Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
ሊሚትድ ኃጳሳያ ወፖረ ዐፀጋደፖ ወይም ዐፀዐዐጋኃዐ ዳዲዕ ለያ ጴዲግምድዖ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው። ል በደከ ፎ የፎቆፎሃፎበ አንደኛ እትም ሕዳር መግቢያ ሞት አይቀሬ ነገር የሁላችንም እጣ ፈንታቸው ደግመውና ደጋግመው ማሰብ ይኖርባቸዋል አላህ በተጨማሪም እንዲህ ይላል ።
ኋ ነፍስ ሁሉ ሞትን ቀማሽ ናት አልአንቢያ በዚህም ምክንያት የሰው ልጆች በዚህች ምድር ላይ ኮንትራታቸውን አጠናቅቀው ከመሄዳቸው በፊት ስለዚህ መራራ የሆነ እጣ ፈንታቸው ደግመውና ደጋግመው ማሰብ ይኖርባቸዋል አላህ በተጨማሪም እንዲህ ይላል ሪጄ መኃሯጄን የሞትም መከራ እውነቱን ነገር ታመጣለች ሰው ሆይ ይህ ያ ከርሱ ትሸሸው የነበረው ነው ይባላል ቃፍ የሰው ልጆች በዚህች ዓለም ላይ ተፈጥረው እንዲገኙ የመደረጋቸው ምስጢር ለፈተና አንደመሆኑ በሕይወት ዘመናቸው ዋነኛውና ታላቁ ግባቸው ሊሆን የሚገባው በጀነት ቦታ ማግኘት ነው ይህንንም ለማድረግ የአለማቱ ሁሉ ጌታ የሆነውን አላህን የሚያስደስቱ መልካም ሥራዎችን በብዛትና በጥራት መሥራት ይጠበቅባቸዋል ይህን ማድረግ ያለባቸው ለምንድን ነው። ሰውንም ሁሉ በራሪውን ሥራውን በአንገቱ አስያዝነው ለአርሱም በትንሣኤ ቀን የተዘረጋ ሆኖ የሚያገኘው የሆነን መጽሐፍ እናመጣለታለን መጽሐፍህን አንብብ ዛሬ ባንተ ላይ ተቆጣጣሪነት በነፍስህ በቃ ይባላል አልኢስራአ የአላህን ምርጥ ባሮች አላህንና መልእክተኛውን ሰዐወ በመውደድና የእነርሱንም ትፅዛዛት ለመፈጸም ደፋ ቀና ሲሉ የኖሩ ናቸው ይህም በመሆነ በመጨረሻው የሕይወታቸው ፍጻሜ ትክክለኛዋን ከሊማ ሸፃዳ ከአንደበታቸው አውጥተው እስትንፋሳቸው ያቆማል እንዲህ አይነት ሰዎችን በተመለከተ ነቢዩ ሰዐወ የሚከተለውን የምሥራች ተናግረዋል የመጨረሻ ንግግሩ ከአላህ በስተቀር በዛቅ የሚያመልኩት ጌታ የለም ሙሐመድም የአላህ መልእክተኛ ናቸው የሚል የሆነ ሰው ጀነት ይገባል ዛፃኪም ሙስተድረክ ቅጽ ቁ በሌላ አባባጂለ ሕይወቱን ሙሉ ይህን ከሊማ ከልቡ በማመን ሲደጋግመው የኖረ ሰው በመጨረሻው እስትንፋሱ ጊዜ ከአንደበቱ አውጥቶት መሞቱ አይቀርም ይህ የዕድሜ ልክ መንፈሳዊ ጉዞ የሚጠይቃቸውን ማናቸውም መስዋአትነቶች ሁሉ ማሟላትን ግድ ይላል የዚህ መልካም ንግግር ከሊመቱ ጠይባ ባለቤቶች እንዲሆኑ የሚመረጡት በምድር ዓለም ሕይወታቸው ከሥጋቸው ይልቅ ለመንፈሳቸው ያደሉ ፃቅን የሚደግፉና ዛሰትን በጽናት የተፋለሙ የእውነት ሰዎች ናቸው ከአላህ ሌላ የሆኑ አማልክት በሙሉ ጣኦታትና በሃሰት ትምህርቶች ላይ የተመሠረተ አምልኮት የሚፈጸምላቸው ናቸውና በዓለማቱ ጌታ ኃያሉ አላህ የ « ሁንቃል የተገኘው ይህ አጽናፈ ዓለምና በውስጡ ያሉ ነገሮች በይበልጥም ደግሞ የሰው ልጅ የሚገኝባት ይህች ዓለም አላፊ ጠፊና በብልጭልጭ ትርዒቶች የተሞላች መሆኗን ማወቅ ተገቢ ነው ። ዝ ው ኤን እናንተ ያመናችሁ ሆይ አላህን ተገቢውን መጠንቀቅን ተጠቀንቀቁት። እናንተም ሙስሊሞች ሆናችሁ እንጂ አትሙቱ አሊዒምራን ዐ አላህ በተጨማሪም እንዲህ ይላል የ ረ ቼ ይ መ ነለ»ጨ ኔ እናንተ ያመናችሁ ሆይ። ብለን ስሞታ አቀረብን ነብዩም ከአናንተ በፊት ባለፉት ሕዝቦች ዘመን አንድ አማኝ ሰው ይያዝና ጉድጓድ ተቆፍሮለት ከጉድጓድ እንዲገባ ይደረጋል ከዚያም መጋዝ ይመጣና ከራሱ ላይ ተደርጎ ለሁለት ይሰነጠቃል ሥጋው ከአጥንቱ በብረት ሚዶዎች ይላጋል ይህ ሁሉ ግን ከኃይማኖቱ አይመልሰውም ነበርማለታቸውን አቡ አብደላህ ኸባብ ኢብን አረት ረዐ አስተላልፈዋል ቡኻሪ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ የአብዱላህ ኢብን ኡመርን ረዐ ትከሻ ያዝ አድርገው እንዲህ ብለውት ነበር በዚህች ዓለም ላይ ስትኖር እንደ እንግዳ ወይም መንገድ አቋራጭ ሁን ከዚያም በኋላ ኢብን ኡመር ረዐ ራሳቸው እንዲህ ይሉ ነበር ካመሸህ ንጋትን አትጠብቅ በንጋት ደግሞ እስከምሽቱ አኖራለሁ ብለህ አትጠብቅ ከጤናህ ለሕመምህ ከሕይወትህ ደግሞ ለሞትህ ተዘጋድይ ቡኻሪ እነዚህ ከላይ በተከታታይ የተጠቀሱ ድንቅ አባባሎች የዚህችን ዓለም ሕይወት አጭር መሆን እንድናስታውስና ለእውነተኛው ዛገር ለአኺራ እንድንዘጋጅ ያደርጉናል የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ በአንድ ወቅት በሶላታቸው ላይ እንዲህ ሲሉ ተደምጠዋል አላህ ሆይ ኑሮ ማለት የመጪው ዓለም አኺራ ኑሮ ነው ቡኻሪ የመልእክተኛው ሰዐወ ባልደረባዎች ይህንን እውነታ በሚገባ በመገንዘባቸው ታላቅ የሚባሉና ሕያው ሆነው የሚኖሩ ተምሳሌቶችን ትተው ለማለፍ በቅተዋል ለምሳሌ ሁበይብ ረዐ ሲገደል ወደ ተንዓም ሜዳ ከተወሰደ በኋላ በመገደያው ቦታ ላይ ሆኖ ለአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ሰላምታ ለማድረስ በጣም ፈለገ ሆኖም በዙሪያው ከተሰበሰቡት ከሃዲያን ውስጥ ይህን አደራ ተቀብሎ ሊያደርስለት የሚችል አንድም ሰው አልነበረም ምርጫ ያልነበረው ሁበይብ ረዐ አይኖቹን ወደ ሰማይ ካቀና በላ እንዲህ አለ አላህ ሆይ። አያሸ እያበቃለት ነበር ውሃውን ተመለከተው ሆኖም ግን ለመጠጣት ጊዜ አልነበረውም የመጨረሻ ንግግሩ ሸዛዳ ማለት ነበር ከዚያም ፈጥጌ ወደ ኢክሪማ ስፄድ እርሱም ሰማአት ሆኖ አገኘሁት በዚህ ጊዜ አሁን ግን ለአጎቴ ልጅ ልደርስለት ይገባል ብዬ በፍጥነት ወደ ሣሪስ ስፄድ ያሳዝናል አርሱም የጓደኞቹን እጣ ተጋርቷል በሚያሳዝን ሁኔታ የውፃ ኮሮጆዬ እንደሞላ ቢሆንም እነዚያ ሶስት ሰማዕታት ሸሂዶች ሳይቀምሱለት ነበር ነፍሶቻቸው ከሥጋቸው የተለዩት ሁዘይፋ ረዐ በዚያ ቦታ ላይ ያን ክስተት ካስተዋለ በኋላ ምን እንደተሰማው ሲናገር እንዲህ ይላል ብሕይወቴ ሁሉ ብዙ አጋጣሚዎችን ተመልክቻለሁ ነገር ግን አንደዚህ ክስተት መንፈሴን የናጠኝ አጋጣሚ አልተፈጠረም በእነዚያ ሶስት ሰዎች መካከል ምንም ዓይነት የዝምድና ትስስር ባይኖርም አንዱ ለሌላው ያሳየውን አሳቢነት ፍቅርና መስዋእትነት ሳስተውል አእንዳደንቃቸው አድርጎኛል ትዝታቸውም እስክሞት ድረስ በሕሊናዬ አብሮኝ ይኖራል ምዕራፍ ሁለት አላህን ማስታወስ በዚህች ዓለም ላይ ቀናውን ጎዳና እንደተመራ ሷሊህ ሰው መኖር ካለብን ለመጪው ዓለም ስኬት ያበቃን ዘንድ በመልካም ሁኔታ ስንቃችንን ልንቋጥር ግድ ነው በቀጣዩ ሐዲስ እንደተጠቀሰውም ሰው የዘራውን እንጂ ሌላን ነገር አያጭድም ነቢዩ ሰዐወ እንዲህ ብለዋል እንደ አኗኗራችሁ ትሞታላችሁ አንደ አሟሟታችሁ ትቀሰቀሳላችሁ ዋናውና የመጨረሻው ግባችን መሆን ያለበት የመጨረሻውን ትንፋሻችንን ስናወጣ አላህ ዘንድ የሚኖረን አቀባበል ያማረ መሆኑን ማረጋገጥ ነው ይህን ሁኔታ በአንክሮ ካስተነተንነው መለኮታዊው ምስጢር ብዙ ነገሮችን ያካተተ ሆኖ እናገኘዋለን አንድ አማኝ ሕይወቱን በሙሉ መልካም ነገሮችን ሲፈጽም ቢኖርም ውድ የሆነችውን ጀነት በእርግጠኝነት ለማግኘት ሙሉ ዋስትና የለውም በሌላ በኩል አንድ ሰው በኃጢአት ተዘፍቆ ቢኖር እንኳ የአላህን ምህረት ሊያገኝና በመጨረሻ ለስኬት ሊበቃ ይችላል ይህን ጉዳይ አስመልክቶ ነቢዩ ሰዐወ የሚከተለውን ሐዲስ ተናግረዋል ከእርሱ በቀር ሌላ ጌታ በሌለው በአላህ ስም እምላለሁ ከእናንተ አንዳችሁ የገነት ሰዎችን ሥራ የሚሰራ የሚመስል በእርሱና በእርሷ በጀነት መካከል የክንድ ያህል ርቀት እስኪቀር ድረስ ነገር ግን የተጻፈው ይቀድመውና የጀፃነም ሰዎች የሚሰሩትን ሰርቶ ጀዛነም ይገባል እንዲሁም ከመካከላችሁ የእሳት ሰዎች የሚሰሩትን የሚፈጽም የሚመስል አለ ግና የተጻፈው ይቀድመውና የጀነት ሰዎች የሚሰሩትን ሥራ በመሥራት ጀነት ይገባል ቡኻሪና ሙስሊም ከአላህ ፍጡራን ውስጥ አውቀትን የታደሉ ሆኖም ግን በዚያ በተሰጡት እውቀት መንፈሳቸውን አስጊጠው የአላህን ሞገስ ከማግኘት ይልቅ ስሜታቸውን በመከተላቸው ምክንያት የከሰሩ ይገኛሉ ከእነዚህ የክስረቱ ባለቤቶች መካከል ሰይጣን ቃሩን ባዕላም ቢን በውራ አንዲሁም የነቢዩ ሰዐወ የቅርብ ባልደረባ የነበረው ሳዕፅለባ ይገኙበታል እነዚህ ሁሉ በቅርቢቱ ዓለም ሕይወት የተታለሉና ከአላህ እዝነት የተባረሩ መሆናቸው ይታወቃል ሁላችንም እንደምናውቀው ሰይጣን በአንድ ወቅት በአላህ ዘንድ የከበረና ቀራቢ ባለሟልም ነበር ሆኖም ግን በውስጡ ባሳደረው ኩራት የተነሣ የአላህን ታላቅነትና የሻውን እንደሚሰራ ማየትና መመዘን አልቻለም አናም ከአቅሙ በላይ አላህን በመገዳደር የሰው ልጆች ሁሉ አባት ከሆኑት ከአደም እንደሚበልጥ ተናገረ በዚሁ ትእቢቱም እየገፋበት መጥቶ የአላህን ትፅዛዝ ወደ መጣሱ ተሸጋገረ በመጨረሻም ከአላህ አዝነት በመባረርና እአስከፍርዱም ቀን ድረስ የእርሱን እርግማን በላዩ በመሸከም ሲባዝን ይኖራል የፍርዱ ቀን ሲመጣም ወደ ዘላለማዊው ጀፃነም ከነዘርማንዘሮቹ ይገባል ቃሩን በአንድ ወቅት ድዛፃ የነበረ ሲሆን አላህን የሚገዛ ሷሊህ ሰው ነበር እንዲሁም የተውራት ዕውቀት ካላቸው ካህናትም ታላቁ ነበር ከዚህም በላይ ሙሣ ዐሰ ባደረጉለት ጸሎት ምክንያት ፃብት የሚያስገኝ የኬሚስትሪ አልኬሚ ምስጢርን ያውቅ ነበር ይሁን እንጂ ኋላ ኋላ ይህንን አውቀቱን ለከንቱና ተራ ፍላጉቱ ማዋል ጀመረ የቃሩን ፃዛብት እጅግ ብዙ ከመሆኑ የተነሣ የካዝናዎቹን ቁልፎች ለመሸከም ብቻ ብዙ ሰዎች ያስፈልጉ ነበር በዚህ ዓይነት ታላቅ ኩራትና ማንአለብኝነት የተወጠረው ቃሩን በአንድ ወቅት ነቢዩ ሙሣ ዐሰ ከገንዘቡ ዘካ አውጥቶ እንዲያካፍል ሲጠይቁት በገንዘቤ የምታዘው አንተ ነህ እንዴ። ስለ አጠመምከኝም ለእነርሱ በቀጥተኛው መንገድ ላይ በአርግጥ አቀመጥባቸዋለሁ አለ ከዚያም ከስተፊቶቻቸው ከኋላቸውምከቀኞቻቸውም ከግራዎቻቸውም በእርግጥ አመጣባቸዋለሁ አብዛኖቻቸውንም አመስጋኞች ሆነው አታገኛቸውም አለ አልአፅራፍ ሰይጣን ይህን ካለ በኋላ አላህን አንድ ውለታ እንዲያደርግለት ጠየቀ እርሱም የፍርዱ ቀን አስኪመጣና የሰው ልጆች ከየመቃብሮቻቸው ወጥተው ለፍርድ ከዓለማቱ ጌታ ፊት እስኪቆሙ ድረስ አላህ እንዲያቆየው ነው አላህም ይህን ጥያቄውን ተቀበለው ከዚያም ሰይጣን እውነተኛ አማኞች ካልሆኑ በስተቀር ከእርሱ ወጥመድ ማንም እንደማያመልጥ እንዲህ በማለት ማፃላውን እየደረደረ ተናገረ ደፈ ጨሬ ሠሯመሾጩሪወ ን ለዮሊፃ እርሱም አለ በአሸናፊነትህ ይሁንብኝ በመላ አሳስታቸዋለሁ ከእነርሱ ምርጥ የሆኑት ባሮችህ ብቻ ሲቀሩ ሷድ ስለዚህም ከሰው ልጅ ውስጥ ነቢይ ካልሆነ በስተቀር ከዚህ አደገኛ ዛቻ የሚያመልጥ የለም ማለት ነው ለዚህም ነው ሁሉም አማኞች አላህ የሰጣቸውን ፀጋ በማመስገን ትዕዛዙን በመፈጸምና ክልከላዎቹንም በመከልከል ቀጥ ማለት ያለባቸው ከሞት አስፈሪ ትዕይንትና በዚያ ጊዜ ከሚመጣው አደጋ መዳኛው ብቸኛ መንገድ ሕይወትን አላህን በመፍራት ማሳለፍ ነው ሞት የማይቀር የሰው ልጅ አዳ መሆኑን አውቀው ሲሰናዱ ለኖሩ ሰዎች አስፈሪ ሳይሆን ከጌታቸው ጋር የሚገናኙበትን ጊዜ የሚያቀርብላቸው በመሆኑ ወደው ይቀበሉታል የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ይህን ዓለም ተሰናብተው ወደ መጪው ዓለም በሞት የተሸጋገሩበት የመጨረሻ ሰዓት በጣም አስደናቂ ናት አርሳቸው በእርግጥም ሕይወታቸውን ሁሉ የአላህን ትዕዛዝ በመጠበቅና እርሱን ከልባቸው በማምለክ ያሳለፉ በመሆኑ የመጨረሻዎቹ ሰዓታቶቻቸው የሙሽርነት ምሽት የሚመስሉና ያማሩ ነበሩ። ዓኢሻና ዓሊ ረዐ እንዳስተላለፉት የአላህ ነቢይ በዚህች ዓለም ላይ ለመጨረሻ ጊዜ ባሳለፏቸው ሶስት ቀናት አላህ መልአኩ ጂብሪልን እየላከ ስለጤንነታቸው እንዲጠይቃቸው ያደርግ ነበር በመጨረሻው ቀን ግን ጅብሪል የሞት መልአክ የሆነውን አዝራኢልን አስከትሎ ነበር የመጣው ከዚያም እንዲህ አለ የአላህ ነቢይ ሆይ። ካልፈለግክ ደግሞ ትቸልህ አሄፄዳለሁ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ በዚህ ጊዜ እንዲህ በማለት ጠየቁት የሞት መልአክ ሆይ። የሞት መልአክ ሆይ። መቹችመሠ ያ የትኛችሁ ሥራው ይበልጥ ያማረ መሆኑን ሊሞክራችሁ ሞትንና ሕይወትን የፈጠረ ነው እርሱም አሸናፊው መሐሪው ነው አል ሙልክ ኢማም አልገዛሊ እንዲህ ይላሉ በዚህ ዓለም ላይ እውቀትን ኢልምን በመማር የሚገኘውን ደስታ ያላጣጣመ ሰው የመጪውን ዓለም ያማረ ሕይወት ማስተንተን አይችልም አንድ ሰው በዚህች ዓለም ላይ ሰርቶ ያላሳለፋትን መልካም ነገር በመጪው ዓለም አያገኛትም ማንም ቢሆን በዚህች ዓለም የተከለውን ፍሬ ነው በመጪው ዓለም የበሰለ ሆኖ የሚያገኘው ሁሉም ሰው እንደ አኗኗሩ ይሞታል እንደ አሟሟቱም ይቀሰቀሳል በመጪው ዓለም ደስታ የምናገኘው አላህን በመፍራት በሰራነው መልካም ሥራ ልክ ነው ስለሆነም በእያንዳንዷ እስትንፋሳችን ራሳችንን አንድም ለታላቅ ቅጣት ወይም ማለቂያ ለሌለው ደስታና ሽልማት እያዘጋጀን ነው ኃያሉ አላህ እንዲህ በማለት ይገስፀናል ሠ ብ። ሯሠ ዴ ጪጤን ለሰጋጆች ወዮላቸው ለእነዚያ እነርሱ ከስግደታቸው ዘንጊዎች ለሆኑት ሰጋጆት አልማዑን አንድ ሰው ከአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ዘንድ በመምጣት የአላህ መልእክተኛ ሆይ።