኢትዮጵያ አካል በሆነው በባሕር ምድር ማለትም የዛሬው ኤርትራ መሬት ላይ ከተቆናጠጠች በኋላ የክፍለ ሐገሩን ሕዝብ በከፍተኛ ቁጥር በመመልመልና በጦር ግንባር በማሰለፍ በዓለም በተከለከተ የመርዝ ጢስና በከባድ መሳሪያ በመታገዝ በቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ወረራ በማካሄድ ዓመት የቆየውን ጭፍጨፋ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ለማካሄድ በቅታለች የኢጣሊያ ወረራ ዋና ዓላማ የነበረውም ቁጥሩ የበረከተውን የሐገሯን ሥራ አጥ ሕዝብ በሰፊው የኢትዮጵያ ለም መሬት ላይ በማስፈር የሐገራችንን ጥሬ ሀብት ለመበዝበዝ እና የኢትዮጵያን ህልውና በረቀቀ ሁኔታ በማጥፋት ቅኝ ገዥነቷን ለማረጋገጥ እንደነበር ይታወሳል የኢጣሊያን ወረራ በኢትዮጵያ ሥር እንዲሰድና የኢትዮጵያን ህልውና እንዳልነበር አድርጎ ቅኝ ገዥነቷን እንዲያረጋግጥ ለማድረግ የታመነበት በኢጣሊያ ዕቅድ መሠረት የሚከተሉት ከኢትዮጵያ ምድር ሲጠፉ ነው ብለው ሲሆን እነሱም ኛ ዘውድ ኛ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ኛ የአማራው ሕዝብ ነበሩ አንደኛ ዘውድ የኢትዮጵያን ሕዝብ በአንድነቱ የሚያስተሳሥር ምልክት ነው በመባሉ አጹ ኃይለሥላሴ በስደት እንግሊዝ ሐገር በስደት ላይ በነበሩበት እንኳን ሳይቀር ሞሶሎኒና የሮማ ካቶሊክ ጳጳስ ከፍተኛ ገንዘብ በማበርከት ንጉሰ ነገስትነታቸውን እዲሰርዙና በዚህም ድርጊታቸው ብዙ ገንዘብ አግኝተው ከችግራቸው ተላቀው በተድላና በድሎት እንዲኖሩ ተማልደዋቸው እንደነበር ይታወሳል አጹ ኃይለሥላሴ ለዚህ ባለመበገራቸውና የኢትዮጵያን ክብር አዋርደው እጃቸውን ባለመስጠታቸው የኢትዮጵያ መንግሥት ህልውና ህጋዊ መሰረቱ ፀንቶ በዓለም ሕዝብ ዘንድ እንደታወቀ በመቆየቱ ኢትዮጵያ በኢጣሊያ ተወረረች እንጅ የቅኝ ተገዥ እንዳልሆነችና እዳልተንበረከከች ተረጋግጦ የአርበኞችም ትግል በኢትዮጵያ መንግሥት እየተመራ ለድል እንዲበቃ ተደርጓል ሁለተኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሃይማኖትም በውጭ ኃይል ስለማትታዘዝና ስለማትገዛ በጥንታዊነቷ በፍልስፍናዋ በትምህርቷ በዓለም የሚወዳደሯት በጣም ጥቂቶች ስለነበሩ በአቋሟና በዕምነት ጽናቷ ታስቀናና ትፈራ ስለነበር ነው እንዲሁም ለሐገራችን የትምሕርትና የሥነጽሁፍ የባሕልና የአስተዳደር መሠረት ስለነበረችና ከሁሉም በላይ ደግሞ ለኢትዮጵያ ህልውና ስለ ነፃነትና ስለ ሰው ልጅ ክብር የምታስተምር በግንባር ቀደምትነት የምትቀሰቅስና የምትመራ ስለሆነች ነው የዛሬውን አያደርገውና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሀይማኖት አባቶች ለሐገራቸው ለሀይማኖታቸውና ለህዝባቸው ነፃነት ክብር በግንባር ቀደምትነት ተሰልፈው በዓርያነት ህዝቡን የሚመሩ እንደ እነ አቡነ ጴጥሮስና እነ አቡነ አብርሃም የመሳሰሉት የሃይማኖት አባቶችም በኢጣሊያ መትረየስ ፊት ቆመው ህዝቡ ለነፃነት እዲነሳሳና እዲዋጋ አስተምረው በመስዋዕትነት ያለፉ መሆኑን በመረዳቱ ነበር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እንድትጠፋ የተፈረደባት በሶስተኛ ደረጃ እንዲጠፋ የተወሰነበት የአማራው ሕዝብ እንደ ኢትዮጵያ ጠላቶች አባባል በራሱና በታሪኩ የሚተማመን አትንኩኝ ባይ ለነፃነቱና ለህልውናው ከምንም በላይ ለሃይማኖቱ እና ለሐገሩ ዳር ድንበር መከበር የሚሞት በመሆኑ ነበር ይህም ሕዝብ በታሪክ ውስጥ በገሃድ እንደሚታየው በማናቸውም ጊዜ ቢሆን ለውጭ ኃይልና ለውጭ ጠላት ለሐገሩ መዋረድና መደፈር መሳሪያ ሆኖ የማያውቅና የማይደለል ከመሆኑም በላይ በሐገሩና በሃይማኖቱ ጉደይ አማራው አክራሪ ነው በመባሉ ነው አማራን ማጥፋትም ለየት ያለና ራሱን የቻለ ሥልት የተቀየሰ ሲሆን አማራው በጣላቱ ፊት ተባብሮ እንደይቆም ለማድረግ በስም ከፋፍለው በተለይ የሸዋ አማራ ከምድረ ገጽ እንዲጠፋ ካልተደረገ በቀር የኢጣሊያ ወረራ ጊዜያዊ ድል ከመሆኑ ባሻገር ሐገሪቱን በቅኝ ግዛትነት ለመያዝ አንችልም የሚል መደምደሚያ ላይ ደርሰው በዚህ ዕቅድ ለመግፋት እንደወሰኑ በታሪክ የተረጋገጠ ነው በዚህ መሠረት ሞሶሎኒ በቀጥታ ለጦር አዛዞቹና ኢትዮጵያ ላሉት ሐገረ ገዥዎቹ ያሥተላለፈው የቴሌግራም ትዕዛዘዝ አማራን ከሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦች ጨርሶ ለማጥፋት የሚያስችል እርምጃ እንዲወስድ የሚያዝ ስለነበር በዚህ ትዕዛዝ መሠረት እልቂቱና ጭፍጨፋው በአማራው እና በካህናቱ ላይ በገሃድና ያለማቋጥም እንዲፈጸም መደረጉን የቅርብ ጊዜ ታሪካችን ይመሰክራል በኢጣሊያን ሥልት የአማራን ሕዝብ የማጥፋቱን ዘመቻ የተጀመረ ሲሆን በሌሎች የኢትዮጵያ ግዛቶችም ትኩረት ተሰጥቶት አማራን የማጥፋቱ ዘመቻ በሌሎች ኢትዮጵያውያን ጎሳዎች እንዲደገፍና እንዲያውም አማራን የማጥፋቱ ተግባር እንዲፈጸም ከቅስቀሳ ጀምሮ እስከ መሳሪያ ድጋፍ ድረስ ተሰጥቷል በዚህ ሁኔታ በአንድ ፊት አማራንና የኦርቶዶክስ ሃይማኖትን የማጥፋቱ ዘመቻ ሲከናዎን በሌላ ወገን ደግሞ የዕሥልምና ሃይማኖትን የማጥፋቱ ተግባር ቀጥሎ ነበር በኢትዮጵያ ምድር እሥልምናን የማስፋፋቱ ተግባር በኢጣሊያ የተደገፈው ለኢትዮጵያ እስላሞች በማሰብ ሳይሆን በወቅቱ የኢጣሊያ መንግሥት ከሊቢያ ቅኝ ግዛቷ እና ከአረቡም ዓለም ድጋፍ ለማግኘት ሲባል ብቻ ነበር በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ በዚህ ሁኔታ የተቀናጀ እልቂትና ጭፍጨፋ እየተካሄደ በሌላ በኩል ደግሞ ሐገራችንን በአምስት የጎሳ ቋንቋዎች ከፋፍሎ የማስተዳደሩ ሥራም ተጀምሮ ነበር ኢትዮጵያን በጎሳና በቋንቋ የመከፋፈሉም ሥልት የአጭር ጊዜ ጥቅሙ አማራን ከሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎች ለማስወገድ እንዲቻልና በአንድ ቦታ ተወስኖ እንዲኖር በማድረግ በኢትዮጵያ ምድር እንደ ሰደድ እሳት እየተቀጣጠለና እየጋመ የነበረውን የአርበኞች ትግል ለማዳከም ነበር የረጅም ጊዜ ጥቅሙ ደግሞ ኢትዮጵያ የሚለውን ቃል ከዓለም ካርታ ላይ ለማጥፋትና ኢትዮጵያ ውስጥ ከኢትዮጵያዊነት ስሜት ይልቅ የጎሳ ስሜትና መንፈስ ገንኖ ኢትዮጵያዊነትን ለዘላለም በማጥፋት በአፍሪካ ቀንድ ወሳኝ ስፍራ ያላትን ሐገራችንን የቅኝ ገዣዎች መፈንጫ ለማድረግ ህዝቧም ለጎሳና ለቋንቋ ስሜት ተገዥ ሆኖ የኢትዮጵያዊነት ክብሩንና ኩራቱን አጥቶ የአድዋን ድል እንዳያስብና ለዘላለማዊ ተገዥነቱ የተመቻቸ ለማድረግ ነው የኢትዮጳያ ሕዝብ ግን ለዚህ የጠላቶቻችን ተንኮል አልተንበረከከም በእርግጥም ከስንዴ መካከል እንክርዳድ እንደማይታጣ ሁሉ በኢጣሊያ ጦር ሥር ሆነው የጠላታችንን አላማ አንግበው በወንድማቸው ቀየ እያደፈጡ ለሐገራቸውና ለነፃነታቸው የቆሙትን የሚሰልሉ ታጥቀው በባንዳነት የተዋጉ ኢትዮጵያኖች ቢኖሩም ጀግና የኢትዮጵያ ሕዝብ የራሱን መሪ በየጎሳው እየመረጠ ለነፃነቱ ተዋግቷል በተለይም የአማራ ሕዝብ በአማራ አገር በባንዳነት መሰለፍን የሞት ሞት እንደሆነ ቆጥሮ እምቢ ለነፃነቴ እያለ ቤቱን እየዘጋ ልጆቹንና ሚስቱን እየተወ የሰባት ዓመት ልጅ ሳይቀር በአርበኝነት በጦር ግንባር ተሰልፎ ለአፍሪካ ምድር የነፃነት ዓርማ የሆነ ሙያ በመፈጸም የሐገሩን ክብር እስመስክሯል የኢትዮጵያዊያን መስዋዕትነት በእግዚአብሔር ፊት ዋጋ አግኝቶ የኢትዮጵያም ነፃነት ተመልሶ በቀዳማዊ ኃይለስላሴ ርዕሰ ብሔርነት የኢትዮጵያን መንግሥት ለማቋቋም በተጀመረበት ወቅት ኢትዮጵያን በሞግዚትት ለመግዛት እንግሊዝ ከነበራት የዕቅድ እንቅስቃሴ ጋር ለሶስት ዓመት ያህል ከፍተኛ ሰላማዊ ትግል ከተደገረ በኋላ የኢትዮጵያ መንግሥት በዘመናዊና በአስተማማኝ መልኩ የማቋቋሙ ተግባር ሊሰምር በቅቷል ከዚህ በኋላ ከኢጣሊያ ጭፍጨፋ ከተረፈው ጥቂት የተማረ የሰው ሀይልና በብድር የተጀመረው ሐገር ግንባታ ያተኮረው በአንድ በኩል የኢትዮጵያ አካል የሆነችውን ኤርትራን ከእናት ሐገሯ ከኢትዮጵያ ጋር ለማቀላቀልና ከአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ይዞታ እንዲኖራቸው ከሚጥሩ ኃያላን መንግስታት ጋር የሚደረግ ትግል ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የአትዮጵያን አስተዳደር እርምጃ ከዓለም የሥልጣኔ እርምጃ ጋር ለማያያዝ የሚያስችለውን ዘመናዊ አስተዳደር በመጀመር መሠረት የመጣል ትግል ማካሄድ ነበር በተለይ የኢጣሊያ ጦር ከኤርትራ ምድር ከወጣ በኋላ እንግሊዝ በኢጣሊያ ተተክቶ በዚያ ምድር ለመቆት ይፈጽም የነበረውን ምስጢራዊ ደባ በሥልት ከመታገል ጀምሮ ኤርትራ ወደ እናት ሐገሯ እንድትዋሃድ ለማድረግ በኤርትራ ጀግኖች የተደረገውም ትግል ቀላል መስዋዕትነት የተከፈለበት አልነበረም ይህ ሁሉ ትግል ከረጅም ጉዞ በኋላ ውጤት አግኝቶ ኢትዮጵያን በኢኮኖሚና በፖለቲካ መስክ ራሷን ችላ የአፍሪካ የነፃነት ዓርማ በመሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚደነቅ ተሰሚነት እድታገኝ ተደርጓል ይህ ሁሉ ሲሆን በሌላው አንጸር በሐገር ውስጥ ያልተፈቱ ችግሮች እንደነበሩና ከሁሉም ጎሳ ተውጣጥተው በኢትዮጵያ መንግሥት ውስጥ ሥልጣን የያዙ ግለሰቦች በሥልጠን ባልገው እንደነበርም የማይታበል ሐቅ ነው አጹ ኃይለሥላሴ ከእናት ሐገራቸው ተለይተው የኖሩትን ኤርትራዊያን በመንከባከብ ላይ ትኩረት ሰጥተው ሁሉን ነገር ወደዚያ ሆኖ በእናት ጥቅም እንዲረኩ ለማድረግ ሲሞከር ሌሎች ኢትዮጵያኖች ተረስተው እንደነበርም ግልጽ ነው። ለወገን ውድቀትና መጠቃት ለሐገር መዋረድና መበታተን ለዲሞክራሲና ለሰብዓዊ መብት መታፈን መሳሪያ የሚሆኑ ሆዳም አማሮች ካሉ አጥብቀን እንመክራቸዋለን በተለይም ወጣቱ ክፍል የአባቶቹን አላማ ያለ ጥርጥር እንደሚያነሳ ሙሉ እምነት አለኝ በሌላ በኩል ግን መዐሕድ ለአማራው ሕዝብ ህጋዊ መብት መጠበቅና ለኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላዊነት መከበር የሚያደርገውን ትግል በቆራጥነት መቀጠሉን ይገፋበታል የተቋቋመበት ዓላማው ስለሆነም በማንኛወም ቦታ የሚፈጸሙትን ኢዴሞክራሲያዊ እንቅስቃሴዎች መታገሉን በግንባር ቀደምነት ማስተባበሩን ይቀጥላል በመጨረሻም ላሳስባችሁ የምፈልገው ዛሬ ዓለም በስነ ጥበብ መጥቃ በመሄድ አገርን በማልማትና የሕዝብን ማህበራዊ ፍላጎት በማርካት ከፍተኛ እርምጃ የሚካሄድበት ጊዜ መሆኑን ነው በዚህም መሠረት ሐገራቸው ምድረ በዳ የሆኑ ሐገሮችም እንኳን በሰላም በመሥራታቸው ለህዝባቸው ብዙ ጥቅም እያስገኙ ናቸው ኢትዮጵያ ሐገራችን በምድር ላይ ያለች ገነት መሆኗን ሞሶሎኒ ሳይቀር ሲመሰክር ለወታደሮቹ ባደረገው ንግግር ይህችን የምድር ገነት ውረሱ ነው ያላቸው ስለዚህ ሁላችንም ህዝቡም ሹማምንትም በሰላምና በእኩልነት ተፈቃቅሮ መሥራቱ ጥቅሙ የሁላችንም መሆኑን ተገንዝበን በመካከላችን ያለውን ልዩነት ከማስፋፋት ይልቅ በመካከላችን ሊጎለብት የሚችለውን ስምምነታችንን እንዲጠናከር በማድረግ አርቀን እንድንመለከት ጥሪ አቀርባለሁ ኢትዮጵያ በልጆቿ መስዋዕትነት አንድነቷና ነፃነቷ ተከብሮ ለዘላለም ይኖራል አሥራት ወልደየስ የመዐሕድ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር አሥራት ይህን ረጅምና ታሪካዊ ንግግር አድርገው ከተመለሱ በኋላ ኢሕአዴግ ከፍተኛ የሆነ ፍርሃት ውስጥ ተዘፍቆ ስለነበር በፕሮፌሰሩ እና በሚመሩት ድርጅት መዐሕድ ላይ ከፍተኛ የሆነ የስም ማጥፋት ዘመቻ ከፈተባቸው በወቅቱ ኢሕአዴግ ይቆጣጠራቸው የነበሩት የመንግሥት ሚዲያዎች በፕሮፌሰር አሥራት ላይ «ረየጦርነት ቅስቀሳ አድርገዋል በሚል ከፍተኛ የስም ማጉደፍ ሥራ ላይ ተሰማሩ የፕሮፖጋንዳው መሽነሪ የነበሩት የኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቪዥንን ጨምሮ እንደ አዲስ ዘመን ኢትዮጵያን ሔራልድ እፎይታ ማለዳ አብዮታዊ ዴሚክራሲና በመሳሰሉት የመንግሥት አፈ ቀላጤዎች በፕሮፌሰር አሥራት ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻቸውን የሚችሉትን ያክል አጧጧፉት በሽግግር መንግስቱ እውቅና ሥር በህጋዊ መልኩ የተደራጀውን መዐሕድም «ረጦረኛና ነፍጠኛ የሚል የዳቦ ስም ተለጠፈለት የሕጋዊው ፓርቲ መዐሕድ መሪው ፕሮፌሰር አሥራት ደግሞ እንደ ጦር መሪ ተቆጥረው የተለያዩ የተቃውሞ ሰልፎች በመንግሥት በኩል ተቀነባበረባቸው የኢሕአዴግ አሳፋሪውና የሚገርመው ድርጊቱ ደግሞ ፕሮፌሰር አሥራትን ፈጽሞ በማያውቋቸው አካባቢዎች ሳይቀር ጦረኛ ናቸው የሚል ህዝባዊ ውግዘት ማካሄዱ ነበር በሐገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ለምሳሌ ያህል እንደ አድዋ ሽሬ አክሱም በመሳሰሉ ከተሞች ፕሮፌሰሩን የሚያወግዝ ሰልፍ ተደረገ እርሳቸው ግን ስለ ደብረ ብርሃኑ ስብሰባ አጠቃላይ ሁኔታ እንዲህ በማለት ተናገሩ ረበደብረ ብርሃን ያለው ሕዝብ ጥሪ አደረገልን በሕግ የተፈቀልኝ የድርጅት መሪ ነኝ ድርጅቱ በህጋዊ መንገድ ፈቃድ ጠየቀና ተሰጠው ደብረ ብርሃን ንግግር ሳደርግ በአደባባይ በሙሉ ከህዝቡ ጋር ፖሊሱ መረጃው የመንግሥት አካል ሁሉ ግጥም ብሏል እኛ ከአዲስ አበባ ጠዋት ተነስተን ሰዓት ላይ ደብረ ብርሃን ደረስን ከተወሰኑ የእኛ ቅርንጫፍ ሰዎች በስተቀር ከአንድም ሰው ጋር ሰላምታ እንኳን አልተለዋወጥኩም ለአንድ ሰዓት ንግግር አደረኩ በሌላ ሰው ሊቀመንበርነት ውይይት ተካሄደ ጥያቄዎች እየቀረቡ እኔም ሌሎችም መልስ ስንሰጥ አንድ ሰዓት ተኩል ቆየንና ሰባት ሰዓት ወጣን አንድ ሆቴል ቤት ምሳ ተሰናድቶልን ስለነበር በላንና መኪና ውስጥ ገብተን ወዲያውኑ ወደ አዲስ አበባ ተመለስን ንግግሩ ጦርነት የሚቀሰቅስ የሚያነሳሳ ነው ወይ። አክለውም በአብዛኛው በክልል ሶስት በክልል አራት ወዘተ የተሰጡት ውግዘቶች የሚያስከስሱ ነበሩ እኛ እንኳን ከሰን ውጤት ልናገኝበት ይቅርና በዚያ ጊዜ ነፃ ፍርድ ቤትን የሚባል አልተቋቋመም አሁንም ቢሆን እኛ የከሰስናቸው ብዙ ነገሮች ልናከናውን እንኳን ስላልቻልን ብቻ ለታሪክና ለጊዜ ትተነው ነው እኛ የተወገዝነው በእውነት ይህን ያክል ጥፋት ኖሮን አይደለም በማለት በኢሕአዴግ ምን ያክል ተስፋ እንዳጡ አስረድተዋል ይህ ፕሮፌሰር አሥራትንና ድርጅታቸውን የማውገዙ ሂደት ቀጥሎ መዐሕድንም ሆነ ፕሮፌሰሩን የማያውቋቸው ሁሉ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተው እንዲያወግዚቸው ተደረገ በተለያየ የኢትዮጵያ ክፍለ ሐገሮች ከፍተኛ የሆነ የአንድ ወር የስም ማጉደፍ ዘመቻ ተደረገባቸው ከዚህም አልፎ በአካላቸውና በሞራላቸው ላይ ችግር ለመፍጠር ሲባል ከፍተኛ የሆነ የደህንነት ክትትል እንዲደረግባቸው ሆነ ከመንግሥት ምርመራ ባለሥልጣናት ከመዐሕድ እንዲወጡ ማስጠንቀቂያ ይደርሳቸው ነበር ለሕይወትህ አስብ የሚል ዛቻና ማስፈራሪያ በተደጋጋሚ ይነገራቸውም ነበር ከዚህም ውጭ አካላዊ ማፈራራት ማጨናነቅና ማዋከብ በመንገድ ላይ ሲጓዙ የፀጥታ ሰዎች ከፊትና ከኋላ እየተከታተሉ በማዋከብ ለአንድ ትልቅ ምሑር ብሎም ሰብዓዊ ፍጡር የማይገባ ዘለፋና ወከባ ይፈጸምባቸውም ነበር ዶክተር አሰፋ ነጋሽ የኢትዮጵያ ሕዝብ በወቅቱ የሚደረገውን ነገር ሁሉ በመከታተል የሚከተለውን ስንኝ ቋጥሮ ነበር ይላሉ ዶክተር አሰፋ ኛው የፕሮፌሰር አሥራት ሙት ዓመት መታሰቢያ ሲከበር ፓልቶክ ሩም ውስጥ እንደተናገሩት ወዛደር አርሶ አደር ከተሜው ገጠሩ ሁሉም ተሰባስቦ ቢመታ ነጋሪት ምላሱን ነው እንጂ ልቡን ማን አየበት ግጥሙ ሕዝብ በመዐሕድና በፕሮፌሰር አሥራት ላይ የሚደረገውን ዘመቻ አስመልክቶ የገጠመው ነበር ፕሮፌሰር አሥራት በደብረ ብርሃን ለተሰበሰበው ሕዝብ ንግግር ሲያደርጉ የመዐሕድ ሥፍራና ምድር የኢትዮጵያ ሕዝብ ልብ ነው ያሉትን አባባል ማስታወስ ይቻላል ረበእኔ አስተያየት በኢትዮጵያ ውስጥና በተለይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተከሰተ የተማሪዎች ችግር ስለነበር ያንን ለመሸፈን ሕዝቡን ለማደናገርና ታዛቢን ለማሳሳት መዐሕድ ተፈልጎ ከዳር እስከ ዳር እንዲወገዝ ተደረገ ያሉትም ዋናው መዐሕድን ለውግዘት የዳረገው ጉዳይ ነበር በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ የተወሰደው እርምጃ ኢሕአዴግን በዓለም ሁሉ አጋልጦት ስለነበር እንደ አጀንዳ ማስለወጫ ሥልት መሆኑ ነው ፕሮፌሰሩ ላይ የመዝመቱ ምሥጢር የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተቃውሞ ረየሞተው አንድ ሰው ነው ያም ቢሆን አድማ መበተኛ መሳሪያ ከቀድሞው መንግሥት ባለመውረሳችን ነው እሱም ቢሆን የኢሰፓ አባል ነው ተስፋሁን ወርቁ የተባለ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ በተፈጠረው ግጭት በፀጥታ ኃይሎች ከተገደለ በኋላ የመንግሥት ባለ ሥልጣናት ከሰጡት መግለጫ የተወሰደ ነው የዛሬን አያድርገውና በደህናው ጊዜ ሐገርን ከጥፋት ሊታደጉ የሚችሉና በአንጻሩ ወደ ከፍታ ሊመሩ የሚችሉ ትልልቅ ሃሳቦች መፍለቂያ የነበሩት የከፍተኛ ትምሕርት ተቋማት ዩኒቨርሲቲዎችን ነበሩ ከእነዚህ የከፍተኛ ትምሕርት ተቋማት መካከል ደግሞ የአብዮቱ መጠንሰሻና መጎልመሻ የነበረውን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን የሚስተካከለው አልነበረም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የንጉሱን ዙፋን የነቀነቁት የቀድሞዎቹ ፋኖ ተማሪዎች ውቃቤ አልራቀውም ነበርና በኤርትራ መገንጠል ዘመንም አጠቃላይ አሰራሩን በድፍረት ካወገዙና ከታገሉ ተቋማት መካከል ተስተካካይ አልነበረውም ማለት ይቻላል የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምንም እንኳን ሰሚ ባያገኙም በወቅቱ የሚከተለውን ከበድ ያለ መልእክት ያዘለ በራሪ ወረቀት አሰራጭተው ነበር ረፈ ሕዝብ ያልመረጠውና ያልወከለው መንግሥት ለራሱና ለተባባሪዎቹ ጥቅም ሲል በነደፈው ቻርተር መሠረት እነሆ የሐገራችን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ሊያፈርስ የቀሩት ትንሽ ጊዜያት ናቸው ይህን የወያኔሻዕቢያ የተቀነባበረ ሴራ ከግብ ለማድረስ በአሜሪካ አስተባባሪነት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኤርትራን ሪፈረንደም አስመልክቶ ውሳኔ ለማሳለፍ ሽርጉድ ይላል የአፍሪካ ቀንድ መጽሔት የካቲት ዓም ምንም እንኳን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ኤርትራን መገንጠል አስመልክቶ የበተኑት በራሪ ወረቀት ይህን ቢልም የተባበሩት መንግስታት መሪ የነበሩት ግብጻዊው ቡትሮስ ቡትሮስ ጋሊም ሆኑ ሌላው ዓለም ለተማሪዎቹ ጩኸት ጆሯቸውን የዝሆን ጆሮ አድርገው ተኝተው ነበር ይህ ድርጊት ያበሳጫቸው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የዋና ፀኃፊውን ወደ አዲስ አበባ መምጣት አስመልክተው ያዘጋጁት የተቃውሞ ሰልፍ በደም መፋሰስ ከመቋጨት አልዳነም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ ግን በወቅቱ ከእነሱ ይጠበቅ የነበረውን የዜግነት አደራቸውን ተወጥተው አልፈዋል ተማሪዎቹ ከሰውየው ወደ አዲስ አበባ መምጣት ጋር በተያያዘ የተዘጋጀውን ሰልፍ ለመቀስቀስ ካሰራጩት ወረቀት በከፊል ብንመለከት የሚከተለውን እናገኛለን ረምንም እንኳን የሚመጡበት ምክንያት ሌላ ነው ቢባልም የተመ የወቅቱ ዋና ፀሐፊ የሆኑት ቡትሮስ ቡትሮስ ጋሊ ወደ አዲስ አበባ በዛሬው ዕለት ይገባሉ በአንድ ወገን የሕዝብ ወሳኝነት አግባብ ያለው መሆኑ እየተናፈሰ በሌላ በኩል ግን ወያኔና ጥርቅም ጀሌዎቹ ባረቀቁትና ሕዝብ ባልተነጋገረበት ቻርተር በመንተራስና ሕዝብ ባልወከለው መንግሥት የሰጠውን የአገር መገንጠል መልካም ፈቃደኝት ከግብ ለማድረስ የተመድ በመጣደፍ ላይ ነው በፋሽስት ኢጣሊያ ወረራ ጊዜ ሐገራችን ለሊግ ኦፍ ኔሽንስ ያሰማችው አቤቱታ ሰሚ አጥቶ እንደነበረው አሁንም የሕዝቧ ድምፅ እየታፈነ ነው ስለዚህ ኢትዮጵያ ሐገሬ ነች የምትል ሁሉ የዚህን አዝማሚያ አደገኝነት በመገንዘብ ዋና ፀሐፊው በሚመጡበት በዛሬው ዕለት ከሕዝብ ጋር በመተባበር የተቃውሞ ድምፅህን እንድታሰማ የዜግነት አደራ ተጥሎብሃል የአፍሪካ ቀንድ መጽሔት የካቲት ዓም በዚህ መልኩ የተሰናዳው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የተቃውሞ ሰልፍ ልክ በሩን እንዳለፈ የታጠቁ የፀጥታ ኃይሎች ተማሪዎቹ ላይ አነጣጥረው መተኮስ ጀመሩ ተማሪዎቹን ተመሳስለው የገቡ ሰርጎ ገቦች ኤርትራዊያኖችና ሰላዮች ሰልፈኛ ተማሪዎቹን በጩቤ በሽጉጥና በመሳሰሉት የጦር መሳሪያዎች መውጋታቸውን ቀጠሉ አሳዛኙ የአዲስ አበባ ተማሪዎች ሰልፍ በደም በተነከረ ፍጻሜ ተጠናቀቀ በዚህ ወቅት የተገደለውን ተስፋሁን ወርቁ የተባለ ተማሪ ነው የኢሰፓ አባል ነበርን ሲሉ ያላገጡበት የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በተጠቀሙት ከፍተኛ ኃይል ብዙ ተማሪዎች ለከፍተኛ ጉዳት ሲዳረጉ ለተስፋሁን ወርቁ ሕይወት ማለፍ ደግሞ ምክንያት ሆኗል በተማሪዎቹ ላይ የተወሰደው እርምጃ በለጋሽ ሐገራት ዘንድ ወጣት የአፍሪካ ዴሞክራት መሪዎች ሲባሉ የነበሩትን የኢሕአዴግ መሪዎች ገመና ደጅ አውጥቶ አሰጣው በዚህም ኢሕአዴግ ከፍተኛ ውግዘት ደረሰበት በደርግ አምባገነናዊ አገዛዝ ተማሮ የነበረው የኢትዮጵያ ሕዝብም ጥቂት ጊዜ ሰጥተን እንያቸው የሚለውን አባባሉን የሞኝ ቀጠሮ መሆኑን እንዲገነዘብ አደረገው ነገሩ ሁሉ የሚሆነው ታህሳስ ቀን ዓም ነበር ይህ ደግሞ ፕሮፌሰር አሥራት ደብረ ብርሃን ላይ ንግግራቸውን ካደረጉ ከቅርብ ቀን ልዩነት በኋላ ነበር ስለዚህ ይህን ህገ ወጥ ድርጊት ለማዳፈን ነው እንግዲህ የፕሮፌሰሩን የደብረ ብርሃን ንግግር ጦርነት ቀስቃሽ ነው የሚል መዝሙር መዘመር የተጀመረው እንደ ጦስ ዶሮ አሥራት ተፈልገው ተገኙ ወንጀልን ለመደበቅ ሌላ ወንጀል ፕሮፌሰር አሥራት ላይ መለጠፍ ስለነበረበት የሆነው ሁሉ ሆነ ፕሮፌሰር አሥራትም ይናገራሉ በእኔ አስተያየት በኢትዮጵያ ውስጥና በተለይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተከሰተ የተማሪዎች ችግር ስለነበር ያንን ለመሸፈን ህዝቡን ለማደናገርና ታዛቢን ለማሳሳት መዐሕድ ተፈልጎ ከዳር እስከ ዳር እንዲወገዝ ተደረገ በነገራችን ላይ የኤርትራ ጉዳይ ለሪፈረንደም ይቅረብ ቢባል እንኳን ህዝባዊ መንግሥት ከተመሰረተ በኋላ የሚሆን እንጂ በሽግግር መንግስቱ ወቅት አይቻልም ነበር የሽግግር መንግሥት ዓላማ ሐገሪቱ ላይ ምንም ነገር ሳያጓድል በሕዝብ ለተመረጠ መንግሥት ማስረከብ ነው በዚያ ላይ ኤርትራ ላይ ድርጅቶች እያሉ ሪፈረንደሙ በአንድ ድርጅት ሻዕቢያን ብቻ የመደረጉ ምሥጢር ማን አለብኝነት ካልሆነ በስተቀር ሌላ ምን ስም ሊሰጠው አይችልም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተቃውሞ ጭብጥም ይሄው ነበር የመዐሕድ ጦረኛ አለመሆን ለመንግሥት ጠፍቶት ሳይሆን ፕሮፌሰሩ በሰኔው ኮንፈረንስ ላይ የኤርትራ መገንጠል የሚፈቅደውን ቻርተር ስለ ተቃወሙ ጥርስ ተነክሶባቸው ስለቆዩና እና የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ የተወሰደውን እመቃ በሌላ አጅንዳ ለማዳፈን ታስቦ ነበር ነገሩ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ እንደማለት ነው የሆነው ሆኖ የመንግሥት ፕሮፖጋንዳና የተቀነባበረ ስም ማጥፋት ሊቆም ባመቻሉ ፕሮፌሰር አሥራት ይህ ዘመቻው ይቆም ዘንድ ለሽግግሩ መንግሥት ፓርላማ ደብዳቤ ጻፉ በወቅቱ ፕሮፌሰር አሥራት ጽፈውት በነበረው ደብዳቤ ላይ ድርጅታቸውም ሆነ እርሳቸው ከሰላማዊ ትግል ውጭ ሌላ መንገድን እንደማይከተሉ ያስረዳል አንባቢ የደብዳቤውን ሙሉ ጭብጥ ይረዳው ዘንድ ሙሉውን አቅርቤዋለሁ ጥር ፅ ቀን ዓም በቁጥር መዐሕድኃፇ ወጭ የሆነው ፕሮፌሰር አሥራት የጻፉት ደብዳቤ የሚከተለውን ይመስላል ርየኢትዮጵያ ሕዝብም ሆነ መዐሕድ የጦርነትን መንገድ አይመርጡም ውድ ሐገራችን ኢትዮጵያ የታወቀች የደመቀች የተከበረች የብዙ ሺህ ዘመን ባለቤት የሆነች አገር ነበረች በህዝቧም ጽኑ እምነትና ደጋግሞ በከፈለው መስዋዕትነት ሐገሩን አንድነቱንና ሉዓላዊነቱን በማስከበር ያሥገኘው ውጤት ለጥቁሩ የአፍሪካ ሕዝብ የነፃነት ዓርማ ሆኖ ኖሯል በዚህም ረጅም ዘመን ታሪክ ውስጥ ሐገራችን የተለያዩ እምነትና የፖለቲካ አመለካከት የነበራቸውን መሪዎች አስተናግዳለች በዚህም ጊዜ ውስጥ በታሪካችን የማይረሱ የሥልጣኔያችንና የእድገታችን አጥፊና ደምሳሽ የሆኑ ሁለት የውስጥ ወረራ ዘመኖች መኖራቸውን ባንረሳም በሐገሪቱ የግዛት አንድነት ነፃነትና ሉዓላዊነት ጥያቄ ላይ ግን ሕዝብና መንግሥት በተጻራሪ የቆሙበት አጋጣሚ ታይቶ አይታወቅም እርግጥ ነው የህዝቧ ልዩ ልዩ ብሔረሰብ ልጆች ለሥልጣን ሲሉ ጎራ ለይተው ተዋግተዋል ይህ ግን የብሔረሰቦችን ባሕል ልምድና ወግ በማቀራረብ አንድነታቸውን እያጎላ መጣ እንጅ የመከፋፈልን ፍንጭ አላሳየም እንዲያውም የአንድነትንና የነፃነትን ህልውና የሚጻረር ኃይል ሲነሳ ስንቃቸውን ሰንቀው እንደ ንብ ተዋግተው እንደ ጉንዳን አብረው የጋራ ጠላታቸውን ድል በመንሳት የሐገራችን ዳር ድንበር ሳይቆረስ ነፃነቷ ሳይገሰስ የነበረችውን ኢትዮጵያ ለዛሬው ትውልድ በክብር አስረክበውናል እንዲሁም ከጥቂት ቀናት በፊት በአዲስ አበባ በተካሄደው የሱማሌ አንጃዎች ጉባኤ ላይ የተከበሩ የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት አቶ መለስ ዜናዊ ባደረጉት ስሜታዊ ንግግር ምንም እንኳን ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተለገሰውን ቻርተር የሚጻረር ቢሆንምአንጃዎች አንድነት ፈጥረው ሶማሊያን እንዲገነቡ ያላስቻላቸውን ምክንያት የማያወላውል ምስክርነት ሲሰጡ የአንጃዎቹ መለያየትና መቃቃር በጎሳ ልዩነት ላይ ብቻ የተመሰረተ መሆኑን ያስተማሩት ትምሕርት መዐሕድን በጣም አስደስቶታል ምክንያቱም ይህም ትሩፋት ለኢትዮጵያ ሕዝብ ይደርሰዋል የሚል ምኞትና ተስፋ ስላደረበት ነው የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድነቱንና ሉዓላዊነቱን ለማስከበር ዴሞክራሲያዊ መብቱንም ከውስጥ ገዥዎቹ መዳፍ ለማላቀቅ በየ ትውልዱ መስዋዕትንትን ሲከፍል ኖሯል የውጭ ወራሪዎችንም በጋራ ሲመክት ለሰብዓዊ መብቱ ከውስጥ ገዥዎች ጋር በጋራ ሲታገልና ሲደማ የኖረውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ጥንካሬ በጎሳ በቋንቋ በሃይማኖት ለመበታተን ከብዙ ጊዜ በፊት ተወስኖ ሲወድቅ ሲነሳ የቆየው ሥልት ዛሬ በመካከላችን የበላይነት አግኝቶ ኢትዮጵያን ለመበታተንና የኢትዮጵያን ሕዝብም የሐገሩን የተፈጥሮ ሐብትና ሰብዓዊ መብቱን አስከብሮ በጀመረው የአንድነት ጎዳና እንዳይጓዝ የሚደረገው ጥረት እጅግ አሳሳቢ እንደሆነ የማይረዳ ዜጋ ሊኖር አይችልም ይህንን በሚመለከት ታሪክን እየጠቀሱ ሕዝብን ማስተማርና ከጎሳ ልዩነት ወደ አንድነት እንዲያተኩር መቀስቀስ ከኢትዮጵያዊያን የሚጠበቅ የወቅቱ ግዴታ መሆኑ ግልጽ ነው ይህም በመሆኑ የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት የኢትዮጵያ ሕዝብ ስለ አንድነቱም ሆነ ስለ ሰብዓዊ መብቱ የሚያደርገው የእርስ በርስ ትግል ከጦርነትና ከእርስ በርስ መጨፋጨፍ ባሻገር በሰላምና በመረጋጋት በውይይትና በሃሳብ በመተማመን ላይ ብቻ እንዲያተኩርና ይህም በሕዝብ ዳኝነትና ይሁንታ ከፍጻሜ እንዲደርስ የሚደረግበትን መድረክ ከልብ ያከብራል ሰላምና መረጋጋትም እንዲሰፍን የታጠቁ የፖለቲካና የብሔረሰብ ድርጅቶች በነፍጥ አስገዳጅነት በህዝቡ ላይ የሚጭኑት ግዴታ ሁሉ ለዘለቄታው መፍትሄ ሊሆን እንደማይችል ስለ አንተ የምናውቅ እኛ ብቻ ነን ጦርነት ይመጣብሃል የሚሉ ወገኖችም የበለጠ ወደ ጦርነት የሚመራ ጸረዴሞክራሲ ድርጊት እንደሆነ በማሳሰብ አሁን የሚታየውን የዴሞክራሲ ጭላንጭል በትዕግስት በጥበብ በመግባባትና በመቻቻል እንድንጠቀምበት ለማድረግ የመዐሕድ ምኞትና ፍላጎት ብቻ ሳይሆን ህዝቡም የሚታገልለት ዓላማው ነው ይህም በመሆኑ ጽቤቶቻችን በተጣቁ ኃይሎች ሲወረሩና ሲዘጉ አባሎቹ ሲታሰሩ ሲደበደቡና ሲገደሉ እንዲሁም የመዐሕድን ፕሮግራም ትደግፋለህ እየተባለ የህዝቡ መንደሮች በወታደራዊ ወረራ ሲቃጠሉ ህዝቡም ሲጨፈጨፍ አቤቱታውን በከፍተኛ ሀዘንና ተቆርቋሪነት ለሽግግሩ መንግሥትና ለተወካዮች ምክር ቤት ከማሰማት በቀር መዐሕድ ሌላ መንገድ አልመረጠም የእኛ ተስፋና ምኞት የኢትዮጵያ ሕዝብ የቆየ ትዕግስቱና አብሮ በመኖር ያካበተውን የጋራ ሕይወቱን መሠረት አድርጎ ዴሞክራሲን ለልዩነት ሳይሆን ለአንድነት እርስ በርስ ለመበላላት ሳይሆን ለጋራ እድገት የሚያውልበትን ሥርዓት እንዲጨብጥ ለማድረግ ስለሆነ የሚፈጸመውን በደልና ግፍ ሁሉ ለመንግሥት በአቤቱታ መልክ ከማቅረብ ባሻገር ሌላ መንገድ አልመረጥንም በእኛ እምነት የኢትዮጵያን ሕዝብ ወደ ጦርነት የሚመራ ምርጫ ምን ጊዜም ሊኖረን አይችልም ሆኖም በአንድነት ማመንና ይህንንም እምነት በስብሰባ ላይ መግለጽ ትምክህተኛ ጦረኛና ጦርነትን እንደ ማወጅ አድርገው የሚገምቱ አንዳንድ ወገኖች ግን መዐሕድን በዚህ ድርጊቱ ጦረኛ ነው እያሉ በፕሮፖጋንዳም ሆነ በሥልጣን ተጽዕኖ ሲያዋክቡት መኖራቸው ለኢትዮጵያ ሕዝብ አዲስ ሳይሆን በይፋ የታወቀ ነው ሆኖም አሁንም እንደገና ለኢትዮጵያን ሕዝብ የምናስታውሰው እጅን ለጠላት ሰጥቶ የሐገርንና የወገንን ክብር ከማስደፈር የጥይት እርሳስ እንደ ውኃ የጠጡ መሪዎችን ያስተናገደች ሐገር መሆኗን ማስታወስ ነው ዛሬ አንዳንድ አካባቢ ህዝቡ ስለ ሰብዓዊ መብቱ ስለ እንድነቱና ስለ ዴሞክራሲ የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ሁሉ መዐሕድ የሚገፋፋቸውና የሚያደራጃቸው እንደሆነ ተደርጎ መነገሩ እየተለመደ ሄዷል ምን አልባትም ባለፈው ወር ያለ ወቅቱ የመጣውንና ለገበሬው ሰብል አሳሳቢ የነበረውንም ዝናብ መዐሕድ ያመጣው መከራ ነው ለማለት የሚቃጣቸው ወገኖች እንደማይታጡ እየገመትን ሄደናል በዚህም አንጻር ለሚከሰቱትና ለሚከተሉት የብሶት ችግሮች ሁሉ መዐሕድ ተጠያቂና ኃላፊ መደረጉ የማይቀር ነው እነኝህም ለምሳሌ ያህል ለውድ ሐገራቸው ሕዝብ ኅብረት እድገትና አንድነት በመቆርቆር ለማሳሰብ በመሞከር ለሚደርስባቸው ኢሰብዓዊ ድርጊቶችና ከፍተኛ እልቂቶች ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሚቆጠር የሐገሪቷ የጦር ኃይልና የፖሊስ ሰራዊት ብሶት ውጤት ብየ መስሪያ ቤቱ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰርተው ያልደከሙ የትኩስ ጉልበትና ዕውቀትየተከማቸ የሥራ ልምድ ባለቤት የሆኑ ሰዎች በነገዳቸው ምክንያት ብቻ በማባረር የተከማቸ ብሶት ከፍተኛ የሥራ አጥ ክምችት ብሶት እንኝህና ተመሳሳይ ተጨማሪ ችግሮች ለሚያስከትሉት ክስተቶች ሁሉ መዐሕድን ቢወነጅሉ በኢትዮጵያ ሕዝብ ፊት ትዝብትን ብቻ ማትረፍ ነው እያልን በዝምታ ስናልፋቸው ቆይተናል ሰሞኑን ደግሞ የክልል እና የክልል መስተዳድር ምክር ቤቶች የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴዎች በመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት ህልውና ላይ በመንግሥት የመገናኛ መስኮች የሰጡትን መግለጫ በተለመደው ሁኔታና ባህሪያችን በሆነው ዝምታ ለማለፍ ያላስቻለን በመሆኑ የመዐሕድን ግልጽ አቋም ለሽግግር መንግሥትና ለኢትዮጵያ ሕዝብ እንደገና በጥሞና ማሳዎቅ ግድ ይሆንብናል የክልል እና የክልል ሶስት መስተዳድር ምክር ቤቶች የጦረኝነትና የዘረኝት ቅስቀሳ ያካሂዳል በማለት ህጋዊና ሰላማዊ እንቅስቃሴውን ለማገድ ያላቸውን ዕቅድ ህጋዊ ለማድረግ ሲሉ እንደ ምክንያት ያቀረቡት ታህሳስ ቀን ዓም የደብረ ብርሃን ከተማና የአካባቢው ሕዝብ በጠየቀው መሠረት የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት ባዘጋጀው ህዝባዊ ስብሰባ ላይ የድርጅቱ መሪ ያደረጉትን ንግግር በመጥቀስ ነው በክልሎቹ ባለሥልጣኖች በቀረበው በዚሁ መግለጫ ላይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በክልላችን የሕዝብን ሰላም ለማናጋት ያገኘነውንም እፎይታ ለማጥፋት አንዳንድ ድርጅቶች በቀቢጸ ተስፋ ሰክረው በሕዝብ መካከል ጦረኛና ዘረኛ የሆነውን መርዘኛ ቅስቀሳቸውን በመንዛት ላይ እንደሚገኙ ከገለጹ በኋላ ከእነዚህም መካከል አንዱ የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት መሆኑን አረጋግጠው የመዐሕድ መሪ በደብረ ብርሃኑ የሕዝብ ስብሰባ ላይ ያደረጉት ንግግር ከሁሉም በላይ ሕዝብን በዘር በሃይማኖት በመከፋፈል አንድ ሕዝብ በሌላው ላይ ጦር እንዲያነሳ የሚማጸን የተለያዩ የሐገሪቷን ህዝቦች የሚያንቋሽሽ የሚንቅ በቀጥታ ሰላምን ሳይሆን እልቂትን የህዝቦች እኩልነትን ሳይሆን መበላለጥን ሕግንና ሥርዓትን ማክበር ሳይሆን ህገ ወጥነትንና ሥርዓት አልበኝነትን የሚያስተጋባ ነበር ሲል ከከሰሰ በኋላ ይህን የመሰለ ተግባር ይህ ድርጅት ከእነማን ጋር እየተመካከረ በእነማን አይዞህ ባይነት ማንን ለመጥቀም እንደሚያደርገው ራሱ ድርጅቱ ያውቀዋል በማለት መዐሕድን ከሌላ ኃይል ጋር ለማስተሳሰር ከሞከረ በኋላ እንዲህ ዓይነቱን ድርጊት የማዕከላዊ የሽግግር መንግሥት በዝምታ ማለፍ እንደማይገባው ጠይቆ ክልሎች የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ለማስከበር በገቡት ቃል መሠረት ጉዳዩን በቸልታ እንደማያዩት በአስፈሪ ሁኔታ የሚያስጠነቅቅ ነው በተጨማሪም በማግስቱ የአማራን ክልል አስተዳደር የተረከበው የክልል መስተዳድር ምክር ቤት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በሰጠው መግለጫ ላይ መዐሕድ አማራው ተበደለ ተጨፈጨፈ እያለ የሚያቀርበው አቤቱታ ሁሉ ሐሰት መሆኑን አረጋግጦ በአማራ ላይ ይፈጸማል እያለ መዐሕድ የሚያሰማው አቤቱታ ሁሉ ጦርነትን ለመቀስቀስ እንደሆነ አድርጎ አቅርቦታል የክልል አስተዳድር ምክር ቤትም መዐሕድን ከአማራው ክልል ለማስወገድ የታቀደውን የሥልት አቅጣጫ ሰንዝሯል ታህሳስ ቀን ዓም በደብረ ብርሃን ከተማ ላይ በተደረገው ስብሰባ የመዐሕድ ፕሬዚዳንት ባደረጉት ንግግር ውስጥ የኢትዮጵያ ሕዝብ በሃይማኖትና በጎሳ መከፋፈሉ ለውጭ ጠላቶቻችንና ኢትዮጵያን ለማዳከም ለሚመኙ የሚበጅ መንገድ መሆኑን የሚገልጽ ከመሆኑ በቀር የኢትዮጵያ ሕዝብ በዘር በሃይማኖት መከፋፈሉን የሚደግፍ አይደለም ስብሰባውም ሆነ ንግግሩ ከማንኛውም ዜጋ ኃይል ጋር የሚገናኝ አይደለም መዐሕድን ደግሞ ከማንም ኃይል ከውስጥም ሆነ ከውጭ ኃይል ጋር ማገናኘት ትልቅ ስድብ አድርገን ብንቆጥረውም ጩኸቴን ቀሙኝ ስለሆነ በዚህ እንዝናናለን እንዲሁም የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚፈቅድለትን የህሊና ፍርዱን እንዲሰጥበት ንግግሩን በሙሉ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ እንዲሰራጭ እንዲደረግም በአክብሮት እንጠይቃለን የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት በየአካባቢው በአማራው ላይ የተፈፀመውንና አሁንም በመፈፀም ላይ ያለውን በደል የክልል መስተዳድር ምክር ቤት በቅርቡ በመፈጠሩ አላወቀም ወይም አልሰማም የሚባል ከሆነ በህዝቡ ላይ የሚደርሰውን በደል ኃላፊነት ላለበት አካል በአቤቱታ መልክ ማሰማት ወንጀል ነው የሚለንም ካልሆነ በቀር አሁንም ቢሆን በዝርዝርና በማስረጃ ማቅረብ እንችላለን ክልሉ የአማራን በደል ለመቅረፍ ኃላፊነት የሚሰማው ከሆነም ድርጊቱን ከመካድ ይልቅ ባለበት ኃላፊነት የሕዝብን ብሶት ሰምቶ መፍትሄ መፈለግ ከታሪክ ትዝብት የሚያድነው ይመስለናል በሐገራችን ላይ እየተካሄደ ያለው ታላቅ የጥፋት አደጋ በዓይነቱም ሆነ በውስጣዊ ሥልቱ በታሪካችን ታይቶና ተሰምቶ የማያውቅ ነው ይህንን ያልተገነዘበ ሰው ካለ ከድርጊቱ አፈጻጸም ጋር ያበረ ወይም ከአፍንጫው አርቆ ለማየት የተሳነው ከመሆኑም በላይ በግላዊ ጥቅም ስሜት መንፈሱ የታሰረ እስረኛ ብቻ መሆን አለበት በደብረ ብርሃን ከተማ የመዐሕድ ህዝባዊ ስብሰባ ላይ የተነገረው የሕዝብ ሰብዓዊ መብቶች መደፈርና መረገጥ ለእርስ በርስ መጨፋጨፍ መንገድ የሚከፍቱ ድርጊቶች ህጋዊ ሽፋን ማግኘታቸው ለሐገሪቱ ሰላምና መረጋጋት ጠንቅ ሊሆን እንደሚችልና በየደረጃው የሚገኙ የመንግሥት ባለ ሥልጣኞችም የሕዝቡን ሰብዓዊ መብት ለማስጠበቅና ራሳቸውም ለመጠበቅ ካልቻሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሰላም ወዳድና ጦርነት የሰለቸው ቢሆንም እንደ ምርኮኛ እጁን ወደ ላይ ሰቅሎ የውርደት ሞትን እንደማይጠብቅ ማወቅ እንዳለባቸው ማሳሰቢያ መቅረቡ የሕዝብን ስሜት ከማንጸባረቅ ባሻገር ጦርነት ማወጅ አድርጎ ማቅረብ ሊበሏት ያሰቧትን አሞራ ጅግራ ናት ይሏታል እንደሚባለው መሆኑ ነው ጦርነት ለማወጅ የጦር ኃይል ወይም በተደራጀ መልኩ የታጠቀ ኃይል መኖር አለበት መዐሕድ አለው ቢባል ቢሮውን የሚጠብቁ ሁለት ሽማግሌዎች ዘበኞች ናቸው እነኝህ ጥበቃዎች ችግር አምጥተዋል ከተባልን ለመለወጥ እንተባበራለን። እኔን አንድ ቀን አንድ ዓለማቀፍ ጉባዔ ላይ እንዳጋጠመኝ ምሑራን ሥራውን ለምርምር እንደተገለገሉበት እያደነቁ ሲጠቅሱ ብትሰሚ ዝሆን አጠገብ የቆመች አይጥ ሆነሽ ነበር ራስሽን የምታገኝው በማለት ረበብቃት ማነስ ነው የተባረሩት ለምትለው ገነት ዘውዴ መልስ ሰጥተዋታል ለነገሩ ሥልጣን ያመጣው የልብ ማበጥ ወይም ተናገሪ የተባለችውን መናገሯ እንጂ የእነዚህ ምሑራን ብቃት ዘንግተው አይደለም በነገራችን ላይ እነ ፕሮፌሰር አሥራት ከዩንቨርስቲ ሲባረሩ በብሽቀት በራሳቸው ፈቃድ ዩኒቨርሲቲውን የለቀቁ መምህራን በጣም ብዙ ነበሩ ኢሕአዴግ በአማራ ምሑራን ላይ የወሰደውን አሳፋሪ እርምጃ ለመሸፋፈን ብቃት የምትል ጭንብል ሊያላብሳት ቢሞክርም ነገሩ እንደ ፍየል ጅራት ሐፍረትን የሚሸፍን በቂ ምክንያት ሆኖ አልተገኘም ስለ ዩኒቨርሲቲ መምህራኑ መባረር ጉዳይ ፕሮፌሰር መስፍን አዳፍኔ በተሰኘ መጽሃፋቸው የሚከተለውን ጠቅሰዋል ርአገዛዝና ሕዝብ ዕውቀትን ከሥልጣን ውጭ ለማድረግ በተስማሙበት ማኅበረሰብ ዕውቀት እየደበዘዘና ጉልበት እየፈረጠመ ይሄዳል ይላሉ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም መስፍን በመጽሃፋቸው ወያኔን ጸረ ዕውቀት ሲሉ ይወርፉታል እስቲ በመጽሃፋቸው ካስቀመጡት ገጣጣ እውነት እንቀንጭብ ርየወያኔን ጸረዕውቀት አቋም በግልጽ የሚያሳየው ከዚህ በታች ያለው መረጃ ነው እነዚህ በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ሙሉ የፕሮፌሰርነት ደረጃ የደረሱ ምሑራን በጣም በታወቁ ከአሜሪካና ከአውሮፓ ዩንቨርሲቲዎች ተመርቀው የወጡና በሥራቸው ለብዙ ዓመታት እውቀታቸውን ያስመሰከሩ ምሑራን ናቸው እንኳን እንደ ኢትዮጵያ ላለ ኋላቀር አገር ይቅርና በአውሮፓና በአሜሪካ አገሮችም ተወዳድረው መሥራት የሚችሉ ናቸው ይሉና የፕሮፌሰሮቹን ሥም ይጠቅሳሉ ኛ ዓሥራት ወልደየስ ኛ ታየ መኩሪያ ኛ አየነው እጅጉ ኛ ዓለማየሁ ተፈራ እነማንና ስንቶቹ የወያኔ ባለ ዲግሪዎች ቢጨፈለቁና ቢጋገሩ ከእነዚህ አንዱን ይወጣቸዋልን ሲሉ ይጠይቃሉ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ወያኔ ከቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩንቨርሲቲ በችሎታ ማነስ ብሎ ያስወጣቸው መምህራን ሁሉ በአውሮፓና በአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች በመምህርነት ተቀጥረዋል በእነሱ ቦታ የተተኩት የድንጋይ ማምረቻ ከሚባለው ማሰልጠኛ ጣቢያ የወጡ ናቸው ሲሉም ያክላሉ ፕር መስፍን ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ለቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጂሚ ካርተር በጻፉት ደብዳቤ ላይ ከአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ከተባረሩት መምህራን መካከል በመቶው የአማራ ተወላጆች መሆናቸውን ይጠቅሳሉ ለዚህ ጸረ ሕዝብ ድርጊታቸው ደግሞ ብቃት ማነስ የምትል ከገለባ የቀለለች ምክንያት በቂ ነበረች እነዚህ የበረሃ ባለድግሪዎች ከኤደንብራ ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቁትን ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ብቃት የላቸውም ብሎ ለማባረር ድፍረቱን የሰጣቸው አላዋቂነታቸው ብቻ ነው የአላዋቂነት ትልቁ ጥቅሙም ይሄ ነው የማያውቁትን ነገር ለማድረግ ደፋር መሆን ይህ ቅኝ ገዥዎች በሚገዚቸው ሐገራት ላይ ሲያደርጉት የነበረው ጸረምሑራን እርምጃ በቀጥታ በአማራ ምሑራን ላይ ያነጣጠረ መሆኑ ደግሞ አበሳው የበዛበትን ሕዝብ ቅስም ለመስበርና ሌሎቹንም አፋቸውን ለማዘጋት የተቃጣ ፍላጻ ነበር በቻይና የባሕል ሪሾሉሽን ወቅት መሪዎቹ እነ ማኦ ዜ ዱንግ በቀጥታ የዘመቱት ምሁራኖቹ ላይ ነበር የኢህአዴጉን ጸረ ምሑራን እርምጃ ከቻይናዎቹ የመንፈስ አባቶቻቸው የተለየ የሚያደርገው እርምጃው አንድ ዘር ላይ ያነጣጠረ መሆኑ ብቻ ነው ርብቃት ያንሳቸዋል ተብለው ከአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ የተባረሩት የኤደንብራው ምሩቅ ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የቀዶ ሕክምና ዶክተር ሲሆኑ የዶክተሮች የሕክምና ማሰልጠኛ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታልን እንዲመሠረት ከፍተኛ ትግል ያደረጉና በፋካልቲው የመጀመሪያው ዲን በመሆን ያገለገሉ ናቸው በሙያቸው አንቱ የተባሉ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ የሚከተሉትን ሽልማቶች ያገኙ ድንቅ የሕክምና ሳይንቲስትም ነበሩ ከአሥራት ሽልማቶች መካከል ኛ የኢትዮጵያ የክብር ኮከብ የፈረሰኛ ደረጃ ኛ የዳግማዊ ምኒልክ ኒሻን የፈረሰኛ ደረጃ ኛ የአብዮታዊ ዘመቻ ዓርማ ኛ ዓለም አቀፍ የወርቅ ሜርኩሪ በግል አስተዋጽኦን ኛ የቀይ ባሕር ኒሻን አንደኛ ደረጃ ያገኙ ሲሆን ፕሮፌሰር አሥራት በመሥራችነት የተሳተፉባቸውና አባል የነበሩባቸው ብዙ የሙያ ማህበራትም ይገኛሉ ከእነዚህም መካከል የኢትዮጵያዊያን ሐኪሞች ማኅበር መሥራችና አባል የኤደንብራ የቀዶ ሕክምና ሐኪሞች ማኅበር አቻ አባል የእንግሊዝ የሐኪሞች ማኅበር አባል የምሥራቅ አፍሪካ የቀዶ ሕክምና ማኅበር አባል ዓለም አቀፍ የሕክምና ማኅበር አባል ነበሩ እኝህን መተኪያ የሌላቸው ምሑር ነው የጫካዎቹ የአቦጊዳ ፋኖዎች ብቃት የላቸውም ብለው ከሚወዱት ሥራቸው ያባረሯቸው እዚህ ጋር ነው የፕሮፌሰር መስፍን በአፍሪካ ምድር ዕውቀት ከሥልጣን ይመጣል የሚለው ዘመን ተሻጋሪ አባባል በትክክል የሚገልጽልን ምዕራፍ ስድስት ፕሮፌሰር አሥራት በኢሕአዴግ እሥር ቤቶች ፕሮፌሰር አሥራት ሐምሌ ቀን ገፀ ዓም ለጥያቄ ይፈልጋሉ ተብለው እንደተጠሩ በዚያው ታስረው ይቀራሉ ነገሩ የሆነው ከዚያ በፊት ይደረግባቸው ከነበረው አሰልች የደህንነት ክትትልና ወከባ በኋላ ነበር በዚያው ሰሞን ከደህንነቶች የመንግሥት አካላትን ኪስ ወድቆ ተገኘ ስለሚባል ወረቀት በሰፊው ይናፈስ ነበር የወረቀቱ ይዘት እንዲህ ይነበባል ርእንደ ኦነግና መዐሕድ ያሉትን የፖለቲካ ተቋሞችና መሪዎቻቸውን ሥልታዊ በሆነ መንገድ መታገል እንደሚገባና ሕይወታቸውን መራራ ማድረግ ሥልካቸውን መጥለፍ እንደ ፕሮፌሰር አሥራት ያሉትን በየጊዜው ማሰርና መፍታት የልብ ሕመም ስላለባቸው በሽታቸውን የሚቀሰቅሱና ለሞት የሚያደርስ ጭንቀት መፍጠር ይህ የተያዘው ሥልት መሆኑን ወድቆ ተገኘ የተባለው ወረቀት አጋለጠ በእርግጥ ወረቀቱ ከመንግሥት ደህንነቶች እጅ መውደቅ አለመውደቁን እርግጠኛ መሆን ባይቻልም ማንም ሰው ለማደናገር ሲልም ጽፎ ሊጥለው እንደሚችል ሁሉን ከሁኔታዎች መረዳት እንደቻልነውና የወረቀቱን መልዕክት አንድ በአንድ ከመፈጸሙ ጋር ስናሰናስለው በእርግጥም ወረቀቱ ከመንግሥት ደህንነቶች እጅ ወድቆ ሊሆን እንደሚችል መጠርጠራችን አይቀርም በአናቱም ፕሮፌሰሩ ላይ ይደረግባቸው ከነበረው ወከባና ማጨናነቅ በመነሳት በዚያው ላይ የልብ በሽታ ታማሚ ከመሆናቸው ጋር ተደማምሮ የወረቀቱ ይዘት ከነባራዊ እውነቱ ጋር ቁልጭ ብሎ ይመሳሰላል ይሁን እንጂ ፕሮፌሰር አሥራት ቀድሞውንም በጸና መሠረት ላይ የተደላደለው መንፈሳቸው በማንኛውም ማጨናነቅም ሆነ ወከባ ከያዙት መንገድ ፈጽሞ አላንገዳገዳቸውም ነበር የግሪኩ የፍልስፍና አባት አርስቶትል ለታላቅነት ተግባር ራሱን ያዋለ ሰው የሰብዓዊ ክብር ዓርማ ነው ሲል ስለ ጀግኖች የተናገረው ፕሮፌሰርን በወጉ ይገልጻቸዋል ፕሮፌሰር አሥራትም ራሳቸውን ለሰብዓዊ ክብር ያጩ ከመሆናቸው የተነሳ ሰማይ በነጎድጓድ ቢታረስ መሬት ብትደረመስ ውቅያኖሶች በማዕበል ቢመቱ አንዳች የመደንገጥ ስሜት አይነበብቻቸውም ነበር ይላሉ የሚያውቋቸው ሰዎች ጆን ኦፍ ኬኔዲ አንድ ደጋግመው የሚጠቅሷት አባባል ነበረቻቸው አንድ ልበ ሙሉ ሰው አንድ ራሱ እንደ ብዙሃን የሚቆጠር ነው የምትል ኬኔዲ ለፕሮፌሰር አሥራት የተናገሩት እንኪመሥል ድረስ አባባሉ እጅጉን ያምርባቸዋል ሁሉም ወርቃማ አባባሎች ለአሥራት በልካቸው የተሰፉ ናቸው አሥራት አንድ ብቻቸውን አንደ ብዙሃን የሚቆጠሩ ራሳቸውን ለታላቅነት ያጩ ልብ ሙሉ ጀግና ናቸው ማለት ይቻላል ለማንኛውም ፕሮፌሰር አሥራትን በወከባ ማስፈራራት ዛቻ በከበባና በእንግልት ወደ ኋላ እንዲያፈገፍጉ ማድረግ አልተቻለም ስለዚህ አንዳች የክስ ጥብቆ አስፈልጓል ለዚህ ደግሞ ከጎጃም ከመጡ አርሶ አደሮች ጋር አሲረሃል የሚል ክስ በቂ ጥብቆ ሆኖ ተገኝቷል አጥንትን እንደ ውሻ እየቆጠረ የሚከስ አቃቤ ሕግ በአለቃው የሥልክ ጥሪ ትዕዛዝ ተቀብሎ የሚፈርድ ዳኛ እስካለ ድረስ የክሱ ጭብጥ ምንም ይሁን ምን ችግር የለውም በቃ ትከሰሳለህ ይፈረድብሃል ዋናው መከሰሱ ነው ተከራክሬ ነፃ እወጣለሁ የሚለው የሕግ ክርክር በአንባገነኖች ችሎች ወረቀት ላይ የተጻፈ የቀለም ጀግና ነው በገ ብር ተገዝቶ የሚመሰክር ቋሚ ምስክር እስካለ ድረስ በደመወዙ እያስፈራራህ የምታከራክው ቋሚ ፍትህ ደፍጣጭ ዐቃቤ ሕግ እስከቀጠርክ ድረስ ምንም ጭብጥ ይዘህ ብትከስ አሸናፊው አንተ ነህ የውሸት ጋወን አጥልቆ እውነትን የሚደፍቅ ፍትህን አፈር ድሜ የሚያስግጥ ዳኛ በሞላበት በዚያና በዚህ ወቅት ማጥፋትህ ሳይሆን ማን መሆንህ ታይቶ በሚስተናገድ የሁለትዮሽ ክርክር እውነት መያዝህ ብቻ ዋስትና ሊሆንህ አይችልም ጠብመንጃ የያዘ በሚያሸንፍበት ሐገር የክሱ ጨብጥ አያሳስብህም ይህ በኢሕአዴግ ዘመን የተረጋገጠና ያገጠጠ እውነት ነው ይህ እውነት ቢመርሕም ትጋተዋለህ በዚህ ረገድ በሐገራችን ታሪክም አንድ ጥቁር ነጥብ አስመዝግበናል ርኢትዮጵያን ለማዳን በልበ ሙሉነት የተጋፈጡት የመዐሕድ መሪ ክቡር ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ አስተዋጽኦ በታሪክ ሲወሳ የሚኖር ነው ይህን የተናገሩት የድርጅቱ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር የነበሩት ቀኛዝማች ነቅዐጥበብ በቀለ ናቸው በአጠቃላይ ልብ አንጠልጣዩ በኮሜዲና ትራጀዲ ዘውግ ራሱን እንደ ሁኔታው የሚለዋውጠው የአሳሪ ታሳሪ ድራማ የተጀመረው ሐምሌ ቀን ዓም ነበር ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ለጥያቄ ይፈለጋሉ ተብለው ሐምሌ ቀን ዓም ተጠርተው ለ ሰዓታት ከታሰሩ በኋላ በዐ ሺህ ብር ዋስ ሐምሌ ቀን ዓም ተለቀቁ ልብ አንጠልጣዩና ኮሜዲ ዘውግ ብየ የሰየምኩት ድራማ ሐምሌ ቀን ዓም ይጀምራል ምናልባትም በሐገሪቱ ከተሰሩት ሳታየር ድራማዎች ሁሉ ይኹ አስቂኙ ሳይሆን አይቀርም ነገሩ እንዲህ ነው ሐምሌ ፅ ቀን በዐ ሺህ ብር ዋስ የተለቀቁት ፕሮፌሰር አሥራት በዚያው ዕለት የማዕከላዊ መንግሥት አቃቤ ሕግ ዐዋጅ ቁጥር አንቀጽ የተሰኘውን ጠቅሶ በቁጥር ጠክማአ በ ለቀጨኔ አውራጃ ፍርድ ቤት ቀዳሚ ምርመራ እንዲጣራ ውክልና ሰጥቻለሁ በሚል ምክንያት በዚሁ ዕለት ከሰዓት በኋላ እንዲቀርቡ ተደርጓል ተወከሉ የተባሉት አቃቤ ሕግ በዚሁ ዕለት በ በቁጥር ቀአ በሆነ ክስ ፕሮፌሰር አሥራትን አንደኛ ተከሳሽ በማለት ከሌሎች ስድስት ሰዎች ጋር በተከሳሽነት ሰይመው የወንጀል መዝገብ ቁጥር ተከፍቶ በዕለቱ ፅ ምስክሮች ከእሥር ቤት ቀጨኔ አውራጃ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ተደርጎ ተሰምተዋል ባለ ተከታታይ ክፍል ሳታየር ድራማው ይቀጥላል በገገ በፕሮፌሰር አሥራት ላይ የተቆጠሩት አምስት ምስክሮች የቀጨኔ አውራጃ ዐቃቤ ሕግ ይመሰክሩልኛል ብሎት የነበረውን ተስፋ በማጨለም ድርጊቱ ሲፈጸም ማየት ይቅርና ፕሮፌሰር አሥራትን በመልክም ሆነ በሙሉ አካል እንደማያውቋቸው ክሱን በማስተባበል ይመሰክራሉ ዐቃቤ ሕግ ግን ሌላ ምክንያት በመደርደር ለፍርድ ቤቱ አቤቱታውን አቀረበ ዐቃቤ ህጉ ኛ እኛ ኛ የዐቃቢ ሕግ ምስክሮች ስላልቀረቡልኝ በተለዋጭ ቀጠሮ እንዲቀርቡ ይታዘዝልኝ በማለታቸው ዐቃቤ ህጉ በጠየቁት ቀጠሮ መሠረት ለሐምሌ ቀን ዓ። ድርጅቶች ወይም የፖለቲካ ፓርቲዎች የፖለቲካ አመለካከታቸውን ለህዝቡ እንዲያሰራጩና ደጋፊዎችና አባላትንም እንዲያሰባስቡ ቻርተሩ ይፈቅድላቸዋል በሌላ አንጻር ደግሞ በተረጋገጡ መረጃዎች ሰላማዊ ያልሆኑ እርምጃዎች በፖለቲካ ድርጅቶች ተወስደዋል ከተባለና ይህም በፍርድ ቤት ከተረጋገጠ በሐገሪቱ ሕግ መሠረት ለጥፋቱ ተመጣጣኝ ቅጣት በድርጅቶቹ ላይ ይወሰናል ቅጣቱም ይፈጸምባቸዋል የዚህን ዓይነት አሰራር ሁላችንም የምንቀበለው ሆኖ ሳለ ከዚህ ውጭ በአንድ ድርጅት ላይ የፕሮፖጋዳ ዘመቻ ማካሄድና በአመራሩና በአባላቱ ላይ ተጽዕኗዊ እርምጃዎችን መውሰድ እየታገልንለት ያለነውን በሐገራችን የዲሞክራያዊ ሥርዓት ማስፈን ተስፋ ያደበዝዘዋል እንጅ የሰላም የነፃነትና የዕድገት በር ከፋች አይሆንም በዚህ መግለጫችን በመዐሕድ ላይ እየደረሰ ያለውን በደል እንደ ምሳሌ አነሳነው እንጂ በደቡብ ህኅረት አባል ድርጅቶች በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ መምህራን በኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር እና በሌሎችም የኢህአዴግን ፖሊሲ ሙሉ በሙሉ አሜን ብለው በማይቀበሉ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይ የሚደርስ ተጽዕኖና ካለ ምክንያት ከሥራ መባረር ከመኖሪያ ቦታ መፈናቀል መታሰር ለጭፍን ፕሮፖጋንዳና የማጥላላት ዘመቻ ኢላማ መሆን በቸልታ መታየት ያለባቸው በደሎች አይደሉም ስለሆነም ከዚህ ቀደም በረቀቀ ሥልት ይፈጸም የነበረው የኢዲሞክራሲያዊነትና የሰብዓዊ መብት ረገጣዎች ገሐድ እየሆኑ መምጣታቸው እንዲቆም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በሐገር ውስጥና በውጭ ሐገር ያሉ ኢትዮጵያዊያን የፖለቲካና ሌሎች ድርጅቶች እንዲሁም ሰላምና ዲሞክራሲ ወዳድ የዓለም መንግስታትና ድርጅቶች በመዐሕድ እና በሌሎችም ነፃ አመለካከት ባላቸው የፖለቲካ ድርጅቶችና የሙያ ማህበራት እና ግለሰቦች ላይ የሚካሄዱትን ኢ ዲሞክሲያዊና ኢሰብዓዊ ድርጊቶች እንዲያወግዙና እንዲታገሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን የሕልውናችን መሠረት የሰብዓዊ መብቶች መከበር ነው የጋራ የፖለቲካ መድረኩ ማዕከላዊ ምክር ቤት ሐምሌ ቀን ዓም አዲስ አበባ የሕዝባዊ ስብሰባው ሳይደረግ መቅረት ብዙውን የመዐሕድ አባላት ደጋፊዎችና ነፃነት ናፋቂዎችን ሁሉ አስቆጥቷቸዋል ፕሮፌሰር አሥራት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ በህዝባዊ ስብሰባ ለመጠየቅ ጉጉቱ የነበረው ኢትዮጵያዊ ሁሉ በክልል አስተዳድር ማን አለብኝት ተደናቀፈ ቀደም ብሎም ፕሮፌሰሩ ፍርድ ቤት በሚቀርቡበት ወቅት ሂደቱን የሚከታተላለው ሕዝብ ብዛት በዓለም ታይቶ የማይታወቅ ቁጥር ነበረው ቀድሞውንም ችሎቱን የሚከታተለው ሕዝብ ቁጥር እጅግ ብዙ የነበረ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ፕሮፌሰር አሥራት እንዲፈቱ የታሰበው ህዝባዊ ሰልፍ ባለመደረጉና ለተደጋጋሚ ቀጠሮ መዳረጋቸው የነሐሴ ዐ ቀኑን ቀጠሮ የበለጠ እንደ ምጽዓት ቀን እንዲጠበቅ አደረገው ነሐሴ እንደተጠበቀች አልቀረችም ምንም እንኳን የፕሮፌሰሩ ችሎት ለስድስት ጊዜ በይደር ቢቀጠርም አድናቂዎቻቸው የፓርቲያቸው አባል እና በእጅ ጥበባቸው ከሕመማቸው የተፈወሱ ሰዎች ፍርድ የቤቱን ቅጥር ግቢ በጠዋቱ ወረውታል የነሐሴው ዶፍ ዝናብ አንድንም ሰው ከችሎቱ እንዲቀር የማድረግ አቅም አልነበረውም ለውሳኔ መስሚያ በተቀጠረው ነሐሴ ቀን ገ ዓም የተከሳሽ ጠበቃና የመዐሕድ ደጋፊዎች በኢትዮጵያ አንድነት የሚያምኑ ዜጎች እንዲሁም አያሌ ጋዜጠኞች ሌሎችም ታዛቢዎች በተገኙበት ልክ ከጠዋቱ ከሁለቱ ሰዓት ተኩል በመጀመር የችሎቱን መሰየም መጠባበቅ ተጀመረ አጥንትን ሰርስሮ በሚዘልቀው የነሐሴ ብርዳማ ጠዋት ተወዳጁ ሐኪም ታዋቂው ፖለቲከኛ የመርሕ ሰውና የግፉአን አባት አሥራት ወልደየስ ሺሆችን በጥበብ ያዳነው እጃቸው በካቴና ታስሮ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ በዚያች ማለዳ የምኒልክ አደባባይና የጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ መሸከም እስኪያቅታቸው ድረስ በሰው ክብደት ተንቀጠቀጡ የመዐሕድ አባላት አመራሮች ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያውያን አሥራት በእጃቸው አልጋህን ተሸክመህ ሂድ ብለው ሕይወታቸውን ከመላዕከ ሞት የነጠቁላቸው ታካሚዎቻቸው ከእውቀታቸው ማዕድ አቋድሰው ጠበብት ያደረጓቸው የቀድሞ ተማሪዎቻቸው የሥራ ባልደረቦቻቸው ጋዜጠኞች ዲፕሎማቶች እንዲሁም ለፕሮፌሰር አሥራት ቅርበት ያለው የሰው ዘር ሁሉ ቤቱ የቀረ አይመሥልም የአካባቢው መሬት መሸከም አቅቷት እስክታቃስት ድረስ በሰዎች ተሞላች በዓለም ደረጃ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ችሎት ለመከታተል የመጣው ሕዝብ ከመብዛቱ የተነሳ አካባቢውን ሰላማዊ ሰልፍ የሚከናወንበት አስመስሎታል ትዕይንቱን በተመስጦ ለሚከታተለው የመጨረሻው ዘመን ፍጻሜ ይመስላል እልህና መገፋት የሚነበብባቸው ነፍሶች ተሰባስበው የፕሮፌሰሩን ወደ ፍርድ ቤት መምጣት እየተጠባበቁ ነው የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ወደ ጊዜያዊ ወታደራዊ ካምፕነት ተቀይሯል ነሐሴ ዐ ቀን ዓም የፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስን ወደ ፍርድ ቤት መምጣት በሚጠባበቁ ታዳሚዎችና የፕሮፌሰሩን አድናቂዎች በሚጠብቁ ወታደሮች መካከል ፍጥጫ ነግሷል በዚያች ብርዳማ የክረምት ማለዳ ጭምብል ያደረጉ እህል ውኃ የማያስብል ቆመጥ የያዙ ጠብመንጃ ያነገቡ ሌለው ቀርቶ አድማ መበተኛ ጭስ የያዙ የፀጥታ ኃይሎች የጭካኔ ምልክት በሚታይት አኳኋን አልፎ አልፎ ጥርሳቸውን የሚነክሱ አለፍ ሲልም አንዳንድ የትንኮሳ ቃላት የሚወረውሩ የፀጥታ ኃይሎች ከሰልፈኛው እኩል አካባቢውን ወረውታል በወቅቱ የነበረው ሁኔታ አንድ ፕሮፌሰር ፍርድ ቤት የሚቀርቡ ሳይሆን አብዮታዊ መፈንቅለ መንግሥት የሚካሔድ ነበር የሚመስለው የተገፊዎችን መብት የሚነጥቁና መብታችን እናስከብራለን የሚሉ ሁለት ቦታ የተከፈሉ የአንዲት ኢትዮጵያ ልጆች የተፋጠጡበት ማለዳ ነሐሴ ዐ ዓም በወቅቱ የፕሮፌሰር አሥራት ደጋፊዎች ችግር ፈጠሩ የሚል ሰበብ እንዳይኖር ሲሉ ብቻ ራሳቸውን እንደ ፀጥታ አስከባሪ በማድረግ የነበረውን ውጥረት የማብረዱ ግዴታ አለባቸው የፀጥታ ኃይሎቹ ብጥብጡን ይፈልጉታል የችሎቱ ተከታታዮች ግን በከፍተኛ መታገስ ሁሉንም እያለፉ ነው ይህ ሁሉ ትዕግስትና ጥበቃ ግን ፍሬያማ አልነበረም በነፃ ፍርድ ቤትነት ስም የሚያምታታው ትክክለኛ ፍትህም እሰጣለሁ የሚለው ፍርድ ቤት የሰጠውን የቀጠሮ ቃል አብሏል ለውሳኔ መስሚያ በተቀጠረው ነሐሴ ቀን ዓም የተከሳሽ ጠበቃና የመዐሕድ ደጋፊዎች በኢትዮጵያ አንድነት የሚያምኑ ዜጎች እንዲሁም አያሌ ጋዜጠኞች ሌሎችም ታዛቢዎች በተገኙበት ልክ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ተኩል በመጀመር የችሎቱን መሰየም በነፃ ፍርድ ቤትነት የሚምል የሚገዘተው ፍርድ ቤት የሰጠውን የቀጠሮ ቃል አክብሮ ሳይሰየም ቀረ የሕዝባዊ ስብሰባው ሳይደረግ መቅረትና ፕሮፌሰር አሥራት በዚያ ወቅት ለችሎት አለመቅረባቸው ያበሳጫቸው የፕሮፌሰር አሥራት ደጋፊዎች በወቅቱ በዚያው ሰልፍ ለማድረግ ሞክረው ነበር ከሠልፈኞቹ መካከል ርፕሮፌሰር አሥራት የኢትዮጵያ እውነተኛ ልጅና የዘመናችን ታላቅ ጀግና የሚል መፈክሮችን የሚያሰሙ ነበሩበት ነሐሴ ቀን የፕሮፌሰር አሥራትን የፍርድ ቤት ችሎት ለመከታተል ከተገኘው ሕዝብ በከፊል በዚያች ቀን ፍርድ ቤት ያልቀረቡበት ምክንያት ሕዝባዊ ሰልፉ በመከልከሉ የፕሮፌሰር አሥራት ደጋፊዎች ቁጥር መጨመር መንግሥትን አሳስቦት ሊሆን ይችላል ብቻ በዚህም ተባለ በዚያ ሕዝቡ ለፕሮፌሰር አሥራት የዘመናችን እውነተኛ ታላቅ ሰው የሚል የክብር ሽልማቱን አጎናጽፏቸዋል ለነገሩ የታላቅ ሰውነቱ ሽልማት ቢያንስባቸው እንጂ አይበዛባቸውም እኝህ እውቅ ምሑር ለሕዝብ ሲሉ የሞቀ ሕይወታቸውን ትተው ቀዝቃዛ ቤት ተጥለዋል ተንደላቀው መኖር ሲችሉ ከድሃው ሕዝብ ጋር አብረው እየወደቁ እየተነሱ የሕዝብ አገልጋይነታቸውን አስመስክረዋል ስለዚህ ረየዘመናችን ጀግናን መባል ሲያንሳቸው ነው ፕሮፌሰር አሥራት እንዲፈቱ በሐገር ቤት ከሚደረገው ትግል ጎን ለጎን ኢትዮጵያዊያ በሚኖሩባቸው ሐገራት ሁሉ ሰልፎችና ስብሰባዎች ተደርገዋል በተለይ በሰሜን አሜሪካ በተለያዩ ግዛቶች ሰልፎችና ስብሰባዎች ተደርገዋል ለምሳሌ በዋሽንግተን ዲሲ በቦን በጀኔቭ በመሳሰሉ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎችን በማድረግ ለዓለም ዓቀፍ ማኅበረሰቡ የማሳወቅ ሥራ ተሰርቶ ነበር በሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ግዛቶችን የሚወክሉ ቁጥራቸው ወደ ፖዐዐ የሚጠጋ ኢትዮጵያውያን ለሰባት ቀናት በየምሽቱ ሻማና ጧፍ በማብራት በዋሽንግተን ዲሲ ዋይት ሐውስ ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍና ስብሰባ አድርገው ነበር በወቅቱ በስፍራው ስለነበረው ሁኔታ የመላው አማራ ሕዝብ የዕርዳታና ልማት ማኅበር» አስተባባሪነት በዋሽንግተን ዲሲ ሐምሌ ቀን ዓም የተደረገው ሠልፍና ስብሰባ ምን ይመሥል እንደነበር የሚናገሩት የማህበሩ ሊቀመንበር ዶክተር ገብርየ ወልደሩፋኤል ለአሜሪካ መንግሥትም ፕሮፌሰር አሥራት እንዲፈቱ በማሳሰብና አስተዳደሩ በኢትዮጵያ ላይ ያለውን ፖሊሲ እንዲለውጥ በመጠቆም ደብዳቤ እንዲደርሰው ተደርጓል ብለዋል ኢዲኃቅን ጨምሮ ብዙ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተገኙበት ሰልፍ አላማው ፕሮፌሰር አሥራት በአስቸኳይ እንዲፈቱና ድርጅታቸው መዐሕድ ላይ የሚደረገው የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ እንዲቆም ለአሜሪካ መንግሥት ማመልከት ነበር በሚኒሊክ አደባባይ የተካሄደ የዓሥራት ይፈቱ የሻማ ምሽ ማንዴላ ወ ጋንዲ ፕሮፌሰር አሥራት ፍርድ ቤት በሚቀርቡበት ቀን ሁሉ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ደጋፊዎቻቸው ሞቅ ባለ ሰላምታ ነው የሚቀበሏቸው በፍርድ ቤቱ ቅጽር ግቢ የሚሰበሰበው ወፈ ሰማይ ሕዝብ አሥራት ማንዴላ እያሉ ይዘምሩ ነበር እንዲሁም በሌላ በኩል አሥራት ኢትዮጵያዊ ጋንዲ የሚሉም ነበሩበት ስለዚህ ጉዳይ የተጠየቁት ፕሮፌሰር አሥራት ለማኅሌት መጽሔት መስከረም ዓም በሰጡት ቃለ ምልልስ በየ ፍርድ ቤቱ አደባባይ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል በዝናብ እየተደበደበ በፀሐይ እየተቆላ በከፊልም በእንባ እየተዋጠ በሚያስተጋባው ልዩ ልዩ የድጋፍ መልዕክቶች ውስጥ የኢትዮጵያ ማንዴላን ሲባል ሰምቻለሁ እንዲሁም በአንዳንድ መጣጥፎችም ማንዴላ ይሁን ጋንዲ ሲባል አንብቤያለሁ ረእነኝህ ሁለቱም ታላቅ ዓለም አቀፍ ዕውቅ ሰዎች በዘመናቸውና በሐገራቸው ህዝባቸውን የተጫነውን ግዙፍ የጭቆና ግዛትና ሰቆቃ በሰላማዊ መንገድ ለማስወገድ ለረጂም ዘመናት ባከናወኑት ትግል በይፋ የታወቁ ሰዎች ናቸው ለኢትዮጵያ አንድነት የቆመ የኢትዮጵያ ሕዝብ በተናጥል የተፈረደበት የአማራ ሕዝብ መልካም ፈቃዱና ስሜቱ ሆኖ ከእነኝህ ታላላቅ ሰዎች ስም ጋር ቢያገናኘኝ ቸርነቱ ነው እንጂ እኔ በምንም ዓይነት ለዚህ ታላቅ ስፍራ ብቁ ሆኘ እንዳልሆነ ግልጽ ነው ሲሉ ይመልሳሉ ማንዴላ ወይም ጋንዲ ሁሉ በታሰሩበት ወቅት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ የፍርድ ችሎቱን ይከታተል ነበር የፕሮፌሰር አሥራትም ቢሆን ቢበልጥ እንጂ አያንስም የፕሮፌሰሩን የፍርድ ችሎት ብዙ ሕዝብ መታደሙ ብቻ ሳይሆን እንደ ሰላማዊ ሰልፍ ነበር የሚቆጠረው በዚያውም ማንዴላ እና ጋንዲ ብለው በፍቅር የሚጠሯው ሰዎች ቁጥር ብዙ ነበር ምንም እንኳን ፕሮፌሰር አሥራት ራሳቸውን በትህትና ዝቅ አድርገው ማንዴላ ወይም ጋንዲ ጋር መወዳደሩን ባይፈልጉትም አስተያየት ሰጭዎች ግን ማንዴም ሆነ ጋንዲ የሚለው ስም ይገባቸዋል ይላሉ የጦቢያ መጽሔት ሪፖርተር በወቅቱ ፍርድ ቤት ተገኝቶ ያነጋገራቸው ሰዎች አስተያየታቸውን እንደሚከተለው ሰጥተዋል ረበአሁኑ ጊዜ የጎሳ ፖለቲካ ወደ ዘረኝነት ይዛወራል ተብሎ ስለሚያሰጋ ፕሮፌሰሩ በአንድ በኩል ማንዴላ ሊባሉ ይችላሉ ምክንያቱም ማንዴላ በዘረኝነት ላይ የተነሱ ስለነበረ ነው እንደሚባለው ግን የሚስማማቸው ጋንዲ የሚለው ስያሜ ነው ሲሉ በሌላ ጎኑ ደግሞ የመዐሕድ ደጋፊ የሆኑት ሻለቃ ምሕረቱ ዘውዴ «ማንዴላ ከማለት ጋንዲ መባሉ ነው የሚስማማቸው ምክንያቱም በሰላም ከዐቡዘዐፀበርፀን የሚያምኑና ያንንም እምነታቸውን ለማራመድ የሚፈልጉ መሆናቸው ነው የጋንዲን ፍጻሜ ያርቅላቸውና ፕሮፌሰሩ እንደ ትሑት ጨዋ እና አዛኝ ሃይማተኛና እምነታቸውን በሰላም ላይ የጣሉ ናቸው ጦቢያ መጽሔት ሁለተኛ ዓመት ቁጥር ነሐሴ ዓም እትም ምንም እንኳን አስተያየት ሰጨው የጋዲን ፍጻሜ ያርቅላቸውና ብለው ስጋታቸውን ቢገልጹም ኢትዮጵያዊው ጋንዲ አሥራት የሞቱት እንደ ህንዱ ጋንዲ በአንድ ወፈፌ መንገደኛ አለመሆኑ እንጂ በግፈኞች ሴራ ከመሞት ግን አላመለጡም። ኢንተርቪው እናደርጋቸዋለን በዚህ የተነሳ በአብዛኛው የነፃው ፕሬስ አባል ጋዜጠኞች ፕሮፌሰር አሥራትን ጋንዲ ማርቲን ሉተር ኪንግ ማንዴላን እያሉ ሲጠቅሷቸው ነበር ይህም የቆሙለትን ከሽብር ነፃ የሆነ ሰላማዊ ትግል ለመግለጥ ነበረ ሲል ሃሳቡን ሰንዝሯል ጦቢያ መጽሔት ቅጽ ቁጥር ዐ ገ ዓም እትም በሌላ በኩል በአንድ ወቅት የመዐሕድ ተቀዳሚ ፕሬዚዳንት የሆኑት ቀኛዝማች ነቅዐጥበብ በቀለ ከሪፖርተር ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ፕሮፌሰር አሥራትን ረምኒልክ ብያቸዋለሁ ሲሉ ተናግረው ነበር እኝህ ታላቅ ሰው የተለያዩ በዓለም የዴሞክራሲያዊ ትግል ሒደት ላይ ጉልህ አሻራ ባላቸው ሰዎች ስም የመጠራታቸው ምሥጢር አጥብቀው ሰላማዊ እና ሃይማኖተኛ ከመሆናቸውም በላይ ከእውነት ማዕቀፍ አንዲት ስንዝር እንኳን ወደ ኋላ አለማፈግፈጋቸው ነው ይኸው ሪፖርተር ጋዜጣ ማንዴላ እና ምኒልክ ስለመባላቸው ያላቸውን አስተያየት ለፕሮፌሰር አሥራት ጥያቄ አቅርቦላቸው ሁለቱም ኔልሰን ማንዴላም ሆኑ ምኒልክ በእኔ መመሰላቸው ይበዛብኛል ከእኔ አቅም በላይ ናቸው ነገር ግን ምረጥ ካልከኝ ምኒልክን እመርጣለሁ ብለው መልሰው ነበር እርግጥ ነው አጹ ምኒልክን መምረጣቸው ትክክል ነበር እንደ ፕሮፌሰር አሥራት ዓይነት ፍጹም ኢትዮጵያዊ የሆነ ሰው ከማንዴላ ይልቅ ለምኒልክ የበለጠ ቅርበትና ክብር ይኖረዋል ለዚህም ይመስላል ፕሮፌሰር አሥራት ምኒልክ መባልን የመረጡት ያልሰነበተ ነፃነት ማኅሌት መጽሔት ቅጽ ገ ቁጥር ዐ ፕሮፌሰር አሥራት ከእሥር ሲፈቱ ማንዴላ በድል ተፈቱ የሚል ርዕስ ያለው ጽሑፍ ይዞ ወጥቶ ነበር ፕሮፌሰር አሥራት ከእሥር ቤት እንደተፈቱ በፍርድ ቤቱ ዙሪያ ተኮልኩሎ መውጫቸውን ሲጠባበቅ የነበረው ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ በደስታ ስሜት ተውጦ ሰልፍ አድርጎ ነበር የሕዝቡ ስሜት በጣም የሚገርምና ለፕሮፌሰር አሥራትም ከጠበቁት በላይ ነበር የሆነው ከእሥር ቤት እንደወጡ በፍርድ ቤቱ ቅጥር ግቢ የነበረው ወፈ ሰማይ ሕዝብ ፕሮፌሰሩን ተሸክሞ ለመጨፈር ሙከራ አድርጎም ነበር ፕሮፌሰር አሥራት በወቅቱ ሕዝቡ ለእርሳቸው ሲል የሚያደርገው ሁሉ ቢገርማቸው ከቁጥጥራቸው ውጭ የሆነ እምባ ከሁለቱም ዓይኖቻቸው ይወርድ ጀመር በወቅቱ ስለ ነበረው ሁኔታ ሲያስረዱ ርእኔኳ ስወጣ ስለ ሕዝቡ ፍጹም ጨዋነትና ለሚጠብቀኝ የተከበረ ሕዝብ አጸፋውን በአክብሮት እፊቱ እጅ ነስቸ መሬቷን ለመሳለም ነበር ነገር ግን የሕዝቡ መፈንደቅ መገንፈል ጩኸት እንዲሁም አቅፎ ለመጨፈር በተደረገው ሙከራና የፖሊስ መከላከል የእምባ መቅረርና መኮብለል ክስተት ለሁኔታው ትንሹ ምላሽ ነው በአጠቃላይ ለ ቀናት በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ታስረው ያሳለፉት ፕሮፌሰር አሥራት ስለ እስሩ ሁኔታና በአጠቃላይ ስለ ክስ ቻርጃቸው አክለው ይናገራሉ ረየተከሰስኩበት የክስ ዘገባ በሕጉ መሠረት የተቀዳሚ ምርመራ ፍርድ ቤት ምርመራውን ባጠናቀቀበትና እኔን አሥር ቤት ባስገባበት ሐምሌ ቀን ጀምሮ ለሚመለከተው ፍርድ ቤት ክሱን በአሥራ አምስት ቀን ውስጥ መክፈት ነበረበት በእነዚህ ቀናት ውስጥ ክሱ ካልተከፈተ በህጉ መሠረት ክሱ ውድቅ መሆን ይገባዋል ይህ እንደዚህ ሆኖ ሳለ ያለ አግባብ እሥራቴን በማስቀጠል ለአርባ ሶስት ቀናት ልታሰር በቃሁ ክሱ አሁንም ለሚመለከተው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርቦ ክሱ ያልተሰማ ስለሆነ የእኔ በአደባባይ ስለ ክሱ መተቸት አግባብም ህጋዊም ስላልሆነ ከመተቸት እቆጠባለሁ ይህም ሆኖ በእሥር ላይ ከሰነበቱት የጎጃም ገበሬዎች ጋር በመታሰሬ ደስታየ ከፍ ያለ ስለነበር ላሰሩኝ ዳኛ ምስጋናየ ከፍ ያለ ነው ፕሮፌሰር ጨምረውም እርግጥ ነው አሁን የተለቀቅኩት በዋስ ነው ይህም በከፍተኛ ፍርድ ቤት በተረኝነት በተገኙ ዳኞች በሰጡት ውሳኔ መሠረት ነው የነፃ ፍርድ ቤት ብሎ ህወሃትኢሕአዴግ ባቋቋመው ውስጥ በዳኝነት ምሳሌነታቸው ባሳዩት እንከን የሌለው የፍርድ ሐተታ ውሳኔ የሰጡት ዳኞች መንግሥትን አስመስግኖታል እኔም በዚህ ውሳኔ መሠረት በዋስ ልለቀቅ በቅቻለሁ አብሮትም መወሰድ ያለበት ይህ ሁሉ በእግዚያብሔር ፈቃድ የተከናወነ መሆኑን ነው የዚህም ማስረጃ ውሳኔ የተሰጠው በኢትዮጵያዊው የዓመቱ የአቡነ ተክለሃይማኖት ቀን መሆኑ ነው በማለት ለአምላካቸው ምን ያክል እምነት እንዳላቸው ይገልጸሉ አክለውም የዋስ መብት ጥያቄው ሲንከባለል ጊዜ በመፍጀቱ ተገቢው ጥያቄየ ለፍርድ ቤቱ ቀርቦ በነፃ የመለቀቄና የሞራልና የሕይወት መጎሳቆል ካሳ እንዲከፈለኝ በተቀዳሚነት እንዲስተናገድ አልተቻለም እንዲሁም በደብረብርሃን ንግግር መሠረት እስካሁን ድረስ ለስድስት ወር በደንብ ያልተከሰስኩ በመሆኔ በማዕከላዊ የፖሊስ ምርመራ መሥሪያ ቤት ሃምሳ ሺህ ብርና ከሐገር እንዳልወጣ ያስጠሩኝ ዋስ ጉዳይ እስከ አሁን ተንጠልጥሎ በመቅረቱ ዋሴ እየተንጋላቱ ነው ይህ የአሁኑ ዋስ መጥራት በተጨማሪ ነው ማለት ነው የወደፊቱንም በዚሁ መሠረት ስቃኘው ወደ ማዕከላዊ የፖሊስ ምርመራ በተጠራውና ጥያቄዎች በቀረቡልኝ ቁጥር ዋስ መጥራት ስለሚኖርብኝ የዋሶች ባንክ ማደራጀት ሳይኖርብኝ የሚቀር አይመስለኝም ይላሉ ከእሥር እንደተፈቱ ለማኅሌት መጽሔት መስከረም ዓም በሰጡት ቃለ ምልልስ በነገራችን ላይ ፕሮፌሰር አስራት ለተደጋጋሚ ጊዜ ለእስር ሲዳረጉ ዋስ እየሆኑ ያስፈቷቸው አቶ ገብረጻድቅ ኃይለማርያም የተባሉ ሰው ናቸው አቶ ገብረጻድቅ ኃይለማርያም የመዐሕድ መስራችና የፕሮፌሰር የቅርብ ሰው ነበሩ ለዚህ ውለታቸውም ከፕሮፌሰር አስራት የምስጋና ደብዳቤ አግኝተዋል ለዋስትና መኪናቸውን ያስያዙት አቶ ገብረጻድቅ መኪናቸውን ያስለቀቋት ከብዙ ዓመት ክርክር በኋላ ነው ፕሮፌሰር አሥራት በዚህ ሳያበቁ ለቃለ መጠይቅ ወደ ማዕከላዊ በተጠራሁ ቁጥር ተደጋግሞ ከኃላፊዎቹ የሚቀርብልኝ ማሳሰቢያ ከመዐሕድ ድርጅት እንድወጣ ነው እንዲያውም ምክትል ሹሙ ሁለት ጊዜ ለብቻየ በማነጋገር ይህንን ባላደርግ በሕይወቴ እንደፈረድኩ እንድቆጥረው መሆኑን በጥብቅ አሳስበውኛል ከዚህ ውጭ ማዕከሉ በአጠቃላይ በጥሩ ሁኔታ አስተናግደውኛል የእሥር ቤቱም አያያዝ በእሥር ቤት ደረጃና በሐገራችን ሁኔታ ሲታይ በጣም ጥሩ ነው ሲሉ አጠቃላይ ስለ እሥር ቤቱ ሁኔታ ገልጸው ነበር በዚያው ሰሞን ከአሜሪካ ኮንግረስ አባላት ጋር በመወያየት በሰጡት መረጃ ነው የታሰሩት ተብሎም ይወራ ነበር ከአሜሪካ የኮንግረስ አባልና የአፍሪካ ኮሚቴ ሊቀመንበር ከነበሩት ከፍሎሪዳው ዴሞክራት ሐሪ ጆንስተን ጋር ተገኛኝተው በማውራታቸው ነው የታሰሩት የሚሉ ሰዎች ቢኖሩም ፕሮፌሰር አሥራት ግን እሥራታቸው ከእኝህ የኮንግረስ አባል ጋር እንደማይገናኝ ያምናሉ ረየአሜሪካን ኮንግረስ አባላት ለማነጋገር የቻልኩት በስንት ችግር ነው ያነጋገርኳቸው ዓርብ ጠዋት ሲሆን በዚያው ሳምንት ከማክሰኞ ጀምሮ እፈለግ እንደነበር በኋላ ልረዳ ችያለሁ ለኮንግረሱ አባላት በድርጅቱ ስም ያቀረብኩት ማስረጃ የኢትዮጵያን ተጨባጭ ሁኔታ በመዘርዘር የሚገልጽና መዐሕድ ሰላማዊ ተግባሩን ለማከናወን ያልቻለበትን መረጃዎችና የታሰሩበትንና የሞቱበትን ዝርዝር የሚያመለክት ነበር ሆኖም የውይይቱም ጊዜ የጠፋው እላይ የተጠቀሱትን በማብራራትና ጠበቃ ሆነው ከቆሙት ከአሜሪካው አምባሳደር ጋር በመሟገት ነበር ይህም ለጊዜውም ቢሆን ጥሩ ውጤት አምጥቷል ከዚያ በኋላ ባጋጠመኝና በገመትኩት መሠረት ውይይቱን እንዳላከናውን ተሞክሮ እንደሆነ እንጅ የታሰርኩት ባቀረብኩት መረጃዎች መረሠት አልነበረም ሲሉ ከአሜሪካ ኮንግረስ ጋር ባወሩት መረጃ መሠረት እንዳልታሰሩ ያስረዳሉ ማኅሌት ቅጽ ቁጥር ዓም ያኔ አሜሪካኖቹ ኢሕአዴጎችን ወጣት የአፍሪካ ዴሞክራት መሪዎች ብለው አሞካሽተው አይወጣላቸውም ነበርና ፕሮፌሰሩ ከአሜሪካኖቹ ጋር እንዳይገናኙ የተፈለገበት ዋናው ምክንያት ገመናቸው እንዳይጋለጥ ከመፍራት ሊሆን ይችላል ብሎ መገመት ይቻላል ፕሮፌሰር አሥራትም የሚገምቱትና የሚያምኑት እንደዚያ ብለው ነው ምንም እንኳን ፕሮፌሰር አሥራት ለጊዜውም ቢሆን ከእሥር ቢፈቱም ከአሰልቹ የፍርድ ቤት ምልልስ ግን ሊላቀቁ እልቻሉም ነበር በሳምንት ሁለትና ሶስት ጊዜ ወደ ፍርድ ቤት እየተጠሩ ሲመላለሱ እንዲከርሙ ተደርጎ ነበር ይህንን አሰልች የፍርድ ቤት ምልልስ ነው ያልሰነበተ ነፃነት ለማለት የተገደድኩት የጅሚ ካርተር ሽምግልና በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳይ ረዳት ሚኒስትር ሚስተር ጆርጅ መስ አዲስ አበባ መጥተው በነበረበት ወቅት ከመዐሕድ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር አሥራት ጋር ውይይት አድርገው ነበር ፕሮፌሰር አሥራትና ጆርጅ መስ ያደረጉት ንግግር ዐ ደቂቃ የፈጀ ሲሆን የወቅቱን የኢትዮጵያን ሁኔታ የዳሰሰ እንደነበርም ለአስተባባሪ ኮሚቴው በሰጡት ልዩ መግለጫ ሊታወቅ ችሏል በዚያው ሰሞን የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሚስተር ጂሚ ካርተር በኢትዮጵያ ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲዎችን አሜሪካ በሚገኘው የካርተር ማዕከል ለማነጋገርና ለማወያየት ቀጠሮ ይዘው ነበር ከየካቲት እስከ ፀ እኤአ የሚካሄደው የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች ስብሰባ ላይ ፕሮፌሰር አሥራት እንዲገኙ በሚስ ሲዛን ፖልማር በኩል ፋክስ ተደርጎላቸውም ነበር ፕሮፌሰር አሥራት ስብሰባው ላይ የማይገኙ መሆናቸውን በዝርዝር ጽፈው መልሰውላቸዋል ረጅሙና ጥልቅ ትንታኔን የያዘው የፕሮፌሰር አሥራት ደብዳቤ ለታሪክ ሰነድነትና ለተጨማሪ ጥናት ሊያገለግል ይችላል በሚል ሙሉውን ቃል አትሜዋለሁ ለክቡር ሚስተር ጂሚ ካርተር የኢምሪ ዩንቨርሲቲ የካርተር ማዕከል አትላንታ ጆርጂያ ክቡር ሆይ በቅድሚያ እኤአ ጥር ቀን በክቡርነትዎ ተጽፎ በሚስ ሱዛን ፖልማር ፋክስ ስለተደረገልኝ ደብዳቤ ምስጋናየን ልገልጽልዎ እወዳለሁ ይህ እኤአ ከየካቲት ፖ እስከ በካርተር ማዕከል ሊደረግ በታቀደው የተቃዋሚ ቡድኖች ስብሰባ ላይ እንድገኝ የክቡርነትዎን ጥሪ የያዘ ደብዳቤ እንደደረሰኝ የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት መዐሕድን ማዕከላዊ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን በአስቸኳይ እንዲሰበሰቡ በማድረግ ደብዳቤዎ ለኮሚቴው ቀርቦ ተገቢው ውይይት ተካሂዷል የሥራ አስፈጻሚው ኮሚቴ አባላትም ድርጅታችን ከላይ በተጠቀሰው ስብስባ ላይ እንዲሳተፍ በክቡርነትዎ በመጋበዙ የተሰማቸውን ጥልቅ ምስጋና እንድገልጽልዎ አሳስበውኛል ክቡርነትዎ የታላቋ አገር የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ከነበሩበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያን ጉዳዮች በተመለከተ ሲጫዎቱ የቆዩትን ሚና ጠንቅቀን እናውቃለን በኤርትራ የነበረው ግጭት በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ለማድረግ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ያሳዩትን ጥረትም አንዘነጋውም በተጨማሪ በመላው የአፍሪካ አህጉር ውስጥ ለሕዝቦች ጤንነት መሻሻልና ለልማት ያለዎትን በጎ ምኞትም ሆነ ያደረጉትን አስተዋጽኦ የማያደንቅ ሰው ያለ አይመስለኝም ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባረዎና ስለ ሰብዓዊ መብቶች ያለዎት አመለካከት በዓለም ተናኝቶ የመንግስታት ምንነት መለኪያ በመሆኑ በታሪክ መዛግብት ውስጥ ልዩ ምዕራፍ የተሰጥዎት ታላቅ ሰው ነዎት ተቃዋሚ ቡድኖችን ሰብስበው እንዲወያዩ ለማድረግ ያነሳሳዎትም ይኸው ለበጎ ምግባር መሰለፍዎንና ስለ ኢትዮጵያ ጉዳዮች ባለዎት የረጅም ጊዜ ፍላጎትና ግንዛቤ መሆናቸውን አንጠራጠርም የክቡርነትዎን ትክክለኛ ማንነት መረዳታችንም በአትላንታ ሊደረግ ስለታቀደው ስብሰባም ሆነ ስለ አገራችን የፖለቲካ ሁኔታ ያለንን አመለካከት በግልጽ እንድንጽፍልዎ አደፋፍሮናል መዐሕድ የተቋቋመው የኢትዮጵያ የሽግግር መንግሥት በተቋቋመ በሰባተኛው ወር እኤአ ጥር ቀን ዓም ነው የተቋቋመውም በወቅቱ በአማራው ሕዝብ ላይ ይፈጸሙ የነበሩ ኢሰብዓዊ ድርጊቶችን ለዓለም ሕዝብ ለማሳዎቅና አማራው እንደ ሌሎች ጎሳዎች ሁሉ መብቱ የሚጠበቅበትን መንገድ ለመጥረግ ነው መዐሕድ የተቋቋመው የዚህን ብዛቱ የአጠቃላዩን የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዐ እስከ በመቶ የሚሆነው ጎሳ መሰረታዊ ስብዓዊ መብቶች ለማስከበር እንጅ በተወካዮች ምክር ቤት ወንበር ለማግኘት አይደለም በሌላ አነጋገር መዐሕድ የተቋቋመውም ሆነ አሁን በመፍጨርጨር ላይ ያለው በአማራው ሕዝብ ላይ የሚፈጸመውን ጭፍጨፋ በሰላማዊ መንገድ ለመከላከል ብቻ ነው አንዳንዶች እንደሚሉት ሳይሆን መዐሕድ ተግባሩን የሚያከናነው ሙሉ በሙሉ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ሲሆን ተግባሩን ለማከናዎን ያመቸውም ዘንድ አማራ ዎች በሚኖሩባቸው ክፍላተ ሐገር ወይም ክልሎች ሁሉ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶችን መክፈት ይፈልጋል ዋናው ተግባሩም በእነዚህ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶቹ አማካይነት ለሥራው የሚያሹትን መረጃዎች በመሰብሰብና የተለያዩ ጎሳዎችም ሆኑ የተለያዩ ሃይማኖቶች ተከታዮች እንደተለመደው ተሳስበውና ተግባብተው መኖር እንደሚሻላቸው ለማስተማር ነው ሌላው ተግባሩ ከቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶቹ የሚደርሱትን መረጃዎች ፈርጅ በማስያዝ ለዓለም አቀፍ ሕብረተሰብ ማሳወቅ ነው በዚህ መንገድ ያገኘናቸውን ልዩ ልዩ መረጃዎች በተደጋጋሚ ኒውዮርክ በሚገኘው ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤታችን በኩል ለካርተር ማዕከል ማሳወቃችንም አይዘነጋም ዓላማችንና ተግባሮቻችን ከዚህ በላይ የተገለጹት ብቻ ቢሆኑም የኢትዮጵያ የሽግግር መንግሥት የዲሞክራሲንና የሰብዓዊ መብቶች መርሆች በመጻረር ገና ከጅምሩ ድርጅታችንን በክፉ ዓይኑ አየው ሰላምም ነሳው ድርጅታችንም በሰላማዊ መንገድ ብቻ የጠብመንጃውን ኃይል መቋቋም ስላቃተው አብዛኞቹ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶቹ ሊዘጉ ቻሉ በተለይ ባለፈው ዓመት የሽግግር መንግሥቱ ባለ በሌለ ኃይሉ በመጠቀም በመዐሕድ ላይ የከፈተውን ዘመቻ አጠናክሯል የዘመቻው ዓላማ እንደተረዳነው መዐሕድን ማጥፋት ሲሆን ይኸንንም እውን ለማድረግ የተነሳው በብቸኝነት በያዘው መገናኛ ብዙሃንና ባለው የገንዘብ ኃይል በመጠቀም በደርጅቱ አሠራር ላይ አስተዳደራዊ ችግሮችን በመፍጠር አባሎቻችንን በማሰር በሆነ ባልሆነው ፍርድ ቤት በማመላለስና ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ በማንገላታት ነው ለማብራራትም ያህል የሚከተሉትን እንጠቅሳለን አማራው በብዛት ከማንኛውም ጎሳ ከፍ ብሎ ያለ ቢሆንም ቅሉ በተወካዮች ምክር ቤት አንድ ወንበር እንኳን ሳይሰጠው በመቅረቱ ቅሬታ አሰምቶ አያውቅም አገሪቱ ጎሳን መሠረት በማድረግ በክልሎች ስትከፋፈል ሌሎች ክልሎች በራሳቸው ተወላጅ መሪነት እንዲተዳደሩ ተደርጓል አማራው ግን የሚመራው በኤርትራዊ ተወላጅ ከመሆኑም በላይ በክልሉ ያሉት ቁልፍ ቁልፍ የሥልጣን ቦታዎች የተያዙት እንዲሁ በኤርትራዊያንና በትግራይ ተወላጆች ነው አማራዎች ከአብዛኞቹ የመንግሥት ቁልፍ ቦታዎች ተባረው በምትካቸው ኤርትራዊያንና የትግራይ ተወላጆች ተሾመዋል ለምሳሌ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከተባረሩት ምርጥ መምሕራን መካከል በመቶው አማራዎች ናቸው ለመምህራኑ ያለ ሥራ መፈለጊያ ወይም ያለ ካሳ መባረር የተሰጠው ምክንያት የዩኒቨርሲቲውን የትምሕርት ጥራት ለማሻሻል ነው የሚል ሲሆን ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት የነበሩትን አማራዎች ከሥልጣናቸው ለማውረድ የተሰጠው ምክንያት ደግሞ የዓለም ባንክና አይኤምኤፍ ለአንድ አገር የኢኮኖሚ ዕድገት ወሳኝ ነው ብለው ያወጡት የመዋቅር ለውጥ ስትራክቸራል አጀስትመንት መሠረት ሠራተኞችን ለመቀነስ በማስፈለጉ ነው እየተባለ ነው የተዘጉትን የመዐሕድ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶችን እንደገና ለመክፈትም ሆነ አዳዲስ ጽሕፈት ቤቶችን በተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች ውስጥ ለመክፈት የተደረገው ጥረት በሽግግር መንግስቱ ወታደሮችና ፀጥታ ጠባቂዎች ዛቻና አስጊ ድርጊቶች ከሽፎአል የሽግግር መንግስቱ በብቸኝነት በሚጠቀምበት መገናኛ ብዙሃን መዐሕድን በየዕለቱ ሲያወግዝ መዐሕድ በበኩሉ ምላሽ ሊሰጥበትና ስለ እርሱ የሚባለው ሁሉ ከእውነት የራቀ መሆኑን ለሕዝብ ሊያስረዳ እንዳይችል ተደርጓል ብብተለይ በገጠር አካባቢዎች የመዐሕድ ፕሮግራም በእጁ የተገኘበት ማንኛውም ሰው ከግርፋት እስከ ሞት ሊደርስ የሚችል ቅጣት ይጠብቀዋል የመዐሕድ አመራር አባላት በተደጋጋሚ ስለሚከሰሱ የመንግሥት ሠራተኞች ከሆኑ ከሥራ ስለሚባረሩና ስለሚዛትባቸው ድርጅቱን ትተው እስከ መውጣት የደረሱበት ጊዜ አለ ለማረጋገጫ ያህል በምሥራቅ ኢትዮጵያ የመዐህድ ተወካይ የነበሩት ግለሰብ እኤአ መስከረም ቀን ዓም ድሬዳዋ ከሚገኘው ቤታቸው በኢሕአዴግ ወታደሮች ተወስደዋል እስካሁን ያሉበት ቦታም አይታወቅም የመዐሕድ ዋና ፀሐፊ ሻለቃ ጌታቸው መንግስቴ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ከታሰሩ አንድ ዓመት ሆኗቸዋል በሰሜን ሸዋ ልዩ ስሙ ጅሩ በተባለው አካባቢ የሚገኘው ቅርንጫፍ ጽቤታችን ጸሐፊ የነበሩት አቶ ባዘዘው ሞገስ ማታ ወደ ቤታቸው ሲሔዱ ተገድለዋል የድርጅታችን አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አቶ ሲለሽ ሙላት ከታሰሩ ስድስት ወር ሆኖአቸዋል የዞን ከፍተኛው ፍርድ ቤት በዋስ እንዲፈቱ ቢወስንም ውሳኔው ተፈጻሚነት ሊያገኝ አልቻለም የሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት ኃላፊያችን ኮሎኔል ጌታሁን እጅጉ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ከታሰሩ ሁለት ወር ሆኗቸዋል በተረፉት የመዐሕድ ቅርንጫፎች ውስጥ የሚሠሩ ሠራተኞቻችን አሁንም የሚኖሩት በከፍተኛ ሥጋትና መንገላታት ነው ፖ የመዐሕድ ፕሬዚዳንት ባለፈው ዓመት በሆነ ባልሆነው ትፈለጋለህ እየተባሉ ፍርድ ቤት ሲመላለሱ ከመቆየታቸውም በላይ ለ ቀናት ከታሠሩ በኋላ ለፍትሕ ቆራጥ ዳኞች ውሳኔ መሠረት ሊፈቱ ችለዋል እንዲሁም ከአገር ላለመውጣት ዋስ እንዲጠሩ ተደርጓል ይህ ሁሉ ሲፈጸም የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ በአዲስ አበባ ክልል ብቻ በሚሰራጩ የነፃ ጋዜጦች ሥርጭት በመታለል የኢትዮጵያን ተጨባጭ ሁኔታ አውቆ ችላ በማለትና የሚፈልጉትን ብቻ በማንጸባረቅ ላይ ይገኛል በአማርኛ ቋንቋ እንደሚባለው አውቆ የተኛን ቢቀሰቅሱትም አይነሳም ይባላል በዚህ መሠረት ከኢትዮጵያ ውጭ የሐገራችን ሁኔታ እንዲታወቅ የሚደረገው በሚከተሉት መልኩ ነው ለሌሎች የአፍሪካ አገሮች በምሳሌነት የሚያገለግል የዴሞክራሲ ሥርዓት መስፈኑን አልፎ አልፎ ስህተቶች ቢከሰቱም ከሞላ ጎደል መሠረታዊ ሰብዓዊ መብቶች እንደሚከበሩ የአገሪቱ ኢኮኖሚ ሰባት በመቶ ዓመታዊ እድገት እንዳሳየ አማራዎች የሚጮሁት ሥልጣን ከእጃቸው ስለወጣ እንደሆነና መዐሕድ የተቋቋመውም የቀድሞውን ሥርዓት ለማስመለስ ነው በማለት ያስነግራል የዚህም አሳሳች ማስረጃ ባለፈው መንግሥት በአብዛኛው ጥቅሙ የተገፈፈበትና ያለቀው አማራው መሆኑ የታወቀ ነው በካርተር ማዕከል ሊደረግ ወደታቀደው ስብሰባ ብንመለስ ኢሕአዴግ በዚህ ስብሰባ ላይ የማይገኝ መሆኑ አሳዛኝ ነው ከዚህ በላይ እንደገለጸነው እንደሚባለው ሳይሆን ድርጅታችን የአማራው ሕዝብ የተነፈገውን ከሌሎች ጎሳዎች ጋር በእኩልነት መኖር ተከብሮለት በሰላም የሚኖርበት ሰብዓዊ መብቶቹ የተከበሩበት እንዲሁም ደግሞ በቃል ብቻ ሳይሆን በተግባር ዲሞክራሲያዊ የሆነች ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ሁሉ ተካፋይ ለመሆን ታጥቆ የተነሳ ድርጅት ነው ለፖለቲካ ሥልጣን ፈላጊነት ሳይሆን በሐገሪቷ ለመኖር የተከለከለውን የአማራ ሕዝብ የመኖር መብት እንዲጠበቅ ነው ከማናቸውም የተቃዋሚ ቡድን ጋር ጥል የሌለን ስለሆነ ከእነዚህ ድርጅቶች ጋር የእንደራደር ነገር ሊኖር አይችልም በእኛ አስተያት አሳሳቢና አጣዳፊ የሆነው ጉዳይ በኢሕአዴግ የሚከናወኑት አፍራሽ ጉዳዮች መፍትሔ እንዲያገኙ ማድረጉ ነው ከቀሩት ቡድኖች ጋርማ በቅርቡ አዲስ አበባ ላይ ተካሂዶ በነበረው የሰላምና የእርቅ ጉባኤ ላይም ተሰብስበን ያለ ምንም ችግር የጋራ ውሳኔዎች ደርሰናል በእኛ እምነት በቶሎ ሊፈታ የሚገባው የኢትዮጵያ ችግር የኢሕአዴግ አምባገነንነት ነው ኢሕአዴግ ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረበት ቀን ጀምሮ በቻርተሩ እየማለ በጠብመንጃ ሲገዛ ቆይቷል አሁን ቻርተሩ ሰጥቶት የነበረው ረሕጋዊነትም አክትሟል በበኩላችን ያለ ምንም አይዞህ ባይ የቀረውንና ለጠባቦች የጥላቻ ፍላጻ የተጋለጠውን የአማራ ሕዝብ ሰቆቃ ለዓለም ኅብረተሰብ ለማሰማትና በተለያዩ ሰላማዊ መንገዶች ለመብቱ ለመታገል የተቻለንን ያህል ሞክረናል ወደፊትም እንሞክራለን ይሁን እንጅ ከላይ እንደጠቀስነው ከአማራ ሕዝብ ጋር ያለንን ግንኙነት የጠብመንጃ መጋረጃ ውሱን አድርጎብናል ስለዚህም በአትላንታው ስብሰባ ላይ መገኘት የሚያስችል የአማራው ውክልና አለን ማለት አንደፍርም መዐሕድ ይህ ውክልና ቢኖረው እንኳን አብዛኞቹ የድርጅቱ የአመራር አባላት እሥር ቤት ስለሆኑና የድርጅቱም ፕሬዚዳንት ከአገር የመውጣት መብታቸው በኢሕአዴግ ስለተገፈፈና በሳምንት ከሁለት እስከ ሶስት ጊዜ ፍርድ ቤት ስለሚመላለሱ ወደ አትላንታ ተወካይ ለመላክ አልተቻለም ማንኛውም ወደፊት የሚታቀድ ውይይት በመጨረሻ ማስገኘት የሚገባው ክስተቶች ይኖራሉ እነኝህም የአስተዳደር ሚዛናዊነት የኢትዮጵያኖችን ሁሉ መብትና እኩልነት መጠበቅና የሐገሪቷን ሉዓላዊነት ማስከበር ማካተት ይኖርበታል በአሁኑ ወቅት ተቃዋሚ ኃይሎች የተባሉት ለእነኝህ ሁሉ መዛባት ተጠያቂ ሊሆኑ አይችሉም ተጠያቂው የኢሕአዴግ መንግሥት መሆኑ ታውቆ የሚደግፉት ኃይሎች እንዲታረም ቢረዱ ታላቅ አስተዋጽኦ ይሆናል በዚህ መሠረት ለመገኘት ብንችል እንኳ የእኛ ከተቃዋሚ ኃይሎች ጋር መሰብሰብ የሚያስገኘው ውጤት ይኖራል ብለን አናምንም ስለዚህ በአትላንታ በታቀደው ስብሰባ ለመገኘት ባለመቻላችን ይቅርታ እንዲያደርጉልን እናሳውቃለን ከአክብሮት ሰላምታ ጋር ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት ፕሬዚዳንት እኤአ የካቲት ቀን ሚስተር ሪቻርድ ጆሴፍ ለአፍሪካ ግዛት ተባባሪ ሹም የኤምሮይ ዩንቨርሲቲ የካርተር ማዕከል አትላንታ ኦርጂያ ውድ ሚስተር ጆሴፍ እኤአ በጥር ቀን የተጻፈውን የሁለተኛ ጥሪ ደብዳዳዎን በፋክስ ስለላኩልኝ አመሰግናለሁ ይህ ደብዳቤ ለመዐሕድ የማዕከላዊ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ቀርቦ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ውይይት ተካሄዶበታል በዚህ ደብዳቤዎ የአትላንታውን ስብሰባ የኢትዮጵያ የተቃውሞ ቡድኖች የጋራ ስብሰባ አድርጌ መውሰዴን ያልተስማሙበት መሆኑን ገልጸውልኛል እኔም በበኩሌ ላሳስብዎ የምፈልገው ይህ የእኔ ፈጠራ ሳይሆን እኤአ በጥር ቀን በፕሬዚዳንት ካርተር ተፈርሞ የተጻፈልኝ ደብዳቤ የሚያመለክተው ይህ ሲሆን እኔም የጠቀስኩት ይህንኑ መሠረት በማድረግ መሆኑን ላረጋግጥልዎ እወዳለሁ እንዲሁም አሁን ደግሞ ከእርስዎ ደብዳቤ እንደተረዳነው የአትላንታው ስብሰባ ዋናው ዓላማ ፕሬዚዳንት ካርተር የኢትዮጵያን ድርጅቶች ያላቸውን ሃሳብና አስተያየት ራሳቸው ከእነርሱ ለመረዳት እንዲያስችላቸው መሆኑን አረጋግጠውልናል ፕሬዚዳንት ካርተር ባለፈው ነሐሴ ኢትዮጵያን በጎበኙበት ወቅት ጠቅላላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ችግሩን ሁሉ ይገነዘቡልኛል በማለት በከፍተኛ ምኞት ይጠባበቅ ነበር እንዲሁም በተመሳሳይ ሁናቴ መዐሕድም የውይይት ዕድል ተሰጥቶት የሃገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታና የአማራውን ዕድል ለማስረዳት ተሰናድቶ ሲጠብቅ ምኞቱ ሳይሳካ ቀርቷል። የእሥር አያያዛቸው ሁኔታ ርእንኳን ከድርጅቱ ጋር ከዘመዶቸ ጋር እንኳን አልገናኝም ከሕይወት በሙሉ የተቆረጥኩ ሰው ነኝ አንድ እሥር ቤት ብቻ አይደለም ያለሁት በተጨማሪ በልዩ ልዩ መንገድ የታሰርኩ ነኝ እንግሊዞች ሶሊተሪ ኮንፋይንመንት ነው የሚሉት ለብቻ የተገለለ እስረኝነትን ላይ ነው ያለሁት በመስኮት የምትገባው አየር እንኳን በስንት መከራ ነው ቅርብ ቀን የተፈቀደችልኝ ሪፖርተር ጥቅምት ቀን ዓም ይህን የሚሉት ፕሮፌሰር አሥራት ናቸው ከፍታብሔር ወንጀለኞች ጋር ለብቻ የታሰሩት ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ለብዙዎች የሚፈቀደውን የመንገድ አልጋ እንኳን እንዳይገባላቸው ተከልክለው ድንጋይ ላይ እንዲያርፉ ነበር የተደረገው በወቅቱ ከጓደኞቻቸው እና ከሌሎች የፖለቲካ ታሳሪዎች ጋር እንዳይገናኙ በሚል በጊዜው የደርግ አመራሮች ሁሉ በዚያው እሥር ቤት ነበር የሚገኙትን ከፀዐ በላይ ከሚሆኑ የፍታብሔር እስረኞች ሌባና ሙሰኛ ጋርን በአንድ ክፍል ታጭቀወው በአንድ ሽንት ቤት እየተጠቀሙ እንዲያሳልፉ ነበር የተደረገው ፕሮፌሰር አሥራት ታስረው በነበሩበት ወቅት ከፍታ ብሔር እስረኞች ጋር ከመታሰራቸውም በላይ መጽሐፍት እንዳይገባላቸውና ጠያቂም እንዳይጎበኛቸው ተደርጎ እንደ ነበር ዶክተር አሰፋ ነጋሽ ጽፈዋል ዶክተር አሰፋ ነጋሽ ተፈራ አስማረ የተባለ ከፕሮፌሰር አሥራት ጋር ከርቸሌ ውስጥ ለሶስት አመታት ታሰሮ የነበረን ሰው አነጋግረው እንደጻፉት ከሆነ ከሌሎች እስረኞች በተለየ መልኩ ፕሮፌሰር አሥራት በወዳጅ ዘመድ የሚጠየቁት በሁለት ሳምንት አንዴ ሲሆን የግንኙነት ሰዓቱም ከዐ ደቂቃ አይበልጥም ነበር ዶክተር አሳፋ አክለውም መጽሐፍ ለማስገባት እንኳን ይቸገሩ እንደነበር ገልጸዋል ቢሆንም ግን ኢትዮጵያውያን ትብብራቸውን አልነፈጓቸውም ነበር እንደ ሐገር መሪ ነበር የሚንከባከቧቸው ሲሉ አትተዋል በዚህ መልኩ የተያዙት ፕሮፌሰር አሥራት ቀደም ብሎ ታክመውት የነበረው የልብ በሽታ እያደገ መጣ በወቅቱ የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ መንግሥትን ቢጠይቁም በአፋጣኝ ባለመታከማቸው የበሽታ መጫዎቻ ሆኑ ስንቶችን ከተጣባቸው ደዌ የፈወሰው እጃቸው ለራሳቸው እንኳን የማይበቃ ሆነ በጠባቧ እሥር ቤት የሕክምና ሳይንቲስቱ ሕክምና አጥተው ተቸገሩ ሲያሳስዱት የኖሩት በሽታ አሁን በግላጭ ያገኛቸው መሰለ ስለ ሁኔታው የሪፖርተር ጋዜጠኛ ባነጋራቸው ወቅት የሚከተለውን ተናግረው ነበር እሥር ቤት ሆኘ አንድ ቀን ጠዋት ስነሳ ማየት አልቻልኩም በዚህ የተፈጠሩ ምክንያቶች አሉ እንግዲህ ይህንን መርምሮ የመሻሻል ምልክቱን መከታተል ያሥፈልጋል የሐገራችን ሁኔታ ሆኖ መሳሪያዎች የሉም ሐኪሞቹም ይህን አሳውቀዋል ሐኪሞቹ ከአቅማችን በላይ ነው ብለው አረጋግጠው ለሚመለከተው ሪፖርትም አድርገዋል ሆስፒታሉም ከአቅሙ በላይ ስለሆነ ሊያክመኝ አልቻለም በእግዚያሄር ሕክምና ላይ ነው ያለሁት ስለ አለብኝ ሕመም መመርመሪያ መሳሪያ የለም ሌላ ሌላ ነገር በተጓዳኝ ያለውን ይረዱኛል እንጅ ዋናው ለገባሁበት ጉዳይ ምርመራ መሳሪያዎች በሙሉ የሉም እንኳን ሕይወቴን ሙሉ ለዚህ ሕዝብ ሳገለግል ለቆየው ቀርቶ ሌላውም ተገቢ ሕክምና ማግኘት አለበት ቀደም ብየ እንደገለጽኩት ዛሬ የተኛሁበት ሆስፒታል ከሥር መሰረቱ አንስቶ አስተዋጽኦ ያደረኩበት ነው የሰው ልጅ ትራጀዲ ነው ያን ያህል በደከምኩበት ሆስፒታል ከመተኛት በቀር ሌላ ነገር ላገኝ አልቻልኩም እዚህ ያሉት ሐኪሞች የተቻላቸውን ሁሉ አድርገዋል ረርየሐገሬ ሰው ይታደሉታል እንጅ አይታገሉትም ይላል በጠና ታምሜ ሆስፒታል ለመግባት ስንት እንደወሰደብኝ ታውቃለህ ትልቁን ነገር እንተወውና ትንጂን ነገር ልንገርህ ብየ ነው ማየት ተስኖኝ ሁለት ስፔሻሊስቶች አይተውኝ በአስቸኳይ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል መግባት አለበት ተብየ ሳምንት ነው የወሰደብኝ እየታወርኩ ስሄድ እረፍቷን ማግኘት እንኳን አዳጋች ሆኖ ነው የቆየብችኝ ፕሮፌሰር አሥራት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ጥቅምት ዓም ፕሮፌሰር አሥራት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ጥቅምት ገ ዓም ከሪፖርተር ጋር ቃለ ምልልስ ሲያደርጉ ፕሮፌሰር አሥራት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በከፍተኛ ጥበቃ ሥር ከመተኛት ያለፈ እዚህ ግባ የሚባል ሕክምና ሳይደረግላቸው በመቆየቱ በከፍተኛ ሁኔታ እየተዳከሙ መጡ የሐኪሞቹ ቡድን ወደ ውጭ ሐገር ሄደው እንዲታከሙ ብሎ ቢጽፍም መንግሥት ተብየው አሻፈረኝ ሲል ትዕዛዙን ለማስተናገድ ፈቃደኛ ሳይሆን ቀረ አምነስቲ ኢንተርናሽናልን ጨምሮ በዓለም ያሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማትና ኢትዮጵያዊያን ፕሮፌሰሩ ወደ ውጭ ሄደው እንዲታከሙ መንግሥትን ወተወቱ በመጨረሻም ከፍተኛ ከሆነ እልህ አስጨራሽ ትግል በኋላ ውጭ አገር ሄደው ይሙቱ በሚመሥል ሁኔታ ወደ እንግሊዝ ሐገር እንዲጓዙ ተደረገ እኝህ መተኪያ የሌላቸው ድንቅ ሐኪም በመሰረቱት ሆስፒታል ውስጥ የበሽታ መጫዎቻ ሆነው ወጡ በወቅቱ አምነስቲ ኢንርናሽናል መግለጫ አውጥቶ ነበር አምነስቲ ቀደም ብሎ የህሊና እስረኛ ሲላቸው «በፍርድ ሂደቱ ወቅት አንዳችም አሳማኝ መረጃ ሳይቀርብባቸው በመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት መሪነት ነውጥ አልባ ትግል በማራመዳቸው ብቻ ለእሥር ተዳርገው ቆይተዋል ሲል አስፍሮ ነበር አምኒስቲ ኢንተርናሽናል ርልበጠበፅኗሃ በፀበበ በመጨረሻም እኤአ ታህሳስ ዓም የኢትዮጵያ መንግሥት ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ወደ ውጭ ሄደው ሕክምና እንዲያገኙ ፈቅዷል ይህም አሥራት በጤና ችግር ምክንያት ፍርድ ቤት ሊቀርቡ አይችሉም በሚል አቃቤ ሕግ እንደገና ያቀረበባቸውን ክስ ውድቅ ማድረጉን ተከትሎ የመጣ ውሳኔ ነው ፕሮፌሰር አሥራት ከ ዓም ጀምሮ የፖለቲካ እስረኛ የነበሩ ሲሆን ለአንድ ዓመት ያህል ሆስፒታል ገብተዋል ለዘጠኝ ቀናት ያህል ደግሞ የልብ ድክመት ስላጋጠማቸው ለከፍተኛ የሕክምና ክትትል በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ቆይተዋል በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሕክምና ያደርጉላቸው የነበሩት ዶክተሮች እንደገለጹት የፕሮፌሰር አሥራት የጤና ሁኔታ ለህይወታቸው አስጊና የመዳናቸው ዕድልም አነስተኛ ሆኗል አሥራት ከሶስት ቀናት የሎንደን ሆስፒታል አሥራት ለንደን በሕክምና ላይ እያሉ ታህሳስ ዓም ቆይታ በኋላ አሜሪካ ይኖር ከነበረው ልጃቸውና ሐኪማቸው ጋር ወደ ሆስተን አሜሪካ አመሩ አሥራት አሜሪካ ሄደው ከዓመታት በፊት የልብ ሕክምና በተከታተሉበት ሆስፒታል እንደገና በመግባት ሕክምና እያደረጉ ነበር ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ በቅርቡ አምኒስቲ ኢንተርናሽናል የህሊና እሥር ሲል የጠራውን አምስት ዓመት የእሥር ጊዜያቸውን ጨርሰው መውጣታቸው ሲሆን በፍርድ ሂደቱ ወቅት አንዳችም አሳማኝ መረጃ ሳይቀርብባቸው በመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት መሪነት ነውጥ አልባ ትግል በማራመዳቸው ብቻ ለእሥር ተዳርገው ቆይተዋል አሥራት በለንደን የቀናት ቆይታቸው ብዙዎች የጎበቿቸው ሲሆን ሕክምና ሲያደርጉም በጥሩ ሁኔታ ላይ ነበሩ ፕሮፌሰር አሥራት የዓይን ብርሃን እይታቸው ባይሻላቸውም ከስኳር በሽታቸው ግን ማገገም ችለዋል አምኒስቲ ኢንተርናሽናል አስከፊውን የጤና ሁኔታቸውን በማስመልከት ተቆርቋሪነቱን ስለገለጸና ሕክምና እንዲያገኙ ዘመቻ ስላደረገላቸው አመስግነዋል የአምኒስቲ እገዛ ባይታከልበት ኖሮ አሥራት ስላሉበት ሁኔታ እንዳይታወቅ ይጥሩ በነበሩት ጠባቂዎቻቸው ተግባር ምክንያት ዲፕሎማቶችና ሌሎች ጎብኝዎቻቸው ባላወቁ ነበር ከእሥር መለቀቃቸው የፈጠረላቸው መነቃቃት በጤናቸው መሻሻል ላይ ለውጥ እንዲታይ አድርጓል አሁን ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ሊያገኙት የማይችሉትን የሕክምና አገልግሎት ያለማንም ጣልቃ ገብነት ማግኘት ይችላሉ ፕሮፌሰር አሥራት ኢትዮጵያ ውስጥ እያሉ ሐኪሞቻቸውን ብቻቸውን ርዐበቨፀፀበዝቋሃን ለማግኘት አይፈቀድላቸውም ነበር ሐኪም አጥተው የሞቱት ሐኪም የሰው ልጅ ክቡር ሰው መሆን ክቡር ሰው ሞቷል ሰው ሊያድን ሰውን ሲያከብር በደግነት በፍቅር በክብር ተጠርቶ በክብር ይሄዳል ሰው ሊኖር ሰው ሞቶ አጅጋየሁ ሽባባው አድዋ ከሚለው የዘፈን ግጥም የተወሰደን ፕሮፌሰር አሥራት በማረሚያ ቤት ሕክምና ተከልክው በመቆየታቸው ወደ ውጭ ሄደው እንዲታከሙ ሲፈቀድ በጣም ከመድከማቸው የተነሳ ወደ እንግሊዝ አምርተው ጥቂት ቀናት እንዲቆዩ ተደርጓል ከእንግሊዝ ቆይታቸው በኋላም ወደ አሜሪካ ቴክሳስ ሲሄዱ እጅግ ተዳክመው ነበር በዚህም የተነሳ የሕክምና ዶክተሮች አውሮፕላኑ ላይ እገዛ እያደረጉላቸው ወደ አሜሪካ ሊሄዱ ችለዋል በአሜሪካ ቴክሳስ ህክማናቸውን ሲከታተሉ ግን የጤንነታቸው ሁኔታ መሻሻል አሳይቶ ነበር አሜሪካ ቴክሳስ በነበሩበት ወቅት ከህመማቸው በማገገማቸው ደስታ እንደፈጠረላቸውና ህዝቡ በችግራቸው ወቅት ከጎናቸው በመሆኑ የተሰማቸውን ክብር ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልዕክት አስፍረው ነበር ረለተከበራችሁ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቸ በሙሉ ምንም የማይሳነው አምላክ ቸሩ እግዚአብሔር ሳላስበውና ሳልጠብቀው ከምወዳችሁ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቸ መካከል እንድሆንና በአሁኑ ሰዓት ሕክምና እንዳገኝ በማድረጉ ከልብ አመሰግነዋለሁ ውድ ወገኖቼ እሥር ቤት እያለሁ ለአንድ አፍታም በመንፈስ ሳትለዩኝ ስሜን በዓርዓያነት እየጠራችሁ ስታስቡኝ ስታግዙኝና ስትጸልዩልኝ በመቆየታቸውሁ በጣም አመሰግናችኋለሁ ከህመሜ ድኘ በአካል እስከማገኛችሁ ድረስ ሰላም ሁኑልኝ እግዚአብሔር ይስጥልኝ አሥራት ወልደየስ ከቅዱስ ሉቃስ ኤጴስቆጳል ሆስፒታል ህዩስተን ቴክሳስ ፕሮፌሰር አሥራት በዚህ መልክ አገግመው የነበር ቢሆንም ባልታወቀ ሁኔታ ተመልሰው ደከሙ ህመማቸው ከፍተኛ ደረጃ ደርሶ በሕይወትና በሞት መካከል ሆኑ በወቅቱ የነበሩበትን የሕመም ደረጃ ዶክተር አበባ ፈቃደ ሲናገሩ እንኳን እኔ የቋንቋ ችሎታ የሌለኝ ሰው ማንም የቋንቋ ሊቅ ሊገልጸው አይችልም ይላሉ ብቻ ተሻላቸው ተብሎ በነበረበት ወቅት ተመልሰው የመዳከማቸው ምሥጢር አነጋጋሪ ነው ዘመዶቻቸው ወደሚገኙበት ፊላደልፊያ ከወር በፊት የተዘዋወሩት ፕሮፌሰር አሥራት ግንቦት ቀን ዓም ፊላደልፊያ በሚገኘው ፔኒሲለቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በዕለተ አርብ አርፈዋል ምዕራፍ ሰባት ፕሮፌሰር አሥራት በሌሎች ሰዎች አንደበት ረየዶክተር አሥራት ወልደየስን ሞት የሰማሁት በታላቅ ሀዘን ነው እኝህ ተሰጥኦ ያላቸው ቀዳጅ ሐኪምና ሩህሩህ የኢትዮጵያ ልጅ ሊረሳ የማይችል መልካም ተግባርና አርዓያ ቅርስ ትተውልናል ዶክተር አሥራት ለዲሞክራሲ ምስረታ ጥርጊያውን በሚከፍቱት በሰላም በሰብዓዊ መብት ጥበቃና በመድብለ ፓርቲ ማመን ብቻ ሳይሆን ጤንነታቸውንና ህይወታቸውን ሰውተውላቸዋል ስለዚህ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስም ልባዊ ሀዘኔን ለቤተሰባቸው እንዳስተላልፍ ይፈቀድልኝ በዚህ በሀዘናችሁ ወቅት በጸሎት አንረሳችሁም የዶክተር አሥራትን አርዓያ በምሳሌነት እንከተላለን የናንተው ከትህትና ጋር። ኮፊ አናን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ረየፕሮፌሰር አሥራት የሕክምና ሙያ ጥራት ወደር የሌለው እንደነበረ በእጃቸው ታክመው የዳኑት ግለሰቦች የሚመሰክሩት ነው ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ጀምሮ ለሁሉም ሕመምተኞቻቸው ሕይወት ይከራከሩ የነበሩት ሰው ለራሳቸው የሚቆምላቸው አጥተው አልፈዋል ፕሮፌሰር አሥራትን የመሰለ ታላቅ ጠቢብ ከዚህ ዓለም በሞት መለየት ለነፃነት ለአንድነትና ለሉዓላዊነት የምናሰማውን ጩኸትና የመከራ ዘመናችንንም ያራዝመዋል ይህ እንዳይሆን በሕይወታቸው መስዋዕትነት ያስገኙትን የኢትዮጵያዊነት ክብር አንግበን ለቅድስት ሐገራችን አንድነትና ሉዓላዊነት ሰላምና ብልጽግና በህብረት አንቁም በረከታቸው አይለየን ፕሮፌሰር ነቢያት ተፈሪ የቅርብ ወዳጅና የ ዓመት የሥራ ጓደኛ ርበብዙዎች ዘንድ የኛው መቶ ክፍል ዘመን የነፃነትና የዲሞክራሲ ጠበቃ የተባለላቸው አሥራት የሐገር ውስጥ ትምህርታቸውን በሚገባ ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ውጭ አገር ተልከው የሕክምና ሙያ በማጥናት ሐገራቸውን ከ ዓመታት በላይ አገልግለዋል ከሕክምናው በተጨማሪ በመምህርነታቸውም እውቅ የሕክምና ጠበብቶችን አፍርተዋል ከንጉሰ ነገስት እስከ ተራ ዜጋ ወንድ ሴት ሕፃን ሽማግሌ ሳይሉ የሙያ ክህሎታቸው በፈቀደው ሁሉ ወገኖቻቸውን ረድተዋል ማን ይመስክር የነበረ ማን ያርዳ የቀበረን እንዲሉ በፕሮፌሰር አሥራት እጅ ሕይወታቸው የተረፈና ዛሬም ለምስክርነት የበቁ ጥቂቶች አይደሉምዎ ረከኃ ዓመታት በፊት ከባድ የመኪና አደጋ ደርሶብኝ ነበር በወቅቱ ከተፈጠሩብኝ ችግሮች ዋነኛው ጭንቅላቴ አብጦ በውስጥ የነበረው ደም ወደ አንጎሌ ውስጥ ገብቶ አደጋ ያስከትላል የሚለው ስጋት ነበር በወቅቱ የነበሩት ሁለት ተረኛ የዩጎዝላቪያ ተወላጅ ሐኪሞች መውሰድ ያለብን ርምጃ ቀዶ ሕክምና ኦፕራሲዮንን አድርገን ፈሳሹ ወደ አንጎልህ ሳይወርድ ማውጣት ነው ብለው ወሰኑ በቀዶ ሕክምናው ብዙ አደጋ ሊከተል ይችላል የተሻለው አማራጭ መርፌ ርስሪንጅን ዓይነት ጭንቅላቱ ውስጥ ከትቶ ደሙን ስቦ ማውጣት ነው ብለው ሃሳብ አቀረቡ ሁለቱ ሐኪሞች ፕሮፌሰር አሥራት ያቀረቡትን አማራጭ ተቀብለው ሥራ ላይ በማዋል ደሙን አውጥተውልኝ ሕይወቴም ተርፎ እስከ ዛሬ በሕይወት ልቆይ ችያለሁ ፕሮፌሰር አሥራትን እኔ በግሌ የማስታውሳቸው በእንደዚህ ዓይነት ከባድ ባለውለታነታቸው ነው አቶ አሸናፊ አበጀ የአሜሪካ ድምፅ የቀድሞ አማርኛው ክፍል አቅራቢ ርፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ከ ዓመታት በፊት ከሞት ያዳኑኝ ባለውለታየ ሐኪም ናቸው ቀድሞ የልዕልት ፀሐይ መታሰቢያ ሆስፒታል ይሰራ የነበረ አንድ ግብጻዊ ዶክተር ምርመራ ካደረጉልኝ በኋላ የሽንት ማጠራቀሚያ ፊኛህ ውስጥ ጠጠር አለና በኦፕራሲዮን ማውጣት አለብኝ አለበለዚያ ለሕይወትህ ያሰጋሃል ይለኛል እተኛለሁ የቀዶ ሕክምና ይደረግልኝና ወደ መኝታ ክፍሌ እወሰዳለሁ ሽንት መሽናት እቸገራለሁ ሆዴ ይነፋል ሰው ሰራሽ ሽንት ማሸሺያ ቧንቧ ያስገቡልኝና እሸናለሁ ግብጻዊው ሐኪም እንደዚያ መሆን እንዳልነበረበት ይረዳና በድጋሚ ወደ ኦፕራሲዮን ክፍል አስገብቶ ለሁለተኛ ጊዜ ቁስሉን ከፍቶ ይዘጋል አሁንም አልሆነለትም እኔ በግቢ ነፍስ ውጭ ነፍስ ውስጥ እሰቃያለሁ ሐኪሙ ለሶስተኛ ጊዜ በተመሳሳይ መልክ ቀዶ ሕክምና አድርጎ ይዘጋልኛል መፍትሄ ግን አልሰጠኝም በሁኔታው ግራ የተጋቡ ሐኪሞችና ዘመዶቼ ችግሩን ለዶክተር አሥራት ይገልጹላቸዋል በማግስቱ ጠዋት ይመጡና በጣም ተዳክሜ ስለነበር ያለ ሰመመን መርፌ አካባቢውን ብቻ በመርፌ በማደንዘዝ ቁስሉን ይከፍታሉ ለካስ ግብጻዊው ሐኪም ደም እንዳይፈስሰኝ ብሎ ስሬን ቆንጥጦ ያስያዘበትን መሳሪያ ሰውነቴ ውስጥ ትቶት ኖሯል ይቺን አግኝተው ያወጡና ይጥላሉ ለሁለት ወራት ሙሉ የአልጋ ቁራኛ የነበርሁት ሕመምተኛ በሁለት ሳምንት ውስጥ አገግሜ ልወጣ ቻልኩ በወቅቱ ተገቢውን ሕክምና ስላደረጉልኝ ነው ሕይወቴ የተረፈው እርሳቸው ያንን ዕድል ሳያገኙ በማረፋቸው ግን ልቤ ደምቷል ሰለሞን ክፍሌ የአሜሪካ ድምፅ የአማርኛው አገልግሎት ረእርሳቸው የቆሙለትን የአንድነት የዴሞክራና የፍትህ ጥያቄ ነፃው ፕሬስም በሚያራምድበት ጊዜ በዚህ በኩል ብዙ ጊዜ እንገናኛለን ኢንተርቪው እናደርጋቸዋለን በዚህ የተነሳ በአብዛኛው የነፃው ፕሬስ አባል የሆኑ ጋዜጠኞች ፕሮፌሰር አሥራትን ጋንዲ ማርቲን ሉተር ኪንግ ማንዴላ እያሉ ይጠቅሷቸው ነበር ይህም የቆሙለትን ከሽብር ነፃ የሆነ ሰላማዊ ትግል ለመግለጥ ነበረ ፕሮፌሰር አሥራት በመጨረሻ ከገ ቀናት በፊት ሳነጋግራቸው እንደምንም እየታገሉ ዓይናቸው እየተንከራተተ አይዚችሁ በርቱ የሚል መልዕክት አስተላልፈዋልና ለኢትዮጵያዊያን ሁሉ የቀረበ መልዕክትና ኑዛዜ አድርጌ ነው የምገልጸው እኔም የኑዛዜ መልዕክተኛ ሆቼ ነው በዚህ ወቅት የምቀርበው አንጋፋው ጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌ ዛሬ ሀቀኛ ኢትዮጵያዊ የሕዝብ ወገናዊነት ወንጀል በሆነበት ጊዜ አሥራት አንተ ከኢትዮጵያዊነት በስተቀር ሌላ ወንጀል የለብህም ዛሬ የእኛ ምስክርነት ለአንተ አያስፈልግህም አሥራት ከሰማዕታት ጎን ቆመህ ግን የሞትክላትን ኢትዮጵያ እኛ ምድራዊያኑ እንዴት እንደተቀራመትናት የምትጠይቀን ገመናዋን እንዴት እንዳራከስነው የምታጋልጠን በጦርነት አለንጋ ገላዋን እንዴት እንደገነጣጠልናት የምትመሰክርብን አንተ ነህ የኢትዮጵያ ጉዳይ ጉዳየ ነው የምንል ዜጎች ሁሉ ዛሬ ከዚህች መራራ ጥያቄ እንደማናመልጥ የምትመሰክርብን አንተ ነህ አሥራት ዛሬ እንደሚባለው በሀረርጌ ድሬዳዋ ልጅነትህ ወይም በመንዜነትህ ወይም በሸዋነትህ ወይም ስለ አማራነትህ ሳይሆን ለቁርጠኛ ኢትዮጵያዊነትህ ነው ዛሬ መላው የኢትዮጵያ ልጅ እጅ የሚነሳህ አምባገነንነትን ታግለህ እኩልነትን በማራመድህ ጦረኝነትን ታግለህ ሰላማዊነትን ዘረኝነትን ታግለገህ ኢትዮጵያዊነትን ጨቋኝነትን ታግለህ አንድ ሰው አንድ ድምፅ የሚለውን ዲሞክራሲያዊ መርሕ በማራመድህ ነው ዛሬ መላዊ የኢትዮጵያ ልጅ እጅ የሚነሳህ ዛሬ በኛው ሳይንሳዊ ዘመን ዘመነ ምጥቀት መግቢያ በር ላይ በማኪያቬሌ ያረጀ ሾተል እንደ ጴላጦስ የሕዝብን ጀግና ለሞት አሳልፎ ሰጥቶ እጅ መታጠብ በሕዝብ ፊት ከተጠያቂነት ከታሪክም ፊት ከኃላፊነት ማናችንም አንድንም ሎሬት ጸጋየ ገብራመድህን የፕፌሰር አሥራት አስከሬን ሽኝት ላይ ከተናገሩት የተወሰደ የፕሮፌሰር አሥራትን መሞት በተመለከተ በዓለም ላይ ያሉ ሚዲያዎች ሰፊ ትንታኔ ሰጥተው ነበር የተወሰኑ ታላላቅ ሚዲያዎች የሰጡትን አስተያየት እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ በነገራችን ላይ እነዚህ የውጭ ሚዲያዎች ከጻፏቸው ቁም ነገሮች ውስጥ ጥቂት መፋለሶች አይጠፉም ቢሆንም ግን ከመረጃ እጥረት ሊሆን ይችላል በሚል ሙሉውን ትርጉም አስፍሬዋለሁ ዘጋርድያን ጋዜጣ በፖዐ ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ የታወቁና በሙያቸው ዝናን ያተረፉ የቀዶ ሕክምና ጠበብት ኢትዮጵያዊ ነበሩ ፕሮፌሰር አሥራት ከቀዶ ሕክምና ጠበብትነታቸው በተጨማሪ የዩኒቨርሲቲ ዲንም ነበሩ ሰውየው በተለይ በአነጋጋሪ የፖለቲካ ፓርቲ መሪነታቸውና በኋላም በፖለቲካ እስረኛነታቸው ይታወቃሉ አሥራት የንጉሰ ነገስት አጹ ኃስላሴ የግል ሐኪም ሆነው ንጉሱ እስካሁን እንቆቅልሽ በሆነው አሟሟታቸው ከዚህ ዓለም እስከተለዩበት እኤአ ዓ ድረስ አገልግለዋል በኋላም እኤአ ገ ዓም ላይ በፖለቲካ እስረኛነት ካሉበት ተጠርተው ንጉሰ ነገስቱ በተፈጥሯዊ ታመውን እንዳልሞቱ በሰው እጅ እንደተገደሉን ማረጋገጫ እንዲሰጡ ተጠይቀዋል ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ በኤደንብራ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ትምሕርት ቤት ትምህርታቸውን ከተከታተሉ በኋላ በሰለጠነው የምዕራቡ ዓለም ዘንድ ብቁ ኢትዮጵያዊ የቀዶ ሕክምና ጠበብት እንደሆኑ የተመሰከረላቸው ነበሩ ፕሮፌሰር አሥራት አብዛኛው ህይወታቸውን በሁለት ዋና ዋና የሐገር ውስጥ ሆስፒታሎች የቀዶ ሕክምና አገልግሎት በመስጠትና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ትምሕርት ቤት ዲን በመሆን አሳልፈዋል አሥራት ባላቸው ሙያዊ ብቃት በተሻለ የኑሮና የሙያ ነፃነት በምዕራቡ ዓለም በመሥራት ብዙ ጥቅም ማግኘት ይችሉ ነበር እርሳቸው ግን የግል ጥቅምና ድሎት ሳያጓጓቸው ህዝባቸውን ማገልገልን መርጠዋል አሥራት ኢትዮጵያ በመንግስቱ ኃማርያም ወታደራዊ የኮሚኒስት ሥርዓት እኤ። ይህንንም ዘጋቢው በወቅቱ በዘጋርዲያን ላይ ምስክርነቱን ጽፏል ሕወሓትና ሻዕቢያ እኤአ በገገ ዓም የመንግስቱ ኃማርያምን መንግሥት ከሥልጣን ማባረራቸውንና ኤርትራ መገንጠሏን ተከትሎ በትግራይ ገዥዎች የበላይነት የተመሰረተው የኢሕአዴግ መንግሥት ቀደም ሲል በነበሩት የንጉሱና የመንግስቱ ኃማርያም መንግስታት ወቅት የፖለቲካ የበላይነት ነበራቸው የሚሏቸውን የአማራዎች ልሂቃን ማሳደድ ጀመሩ በዚህም ፕሮፌሰር አሥራት በመንግሥት እኤአ በ ዓም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከተባረሩት የአማራ ፕሮፌሰሮች አንዱ ነበሩ ሰውየው በዚሁ ዓመት የኢትዮጵያን አንድነት ለማስመለስና ለማስጠበቅ እንዲሁም በመለስ ዜናዊ ጎሳን መሠረት ያደረገ አስተዳደር የጥቃት ሰለባ የሆነውን የአማራ ሕዝብ ለማዳን አልሞ የተመሰረተው የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት መዐሕድን መሥራች ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል ምንም እንኳ የመዐሕድ ሕጋዊነት እንዳለ ቢሆንም ድርጅቱ ከመለስ መንግሥት ጋር ያለው ግንኙነት ግን ሰኔ እኤአ የፕሮፌሰር አሥራትን መታሰር ተከትሎ ኩፉኛ ሻከረ በወቅቱ በመንግሥት ላይ ብጥብጥ ለማስነሳት አቅደዋል ተብለው ለሁለት ዓመታት ታሰሩ አምኒስቲ ኢንተርናሽናልና ሌሎች ገለልተኛ ታዛቢዎች ግን በፕሮፌሰር አሥራት ላይ መንግሥት ያቀረበባቸውን ማስረጃ ፈጠራ ነው ሲሉ አጣጥለውታል አሥራት በጊዜው የተከሰሱበትን ብጥብጥ ማስነሳት የመሳሪያ ትግልን የሚያወግዝ ንግግር ማድረጋቸው ይታወቃል የኢሕአዴግ መንግሥት ግን በቀጣይም በፕሮፌሰር አሥራት ላይ ሌሎች የፈጠራ ማስረጃዎችን በማቅረብ እሥራታቸውን እስከ አምስት ዓመት አራዘመ እኤአ በ ዓም ደግሞ ሌላ ክስ ተመሰረተባቸው መንግሥት በዚህኛው ክስ ማብቂያ በሌለው ተደጋጋሚ ቀጠሮ በማንገላታት ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስን ቀደም ብሎ ካስተላለፈባቸው የእሥር ቅጣት በላይ ለማሰር ያለውን ፍላጎት በግልጽ አሳይቷል ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ዕድሜያቸው በሥልሳዎቹ መጨረሻ ሆነውና በልብ ድካም እየተሰቃዩ ባሉበት ወቅት ጠያቂ ተከልክለው በእሥር ቤት ታጉረዋል አሥራት የታሰሩበት እሥር ቤት ሌሎች እስረኞችም ያሉበት ቢሆንም እሳቸው ግን ከማንም እስረኛ ጋር የመነጋገር ፍቃድ አላገኙም ይህም የእሳቸውን የእሥር ሁኔታ ውስብስብና አሳሳቢ ያደርገዋል በዚህም ምክንያት እኤአ በፀ ጥር ላይ ጤናቸው ክፉኛ አሳሳቢ እየሆነ በመሄዱ በከፍተኛ የታጠቁ ኃይሎች ታጅበው ቀድሞ ያገለግሉበት ወደነበረው ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ተወስደዋል ህዳር ላይም እንዲሁ የጤና ሁኔታቸው ከፍተኛ ትኩረትን የሚጠይቅ ሆኖ ነበር ምንም እንኳ ስለጤናቸው ያለው እውነታ በምሥጢር ቢያዝም ስለ ልብ ህመማቸው ስለ ስኳር ስለ ደም ግፊትና የጭንቅላት ደም መርጋት እንዲሁም እየባሰ ስለነበረው የዓይን ብርሃን ግርዶሽ የነበረው አደገኛ ሁኔታ በደጋፊዎቻቸው ዘንድ ጭንቀትን ፈጥሮ ቆይቷል በወቅቱ በመንግሥት ተቀጥረው ሕክምና ያደሩጉላቸው የነበሩት ዶክተሮች ፕሮፌሰር አሥራት ወደ ውጭ ሐገር ሄደው መታከም እንደሚኖርባቸው ገልጸው ነበር በ ዓም የፈረንጆች ዘመን መለወጫ ወቅት የኢትዮጵያ መንግሥት በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚደርስበትን ጫና ተከትሎ አሥራት ወደ ውጭ ሐገር ሄደው እንዲታከሙ ተፈቀደ በዚህም ፕሮፌሰር አሥራት ወደ ለንደን ከዚያም ሆስተን ቴክሳስ እንዲጓዙ ተደረገ ፕሮፌሰር በውጭ ሐገር ሕክምናቸው ለአጭር ጊዜ ያገገሙ ቢመሥልም ህመማቸው እንደገና ጸንቶባቸው ከሐገር ከወጡ አምስት ወር ሳይሆናቸው በፔኒሲለቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገላቸው እያሉ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል ምንም እንኳ ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ገራገር ፖለቲከኛ እንደነበሩ የሚናገሩ ባይጠፉም በተቀባይነት ግን የትልቅ ክብር እና ስብዕና ባለቤት ነበሩ በአምስት ዓመት አስከፊ የእሥር ቆይታቸው ወቅት ሁሉ እንደ አምኒስቲ ኢንተርናሽናል ያሉ ዓለም አቀፍ ተቋማትና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችና ግለሰቦች ፕሮፌሰሩ ከእሥር እንዲፈቱ ያላሳለሰ ዘመቻ ያደርጉ ነበር ሆኖም ግን ተጽዕኗቸው ከፍተኛ ነው የሚባሉት የምዕራብ ዓለም መንግስታት አልፎ አልፎ በቃል ከመናገር ባለፈ በተግባር በመለስ ዜናዊ መንግሥት ላይ ግፊት ሳያደርጉ ታቅበዋል ይህም ካለፈው ሥርዓት ተሽሏል የሚሉትን የመለስ ዜናዊን መንግሥት ላለማስከፋት ያደረጉት መታቀብ ነበር ምንም እንኳ በእርግጠኝነት ማጠቃለል ባይቻልም እነዚህ የምዕራብ መንግስታት በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ቀደም ብለው ጫናቸውን ቢያሳርፉና የአሥራትን ስቃይ ቢቀንሱ ኖሮ የዘመናችንን ምርጥና የታወቁ ኢትዮጵያዊ ሰው ሞት ባዘገዩት ነበር። ኢትዮጵያዊው ዶክተርና ተቃዋሚ አሥራት ወልደየስ አረፉ ኤሪስ ፔስ ለኒዮርክ ታይምስ እንደጻፈው ግንቦት እኤአን በኢትዮጵያ ዋነኛው የተቃዋሚ ድርጅት መሪ ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ የሕክምና ትምህርታቸውን እንግሊዝ ሐገር የተከታተሉት እውቁ የሕክምና ባለሙያ አሥራት ወልደየስ ፊላደልፊያ በሚገኘው ፔኒሲለቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በዕለተ አርብ አርፈዋል ፕሮፌሰር አሥራት እድሜያቸው ከዐ ዓመት በላይ ሆኗቸዋል የወንድማቸው ልጅ ዮም አብይ ለአሶሼትድ ፕሬስ እንደገለጸው የአሥራት ሞት ምክንያቶች የልብ ሕመምና በእሥር ቆይታ የተነሳ የደረሰባቸው አጠቃላይ አካላዊ መዳከም ናቸው ፕሮፌሰር አሥራት ኢትዮጵያ ውስጥ በሕክምና መምህርነትና በቀዶ ሕክምና ሥራ አገልግሎት የሰጡ ሲሆን የውጭ ሕክምና ለመከታተል ፊላደልፊያ መጥተው ለሶስት ሳምንታት ሆስፒታል ውስጥ ቆይተው ማረፋቸውን ዮም አብይ ተናግሯል አሥራት ለሞት ካበቁት የልብ ሕመምና ከፍተኛ የአካል መዳከም በተጨማሪ በደም ግፊትና በስኳር በሽታም ይሰቃዩ ነበር ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ መንግሥትን በመቀናቀን የሚታወቀው የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅትን ይመሩ ነበር በተለይም አሥራት በጎሳና በቋንቋ ላይ የተመሰረተውን የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የፌደራላዊ መንግሥት አወቃቀር ክፉኛ በመተቸት ይታወቃሉ በዚህ የተነሳም እኤአ በ በኢትዮጵያ የፖለቲካ እስረኛ ለመሆን ተዳርገዋል አሥራት ፓርቲያቸውን በመጠቀም በሰሜን ምዕራብ የሐገሪቱ ክፍል ፀረመንግሥት ትጥቅና አመጽ አደራጅተዋል በሚልም ለአምስት አመታት በእሥር ቤት አሳልፈዋል እንግሊዝ ሐገር የሚገኘው ላንሴት የተሰኘ የሕክምና ጆርናል እንደገለጸው ፕሮፌሰር አሥራት ኢትዮጵያ ውስጥ ለወራት ሆስፒታል ከርመዋል በተለይም ውጭ ወጥተው እንዲታከሙ አምኒስቲ ኢንተርናሽናልና ሌሎች ሰብዓዊ ድርጅቶች ዓለም አቀፍ ግፊት አሳድረው ይሁንታ እስኪገኝ ድረስ የልብ ህመማቸው ጸንቶባቸው ለዘጠኝ ቀናት ያህል ሐገር ውስጥ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በከፍተኛ የሕክምና ክትትል ቆይተዋል ፕሮፌሰር አሥራት ለጊዜው ከእሥር ቤት ወጥተው ወደ አሜሪካ ለሕክምና በተወሰዱበት ወቅት እንኳ በተመሳሳይ ክስ ሌላ የፍርድ ቤት ቀጠሮ ነበረባቸው በኋላ ላይ ግን አቃቤ ሕግ ፕሮፌሥር አሥራት በጤና እክል ምክንያት እንደገና ፍርድ ቤት ለመቅረብ ስለማይችሉ በሚል ክሱን አንስቶታል በወቅቱ አሥራት ለሕክምና ከእሥር መውጣታቸውን ተከትሎ የወቅቱ የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቶኒ ልዮድ ይህ የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰብዓዊ መብት መከበር የገባውን ግዴታ ለመወጣት ያለውን ግልጽ ቁርጠኝነት ያሳያል ብለው ነበር አሥራት ወልደየስ በኢትዮጵያ ለሩብ ምዕተ ዓመት ያህል በሕክምና ሙያ አገልግለዋል የንጉሰ ነገስት ኃይለ ሥላሴ የግል ሐኪም በመሆንም ሰርተዋል አሁን በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት እኤአአ ላይ ሥልጣን መያዙን ተከትሎ ደግሞ የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅትን መሥርተዋል በዚህ የተነሳም ወዲያው ከጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ተባረዋል ዋሽንግተን ፖስት ሼልሃ የሕክምና ባለሙያው አሥራት ወልደየስ አረፉ እንግሊዝ ሐገር ትምህርታቸውን የተከታተሉት እውቁ ኢትዮጵያዊ የቀዶ ሕክምና ባለሙያ አሥራት ወልደየስ አሜሪካን ሐገር ፊላደልፊያ ሕክምናቸውን እየተከታተሉ እንዳሉ በፖዐ ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል በልብ ሕመም ሲሰቃዩ የቆዩት ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን አምባገነን መንግሥት በመቃወም የሚታወቁ የረጅም ጊዜ የዴሞክራሲ አቀንቃኝ ነበሩ ለድሆችና ለተገፉት ሁሉ ድምጻቸውን የሚያሰሙት ፕሮፌሥር አሥራት ነውጥ አልባ የፖለቲካ ለውጥ እንዲመጣ የሚታገለው የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት ፕሬዚደንት ነበሩ አሥራት ቋንቋን እና ጎሳን መሠረት አድርጎ የተዋቀረውን የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ መንግሥት እና ፖሊሲዎቹን አምርረው በመተቸት ይታወቃሉ የቀዶ ሕክምና ባለሙያው አሥራት ወልደየስ በድሃዋ ግን ደግሞ ኩሩዋ ሐገሩ ውስጥ የሕክምና ትምሕርት ፈር ቃዳጅ በመሆን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ትምሕርት ክፍል ዲን ሆነው አገልግለዋል ለንጉሰ ነገስት አጹ ኃይለ ሥላሴ የግል ሐኪምም ነበሩ አሥራት ለአምስት ዓመታት በእሥር ቤት ካሳለፉ በኋላ ተፈትተው ለሕክምና ወደ ውጭ ወጥተዋል በእንግሊዝና ቴክሳስ ሕክምና ከተደረገላቸው በኋላ ለሌላ ሕክምና ዘመዶቻቸው ወደሚገኙበት ፊላደልፊያ ከወር በፊት ተዛውረዋል አሥራት በሁለት ንግግሮቻቸው መነሻነት ኢትዮጵያ ውስጥ ለአምስት ዓመታት ታስረዋል በተጨማሪም ለሕክምና ከመለቀቃቸው በፊት በሐገር ክህደት ክስ ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ቀጠሮ ተይዞላቸው ነበር ፕሮፌሥር አሥራት ከግራ ዘመሙ የመለስ ዜናዊ መንግሥት ጋር ችግር ውስጥ የገቡት እኤአ ላይ ሬፕኤጆንስተን ዳግማዊን አግኝተው በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ የሰላ ትችት ከሰነዘሩ ወዲህ ነበር በወቅቱ መለስ ዜናዊ ቃል የገባውን ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ ማስፈን አለመቻሉን በማውሳት ተችተዋል በዚህም ከሦስት ቀናት በኋላ አመጽ አነሳስተሃል በሚል ለእሥር ተዳርገዋል ፕሮፌሰር አሥራት ላይ የነበረው የፍርድ አሰጣጥ አሳፋሪ ነበር በእሳቸው ላይ ሊመሰክሩ የመጡት የአቃቤ ሕግ ምስክሮች የመንግሥት ባለሥልጣናት አስገድደዋቸው በሀሰት ለምስክርነት እንደቀረቡ ለችሎት አስረድተዋል ይህም ሆኖ ግን አሥራት ስለ ዴሞክራሲ በመናገራቸው ብቻ ወደ እሥር ቤት ተግዘዋል እሥር ቤት ሆነውም ግን አንድ የዋሽንግተን ፖስት ጸሐፊ እንደገለጻቸው በኢትዮጵያ በጣም የታወቁ የዴሞክራሲ ተምሳሌት መሆን ችለዋል ዴቪድ ኢጌ ስቴነማን በ እኤአ እንደጻፈው አሥራት በመለስ ዜናዊ ከምርጫ በፊት ወደ እሥር ቤት ባይወረወሩ ኖሮ የኢትዮጵያ ፕሬዚደንት ሆነው መመረጥ ይችሉ ነበር በወቅቱ አምኒስቲ ኢንተርናሽናል ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስን ርበአስቸኳይ ከእሥር መለቀቅ የሚገባቸው የህሊና እስረኛ ሲል ገልጹዋቸውም ነበር እኤአ በ በግለሰቦችና በአሜሪካ ባለሥልጣናት ግፊት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ዲፓርትመንት ስለ ፕሮፌሰር አሥራት የእሥርና የጤና ሁኔታ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪዎች ያራምዱት የነበረውን አቋም በይፋ ሊቀበለው ችሏል የመጨረሻ ምዕራፍ የፕሮፌሰር አሥራት ግብዓተመሬት ስነሥርዓት ርየፕሮፌሰር አሥራት መሞት ሲነገር አብዛኛው ያልሰማ ነበርና ቤቱ በለቅሶ ተናወጠ ሀዘናችንን ተወጥተን እንባችንን ከአበስን በኋላ ድርጅቱ ምን ያደርግ ይሆንን ሌሎቹ ሰዎችስ መንግሥትስ ምን ያደርጉ ይሆን።